አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ዝግመተ_ለውጥ


#በአሌክስ_አብርሃም


...እንዲሁ ስለመምሬ እና ለትዳር ስላሰቡልኝ ልጅ እያሰብኩ የያዝኩትን ጋዜጣ መቃኘት ጀመርኩ፡፡.

በደማቅ ጥቁር ቀለም፣ “በማኅበር ተደራጅተው ጫት የሚያመርቱ አርሶ አደሮች ኑሯችን
ተለውጧል አሉ...” ይላል፡፡

ወረድ ብሎ፣ “አንዳንድ የማኅበሩ አባላት “ጫት በመሸጥ አይሱዙ መኪና ገዝተናል፣ ልጆቻችንንም
ከተማ ልከን እያስተማርን ነው ሲሉ ገልፀዋል” ከጽሑፉ ስር አይሱዙ መኪና ተደግፈው ፎቶ
የተነሱ አርሶ እደር ምስል ይታያል፡፡

ወረድ ብሎ ሌላ አርዕስት፣

አንድ አይሱዙ መኪና ሃያ ሜትር ጥልቀት ያለው ገደል ውስጥ ገብቶ ከላይ ጭኗቸው የነበሩ
ሰባት ሰዎች ሞቱ፡፡ ከሟቾቹ አራቱ ከገጠር ከተማ እየተመላለሱ የሚማሩ ተማሪዎች ሲሆኑ
ፖሊስ የአደጋው መንስዔ ሹፌሩ ጫት እየቃመ ማሽከርከሩ ነው ብሏል !"

ጋዜጣውን እጥፌ ሰፈራችንን ማየት ጀመርኩ፡፡ ቅድስት ቀይ የእራት ልብስ ለብሳ እቃ ታጥባለች፧እያንጎራጎረች፣ “በሰባራ ፎሌ ውሀ አያጠለቅም" አይ ቅድስት ! እንደኛ ሰፈር ሴት የባከነበት መንደር ያለ አይመስለኝም፡፡ ቆንጆ ናት 'ሞዴል' የመሆን ፅኑ ፍላጎት ነበራት፡፡ እንደውም የሰፈር ልጆች ሲፎግሯት፣ “ውበት ውጪያዊና ውስጣዊ ነው' ሲሉ ሰምታ ውስጣዊ ውበቷን ለማየት
እልትራሳውንድ ተነሳች” ይሏታል፡፡ ሰታንጎራጉር እየሰማኋት የድምጿ ማማር ተገረምኩ፤
“ወይ ይህቺ አገር ዘፋኞቿ በየማጀቱ እቃ እያጠቡ እቃ አጣቢዎቿ በየአደባባዩ እንዝፈን እያሉ ያደነቁሩናል" አልኩ ለራሴ፡፡ የቄሳርን ለእግዜር፡ የእግዜርን ለእግዚሃር፡፡

የመንደራችን የአንድ እሁድ ውሎ ከሞላ ጎደል እንደሚከተለው ነው:: ከጧቱ 12፡00 ሰዓት
አልማዝ የምትባለው ጎረቤታችን በሯ ላይ ስለተጣለው ድግምት ታማርራለች፣ ትራገማለች፡
ጠበል ታርከፈክፋለች፡፡ ድግምት በመጣል የሚጠረጠሩ ጎረቤቶቿን ታሸሙራለች፣ “እችኑ ኑሮ
ብለዋት...” እያለች፣ ብዙ ጊዜ የሞተ እይጥ ነው በሯ ላይ ተጥሎ የሚገኘው:

ከ 12፡30 እስከ ጧቱ 2፡00 ሰዓት እማማ ዘብይደሩ ጭንቅሎ የተባለውን የልጅ ልጃቸውን
ይረግማሉ፣ ይሳደባሉ፣ ይውገራሉ፡፡ አንዳንዴ ወገራው ሲበዛ ገላጋዮች ይገባሉ፡፡ “ባጭር ቅር….ይሉትና ሲታመም ሆስፒታል ለሆስፒታል አዝለውት ይዞራሉ፡፡
ከሁለት ሰዓት እስከ አራት ሰዓት የመንደሩ ልጆች እኔ ቤት ፊት ለፊት ያለች (ሰርቪስ ቤት እንኳን
የማታቆም) ቢጢቃ ሜዳ ላይ ኳስ ይራገጣሉ፡፡ የሚያስነሱት አቧራ ልጆቹን ስለሚሸፍናቸው
እንደ ህልም ነው ብዥ ብለው የሚታዩት፡፡

ከሚጫወቱት ልጆች መሃል ጭንቅሎ (የእማማ ዘብይደሩ የልጅ ልጅ)፤ ሃይለሚካኤል 'አረቡ'
(የእማማ የውብዳር የልጅ ልጅ)፣ ሙስጠፋ (የእማማ ዘሃራ የልጅ ልጅ)፣ ሲቲና ወንዳወንድ ሰለሆነች 'ከቤ' ይሏታል (የነማማ ትርሃስ የልጅ ልጅ ናት)፤ ከላይ ከተዘረዘረው የዘር ሃረግ
እንደሚታየው መንደራችን አንድ እናት' የሚባል ትውልድ ገድፏል፣ አባት የሚባል ሃረግ ዘሏል
ሕፃናቱ ከአያቶቻቸው ጋር ነው ያደጉት፡፡ ያውም አቅም ከሌላቸው ደሃና እቅመ ደካሚ ባልቴት
አያቶቻቸው ጋር! እናቶቻቸው የት ሄዱ? አባቶቻቸውን ምን በላቸው?' ቢባል መልሱ ከሁለት
ጉዳዮች አያልፍም፡፡ እንድም ወልደው ለእናቶቻቸው እየሰጡ አረብ እገር ሄደዋል፡ አልያን
በኤችአይቪ አልቀዋል፡፡ የመንደራችን እውነታ ነው ይሄ !! ደግሞ ሕፃናቱ የተመካከሩ ይመስል በየምክንያቱ ሲጣሱና ሲነታረኩ የሁሉም መሃላ አንድ ዓይነት፣ እናቴ ትሙት !” የሚል ነው፡፡

ልክ ከአራት ሰዓት እስከ አምስት ሰዓት፣ ሁላቱ የመንደራችን እንጀራ ሻጮች ሙሉና ዝናሽ. ዱላ ቀረሽ ስድድብ ይጀምራሉ፡፡ በደንበኛ መቀማማት ነው የሚጣሱት፣

“ለማያውቅሽ ታጠኚ..ደግሞ ሙያ እንዳለው ሰው:: ማየት የተሳነው እንጀራ እየጠፈጠፍሽ.
እኩል ታወሪያለሽ…"

“ኤጅ እባከሽ…እኔ ሙሉ በወፍጮ ቤት ጥራጊ አይደለም ደንበኞቼን የማስተናግደው፣ ጥርት
ባለ ጤፍ ጥር…ት”

“ሂሂሂሂሂ መጣፈጡ ቀርቶ እጄን በሰቀቀኝ አሉ እትዬ አሰለፍ፣ ጥራቱ ቀርቶብሽ ቡሃቃሽን
በወር እንዴ እንኳን ባጠብሽው:: ሰዉን ሁሉ በሆድ ቁርጠት ጨረሽው” ትላለች ዝናሽ። የሙሉ
ደንበኛ ስለሆንኩ በዚህ ኣባባሏ ሆዴ ይጮሃል፣ ..ኡ... ወር ሙሉ የማይታጠብ ቡሃቓ እቺ
ስድድብ ደንበኛን ለማስከዳት ወሳኝ የቃላት ጦርነታቸው ናት፡፡

ልክ አምስት ሰዓት ሲሆን እማማ መጣፈጥና ስንቅነሽ ቡና ይጠራራሉ፡፡ ወደ ስድስት ሰዓት
ጀሚላ የቅንድቧን ኩል ጆሮና ጆሯዋ ጥግ ድረስ ተኩሳ በስልኳ እያወራች ወደላይ ትጣደፋለት፡
ሃቢቢ መጣሁ ወጥቻለሁ” እያለች፡፡ ኣፍንጫ የሚሰነፍጥ ሽቶዋ መንደሩን ያውደዋል፡፡ ጀሚላ ስታልፍ ጥርኝ ያለፈች ነው የሚመስለው:: የታከከችው ነገር ሁሉ ሽቶ ሽቶ፣ መቼም ሃቢቢዩ
የአፍንጫ መሸፈኛ ማስካ ያደረገ ሰው መሆን አለበት፡፡

ይሄን ሁሉ ሳይ ይከፋኛል። ብቸኝነት ይጫጫነኛል፡፡ ከወንዙ ተገንጥሎ ኩሬ ውስጥ እንደተኳታሪ ውሃ እዛው የምሻግት አልያም የተቀመጥኩበት በትነት የማልቅ ነገር መስሎ ነው የሚሰማኝ

ይሄን…የተረገመ እሁድ ወደዛ አልቆ ሥራዩ በገባሁ ! ለነገሩ ከእሁድ ይሻላል ብዬ እንጂ ሥራዬም ሠልችቶኛል፡፡ የባንክ ሠራተኛ ነኝ፡፡ ብዙ ሰዎች የባንክ ሠራተኛ መሆኔን እንደትልቅ እና አስደሳች ሥራ እድርገው ሲያወሩ ይገርመኛል፡፡ ለእኔ የባንክ ሥራ በምድር ላይ ካሉ አስከፊ ሥራዎች
ሁሉ አስከፊው ይመስለኛል፡፡ እንደውም ለሰው ሳይሆን ለሮቦቶች የሚስማማ ሥራ ቢኖር የባንክ ሥራ ነው እያልኩ አስባለሁ፡፡

አንድ አይነት ቅርፅ ያላቸው ብር ዮሚባሉ መርገምቶችን መቁጠር፡፡ አራት ዓመት ሙሉ
ቆጠርኳቸው..ኤጭ ድፍን አገር የሚራኮትለት ብር ለእኔ አንዳች ቆሻሻ ነገር መስሎ ነው
የሚታየኝ፡፡ ብር ይሸታል፡፡ ካላመናችሁ ወደ ኣፍንጫችሁ አስጠጉና ሞክሩት፡፡ እንደ ብር
መጥፎ ሽታ ያለው ነገር ምን አለ ? ለነገሩ የዘንድሮ ብር ላሸትተውም ብትሉ አፍንጫችሁ ላይ
ላይደርሰ ያልቃል ሰላቢ ነገር ነው::

ምስላቸው ብር ኖት ላይ ያሉት ሰዎች ከመኖር ብዛት የቢሮ ባልደረባ መስለውኛል፡፡ ደግሞ
አልወዳቸውም፡፡ ለምሳሌ አንድ ብር ኖት ላይ ምስሉ ያላውን ሰው መንገድ ላይ ባገኘው ገላምምጬው የማልፍ ይመስለኛል፡፡ አስር ብር ላይ ያለችው ሴትማ ስታበሳጨኝ፤
የሆነች ነገረኛ ነገር፡፡ በደንብ አይታችኋታል? ስፌት የምትሰፋ ትመስላለት እንጂ ጆሮዋን አቁማ
ነገር የምትሰማ እኮ ነው የምትመስለው፡፡ ደግሞ ፊቷ ላይ የአሽሙር ፈገግታ አለ፡፡ ከሁሉም
ከሁሉም የሚያበሳጨኝ ነገር ደግሞ ከንፈሯ ! የከንፈሯ ማማር የሰብለን ከንፈር እኮ ነው
የሚመስለው !! ከነስፌቷ እጎኗ ላለው አንበሳ ነበር መስጠት !!

ባንክ ቤት ስትሰሩ ስጋችሁ በሱፍ ተጀቡኖ ወሩ መጨረሻ ላይ የሱፍ ቆሎ መግዣ እንኳን የማይተርፋችሁ መናጢ ደሃ መሆናችሁን ብዙ ሰው አይረዳም፡፡ ቁጥርና ስጋት ባንድ ላይ
የሚኖሩት ባንክ ቤት ውስጥ ነው፡፡ ብር ስትቆጥሩ በስጋት ነው:: አንዱን የብር ኖት ሌላ የተደራረበ እየመሰላችሁ በፍትጊያ ፍዳውን ታበሱታላችሁ፡፡ በዛ ላይ ሰው ለብር ያለውን ሟችነት፣ ስግብግብነት፣ ደግነትም ጭምር ትታዘባላችሁ፡፡
👍321👎1👏1🎉1
#ፈንዲሻ_ሲቆሎት_ድምፅ #ሲሰሉት_ድምፅ


#በአሌክስ_አብርሃም


የአንድ ደቂቃ የህሊና ጸሎት አድርገን እንደተቀመጥን፤ ፕሮግራሙ ቶሎ እንዲያበቃ ሌላ የህሊና ጸሎት ጀመርኩ፡፡ ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀንን ለማከበር የክፍለ ከተማው የሴቶች ሊግ ባዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ተገኝቻለሁ፡፡

ሊጉ በመሥሪያ ቤታችን በኩል ግዳጅ የተቀላቀለበት ጥሪ አቅርቦልን አለቃዬ ሂድ !" ስላለኝ
የቀበሌው አዳራሽ ውስጥ ተገኝቻለሁ። ያውም ቅዳሜን በሚያክል ቀን ከሰዓት!! ሰኔና ሰኞ
ገጥሞብኝ፡፡

አሁን ደግሞ የከፍለ ከተማችን የሕፃናትና ሴቶች ፑል ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ደርባቤ በላቸው
እንስራውን ሰብሮ ወሰዳት ልጅቱን የሚል ምርጥ ግጥም ያቀርቡልናል…" አለ ጉጉት የመሰለው መድረክ አስተዋዋቂ፡፡ አፉ ላይ የደቀነውን ማይክሮፎን ድምፅ ማጉላቱን የተጠራጠረ ይመስል በጣም እየጮኸ ነው የሚናገረው::

ቀጠለ "ወ/ሮ ደርባቤ ለክፍለ ከተማችን፣ ብሎም ለከተማችን፣ ብሎም ለኢትዮጵያ ሴቶች፣
ብሎም ለአፍሪካ ሴቶች ታላቅ ምሳሌ የሚሆኑ የዘርፈ ብዙ ሙያዎች፣ ተሰጥኦዎች፣ ትምህርቶች፣ስልጣኖች ባለቤት ናቸው” አለና፣ “…እስቲ ወ/ሮ ደርባቢን ወደ መድረክ…”

...ቿ..ቿ...ቿ..

