#ዐልቦ
:
:
#በሕይወት_እምሻው
:
#ክፍል_ሦስት (የመጨረሻ ክፍል)
:
:
....''ልጄን ስጪኝ...! እንዲህ ሆነሽ ማልቀስ አያቆምም'' አለና ባርኮንን ተቀበለኝ፣ ሳላንገራግር አቀበልኩት። ቤሪ ልጃችንን በለመድነው ወጉ፣ በእሹሩሩ ዜና ለማስተኛት ሲያባብል፣ በለመደው ወጉ ጥሩ አባት ሲሆን እያየሁ እራሴን እንዲህ አልኩት።
'' እውነት ግን ምን ሆኜ ነው?''
===========================
በሱ ቀሚስ ብታስነጥሺ የጡቶችሽ ጫፍ ሳይታዩ አይቀሩም አለኝ ቤሪ፣ ከእስኩ ጋር ላለኝ የማታ ቀጠሮ ስበጃጅ።
ትላናንት ማታ ከተፈጠረው ነገር በኋላ ፣ ለቀልድ የሚሆን ፍቅር ስለቀረው አንጀቴን በላው። ፊቴን ባልለመደው አኳኋኑ ስቀባና ሳጠፋ፣ ሥሰራና ሳፈርስ፣ አዲስ ሰው ስሆን ፤ እያየኝ ለመሳቅ መሞከሩን ሳይ አንጀቴ ተንሰፈሰፈ። ዞር ብዬ አየሁት።
ባርኮንን እያጫወተ ሳይሰርቅ ያየኛል።
''በጣም ጠበበ እንዴ....''? ሊያይወም እሷ ድሮ ገዝታው ሳትለብስ የቀረችውንእኮ ነው የሰጠችኝ
.. አሁንማ ተቀዶም ሌላ ቀሚስ ገብቶበትምአይሆናት'' አልኩት፣ እኔም ሳቅ ለመፍጠር እየሞከርኩ።
''ቢጠብም ያምርቦሻል...የኔ ሚስት እንኳን ሦስት የወለድሽ በልተሽ የምታድሪ አትመስይም እኮ....! አለኝ፣ ልጁን እንደያዘ እየተጠጋኝ።
ማታ እንድያ ጥንብ እርኩሱን አውጥቼው ጠዋት ቅዱስ የሚሆን ይሄ ሰው ከምንድን ነው የተሰራው ..? ለምንስ ነው ለኔ የተሰጠኝ..? ጸጸት ሹክ አለኝ።
''ቂጣምዬ....'' አለኝ ፣ ባርኮንን ባልያዘው እጁ ቂጤን ቸብ እያደረገኝ።
''አንተ እረፋ...''
''ምን አገባሽ በኔ ቂጥ....''
''ሂድ ወደዛ...የኔ ነው...''
በሚጢጢ ቤታችን ውስጥ እንኳን መሮጥ ፈጠን ብዬ ብራመድ ከግድግዳ እጋጫለሁ እንጂ፣ ሮጬ የህንድ ፊልም ነገር ብንሰራ ደስ ይለኝ ነበር። ይሄንን ጊዜ ልሰጠው ፣ ይሄንን ጨዋታ ልሸልመው ብችል፣ ደስ ይለኝ ነበር።
''እረፍ እየጠበቀችኝ ነው አሁን ቶሎ ልሂድ..'' ስለው ፣ ወደ አሮጌው ፎቴ ተመለስና ዝርፍጥ አለ።
''ቤሪ...?'' አልኩት ሊፒስቲኬን መልሼ እያስተካከልኩ። ከንፈሬ ወሰኑ አይታወቅም። አገጬን እየተቀባሁ ተቸገርኩ።
''ወይ ፍቅር..''
''እንዲህ ብዘንጥ ደስ አይልክም ሁሌ...? ማለቴ እንዲህ ቁልትልት ብል..ዝንጥንጥ...?''
''አንችን ደስ ይልሻል ፍቅር...? ያ ሰባራ ድምፁ ተመልሶ መጣ። ''መዘነጥ ማን ይጠላል...? ዞር ብዬ ወገቤን ያዝኩና መለስኩለት።
''ለኔ ጆንያም ብትለብሺ ውብ ነሽ..ደስ ካለሽ ግን ዘንጪ...''
ቮድካ በዚህ መጠን ጠጥቼ አላውቅም። ነገሮች ሁሉ ይበወዝብኝ ጀመር። አስኩ አራት ከንፈር፣ ስድስት ጆሮና አራት ዐይን ያላት ይመስለኝ ጀመር።
የጎደለ ብርጭቆዬን ልትሞለው ስትል በደመነፍስ፣ አንቺ በቤሪ ሞት...በቃኝ...'' አልኩኝ፣ የብርጭቆዬን አፍ በእጄ ለመክደን እየሞከርኩ።እኔ ይህን እያልኩ፣ ክዳን ያደረኩትን እጄ ላይ ቮድካውን ስትቀዳ፣ ነገር አለሙን ትተን እንደ ቂል መሳቅ ጀመርን።
''አንቺ እረፊ....ሰካራም!'' እላታለሁ፣ ትስቃለች።
''ወይኔ ቤሪ ይሙት...ቤሪ ይሙት...በቃኝ አልኩሽ እኮ!'' አልኩኝ እየሳቅኩ።
እጄ ላይ መቅዳቷን ሳታቆም አሁንም ትስቃለች። የሞት ሞቴን ጠርሙሱን ተቀበልኳትና ሶፋው ላይ በጀርባዬ ተጋለልኩ። ስገባ በብርሀን ተሞልቶ የነበረው ክፍል ጨላለመብኝ። አይኖቼን አሸሁ። አሁንም እንደጨላለመብኝ ነው።
''ውሃ...ውሃ ስጪኝ አስክዬ...'' አልኳት በተንጋለልኩበት።
''ምን ሆንሽ....?'' አለች፣ ውፍረቷ እና ጫማ የጨመረው ቁመቷ ተኝተው ሲያዩት ያስፈራል። ቀና ለማለት ሞከርኩ።
''ተቃጠልኩ አስኩ...ቅጥል አደረገኝ...''
''ጎሽ...የሚያቃጥልሽን አቃጠለው ማለት ነው አሁን...ሠርቷል ማለት ነው...!'' አለችና መውደቅን እንደ ፈራ ሰው እየተጠነቀቀች አጠገቤ ቁጭ አለች።
''አረ እኔ በዚህ ሁሉ የሚቃጠል ነገር የለኝም!'' አልኳት፣ አልታዘዝ ያለኝ አንገቴን አዙሬ ላያት እየሞከርኩ።
''እስኪ ማይልኝ...!'' አለችኝ እግሯን ወደ እጆቼ እየላከች፣ ክትክት ብለን ሳቅን።
''ቤሪ ይሙት..!'' አልኳሏት አየሩን በእጄ በመሀላ እየመታው።
''ወይ ይሄ ቤሪ ይሙት..ከእነረ እኮ በባሌ ብምል.'' አለችኝ እየሳቀች፤
''እ...'' አልኳት
''ይሙት ካሉክ ምኞት ነው እንጂ መሀላ አይሆንም''
''ሃ ሃ አስኩ ቀልደኛ ነሽ....''
''ቀልዴን አይደለም..." ክልትው ይበል!''
ሣቋ በዚህ ፍጥነት የት ገባ?
''አንቺ በቮድካ የሚቃጠል የለኝም አልሽ አይደል እኔ ግን አለኝ...ውቅያኖስ የሚያክል ቮድካ አቃጥሎ የማይጨርሰው ነገር ውስጤ አለ ፍቅር...ተቃጠልኩልሽ....''
በድንገት እንደሚያቅፍም እንደሚደግፍም ሰው፣ በተቀመጥኩበት አፍናኝ ታለቅስ ጀመር። ወዝገብ አለብኝ።
''እንዴ...! ምን ሆንሽ ድንገት...?'' አልኳት፣ ሶፋው ላይ ተመቻችቼ ላመቻቻት እየሞከርኩ።ቆዳ ነኝ የሚለው ጥቁር ፕላስቲክ ልብሱ፣ መልሶ መላልሶ ያንሸራትታል።
''ኑሮ አቃጠለኝ...ተቃ...ጠልኩ አልኩሽ በቃ...ጓደኛዬ ሕይወቴ አቃጠለኝ....''
ለቅሶዋ ባሰ፣ ሁሉ ነገር ድንገት ሆነብኝ። እንባዋ ቮድካዬን የመጠጠው ይመስል ስካሬ ሲበን ተሰማኝ። ቀና አልኩ።
''ምን ሆንሽ..?'' ምን ጎደለብሽ....? ሰክረሽ ነው.. የምትቀባጥሪው...? '' ምን አለኝ...? ምንም የለኝም እኮ ጓደኛዬ...ባዶ...ባዶ ነኝ እኮ እኔ... ኔፓ ...ዜ...ሮ...ዜ....ሮ....!''
