#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_አምስት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
:
...አሁን እያወራዋችሁ ያለውት ተጨባጭ ስለሆነው እውነታ ነው፡፡ተጨባጭ እውነታ ማለት ምን ማለት ነው ካላችሁኝ በአምስቱ የስሜት ህዋሳቶች ተጠቅመን አዕምሮችን እንዲያስበው ወይም ልባችን እንዲሰማው ማድረግ የምንችለው ነገር ነው፡፡እርግጥ የሰው ልጅ አምስት የስሜት ህዋሳት ብቻ አይደለም ያሉት፡፡ብዙዎቻን የማንረዳውና ስድስተኛው የሆነውን የስሜት ህዋሳት ከተጨባጭ ዓለም ባሻገር ያለውን እወነታ የምን
…..አሁን ስለሌላው ችግሬ ልንገራችሁ..መናገር የቻልኩት ደግሞ በአስር አመቴ ነው፡፡ተገረማችሁ፡፡እውነቴን ነው ልክ እስከአራት አመት ስንፎቀቅ ኖሬ ድንገት ታምራዊ በሆነ መንገድ ብደግ ብዬ መሮጥ ጀመርኩ ፤በአስር አመቴም ድንገት በአንዴ ነው በሁለት ቋንቋ መናገር የቻልኩት፡፡አዎ ገብቶኛል አላመናችሁኝም አይደል፡፡እውነቱ ያነው፡፡
…የእግሬ ጉዳይ ተአምራዊ በሆነ አጋጣሚ እና ሁኔታ እልባት ካገኘ ብኃላ አንደበቴ ግን ባለበት ነበር የቀጠለው…፡፡ .አንዳንድ ትርጉም አልባ የሆኑ ድምፆችን ለምሳሌ ታታታ..ዳዳዳ የመሳሰሉትት ከአንደበቴ ለዛውም በጣም በምበሳጭበት ወቅት ይሰማ ይሆናል እንጂ የሚሰማኝ ስሜት የሚሰጥ ነገር ከእኔ አንደበት ማድመጥ ማይታሰብ ሆኖ ቀጠለ…..
በዚህ ሁኔታዬ የሰፈር ሰዎችም ሆኑ ዘመድ አዝማዶች የሆን በስህተት እንደተፈጠረ ሰው መሳይ ሸክም እንደሆነ ሰው ነበረ የሚያዩኝ፡፡ብዙዎቹ አዕምሮዬም ማሰብ የሚችል ሁሉ አይመስላቸወም ነበር፡፡‹‹ምን አለ ወዲያ ወስዶ በገላገላት ››ብሎ ለፈጣሪው መልሶ እንዲወስደኝ ስለት የሚሳሉ የእናቴ ወዳጆች ቀላል ቁጥር የላቸውም፡፡
ግን እነሱ ያልገባቸው የአዕምሮዬን የማሰብ ብቃት ስል መሆኑን ነው፡፡ከእግሮቼ እና ከአንደበቴ በልተጣጣመ መልኩ እንደውም ፍጽም ተቃራኒ በሆነ መንገድ አዕምሮዬ ክፉና ደጉን መለየት እና የሰላ እሳቤ ማሰብ የጀመረው ገና በጮርቃነቴ ነው ፡፡ይሄንን ግን ከእናቴ በስተቀር ማንም አይረዳልኝም ነበር፡፡እርግጥ አሁንም ድረስ ብዙዎቹ አያውቁም… ቢያውቁም ማመን አይፈልጉምን ፡፡
ከህፃንነቴ ጀምሮ እኔ የምጫወተው ዕቃ ዕቃ በመደርደር፤ወይም ከልጆች ጋር ሌባና ፖሊስ በመሯሯጥ ፤ወይንም ደግሞ ቡድን ለይቷ በሰፊ የሳር ሜዳ ላይ ከውሪ ህፃናት ጋር ተበትኖ በመሯሯጥ ኳስ በመጠለዝ አይደለም… ረጅም የተባለውን የልጅነት ጊዜዬን የቲቪ ስክሪን ላይ አፍጥጬ የተለያዩ አለማቀፍ የቲቪ ቻናሎችን በመከታተል ነው.....፡አረብኛ ቻናሎችን እንግሊዘኛ ቻናሎችን አማራኛ ቻናሎችን ወዘተ…
ከዛ የተረፈኝን ቀሪ ሙሉ ጊዜ ደግሞ በተመስጦ በማሰብ ነው የማሳልፈው፡፡ስለሆነ ነገር በጥልቀት እና በፍዘት ለሳዕታት በመተከዝ ማሰብ....ለዛውም ከተቀመጥኩበት ሳልንፎቀቅ እና አይኖቼን ከተከልኩበት ሳላንቀሳቅስ ..፡፡
የአማልክት ዝርያ ከሌለበት በስተቀር እስቲ አንድ የአምስት እና የስድስት አመት ልጅ በዚህ መልክ ሊያስባቸው የሚችላቸው ነገሮች ከየት ያመጣል…?፡፡ስለሆነ ነገር ለማሰብ እኮ ስለነገሩ ወይ በትምህርት ያገኙት ዕውቀት ካልሆነም በኑሮ ልምድ ያካበቱት የልምድ ክምችት ሊኖር የግድ ነው፡፡ከዛ ያንን መነሻ በማድረግ ስለነገሩ ይበልጥ ለመረዳት ወይንም ካወቅነው ጀርባ ያለን ድብቅ ወይም ሽሽግ ያልታወቀ እውቀትን ለመግለጽ ማሰብ ያለ ነው፡፡በዛ ላይ ለማሰብ እራሱ በመጠኑም ቢሆን የበሰለ አዕምሮ፤የዳበረ ስሜት ፤የበለፀገ እይታ ከሁሉም በላይ የፈካ ንቃተ-ህሊና አስፈላጊ ነው፡፡ሁሉም የሰው ልጅ ከማሰብ ችሎታ ጋር እንደሚፈጠር ባምንም ማሰብ እንደሚችሉ አውቀው በጊዜው ማሰብ የሚጀምሩ ሰዎች ግን ጥቂቶች እንደሆኑ አምናለው፡፡ ብዙዎቹ የማሰብን ፀጋ በተግባር ማጣጣም የሚጀምሩት በእርጅና ዕድሜ ውስጥ ከገቡ ቡኃላ ነው፡፡ወደኃላ በትዝታ እየተሳቡ እና በፀፀት እየተንገላቱ ፡፡ከዛም በባሰ ሁኔታ ከሚስጥራዊው አለም ይዞት የመጣውን ንጽህ አዕምሮ ሳይነካካው ይዞት የሚሞትም የሰው ልጅ ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡በደመነፍስ ብቻ በመኖር፡፡
እኔ ታዲያ በተጋነነ ሁኔታ በጮርቃነት ዕድሜዬ እንዲያ ዓይነት ብስለት ከየት አመጣውት…? ይሄንን እናቴ ነች ምታውቀው፡፡ሌላውማ በዛ ሁኔተ ሲታዘበኝ እያሰብኩ እንደሆነ ሳይሆን የሚረዱት በአዕምሮ ዝግመት በሽታ ተጠቅቼ እየነሆለልኩ እንደሆነ ነው፡፡ለነገሩ ማን ነበር ‹በጂኒዬስነትና በእብደት መካከል ያለችው መስመር በጣም ቀጭን ነች ያለው ››….በዚህ እሳቤ እንደእብድ እኔን ማሰባቸው ብዙም አልተሳሳቱም፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_አምስት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
፡
:
...አሁን እያወራዋችሁ ያለውት ተጨባጭ ስለሆነው እውነታ ነው፡፡ተጨባጭ እውነታ ማለት ምን ማለት ነው ካላችሁኝ በአምስቱ የስሜት ህዋሳቶች ተጠቅመን አዕምሮችን እንዲያስበው ወይም ልባችን እንዲሰማው ማድረግ የምንችለው ነገር ነው፡፡እርግጥ የሰው ልጅ አምስት የስሜት ህዋሳት ብቻ አይደለም ያሉት፡፡ብዙዎቻን የማንረዳውና ስድስተኛው የሆነውን የስሜት ህዋሳት ከተጨባጭ ዓለም ባሻገር ያለውን እወነታ የምን
…..አሁን ስለሌላው ችግሬ ልንገራችሁ..መናገር የቻልኩት ደግሞ በአስር አመቴ ነው፡፡ተገረማችሁ፡፡እውነቴን ነው ልክ እስከአራት አመት ስንፎቀቅ ኖሬ ድንገት ታምራዊ በሆነ መንገድ ብደግ ብዬ መሮጥ ጀመርኩ ፤በአስር አመቴም ድንገት በአንዴ ነው በሁለት ቋንቋ መናገር የቻልኩት፡፡አዎ ገብቶኛል አላመናችሁኝም አይደል፡፡እውነቱ ያነው፡፡
…የእግሬ ጉዳይ ተአምራዊ በሆነ አጋጣሚ እና ሁኔታ እልባት ካገኘ ብኃላ አንደበቴ ግን ባለበት ነበር የቀጠለው…፡፡ .አንዳንድ ትርጉም አልባ የሆኑ ድምፆችን ለምሳሌ ታታታ..ዳዳዳ የመሳሰሉትት ከአንደበቴ ለዛውም በጣም በምበሳጭበት ወቅት ይሰማ ይሆናል እንጂ የሚሰማኝ ስሜት የሚሰጥ ነገር ከእኔ አንደበት ማድመጥ ማይታሰብ ሆኖ ቀጠለ…..