ጥልፍ ቀሚስ የለበሱትና አንዳንድ ልማታዊ ዝግጅቶች ላይ ልማታዊ ግጥም በማቅረብ የሚታወቁት
ወ/ሮ ደርባቤ መድረክ ላይ ቆመው በፈገግታ ለሕዝቡ ጎንበስ ቀና እያሉ ምስጋና ይሁን ሰላምታ
ያለየለት ግማሽ ስግደት አቀረቡ፡፡ ግጥሙን ሊያቀርቡ ነው ብለን ፀጥ ስንል አስተዋዋቂው
ማዋደዱን ቀጠለ፣ “….ብታምኑም ባታምኑም ወ/ሮ ደርባቤ ይሄን ዝግጅት አስመልከቶ ግጥም
እንድትፅፍልን የነገርናት (አንች አላት) ትላንት ዘጠኝ ሰዓት ነው፡፡ ይገርማችኋል ሌሊቱን ስትፅፍ
አድራ ጧት ስደውልላት በስልክ ግጥሙን አነበበችልኝ…'ወይ መባረክ' ነው ያልኩት።( በሕዝብ
ስልክ ስምንት ገፅ ግጥም እያነበቡ አላየንም ባርኮት)፡፡

“...የግጥሙን ጥልቀት እና ውበት ራሳችሁ ታዘቡት እስቲ ለዚህች ብርቱ ሴት ሞቅ ያላ ጭብጨባ…" ብሎ ጭብጨባውን ራሱ ጀመረው፡፡ ማይኩን በሌላኛው እጁ ሲጠፈጥፈው አዳራሹ ጓጓጓ.. በሚል ልጆሮ የሚቀፍ እስቅያሚ ድምፅ ተሞላ፡፡ ከታዳሚው የተንቦጫረቀ ደካማ ጭብጨባ ጋር ተዳምሮ ጓጓታው በቀላል የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች የታጀበ የከባድ መሳሪያ ድምፅ ነበር የሚመስለው፡፡

ብዙው ታዳሚ በየእጁ ፈንዲሻ እና ለስላሳ ይዞ ስለነበረ ማጨብጨብ አልቻለም እንጂ በጭብጨባማ የእኛን ኮፍለ ከተማ ሴቶች ሊግ ጽሕፈት ቤት ሰራተኞች ማን ብሏቸው::በተለይ እጃቸው ባዶ ሲሆን የሚያጨበጭቡት ጭብጨባ ቢሾፍቱ ይሰማል፡፡ እጃቸው ባዶ ሲሆን ለዜና ያጨበጭባሉ፣ ለሪፖርት ያጨበጭባሉ፣ የቀበሌው ሊቀመንበር ሲያስነጥሱ ሁሉ
ያጨበጭባሉ፣ እጃቸው ሞላ ካለች ግን ጠቅላይ ሚንስትራችን ቢዘፍኑም አያጨበጭቡም
እንዳንዴ ታዲያ ጭብጨባዎች ሲቀንሱ ኢኮኖሚያችን ያደገ ይመስለኛል፡፡

ቀጠለ አስተዋዋቂው (ወ..ይ ዛሬ) "ወ/ሮ ደርባቤ.ገጣሚ ብቻ አይደሉም፤ የታሪክ ተመራማሪም
ናቸው፡፡ (ወ/ሮ ደርባቤ ቆመው በቁማቸው ገድላቸው ሲለፈፍ በፈገግታ ያዳምጣሉ )..ከፍተኛ
አድናቆት ያተረፈውንና የከፍላ ከተማችን የእድገት ማራቶን ሩጫ ከዘመነ ደርግ ውድቀት ቀኋላ' የሚለውን መጽሐፍ ጨምሮ አራት የግጥም መጻሕፍትን አሳትመዋል፤ ይሄን ያህል
ካልኩ እንዳላሰለቻችሁ ወደ ወ/ሮ ደርሳቤ ልምራችሁ...” ብሎ ማይኩን በአክብሮት ለሴትዬዋ
አቀበላት፡፡ (እፎይ! አንድ አዛ ለቀቅ ይላሱ እማማ ሩቅያ ሲተርቱ)

..ማይኩን ተቀብላ ጓ...ጓ አደረገችና (የፈረደበት ማይክ ተጠፍጥፎም፣ ያወሩትን ሁሉ ተቀብሎ አጉልቶም እሳዘነኝ)፡፡ እ..እኔ እንኳን የተባለውን ያህል ነኝ ብዬ አላምንም.፣ ምከንያቱም እንደ እኔ ዕድሉን ቢያገኙ እንኳን ኢትዮጵያን ዓለምን ጉድ የሚያስብሉ ሴቶች ከእናንተ መሀል አሉ ብዬ ስለማምን ነው…" አለች ወይዘሮ ደርባቤ፡፡

ጭብጨባ…! ቿቿቿቿቿቿቿቿቿ (ፈንዲሻው አለቀ ባአንዴ ጭብጨባው ደመቀኮ)
ከጎኔ የተቀመጠች ሴት “እውነት ነው" ብላ ጮኸት፡፡ (ዓለምን 'ጉድ' ከሚያስብሉት ሴቶች
መሐል እንዷ ሳትሆን አትቀርም፡፡ ዞር ብዬ ሳያት በግራ እጇ ሞባይል ስልኳን፣ በቀኟ፣ መዳፏ
እስኪወጣጠር የዘገነችውን ፈንዲሻ ይዛ በስሜት ወደ መድረኩ እያየች ቁጭ ብድግ ትላለች፡፡
..ከፈንዲሻው ኮርሽም አደረገችለት፡፡)

ሴትዮዋ ግጥሟን ከማቅረቧ በፊት ሰላሳ ደቂቓ አወራች፡፡…እንዴት የወንዶችን ተፅዕኖ ተቋቁማ ታላቅ ገጣሚ' ለመሆን እንደበቃች፣ ሴቶች የርሷን ፈለግ ይዘው እንዲከተሏት፣(ብትወዱስ እኔን ምስሉ ዳርዳርታ)ይሄን ሁሉ አወራችና “እንዳላሰለቻትሁ” በማለት ወደ ግጥሟ ተሸጋገረች
(ገና ድሮ የሰለቸንውን !?)

ወደ መድረክ ስትወጣ መነፅሯኝ ቦታዋ ላይ ረስታው ስለነበር፣ " አቀብሉኝ”ስትሳቸው የእጅ ቦርሳዋን አራት ሰዎች ግራና ቀኝ ይዘው (ማሸርገዳቸው ስላበሳጨኝ የጨመርኩት ነው) አቀበሏት፡፡ቦርሳዋ ውስጥ አስር ደቂቃ ፈልጋ መነፅሯን ቤቷ መርሳቷን አረጋገጠች፡፡..እናም ወደ ብርሃኑ ቀርባ ግጥሟን ማንበብ ጀመረች፡፡

እንስራውን ሰብሮ ወሰዳት ልጅቱን(ርዕስ)
አረ አያ ደገፋው አንተ ትልቀ ሰው፣
አንዲት ፍሬዋን ልጅ ማስቸገርህን ተው!
ውሃ ልትቀዳ ወንዝ ስትሄድ፡
ቁመሽ አውሪኝ አልካት በግድ፣
ይሄ እልበቃ ብሎህ ሰው ጭር ሲልልህ
ሕፃኗን ደፈርካት እግዜር ይይልህ (ውይ ወንዶች አለች ከጎኔ ያለችዋ ባለ ፈንዲሻ)
ደሟን እያዘራች እቤቷ ስትደርስ፣
እንስራ ሰበርሽ ብለው ጎረፉት አያድርስ.
ደሞ በሌላ ቀን እንደገና አድብተህ..፣
አሁንም ደፈርካት አንተ ምን ዓይነት ሰው ነህ። ('በስማም ጭካኔ.ሌላዋ ሴት)

አዳራሹ ፀጥ ብሎ 'ግጥሙን' እያዳመጥን ድንገት ጎኔ ያለችው ሴት ጎርደምደምደም…ከሻሸሽ…
ስታደርግ ደንግጬ ዞሬ ተመለከትኳት፡፡ ተመስገን ፈንዲሻ እየበላች ነው፡፡…እኔማ በግጥሙ
ተመስጣ በስህተት ስልኳን ቆረጣጠመቻት ብዬ ነበር፡፡
ግጥሙ ለድፍን ሀያ ሰባት ደቂቃ ተነበበ፡፡ የግጥሙ የመጨረሻ ስንኞች

ፊስቱላ ተይዛ ስትንከራተት፣
ጤና ኤክስቴንሽን ሠራተኛ አግኝታታ!
እዲሳባ በመኪና አመጣቻት.
መንግሥታችን በሠራው ዘመናዊ አስፓልት…?

አመሰግናለሁ !!

ቿቿቿቿቿቿቿቿቿ….(ታዳሚው ፈንዲሻውን ጨርሶ ነበር)

ለመውጣት ሳቆበቁብ አስተዋዋቂው እንዲህ አለ….

“ለሴቶች ቀን ያልሆነ ግጥም ለመቼ ይሆናል' በማለት ወይዘሪት ዘቢደር የወጣቶች ሊግ አትተባባሪ
ለግንቦት ሃያ አንብባው የተደነቀላትን 'ታታሪዋ ሥራ ፈጣሪ' የሚለውን ግጥምን ላቅርብ
ብላለችና እስቲ ወደ መድረክ…”

ተነስቼ ወጣሁ፡፡ ወደ ቤቴ ስሄድ ከኋላዬ የአስተዋዋቂው ድምፅ ይሰማኛል፡፡

"ወጣት ዘቢደር የእንስቷ ጣጣ የሚል በቅርቡ በታተመ የግጥም መድብሏ ከፍተኛ እውቅና
ያተረፈች ብርቱ ሴት ስትሆን...” እያለ ቀጠለ፡፡

ይሄ ቀበሌ ነዋሪው ሳይሰማ ማተሚያ ቤት ከፈተ እንዴ?.. እንዴት ነው ይሄ መድብል ማሳተም እንዲህ የቀሰለው ጎበዝ? ?!

አለቀ
👍24😁12👎1
#ከፍሪጅ_የተጫረ_እሳት


#በአሌክስ_አብርሃም

አዲሳባ ውስጥ ከሚኖሩ ሃምሳ ዱርዬ ሴቶች መካከል የሰላሳ ዘጠኙ ስም ሜሮን ይመስለኝ
ነበር፡ አምስቱ ሄለን አምስቱ ሃያት፣ አንዷ ግን አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ስም እየቀያየረች
የምታጭበረብርና ስሟ የማይታወቅ፤ ቦሌ ቢባል ካዛንችስ፣ ፒያሳ ቢባል አራት ኪሎ፣ ነርስ ብትሆን ሱቅ ጠባቂ፣ የዩኒቨርስቲ ተማሪ ብትሆን ሴተኛ አዳሪ…ብቻ ስሟን የምትቀያይር ሴት ነበረች የምትመስለኝ፡፡

አዎ ስሟን እየቀያየረች በአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ስም የምትዶርር (ዱርዬ የምትሆን) ትዕግስት፣ ሳባ፣ ገነት፣ ማርታ፣ መቅደስ፣ ትርሃስ፣ ሐረገወይን፣ ወላንሳ፣ ዙሪያሽ፣ ፍሬ፤ቃልኪዳን፣ ቲቲ፣ መዓዛ፣ ራሄል፣ ሚሚ፣ ሙና፣ አስናቁ፣ ዘሪቱ፣ መንበረ፣ አለምነሽ፣ ያኔት፤ሊና፣ ላራ፣ ሃና አንድ ነጥብ አምስተኛው ላይ ሜሮን ትሆናለች፡፡ እች እስስት !!

እስስት ብያለሁ አዎ !! ስም እኮ ቀለም ነው፤ ሰው ስሙን ሲቀያይር ቀለሙን ለመቀየር መሞከሩ ነው፡፡ እና ጥሩወርቅ ጎጃምኛ ቀለሟን ቀይራ ሊያ ነኝ ስትል ምን እየሆነች ነው? አካባቢዋን እየመሰለች፤ አዲሳስባን እየመሰለች፡፡ እስስትስ ከዚህ የተለየ ምን አደረገች ? ያው አካባቢዋን ለመምሰል ቀለሟን ነው የቀየረችው፡፡ አነጋገርን ለመቀየር የሚደረግ ድካም ምንን ለመቀየር ነውጥ ? ቀለምን ! እናም ሰውና እንስሳት ከሚመሳሰሉስት ባህሪ ዋናው የተጠጉትን መምሰላቸው ይመስለኛል፡፡

ስምንተኛ ክፍል እንደነበርኩ ፍቅር ያዘኝ፡፡ ሜሮን ከምትባል፣ ሁልጊዜ በብዙ ሴት ጓደኞቿ ከምትከበብ ልጅ ደግሞ ስትስቅ ታምራለች ስትኮሳተር ግን ታምራለች፣ አነጋገሬ ተምታታ አይደል ? እንዲህ ነበር የተምታታብኝ !! ቀይ ናት፣ ከቢጫነት ጋር የሚዋሰን ቅላት፡፡ አፏ ሰፋ ያለ ከንፈሯ ቀይና ወደታች ወረድ ብሎ የሆነ “ከምታፈጥ መጥተህ አትስመኝም” ብሎ የሚጣራ ነገረኛ ከንፈር፤ ሕፃን ሆነን አባ ገመቹ አጥር ላይ ተንጠልጥሎ የሚያስጎመዥንን ፕሪም የመሰለ፡፡

የላይ እና የታች ከንፈሮቿ በአንድ ላይ ሲታዩ የሆነ ልብ የሚሰውሩ የልብ ቅርፅ፡፡ ሜሮንን በአይኔ
ሳይሆን በልቤ ነበር የማያት፡፡ ሳያት የልቤ ሽፋሽፍት ይርገበገባል ! በስንት መከራ ያውም ወደ ዘጠነኛ ክፍል ስናልፍ “ሳይሽ የልቤ ሽፋሽፍት ይርገበገባል..” ብዬ ደብዳቤ ፃፍኩላት፡፡ ሄለን እና ሃያት የሚባሉት ጋጠወጥ ጓደኞቿ ጋር በመሆን በዚች ዓረፍተ ነገር ምክንያት ዓመቱን
ሙሉ መሳቂያ መሳለቂያ አደረጉኝ:: መሪያቸው አንዲት ስሟን የማላውቃት አይጠ መጎጥ የመሰለች ልጅ ነበረች፡፡ልክ እኔ ሳልፍ ደረታቸውን በእጆቻቸው እያራገቡ በሳቅ ያውካካሉ፡፡
እይጠ መጎጧ በአካፋ ዓይኗ አሸዋ ወንድ ስትግፍ የምትውል ከንቱ !! ስሟን አላውቀውም፤
ስሟን አስር ጊዜ ትቀያይራለች ስሟ ብዙ ነው፡፡ ሁሉንም ስሞቿን የኢትዮጵያ ቄሶች ሁሉ እየተጋገዙ ይጥሩት !!