ለሀጯ እየትዘረበረበ፤ ንፍጧ እየትዘረከረከ፤ እምባዋ እየወረደ፤ ሳያት፣ ቮድካው ሳይሆን እሷ እያወራች መሆኑ ገባኝ።
''ምን የለሽም....? ቤት መኪና... ልጅ.... ባልሽ.. እኔ ምን አለኝ...? ሩዬን እያየሽው ባንቺ ኑሮ ትማረርያለሽ ? ቤቴን አይተሽው ምንም የለኝም ትያለሽ..እኔኮ መንግስጥ የሰጠኝ ኮንደሚኒየም ቤት አድሼ መግባት አቅቶኝ፣ እዛ ጉሮኖ ውስጥ የምኖር ሰው ነኝ...እንቺ ምን የለሽም?'' አልኳት እያቀፍኳትእያቀፍኳት፤ እንደ ህፃን ልጅ እያናፈጥኳት፣ እንደ ባርኮን እያባበልኳት።
'' ባሌ...ቴዲ...ባሌ እኮ ጥሎኝ ከሄደ ዓመት ሞላው ፍቅር....ጥሎኝ ሄደ.....ትቶኝ ሄደ.....''
ደነገጥኩ።
''እንዴ....መቼ....?''
''አመት አልኩሽ አይደል....?''
''አይደለም...እንዴት ማለቴ ነው...? መቼ ሳይሆን እንዴት....? ደንበርበር አልኩች።
እስካሁን ያልነበረኝ እንግዳ መረጃ ነው። ያን ሁሉ የምቾት ክምሯን በፎቶ ላይ፣ በቪዲዬ ስመለከት ፣ ''ባልሽ የታለ?'' ብዬም አልጠየቅኩ፣ እሷም አልነገረችኝ።
''ይሄውልሽ ....'' አለች፣ እየተንፏቀቀች ከተጋደመጅበት የሆቴሏ ሶፋ እየተነሳች ፣ ''ይሄውልሽ...ጢቢጢቢ ሲጫወትብኝ ኖሮ... ጥሎኝ ሄደ...''
''እ...ማለት....ምን ብሎ?''
''ከአንዷ ደጋን እግር ጋር ፍቅር ያዘኝ ብሎ'' ዝም አልኩ።
ለእንዲህ ያለው ነገር ምን ተብሎ ይመስላል? ጓደኛዬ፣ ''ባሌ ጢቢጢቢ ተጫወተብኝ፣ ሌላ ሴት ወዶ ጥሎኝ ሄደ....ተቃጠልኩ!'' ብላ ስትል ፣ ምን ማለት ነው ያለብኝ?
''አይዞሽ አስኩዬ....''
ለማለት የቻልኩት ይህችን ብቻ ነበር።
''አይዞሽ አሰኩዬ...'' ደገምኩት
''አውሬ ነበር፣ የሰው አውሬ።እኔ ጫካ ሆኜለት ችዬው ኖርኩ እንጂ፣ አውሬ ነበር...እላዬ ላይ ሴት ይዞ ይመጣል፣ ልጁን ይክዳል ፣ ሌላውን ተይው ፍቅር....እርጉዝ ሆኜ...እርጉዝ ሆኜ እንኳን ፍቅር..'' ለቅሶ አሸነፋትና መናገር አቆመች።
የምላት ነገር አጣሁ።
:
:
#በሕይወት_እምሻው
:
#ክፍል_ሦስት (የመጨረሻ ክፍል)
:
:
....''ልጄን ስጪኝ...! እንዲህ ሆነሽ ማልቀስ አያቆምም'' አለና ባርኮንን ተቀበለኝ፣ ሳላንገራግር አቀበልኩት። ቤሪ ልጃችንን በለመድነው ወጉ፣ በእሹሩሩ ዜና ለማስተኛት ሲያባብል፣ በለመደው ወጉ ጥሩ አባት ሲሆን እያየሁ እራሴን እንዲህ አልኩት።
'' እውነት ግን ምን ሆኜ ነው?''
===========================
በሱ ቀሚስ ብታስነጥሺ የጡቶችሽ ጫፍ ሳይታዩ አይቀሩም አለኝ ቤሪ፣ ከእስኩ ጋር ላለኝ የማታ ቀጠሮ ስበጃጅ።
ትላናንት ማታ ከተፈጠረው ነገር በኋላ ፣ ለቀልድ የሚሆን ፍቅር ስለቀረው አንጀቴን በላው። ፊቴን ባልለመደው አኳኋኑ ስቀባና ሳጠፋ፣ ሥሰራና ሳፈርስ፣ አዲስ ሰው ስሆን ፤ እያየኝ ለመሳቅ መሞከሩን ሳይ አንጀቴ ተንሰፈሰፈ። ዞር ብዬ አየሁት።
ባርኮንን እያጫወተ ሳይሰርቅ ያየኛል።
''በጣም ጠበበ እንዴ....''? ሊያይወም እሷ ድሮ ገዝታው ሳትለብስ የቀረችውንእኮ ነው የሰጠችኝ
.. አሁንማ ተቀዶም ሌላ ቀሚስ ገብቶበትምአይሆናት'' አልኩት፣ እኔም ሳቅ ለመፍጠር እየሞከርኩ።
''ቢጠብም ያምርቦሻል...የኔ ሚስት እንኳን ሦስት የወለድሽ በልተሽ የምታድሪ አትመስይም እኮ....! አለኝ፣ ልጁን እንደያዘ እየተጠጋኝ።
ማታ እንድያ ጥንብ እርኩሱን አውጥቼው ጠዋት ቅዱስ የሚሆን ይሄ ሰው ከምንድን ነው የተሰራው ..? ለምንስ ነው ለኔ የተሰጠኝ..? ጸጸት ሹክ አለኝ።
''ቂጣምዬ....'' አለኝ ፣ ባርኮንን ባልያዘው እጁ ቂጤን ቸብ እያደረገኝ።
''አንተ እረፋ...''
''ምን አገባሽ በኔ ቂጥ....''
''ሂድ ወደዛ...የኔ ነው...''
በሚጢጢ ቤታችን ውስጥ እንኳን መሮጥ ፈጠን ብዬ ብራመድ ከግድግዳ እጋጫለሁ እንጂ፣ ሮጬ የህንድ ፊልም ነገር ብንሰራ ደስ ይለኝ ነበር። ይሄንን ጊዜ ልሰጠው ፣ ይሄንን ጨዋታ ልሸልመው ብችል፣ ደስ ይለኝ ነበር።
''እረፍ እየጠበቀችኝ ነው አሁን ቶሎ ልሂድ..'' ስለው ፣ ወደ አሮጌው ፎቴ ተመለስና ዝርፍጥ አለ።
''ቤሪ...?'' አልኩት ሊፒስቲኬን መልሼ እያስተካከልኩ። ከንፈሬ ወሰኑ አይታወቅም። አገጬን እየተቀባሁ ተቸገርኩ።
''ወይ ፍቅር..''
''እንዲህ ብዘንጥ ደስ አይልክም ሁሌ...? ማለቴ እንዲህ ቁልትልት ብል..ዝንጥንጥ...?''
''አንችን ደስ ይልሻል ፍቅር...? ያ ሰባራ ድምፁ ተመልሶ መጣ። ''መዘነጥ ማን ይጠላል...? ዞር ብዬ ወገቤን ያዝኩና መለስኩለት።
''ለኔ ጆንያም ብትለብሺ ውብ ነሽ..ደስ ካለሽ ግን ዘንጪ...''
ቮድካ በዚህ መጠን ጠጥቼ አላውቅም። ነገሮች ሁሉ ይበወዝብኝ ጀመር። አስኩ አራት ከንፈር፣ ስድስት ጆሮና አራት ዐይን ያላት ይመስለኝ ጀመር።
የጎደለ ብርጭቆዬን ልትሞለው ስትል በደመነፍስ፣ አንቺ በቤሪ ሞት...በቃኝ...'' አልኩኝ፣ የብርጭቆዬን አፍ በእጄ ለመክደን እየሞከርኩ።እኔ ይህን እያልኩ፣ ክዳን ያደረኩትን እጄ ላይ ቮድካውን ስትቀዳ፣ ነገር አለሙን ትተን እንደ ቂል መሳቅ ጀመርን።
''አንቺ እረፊ....ሰካራም!'' እላታለሁ፣ ትስቃለች።
''ወይኔ ቤሪ ይሙት...ቤሪ ይሙት...በቃኝ አልኩሽ እኮ!'' አልኩኝ እየሳቅኩ።
እጄ ላይ መቅዳቷን ሳታቆም አሁንም ትስቃለች። የሞት ሞቴን ጠርሙሱን ተቀበልኳትና ሶፋው ላይ በጀርባዬ ተጋለልኩ። ስገባ በብርሀን ተሞልቶ የነበረው ክፍል ጨላለመብኝ። አይኖቼን አሸሁ። አሁንም እንደጨላለመብኝ ነው።
''ውሃ...ውሃ ስጪኝ አስክዬ...'' አልኳት በተንጋለልኩበት።
''ምን ሆንሽ....?'' አለች፣ ውፍረቷ እና ጫማ የጨመረው ቁመቷ ተኝተው ሲያዩት ያስፈራል። ቀና ለማለት ሞከርኩ።
''ተቃጠልኩ አስኩ...ቅጥል አደረገኝ...''