በዚህ ሁኔታዬ የሰፈር ሰዎችም ሆኑ ዘመድ አዝማዶች የሆን በስህተት እንደተፈጠረ ሰው መሳይ ሸክም እንደሆነ ሰው ነበረ የሚያዩኝ፡፡ብዙዎቹ አዕምሮዬም ማሰብ የሚችል ሁሉ አይመስላቸወም ነበር፡፡‹‹ምን አለ ወዲያ ወስዶ በገላገላት ››ብሎ ለፈጣሪው መልሶ እንዲወስደኝ ስለት የሚሳሉ የእናቴ ወዳጆች ቀላል ቁጥር የላቸውም፡፡
ግን እነሱ ያልገባቸው የአዕምሮዬን የማሰብ ብቃት ስል መሆኑን ነው፡፡ከእግሮቼ እና ከአንደበቴ በልተጣጣመ መልኩ እንደውም ፍጽም ተቃራኒ በሆነ መንገድ አዕምሮዬ ክፉና ደጉን መለየት እና የሰላ እሳቤ ማሰብ የጀመረው ገና በጮርቃነቴ ነው ፡፡ይሄንን ግን ከእናቴ በስተቀር ማንም አይረዳልኝም ነበር፡፡እርግጥ አሁንም ድረስ ብዙዎቹ አያውቁም… ቢያውቁም ማመን አይፈልጉምን ፡፡
ከህፃንነቴ ጀምሮ እኔ የምጫወተው ዕቃ ዕቃ በመደርደር፤ወይም ከልጆች ጋር ሌባና ፖሊስ በመሯሯጥ ፤ወይንም ደግሞ ቡድን ለይቷ በሰፊ የሳር ሜዳ ላይ ከውሪ ህፃናት ጋር ተበትኖ በመሯሯጥ ኳስ በመጠለዝ አይደለም… ረጅም የተባለውን የልጅነት ጊዜዬን የቲቪ ስክሪን ላይ አፍጥጬ የተለያዩ አለማቀፍ የቲቪ ቻናሎችን በመከታተል ነው.....፡አረብኛ ቻናሎችን እንግሊዘኛ ቻናሎችን አማራኛ ቻናሎችን ወዘተ…
ከዛ የተረፈኝን ቀሪ ሙሉ ጊዜ ደግሞ በተመስጦ በማሰብ ነው የማሳልፈው፡፡ስለሆነ ነገር በጥልቀት እና በፍዘት ለሳዕታት በመተከዝ ማሰብ....ለዛውም ከተቀመጥኩበት ሳልንፎቀቅ እና አይኖቼን ከተከልኩበት ሳላንቀሳቅስ ..፡፡
የአማልክት ዝርያ ከሌለበት በስተቀር እስቲ አንድ የአምስት እና የስድስት አመት ልጅ በዚህ መልክ ሊያስባቸው የሚችላቸው ነገሮች ከየት ያመጣል…?፡፡ስለሆነ ነገር ለማሰብ እኮ ስለነገሩ ወይ በትምህርት ያገኙት ዕውቀት ካልሆነም በኑሮ ልምድ ያካበቱት የልምድ ክምችት ሊኖር የግድ ነው፡፡ከዛ ያንን መነሻ በማድረግ ስለነገሩ ይበልጥ ለመረዳት ወይንም ካወቅነው ጀርባ ያለን ድብቅ ወይም ሽሽግ ያልታወቀ እውቀትን ለመግለጽ ማሰብ ያለ ነው፡፡በዛ ላይ ለማሰብ እራሱ በመጠኑም ቢሆን የበሰለ አዕምሮ፤የዳበረ ስሜት ፤የበለፀገ እይታ ከሁሉም በላይ የፈካ ንቃተ-ህሊና አስፈላጊ ነው፡፡ሁሉም የሰው ልጅ ከማሰብ ችሎታ ጋር እንደሚፈጠር ባምንም ማሰብ እንደሚችሉ አውቀው በጊዜው ማሰብ የሚጀምሩ ሰዎች ግን ጥቂቶች እንደሆኑ አምናለው፡፡ ብዙዎቹ የማሰብን ፀጋ በተግባር ማጣጣም የሚጀምሩት በእርጅና ዕድሜ ውስጥ ከገቡ ቡኃላ ነው፡፡ወደኃላ በትዝታ እየተሳቡ እና በፀፀት እየተንገላቱ ፡፡ከዛም በባሰ ሁኔታ ከሚስጥራዊው አለም ይዞት የመጣውን ንጽህ አዕምሮ ሳይነካካው ይዞት የሚሞትም የሰው ልጅ ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡በደመነፍስ ብቻ በመኖር፡፡
እኔ ታዲያ በተጋነነ ሁኔታ በጮርቃነት ዕድሜዬ እንዲያ ዓይነት ብስለት ከየት አመጣውት…? ይሄንን እናቴ ነች ምታውቀው፡፡ሌላውማ በዛ ሁኔተ ሲታዘበኝ እያሰብኩ እንደሆነ ሳይሆን የሚረዱት በአዕምሮ ዝግመት በሽታ ተጠቅቼ እየነሆለልኩ እንደሆነ ነው፡፡ለነገሩ ማን ነበር ‹በጂኒዬስነትና በእብደት መካከል ያለችው መስመር በጣም ቀጭን ነች ያለው ››….በዚህ እሳቤ እንደእብድ እኔን ማሰባቸው ብዙም አልተሳሳቱም፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍3👏1
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_ስድስት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
..… እንደነርኮችሁ የመራመዴ ጉዳይ ተአምራዊ በሆነ መንገድ እልባት ካገኘ ቡኃላ እናቴ ለአንደበቴ መከፈት መጓጓት ጀመረች፡፡ያው እናት አይደለች ፡፡በተለይ ስድስት አመት ከሞላኝ ቡኃላ እኩዬቼ ሁሉ ወደትምህርት ቤት ሲጓዙ እኔ አንደበቴ መላቀቅ ባለመቻሉ ምክንያት እቤት በመቅረቴ ውስጧ ተጎዳና እንደአዲስ እኔን ለማዳን የምታደርገውን እንቅስቃሴ ጀመረች ፡፡በዚህ እንቅስቃሴዎ ወቅት ስታልፍም ሆነ ስታገድም የሚያገኞት ሰዎች ሁሉ የሆነ ነገር ሳይሏት ዝም ብለው አያልፎትም፡፡
መቼስ ሀበሻ ባህል ውስጥ አንዱ አስቸጋሪው ነገር የሆነ ሰው ችግር ላይ በወደቀ ቁጥር ምክር ሰጪ ሰው መብዛቱ የታወቀ ነው፡፡ለምን ጠበል አትወስጂውም……?አዋቂ ቤት ይሻልሻል……?እዚህ ከተማ ላይ አዲስ ሀኪም መጥቷል አሉ….…? ውጌሻ ጋር አይሻልሽም….የማይባል ነገር የለም፡፡ታዲያ ይሄ ችግር ውስጥ ላለችና ግራ ለገባት እናቴ በወቅቱ ምን ያህል ግራ አጋቢና አስጨናቂ እንደሚሆንባት መገመት አይከብድም፡፡
እናቴ አንደወትሮዋ እኔን ለማዳን ስትንከራተት ውላ ስትመለስ አባቷ ይናገራታል፡፡
-ልጄ በቃ ለአምላክ ተይው…እሱ እንዳደረገ ያድርገው
-እንዴት እንዳደረገ ያድርገው ስትል…?...ትጠይቃለች
-በቃ አንዳንዴ ከአምላክ ጋር እልክ መጋባት አያስፈልግም…አሱን አድናለው ብለሽ ከእዚህ እዛ ስትካለቢ አንቺም ከሰውነት ጓዳና ወጣሽ…እራስሺን እስኪ እይ… የአርባ አመት አሮጊት መስለሻል እኮ…ገና በሀያ ሶስት አመትሽ ፊትሽን ማድያት እየበላው ነው፡፡በዚህ ከቀጠልሽ የከፋ በሽታ ላይ መውደቅሽ አይቀርም፡፡
-እና ምን አድርጊ ነው የምትለኝ፡፡…?
በቃ እሱን አድናለው ብለሽ ከወዲህ ወዲያ መንከራተቱን አቁሚ.. እግዜያብሄር እግሩን ተርትሮልሻል …በቃ በዛ ተመስገን ብለሽ ሌላውን ተይው…ይሄው ለዓመታት ተንከረተሽ፡፡ ..ህክምናውንም ጠበሉንም ሞክረሻል፡፡ይሄ ነው ችግሩ ብሎ ሊነግርሽ የቻለ የህክምና ጠቢብ የለም፡፡ይሄ ማለት ደግሞ የልጅሽ ችግር ሚስጥር በአምላክ እጅ ብቻ እንደሆነ ነው የሚገባኝ፡፡ በእሱ እጅ ከሆነ ደግሞ ታአምሩን የሚያደርግበት የራሱ ቀንና ጊዜ አለው፡፡እሱን በትዕግስት መጠበቅ ነው፡፡ስለሆነም መንከራተቱን አቁሚ፡፡እዚሁ እንከባከበዋለን፡፡ምንም ነገር እንዳይጎልበት ማድረግ እንችላለን፡፡የሚጠብቁት ተጨማሪ ሰራተኞችም ልንቀጥርለት እንችላለን፡፡አንቺ ግን ከዚህ በላይ እራስሽን አትጣይ፡፡ ……
-አባዬ እናቱ እኮ ነኝ፡፡እንዴት ይሄ የእግዜር ስራና ፍቃድ ነው ብዬ እጆቼን አጣጥፌ ተስፋ ቆርጬ ልቀመጥ እችላለው…?፡፡አንተ እኔ እንደዛ ብሆንብህ የሆነችውን ትሁን ብለህ ተስፋ ቆርጠህብኝ ትተወኝ ነበር…?፡፡…….የትዝብት ጥያቄ ጠየቀቺው፡፡
-አይ…ስለልጅ ልጄ እኮ ነው እያወራን ያለነው… ለአንቺ ብቻ ሳይሆን ለእኔም ልጄ ነው፡፡ጨካኘ ሆኜ አይደለም፡፡ግን እሱን ለማደን በሚል ያልተረጋገጠ ተስፋ አንቺን እንዳላጣ ስለፈራው ነው፡፡ሰለጨነቀኝ ነው፡፡
-በቃ አባዬ በቃ …. መቼም በልጄ ተስፋ አልቆርጥም፡፡መቼም እግዜር እንዳደረገ ያድርገው ብዬ ልቤን አረጋግቼ እድሜ ልኩን ከሰው ተገልሎ በተዘጋ ቤት ውስጥ እንዲኖር በመፍረድ እኔ ለመሽቀርቀርና እራሴን ለማሽሞንሞን አልሞክርም…..መቼም፡፡……ብላ ከአባቷ በንዴት እና በለቅሶ ተለይታ እኔን ወደመኝታ ቤት ይዛ ገብታ ግንባሬ ላይ ተደፍታ በእንባ እየታጠበች ከፈጣሪዋ ጋር ለሳዕታት በምሬት ካወራች..(እናንተ ከፀለየች )ብላችሁ ማንበብ ትችላላችሁ አቅፋኝ ትተኛለች፡፡
ማለዳ ሊነጋጋ ሲል ጥርት ያለ ህልም ታያለች፡፡ተመሳሳይ አይነት ህልም እኔም አይቻለው፡፡ልዩነቱ እሷ ያየችውን ህልም ለአባቷ መናገር ስትችል..እኔ ደግሞ ምናገርበት አንደበት ስላልነበረኝ ለእሷ እንኳን መናገር አልቻኩም፡፡
-ህልሙ እንዲህ ነው
ጠይም የተለጠለጠ ኑግ የሚመስል የሰውነት ቀለም ያላቸወ ፊታቸው በአደገ እና በተንዠረገገ ነጭ ፀጉር የተሸፈነ ሽማግሌ መኝታ ክፍላችን ሰተት ብለው ይገባሉ፡፡እናቴ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጣ እኔን ጉልበቷ ላይ ታቅፋ በተመስጦ ላይ ሳለች ሰውዬው ወደእኛ ቀርበው ወለሉ ላይ በርከክ ይሉና ጭንቅላቴን እየዳበሱ
‹‹ ..ልጅሽ ታላቅ ሰው ይሆናል፡፡አንድ ቀን ዓለም ስለእሱ በመደመም ያወራል፡፡ምድራዊውን አለም ከመንፈሳዊው አለም ጋር ድልድይ ሆኖ ያስተሳስራል…ስለዚህ አንቺ መጨነቅሽን አቁሚ .. እሱ በፈለገ ቀን እራሱን ማዳን ይችላል፡፡ ከራሱም ተርፎ ሌላውን ያድናል፡፡ግን ሲፈልግ…ቀኑ ሲደርስ ብቻ ነው እንደዛ የሚያደርገው፡፡
-አባት ስለእኔ ልጅ ነው የሚያወሩት..?በጥርጣሬ እና ያሉትን ባለማመን ትጠይቃለች፡፡
-አዎ ልጄ ..እኔ የአማላክ መልዕክተኛ ነኝ፡፡ አምላክ እንደገለፀልኝ ከሆነ የልጅሽ እውቀት ጥልቅና ከዛኛው አለም ይዞት የመጣው ነው፡፡
-ከዛኛው አለም ሲሉ…?፡፡
ዳግመኛ ስለመወለድ የምታውቂው ነገር አለ ልጄ.?.