የእርሷ ሳቅ ሳቄን ገድሎታል፡፡ የእርሷ የፌዝ ዕይታ ሩቅ እንዳላይ አንገቴን አስደፍቶኛል:: የልብ ሽፋሽፍት የሚል ግጥም ፅፋ ለፀረ ምንትስ ከበብ ዓመታዊ ዝግጅት ሰልፍ ሜዳ ላይ አንብባ 843 ተማሪ ሲባዛ 32 ጥርስ = 26 976 ጥርስ ይርገፍና !! ቆይ የአስተማሪዎቹን ረስቼው ነበር፡፡ ሲደመር 23 ሲባዛ 32 = 736 ሲቀነስ 32 (ቲቸር አንድም ጊዜ አልሳቁም)፡፡

የፍቅር አፒታይቴን” ምድረ ጥርሳም በሳቃቸው ቆልፈውት አስራ ሁለተኛ ክፍል ጨርሼ ዩኒቨርስቲ እስከምገባ ድረስ ሴት የምትባል ፍጥረት አጠገብ ድርሽ ብዬ አላውቅም፡፡ እና ምን ተባልኩ ?ጨዋ !! እንኳንም ያልቀረብኩ !! ምናቸው ይቀራል? ያች አይጠ መጎጥ፣ አስቀያሚ፣ ጥርሳም፣ አንድ ነጥብ አምስት ሚሊየን ስማም ! ዛሬ የራሷ አንድ ስም እንኳን ጠፍቶ ማንም አንቺ
የሚላት የካፍቴሪያ አስተናጋጅ ሆናለች፡፡ ሻይ አዞ ስሙኒ ጉርሻ ለተወላት ሰብለ፤ ቡና ጠጥቶ ለገለፈጠላት ናኒ እየሆነች እስስቷ የስሟን ቀለም እየቀያየረች አለች፡፡ ብር ዛፍ ቁርስ ቤት ሳልፍ ሳገድም ከነቀይ ሽርጧ አያታለሁ

ዩኒቨርስቲ የተመደብኩት እዚሁ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ነበር፡፡ ደስ አላለኝም፡፡ ምክንያቱም ከአዲስ አበባ ውጭ ከወላጅ ራቅ ብዬ የመኖር የቆየ ፍላጎቴ ተሰናክሏልና፡፡ አስከፊው ነገር
ደግሞ ዩኒቨርስቲው “የአዲስ አበባ ልጆች እየተመላለሳችሁ ተማሩ በቂ መኝታ የለኝም አለ ይሄ ደግሞ ዩኒቨርስቲና ሃይ ስኩል የሚለያዩበትን አንድ ድንበር አፈራረሰው፡፡ ዩኒቨርስቲ
ውስጥ የገባሁ አልመስልህ አለኝ፡፡ ወደ አስራ ሶስተኛ ክፍል ያለፍኩና እዛው የነበርኩበት ትምህርት ቤት የቀጠልኩ አይነት ስሜት ነበር የተሰማኝ፡፡ ያ ሁሉ የተወራለት፣ በፊልም እና በሰመመን መጽሐፍ ብዙ የተባለለት የዩኒቨርስቲ ሕይወት፣ ላየው የጓጓሁለት “የግቢ ላይፍ ውሃ በላው !! ወይ ነዶ! አንድ አራት ወር እየተመላለስኩ እንደተማርኩ እዛው ዩኒቨርስቲው አካባቢ ቤት ተከራይቼ ለመማር ወሰንኩ፡፡ ምንም አስቤ ሳይሆን የአዲስ አበባ ታክሲ ጊዜዬን እየበላብኝ ስለተቸገርኩ ነበር፡፡ ማንም አልተከራከረኝም፤ ዩኒቨርስቲው ከሚወረውርልኝ ሳንቲም ላይ ቤተሰብ በየወሩ ድጎማ እየመረቀበት ቤት ተከራየሁ፡፡ድከም ያለች ቤት አንድ ሰፈር ውስጥ፡፡ እንግዲህ የእኔ
ቤትና ከጎኔ ያሉት ጭርንቁስ ቤቶች በመደዳ የተሰለፉ ነበሩ ፊት ለፊት ደግሞ ፊታቸውን
ወደ እኔ ቤት ያዞሩ ስስሪትም፣ በመጠንም ከእኔ ቤት ጋር ተመሳሳይ የሆኑ ሌላ መደዳ ቤቶች አሉ፡፡ መስኮቴን ስከፍት ፊት ለፊት ያለው ቤት መስኮት ጋር እፋጠጣለሁ፡፡ በሬን ስከፍት ፊት
ለፊት ካለ በር ጋር ! በሁለቱ መደዳ ቤቶች መካከል ቀጭን የእግር መንገድ አለች፡፡ የእኔ ቤትና ፊት ለፊቴ ያለው ቤት ጣራቸው ሊገጣጠም ምንም ያህል ስለማይቀረው በመካከላችን በቀጭኗ የእግር መንገድ የሚያልፍ ሰው ረዥም ኮሪደር ውስጥ የሚያልፍ ሊመስለው ይችላል፡፡ ከበሬ ላይ አንድ ጠቀም ያለ ርምጃ ወደፊት ብራመድ ፊት ለፊት ያለው ቤት በር ላይ አርፋለሁ፡፡ ይሄ ነው የተከራየሁት ቤት::

ሜሮንን ትሻግሮ ሜሮን አለች ወይ…

በአንድ ርምጃ ርቀት ጣራዬ፣ ከጣራው የሚነካካው ቤት ውስጥ ፊት ለፊቴ 'ሜሮን' የምትባል
ልጅ መኖሯን ያወቅኩት ቤቱን በተከራየሁ በሁለተኛው ቀን ነበር፡፡ በጊዜና ቦታ ርቀት ትቼ የመጣሁት “ሜሮን” የሚባል እንደ ጥላ የሚከተል ስም እዚህም መጣ፡፡ ሜሮን ሜሪ ሜሪቾ ሜሪዬ…ይላታል የመንደሩ ሰው፡፡ ጥቁር ትሁን ቀይ አይቻት አላውቅም ነበር፡፡ ለሰባት ወራት
ያህል ጧት እየወጣሁ፣ ማታ እየገባሁ በሰላም ኖርኩ፡፡

በአንድ ጠራራ የግንቦት ቀን ከክላስ ወደ ቤቴ እየገባሁ ነበር፡፡ የፀሐዩ ቃጠሎ ከንፈሬን ሁሉ
አድርቆታል፤ ሰውነቴ ሁሉ የተነነ ነው የመሰለኝ፡፡ ድርቅ የመታኝ !! ቀዝቃዛ ውሃ ለመግዛት ጫፍ ላይ ወዳለች ኪዮስክ ሄድኩና “ቀዝቃዛ ውሃ ስጭኝ እስቲ” ብዬ አስር ብር ባለሰሃኑ
ሚዛን ላይ ጣል አደረግኩላት፡፡ አስር ብሩ ሚዛኑ ላይ ሲያርፍ ሚዛኑን ዝቅ አላደረገው ከፍ…

“ቀዝቃዛ የለም !” አለች እስር ብሩን በእጇ ይዛ፣
"እሽ ቀዝቃዛ ኮካ”
“ቀዝቃዛ ኮካም የለም ከውጭ ልስጥህ ?” አለች፣
ቀዝቃዛ ነገር ምንድን ነው ያለሽ ?”
“ፍሪጅ የለኝም ከውጭ ነው ሁሉም !”
“ተይው በቃ !” ብዬ ብሬን ልቀበል እጄን ዘረጋሁ፡፡ ቅር እያላት ብሬን መለሰችልኝ፡፡ ፊቴን ኮሰኮስኩ በጣም ነበር የተበሳጨሁት፡፡ ኤጭ!!
👍33
#ከፍሪጅ_የተጫረ_እሳት


#በአሌክስ_አብርሃም

...በቃሌ መሰረት ልደቷን ልናከብር ተቀጣጠርን፡፡ ከሰፈር አብረን መውጣቱ ለጎረቤት ሃሜት
ስለሚዳርግ የሆነ እሷ የመረጠችው ሬስቶራንት ስምንት ሰዓት ላይ እንገናኝ ተባባልን፡፡....
እኔ በበኩሌ የዚህ ዓይነት ሴት አይቼ አላውቅም፤ ቀድሚያት ነበር የደረስኩት፡፡ ቀይ የለበሱት
ጠረጴዛዎች የአገር ሹካና ማንኪያ፣ ቢላዋና የጨው የምናምን እቃ ዙሪያቸውን ተደርድሮባቸው፣ፈዘዝ ያለ ብርሃን ያለበት አዳራሽ ውስጥ በሰፊው ተንጣለዋል፡፡

ምቾት አይመቸኝም፤ ቅንጦት አያቀናጣኝም፤ ጨነቀኝ !
ሜሮን ስትደርስ ልቤ በድንጋጤ ልትቆም ምንም አልቀራትም፡፡ የሚያምር አጭር ጉልበቷ ላይ
የቆመ ቡና ዓይነት ቀሚስ ለብሳለች፡፡ ውብ እግሮቿን ለማሳየት ሆን ተብሎ የተሰራ የሚመስል ረዥም ተረከዝ ያለው ጫማ፣ ጥልፍልፉ ፍርጥም ያለ ባቷ ላይ እንደሃረግ እየተጠመጠሙ ወጥቶ ጉልበቷ ላይ የደረሰ፣ ጡቶቿ ደረቷ ላይ ክፍት በሆነው ቀሚሷ ታቅፈውና ተሳስመው የሲኦል ሸለቆ እንደሰሩ፣ ፀጉሯ ወደ አንድ በኩል ተሰብስቦ በማስያዣ ተይዟል፤ ዓይኗ በኩል ተከቧል፣ ኦህህህህህህ ስታምር! የአዲስ አበባ እናቶች እድሜ አቆጣጠር አይችሉም ይሆናል እንጂ ይህቺ ልጅ አስራ ስድስት ዓመቷ ብቻ አይመስለኝም፡፡ በዚህ እድሜ ቀጠሮን የመከሸን ሳይንስ እንዴት ነው መካን የሚቻለው? እኔ እኮ በዚህ እድሜም አልችልበትም፡፡

ቆሜ ተቀበልኳት፤ ጉንጫችንን አነካካነው፤ መሳሳም መሆኑ ነው፡፡ አቤት ሽቶዋ! ..ፊቴ ዝም
ብላ ቆመች ! ..ቆምኩ …አሃ ለካ ወንበር ይሳባል ! ሳብኩላት፤
“ቴንኪው !” ብላ ተቀመጠች፤

“በጣም ቆንጆ ሆነሻል”

“እመሰግናለሁ” የተጠና ምልልስ መሰለብኝ እንጂ ከልቤ ነበር የተናገርኩት፡፡ በዚህ ቀን ከሜሮን
ጋር ከዘፍጥረት እስከ ራእይ አወራን፡፡ ሜሮን ካለ እድሜዋ የበሰለች ጉድ ነበረች፤ እናም
እንዲህ አልኩ፣

“ 'አዲስ አበባ ውስጥ ከሚኖሩ ሃምሳ ዱርዬ ሴቶች ውስጥ ሰላሳ ዘጠኙ ስማቸው ሜሮን
ይመስለኛል ግን ማናባቱ ነው ይሄን ቆጠራ ያካሄደው ደደብ!”ሜሮን ጋር ተዋድደን
ነበር በቃ ! እኔ ጋር በመሆኗ ነፍሷን እስክትስት ተደስታ ነበር፡፡እኔማ ነፍሴን ከሳትኩ ሰንብቻለሁ፡፡ ልዩ ሰው አድርጋ እንደምታስበኝ ነገረችኝ፤ ሰፈር ውስጥ ዝምታዬ መስጧታል።

ደግሞ ወሬው ሁሉ ከየት መጣልኝ ? የሰው ሰው በሳቅ ልገድል !! እግዜር ሲያስወድድህ ብዙ ሳቅ የወደደህ ሰው ልብ ውስጥ ያስቀምጣል፤ ከዛም የውድህ ሳቅ መውጫ በር፣ መተንፈሻ መስኮት ያደርግሃል፡፡ አንተ በፈለግከው መንገድ አፍህን ክፈት፣ ቃላትን አውጣ፤ ሜሪዬ የኔ ውብ አቤት ሳቋ ሲያምር ! እዛ ዩኒቨርስቲ “ሄይይ ምን አዲስ ነገር አለ ” እያሉ ሳቅ ፍለጋ እንደሚባዝኑ ሕይወታቸውን በጊዜ ያሟጠጡ ደነዝ ሴቶች አይደለችም፡፡ ቻፕስቲካም ከንፈራቸውን እስከጆር
ግንዳቸው ለቀው በ 'ዊትኒ ሆስተንኖ ለመሳቅ ቆርቆሮ ድምፃቸውን እንደሚያንኳኩ ኳኳታሞች አይደለችም፤ ሜሪ ራሷ ሳቅ ነበረች፤ ፍንትው ስትል ከእግር ጥፍሯ እስከ ራስ ፀጉሯ በሳቅ
የምትጥለቀለቅ ! እንደእኔ አይነቱ ሰው ተሳቀልኝ ቢል ያምርበታል፤