''ጎሽ...የሚያቃጥልሽን አቃጠለው ማለት ነው አሁን...ሠርቷል ማለት ነው...!'' አለችና መውደቅን እንደ ፈራ ሰው እየተጠነቀቀች አጠገቤ ቁጭ አለች።
''አረ እኔ በዚህ ሁሉ የሚቃጠል ነገር የለኝም!'' አልኳት፣ አልታዘዝ ያለኝ አንገቴን አዙሬ ላያት እየሞከርኩ።
''እስኪ ማይልኝ...!'' አለችኝ እግሯን ወደ እጆቼ እየላከች፣ ክትክት ብለን ሳቅን።
''ቤሪ ይሙት..!'' አልኳሏት አየሩን በእጄ በመሀላ እየመታው።
''ወይ ይሄ ቤሪ ይሙት..ከእነረ እኮ በባሌ ብምል.'' አለችኝ እየሳቀች፤
''እ...'' አልኳት
''ይሙት ካሉክ ምኞት ነው እንጂ መሀላ አይሆንም''
''ሃ ሃ አስኩ ቀልደኛ ነሽ....''
''ቀልዴን አይደለም..." ክልትው ይበል!''
ሣቋ በዚህ ፍጥነት የት ገባ?
''አንቺ በቮድካ የሚቃጠል የለኝም አልሽ አይደል እኔ ግን አለኝ...ውቅያኖስ የሚያክል ቮድካ አቃጥሎ የማይጨርሰው ነገር ውስጤ አለ ፍቅር...ተቃጠልኩልሽ....''
በድንገት እንደሚያቅፍም እንደሚደግፍም ሰው፣ በተቀመጥኩበት አፍናኝ ታለቅስ ጀመር። ወዝገብ አለብኝ።
''እንዴ...! ምን ሆንሽ ድንገት...?'' አልኳት፣ ሶፋው ላይ ተመቻችቼ ላመቻቻት እየሞከርኩ።ቆዳ ነኝ የሚለው ጥቁር ፕላስቲክ ልብሱ፣ መልሶ መላልሶ ያንሸራትታል።
''ኑሮ አቃጠለኝ...ተቃ...ጠልኩ አልኩሽ በቃ...ጓደኛዬ ሕይወቴ አቃጠለኝ....''
ለቅሶዋ ባሰ፣ ሁሉ ነገር ድንገት ሆነብኝ። እንባዋ ቮድካዬን የመጠጠው ይመስል ስካሬ ሲበን ተሰማኝ። ቀና አልኩ።
''ምን ሆንሽ..?'' ምን ጎደለብሽ....? ሰክረሽ ነው.. የምትቀባጥሪው...? '' ምን አለኝ...? ምንም የለኝም እኮ ጓደኛዬ...ባዶ...ባዶ ነኝ እኮ እኔ... ኔፓ ...ዜ...ሮ...ዜ....ሮ....!''
ለሀጯ እየትዘረበረበ፤ ንፍጧ እየትዘረከረከ፤ እምባዋ እየወረደ፤ ሳያት፣ ቮድካው ሳይሆን እሷ እያወራች መሆኑ ገባኝ።
''ምን የለሽም....? ቤት መኪና... ልጅ.... ባልሽ.. እኔ ምን አለኝ...? ሩዬን እያየሽው ባንቺ ኑሮ ትማረርያለሽ ? ቤቴን አይተሽው ምንም የለኝም ትያለሽ..እኔኮ መንግስጥ የሰጠኝ ኮንደሚኒየም ቤት አድሼ መግባት አቅቶኝ፣ እዛ ጉሮኖ ውስጥ የምኖር ሰው ነኝ...እንቺ ምን የለሽም?'' አልኳት እያቀፍኳትእያቀፍኳት፤ እንደ ህፃን ልጅ እያናፈጥኳት፣ እንደ ባርኮን እያባበልኳት።
'' ባሌ...ቴዲ...ባሌ እኮ ጥሎኝ ከሄደ ዓመት ሞላው ፍቅር....ጥሎኝ ሄደ.....ትቶኝ ሄደ.....''
ደነገጥኩ።
''እንዴ....መቼ....?''
''አመት አልኩሽ አይደል....?''
''አይደለም...እንዴት ማለቴ ነው...? መቼ ሳይሆን እንዴት....? ደንበርበር አልኩች።
እስካሁን ያልነበረኝ እንግዳ መረጃ ነው። ያን ሁሉ የምቾት ክምሯን በፎቶ ላይ፣ በቪዲዬ ስመለከት ፣ ''ባልሽ የታለ?'' ብዬም አልጠየቅኩ፣ እሷም አልነገረችኝ።
''ይሄውልሽ ....'' አለች፣ እየተንፏቀቀች ከተጋደመጅበት የሆቴሏ ሶፋ እየተነሳች ፣ ''ይሄውልሽ...ጢቢጢቢ ሲጫወትብኝ ኖሮ... ጥሎኝ ሄደ...''
''እ...ማለት....ምን ብሎ?''
''ከአንዷ ደጋን እግር ጋር ፍቅር ያዘኝ ብሎ'' ዝም አልኩ።
ለእንዲህ ያለው ነገር ምን ተብሎ ይመስላል? ጓደኛዬ፣ ''ባሌ ጢቢጢቢ ተጫወተብኝ፣ ሌላ ሴት ወዶ ጥሎኝ ሄደ....ተቃጠልኩ!'' ብላ ስትል ፣ ምን ማለት ነው ያለብኝ?
''አይዞሽ አስኩዬ....''
ለማለት የቻልኩት ይህችን ብቻ ነበር።
''አይዞሽ አሰኩዬ...'' ደገምኩት
''አውሬ ነበር፣ የሰው አውሬ።እኔ ጫካ ሆኜለት ችዬው ኖርኩ እንጂ፣ አውሬ ነበር...እላዬ ላይ ሴት ይዞ ይመጣል፣ ልጁን ይክዳል ፣ ሌላውን ተይው ፍቅር....እርጉዝ ሆኜ...እርጉዝ ሆኜ እንኳን ፍቅር..'' ለቅሶ አሸነፋትና መናገር አቆመች።
የምላት ነገር አጣሁ።
👍5❤1👎1
#ለእኔ_ያላት_እንጀራ
:
#በሕይወት_እምሻው
:
:
#ክፍል_ሦስት (የመጨረሻ ክፍል)
:
:
...''ምንድን ነው ይሄ ሁሉ ?'' አለ፣ አንዴ እኔን አንዴ ትንሾ ጠረጴዛ ላይ ተፋፍገው የተቀመጡትን የምግብ የምግብ አይነቶች ፣ ከዚያ ደግሞ በትልቅ ብልጭልጭ ወረቀት የጠቀለልኩትን ስጦታዬን እያየ።
ሻማም አልቀረኝ።
''ልደትህ አይደል.... በደንብ ይከበርልህ ብዬ ነዋ ...'' አልኩት ፣ ከጥብሱ ጎርሼ ቀይ ወይኔን እየተጎነጨሁ...
''እሱማ ገባኝ ግን በጣም በዛ ሜዲዬ...ብዙ ወጪ ሳታወጪ አትቀሪም ለዚህ ሁሉ....''
''ታድያ ምናባቱ! እኔ ለዛሬ ነው የምኖረው ጌታዬ!'' አልኩ! ግራ እጁን ጎትቼ ጭምቅ አድርጌ እየያዝኩ። ሰውነቴ የኔ ነው አፌ ግን የሄዋን ከሆነ ቆየ። ዝም አለ።
''ደስ አላለክም መስፍኔ?'' እጁን እንደያዝኩ ጠየቅኩ።
''ደስ ብሎኛል....'' ቅዝዝ ብሎ መለሰ ራት ስንጨርስ ስጦታውን ሰጠሁት። ዋጋውን ጠየቀኝ።
''እንዴት የስጦታ ዋጋ ይጠየቃል ?'' ምናምን ብዬ አኮረፍኩት።
''ውድ ይመስላል....'' አለኝ።
''እና?''
''አይ ምንም....''