-እኔ እንጃ ብቻ ከዚህ በፊት የሰማው መሰለኝ፡፡አዎ ክርስቲያን አይደለው..ሰው ከውሀና ከመንፈስ ዳግመኘ ካልተወለደ በስተቀር ወደመንግስቱ መግባት እንደማይችል አምላክ ተናግሯል፡፡
-ትክክል እኔ ግን እያልኩ ያለውት ልጅሽች ወደ እዚህች ምድር ሲመጣ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡ ከሁለት ሺ አመታት በፊት ነፍሱ እዚህች ምድር ላይ ነበረች…የበለፀገ ህይወት እና በእውቀት የተሞላ ስብዕና ነበረው..እና ያንን እውቀት ነፍሱ ይዛው የመጣች ይመስለኛል፡፡
-እና እኔ ምን ላድርግ …?
-ምንም ፤እራሱ ፈልጎ የሆነ ነገር ማድረግ እስኪችል ድረስ አትጫኚው..አንቺም አትባክኚ፡፡ ብቻ በእሱ ላይ ሁሌም እምነት ይኑርሽ..ወስጡ የተቀበረውን እውነትና እውቀት ብቻ እንዲገለፅለት ሁሌ ከጎኑ ሁኚ…ከጎኑ መሆንሽ ብቻ ለእሱ በቂው ነው..ሌላውን በጊዜው እራሱ ያደርገዋል፡፡
-ሽበታሙ መልዕክት አድራሽ ሽማግሊ ከክፍላችን ሳይወጣ ነበር የሰራተኛችን የመኝታ ቤታችንን በራፍ መቆርቆር ሁለታችንንም ከእንቅልፋችን የቀሰቀሰን
-እናቴ ህልሙን ልትረሳ ሰውዬውንም ልትዘነጋ አልቻለችም፡፡ሰራ አልቻለችም..ሰውዬውን ልትዘናጋ.
ዘወትር እንደምታደርገው ማታ አካባቢ ቤተክርስቲያን ሄድን፡፡የተለመደውን የማታ ትምህርት ተከታትላ..ያው እንደወትሮዋ ከአምላኮ ጋር አንሾካሽካ ፤ስትጨርስ ስለህልሞም እያሰበች የመልስ ጉዞ ለማድረግ የቤተክርሲቲያን አጥር ግቢ ወጥተን ብዙም ሳንርቅ እኛ ሁለታችንም በህልማችን ያየናቸው ሽማጊሌ በትክክል እሳቸው ድንገት ከፊታችን ተደንቅረው መንገዳችንን ገቱት.እኔ ብዙም ባይደንቀኝም እናቴ ግን በድንዛዜ ሀውልት መስላ ነበር ባለችበት የቆመችው
-ሰውዬው ለእናቴ ድንጋጤ ብዙም ትኩረት ሳይሰጡ ጎንበስ ብለው እጃቸውን ጭንቅላቴ ላይ አሳርፈው በመዳበስ እይታቸውን ወደእናቴ አድርገው ‹‹ጌታ ችግርሽን ይፍታልሽ…እግዜያብሄር ለቅሶሽን ሰምቶል ››በማለት የብስራት ቃላቸውን አሰሟት
-ተአምር ነው፡፡እርሷ መላአክ ኖት…?
-አይ አይደለውም ሰው ነኝ፡፡ተራ ሰው ለሶስት ቀን በተከታታይ በህልሜ ሳያችሁ ነበር፡፡ህልሜን አምኜ እዚህ ስመጣ ደግሞ በአካል አገኘዋችሁ፡፡››
-እኔም አይቼዎታለው››
-በይ እንግዲህ የምኞትሽ ይሙላልሽ ?
-በህልሞት ምንም እንዲነግሩኝ አልተነገሮትም.››
-አይ ሁሉንም ለእሷ ነግሬያታለው..አንተ ብቻ አግኛትና ልጇን ደባብስላት ነው የተባልኩት፡፡……..ብለው አልፈውን መንገዳቸውን ሲቀጥሉ…እናቴ ከድንዛዜዋ ባና -እሺ እግዜር ይከተሎት..አለቻቸው
-አንቺንም ልጄ....ከእነልጅሽ እግዜያብሄር ይጠብቅሽ ፡፡ብለው ከእይታችን ተሰወሩብን
ከዛ ቡኃላ እናቴ ፍፁም ተረጋጋች
:
#ክፍል_ስድስት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
..… እንደነርኮችሁ የመራመዴ ጉዳይ ተአምራዊ በሆነ መንገድ እልባት ካገኘ ቡኃላ እናቴ ለአንደበቴ መከፈት መጓጓት ጀመረች፡፡ያው እናት አይደለች ፡፡በተለይ ስድስት አመት ከሞላኝ ቡኃላ እኩዬቼ ሁሉ ወደትምህርት ቤት ሲጓዙ እኔ አንደበቴ መላቀቅ ባለመቻሉ ምክንያት እቤት በመቅረቴ ውስጧ ተጎዳና እንደአዲስ እኔን ለማዳን የምታደርገውን እንቅስቃሴ ጀመረች ፡፡በዚህ እንቅስቃሴዎ ወቅት ስታልፍም ሆነ ስታገድም የሚያገኞት ሰዎች ሁሉ የሆነ ነገር ሳይሏት ዝም ብለው አያልፎትም፡፡
መቼስ ሀበሻ ባህል ውስጥ አንዱ አስቸጋሪው ነገር የሆነ ሰው ችግር ላይ በወደቀ ቁጥር ምክር ሰጪ ሰው መብዛቱ የታወቀ ነው፡፡ለምን ጠበል አትወስጂውም……?አዋቂ ቤት ይሻልሻል……?እዚህ ከተማ ላይ አዲስ ሀኪም መጥቷል አሉ….…? ውጌሻ ጋር አይሻልሽም….የማይባል ነገር የለም፡፡ታዲያ ይሄ ችግር ውስጥ ላለችና ግራ ለገባት እናቴ በወቅቱ ምን ያህል ግራ አጋቢና አስጨናቂ እንደሚሆንባት መገመት አይከብድም፡፡
እናቴ አንደወትሮዋ እኔን ለማዳን ስትንከራተት ውላ ስትመለስ አባቷ ይናገራታል፡፡
-ልጄ በቃ ለአምላክ ተይው…እሱ እንዳደረገ ያድርገው
-እንዴት እንዳደረገ ያድርገው ስትል…?...ትጠይቃለች
-በቃ አንዳንዴ ከአምላክ ጋር እልክ መጋባት አያስፈልግም…አሱን አድናለው ብለሽ ከእዚህ እዛ ስትካለቢ አንቺም ከሰውነት ጓዳና ወጣሽ…እራስሺን እስኪ እይ… የአርባ አመት አሮጊት መስለሻል እኮ…ገና በሀያ ሶስት አመትሽ ፊትሽን ማድያት እየበላው ነው፡፡በዚህ ከቀጠልሽ የከፋ በሽታ ላይ መውደቅሽ አይቀርም፡፡
-እና ምን አድርጊ ነው የምትለኝ፡፡…?