ልብ ነበራት፤ የፍቅር የሰላም ያልተነካካ፡፡ 'ውይ ወንዶች? እያሉ ያለፈ እንኩሮ ሕይወታቸውን
አዲስ የፍቅረኛ ምጣድ ላይ በትዝታ ስም እንደሚጠፈጥፉ ሴቶች አልነበረችም፡፡ ብታውቀውም ባታውቀውም ነገ ይናፍቃታል፡፡ ማንንም አልጎዳች፣ ማንም አልጎዳትም፡፡ ተረት የላትም ! ተረት አይደለችም፡፡ እነእከሌ ተፋቀሩ” ስትባል አትቀናም፡፡ “ተለያዩ" ሲባል አትፈርድም፤ ከተማውን የሞላው ፈራጅኮ ግማሽ ፍርዱ በቀል ነው፡፡ የደረሰበትን ሊስቀል፣ ያደረሰውን
ሊያስተባብል! ሜሪ ግን ብቻዋን ናት፡፡ ብቻዋን ወደ ሕይወቴ መጣች፤ አልከበደችኝም፡፡

ከዛን ቀን ጀምሮ ሁልጊዜ ማታ ማታ በር ላይ እንቆምና ስናወራ እናመሻለን፡፡ ውሃ ልትደፋ
ወጥታ ሊሆን ይችላል፡፡ “ቻው በቃ መሸ !” ትለኝና ቆም ትላለች፡፡ ከቻው በኋላ አንድ የሆነ
ነገር የማድረግ ፍላጎት ሁለታችንም ልብ ውስጥ አለ፡፡ ግን ማን ይድፈር ? ከቻው በኋላ
አንድ ሰዓት እናወራለን፡፡ “ምን አወራችሁ ?” ቢባል እንጃ !! ብዙ ጊዜ ቤቴ እንዳትገባ ሆነ
ብዬ እከላከላለሁ፤ ፈተናው ይከብደኛል፤ ስለዚህ በር ላይ ቆመን እናወራለን፡፡ ወሬኛ ነኝ፡፡
የማላወራላት ነገር የለም !! ባወራሁበት የምከፈለው ደመወዝ ሳቋ ነው፡፡ የጠገበ ደመወዝ፡፡
እግዜርዬ የፍቅር ዩኒቨርስቲ አስመርቆ የሰጠኝ ምርጥ ስራ - ሃሌ ሉያ !” አስመርቆ 'ስራ ፍጠር
ቢለኝ ምን ይውጠኝ ነበር ? ሳቋ ደመወዜ ነው፡፡….ስቃታለሁ፤ የማወራላት ምንም የማይጠቅም
ነገር ቢሆንም የሳቅ ደመወዜን አስቀርታብኝ አታውቅም፡፡

ታዲያ አንዳንዴ ማታ ቆመን ስናወራ ከሩቅ የጅብ ድምፅ ይሰማል፡፡ አውውውው…! ወደ እኔ
ጠጋ ትላለች፤ ሜሪዬ የመጨረሻ ፈሪ ናት፡፡ ጠረኗ ይጠርነኛል፡፡ ከምሽቱ አየር ጋር ወደ ሳንባዬ
ተስገብግቤ እስበዋለሁ፤ ጠረኗን !! እሷን ራሷን እንደአየር ስቤ ውስጤ ያስገባኋት እስኪመስለኝ፤ ጅቡን እድሜውን ያርዝምልኝና በጣም ትጠጋኛለች፡፡

ስለጅብ አወራላታለሁ፡፡ “የጅብ ጥፍር አንገትሽ ላይ ካሰርሽ በቃ የሄድሽበት ሁሉ ሲበሉ ነው
የሚያደርስሽ”
“ውሸትህን ነው ! ሂሂሂሂሂሂሂ…”
“ለምን እዋሽሻለሁ በሳይንስ የተረጋገጠ ነው”
“አላምንህም ! ሃሃሃሃሃሃ…”
እይውልሽ የአሜሪካ ሳይንቲስቶች ናቸው እኮ ያጠኑት”
“ውይ ውሸት አላምንልህም ! እንዴት አድርገው ያጠኑታል ? ... ታየኝ እኮ ስንት ስራ ትተው
አንገታቸው ላይ የጅብ ጥፍር አስረው ሲዞሩ ! ሂሂሂሂሂሂሂሂሂ…” ፍልቅልቅ ትላለች፡፡

ቀላል ነው፤ አንድ ጊዜ ይህን ጥናት እናጥና ብለው አለቃቸውን ሊያስፈቅዱት የጅብ ጥፍር አንገታቸው ላይ ልክ እንደዚህ እንደማተብ (እንገቷ ላይ ያሰረችውን ማተብ እየነካካሁ) አስረው ሳይንቲስቶቹ
ወደ ኃላፊያቸው ክፍል ሊገቡ ኃላፊው ምን እያደረገ አገኙት መሰለሽ…? በርገሩን እየገመጠ፡፡

ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ…ውሸት ! ውሸት ”

“..ከዛ ጥናቱ ተፈቀደላቸውና ወደ አፍሪካ መጡ፤ የሆነ ሰው የማይኖርበት ጫካ እካባቢ
አውሮፕላናቸው ተከለከሰ”
ኦ ማይ ጋድ! እውነትህን ነው ?” አለች ደንገጥ ብላ፡፡
ያ! ግን ማንም አልሞተም፡፡በተዓምር ተረፉ፡፡ ሁሉም አንገታቸው ላይ የጅብ ጥፍር አስረዋል፤ ከዛ የሆነ
ነገር ሸትቷቸው ዞር ሲሉ ጫካው ውስጥ የሚኖሩ አዳኞች ምን የመሰለች ጥንቸል ለምሳቸው እየጠበሱ:

“ወይኔ ውሸትህ ሂሂሂሂሂ…አልሰማህም !”

“እስኪ ጥናቱን የበለጠ ለማረጋገጥ ወደ ሌላ ዓለም እንውሰደው አሉና ናሳ ጋር ተነጋግረው ወደ ጨረቃ የሚጓዙ ጠፈርተኞች አንገት ላይ የጅቡን ጥፍር አሰሩላቸው፡”

“አሁንስ አበዛኸው ሕፃን ልጅ መሰልኩህ እንዴ ?” ብላ የውሸት ተቆጣች፡፡ ሜሪ ከዚህ »
ቀጥሎ የሚፈነዳውን ሳቅ ስለማውቅ ውሸቴን ቀጠልኩበት፡፡
“ልክ ጠፈርተኞቹ ጨረቃ ላይ ሲያርፉ ከእነሱ ቀድመው ጨረቃ ላይ ያረፉ የሩሲያ ጠፈርተኞት
ራት ሊበሉ ሲዘገጃጁ ደረሱ እልሻለሁ”

ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ ሁለተኛ አላዋራህም እሺ ! ስታስጠላ ! እኔ ቁም ነገር የምታወራ መስሎኝ ! ሂሂሂሂ…” ሳቋ መቆሚያ የለውም፡፡ እኔም በሳቋ ልቤ ሃሴት ያደርጋል፡፡
👍31👏1
#ሸረኛ_እና_ደህና_በአንድ_ላይ #ሲሄዱ_በሸረኛው_በኩል_ተናደ #መንገዱ


#በአሌክስ_አብርሃም

#ሸረኛ

የዶክተር ደበጫ እርገጤ መዝገበ ቃላት ሸረኛ የሚለውን ቃል ሲያብራራው እንዲህ ይላል፡
ሸረኛ ስም፣ እንዳገባቡ 'ተውላጠ ስም፣ አንዳወጣጡ ግስ'፣ ሳይገባም ሳይወጣም ራሱን ችሎ
ዓረፍተ ነገር !

ትርጉሙ፡- (በተንኮል የሰው ማንነት፣ መልካም ስም፣ መልካም ሥራ፡ መልካም ግንኙነት
የሚሸረሸር፣ የሚሰረስር፣ የሚቦረቡር፣ የሚደረምስ፣ የሚያጠለሽ... ይለዋል። መዝገበ ቃላቱ ይሄን ሁሉ ነገር ከሚያንዛዛ በቀላሉ መግለፅ ይችል ነበር ልክ እንደዚህ፣

ሸረኛ፡- ሰው አቶ እጅጉ ! በቃ! አጭር ግልፅና ወቅታዊ ፍቺ !!

ምሳሌ፣ አቶ እጅጉ ሸረኛ ነው። ትክከል !! ይሄ ምሳሌ አይደለም፣ እጅጉ (እጅ እግሩን አስሮ
ሲኦል ይወርውረውና) 'ሸረኛ' ነው፡፡ ሸረኛ ብቻ አይደለም፣ ምቀኛም ነው፡፡ የሚቀናበት ነገር
ሲያጣ እኩል በተሰጠን 24 ስዓት ይቀናል፡፡ (“እንደው በየትኛው ጊዜ ብትማሩት ነው ይሄን ሁሉ ነገር ያወቃችሁት?” ይላል የማያውቀውን ነገር አውቀን ካገኘን፡፡ ለነገሩ እሱ ምንም
አያውቅም፡፡) ምን ይሄ ብቻ! እግዜር በፈጠረው አየር ሳይቀር ይቀናል፤ የቢሯችን መስኮት
ተከፍቶ እንደልብ አየር ሲገባ ብቅ ይልና፤ ይሄን አየር በነፃ ትሉታላችሁ” ይላል፡፡ እንከፈል?
ሸረኛም ምቀኛም ብቻ አይደለም መሰሪ ተንኮለኛም ነው:: አሟልቶ አይሰጥም' ይባላል አንጂ
ይሄው የተሟላ ክፉ ሰው፡፡

እንግዲህ ሸረኛ፣ ምቀኛ፣ መሰሪ ሆኖ ደግሞ አለቃዬም ነው፡፡ ጥሎበት አይወደኝም፡፡ እኔም
ሰለማልወደው ተመስገን ቢወደኝ ምን ይውጠኝ ነበር?' እላለሁ ሁልጊዜ፤ ለምወደው ሰው
ነው የምጨነቀው፡፡ አሁን በዚች ቅፅበት በሆነ አጋጣሚ ነገር ሎተሪ ምናምን ኣይነት እድል
ገጥሞኝ በድንገት የብዙ ኢ ቢሆን የመጀመሪያ ሥሪዬ ሁለት እጆቼን ኪስና ኪሴ ከትቼ በቀዳዳ ኪሴ ውስጥ በሾለኩ ጣቶቼ ራቁት ታፋዩን በማፏጨው ሙዚቃ 'ሪትም' እየተመተምኩ ጀነን ብዪ ወደ አለቃዬ ቢሮ ሄድና አንኳኳለሁ፣ ኖ..ኖ.አላንኳኳም፤ በሩን በእግሬ ገፋ አድርጌው እገባለሁ፡፡ (ካፈቀሩ ከነፍስ፣ ከጠሉም ከነፍስ ነው የምን ማስመሰል) ፊት ለፊት፣ ጉማሬ ፊቱ አለቃዬ ሁልጊዜ በሚደፈርሱ አስቀያሚ ደመኛ አይኖቹ ያፈጥብኛል። ቀጥሎ ኪሶቼ ውስጥ የወሸቅኳቸውን እጆቼን በቁጣ ያያል፤ (ደንግጨ
ከኪሲ እንዳወጣቸው እንድርበተቡት፡፡) ፀጥ ብዪ በትዕቢት ሳየው የኢትዮጵያን ሲጋራ ሁሉ ብቻውን ያጨሰ ከሚያስመስሉት አስቀያሚና ገጣባ ከንፈሮቹ ቃላት ደፈለፈላሉ፤ ሰው ሰው የማይሸቱ እብሪተኛ ቃላት፡፡

ምናልባትም፣ “ብላችሁ ብላችሁ ማንኳኳቱንም ተዋችሁት." ይል ይሆናል፡፡ (እግዜርና ሰይጣን
ለዚህች ቅፅበት እርቅ አውርደው ይሄን ድንጋይ ራስ ኣለቃዬን በመዶሻ ያንኳኩትና።) ወይም
“ኪስህ የወሸቅከውን እጅህን አውጣ!" ሊልም ይችላል፣ አላወጣም !(ኪሴ ቀዳዳ ሲሆን
ቀዳዳውን ተሻግሮ ያለም ወንድነት የራሴ ርስት ነው . ዘራፍ ! በቀዳዳ እኛነታችን ውስጥ እያለፈ ወንድነታችንን ያኮላሹን ክፉዎች ሁሉ ከዛሬ ጀምሮ አድርጉ ያሉትን አናደርግም፡፡

ኮራ ብዬ "እእእእ አቶ እጅጉ” እለዋለሁ፡፡ (“አቶ" በማሾፍ ሲጠራ እንዴት ያለ አሪፍ ስድብ ነው፡፡) ለምሳሌ፣ እኔ "አቶ” ከሚለው ቅፅል ይልቅ ከስሜ በፊት ሰሃራን የሚያህል ባዶ ምድረ በዳ ቢዘረጋ ይሻለኛል፡፡ በተለይ አለቃዬ "አቶ" ከሚለኝ ። ...አዎ ! እሱ "አቶ"
ሲለኝ በውስጡ “መቼም ለአቶነት አትበቃም በቸርነቴ 'ከቶ'ነት ልስጥህ እሰቲ” የሚል ይመስልበታል፡፡ አቷም።

እና አቶ እጅጉ ከዛሬ ጀምሮ ሥራ ለቅቄያለሁ” እለዋለሁ በኩራት፡፡ 'እእእእ' የምትለዋን ዘገምተኛ ቃል ማስቀደም አልረሳም፡፡ አራት ዓመት ሙሉ የሱን አስቀያሚ እእእ' ችዬ ኖሬ የለ ስለዚህ የምለው እንደዚህ ነው:: “እእእእ.አቶ እጅጉ ከዛሬ ጀምር...እእእእ ሥራ ለቅቄያለሁ !”