ልደቱን ካከበርን በኋላ ባሉት ሳምንታት፣ መስፍኔ ቀስ በቀስ እየተሸራረፈ ሌላ ሰው መሆን ጀመረ።
ስደውል አያነሳም። ሲያነሳ ሰበብ ይደረድራል። አንዴ ''ስራ በዝቶ ነው፣ስብሰባ ነበርርን፣ ስልኬ ጠፍቶ ነበር፣ ካርድ አልነበረኝም....''
ዓይነት።
ቴክስትም ስልክ አይመልስም። ለአስር ቴክስት አንድ ሲመልስም ሰበብ ይደረድራል፣ ወይ ስሜት የሌለው ነገር ይፅፋል። ለምሳሌ ''ትንሹ መስፍኔ ናፈቀኝ ዛሬ አብረን አናድርም?'' ዓይነት ነገር ፅፌለት፣ ''ኢን ኤ ሚቲንግ'' ምናምን የሚል ከስልኩ ጋር የመጣ መጠባበቅያ መልእክት ይልክልኛል። ካልመለሰልኝ ደግሞ አግኝቼው ''ምነው?'' ስለው፣ ''ካርድ የለውም ነበር። ስብሰባ አለቃዬ ፊት ተቀምጬ ስለነበር ነው'' ይለኛል።
እንደበፊቱ ቀን በቀን ቀርቶ ፣ በሳምንት አንዴ ለመገናኘት ቀጠሮ ይዘን ባለቀ ሰአት ይሰርዝብኛል ሲሰርዝ ሰበብ ይደረድራል ። እንደ ድንገት ፊልድ ሂድ ተባልኩ፣ እማዬን ትንሽ አመማት ፣ ሃይለኛ ጉንፋን ይዞኛል፣ የወይንዬ እናት አረፉ...''ዓይነት።
''ምን አጠፋሁ ?'' ስለው፣
''ውይ አረ ምንም'' ብሎ ፣ ይምላል፣ ይገዘታል። ከሰበቦቹ ተርፈው በማገኘው ቀን ግን ከወትሮው ተለይቶ ዝም ይለኛል። ፊቴ ይደበታል። አጠገቡ በመቀመጤ አየሩን የተሻማሁ እስኪመስለኝ ድረስ ዐስሬ ቁና ቁና ይተነፍሳል።
ጨነቀኝ።
ጠማማ እድሌ አድብቶና ዘግይቶ፣ቀስ ብሎ የቀደመኝ መሰለኝ። ብሮጥ የማላመልጠው የአርባ ቀን እድል አለኝ ልበል? ጸደቀ ያልኩት የሚደርቅብኝ፣ ሞቀ ያልኩት የሚበርድብኝ፣ የሣሣሁለት የሚሸሸኝ ለምንድን ነው ?
ሳምንታት በእንዲህ ሁኔታ ሲያልፉ የማደርገው ጠፋኝና ተውኩት። ሄዋን፣ ''ወንድ እንዲህ ነው። መወትወትሽን ብታቆሚ ራሱ ይፈልግሻል'' ስትለኝ ተውኩት።
ግን እኔ መደወል ሳቆም በስልክም መነጋገር አቆምን። እኔ እንገናኝ ብዬ መጠየቅ ስተው መገናኘት ተውን። ጥፋቴ ሳይገባኝ እንደዛ የወደድኩት ሰው እንደ ጠዋት ጤዛ ባንዴ ታይቶ ባንዴ ጠፋ።
ጠፋ፣ ጠፋ፣
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ከሰባት ወራት በኋላ......
ከመስፍኔ ህመም እንደምንም ማገገም በጀመርኩበት ሰሞን፣ ከቤቲና ሄዋን ጋር ቁጭ ብለን ቡና እየጠጣን ነበር። ከማይረባ ብዙ ወሬ በኋላ ቢቲ በተለመደ ችኮላዋ ፣
''ሰምተን መደበቅ ሙድ የለውም...በቃ ዕወቂው '' አለች እያየችኝ ሄዋን ክው አለችና ፣ ''በናትሽ ቤቲ ..! ራሷ ሌላ ጊዜ ትስማው በናትሽ'' አለች።
''ምንድን?'' አልኩኝ ቆጣ ብዬ...
ተያዩ።
''ምንድን ነው ለምን አትነግሩኝም?'' አልኩ እንደገና ተቆትቼ። ቤቲ ያለወትሮዋ ትንሽ አቅማማችና ፣
''ማዲዬ...፣ መስፍን አግብቶል። ማወቅ አለብሽ ብዬ ነው...''
አለች።
እሳት የተፋችብኝ ይመስል ፊቴ ተቃጠለ። በቀለም ተነፍታ በነበልባል የምትቃጠል ዶሮ የሆንኩ መሰለኝ። አጥንቶቼ ሁሉ የቀለጡና ከስጋ ብቻ የተሰራሁ መሰለኝ። ምራቄ ከአፌ ያለቀ መሰለኝ። እንደምንም ሶፋውን ደገፍ ብዬ ሁለቱንም አየኋቸው።
''ሶሪ ማዲዬ በቃ...ተይው...'' አለች ሄዋን ፣ ፀጉሬን እየደባበሰች። ''ራይድ ጥሩልኝ ቤቴ መሄድ እፈልጋለው....'' ስል ብቻ ትዝ ይለኛል።
ቤቴ ገብቼ አንዴ እያለቀስኩ፣ አንድ በንዴት ጦፌ መኝታ ቤቴ ውስጥ እየተንጎራደድኩየሆነውን ሁሉ አንድ በአንድ ሳብሰለስል ብውልም ፣ ባወጣም ባወርድም፣ የሆነው ለምን እንደሆነ ሊገባኝ አልቻለም። የእኔና የመስፍኔ መጨረሻ ይሄ መሆኑ በምንም ስሌት ባስበው ሊገባኝ አልቻለም ።
ሞባይሌን አንስቼ ሰዐቴን ዐየሁ። ሁለት ሰዐት ከሀምሳ አምስት ደቂቃ። በጣም አልመሸም።
ደወልኩት። ለመስፍኔ ደወልኩለት ። ያነሳ ይሆን ሁለቴ እንኳን ሳይጠራ አነሳው። ይባስ ብሎ፤ ልክ ስልኬን ይጠብቅ እንደነበር ሰው ፣ ሳይገረም ሰላም አለኝ።
''ሃይ....መሀደር እንዴት ነሽ?''
ማህደር? ማህደር ነው ያለኝ?
''ደህና ነኝ...እንኳን ደስ ያለክ ልልክ ነው...''
''አመሰግናለው....አንቺ ደህና ነሽ?''
''ደህና ነኝ...ማውራት ትችል ይሆን ? አንድ ነገር ልጠይቅክ ነበር?''
''እንችላለን...''
ስሜቴን ተቆጣጠርኩ። ጉሮሮዬን ጠረኩ። ቃላቶቼን መረጥኩ።
''በዚህ ፍጥነት እንዴት አገባህ...? ማለቴ...ማ..ለቴ ለምን እኔን ለማግባት...''
ሳልጨርስ አቋረጠኝ።
''ትዳር የምትፈልጊ አልመሰለኝም...ማህደር ፣ እኔ ሀያ ምናምን ዓመት ሙሉ ገርል ፍሬንድ ነበረኝ። በዚህ እድሜዬ ሚስት ነበር የምፈልገው....ሳይሽ ስለወደፊት አታስቢም ...እና...ጊዜ ማጥፋት አልፈለኩም ....እ?''
ዝም አልኩ።
''ማህደር?''
''አ..ለ..ሁ....'' አልኩ። ግን አልነበርኩም።
''እህ...ማንን ነው ያገባከው?'' አልኩ፣ የሚያውቃቸውን ሴቶች በሙሉ በአእምሮዬ ሳመላልስ መዋሌ በማያስታውቅ ሁኔታ።
''እ..ወይንሸትን...ወይንዬን ነው ....''
ባለ አርባ ስልሳዋ ወይንሸት !
ምን ብዬ እንደጨረስኩ ሳላውቅ ስልኩን ዘጋሁ ። ፊቴ እንደገና ሲነድ፣ዐጥንቴ በንዴት ሲቀልጥ ይሰማኛል። አልጋዬ ላይ ተዘረጋሁ።
ለኔ ያላትን እንጀራ እኔ ብገፋትም አልሻገተችም። ወይንሸት በልታታለች።
ሔዋን.... አንቺ ደሞ አፈር ብዬ። አፈር ያስበላሽ።
🔘አለቀ🔘
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
:
#በሕይወት_እምሻው
:
:
#ክፍል_ሦስት (የመጨረሻ ክፍል)
:
:
...''ምንድን ነው ይሄ ሁሉ ?'' አለ፣ አንዴ እኔን አንዴ ትንሾ ጠረጴዛ ላይ ተፋፍገው የተቀመጡትን የምግብ የምግብ አይነቶች ፣ ከዚያ ደግሞ በትልቅ ብልጭልጭ ወረቀት የጠቀለልኩትን ስጦታዬን እያየ።
ሻማም አልቀረኝ።
''ልደትህ አይደል.... በደንብ ይከበርልህ ብዬ ነዋ ...'' አልኩት ፣ ከጥብሱ ጎርሼ ቀይ ወይኔን እየተጎነጨሁ...