በቃ እሱን አድናለው ብለሽ ከወዲህ ወዲያ መንከራተቱን አቁሚ.. እግዜያብሄር እግሩን ተርትሮልሻል …በቃ በዛ ተመስገን ብለሽ ሌላውን ተይው…ይሄው ለዓመታት ተንከረተሽ፡፡ ..ህክምናውንም ጠበሉንም ሞክረሻል፡፡ይሄ ነው ችግሩ ብሎ ሊነግርሽ የቻለ የህክምና ጠቢብ የለም፡፡ይሄ ማለት ደግሞ የልጅሽ ችግር ሚስጥር በአምላክ እጅ ብቻ እንደሆነ ነው የሚገባኝ፡፡ በእሱ እጅ ከሆነ ደግሞ ታአምሩን የሚያደርግበት የራሱ ቀንና ጊዜ አለው፡፡እሱን በትዕግስት መጠበቅ ነው፡፡ስለሆነም መንከራተቱን አቁሚ፡፡እዚሁ እንከባከበዋለን፡፡ምንም ነገር እንዳይጎልበት ማድረግ እንችላለን፡፡የሚጠብቁት ተጨማሪ ሰራተኞችም ልንቀጥርለት እንችላለን፡፡አንቺ ግን ከዚህ በላይ እራስሽን አትጣይ፡፡ ……
-አባዬ እናቱ እኮ ነኝ፡፡እንዴት ይሄ የእግዜር ስራና ፍቃድ ነው ብዬ እጆቼን አጣጥፌ ተስፋ ቆርጬ ልቀመጥ እችላለው…?፡፡አንተ እኔ እንደዛ ብሆንብህ የሆነችውን ትሁን ብለህ ተስፋ ቆርጠህብኝ ትተወኝ ነበር…?፡፡…….የትዝብት ጥያቄ ጠየቀቺው፡፡
-አይ…ስለልጅ ልጄ እኮ ነው እያወራን ያለነው… ለአንቺ ብቻ ሳይሆን ለእኔም ልጄ ነው፡፡ጨካኘ ሆኜ አይደለም፡፡ግን እሱን ለማደን በሚል ያልተረጋገጠ ተስፋ አንቺን እንዳላጣ ስለፈራው ነው፡፡ሰለጨነቀኝ ነው፡፡
-በቃ አባዬ በቃ …. መቼም በልጄ ተስፋ አልቆርጥም፡፡መቼም እግዜር እንዳደረገ ያድርገው ብዬ ልቤን አረጋግቼ እድሜ ልኩን ከሰው ተገልሎ በተዘጋ ቤት ውስጥ እንዲኖር በመፍረድ እኔ ለመሽቀርቀርና እራሴን ለማሽሞንሞን አልሞክርም…..መቼም፡፡……ብላ ከአባቷ በንዴት እና በለቅሶ ተለይታ እኔን ወደመኝታ ቤት ይዛ ገብታ ግንባሬ ላይ ተደፍታ በእንባ እየታጠበች ከፈጣሪዋ ጋር ለሳዕታት በምሬት ካወራች..(እናንተ ከፀለየች )ብላችሁ ማንበብ ትችላላችሁ አቅፋኝ ትተኛለች፡፡
ማለዳ ሊነጋጋ ሲል ጥርት ያለ ህልም ታያለች፡፡ተመሳሳይ አይነት ህልም እኔም አይቻለው፡፡ልዩነቱ እሷ ያየችውን ህልም ለአባቷ መናገር ስትችል..እኔ ደግሞ ምናገርበት አንደበት ስላልነበረኝ ለእሷ እንኳን መናገር አልቻኩም፡፡
-ህልሙ እንዲህ ነው
ጠይም የተለጠለጠ ኑግ የሚመስል የሰውነት ቀለም ያላቸወ ፊታቸው በአደገ እና በተንዠረገገ ነጭ ፀጉር የተሸፈነ ሽማግሌ መኝታ ክፍላችን ሰተት ብለው ይገባሉ፡፡እናቴ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጣ እኔን ጉልበቷ ላይ ታቅፋ በተመስጦ ላይ ሳለች ሰውዬው ወደእኛ ቀርበው ወለሉ ላይ በርከክ ይሉና ጭንቅላቴን እየዳበሱ
‹‹ ..ልጅሽ ታላቅ ሰው ይሆናል፡፡አንድ ቀን ዓለም ስለእሱ በመደመም ያወራል፡፡ምድራዊውን አለም ከመንፈሳዊው አለም ጋር ድልድይ ሆኖ ያስተሳስራል…ስለዚህ አንቺ መጨነቅሽን አቁሚ .. እሱ በፈለገ ቀን እራሱን ማዳን ይችላል፡፡ ከራሱም ተርፎ ሌላውን ያድናል፡፡ግን ሲፈልግ…ቀኑ ሲደርስ ብቻ ነው እንደዛ የሚያደርገው፡፡
-አባት ስለእኔ ልጅ ነው የሚያወሩት..?በጥርጣሬ እና ያሉትን ባለማመን ትጠይቃለች፡፡
-አዎ ልጄ ..እኔ የአማላክ መልዕክተኛ ነኝ፡፡ አምላክ እንደገለፀልኝ ከሆነ የልጅሽ እውቀት ጥልቅና ከዛኛው አለም ይዞት የመጣው ነው፡፡
-ከዛኛው አለም ሲሉ…?፡፡
ዳግመኛ ስለመወለድ የምታውቂው ነገር አለ ልጄ.?.
-እኔ እንጃ ብቻ ከዚህ በፊት የሰማው መሰለኝ፡፡አዎ ክርስቲያን አይደለው..ሰው ከውሀና ከመንፈስ ዳግመኘ ካልተወለደ በስተቀር ወደመንግስቱ መግባት እንደማይችል አምላክ ተናግሯል፡፡
-ትክክል እኔ ግን እያልኩ ያለውት ልጅሽች ወደ እዚህች ምድር ሲመጣ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡ ከሁለት ሺ አመታት በፊት ነፍሱ እዚህች ምድር ላይ ነበረች…የበለፀገ ህይወት እና በእውቀት የተሞላ ስብዕና ነበረው..እና ያንን እውቀት ነፍሱ ይዛው የመጣች ይመስለኛል፡፡
-እና እኔ ምን ላድርግ …?
-ምንም ፤እራሱ ፈልጎ የሆነ ነገር ማድረግ እስኪችል ድረስ አትጫኚው..አንቺም አትባክኚ፡፡ ብቻ በእሱ ላይ ሁሌም እምነት ይኑርሽ..ወስጡ የተቀበረውን እውነትና እውቀት ብቻ እንዲገለፅለት ሁሌ ከጎኑ ሁኚ…ከጎኑ መሆንሽ ብቻ ለእሱ በቂው ነው..ሌላውን በጊዜው እራሱ ያደርገዋል፡፡
-ሽበታሙ መልዕክት አድራሽ ሽማግሊ ከክፍላችን ሳይወጣ ነበር የሰራተኛችን የመኝታ ቤታችንን በራፍ መቆርቆር ሁለታችንንም ከእንቅልፋችን የቀሰቀሰን
-እናቴ ህልሙን ልትረሳ ሰውዬውንም ልትዘነጋ አልቻለችም፡፡ሰራ አልቻለችም..ሰውዬውን ልትዘናጋ.
ዘወትር እንደምታደርገው ማታ አካባቢ ቤተክርስቲያን ሄድን፡፡የተለመደውን የማታ ትምህርት ተከታትላ..ያው እንደወትሮዋ ከአምላኮ ጋር አንሾካሽካ ፤ስትጨርስ ስለህልሞም እያሰበች የመልስ ጉዞ ለማድረግ የቤተክርሲቲያን አጥር ግቢ ወጥተን ብዙም ሳንርቅ እኛ ሁለታችንም በህልማችን ያየናቸው ሽማጊሌ በትክክል እሳቸው ድንገት ከፊታችን ተደንቅረው መንገዳችንን ገቱት.እኔ ብዙም ባይደንቀኝም እናቴ ግን በድንዛዜ ሀውልት መስላ ነበር ባለችበት የቆመችው
-ሰውዬው ለእናቴ ድንጋጤ ብዙም ትኩረት ሳይሰጡ ጎንበስ ብለው እጃቸውን ጭንቅላቴ ላይ አሳርፈው በመዳበስ እይታቸውን ወደእናቴ አድርገው ‹‹ጌታ ችግርሽን ይፍታልሽ…እግዜያብሄር ለቅሶሽን ሰምቶል ››በማለት የብስራት ቃላቸውን አሰሟት
-ተአምር ነው፡፡እርሷ መላአክ ኖት…?
-አይ አይደለውም ሰው ነኝ፡፡ተራ ሰው ለሶስት ቀን በተከታታይ በህልሜ ሳያችሁ ነበር፡፡ህልሜን አምኜ እዚህ ስመጣ ደግሞ በአካል አገኘዋችሁ፡፡››
-እኔም አይቼዎታለው››
-በይ እንግዲህ የምኞትሽ ይሙላልሽ ?
-በህልሞት ምንም እንዲነግሩኝ አልተነገሮትም.››
-አይ ሁሉንም ለእሷ ነግሬያታለው..አንተ ብቻ አግኛትና ልጇን ደባብስላት ነው የተባልኩት፡፡……..ብለው አልፈውን መንገዳቸውን ሲቀጥሉ…እናቴ ከድንዛዜዋ ባና -እሺ እግዜር ይከተሎት..አለቻቸው
-አንቺንም ልጄ....ከእነልጅሽ እግዜያብሄር ይጠብቅሽ ፡፡ብለው ከእይታችን ተሰወሩብን
ከዛ ቡኃላ እናቴ ፍፁም ተረጋጋች
👍4
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_ሰባት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
ትምህርት ቤት ገባው፡፡መናገር ባልችልም የምማረው ከተናጋሪዎች ጋር ነበር፡፡አርግጥ ተማሪዎቹም ሆነ አስተማሪዎቹ ብዙም አይጥሙኝም፡፡ትምህርቱም እንደዛው ፡፡ግን ተማርልኝ ያለቺኝ እናቴ ስለሆነችና እሷ ያለቺኝን ነገር ሁሉ ተመቸኝም አልተመቸኝም …አስደሰተኝም ፤አስከፋኝም ማድረግ ስላለብኝ ነው ያደረኩት፡፡
አንደኛ ክፍል አንደኛ ሴሚስተር በከፍሉ ካሉት 56 ተማሪዎች 55ተኛ ደረጃ ወጣው ፡፡የበለጥኩት አንድ ልጅ በመጨረሻዎቹ የፈተና ቀኖች ትምህርት ቤት ተገኝቶ ዋናውን ፈተና መውሰድ ስላልቻለ እና ካርዱ ላይ የተቀመጠለት ውጤት ቴስት ላይ ያገኛቸው ውጤቶች ብቻ ነበሩ፡፡
እኔ ባመጣውት ውጤት ማንም አልተደነቀም ምክንያቱም ማሰብ እንደምችል እራሱ የሚያምን ሰው ጥቂት ነው፡፡ማሰብ ማይችል ሰው እንዴት መማር ይችላል ብለው ይገምታሉ…?፡፡ ካርዴን ይዤ መጥቼ ለእናቴ ስሰጣት እቤቱ ሙሉ ወዳጅ ዘመድ በተሰበሰበበት ነበር፡፡ልክ ድንበር ሊወር የመጣን የጠላት ወታደር ፊት ለፊት በጀግንነት ተፋልሞ በማሸነፍ የድል ብስራት ለወገኖቹ እንደሚያስር ወታደር ደረቴን በኩራት ገልብጬ…
-አይ ዝም ብለሽ እኮ ነው የምትለፊው…..እቤት ከነበሩት መካከል አንዱ ዘመድ የተናገረው ነበር..
-እንዴት ዝም ብዬ…?
-ትምህርት እኮ ለእሱ ይከብደዋል፡፡እንዲሁ ከልጆች ተቀላቅሎ ይዋል ብለሽ እንደሆነ ይገባናል፡፡ግን ማሰብ ያለብሽ ወደሁለተኛ ክፍል ለመዘዋወር ስንት አመት ይፈጅበታል የሚለውን ነው……?ሶስት……?አራት….…?
.
-ለእኔ ስሜት ሳይጨነቁ እንደአፌ አእምሮዬም ዝግና ዱልዱም መሆኑን እርግጠኛ ሆነው እናቴን የሚያሳቅቁበት መርዝ ንግግር ሰነዘሩ..
