አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የድንቄ_ኑዛዜ

አባ ምንተስኖት እና የሰፈር አዛውንቶች ለምን የጎረቤታችንን የድንቄን ኑዛዜ እንድንሰማ እንደፈለጉ ለጊዜው አልገባንም፡፡ ድንቄ አለኝ የምትለው ልጅ እስከ አሁን ብቅ አላለም፡፡ በሰፈሩ ውስጥም እሱን ያየ ወይም ስለሱ የሰማ የለም፡፡ የንስሐ አባቷ የሆኑት አባ
ምንተስኖት ድንቄ ለልጇ የሰጠችውን ኑዛዜ ሊያሳውቁን በቦታው እንድንገኝ ባደራ ጭምር አስጠንቅቀውናል።

አባ ምንተስኖትንና የማናውቀውን የድንቄን ብቸኛ ወራሽ ልጅ በጉጉት መጠበቅ ጀመርን፡፡ ሁሉም የራስ የራሱን ወሬ ይዟል፡፡እኔም አልፎ አልፎ እነሱ የሚያወሩትን እያዳመጥኩ በራሴው
ትዝታ እቆዝማለሁ፡፡

ድንቄ እንደ ጎረቤቷ ሳይሆን እንደ ልጇ ትወደኝና ትንከባከበኝ ነበር፡፡ እናቴም ድንቄ ለኔ ያላትን ታላቅ ፍቅር ስለምታውቅ ሁልጊዜም ብሄድ አትከለክለኝም፡ስትሞት
ልቆጣጠረው የማልችለው ጥልቅ ሀዘን ተሰምቶኛል፡፡ ድንቄ በዐይነ ህሊናዬ አዘውትራ ትመጣለች።

የሚያብረቀርቀው ወዟ በጥቁር መልኳ ላይ ሲታይ ፈጣሪ በጥሩ ቅባት ሲወለውላት አድሮ የዋለ ይመስላል፡፡ ዐይኗ የጥንታዊ ስዕሎችን ዐይን አይነት የነጻና ቦግ ያለ ነው። ከንፈሮቿ ሁሌም
ያስደንቁኛል፡፡ በላይኛው ከንፈሯ ብቻ መኸል ለመሀል አግዳ መስመር ቢሳልበት ራሱን የቻለ የአንድ ሰው ከንፈር ይወጣዋል ረጅምና ወፍራም ናት።

“አመድዬ አመዶ መርሻ! መርሻዬ የኔ መርሻ” የኔን ስም እያቆላመጠ ጮክ ብሎ በጎረነነ ድምጽ የሚጣራ ሰው ከድንብ
በስተቀር ማንም እንዳይደለ የታወቀ ነው፡፡

አቀበቱን ጨርሳ ዘቅዘቅ ያለውን የቡሐ መንገድ ስትጀምር እጇን እያጋጨችና ያለርህራሄ በኃይለኛ እርምጃ ቡሐ ድንጋዩን እየደቀደቀች ከመንደር ስትደርስ፣
“መርሻ! መርሻዬ የኔ መርሻ...” እያለች የኔን ድምጽ በጎረነነ ድምጿ ትጣራለች፡፡

ከሰፈር ውስጥ ካሉ ልጆች ሁሉ መርጣ እኔን እንዴት እንደ ወደደችኝ ከድንቄ በቀር ማንም የሚያውቅ የለም። ምናልባት የራሴ የሆኑ ግምቶች አሉኝ፡፡ ድንቄ የሚያዳምጣትን የሚያጫውታትን
ትወዳለች፡፡ በተጨማሪም ደግሞ፣
“ሌሉቹ ልጆች በልተው ስለሚሄዱ አልፈልጋቸውም።
ለሆዱ ብቻ የማይቀርበኝ አመዶ ብቻ ነው::” ስትል ሰምቻታለሁ።እኔም ደግሞ የአቅሜን ለሷ ከማድረግ ቦዝኜ አላውቅም። ሳላያት ከዋልኩኝ ትናፍቀኛለች። ብርጉድ ብርጉድ የሚሸት ልብሷንና ገላዋን እወድላታለሁ፡፡