''እሱማ ገባኝ ግን በጣም በዛ ሜዲዬ...ብዙ ወጪ ሳታወጪ አትቀሪም ለዚህ ሁሉ....''
''ታድያ ምናባቱ! እኔ ለዛሬ ነው የምኖረው ጌታዬ!'' አልኩ! ግራ እጁን ጎትቼ ጭምቅ አድርጌ እየያዝኩ። ሰውነቴ የኔ ነው አፌ ግን የሄዋን ከሆነ ቆየ። ዝም አለ።
''ደስ አላለክም መስፍኔ?'' እጁን እንደያዝኩ ጠየቅኩ።
''ደስ ብሎኛል....'' ቅዝዝ ብሎ መለሰ ራት ስንጨርስ ስጦታውን ሰጠሁት። ዋጋውን ጠየቀኝ።
''እንዴት የስጦታ ዋጋ ይጠየቃል ?'' ምናምን ብዬ አኮረፍኩት።
''ውድ ይመስላል....'' አለኝ።
''እና?''
''አይ ምንም....''
ልደቱን ካከበርን በኋላ ባሉት ሳምንታት፣ መስፍኔ ቀስ በቀስ እየተሸራረፈ ሌላ ሰው መሆን ጀመረ።
ስደውል አያነሳም። ሲያነሳ ሰበብ ይደረድራል። አንዴ ''ስራ በዝቶ ነው፣ስብሰባ ነበርርን፣ ስልኬ ጠፍቶ ነበር፣ ካርድ አልነበረኝም....''
ዓይነት።
ቴክስትም ስልክ አይመልስም። ለአስር ቴክስት አንድ ሲመልስም ሰበብ ይደረድራል፣ ወይ ስሜት የሌለው ነገር ይፅፋል። ለምሳሌ ''ትንሹ መስፍኔ ናፈቀኝ ዛሬ አብረን አናድርም?'' ዓይነት ነገር ፅፌለት፣ ''ኢን ኤ ሚቲንግ'' ምናምን የሚል ከስልኩ ጋር የመጣ መጠባበቅያ መልእክት ይልክልኛል። ካልመለሰልኝ ደግሞ አግኝቼው ''ምነው?'' ስለው፣ ''ካርድ የለውም ነበር። ስብሰባ አለቃዬ ፊት ተቀምጬ ስለነበር ነው'' ይለኛል።
እንደበፊቱ ቀን በቀን ቀርቶ ፣ በሳምንት አንዴ ለመገናኘት ቀጠሮ ይዘን ባለቀ ሰአት ይሰርዝብኛል ሲሰርዝ ሰበብ ይደረድራል ። እንደ ድንገት ፊልድ ሂድ ተባልኩ፣ እማዬን ትንሽ አመማት ፣ ሃይለኛ ጉንፋን ይዞኛል፣ የወይንዬ እናት አረፉ...''ዓይነት።
''ምን አጠፋሁ ?'' ስለው፣
''ውይ አረ ምንም'' ብሎ ፣ ይምላል፣ ይገዘታል። ከሰበቦቹ ተርፈው በማገኘው ቀን ግን ከወትሮው ተለይቶ ዝም ይለኛል። ፊቴ ይደበታል። አጠገቡ በመቀመጤ አየሩን የተሻማሁ እስኪመስለኝ ድረስ ዐስሬ ቁና ቁና ይተነፍሳል።
ጨነቀኝ።
ጠማማ እድሌ አድብቶና ዘግይቶ፣ቀስ ብሎ የቀደመኝ መሰለኝ። ብሮጥ የማላመልጠው የአርባ ቀን እድል አለኝ ልበል? ጸደቀ ያልኩት የሚደርቅብኝ፣ ሞቀ ያልኩት የሚበርድብኝ፣ የሣሣሁለት የሚሸሸኝ ለምንድን ነው ?
ሳምንታት በእንዲህ ሁኔታ ሲያልፉ የማደርገው ጠፋኝና ተውኩት። ሄዋን፣ ''ወንድ እንዲህ ነው። መወትወትሽን ብታቆሚ ራሱ ይፈልግሻል'' ስትለኝ ተውኩት።
ግን እኔ መደወል ሳቆም በስልክም መነጋገር አቆምን። እኔ እንገናኝ ብዬ መጠየቅ ስተው መገናኘት ተውን። ጥፋቴ ሳይገባኝ እንደዛ የወደድኩት ሰው እንደ ጠዋት ጤዛ ባንዴ ታይቶ ባንዴ ጠፋ።
ጠፋ፣ ጠፋ፣
፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥፥
ከሰባት ወራት በኋላ......
ከመስፍኔ ህመም እንደምንም ማገገም በጀመርኩበት ሰሞን፣ ከቤቲና ሄዋን ጋር ቁጭ ብለን ቡና እየጠጣን ነበር። ከማይረባ ብዙ ወሬ በኋላ ቢቲ በተለመደ ችኮላዋ ፣
''ሰምተን መደበቅ ሙድ የለውም...በቃ ዕወቂው '' አለች እያየችኝ ሄዋን ክው አለችና ፣ ''በናትሽ ቤቲ ..! ራሷ ሌላ ጊዜ ትስማው በናትሽ'' አለች።
''ምንድን?'' አልኩኝ ቆጣ ብዬ...
ተያዩ።
''ምንድን ነው ለምን አትነግሩኝም?'' አልኩ እንደገና ተቆትቼ። ቤቲ ያለወትሮዋ ትንሽ አቅማማችና ፣
''ማዲዬ...፣ መስፍን አግብቶል። ማወቅ አለብሽ ብዬ ነው...''
አለች።
እሳት የተፋችብኝ ይመስል ፊቴ ተቃጠለ። በቀለም ተነፍታ በነበልባል የምትቃጠል ዶሮ የሆንኩ መሰለኝ። አጥንቶቼ ሁሉ የቀለጡና ከስጋ ብቻ የተሰራሁ መሰለኝ። ምራቄ ከአፌ ያለቀ መሰለኝ። እንደምንም ሶፋውን ደገፍ ብዬ ሁለቱንም አየኋቸው።
''ሶሪ ማዲዬ በቃ...ተይው...'' አለች ሄዋን ፣ ፀጉሬን እየደባበሰች። ''ራይድ ጥሩልኝ ቤቴ መሄድ እፈልጋለው....'' ስል ብቻ ትዝ ይለኛል።
ቤቴ ገብቼ አንዴ እያለቀስኩ፣ አንድ በንዴት ጦፌ መኝታ ቤቴ ውስጥ እየተንጎራደድኩየሆነውን ሁሉ አንድ በአንድ ሳብሰለስል ብውልም ፣ ባወጣም ባወርድም፣ የሆነው ለምን እንደሆነ ሊገባኝ አልቻለም። የእኔና የመስፍኔ መጨረሻ ይሄ መሆኑ በምንም ስሌት ባስበው ሊገባኝ አልቻለም ።
ሞባይሌን አንስቼ ሰዐቴን ዐየሁ። ሁለት ሰዐት ከሀምሳ አምስት ደቂቃ። በጣም አልመሸም።
ደወልኩት። ለመስፍኔ ደወልኩለት ። ያነሳ ይሆን ሁለቴ እንኳን ሳይጠራ አነሳው። ይባስ ብሎ፤ ልክ ስልኬን ይጠብቅ እንደነበር ሰው ፣ ሳይገረም ሰላም አለኝ።
''ሃይ....መሀደር እንዴት ነሽ?''
ማህደር? ማህደር ነው ያለኝ?
''ደህና ነኝ...እንኳን ደስ ያለክ ልልክ ነው...''
''አመሰግናለው....አንቺ ደህና ነሽ?''
''ደህና ነኝ...ማውራት ትችል ይሆን ? አንድ ነገር ልጠይቅክ ነበር?''
''እንችላለን...''
ስሜቴን ተቆጣጠርኩ። ጉሮሮዬን ጠረኩ። ቃላቶቼን መረጥኩ።
''በዚህ ፍጥነት እንዴት አገባህ...? ማለቴ...ማ..ለቴ ለምን እኔን ለማግባት...''
ሳልጨርስ አቋረጠኝ።
''ትዳር የምትፈልጊ አልመሰለኝም...ማህደር ፣ እኔ ሀያ ምናምን ዓመት ሙሉ ገርል ፍሬንድ ነበረኝ። በዚህ እድሜዬ ሚስት ነበር የምፈልገው....ሳይሽ ስለወደፊት አታስቢም ...እና...ጊዜ ማጥፋት አልፈለኩም ....እ?''
ዝም አልኩ።
''ማህደር?''