እናቴ ከተቀመጥኩበት ወደራሷ ስባኝ ጭኖቾ ላይ በማጋደም ጭንቅላቴን እየዳበሰች…
-ልጄ በአመቱ መጨረሻ ወደ ሁለተኛ ክፍል በበቂ ውጤት አልፎ ካልገባ እኔ ላይ ሳቁብኝ፡፡…አለቻቸው እሷም ልክ እንደእኔው ጀግና ልጅ እንዳለት እርግጠኛ በመሆን ደረቷን ነፍታ..
-አረ ተይ የማይሆነውን ….ብለው ወዲያውኑ ሳቃቸውን የለቀቁት በርከት ይሉ ነበር….እኔ ግን የእናቴ ንግግር ትንሿን አዕምሮዬን ሰንጥቆ ነበር የገባው፡፡‹በዓመቱ መጨረሻ ልጄ ወደ ሁለተኛ ክፍል ካላለፈ ሳቁብኝ›…ፃድቋ እናቴ ላይማ ማንም አይስቅባትም…..ወሰንኩ፡፡
-ማታ ብቻችንን ሆነን ደረቷ ላይ ተኝቼ ማስበው ወደ ሁለተኛ ክፍል ስለማለፍ ነበር፡፡
-ምን ማድረግ አለብኝ…?፡፡በአንደኛ ሲሚስተር እንዴት እንደተማርኩና …?እንዴት እንደተፈተንኩ…? አሰብኩ.. አስተማሪዎች ሲያስተምሩ አንድም ቀን አዳምጬያቸው አላውቅም…አንዳንድ ቀን በመስኮት አሻግሬ ሜዳ የሚጫወቱትን ልጆች ወይም ዛፍ ላይ አርፋ የምትዘምረዋ ወፍ ወይም በሰማይ ላይ የሚጓዘውን ደመና ስመለከት ነው ክፍለ ጊዜው የሚያልቀው፡፡አንዳንዴ ደግሞ ወረቀት ቀድና በምራቄ አለስልሼ ጆሮዬ ውስጥ ጠቀጥቃለው..
---አንድ ቀን ይሄንን ሳደርግ እጅ ከፍንጅ የያዘኝ አንድ መምህር..አንደበትህን እንደዘጋው ጆሮህንም እንዲደፍንልህ ትፈልጋለህ…ሲል ጠየቀኝ በመገረምና በንዴት አፍጥጦብኝ
ግንባሬን በመወዝወዝ‹‹አዎ…›› የሚል ምልክት አሳየውት
አማተበና‹‹አንተንስ ትልቁ አጋንንት ነው የተጠጋህ ››ብሎኝ ወደማስተማሩ ተመለሰ…..ከዛን ቀን ቡኃላ ጭራሽ የዛ ክፍል ተማሪ እንዳልሆንኩ በመቁጠር ረሳኝ … እኔም ተመቸኝ..፡፡
ስለዚህ አሁን በዓመቱ መጨረሻ እኚ ወሬኞች እናቴ ላይ እንዳይስቁባት..አስተማሪዎች የሚሉትን ትንሽ ትንሽም ቢሆን ማዳመጥ መጀመር አለብኝ ብዬ ወሰንኩ፡፡
የትምህርት ዘመኑ ተጠናቆ ..ሰኔ ሰላሳ መጥቶ የወላጆች በዓል ላይ ያልታሰበ ነገር ተከሰተ….ልዩ ተሸላሚ ሆኜ መድረክ ላይ ተጠራው.. ሰው ሁሉ የፀባይ ሽልማት መስሎት ነበር..ያው ድዳ በመሆኔ ተናግሬ መበጥበጥ ስለማልችል በተጨማሪም በፀባዬ ጠማማነትም የተነሳ ከልጆች ጋርም እንደማልገጥም ብዙዎች ስለሚያውቁ የፀባይ ሽልማትማ ይገባዋል… ብለው ነበር ያሰቡት፡፡
-የትምህርት ቤቱ ዳሪክተር ግን እኔን ስራቸው አቁመው ጭንቅላቴን ልክ እንደ አባት እየዳበሱ በአስገምጋሚ ሻካራ ድምፃቸው የትምህርት ቤቱን ግቢ ለሞሉት ተማሪዎቻቸውና ወላጆቻቸው መናገር ጀመሩ…
***
በ25 ዓመት የማስተማር ልምዴ እንዲህ አይነት ተአምር ገጥሞኝ አያውቅም፡፡ማመን አቅቶን ውጤቶቹን ሁሉ ደግመን ፈትሸን ነበር የሚገርመው ምንም እንከን አልተገኘባቸውም ፡፡በአንደኛ ሴሚስተር ከክፍሉ የመጨረሻውን ደረጃ ነበር የያዘው…
ኹ ..ሁሁሁ ብሎ ታደሚው ሁሉ አውካካ..
በዚህኛው ሴሚስተር ደግሞ አንደኛ ….ከሰባት ትምህርት ስድስቱን መቶ.... አንዱን ዘጠና ስምንት ነው ያመጣው፡፡አማካኝ ደረጃው 23ተኛ ደረጃ ፡፡እንዲህ አይነት ለውጥ በማምጣቱ ትምህርት ቤታችን እንዶኮራበት ወላጆቹም ልትኮሩበት ይገባችሆል..በቀጣይ በዚሁ እንዲቀጥልም አስፋላጊውን ድጋፍ አድርጉለት ..በማለት ከአቅሜ በላይ የሚከብድ መዝገበ ቃላት በሽልማት መልክ አሸከሙኝ››
መድረኩን ለቅቄ እየወረድኩ እናቴን አየዋት… ከአምስት ወራት በፊት ሳቁብኝ ብላቸው ወደነበሩ ወዳጆቾ ዞራ ቅዱስ የእርካታ ሳቅ እየሳቀችባቸው ነበር….እኔም በፈገግታ አገዝኳት።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_ሰባት
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
ትምህርት ቤት ገባው፡፡መናገር ባልችልም የምማረው ከተናጋሪዎች ጋር ነበር፡፡አርግጥ ተማሪዎቹም ሆነ አስተማሪዎቹ ብዙም አይጥሙኝም፡፡ትምህርቱም እንደዛው ፡፡ግን ተማርልኝ ያለቺኝ እናቴ ስለሆነችና እሷ ያለቺኝን ነገር ሁሉ ተመቸኝም አልተመቸኝም …አስደሰተኝም ፤አስከፋኝም ማድረግ ስላለብኝ ነው ያደረኩት፡፡
አንደኛ ክፍል አንደኛ ሴሚስተር በከፍሉ ካሉት 56 ተማሪዎች 55ተኛ ደረጃ ወጣው ፡፡የበለጥኩት አንድ ልጅ በመጨረሻዎቹ የፈተና ቀኖች ትምህርት ቤት ተገኝቶ ዋናውን ፈተና መውሰድ ስላልቻለ እና ካርዱ ላይ የተቀመጠለት ውጤት ቴስት ላይ ያገኛቸው ውጤቶች ብቻ ነበሩ፡፡
እኔ ባመጣውት ውጤት ማንም አልተደነቀም ምክንያቱም ማሰብ እንደምችል እራሱ የሚያምን ሰው ጥቂት ነው፡፡ማሰብ ማይችል ሰው እንዴት መማር ይችላል ብለው ይገምታሉ…?፡፡ ካርዴን ይዤ መጥቼ ለእናቴ ስሰጣት እቤቱ ሙሉ ወዳጅ ዘመድ በተሰበሰበበት ነበር፡፡ልክ ድንበር ሊወር የመጣን የጠላት ወታደር ፊት ለፊት በጀግንነት ተፋልሞ በማሸነፍ የድል ብስራት ለወገኖቹ እንደሚያስር ወታደር ደረቴን በኩራት ገልብጬ…
-አይ ዝም ብለሽ እኮ ነው የምትለፊው…..እቤት ከነበሩት መካከል አንዱ ዘመድ የተናገረው ነበር..
-እንዴት ዝም ብዬ…?
-ትምህርት እኮ ለእሱ ይከብደዋል፡፡እንዲሁ ከልጆች ተቀላቅሎ ይዋል ብለሽ እንደሆነ ይገባናል፡፡ግን ማሰብ ያለብሽ ወደሁለተኛ ክፍል ለመዘዋወር ስንት አመት ይፈጅበታል የሚለውን ነው……?ሶስት……?አራት….…?
.
-ለእኔ ስሜት ሳይጨነቁ እንደአፌ አእምሮዬም ዝግና ዱልዱም መሆኑን እርግጠኛ ሆነው እናቴን የሚያሳቅቁበት መርዝ ንግግር ሰነዘሩ..
እናቴ ከተቀመጥኩበት ወደራሷ ስባኝ ጭኖቾ ላይ በማጋደም ጭንቅላቴን እየዳበሰች…
-ልጄ በአመቱ መጨረሻ ወደ ሁለተኛ ክፍል በበቂ ውጤት አልፎ ካልገባ እኔ ላይ ሳቁብኝ፡፡…አለቻቸው እሷም ልክ እንደእኔው ጀግና ልጅ እንዳለት እርግጠኛ በመሆን ደረቷን ነፍታ..
-አረ ተይ የማይሆነውን ….ብለው ወዲያውኑ ሳቃቸውን የለቀቁት በርከት ይሉ ነበር….እኔ ግን የእናቴ ንግግር ትንሿን አዕምሮዬን ሰንጥቆ ነበር የገባው፡፡‹በዓመቱ መጨረሻ ልጄ ወደ ሁለተኛ ክፍል ካላለፈ ሳቁብኝ›…ፃድቋ እናቴ ላይማ ማንም አይስቅባትም…..ወሰንኩ፡፡
-ማታ ብቻችንን ሆነን ደረቷ ላይ ተኝቼ ማስበው ወደ ሁለተኛ ክፍል ስለማለፍ ነበር፡፡
-ምን ማድረግ አለብኝ…?፡፡በአንደኛ ሲሚስተር እንዴት እንደተማርኩና …?እንዴት እንደተፈተንኩ…? አሰብኩ.. አስተማሪዎች ሲያስተምሩ አንድም ቀን አዳምጬያቸው አላውቅም…አንዳንድ ቀን በመስኮት አሻግሬ ሜዳ የሚጫወቱትን ልጆች ወይም ዛፍ ላይ አርፋ የምትዘምረዋ ወፍ ወይም በሰማይ ላይ የሚጓዘውን ደመና ስመለከት ነው ክፍለ ጊዜው የሚያልቀው፡፡አንዳንዴ ደግሞ ወረቀት ቀድና በምራቄ አለስልሼ ጆሮዬ ውስጥ ጠቀጥቃለው..