ይደነግጣል፣ አያምንም፡፡ እኔ ስፈጋ የዋልኩበትን ሥራ ሁሉ ለአለቆቹ እንዲህ ሠርቼው እንዲህ
አድርጌው እያለ በስልክ መወሽከቱ ሊቆም ሲሆነ ይደነግጣል እሰይ ! ወሽካቶች መደንገጥ አለባቸው።

ወዲያው የበሰበሰ የማኔጅመንት 'ሲስተሙን' እኔ ላይ ሊሞክራት ይፍገመገማል፣ “አትደነግጥ
የበታች ሠራተኛህ ፊት አዋቂ፣ ልብ ሙሉ ምንትስ ሆነህ ቅረብ፣ ባትሆንም ሁን…” የምትለዋን
ያስብና ጉሮሮውን ጠራርጎ፣ “እእእ….እዚህ መሥራቱ ራስህን ለማሳደግም ሆነ ቤተሰብህን ለመርዳት አይሻልህም? ይላል፡፡ ሥራ ብለቅ ቤተሰቦቼ በረሃብ ዛሬውኑ የሚያልቁ በሚያስመስል ሁኔታ 'ቤተሰብ የምትለዋ ቃል ላይ አፅንኦት ሰጥቶ፡፡

ከፉዎች መሳሪያ ልጅህ ላይ ባይደግኑም፡ እናትና አባትህን አፍነው ባይወስዱም፣ የነገን ጨለማነት እየነገሩ ያግቱUል፡፡ ስንቱ መሰለህ ቁራጭ ዳቦ እንዳይነሱት ፈርቶ ለማንም አጋሰስ ጉልበቱን የሚገፈግፈው፤ ስንቱስ ነው ' ከሥራ መባረር የሚባል የታንክ አፈ ሙዝ ልቡ ላይ ተደግኖበት ዘመናዊ ባርያ የሆነው !! ስንቷን ሚስኪን በፀሃፊነት ስም የጭን ገረዱ ያደረጋት ጋንጩር አለ ቢሮ ይቁጠረው !

ሀላፊ ሲባል አርቲስት ነው፡፡ ወንበሩን መድረክ ያደረገ ተዋናይ፡፡ ያውም ድብን ያለ ትራጀዲ
የሚተውን፡፡ እና እኔ ምን እለዋለሁ ሃሳቤ ደስ ብሎኝ ሳምሰላስል፣ ዙፋን ዘው ብላ ወደ ቢሮዬ
ገባች፡፡ ጥሎባት ማንኳኳት አትወድም፡፡ 'እንኳኪ!' ብሏት የሚያውቅም የለም፡፡

"ብርሽዩ” ትለኛለች፡፡ (ስሟን ከነአያቷ ቄስ ይጥራትና) ! ሁልጊዜ ስትጠራኝ እንዲሁ ነው፡፡ ታዲያ አጠራርዋ ከማማሩ ብዛት እኔን ለጠራችኝ ሌሎቹ 'ወይዬ' ሊሏት ይዳዳቸዋል፡፡

እንዲህ በሀሳብ ጭልጥ ያልከው ወዴት ሄደህብኝ ነው?” ወዴትስ ብሄድ ምን አገባት፡፡ ጭራሽ
የምሄደውስ የምቀረውስ ለሷ ነው እንዴ? (ሄደህብኝ !! ጥርግ ብል እንትናዬ እያለች አንዱ ቢሮ ልትንኳተት፡፡

"እ..ምነው ጠፋሽ?” አልኩ እንደመጣልኝ፡፡ የምለው አጥቼ እንጂ ዙፋን ደግሞ መቼ ጠፍታ
ታወቅና፡፡ በአንድ ጊዜ ሰባት ቢሮ ውስጥ የምትገኘውን ዙፋንን ጠፋሽ ማለት መሬትን “ምነው
በዚህ ሳምንት መዞርሽን አቆምሽ?” ብሎ ከመጠየቅ አይተናነስም፡፡

ሆሆ ከየት ተገኘሽ፣ አሁን እንኳን ስመጣ አራተኛዬ ነው” አለችና ከጠረጴዛዬ ፊት ለፊት ወንበር
ስባ ተቀመጠች፡፡ ወንበሩ ተንጫጫ፡፡ ጉርድ ቀሚሷ ቀይ ታፋዋን ወለል አድርጎ ያሳያል…..
ኤጭጭጭጭጭ!!

“ቆንጆ ናት” ይባላል፡፡ “ትሁት ናትም” ይሏታል። “የሰለጠነች፣ ሰው አከባሪ" የሚሏትም ብዙ
ናቸው፤ እንደው ባጠቃላይ እዚህ ቢሮ ዙፋንን ለማናገር፣ ለማቅረብ፣ ሲመቸው ወደ ኣልጋው
ጎትቶ አብሯት ለመጋደም የማይመኝ ያለ አይመስለኝም፡፡

ዙፋን እኛ ቢሮ ሥራ ስትጀምር ከሥራ ልምዷ ጋር ከእግዜር የተላከ “ከዛሬ ጀምሮ ያየ አመነዘረ፤ የሚለው ጥቅስ ተሰርዟል” የሚል ደብዳቤ ይዛ የመጣች ይመስል፣ እዛ ፋይናንስ ከሚሠራው ዲያቆን ወልዱ ጀምሮ ሰው ሰላም ሲል እገጩ መሬት እስኪነካ የሚያጎነብሰው ጴንጤው ምክትል ኃላፊያችን የዙፋንን እግርና መቀመጫ አይተን እንሙት አሉ፡፡ ዙፋንም ታዲያ የዕለት እንጀራዋ የሰው አይን ይመስል ነገረ ሥራዋ ሁሉ የታይታ ነው፡፡ አቤት መታየት ስትወድ፡፡ ሰው ከኋላዋ እንደሚያያት ከጠረጠረች ለከፉ ቀን ያስቀመጠችውን መቆናጠር ሁሉ ትጠቀምበታለች፡፡
👍26🔥1
#ሸረኛ_እና_ደህና_በአንድ_ላይ
#ሲሄዱ_በሸረኛው_በኩል_ተናደ
#መንገዱ


#በአሌክስ_አብርሃም

...ፊታቸው በሀዘን አኮፍኩፎ በእድሜ እናቴን ይበልጣሉ፡፡ ከወንበሬ ተነስቼ ለሰላምታ እጄን ዘረጋሁላቸው፡
በሁለት እጆቻቸው አሁንም ጎንበስ ብለው ሰላም አሉኝ፣ እጃቸው ይሻክራል፡ ልክ እንደ እናቴ.
እነዚህ ሞረድ እጆች የስንቶቻችንን ባለ ለስላሳ እጆች ሆይወት እንደሞረዱ ፈጣሪ ይወቅ!

እንዲቀመጡ ወዳመለከትኳቸው ወንበር ቀስ ብለው ተቀመጡና የመጡበትን ጉዳይ ቀስ ብለው
እንደምታውቀው እዚህ ቤት ነገረ ሥራቸው ሁሉ ውስጥ ለውስጥ ነው:: ደከመኝ፣ ሰለቸኝ
አስረዱን፣ አቶ አብረሃም (አቤት አቶ በእሳቸው አንደበት እንዴት ክብር እንዳለው ) ያው እንደምታውቀው እዚህ ቤት ነገረ ስራቸው ሁሉ ውስጥ ለውስጥ ነው ደከመኝ ሰለችኝ ሳልል በሰራህ ለትንሽ ትልቁ 'እሺ' ብዬ ባደርኩ ድንገት ከሥራዬ ነቀሉኝ፡፡" አሉና እንባቸው ተዘረገፈ፡ እድሜ በሸነተረው የቆዳቸው እጥፋት ሽብሽብ ውስጥ እንባቸው ጎረፈ፡፡ በነጠላቸው ጫፍ እይናቸውን ጠረጉ፡፡ (እዚህች ባልቴት ውስጥ ይሄ ሁሉ እንባ እንዴት ሊኖር ቻለ? እድሜ ልካቸውን ያጠራቀሙት ይሆን?) እማማ መለኮት ከፅዳት የሥራ ገደብ ተነስተው በሀያ ዓመት የሰርክራሲ ባቡር ተጉዘው ፅሃፈ ለመሆን የበቁ ፅኑ ሴት ናቸው፡፡ ከልምድ እንዳየሁት ብዙ
ታላላቅ ድርጅቶች ሱፍ ለብሰው በሚኮፈሱት አለቆቻቸው ሳይሆን በሚስኪኖች ትከሻ ላይ
ተጭነው ነው የቆሙት፡፡ እማማ መለኮት የድርጅታችን ዋልታ ይሄው ተባረሩ፡፡

ከዛ በፊት፡ ከመባረራቸው በፊት፤ አሽሙር የሚመስል ስብሰባ ተደረገ፡፡ አንዲት ረዳት የሌላቸው
ሚስኪን ባልቴት ለማባረር ቱባ ቱባ ባለስልጣን፣ ከቱባው የተተረተሩ ክር አቃጣሪዎች እና እኛዎች" ውሃ ቡና ቀርቦ ስብሰባ ተደረገ፡፡የስብሰባው መሪ፣ "ሸረኛው" እጅጉ፣ ፀሃፊው “ሽረኛው"
አለሙ፣ ተላላኪው፣ ወሬ አቀባዩ (እንደ ሰው አልባ አውሮፕላን እያንዣበባ ሰላሉት አለቆቹ ወሬ ይቃርማል፡፡ “መታዘዝ ፅድቅ ነው” ሲባል የመታዘዝ ፅድቅነትን የማያመዛዝን አዕምሮ ተሸክሞ የሌሎች ባሪያ መሆን ማለት አይደለም፡፡ ሰብዓዊ ትዕዛዝ፣ ሰው መሆን ይቅርብሆ ተብለህ ሳይሆን፣ ለእኔ ማለት ይቆየኝ፣ ቅድሚያ ለሌሎች ከሚል በጎነት መነሳት ነው:: በጎነት በትዕዛዝ አይመጣም፡፡)

ስብሰባው ተጀመረ፡፡ ለአንዲት ባልቴት ተሰበሰቡ እንዳይባል የማይረባ አርሲ ኩርሲ አጀንዳ
ጋር ተደምሮ የእማማ መለኮት መባረር መቀነስ” የሚል የዳቦ ስም ተሰጥቶት አጀንዳ ሆነ፡፡

“ባንድ ላይ ሲሄዱ” መዝገብ ቃላቱ በአንድ ላይ መሄድን በአንድ ላይ ከመታየት ነጥሎ አለማየቱ ትልቅ ጉድለት ነው::

የሸረኛ፣ “እና” ና “ደህና” ስብሰባው ላይ በአንድ ላይ ተገናኘን፣ በማንኛችን በኩል መንገዱ እንደሚናድ ልናይ - ቀድሞ የተናደውን፡፡

“ተናደ"

ስብሰባውን የጀመረው አለቃችን አቶ እጅጉ ነበር፡፡ ኩፍስ ብሎ የኮቱ አጥፋት ሸብዳዳ ትከሻው ላይ ተከምሮ (ከኮቱ ውስጥ ትንሽ የሶፋ ትራስ ያስቀመጠ ይመስለኛል)፡፡ ጨዋ ለመምሰል በሚዳዳው ድምፅ ስብሰባው መጀመሩን አረዳ (አበሰረ የሚሉም አሉ “ከሸረኞች ወገን ናቸው)

እ...ያው እንደምታውቁት…" አለ (ምንም በማናውቀው ነገር) ...መሥሪያ ቤታችን ያለውን
መልካም ሰምና ዝና ለማስቀጠል (ሂሂሂሂ ጉድ ፈላ በቀን የሚመጣው ባለጉዳይ ሁሉ እዩዬ እያለ ተራግሞ የሚሄድበት መሥሪያ ቤት መልካም ስምና ዝና ይሁና) ዘመናዊ የአሠራር ሲሰተም
ዘመን አፈራሽ መሳሪያዎች እንደሚያስፈልጉ በማመን የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ወስደን
እየተንቀሳቀሰን 'ያለበት ሁኔታ ነው ያለው….

እነዚህ ዘመናዊ መሳሪያዎች ደግሞ ብቻቸውን ጠብ የሚል ለውጥ እንደማያመጡ እሙን
ነው፣ ስለዚህ ቢሯችንን 'በአመለካከት በእውቀት እና በተግባር ከመሳሪያዎቹ ጋር አብሮ
በሚሄድ ወጣት የሰው ኃይል ማደራጀቱ ለነገ የማይባል አንገብጋቢ ተግባር ነውሸ

(እማማ መለኮት በኩል መንገዱ ተናደ:: ጨዋነትን የጫነው መኪና ገደል ገባ፡፡ ትህትና ተሽቀነጠረ፡፡ መንገድ ስለሌለ ወደኋላ ተመለስን፡፡ መንገድ አፍራሽ ሸረኞች ራእይ እንደ ህልም
ያያሉ፡፡ ከመድረስም ተጣልተዋል፡፡ መንገድ የለማ ...! ከአባይ ወዲያ ማዶ ያለ ዘመድ ሆነ የእማማ መለኮት ሥራ፣ እንባቸው በአይናቸው የሞላ እለት ዋይ ብለው ቀሩ፡፡

እንዲት በእድሜ የገፉ ሚስኪን አባሮ በየቢሮው እየዞረች ምስጋና የምትቀላውጥ ገልቱ
ለመቅጠር ምድረ ጉማሬ ሚስኪኑን ላብ አደር ሰብስቦ አላዘነ፡፡ ደግሞ ስላዘመናዊነት
ያወራሉ፣ እግዚኦ አለቆቻችን ስለዘመናዊነት አወሩ፡፡ስልካቸው ባትሪ ሲጨርስ ተበላሸ
ብለው ሠሪ ቤት የሚሮጡ አለቆቻችን ዘመናዊነትን ሰበኩ፡፡ ከፕሪንተር የሚወጣ ወረቀት ደመና ሰንጥቆ እንደሚወጣ መልአክ በግርምት የሚመለከቱ፡፡ (አይ ፈረንጅ ነፍስ መፍጠር እኮ ነው የቀረው!' እየተባባሉ፡፡) እለቆቻችን ዘመናዊ እንሁን አሉ፡፡

እማማ መለኮት በጡረታ ስም ተባረሩ፡፡ (ተቀነሱ በል አቶ አብረሃም ተብያለሁ፡፡) ዙፋን
ተቀጠረች አሁን ድርጅቱ ዘመናዊ ሆነ፡፡ “እንደምን ዋላችሁ…”፣ “ሃይ ጋይስ” በሚል ሰላምታ .
በመተካቱ እልልል ቢሯችን ዘመናዊ ሆነ፡፡

ዙፋን የዘመናዊነት ፋና ወጊ፣ አንድ ገፅ ደብዳቤ ስትፅፍ አንድ ከግማሽ ገፅ ስህተት የምትዘራ
ጉድ፡፡ ወሬ ብቻ መሽኮርመም ብቻ፣ በየሰሙ ላይ “ዬ" መጨመር ብቻ (አብርሽዬ..ቶማስዬ.
ጋሽ ሰይድዬ ተፈራዬ... ሐጎስዬ.. ገኒዬ..እግዚያብሄርዬ..ጂሰስዬ_) እንደ ዬ ፈደል ትልቅ አፍ ብቻ
ያላት መርገምት፡፡ደህና ነገር ሲናገር ከንፈሩ እንደደረቀ ሰው በየደቂቃው ቻፕስቲክ እየተለቀለቀች በየቢሮው ማውራት !! (ውይ ጥርስ አታስከድንም፤ ተጫዋች ምናምን ይሏታል የሸረኛው መንጋ፡፡

ቆንጆ ብቻ መሆን እንዴት ይቃፋል፡፡ ሴት ብቻ በመሆን ከወንድ የሚቻር ወሲባዊ ክብር ምንኛ ውድቀት ነው?! ዕድሜ ከፍ ባለ ቁጥር የሚናድ የእንቧይ ካብ፡፡ እንዴት ሰውን ያህል ፍጥረት
ያውም እናትነትን ያሀል አደራ ትቀበል ዘንድ ተፈጥሮ የወከለቻት ሴት ስለጥፍር አንድ ሰዓት ሙሉ ታወራለች? ስለፀጉር ሁለት ሰአት፣ ስለጥፍር ቀለም ሙሉ ሸን፣ስለ ልብስ...