''አ..ለ..ሁ....'' አልኩ። ግን አልነበርኩም።
''እህ...ማንን ነው ያገባከው?'' አልኩ፣ የሚያውቃቸውን ሴቶች በሙሉ በአእምሮዬ ሳመላልስ መዋሌ በማያስታውቅ ሁኔታ።
''እ..ወይንሸትን...ወይንዬን ነው ....''
ባለ አርባ ስልሳዋ ወይንሸት !
ምን ብዬ እንደጨረስኩ ሳላውቅ ስልኩን ዘጋሁ ። ፊቴ እንደገና ሲነድ፣ዐጥንቴ በንዴት ሲቀልጥ ይሰማኛል። አልጋዬ ላይ ተዘረጋሁ።
ለኔ ያላትን እንጀራ እኔ ብገፋትም አልሻገተችም። ወይንሸት በልታታለች።
ሔዋን.... አንቺ ደሞ አፈር ብዬ። አፈር ያስበላሽ።
🔘አለቀ🔘
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ምሽት። 🙏
👍4😁2❤1
#ፍቅር_ከፈላስፋ
፡
✍
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
#ክፍል_ሦስት
፡
❤️ፌናን
...ፌናን እባላለው ብዬ ታሪኬን ልጀምር እንዴ..?በነገራችን ላይ ይሄ ስም በሰው አፋ ሲጠራ ድንግርግር ይለኛል…ብቻውን የራሱ የሆነ አካል አልባ ነፍስ ኖሮት የሚንቀሳቀስ ነው የሚመስለኝ…በአየር ላይ ሲንሳፈፍ ሁሉ የሚታየኝ ጊዜ አለው…ያ ተንሳፋፊ እራሱን የቻለ የራሱ ህይወት እና ህልውና ያለው ስም የሚሉት መንፈስ መጥቶ በሰውነቴ ሰርጎ ሲዋሀደኝ እና ከማንነቴ ጋ ተቀይጦ ነፍሱን ከነፍሴ ህልውናውን ከህልውናዬ ካዋሀደ ብኃላ አፌ ይላቀቃል…አቤት ብዬ እመልሳለው..እኔን ባይወክልም እኔ ውስጥ የሰረገውን መንፈስ ሊወክል ይችላል በሚል እምነት…ዘግይቼ አቤት እላለው…ጠሪዎቼ ይሄንን ስለማይረዱልኝ ብዙውን ጊዜ ትለጠጣለች ይሉኛል፡፡
እናቴ አምጣ ወለደችኝና ጣለችኝ… አባቴ አነሳና አሳደገኝ… ፡፡እናቴ ጣለቺኝ ስላችሁ ለሰራተኞች ነው…ምን አልባት ሶስት ወይም አራት ለሚሆኑ ሞግዚቶች፡፡እኔን አጫዋችና ተንከባካቢ አንድ ሴት ፤ምግቤን የምታበስል ሌላ ሴት፤ልብሶቼን የምታጥብ ሌላ፡ጤንነቴን የምትከታተልም ሌላ ነርስ….፡፡
ታዲያ እሷም ሆነች በዙሪያዬ ያለውን ጋጋታ የሚታዘብ ሌሎች ሰዎች ልጅን ማሳደግስ እንደዚህ ነው ይላሉ…..እሷም በዛ ኩራት ይሰማታል…፡፡
….እናቴ የጡቷን ጫፍ አንድ ቀን በስህተት አንኳን በአፌ ውስጥ አስገብታ አታውቅም…ስለሚያማት አልነበረም..እንደዘማናዬቹ ሴቶችም ጡቶቾ እንዳይረግቡባትም አልነበረም..ጊዜ ስለሌላት ነው፡፡ከወለደቺኝ ከሶስት ቀን ቡኃላ ቢሮዋ ነበረች….ምክንያቱም ቢዝነስ ነዋ..ደንበኞቾን ተቀናቃኞቾ ይነጥቁባታል ..ሰራተኞቾ በአሻጥር የሆነ ያህል ብር ያጭበረብሯታል….እና ብር ስላላት በሰራተኞች አስከብባኛ ከፊቴ ዞር አለች.
ነገር ግን አንድ እናትን አንድ ሺ ተንከባካቢ ሴት እንደማይተካት የሚያውቀው እንደእኔ የደረሰበት ብቻ ነው…
አባቴ…ዋው !!!!አባቴ ዕድሜውን ሙሉ አስተማሪ ሆኖ ኖሮ አሁንም በአስተማሪነት እያሰራ ያለ ሰው ነው፡፡በዛ ላያ ደራሲ ነው፡፡ምርጥ አሳቢም ነው፡፡እኔን ማፍቀር እና ማሰብ ቋሚ ስራው ነው፡፡ አባቴ ብስለት… እርጋታ…ቁጠብነት እና ረህራሄ መገለጫዎቹ ናቸው፡፡አባቴ ወደዚህ ምድር ከመጣውበት ቀን አንስቶ ለእኔ የሚሆን ጊዜ አጥቶ አያውቅም…ከማስተማር እና ከማንበብ የተረፈው ጊዜ የእኔው ነው፡፡
ከውልደቴ ጀምሮ የህፃንነት አልጋዬ አባቴ መኝታ ክፍል ውስጥ ከእሱ አልጋ ተጠግቶ ነበር ያለው…እናቴ ቀኑን ሙሉ በቢዝነስ ስብሰባዎች በድርድር እና ክርክር ደክሞት ሰለሚውል እናም ደግሞ ወደቤትም እኩለሊት አካባቢ ስለምትመጣ ወደክፍሎ ከገባች ቡኃላ መረበሽ አትፈልግም..በተለይ እንቅልፍ ከወሰዳት ቡኃላ የህጻን እሪታ እንዲረብሻት በፍጽም አይታሰብም…..አይኔን የምታየኝ ጥዋት ወደስራ ለመሄድ ለባብሳና ተኮኩላ ቁርስ አፈ ላይ ጣል አድርጋ ዝግጅቷን ካጠናቀቀች ቡኃላ እግረመንገዶን ለአንድ ወይም ለሁለት ደቂቃ ነው፡፡በዛ ላይ በዛን ሰዓት እኔ ብዝውን ጊዜ እንቅልፍ ላይ ልሆን እችላለው….
አባቴ በሚያስተማራቸው ሁለት ክፍለጊዜ መካከል የእንድ ክፍለጊዜ ክፍተት ካለው መኪናን አስነስቶ ወደቤት በመምጣት ጤና መሆኔን አይቶች አቅፎኝና ስሞኝ ተመልሶ ይሄዳል…ትንሽ ከፍ ስል የህፃን አልጋዬን ጥዬ የእሱን አልጋ መጋራት ጀመርኩ…በነገራችን ላይ የእናቴን ጡት አልጠባውም ስላችሁ ጡት ሳልጠባ ነው ያደኩት እያልኳችሁም አይደለም…ሶስት አመት እስኪሆነኝ ድረስ እንቅልፍ የሚወስደኝ የአባቴን ጡት ጫፍ አፌውስጥ ጨምሬ እየመጠጥኩ ከሆነ ብቻ እንደሆነ የቤቱ ሰው ሆነ ጎረቤት የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡ የእኔ የአባቴን ጡት መጥባት ለሚመለከቱ ሰዎች አይገባቸውም… ቅብጠት ይመስላቸዋል ፤እወነቱን ግን እኔ ገላ ውስጥ የምትገኝ ነፍሴና አባቴ ብቻ ብቻ ነን ምናውቀው ….በልቡ ውስጥ የታጨቀው ለእኔ ያለው ፍቅር በደምስሩ በመሽሎክሎክ በጡቱ ጫፎች በመትነን ወደሁለንተናዬ ገብቶ ሲሰራጭ የሚሰማኝን እርካታ ቃላት ተሰብስበው ለማስረዳት ጉልበት አይኖራቸውም….የዛን ጊዜ እግዜብሄር ደረት ላይ የተለጠፍኩ ይመስለኛል…የዛን ጊዜ የእግዜር ቅዱስ እጅ እጣቶች ግንባሬ ላይ አርፈው ፀጉሬን የሚያርመሰምሱት ይመስለኛል…..