---አንድ ቀን ይሄንን ሳደርግ እጅ ከፍንጅ የያዘኝ አንድ መምህር..አንደበትህን እንደዘጋው ጆሮህንም እንዲደፍንልህ ትፈልጋለህ…ሲል ጠየቀኝ በመገረምና በንዴት አፍጥጦብኝ
ግንባሬን በመወዝወዝ‹‹አዎ…›› የሚል ምልክት አሳየውት
አማተበና‹‹አንተንስ ትልቁ አጋንንት ነው የተጠጋህ ››ብሎኝ ወደማስተማሩ ተመለሰ…..ከዛን ቀን ቡኃላ ጭራሽ የዛ ክፍል ተማሪ እንዳልሆንኩ በመቁጠር ረሳኝ … እኔም ተመቸኝ..፡፡
ስለዚህ አሁን በዓመቱ መጨረሻ እኚ ወሬኞች እናቴ ላይ እንዳይስቁባት..አስተማሪዎች የሚሉትን ትንሽ ትንሽም ቢሆን ማዳመጥ መጀመር አለብኝ ብዬ ወሰንኩ፡፡
የትምህርት ዘመኑ ተጠናቆ ..ሰኔ ሰላሳ መጥቶ የወላጆች በዓል ላይ ያልታሰበ ነገር ተከሰተ….ልዩ ተሸላሚ ሆኜ መድረክ ላይ ተጠራው.. ሰው ሁሉ የፀባይ ሽልማት መስሎት ነበር..ያው ድዳ በመሆኔ ተናግሬ መበጥበጥ ስለማልችል በተጨማሪም በፀባዬ ጠማማነትም የተነሳ ከልጆች ጋርም እንደማልገጥም ብዙዎች ስለሚያውቁ የፀባይ ሽልማትማ ይገባዋል… ብለው ነበር ያሰቡት፡፡
-የትምህርት ቤቱ ዳሪክተር ግን እኔን ስራቸው አቁመው ጭንቅላቴን ልክ እንደ አባት እየዳበሱ በአስገምጋሚ ሻካራ ድምፃቸው የትምህርት ቤቱን ግቢ ለሞሉት ተማሪዎቻቸውና ወላጆቻቸው መናገር ጀመሩ…
***
በ25 ዓመት የማስተማር ልምዴ እንዲህ አይነት ተአምር ገጥሞኝ አያውቅም፡፡ማመን አቅቶን ውጤቶቹን ሁሉ ደግመን ፈትሸን ነበር የሚገርመው ምንም እንከን አልተገኘባቸውም ፡፡በአንደኛ ሴሚስተር ከክፍሉ የመጨረሻውን ደረጃ ነበር የያዘው…
ኹ ..ሁሁሁ ብሎ ታደሚው ሁሉ አውካካ..
በዚህኛው ሴሚስተር ደግሞ አንደኛ ….ከሰባት ትምህርት ስድስቱን መቶ.... አንዱን ዘጠና ስምንት ነው ያመጣው፡፡አማካኝ ደረጃው 23ተኛ ደረጃ ፡፡እንዲህ አይነት ለውጥ በማምጣቱ ትምህርት ቤታችን እንዶኮራበት ወላጆቹም ልትኮሩበት ይገባችሆል..በቀጣይ በዚሁ እንዲቀጥልም አስፋላጊውን ድጋፍ አድርጉለት ..በማለት ከአቅሜ በላይ የሚከብድ መዝገበ ቃላት በሽልማት መልክ አሸከሙኝ››
መድረኩን ለቅቄ እየወረድኩ እናቴን አየዋት… ከአምስት ወራት በፊት ሳቁብኝ ብላቸው ወደነበሩ ወዳጆቾ ዞራ ቅዱስ የእርካታ ሳቅ እየሳቀችባቸው ነበር….እኔም በፈገግታ አገዝኳት።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍7
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_ዘጠኝ
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ከአስር አመት ቡኃላ ማለቴ አንደበቴ ከተፈታ ቡኃላ ያለኝ ህይወት ከዛ በፊት ከነበረው ፍጽም በተቃራኒ መንገድ የተጓዘ ነበር፡፡
በተለይ አንደበቴ እንዲፈታና እንድናገር ምክንያት የሆነው የቤታችን የመዘረፍ ሙከራ እና እኔ እራሴንም ሆነ እናቴን ከጥቃት የታደኩበት ሁኔታ ቅጽበታዊ የአንድ ቀን ክስተት ብቻ ሆኖ አላለፈም ፡፡የህይወቴን አቅጣጫና መላ አመለካከቴንም ሙሉ በሙሉ ነው የቀየረው፡፡
ሌቦቹ ልምድ ያላቸው ደፋርና ጨካኝ ቢሆኑ ኖሮ የዛን ለሊት እኔና እናቴ አልቆልን ነበር ማለት ነው፡፡ወይ ሞተን ወይ ደግሞ አካላ ጎዶሎ ሆነን ነበር፡፡ከዛ ታሪክ የተማርኩት በዚህ አለም ላይ አሸናፊ ሆኖ ለመኖር ብልህነት ብቻ ሳይሆን የአካል ጥንካሬም ወሰኝ እንደሆነ ነው፡፡
ብዙውን ጊዜ ምሉዕ እና ስኬታማ የሆኑ ሰዎች የአዕምሮአዊና እና የአካላዊ ጥንካሬያቸው ምርጥ በሚባል የብቃት ደረጃ የሚገኝ መሆኑን ታሪክ ይመሰክራል ፡፡ያ መሆኑ ሰዎቹ በሚጓዙበት በህይወት መስመር ላይ የፊት መሪ ሆነው ለመመረጣቸው ባይመረጡም እንኳን እራሳቸውን በራሳቸው መሪ አድርጎ ለመሾም እና ለዛም የሚደግፎቸው በርካታ ሰዎች በዙሪያቸው ማሰለፍ የመቻላቸው ሚስጥር የነፍስ ልህቀት ቅኝታቸው እና የአካል ጥንካሬ ብርታታቸው እኩል ዳብሮ መገኘቱ …በማድረግ ብቃታቸው ላይ ሆነ ሌላው ማህበረሰብ ላይ ተፅዕኖ የማሳደር ሚስጥራዊ ሀይል እንደሚያጎናጽፋቸው ገና በጥዋቱ በአስር አመቴ ተገለፀልኝ፡፡እና ሰፈራችን የሚገኝ ቴኮንደ ማሰልጠኛ ቤት መማር እንደምፈልግ ለእናቴ የነገርኮት ወዲያውኑ ነበር፡፡ለምን ፈለከው . ..?ምን ያደርግልሀል..? ምናምን ብላ ሳትጨቀጭቀኝ..ወዲያው የሚከፈለውን ከፍላ ወስዳ እስመዘገበቺኝ፡፡እናቴ የእኔ ጀግና ፡፡
ታዲያ የዛ ውጤት 15 ዓመት ሲሞላኝ ደረቴ ወደፊት የተገለበጠ…ሆዴ እንደብረት ጠጥሮ ወደ ውስጥ የተጠቀለለ…የእጆቼ ጡንቻዎች ፈርጣማ ..ተፈጥሮ ከለገሰኝ ዘለግ ያለ ቁመት ጋር የሀያ አመት ጓረምሳ አስመስለኝ፡፡በአካልም ሆነ በአዕምሮ ከእኩዬቼ አንፃር በጣም በሚባል ደረጃ ቀድሜ አደኩ፡፡ በዚህ ምክንያት ይሁን በተፈጥሮ ባለኝ መስህብ በእንስቶች የፍቅር እይታ ውስጥ በቀላሉ እገባለው፡፡ይቀርቡኛል …ሊፈትኑኝ፡፡ሸሻቸዋለው… እንዳይጥሉኝ ፡፡
ሌላው ትምህርቴን በተመለከተ በቀላል ልፋት አስደማሚ ውጤት ማምጣት ለእኔ የሚወዱትን አስደሳች የካርታ ጫወታ የመጫወትን ያህል ቀላል ሲሆን ለሌላው ተመልካች በተለይ በቀን ስንት ሰዓት እንደማጠና ..?ምን ስሰራ እንደምውል..? ለሚያውቁ ሰዎች እና ጓደኞቼ አስደማሚ እና ግራ አጋቢ ነበር፡፡
‹በልጅነቱ እናቱ አብሾ አግታው ነው ጎበዝ የሆነው ›ብለው ሚያሙኝ እኩዬቼም ሆኑ የሰፈር አዛውንቶች እንዳሉም አውቃለው፡፡
***
ሌላው ባህሪዬ ከትምህርት ጉብዝናዬ ጋር የማይሄድ የማፊያነት ባህሪ ይታይብኝ የጀመረው ገና በጥዋቱ ነበር፡፡መጀመሪያ በእኔ መሪነት የሚንቀሳቀሱ ሶስትና አራት ልጆችን በማስተባበር ጥቃት የሚደርስባቸውን የሰፈር እና ሌሎች የማቀቸውን ሰዎች ከጥቃት በመከላከል ነበር የጀመርኩት፡፡እያደር ግን በትምህርት ቤቱ ስውር መንግስት ሆንኩ፡፡እኔ ያወጣውትን ህግ እንኳን ተማሪዎች አስተማሪዎች ወደውም ሆነ ፈርተው ይተገብሩታል፡፡
ግን ጉልበት አለኝ ብዬ በመታበይ ከመሬት ተነስቼ ሰውን አልጋጭም፡፡በማንም ላይ ከአስፈላጊው በላይ ጉልበትም ሆነ ጫና አልፈፅምም ፡፡ግን ተገቢውን እርምጃ በተገቢው ጊዜና መጠን ለመውሰድ ሰውዬው ማንም ይሁን ማንም አልፈረምም …ላቅማማምም፡፡
ኃይልን በተመለከተ አንድ ምክር ልስጣችሁ ፡፡የሆነ ስልጣን አለኝ ወይም አስተማማኝ ጉልብት አለኝ ብላችሁ ማንኛውንም የመጨረሻ ደካማ ነው የምትሉትን ሰውም ላይ ቢሆን የመጨረሻ ውን ተስፋ እስኪቆርጥ ድረስ አትቅጡትም … አትግፉትም ፡፡..ያንን ካደረጋቹ የራሳችሁን ጉድጓድ እየቆፈራችሁ መሆኑን እወቁት ፡፡ተስፋ የቆረጠ ድመት የነብር አንገት መቀንጠስ ቢያቅተው እንኳን የነብርን አይን ለማጥፋ አይሰንፍም፡፡
እና ምን ጊዜም ይሄ የሀይል አጠቃቀም ለእኔ መመሪያዬ ነው፡፡ያሸነፍኩትን በምን ያህል መጠን መቅጣትና መቼ ይቅር ማለት እንዳብኝ በጥንቃቄ አስብበታለው፡፡