የመታየት ልክፍት (ኤግዝቢሽኒያም ይለዋል በሬቻ)፡፡ በፋሽን ስም ነጋቸው ላይ ውበት ሊዘሩለት ሚችሉትን ዛሬ አርሲ ኩርሲ የውበት ኮተት እያወሩ ይፈጁታል፡፡ ይሄ የሴት ውበት ነው የሴት ብክነት፡፡ ስለውበት የሚደሰኩር ሚዲያ ላይ አፍጥጣ የምትውል ዙፋን፣ ቆዳዋን በምናምን አደንድና ፍቅር እንዳይስርአት ራሷን ሳታዋድድ ትኖራለች። ሴት ከምልክ የተሻለ መወዳደሪያ በሌላት ውድድሩ ውስጥም የምትኖረው ቢበዛ ለጥቂት ዓመታት ነው፡፡ ባካና ! ዙፋን ባካና ናት፤ ስሟ ራሱ እሷ ላይ ሲደርስ 'ዙፋን' የሆነ፣ የመወዘፍ አይነት ደውል ነው፡፡ (ውዝፍ ከሚለው ስረወ ቃል የመጣ)

ከአለቃዬ ጋር በአይኗ ስትዳራ ስንት ጊዜ ታዘብኩ፡፡ እማማ መለኮትን ነቅላ ላትፀድቅ ነገር
ራሷን የተከለችበትን ቆሻሻ መንገዷን አይቻለሁ፡፡ ለፀሃፊነት ሥራ ውድድር መሰለፍ የማይችል
ባልጩት ጨንቅላቷ ላይ ሰው ሰራሽ ፀር ጎዝጉዛ ክቡር ሴትነቷን በየቢሮው ስትጎዘጉዝ ሳናይ
አላወራንም፤ “ጭስ ካለ እሳት አለ” ብለንም እይደለም፡፡ ቆይቶ የተደረገ ግምገማ ላይ የተገደደች
አስመስላ ቀባጠረችው እንጂ፡፡ (የሸረኞች መንገድ የተናደች" እለት)
👍192
#የመደርደሪያው_ጫፍ


#በአሌክስ_አብርሃም

አብርሃም !"

“አቤት”

“ስምህ ማነው ?” አለኝ ፊቴ የተቀመጠው ደግ ፖሊስ፡፡ ፊቱን ሳየው ማፏጨት ጀምሮ መሐል
ላይ ሲደርስ ሊያፏጭ የፈለገው ዜማ የጠፋበት ጎረምሳ ይመስላል፡፡ ስሜን ጠርቶ ስምህ
ማነው? ሲለኝ ቢጎርመኝም በትህትና ተናገርኩ፡፡

“አብረሃም”

“አ.ብ.ር.ሃ.ም”ፊደል የቆጠረ ፃፈ፡፡

የአባትህ ስም" ነገርኩት ጻፈ፡፡
“አብረሃም ! ለምንድነው የሰው ባል ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በሚዛን ስሀን የፈነከትከው”
አለኝ፡፡ አጠያየቁ 'ባትመልስልኝም ግድ የለም” የሚመስል ሰሜት ነበረበት፡፡

ኧረ ስላበሳጨኝ ነው እንጂ እኔ ሰው ጋር ተሰዳድቤ እንኳን አላውቅም፤ እንኳን በጭካኔ..
ዓረፍተ ነገሬ እየተወለጋገደ መለስኩ፡፡

“እሱማ ታስታውቃለህ፡፡ ጨዋ ልጅ ነህ፡፡ ጨዋ ባትሆን ኖሮ ሰሀኑ ላይ የተቀመጠውን አንድ ኪሎ መመዘኛ ብረት ትተህ በሰሃኑ ብቻ ኣትፈነከተውም ነበር፡፡ ጎበዝ ራስህን መግዛትህ ትልቅ ነገር ነው:: ራሱን የሚገዛ አገር ከሚገዛ ይበልጣል ይባላል፡፡ ቢሆንም ግን አብረሃም ዋስ ትጠራለሁ፡፡

“እሺ አልኩና ትዝ ሲለኝ የሚዋስ ሰው የለኝም፡፡

እንካ ደውልና ጥራ !" ብሎ ቅድም ወደ ማረፊያ ቤት ስገባ የተቀብለኝን ስልኬን ወደ ፊቴ
ገፋልኝ፡፡

ወደ አእምሮዬ የመጣችው ሂሉ ነበረች፡፡ ግን ሀሳቡ በራሱ ሳቁን አመጣብኝና ተውኩት፡፡ ባሏን
ፈንክቼ ሚስቱን ዋስ ሁነኝ ማለት በእርግጥ ያስቃል፡፡ ዝም ብዬ ዋስ የሚሆነኝ ሰው ሳወጣና ሳወርድ ቆየሁና "ዋስ የለኝም !" አልኩት ለደጉ ፖሊስ፡፡

እንዴት ዋስ አይኖርህም? ከሰው አልተወለድክም ? ጓደኛ የለህም? ወይም ጎረቤት ” አለ ፖሊሱ፡፡ እንዲህ ሲለኝ ዘመድም ጓደኛም የምለው ሰው እንደሌለኝ ትዝ አለኝና እንባዬ በዐይኔ
ግጥም አለ፡፡

“ደህና እስቲ የአንድ ሰው ስም ንገረኝ አለ ለመፃፍ እየተመቻቸ፡፡

“የአንድ ሰው ማለት?

"በቃ ዝም ብለህ የአንድ ሰው ስም ንገረኝ” አለ፡፡

"እበራ " ማረፊያ ቤቷ ውስጥ አበራ አንበሳው ! የሚል ስም በተወለጋገደ የእጅ ጽሁፍ አይቼ
ሰለነበር አፌ ላይ ድንገት መጣልኝ፡፡

“የአባቱ ስም ማነው ?"

"እኔ ንጃ ተገርሞ አየኝና ፈገግ ብሎ አጉተመተመ፡፡

“በቃ አበራ ቀለጠ ብዬዋለሁ - ዋስሀ ነው:: አብረሃም አምንሃለሁ፤ ጥሩ ልጅ ነህ፤ ይሄ መቼም
የዕለት ግጭት ነው:: ከአሁን በኋላ እዛ ሱቅ አካባቢ ብትደርስ ግን ዋስህን እቀፈድደዋለሁ፤

' ነግሬያለሁ” አለ እየሳቀ፡፡
እዚች ምድር ላይ ይኑር አይኑር በማይታወቅ ዋስ ከእስር የወጣሁ ሚስኪን ሰው፣ ቀበቶዬን
ተቀብዬ ከታጠቅኩ በኋላ ወደ ቤቴ አዘገምኩ፡፡ ፖሊሱ ያሳየኝ እምነት በጣም ነው የገረመኝ፡፡
ለምን እንደሆነ ባላውቅም ሰው ከመሬት ተነስቶ ያምነኛል፡፡ ሌባ ብሆን መቼም ባንዴ ሃብታም
ነበር የምሆነው፤ ሰዎች እንዲያምኑህ እና እንዲዘናጉ ማድረግ ትልቁ የሌብነት ጥበብ ነውና፡፡
ሰፈሬ ስደርስ ወደ ህሊና ሱቅ መንገድ ጀመርኩና ትዝ ሲሰኝ ደንግጬ መንገዴን ቀየርኩት፡፡ ሱቅ አካባቢ እንዳልደርስ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶኛል፡፡ ወይኔ ከሁሉም ከሁሉም ህሌናን ሳላይ መዋል እንዴት ያስጠላል?! ህሊናን እንዳላይ በህግ ተከልክያለሁ፡፡ ያ ፖሊስ በሕግ አላስፈራራኝም
ሕጉን ነው አእምሮዬ ውስጥ ተክሎ በፍቅር ያጠረው፡፡

ሂሉ እስካሁኝ በዱቄት የተበከለ ጋውኗን ስብሳ ፊቷ በሚነድ ሻማ የሆነ ነገር እያደረጋች ይሆናል፤
ወይም የለስላሳ ሳጥን ላይ ቆማ እንደ ነብር ሽንጧ ተመዞ የላይኞቹ መደርደሪያዎት ላይ ሳሙና
እየደረደረች ይሆናል፡፡ ስትንጠራራ እኮ ስታምር! ሰማይ ላይ በተቀመጠ ገብታ በሚያማምሩ
ጣቶቿ እግዜር ጋር ቼዝ የምትጫወት ነው የሚመስለኝ፡፡
ሂሉ የኔ ውብ ! የኔ ቆንጆ! የግርማ
ሚስት ፤ ሰው እንዴት ግርማን ያገባል በእግዚኣብሔር

ብቸኛ ነኝ ! ሁሉም ነገር የሰለቸኝ የሃያ ሰባት ዓመት ወጣት፡፡ ቤቴ እገባለሁ፤ እወጣለሁ ሶስት ዓመት ሙሉ እዚህ ሰፈር ስኖር የማውቃት ህሌናን ብቻ ነው፡፡ መንገዴ ላይ ሱቅ አላት፣ድምቅ ያለ ሱቅ፡፡ የሱቁ ድምቀት ህሊና ራሷ ሳትሆን አትቀርም፡፡

ህሊና ጨዋ ሴት ነበረች። እኔም ጨዋ ልጅ ነበርኩኝ፡፡ የህሊና ባል ግን ጨዋ ስላልነበረ ሊያሳሰተኝ
ሞከረ፡፡ ይሄ አሳሳች ደስ ይበለው፤ ተሳክቶለት ተሳሳትን፡፡ በእርግጥ ስሀተታችን ጣፋጭ ነበር፡፡

ለሚስቱ ሱቅ ከፍቶ ወንድ ደንበኛ በመጣ ቁጥር 0ይኑን ማጉረጥረጥ ተገቢ ነው? ገበያተኛ በመጣ ቁጥር የሚስቱን ፈገግታ መለካት እና ማታ ማታ በልክ ፈገግ በይ እያለ መነትረክ
እግዚር ይወደዋል? እሽ ይሄ ይሁን ግዴለም…ግን አብረሃም የሚባል ልጅ እዚህ ሱቅ ለምን ይመጣል ለሞላ ሱቅ?!” ብሎ መጠየቅ ከአንድ ባለ ሱቅ ይጠበቃል? ... መንግስት ሳያዳላ ሕዝብ
እንዲያገለግልበት በሰጠው ንግድ ፈቃድ እከሌ ይምጣ እከሌ ይሂድ ብሎ ሰው ይመርጣል?
እሺ (ሂሂሂሂ…ኧረ ይሄስ ያሳፍራል) ግን ሚስቱ ጋር፤ ቆንጅዬ ሚስቱ ጋር እቅፍቅፍ ብሎ ከመተቃቀፍም አልፎ መርፌና ክር ሆነው ሌላ ዓለም ውስጥ ሲዋኙ ድንገት የማይቋረጥ ነገር
አቋርጦ፣ “ለምንድን ነው አብረሃም ቲማቲም የሚገዛው? ማን ሊያበስልለት?” ብሎ ሚስቱን
ይጠይቃል፥ እንዲህ ይደረጋል ?

ሂሉዬ ብስጭት ብላ “ራሱ ይሰራላ” ስትለው፣ ራሱ እንደሚሰራ በምን አወቅሽ ?” ይባላል ?ለጥያቄና መልስ ይሄ ቦታው ነው ? ሰዓቱስ ነው ?

ባሏ ቀልቡ አይወደኝም፥ እቀፈዋለሁ፡፡ እኔ ሱቁ በር ላይ ስቆም ዐይኔን ላለማየት የማያየው ነገር የለም፡፡ የተደረደረውን ሳሙና፣ የተሰቀለውን ሙዝ፣ የተለጠፈውን "ዱቤ ክልክል" ነው የሚል ማስታወቂያ...ብቻ ማየት የቻለውን ሁሉ ፌቱን እጨፍግጎ ይቃኛል፡፡ አናቴን ሊፈነከተኝ ፈልጎ
ደህና መፈንከቻ ያጣ ነው የሚመስለው:: በዛ ላይ ሆነ ብሎ ህሊናን በወሬ ያጨናንቃታል፡፡
እንዳናወራ መከላከሉ እኮ ነው፡፡

እጃክስ አለቀ እንዴ?” ይላታል፤

ኧረ አለ!"

"ለስላሳ ዛሬ አላወረድሽም ?"

“ገና ትላንት እኮ ነው ያወረድኩት !”