ሶስት አመት ካለፈኝ ቡኃላም ይሄንን ዓመሌን አላቆመክም…ደረቱ ላይ ተለጥፌ ጡቶችን እየመዘመዝኩ ተረት ያነብልኛል….የአባቴ ድምጹ ሙዚቃ ነው…የራሱ ምት የራሱ ዜማ እና የራሱ ውበት አለው…ደሞ ሚገርመኝ እግሮቼን ሰውነቱ ላይ ጭኜ ፤እጆቼን በአንገቱ ዙሪያ ጠምጥሜ፤ ደረቱ ላይ ተለጥፌ ለጆሮዬ ቅርብ ሆኖ የሚያነብልኘ የተረት መፃፍ ድምጽ ከፀሀይ ሽራፊ አካል ተሸርፎ… በጨረቃ አንደበት ውስጥ አልፎ… የሰማይ መስኮትን ልክ እንደማይክራፎን ተጠቅሞ ኩልል እያለ ከዛ እርቀት በመምጣት በጆሮዬ አድርጎ ሳይሆን ቀጥታ በልቤ ላይ በመንጠባጠብ በዝግታ እየቀለጠ ከማንነቴ ጋር የሚዋሀድ የፍቅር አዚም ነው የሚመስለኝ…
እንደነዚህ አይነት የጊዜ ሽራፌዋች ለእኔ የፀሎት ጊዜዎቼ እንደሆኑ ነበር የማስበው…የምመሰጥበት እና የምቀልጥበት….ማንነቴን የማጣበት እና የምጠፋበት….ለነገሩ አሁንም ድረስ የአባቴ ጉያ የእኔ የፀሎት ዋሻዬ ነው…::ደረቱ መስገጂያ መቅደሴ ፤ትንፋሹ ፀሎቴን ወደ ፈጣሪዬ የሚያደረስልኝ ከመቅደሱ የሚበተን የከርቤ ጭሴ ነው ….
አይዞችሁ አትሰልቹ የእኔ ታሪክ ሙሉ የአባቴ ታሪክ ነው…እኔ አባቴን ነኝ ፡፡በስጋ ብቻ አይደለም የወለደኝ በመንፈስም ጭምር ሙሉ የእሱ ልጅ ነኝ፡፡የሚያየውን አይቼ የሚያስበውን ማሰብ እችላለው…ከዛም በላይ አንድ ነን፡፡
====
አባቴ እና እናቴስ..የሁለቱ ግንኙነት በራሱ የተፈጥሮ ሚስጥር ነው፡፡እኔ በእድሜዬ ባልና ሚስት ሆነው አይቻቸው አላውቅም….ደግሞ አንደኛው ስለአንደኛው አደናቅፎት እንኳን ክፋት ፤ ስሞታ ወይም ቅሬታ ሲያሰማ ሰምቼ አላውቅም…ለምሳሌ ያው እንደነገርኳችሁ አባቴ አስተማሪ እንደመሆኑ መጠን የእሱ ወር ደሞዝ ለእናቴ አንድ የእራት ቀሚስ አይገዛላትም….እና ለነዳጅ እንዲሆንህ አንድ ሚሊዬን ብር ደብተርህ ላይ እስገብቼልሀለው ትለዋለች..ያው የእኔንም ሆነ የአባቴ መኪኖች የተገዙት በእናቴ ብር ነው…. ‹‹አመሰግናለው››ይላታል..ከሌላው ቀን ሳይፈግግ ሳይኮሳተርም….ከአምስት ወይም ከስድስት ወር ቡኃላ ‹‹ወይ በስራ ስሯራጥ እረሳውህ..ምን አለ ብታስታውሰኝ ትልና… ቼኳን አውጥታ አንድ‹‹አላምንህም ሚሊዬን ብር ጫር ጫር ታደርግና ታቀብለዋለች‹‹ግን የባለፈውን አልጨረስኩትም››ይላታል በዛው ተለመደ እርጋታው
አሳየኝ››
‹‹ሂጂ ደብተሬን ከምኝታ ቤት አምጪና አሰያት››ያዘኛል እኔን
ሄጄ ሳመጣው….ስምንት መቶ ሃምሳ ሺ ብር…..
‹‹ምን እየሰራህ ነው..?››ትንጨረጨራለች
‹‹ምን ሰራው..?››
‹‹እንዳለእኮ ነው ብሩ››
‹‹ምን ይሰራልኛል…ለቤት ወጪ አላወጣ….ደሞዝ አለኝ መፃፍ ብገዛ ና በሳምንት አንድ ቀን ከልጄ ጋ ወጣ ብለን ብንዝናና ነው…እሱንም ቢሆን እሷው ነች የምትከፍለው…እንደውም በትምህርት ቤት ትንሽ ገንዘብ የሚቸግራቸው አንድ አስር የሚሆኑ ተማሪዎቼን ትንሽ ትንሽ ብር ስለምሰጣቸው ነው….እንዴ እንደውም እኳ አንድ መፃፍም አሳትሜበታለው››ሊያሳምናት ይጥራል፡፡
‹‹አታበሳጨኝ ባክህ …የሆነ የሆነ ነገር አድርገህ ተጠቀምበት እንጂ….ሰው እንዴት ቢያንስ ከልጁ እኩል ብር መጠቀም ያቅተዋል…››…(ቁጣዋን ትቀጥላለች እግረመንገዶንም የእኔን አጥፊነት እየጠቆመች…)
‹‹እሺ አጠፋለው››
በኩርፌያ ወጥታ ወደተለመደ ስራዋ ትሄዳለች….
ሌላው ያው ብዙ ግዜ እናቴ በሽታ አያጣትም….እና ከሀኪም መድሀኒት ሲታዘዝላት….ስድስት ሰዓት
፡
✍
፡
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
#ክፍል_ሦስት
፡
❤️ፌናን
...ፌናን እባላለው ብዬ ታሪኬን ልጀምር እንዴ..?በነገራችን ላይ ይሄ ስም በሰው አፋ ሲጠራ ድንግርግር ይለኛል…ብቻውን የራሱ የሆነ አካል አልባ ነፍስ ኖሮት የሚንቀሳቀስ ነው የሚመስለኝ…በአየር ላይ ሲንሳፈፍ ሁሉ የሚታየኝ ጊዜ አለው…ያ ተንሳፋፊ እራሱን የቻለ የራሱ ህይወት እና ህልውና ያለው ስም የሚሉት መንፈስ መጥቶ በሰውነቴ ሰርጎ ሲዋሀደኝ እና ከማንነቴ ጋ ተቀይጦ ነፍሱን ከነፍሴ ህልውናውን ከህልውናዬ ካዋሀደ ብኃላ አፌ ይላቀቃል…አቤት ብዬ እመልሳለው..እኔን ባይወክልም እኔ ውስጥ የሰረገውን መንፈስ ሊወክል ይችላል በሚል እምነት…ዘግይቼ አቤት እላለው…ጠሪዎቼ ይሄንን ስለማይረዱልኝ ብዙውን ጊዜ ትለጠጣለች ይሉኛል፡፡
እናቴ አምጣ ወለደችኝና ጣለችኝ… አባቴ አነሳና አሳደገኝ… ፡፡እናቴ ጣለቺኝ ስላችሁ ለሰራተኞች ነው…ምን አልባት ሶስት ወይም አራት ለሚሆኑ ሞግዚቶች፡፡እኔን አጫዋችና ተንከባካቢ አንድ ሴት ፤ምግቤን የምታበስል ሌላ ሴት፤ልብሶቼን የምታጥብ ሌላ፡ጤንነቴን የምትከታተልም ሌላ ነርስ….፡፡
ታዲያ እሷም ሆነች በዙሪያዬ ያለውን ጋጋታ የሚታዘብ ሌሎች ሰዎች ልጅን ማሳደግስ እንደዚህ ነው ይላሉ…..እሷም በዛ ኩራት ይሰማታል…፡፡
….እናቴ የጡቷን ጫፍ አንድ ቀን በስህተት አንኳን በአፌ ውስጥ አስገብታ አታውቅም…ስለሚያማት አልነበረም..እንደዘማናዬቹ ሴቶችም ጡቶቾ እንዳይረግቡባትም አልነበረም..ጊዜ ስለሌላት ነው፡፡ከወለደቺኝ ከሶስት ቀን ቡኃላ ቢሮዋ ነበረች….ምክንያቱም ቢዝነስ ነዋ..ደንበኞቾን ተቀናቃኞቾ ይነጥቁባታል ..ሰራተኞቾ በአሻጥር የሆነ ያህል ብር ያጭበረብሯታል….እና ብር ስላላት በሰራተኞች አስከብባኛ ከፊቴ ዞር አለች.