ያው የትምህርት ቤቱ ስውር መንግስት ነኝ ብያችሁ የለ፡፡መጀመሪያ በዘፈቀደ ነበር ነገሮችን የምከውን የነበረው፡፡ዋናው ትኩረቴ የሆነ ታዛዥ ጦር ከኃላዬ ማሰለፌ እና በሚያውቁኝም (እጄን በቀመሱትም) ወይም በዝና ብቻ በሰሙትም ዘንድ መፈራቴ እና መከበሬ ነበር፡፡
በነገራችን ላይ በሄድኩበት ሁሉ የመከበርና እና የመደመጥ ሱስ አለብኝ፡፡ማንም ቢሆን በእድሜ እኩያዬ ይሁን ወይም ታላቄ ትኩረት እንዲነፍገኝ ወይም ዝቅ አድርጎ እንዲያኝ ፈጽሞ አልፈቅድም፡፡ሲያከብሩኝ ደስ ይለኛል፡፡አዎ ማንኛውም ሰው ከቻለ እየወደደ ቢያከብረኝ ደስ ይለኛል ካልሆነ ግን እየጠላኝም ቢሆን እንዲፈራኝና እንዲያከብረኝ ፈልጋለው፡፡በሚወዱኝም ሆነ በሚጠሉኝ ሰዎች እኩል መፈራትና መከበር ፍላጎቴ ነው፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_ዘጠኝ
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
:
...ከአስር አመት ቡኃላ ማለቴ አንደበቴ ከተፈታ ቡኃላ ያለኝ ህይወት ከዛ በፊት ከነበረው ፍጽም በተቃራኒ መንገድ የተጓዘ ነበር፡፡
በተለይ አንደበቴ እንዲፈታና እንድናገር ምክንያት የሆነው የቤታችን የመዘረፍ ሙከራ እና እኔ እራሴንም ሆነ እናቴን ከጥቃት የታደኩበት ሁኔታ ቅጽበታዊ የአንድ ቀን ክስተት ብቻ ሆኖ አላለፈም ፡፡የህይወቴን አቅጣጫና መላ አመለካከቴንም ሙሉ በሙሉ ነው የቀየረው፡፡
ሌቦቹ ልምድ ያላቸው ደፋርና ጨካኝ ቢሆኑ ኖሮ የዛን ለሊት እኔና እናቴ አልቆልን ነበር ማለት ነው፡፡ወይ ሞተን ወይ ደግሞ አካላ ጎዶሎ ሆነን ነበር፡፡ከዛ ታሪክ የተማርኩት በዚህ አለም ላይ አሸናፊ ሆኖ ለመኖር ብልህነት ብቻ ሳይሆን የአካል ጥንካሬም ወሰኝ እንደሆነ ነው፡፡
ብዙውን ጊዜ ምሉዕ እና ስኬታማ የሆኑ ሰዎች የአዕምሮአዊና እና የአካላዊ ጥንካሬያቸው ምርጥ በሚባል የብቃት ደረጃ የሚገኝ መሆኑን ታሪክ ይመሰክራል ፡፡ያ መሆኑ ሰዎቹ በሚጓዙበት በህይወት መስመር ላይ የፊት መሪ ሆነው ለመመረጣቸው ባይመረጡም እንኳን እራሳቸውን በራሳቸው መሪ አድርጎ ለመሾም እና ለዛም የሚደግፎቸው በርካታ ሰዎች በዙሪያቸው ማሰለፍ የመቻላቸው ሚስጥር የነፍስ ልህቀት ቅኝታቸው እና የአካል ጥንካሬ ብርታታቸው እኩል ዳብሮ መገኘቱ …በማድረግ ብቃታቸው ላይ ሆነ ሌላው ማህበረሰብ ላይ ተፅዕኖ የማሳደር ሚስጥራዊ ሀይል እንደሚያጎናጽፋቸው ገና በጥዋቱ በአስር አመቴ ተገለፀልኝ፡፡እና ሰፈራችን የሚገኝ ቴኮንደ ማሰልጠኛ ቤት መማር እንደምፈልግ ለእናቴ የነገርኮት ወዲያውኑ ነበር፡፡ለምን ፈለከው . ..?ምን ያደርግልሀል..? ምናምን ብላ ሳትጨቀጭቀኝ..ወዲያው የሚከፈለውን ከፍላ ወስዳ እስመዘገበቺኝ፡፡እናቴ የእኔ ጀግና ፡፡
ታዲያ የዛ ውጤት 15 ዓመት ሲሞላኝ ደረቴ ወደፊት የተገለበጠ…ሆዴ እንደብረት ጠጥሮ ወደ ውስጥ የተጠቀለለ…የእጆቼ ጡንቻዎች ፈርጣማ ..ተፈጥሮ ከለገሰኝ ዘለግ ያለ ቁመት ጋር የሀያ አመት ጓረምሳ አስመስለኝ፡፡በአካልም ሆነ በአዕምሮ ከእኩዬቼ አንፃር በጣም በሚባል ደረጃ ቀድሜ አደኩ፡፡ በዚህ ምክንያት ይሁን በተፈጥሮ ባለኝ መስህብ በእንስቶች የፍቅር እይታ ውስጥ በቀላሉ እገባለው፡፡ይቀርቡኛል …ሊፈትኑኝ፡፡ሸሻቸዋለው… እንዳይጥሉኝ ፡፡
ሌላው ትምህርቴን በተመለከተ በቀላል ልፋት አስደማሚ ውጤት ማምጣት ለእኔ የሚወዱትን አስደሳች የካርታ ጫወታ የመጫወትን ያህል ቀላል ሲሆን ለሌላው ተመልካች በተለይ በቀን ስንት ሰዓት እንደማጠና ..?ምን ስሰራ እንደምውል..? ለሚያውቁ ሰዎች እና ጓደኞቼ አስደማሚ እና ግራ አጋቢ ነበር፡፡
‹በልጅነቱ እናቱ አብሾ አግታው ነው ጎበዝ የሆነው ›ብለው ሚያሙኝ እኩዬቼም ሆኑ የሰፈር አዛውንቶች እንዳሉም አውቃለው፡፡
***
ሌላው ባህሪዬ ከትምህርት ጉብዝናዬ ጋር የማይሄድ የማፊያነት ባህሪ ይታይብኝ የጀመረው ገና በጥዋቱ ነበር፡፡መጀመሪያ በእኔ መሪነት የሚንቀሳቀሱ ሶስትና አራት ልጆችን በማስተባበር ጥቃት የሚደርስባቸውን የሰፈር እና ሌሎች የማቀቸውን ሰዎች ከጥቃት በመከላከል ነበር የጀመርኩት፡፡እያደር ግን በትምህርት ቤቱ ስውር መንግስት ሆንኩ፡፡እኔ ያወጣውትን ህግ እንኳን ተማሪዎች አስተማሪዎች ወደውም ሆነ ፈርተው ይተገብሩታል፡፡
ግን ጉልበት አለኝ ብዬ በመታበይ ከመሬት ተነስቼ ሰውን አልጋጭም፡፡በማንም ላይ ከአስፈላጊው በላይ ጉልበትም ሆነ ጫና አልፈፅምም ፡፡ግን ተገቢውን እርምጃ በተገቢው ጊዜና መጠን ለመውሰድ ሰውዬው ማንም ይሁን ማንም አልፈረምም …ላቅማማምም፡፡
ኃይልን በተመለከተ አንድ ምክር ልስጣችሁ ፡፡የሆነ ስልጣን አለኝ ወይም አስተማማኝ ጉልብት አለኝ ብላችሁ ማንኛውንም የመጨረሻ ደካማ ነው የምትሉትን ሰውም ላይ ቢሆን የመጨረሻ ውን ተስፋ እስኪቆርጥ ድረስ አትቅጡትም … አትግፉትም ፡፡..ያንን ካደረጋቹ የራሳችሁን ጉድጓድ እየቆፈራችሁ መሆኑን እወቁት ፡፡ተስፋ የቆረጠ ድመት የነብር አንገት መቀንጠስ ቢያቅተው እንኳን የነብርን አይን ለማጥፋ አይሰንፍም፡፡
እና ምን ጊዜም ይሄ የሀይል አጠቃቀም ለእኔ መመሪያዬ ነው፡፡ያሸነፍኩትን በምን ያህል መጠን መቅጣትና መቼ ይቅር ማለት እንዳብኝ በጥንቃቄ አስብበታለው፡፡
ያው የትምህርት ቤቱ ስውር መንግስት ነኝ ብያችሁ የለ፡፡መጀመሪያ በዘፈቀደ ነበር ነገሮችን የምከውን የነበረው፡፡ዋናው ትኩረቴ የሆነ ታዛዥ ጦር ከኃላዬ ማሰለፌ እና በሚያውቁኝም (እጄን በቀመሱትም) ወይም በዝና ብቻ በሰሙትም ዘንድ መፈራቴ እና መከበሬ ነበር፡፡
በነገራችን ላይ በሄድኩበት ሁሉ የመከበርና እና የመደመጥ ሱስ አለብኝ፡፡ማንም ቢሆን በእድሜ እኩያዬ ይሁን ወይም ታላቄ ትኩረት እንዲነፍገኝ ወይም ዝቅ አድርጎ እንዲያኝ ፈጽሞ አልፈቅድም፡፡ሲያከብሩኝ ደስ ይለኛል፡፡አዎ ማንኛውም ሰው ከቻለ እየወደደ ቢያከብረኝ ደስ ይለኛል ካልሆነ ግን እየጠላኝም ቢሆን እንዲፈራኝና እንዲያከብረኝ ፈልጋለው፡፡በሚወዱኝም ሆነ በሚጠሉኝ ሰዎች እኩል መፈራትና መከበር ፍላጎቴ ነው፡፡
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
#የመልስ_ጉዞ_ወደ_መነሻ
:
#ክፍል_አስር
:
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...አደኩ፡፡ጎረመስኩ፡፡ጉንጬ ላይ ብጉር አገጬ ላይ ፀጉር አበቀልኩ፡፡ያንንም ተከትሎ
➶➶➶