በቃ የማይቀባጥረው ነገር የለም፡፡

እንግዲህ ስገባና ስወጣ ሰላም የምላት ብቸኛ ሴት ባለ ሱቋ ህሊና ነች፡፡ ሱቋ መንገዴ ላይ
ስለሆነች አስቤዛዬን የምሸምተው ከሷው ነው፡፡ ታዲያ ህሊና ጥሩ ልጅ ስለሆነች ነው መሰል
ከደንበኝነት ከፍ ያለ ቅርርብ ነው ያለን፡፡

ዛሬም ልክ ደመወዝ እንደተቀበልኩ ሄድኩ፤ ባሏ የለም፡፡ ሁለታችንም ደስ አለን፡፡

አንተ?" ትለኛለች፡

በቃ ስሜን ጠርታኝ አታውቅም፡፡ አንተ ነው የምትለኝ፡፡ እውነቱን ለመናገር ህሊና 'አንተ'
ስትለኝ ስሜን ያቀናጣችው ነው የሚመስለኝ፡፡ አብርሃም ሲቀናጣ 'አንተ ! በእኔ ጆሮ ብትሰሙት
በጣም ይገጣጠማል !!

ሰላም 'ሂሉ' ባሏ ከሌለ ሂሉ ነው የምላት፤ በእርግጥ አንዳንዴ እሱም እያለ ያመልጠኛል፡፡

“ምን ሆነህ ነው ዐይንህ የቦዘዘው” ትላለች በትልልቅ ዐይኗ እያየችኝ፡፡ ዐይኖቿ ዐይኔን
ይስሙኛል፡፡

“ዱቤ ልከፍል ስለሆነ ይሆናላ !”

በዚህ ሁኔታ መቀለድ መቻሌ ግዴላችሁም ብርቱ ሰው ብሆን ነው!

ሂሂሂሂሂሂሂሂ….ውይ አታስቀኝ ከምሬ ነው!” ትላለች፣ ስቃ ከወጣላት በኋላ እኮ ነው፡፡ ከዛም
የወሩ እዳዩን እንተሳሰባለን፡፡
"ዱቤ ክልክል ነው" ከሚለው ጽሑፍ ስር ያስቀመጠችውን የዱቤ መጻፊያ ደብተር ታወጣና
ቁልቁል በእስክርቢቶዋ እየጠቆመች “ካርድ የ 100 ብር ግን መቶ ብር ካርድ ምን ያደርግልሃል?
ወሬ እንኳን አታበዛ” ትላለች፤

ዳቦ

ዳቦ

ዳቦ ሰነፍ ስለሆንክ እኮ ነው ዳቦ የምትበላው ! ብቻ አንጀትህ እንዳይደርቅ ፤ ምናለ እንደ
ወንዶቹ እንቁላል እንኳን ብትጠብስ …" ትቀጥላለች፡፡

“…የተፈጨ ቡና…!
👍23👏1😁1
#የመደርደሪያው_ጫፍ

፡(የመጨረሻ ክፍል)
#በአሌክስ_አብርሃም


....ሳሙናዬን ተቀብዬ ወደ ቤቴ አዘገምኩ፡፡ በቀጣዩ ቀን ቅዳሜ ሂሉ እንባዋ ጠብ እስኪል እየሳቀች ሳሙናውን ገዝቼ ከሄድኩ በኋላ ከግርማ ጋር የተባባሉትን እንዲህ ስትል ነገረችኝ፡፡.አወራሯ
ድራማ ነው የሚመስለኝ። ሂሉ ሲበዛ ነፃ ነች፡፡

እንተ ” በሳቅ ፍርስርስ አለች፤

“ምን ያስቅሻል?”

"እይውልህማ…ብታይ…ትላንት ሳሙና ስጭኝ ስትለኝ ሰጥቼህ (ረዥም ሳቅ )..ሰጥቼህ ከሄድክ
በኋላ ግርምሽ ብስጭት ብሎ ሲነዘንዘኝ አላመሽ መሰለህ! ሆሆ!”

“ምን አነዛነዘው ?”

ነገረችኝ፤ ልከ እኔ እንደወጣሁ ግርማ ሂሉን ጠየቃት፣

".…እኔ የምልሽ! አብረሃም 'ሳሙና ስጭኝ' ነው ያለሽ አይደለም እንዴ?”

“እዎ እና እኔስ ሌላ ምን ሰጠሁት?”

“ምን እንደሰጠሽውማ አንችው ታውቂያለሽ”

“እንዴ! ግርምሽ ምን ማለትህ ነው?”

“የሳሙናውን ዓይነት አልተናገረም፡፡ እንዴት ዘለሽ እዛ ትንጠላጠያለሽ? እዚህ የገላ ሳሙና አለ፥ እዛጋ አጃክስ አለ፤ ላርጎ ፈሳሽ ሳሙና አለ፤ ምን እንደፈለገ በምን አወቅሽ ?”

ሂሉ ደነገጠች፡፡ ቢሆንም ኮስተር ብላ መለሰችለት፡፡

“ሁልጊዜ የሚወስደው ይሄንን ነዋ!"

“እስኪ እሱን የዱቤ ደብተር አቀብይኝ አለ፤ አቀበለችው፡፡ የወሰድኩትን ዝርዝር አየና የታለ
ሳሙና ወስዶ የሚያውቀው?” አላት በብስጭት፡፡

“እየከፈለ ነው የሚወስደው"

“ያሁኑን መቼ ከፈለ ?

“ኤጭ እንግዲህ አትጨቅጭቀኝ ! ወይ 'ሱቁን ዝጊና ቤት ተቀመጭ! በለኝ አለች ብስጨት ብላ፤

በዱቤ ደብተሩ ወርውሮ ሳታት፡፡ ከፀያፍ ስድብ ጋር “ሸርሙጣ!"

ይህን ሰትነግረኝ ሁለታችንም ከልባችን ሳቅን፡፡ ስቃ ስቃ ሲወጣላት “እንተ ምናለብህ ሳቅ ገብተህ በሰላም ለጥ ትላለህ፤ የሰው ትዳር እየበጠበጥክ ልክ ስለሌላ ሰው ትዳር የምታወራ ነበር የምትመስለው።

ባሏ ግርማ ከሌለ ወሬያችን መቆሚያ የለውም፡፡ እንደማልወደው ታውቃለች፡፡ እሱም እንደማይወደኝ ታውቃለች። ይሄ ነገር ሳያስቃት አይቀርም፡፡ ሰው ከመሬት ተነስቶ ይጠማመዳል?ሆሆሆ ትላላች። ከዛም ልክ የመጀመሪያው ወሬ አካል እስኪመስለኝ ሌላ ርዕስ ውስጥ ትገባለች፡፡

"አንተ እቺ ሸሚዝ አሁንም አለች?” አለችኝ ድንገት የለሰስኳትን ሸሚዝ በግርምት እየተመለከተች፡፡

"አዎ የት ትሄዳለች ?”

የመጀመሪያ ቀን እዚህ ሱቅ ስትመጣ እችን ነበር የለበስከው..ፀጉርህ ጨብረር ብሎ እዚች ጋ ቆመህ.ወረፉ ነበር፣ ሰው ሁሉ እያለፈህ ገዝቶ ሲሄድ እንተ ዝም ብለህ ቆመህ ..ሂሂሂሂ
ሌባ መስለከኝ፣ ስልኬን አንስቼ መሳሲያዩ ውስጥ አስቀመጥኩት ሃሃሃሃ…ከዛ በአንድ ዐይኔ አንተን
እያየሁ፡ በአንድ ዐይኔ ደንበኞቼን ሳስተናግድ ነበር፡፡…ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ !” አወራሯ ያስቃል፡፡ ሌባ ትመስላለህ እያለች እንኳን ታስቃኛለች።.ደግሞ የሚገርመኝ አሳሳቋ ሳቁ
እንሳቅ ዓይነት ግብዣ ነው በቃ !

ግርምሽም ሌባ ነበር የምትመስለው አሁንም ሐሳቡን የቀየረ አይመስለኝም፡፡
ሃሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂሂ…” ሁለተኛዋን አረፍተ ነገር ስራዬ ብላ እኔን ለማብሸቅ የጨመረቻት
ብትሆንም እያውቅኩም ተበሳጨሁ፡፡

"እናትክን በይው እሺ!”

"ሃሃሃሃ አንተ ባለጌ ስድ ባሌ እኮ ነው! ሂሂሂሂሂሂሂ…»

"እኮ ባልሸን እናትክን በይው!.…ማታ እቅፍ አድርገሽ ጉንጩን እየሳምሽ : መቼም ይሄ ማቀፍም
መሳምም አይገባው…'የኔ ቆንጆ አብርሃም እናትክን ብሎሃል እሽ ! በይው"

ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃም የሚያልፈው ሰው እየዞረ እስኪመለከት ሳቋን ለቀቀችው፤
እየሳቀች እንባዋ ሲፈስ ገርሞኝ ነበር፡፡ በቀጥታ እየሳቀች ማልቀስ መጀመሯን ያወቅኩት ወዲያው
ነበር፡፡

እንዴት እንደመረረኝ!” አለችኝ፡፡ ደነገጥኩ፡፡ ብሶቷን ዘረገፈችው፡፡

የሐረር ልጅ ናት፡፡ ዘጠነኛ ክፍል እያለች ይሄ ያሁኑ ባሏ ግርማ ወታደር ሆኖ ሰፈራቸው የነበረ
ካምፕ ውስጥ ይኖር ነበር፡፡ ያኔ ተጫዋች፣ ወንዳወንድ፣ በቃ የሚፈቀር ሰው ነበር፡፡ ለጓደኝነት
ሲጠይቃት አላንገራገረችም፡፡ “
ይዤሽ ልጥፋ!” ሲላት አምናዋለች፡፡ ካለ እናት ያሳደጋትን አንድ አባቷን ጣጥላ ይሄን መዶሻ ራስ ተከትላ እዲስ አበባ ገባች፡፡ እናቱ፣ እህቶቹ፣ ወንድሞቹ
ሳይቀሩ አተካኗት፡፡ ለጎብረት ያገቧት ይመስል በትዳሯ እየገቡ መፈትፈት ጀመሩ፡፡ ነፃ ሆኗን
አለሌነት፣ ሳቋን የሽርሙጥና ደውል አድርገው ዐይንሽን ላፈር አሏት፤ እንደ አዲሳባ ሰው በሯንም
ጥርሷም በልኩ መከፈት ያላደገባትን፡፡ ሚስኪን ! ልለማመድህ ብትለውም አልሆነላትም፡፡

" ኤጭጭ አቦ እንደፈለጉ ይሁኑ!" ብላ ሳቋንም ነፃነቷንም ተያያዘችው፡፡ ይባስ ብሎ ሳቋ ማርኮት እንዳልወደዳት “ሳቅሽን አቁሚ!“ አላትና አረፈው!! ብዙ ባሎች የባል ድንበሩ የት ድረስ እንደሆነ አያውቁም፡፡ ትንሽ ባሎች ደግሞ ድንበራቸው ላይ ሳይደርሱ ይቆማሉ፡፡

አባቷ እሷን ፍለጋ ተከራትቶ ተንከራትቶ ሲሞት አፈር አላለበሰችውም፡፡ የሐረር ሰው ውሎ ይግባ አልቅሶ ቀበረው፡፡ በምድር ላይ የነበራት አንድ መሸሻ ዋሻ ተደፈነ፡፡አሁን ግርማ መድረሻ
የሌላት ከንፏ የተሰበረ ወፍ አደረጋት። “በየመንገዱ ስታገጭ ነው ያገኘሁሽ" አላት ፣ እንደ
ሚስት ሳይሆን እንደ ሰራተኛ ከፍ ዝቅ አድርጎ ያዝዛት ጀመረ፡፡ ያኔ ካስቀመጠባት መንበር ጎትቱ
አወረዳዳት፡፡ ለሴት ልጅ ትልቁ ከብሯ ቤተሰቧ መሆኑን አመነች፡፡ ለምን አፈር ጠርጎ የሚተኛ
ደሃ አይሆንም ቤተሰብ አለኝታ ነው ! ፍቅር ይወጣል፣ ይጠልቃል፡፡ እቃ ! የሰው ፍቅር እንደ ፀሐይ ምስራቅና ምዕራብ አለው:: እየጣፈጠ ወጥቶ፣ እያቃጠለ ይጠልቃል! ቤተሰብ ግን ሰማይ ነው:: የሕይወት ፀሐይና ጨረቃ ሰፈራረቅ የማይቀያየር፣ የማይጠልቅ፣ የማይጠቀለል ቦታውንም
የማይቀይር ሰፊ ሰማይ ማለት ቤተስብ ነው፡፡ ሂሉ ቤተሰብ የላትም፡፡ ሰማይ የለም፡፡ ቀጥ ስትል ኦና ነው ባዶ ነው ! ኮከብ የለም፣ ጨረቃ የለችም፣ ፀሐይም የለችም፡፡ ሰማይ በሌለበት
ምንም የለም፡፡ እግዜር የት ይሆን መቀመጫው ? የት ሆኖ ይሆን ይህን ጉድ የሚመለከተው?!

የአዲስ አበባ ኑሮ አንሸገሻት። ለምሬቷ ጣዕም ኮሶ የጨመረው ባሏ ነው:: “ታምናለህ…. ከሳመኝ
ስንት ጊዜው ? አለችኝ፡፡ ግን እወደዋለሁ ! ስድቡ፣ ማቃለሉ እያቃጠለኝ እንኳን እወደዋለሁ !

ሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃሃ አንተ እስለፈለፍከኝ :" አለችና ሳቋን ለቀቀችው:: የኔ ሚስኪን !!
ባለፈው ሐሙስ ደግሞ ሂሉ ወደኔ ጠጋ ብላ ፊት ለፊቴ ቆመች::መሐላችን ላይ ሚዛኑ አለ፡፡ ፊቷ ልክ አልነበረም፡፡ ቶሎ እንድሄድባት መፈለጓ በግልፅ ያስታውቃል፡፡

አንድ ትንሽ ልጅ መጥቶ "ሳሙና ስጭኝ ! ቢጫውን አላት፤
“የለም " አለች፣ ግን ፊት ለፊት ተደርድሮ ነበር፡፡
ሌላ ሴት መጣችና “ስኳር ስጭኝ ሕሊና ኣለቻት፡፡
“የለም !" ፈት ለፊት ኩንታል ስኳር ተቀምጧል፡፡ ገርሞኝ ጠየቅኳት፡፡
“ሂሂሂ.አንተ ካልሄድhልኝ በስተቀር ምንም ነገር አልሸጥም ዛሬ እየቀለደች መስሎኝ ነበር።
“ማሪያምን !" ስትለኝ የላፕቶፕ ቦርሳዬን እንስቼ፣ “በይ ቻው !” አልኳት፡፡
“ቻው አብርሽ !" አለችኝ በቅሬታ ፈገግታ፡፡ “አብርሽ ብላኝ አታውቅም፤ ግራ ገባኝ፡፡
በቀጣዩ ቀን ሂሉ የለችም ነበር፤ ባሏ ተገትሯል፡፡

"ሰላም ዓርማ"
“ምን ልስጥህ?” አለኝ ኮስተር ብሎ፣
"ኮካ"
"የለም"
"እሺ ቀዝቃዛ ሰፕራይት አድርገው"
"የለም"
👍32👎2
#አለሁላት…!


#በአሌክስ_አብርሃም


እናቴ ሁልጊዜ ሁለት እጆቿን ወደ ሰማይ ዘርግታ እግዜርን እንዲህ ትለዋለች፣
“አብርሽዬ የሚያገባትን ሴት ሳታሳየኝ እንዳትገለኝ፡፡


አገባሁ !
እናቴ እለት እጆቿን ወደ ሰማይ ዘርግታ እግዜርን እንዲህ አለችው፣

“ምነው ይሄንንስ ከሚያሳየኝ በገደለኝ

ሀና ምንተስኖት ትባላለች የምኮራባት ሚስቴ፡፡ እወዳታለሁ፣ አፈቅራታለሁ፡፡ ክፉ ነገር በሰፈሯ
እንዲያልፍ አልፈልግም፡፡ ሀኒዬ የእኔ ጥሩ ሱስ፣ ካላየኋት ያዛጋኛል' ስል ሰዎች አያምኑኝም፤ ሀኒ
የእኔ ልብ፣ የጠላችው ጠላቴ ነው:: ይሄ አባማ የሚባል ሰውዬ በቴሌቪዥን ያደረገው ንግግር
አስጠላኝ ብትለኝ፣ ሲ አይ ኤን ሳልፈራ፣ ኤፍ.ቢ.አይን ከቁብም ሳልቆጥረው ኦሳማ ላይ የግድያ
ሙከራ ባደርግ ደስታዬ ነው:: እንቅ አድርጌ አይኑን አፍጥጦ፣ “ኧረ አብርሽ በእናትህ የዛሬን
ማረኝ..ሁለተኛ በየትኛውም ሚዲያ ከመቅረቤ በፊት ንግግሬን ለሀና ምንተስኖት ኣሳውቃታለሁ..
ካልፈቀደችልኝ ኣላደርጎውም” ቢለኝ አልምረውም፡፡ እማምላክን አልምረውም !!

ሀናዬ የነብሴ ፍራሽ…ላያት ድሎቴ ናት። ሀና ካዘዘችኝ…አቤት ፍጥነቴ ገና ልትናገር ስትጀምር እኔ ሮጫለሁ፡፡ አልጋ ላይ ጋደም ብላ ቴሌቪዥን እያየች እኔ ቆንጆ ቡና እያፈላሁላት…የሆነ ነገር ብትፈልግል ልትናገር ስትጀምረው ነገሩን አምጥቼዋለሁ ፡፡ ለምን ትጨርሰዋለች.…ቃሏ ፍቅር
ነው..ፊደሎቾ እንደ ረሀብ ቀን እህል ያሳሱኛል፡፡

“አብርሽ " ስትለኝ በቦታህ!' እንዳሉት ሯጭ እዘጋጃለሁ፡፡ ወደ መሻቷ ተፈትልኮ በምድር
ላይ ያሉ ወንዶች ሁሉ የሚሰቶቻቸውን ፍላጎት ካሟሉበት ሰዓት የተሻለውን ለማስመዝገብ፡፡
"ድ." ብላ ስትጀምር ፈትለክ ብዬ ድስት…ድራፍት…ድንች ድልህ...ድፍድፍ (ከእማማ ፈጠኑ ቤት ድመት...ድንጋይ..ድራማ (ሲዲ) ይዤላት እያለከለኩ ከተፍ ስል፣ "ውይ አብርሽዬ…በቲቪ ድብ አይቼ ድቡን እየው ልልህ ነበር እኮ" ትለኛለች በፍቅር ዐይን እያየችኝ...!! አይከፋኝም ለምን እከፋለሁ፡፡ እንደገና ድብ ባየችና “ድ ብላ ስትጀምር፣ አሁን ባመጣኋቸው ነገሮች ላይ
ድብ ጨምሬ ባመጣሁላት..የእኔ ሀኒ መክሊት ብያታለሁ፡፡ እሷ ናት ቀኝም ግራም ጎኔ፡፡

ሀኒዬን እናቴ አትወዳትም፡፡ “አንዳች አስነክታው ነው ልጄን እቺ የሰው ጉድ” ትላታለች፡፡
አባቴ ገና ሲያያት የእናቱ፣ የአባቱ፣ የሁለት እህቶቹ ገዳይ ነው የምትመስለው አቤት ሲጠላት፡፡ በወሬ ወሬ “መንገድ ላይ አብረሃም እና... ሲሉት፣ "በቃ " ብሎ ይጮሀል።አብርሃም ካላችሁ አይበቃም….እናን ምን አመጣው?” ይላል፡፡ ያውቃል ማንም ጋር እንደማልታይ፤
ሀኒ ጋር ነኝ ቤት ውስጥ የምትበላውን እየሰራሁላት፡፡ ሀኒ ጋር ነኝ መንገድ ላይ ቦርሳዋን ይዤላት፤….ዣንጥላዋን ይዤላት ዕቃ ከገዛን አስቤዛም ቢሆን እኔ ይዣላት ሀኒ ጋር ነኝ የትም!!

ሀኒን እህቴ አትወዳትም፡፡ ከዘመናዊ ጓደኞቿ ጋር ሆና ከሩቅ ካየችኝ በሬ እንዳሯሯጠው ሰው መንገድ አሳብራ የጓደኞቿን እጅ እየጎተተች ትሸሻለች፡፡ “ወንድሜ በሬ አገባ” እያለች ነው የምታወራው አሉ!

ወንድሜ ሀናን አይወዳትም፡፡
"ለስንት ስንጠብቅህ እዚሂች አዚፋ ጋር ትወዘፋለህ” ይለኛል፡
&አዚፋ' ምን እንደሆነ አላውቅም፡፡ ግዴለም ሀኒዬ 'አዚፋ ከሆነች፣ አዚፉ ይባረክ ! ስድብ ሰውን ካረከሰው፡ ሰው ስድቡን ስለምን አያከብረውም? ሀኒዬ አዚፉን አከበረች… እወዳታለሁ፡፡

ሀኒ ቆንጆ አይደለችም፡፡ የኔ ቆንጆ፣ ቆንጆ አይደለችም፡፡ "ኪንኪ ፀጉሯ ጠዋት ስትነሳ ያስፈራል”
ይላሉ፣ አዎ እውነት ነው፡፡ “አፍንጫዋ በአይኗና ቀላይኛው ከንፈሯ መካከል ያለ ሁለት የሽንቁር ነጥብ ነው እያሉ ያሟታል…እውነት ነው !!

ከንፈሯ ወጣ ወጣ ባሉ ጥርሶቿ (ገጣጣ ነው እነሱ የሚሉት) ከርስቱ ተገፍቷል፡፡ በዛ ላይ
ብትስቅ ዞሮ ማጅራቷ ላይ ይዘያየራል ይላሉ፡፡ አዎ እውነት ነው !!

የጣቶቿ መዶልዶም ከዘጠኝ ዓመቷ እስከ አስራ ዘጠኝ ዓመቷ 10000000000000000000
ኩንታል ገብስ ሳታቋርጥ የወቀጠች ያስመስላታል" ቢሉም (ተጋነነ እንጂ) እውነት ነው !!

“እግሯ ከየትኛውም ጫማ እንዲጣላ ተደርጎ ነው የተፈጠረው” ያሉትም አልዋሹም፡፡

lዚህ ሁሉ መናቅ፣ በዚህ ሁሉ መገፋት ተገፍታ እኔ የምባል ጥግ ላይ ደረሰች የሀኒ ዓለም
መጨረሻ፡፡የት ትሂድላቸው? አለሁላት ወንድሟ ነኝ:: ፍቅረኛዋ ነኝ፡፡ባሏም ነኝ!! አላፍርባትም፡፡
ኮራባታለሁ !! ሀኒዬ የኔ ናት:: ማነው እኔን አልፎ የሚዘልፉት ወንድ ?' የኤሌክትሪክ አጥሯ
ጠባቂ ውሻዋ ነኝ፡፡ ከእግሯ ስር የማልጠፋ::ባለቤቱ ያላከበረው አሞሌ፡ ወላ መልኩ ወላ
ዘመናዊነቱ አያስከብረውም፡፡ አንዱ የወረወራቸው አይደሉ ሌላኛው መኪና ላይ የሚኮፈሱት!
የተናቁ አሞሌዎች !! ሀኒዬን አከብራታለሁ !! እግዜር ያውቃል ልቤን !!

“ጥርስሽ አያምርም ቢሏት ከሳቅ ተጣላችላቸው፡፡ ሰው ፊት አትስቅም ሀኒ፡፡ የመጻፍ መብታችን፣የመሰለፍ መብታችን ተነካ የሚሉ የአገሬ ልጆች፣ የህኒዩን የመሳቅ መብት በአደባባይ ነጠነቁ፡፡እስካሁን ሻይ ቡና ለማላት ካፍቴሪያ መግባት ያስፈራታል፡፡ ራሷ ቤት ውስጥ ስትቀመጥ እንኳን እግሮቿን ሶፋ ስር ልትደብቅ ይከጅላታል፡፡ በመንገድ ዳር ዘለፋ መሳቀቅን ሸልመዋታል፡፡ ሰው ለሰላምታ ስትጨብጥ ትሳቀቃለች፡፡ የመዳፏን ሻካራነት በየጭብጡ የሚጮኸ አዋጅ አድርገው
ልቧ ውስጥ ተክለውባት፡፡

ሆኒዩን ቆንጆ ካልሆንሽ ሰው ከመሆን መንበር ተንኮታኩተሻል” ብለዋታልና ቆንጆዎች አምላክ
ይመስሏታል፡፡ የሴት ልጅ የክብር ጥጉ በየሆቴሉ ወንበር ተጎትቶላት መቀመጧ ነውን ? በአደባባይ
መታቀፍስ የፍቅር ኦሜጋ ሆኖ የታወጀው መቼ ነው ? እየተውረገረጉ የወንድ ጭብጨባ
ያደነቆራቸው ሀኒዬን ቃል ሳያወጡ በድርጊት ቀበሯት፡፡

አነሆ ለአንዲት ደሀ.ለአንዲት መልከ ጥፉ ደሀ ተልኬ የምታስተናግድበት ተራ ሻይ ቤት ተከሰትኩ፡ ያውም 'አዩኝ' ብሎ የሚቆሽሽ ነጭ ሸሚዝ ባማረ ጂንስ ሱሪ ለብሼ፣ ጥቁር መነፅሬን ሰክቼ እየተቆነንኩ በረንዳው ላይ ካሉት ወንበሮች በአንዱ ላይ ሰፈርኩ፡፡

“ምን ልታዘዝ!” አለች ሀኒዬ እየተሸቆጠቆጠች፡፡ ሳያት ላማትብ ቃጥቶኝ ነበር፡፡ እግዜር ሰውን
የት ድረስ ውብ እንደሚያደርግ አውቃለሁ፡፡ የት ድረስ መልከ ጥፉ አድርጎ እንደሚፈጥር እነሆ
የእጁን ውጤት ፊቴ አቁሞ አሳየኝ፡፡ “አቤት ችሎታው ምን ይሳነዋል!” አልኩ ::

ስራዬ በዛው ግድም ነበርና ደጋግሜ ሳያት ከቀን ወደቀን እየባሰ የሚሄድ ይሄ ጎደለው የማይባል ፍፁም የሆነ አስቀያሚነት እንዳሸከማት እየተገረምኩ ታዘብኩ፡፡ ግና የገረመኝ፣ “አቤት ስታስጠላ
እያልኩ ላያት መፈለጌ ደንበኛ ሆንኩ፡፡

“ምን ልታዘዝ?"

"ቡና"

"ምን ላምጣልህ?"

“ቡና”

“ሰላም! ምን ላምጣልህ?”

“ቡና”

“ቡና ነው ዛሬም” (ፈገግ ለማለት እየሞከረች)

"አዎ" (በፈገግታ)

ከዛ ሳላዛት ቡና አመጣችልኝ…ቡና..ቡና….ቡና.…ሰላምታ ሀና ነው ስሟ፣ አንድ ቀን ጠየቅኳት…
ነገረችኝ፡፡ ስራ ከሌላት አጠገቤ ትመጣለች እናወራለን…እንዴት ደስ እንደምትል፡፡ ትልልቅ ጡቶቿን አልፎ ልቧ ይታያል ንጹህ ነው !

አንድ ቀን ከጎኔ የተቀመጡ ተስተናጋጆች "የሰው ጅብ” ሲሏት ጆሮዬ ጥልቅ አለ ያዘዝነው ዘገየብን ብለው !! በመሰደቧ ሳይሆን እኔ ፊት በመሰደቧ
በመሰደቧ የቅስሟ መስተዋት
ክፍት አፍ በወረወረው የዘለፉ ጠጠር ሲንኮታኮት ፊቷ ላይ እንዴት አንጀት የሚበላ መሳቀቅ አየሁ፡፡ ተሳዳቢዎቹ ጋር
የነበረች አንዲት ሴትም ላንቃዋ እስኪላቀቅ ሳቀች፡፡ አዘንኩ፡፡ ለምን አዘንኩ እኔንጃ !!
👍30😁4