ነገር ግን አንድ እናትን አንድ ሺ ተንከባካቢ ሴት እንደማይተካት የሚያውቀው እንደእኔ የደረሰበት ብቻ ነው…
አባቴ…ዋው !!!!አባቴ ዕድሜውን ሙሉ አስተማሪ ሆኖ ኖሮ አሁንም በአስተማሪነት እያሰራ ያለ ሰው ነው፡፡በዛ ላያ ደራሲ ነው፡፡ምርጥ አሳቢም ነው፡፡እኔን ማፍቀር እና ማሰብ ቋሚ ስራው ነው፡፡ አባቴ ብስለት… እርጋታ…ቁጠብነት እና ረህራሄ መገለጫዎቹ ናቸው፡፡አባቴ ወደዚህ ምድር ከመጣውበት ቀን አንስቶ ለእኔ የሚሆን ጊዜ አጥቶ አያውቅም…ከማስተማር እና ከማንበብ የተረፈው ጊዜ የእኔው ነው፡፡
ከውልደቴ ጀምሮ የህፃንነት አልጋዬ አባቴ መኝታ ክፍል ውስጥ ከእሱ አልጋ ተጠግቶ ነበር ያለው…እናቴ ቀኑን ሙሉ በቢዝነስ ስብሰባዎች በድርድር እና ክርክር ደክሞት ሰለሚውል እናም ደግሞ ወደቤትም እኩለሊት አካባቢ ስለምትመጣ ወደክፍሎ ከገባች ቡኃላ መረበሽ አትፈልግም..በተለይ እንቅልፍ ከወሰዳት ቡኃላ የህጻን እሪታ እንዲረብሻት በፍጽም አይታሰብም…..አይኔን የምታየኝ ጥዋት ወደስራ ለመሄድ ለባብሳና ተኮኩላ ቁርስ አፈ ላይ ጣል አድርጋ ዝግጅቷን ካጠናቀቀች ቡኃላ እግረመንገዶን ለአንድ ወይም ለሁለት ደቂቃ ነው፡፡በዛ ላይ በዛን ሰዓት እኔ ብዝውን ጊዜ እንቅልፍ ላይ ልሆን እችላለው….
አባቴ በሚያስተማራቸው ሁለት ክፍለጊዜ መካከል የእንድ ክፍለጊዜ ክፍተት ካለው መኪናን አስነስቶ ወደቤት በመምጣት ጤና መሆኔን አይቶች አቅፎኝና ስሞኝ ተመልሶ ይሄዳል…ትንሽ ከፍ ስል የህፃን አልጋዬን ጥዬ የእሱን አልጋ መጋራት ጀመርኩ…በነገራችን ላይ የእናቴን ጡት አልጠባውም ስላችሁ ጡት ሳልጠባ ነው ያደኩት እያልኳችሁም አይደለም…ሶስት አመት እስኪሆነኝ ድረስ እንቅልፍ የሚወስደኝ የአባቴን ጡት ጫፍ አፌውስጥ ጨምሬ እየመጠጥኩ ከሆነ ብቻ እንደሆነ የቤቱ ሰው ሆነ ጎረቤት የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡ የእኔ የአባቴን ጡት መጥባት ለሚመለከቱ ሰዎች አይገባቸውም… ቅብጠት ይመስላቸዋል ፤እወነቱን ግን እኔ ገላ ውስጥ የምትገኝ ነፍሴና አባቴ ብቻ ብቻ ነን ምናውቀው ….በልቡ ውስጥ የታጨቀው ለእኔ ያለው ፍቅር በደምስሩ በመሽሎክሎክ በጡቱ ጫፎች በመትነን ወደሁለንተናዬ ገብቶ ሲሰራጭ የሚሰማኝን እርካታ ቃላት ተሰብስበው ለማስረዳት ጉልበት አይኖራቸውም….የዛን ጊዜ እግዜብሄር ደረት ላይ የተለጠፍኩ ይመስለኛል…የዛን ጊዜ የእግዜር ቅዱስ እጅ እጣቶች ግንባሬ ላይ አርፈው ፀጉሬን የሚያርመሰምሱት ይመስለኛል…..
ሶስት አመት ካለፈኝ ቡኃላም ይሄንን ዓመሌን አላቆመክም…ደረቱ ላይ ተለጥፌ ጡቶችን እየመዘመዝኩ ተረት ያነብልኛል….የአባቴ ድምጹ ሙዚቃ ነው…የራሱ ምት የራሱ ዜማ እና የራሱ ውበት አለው…ደሞ ሚገርመኝ እግሮቼን ሰውነቱ ላይ ጭኜ ፤እጆቼን በአንገቱ ዙሪያ ጠምጥሜ፤ ደረቱ ላይ ተለጥፌ ለጆሮዬ ቅርብ ሆኖ የሚያነብልኘ የተረት መፃፍ ድምጽ ከፀሀይ ሽራፊ አካል ተሸርፎ… በጨረቃ አንደበት ውስጥ አልፎ… የሰማይ መስኮትን ልክ እንደማይክራፎን ተጠቅሞ ኩልል እያለ ከዛ እርቀት በመምጣት በጆሮዬ አድርጎ ሳይሆን ቀጥታ በልቤ ላይ በመንጠባጠብ በዝግታ እየቀለጠ ከማንነቴ ጋር የሚዋሀድ የፍቅር አዚም ነው የሚመስለኝ…
እንደነዚህ አይነት የጊዜ ሽራፌዋች ለእኔ የፀሎት ጊዜዎቼ እንደሆኑ ነበር የማስበው…የምመሰጥበት እና የምቀልጥበት….ማንነቴን የማጣበት እና የምጠፋበት….ለነገሩ አሁንም ድረስ የአባቴ ጉያ የእኔ የፀሎት ዋሻዬ ነው…::ደረቱ መስገጂያ መቅደሴ ፤ትንፋሹ ፀሎቴን ወደ ፈጣሪዬ የሚያደረስልኝ ከመቅደሱ የሚበተን የከርቤ ጭሴ ነው ….
አይዞችሁ አትሰልቹ የእኔ ታሪክ ሙሉ የአባቴ ታሪክ ነው…እኔ አባቴን ነኝ ፡፡በስጋ ብቻ አይደለም የወለደኝ በመንፈስም ጭምር ሙሉ የእሱ ልጅ ነኝ፡፡የሚያየውን አይቼ የሚያስበውን ማሰብ እችላለው…ከዛም በላይ አንድ ነን፡፡
====
አባቴ እና እናቴስ..የሁለቱ ግንኙነት በራሱ የተፈጥሮ ሚስጥር ነው፡፡እኔ በእድሜዬ ባልና ሚስት ሆነው አይቻቸው አላውቅም….ደግሞ አንደኛው ስለአንደኛው አደናቅፎት እንኳን ክፋት ፤ ስሞታ ወይም ቅሬታ ሲያሰማ ሰምቼ አላውቅም…ለምሳሌ ያው እንደነገርኳችሁ አባቴ አስተማሪ እንደመሆኑ መጠን የእሱ ወር ደሞዝ ለእናቴ አንድ የእራት ቀሚስ አይገዛላትም….እና ለነዳጅ እንዲሆንህ አንድ ሚሊዬን ብር ደብተርህ ላይ እስገብቼልሀለው ትለዋለች..ያው የእኔንም ሆነ የአባቴ መኪኖች የተገዙት በእናቴ ብር ነው…. ‹‹አመሰግናለው››ይላታል..ከሌላው ቀን ሳይፈግግ ሳይኮሳተርም….ከአምስት ወይም ከስድስት ወር ቡኃላ ‹‹ወይ በስራ ስሯራጥ እረሳውህ..ምን አለ ብታስታውሰኝ ትልና… ቼኳን አውጥታ አንድ‹‹አላምንህም ሚሊዬን ብር ጫር ጫር ታደርግና ታቀብለዋለች‹‹ግን የባለፈውን አልጨረስኩትም››ይላታል በዛው ተለመደ እርጋታው
አሳየኝ››
‹‹ሂጂ ደብተሬን ከምኝታ ቤት አምጪና አሰያት››ያዘኛል እኔን
ሄጄ ሳመጣው….ስምንት መቶ ሃምሳ ሺ ብር…..
‹‹ምን እየሰራህ ነው..?››ትንጨረጨራለች
‹‹ምን ሰራው..?››
‹‹እንዳለእኮ ነው ብሩ››
‹‹ምን ይሰራልኛል…ለቤት ወጪ አላወጣ….ደሞዝ አለኝ መፃፍ ብገዛ ና በሳምንት አንድ ቀን ከልጄ ጋ ወጣ ብለን ብንዝናና ነው…እሱንም ቢሆን እሷው ነች የምትከፍለው…እንደውም በትምህርት ቤት ትንሽ ገንዘብ የሚቸግራቸው አንድ አስር የሚሆኑ ተማሪዎቼን ትንሽ ትንሽ ብር ስለምሰጣቸው ነው….እንዴ እንደውም እኳ አንድ መፃፍም አሳትሜበታለው››ሊያሳምናት ይጥራል፡፡
‹‹አታበሳጨኝ ባክህ …የሆነ የሆነ ነገር አድርገህ ተጠቀምበት እንጂ….ሰው እንዴት ቢያንስ ከልጁ እኩል ብር መጠቀም ያቅተዋል…››…(ቁጣዋን ትቀጥላለች እግረመንገዶንም የእኔን አጥፊነት እየጠቆመች…)
‹‹እሺ አጠፋለው››
በኩርፌያ ወጥታ ወደተለመደ ስራዋ ትሄዳለች….
ሌላው ያው ብዙ ግዜ እናቴ በሽታ አያጣትም….እና ከሀኪም መድሀኒት ሲታዘዝላት….ስድስት ሰዓት
👍1