ፍቅሬ አስትንፋስህ ህይወቴ ነው፡፡ያንተ መኖር ደግሞ ለእኔ ብቸኛ የመኖር ዓላማዬ፡፡አንተ ፀሀዬ ነህ፡፡ እንጦጦ ተራራ ላይ በበቀለ አረንጎዴ ሳር ላይ በጀርባ ተንጋለው ከጥዋት ሦስት ሰዓት አካባቢ የሚሞቋት ሰውነትን የምታፍታታ፤አዕምሮን የምታነቃቃ፤የቆዳን ቀለም የምታፈካ ምጥን የእግዜር ፀሀይ፡፡ አዎ አንተ እንደዛ ነህ፡፡ሙሉ ፀሀይ ከእነግለቷ፤ ሙሉ ፀሀይ ከነኩነቷ ፡፡ከአንተ ሙቀት ተሸርፎ አኔ ጋር የሚደርሰው ሙቀት ፍፅም ያኖረኛል…ፍፅም ያፈካኛል፡፡
እንደእኔው ፈገግታህን ለማድነቅና ከዛም አለፍ ሲል በሙቀትህ ለመቅለጥ በመፈለግ በየእለቱ በዙሪያህ ሲያንዣብቡ የሚውሉ የትምህርት ቤታችን ቆነጃጅቶች እንዳሉ አውቃለው፡፡ግን ደግሞ አንዳቸውም በእኔ መጠን ውብ እንዳልሆኑ በእኔ መጠንም አንተን አንደማያፈቅሩ በእርግጠኝነት አውቃለው፡፡ባውቅም ዳሩ ተረጋግቼ መቀመጥ አልቻልኩም ፡፡..ልቤ በቅናት ያራል….ውስጤ እርብሽብሽ ይላል፡፡አንዳንዴ የሆነ ሽጉጥ ፈልጌ በእየእለቱ አንትን በሙሉ አይኗ ለማየት የምትደፍርን ማንኛዋንም ልጅ-አገረድ ግንባሯን ብቀነድባት ደስታዬ ነው፡፡ግን ያንንነ ለማድረግ ችሎታውም ሆነ ድፍረቱ ለጊዜው የለኝም፡፡በቅርብ ግን አምላክ ኃይሉን እንደሚያጎናፅፈኝ አምናለው..እናም የዛን ጊዜ አደርገዋለው፡፡ለአንተ ስል ከተማ አቃጥላለው፤ ለአንተ ስል ሺ ሰው ገድላለው…ለአንተ ስል እራሴን ከ20 ኛው ፎቅ ላይ ልወረውርም ችላለው…ለአንተ ስል የማላደርገወ ነገረ የለም…አስፈላጊ ከሆነ ለአንተ ስል አንተ ራስህንም መግደል ችላለው፡፡
ጊዜው ደርሷ ሁሉን ማድረግ እስክችል ግን አንተን የመጠበቅ አደራውን ለአንተው ለራስህ ሰጥቼያለው፡፡ የእኔ ጀግና ሴቶችን በተመለከተህ ባለህ አቋም ታኮራኛለህ እናም በዚሁ ቀጥል፡፡ ለአንዳቸውም ፊት አትስጣቸው፤ለአንዷም የልብህን ወርቃማ በር አትክፈትላት…የትኛዋም ብትሆን በብሩህ አይኖችህ አይታ ውስጥ አትግባ…ክንዶችህ የማንኛዋንም ወገብ ለማቀፍ አይሞክሩ …ወለላ ማር የሚንጠባጠብባቸው ሚመስሉ ከንፈሮችህ የማንኛዋም ቆርፋዳ ከንፈር ላይ አይረፍ …ቅዱስ ትንፋሽህን የትኛዋም ሄዋን ከእራሷ ሙትና ደካማ ትንፋሽ ጋር ቀይጣ ወደውስጦ ለመሳብ እድል አታግኝ ፡፡…በማንም ሴት ቀልድ ጥርሶችህ ተፈልቅቀው ፈገግታህ እንዳይረጭ…፡፡ለአንተ የምገባህ እኔ ነኝ..ከጎንህ አጥንት ተፈልቅቄ የተፈጠርኩ ሄዋንህ…ብትረግጠኝ ማይቆረቁረኝ፤ ብትገለኝ ቂም ማሊዝብ፡፡ብታቅፈኝ ማልጎረብጥህ ብትሰመኝ የማስደስትህ፡፡እኔ ለአንተ ጌጥህ እኔ ለአንተ ክብርህ ነኝ …፡፡በፈለከው ደቂቃ ጥራኝ በርሬ ወዲያው መጣለው፡፡ያሰኘህ ቦታ ቅጠረኝ ሲኦልም ቢሆን እገኛለው፡፡ ………..
***
ይሄ አስራ አምስት አመትና የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ እያለው ከክፍሌ ልጅ የተፃፈልኝ የመጀመሪያው የፍቅር ደብዳቤዬ ነው፡፡ከዛ ቡኃላ ያለውን የአፍላነት የፍቅር መሳሳቡንና የስሜት መላተሙን አትጠይቁኝ ፡፡ ይሄንን ለእናንተ እንደምሳሌ መናገር የፈለኩት እያደኩ ስመጣ ምን ያህል ማራኪ ወንዳ ወንድ እና ተፈቃሪ ወጣት መሆኔን እንድትገዘቡልኝ ስለፈለኩ ነው።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
:
#ክፍል_አስር
:
:
✍ደራሲ -ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
:
:
...አደኩ፡፡ጎረመስኩ፡፡ጉንጬ ላይ ብጉር አገጬ ላይ ፀጉር አበቀልኩ፡፡ያንንም ተከትሎ
➶➶➶
ፍቅሬ አስትንፋስህ ህይወቴ ነው፡፡ያንተ መኖር ደግሞ ለእኔ ብቸኛ የመኖር ዓላማዬ፡፡አንተ ፀሀዬ ነህ፡፡ እንጦጦ ተራራ ላይ በበቀለ አረንጎዴ ሳር ላይ በጀርባ ተንጋለው ከጥዋት ሦስት ሰዓት አካባቢ የሚሞቋት ሰውነትን የምታፍታታ፤አዕምሮን የምታነቃቃ፤የቆዳን ቀለም የምታፈካ ምጥን የእግዜር ፀሀይ፡፡ አዎ አንተ እንደዛ ነህ፡፡ሙሉ ፀሀይ ከእነግለቷ፤ ሙሉ ፀሀይ ከነኩነቷ ፡፡ከአንተ ሙቀት ተሸርፎ አኔ ጋር የሚደርሰው ሙቀት ፍፅም ያኖረኛል…ፍፅም ያፈካኛል፡፡
እንደእኔው ፈገግታህን ለማድነቅና ከዛም አለፍ ሲል በሙቀትህ ለመቅለጥ በመፈለግ በየእለቱ በዙሪያህ ሲያንዣብቡ የሚውሉ የትምህርት ቤታችን ቆነጃጅቶች እንዳሉ አውቃለው፡፡ግን ደግሞ አንዳቸውም በእኔ መጠን ውብ እንዳልሆኑ በእኔ መጠንም አንተን አንደማያፈቅሩ በእርግጠኝነት አውቃለው፡፡ባውቅም ዳሩ ተረጋግቼ መቀመጥ አልቻልኩም ፡፡..ልቤ በቅናት ያራል….ውስጤ እርብሽብሽ ይላል፡፡አንዳንዴ የሆነ ሽጉጥ ፈልጌ በእየእለቱ አንትን በሙሉ አይኗ ለማየት የምትደፍርን ማንኛዋንም ልጅ-አገረድ ግንባሯን ብቀነድባት ደስታዬ ነው፡፡ግን ያንንነ ለማድረግ ችሎታውም ሆነ ድፍረቱ ለጊዜው የለኝም፡፡በቅርብ ግን አምላክ ኃይሉን እንደሚያጎናፅፈኝ አምናለው..እናም የዛን ጊዜ አደርገዋለው፡፡ለአንተ ስል ከተማ አቃጥላለው፤ ለአንተ ስል ሺ ሰው ገድላለው…ለአንተ ስል እራሴን ከ20 ኛው ፎቅ ላይ ልወረውርም ችላለው…ለአንተ ስል የማላደርገወ ነገረ የለም…አስፈላጊ ከሆነ ለአንተ ስል አንተ ራስህንም መግደል ችላለው፡፡
ጊዜው ደርሷ ሁሉን ማድረግ እስክችል ግን አንተን የመጠበቅ አደራውን ለአንተው ለራስህ ሰጥቼያለው፡፡ የእኔ ጀግና ሴቶችን በተመለከተህ ባለህ አቋም ታኮራኛለህ እናም በዚሁ ቀጥል፡፡ ለአንዳቸውም ፊት አትስጣቸው፤ለአንዷም የልብህን ወርቃማ በር አትክፈትላት…የትኛዋም ብትሆን በብሩህ አይኖችህ አይታ ውስጥ አትግባ…ክንዶችህ የማንኛዋንም ወገብ ለማቀፍ አይሞክሩ …ወለላ ማር የሚንጠባጠብባቸው ሚመስሉ ከንፈሮችህ የማንኛዋም ቆርፋዳ ከንፈር ላይ አይረፍ …ቅዱስ ትንፋሽህን የትኛዋም ሄዋን ከእራሷ ሙትና ደካማ ትንፋሽ ጋር ቀይጣ ወደውስጦ ለመሳብ እድል አታግኝ ፡፡…በማንም ሴት ቀልድ ጥርሶችህ ተፈልቅቀው ፈገግታህ እንዳይረጭ…፡፡ለአንተ የምገባህ እኔ ነኝ..ከጎንህ አጥንት ተፈልቅቄ የተፈጠርኩ ሄዋንህ…ብትረግጠኝ ማይቆረቁረኝ፤ ብትገለኝ ቂም ማሊዝብ፡፡ብታቅፈኝ ማልጎረብጥህ ብትሰመኝ የማስደስትህ፡፡እኔ ለአንተ ጌጥህ እኔ ለአንተ ክብርህ ነኝ …፡፡በፈለከው ደቂቃ ጥራኝ በርሬ ወዲያው መጣለው፡፡ያሰኘህ ቦታ ቅጠረኝ ሲኦልም ቢሆን እገኛለው፡፡ ………..
***
ይሄ አስራ አምስት አመትና የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ እያለው ከክፍሌ ልጅ የተፃፈልኝ የመጀመሪያው የፍቅር ደብዳቤዬ ነው፡፡ከዛ ቡኃላ ያለውን የአፍላነት የፍቅር መሳሳቡንና የስሜት መላተሙን አትጠይቁኝ ፡፡ ይሄንን ለእናንተ እንደምሳሌ መናገር የፈለኩት እያደኩ ስመጣ ምን ያህል ማራኪ ወንዳ ወንድ እና ተፈቃሪ ወጣት መሆኔን እንድትገዘቡልኝ ስለፈለኩ ነው።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍👍 ማድረግ እንዳይረሳ
ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4