ሁልጊዜም እቤታችን ስትመጣ የምትለብሳትን ነጠላ ሳብ አድርጌ አሽትና፣ አንዳንዴም በነጭ ጨርቆች መጣፉ ስለሚገርመኝ፣
“በነጠላ ላይ ነጠላ ይጣጣፋል?” ስላት ወደኔ መቀመጫ በእጇ እያመለከተች "ያንተ ቂጥ ብቻ ነው የሚጣፍ አሐዶ ትለኛለች።"

ደግሞ ሌላ ስራ እሰራለሁ። ከፊቷ ላይ ያለውን ወዝ ጥርግ አደርግና አመድ የመሰለውን እግሬን እባብሰዋለሁ

“አመዶ ተቀባ የኔ ወዝ እንኳን ላንተ ላስር አመዳም ይበቃል፡፡ እ...” ትለኝና ትስቃለች፡፡ ስትስቅ ደስ ትላለች። ጠቅላላ
ፊቷ ላይ ያለው ስጋ ተሰብስቦ ጉንጫ ላይ ይመጣና ይከመራል፡፡ ሳቋ ሳያልቅ የተጠራቀሙ ጉንጮቿን እይዛቸዋለሁ። እሷም ይህንን ስለምታውቅ እንደፈገገች ትቆያለች።

እሷን ከማጫወት ውጭ ሲደክማት የስሙኒ ቫዝሊን እገዛላትና እግሯን ከታጠበች በኃላ በትናንሽ እጆቼ እያሻሽሁ እሷን ማስደሰቴ አይቀርም፡፡

የድንቄ መሳቅና መጫወት ብቻ ለኔ በቂ ደስታ ነው፡፡ሁልጊዜ ድንቄ ስትጣራ ያለአንዳች ከልካይ እወጣለሁ። እሷም ያንን ለምዳዋለች፡ ሮጬ ካልወጣሁ ገስግሳ መጥታ፣ “አመድየ ምን ሆኖ
ነው?” ትላለች።

“እትዬ ድንቄ ምናለ አመዶ ባትይኝ?” እያልኩ ስወተውታት “ምን አይነት ስም ላውጣልህ አመድዬ?” ትልና እንደተለመደው ራሴን ታባብሳለች፡፡

አባ ምንተስኖትና በጉጉት የሚጠበቀው ልጅ አልመጡም፡፡
እናቴና ጎረቤቶቿ የማያቁትን የድንቄን ልጅ እያሽሟጠጡ ያወራሉ፡፡
“አበስኩ ገበርኩ እቴ! እስከዛሬ አይዞሽ ያላላት ልጅ ምን አይነት ይሆን?” አለች እናቴ፣ ሌላኛዋ ጎረቤታችን ቀጠሉ፡፡
“እኔ ብሆን ለማላውቀው ደሃ አወርሳለሁ እንጂ አንድም ቀን መጥቶ አይዞሽ ላላለኝ ልጅ...አላደርገውም።”

“እኛ የምናውቀው እሷንና ይሄን ቤት ያወረሷትን አክስቷን ብቻ ነው። እሷም እኮ የመጣችው እሳቸው ታመው ነው፡፡ እኔና
አክስቷ ይህን መሬት ከመመራታችን በፊት ሌላ አካባቢ አብረን ነበርን፤ ያኔም ቢሆን እሳቸውን ብቻ እንጂ ድንቄን አላውቅም፡፡
ድህነት ያዛትና ቤቱንም አስፋፍታ ሳትሰራ እሳቸው ያወረሷትን አንድ ክፍል ቤት ይዛ ኖረች፡፡ ግቢውን ከፍላ ሸጣ እንኳን ጥሩ ኑሮ ብትኖር ጥሩ ነበር።” አለችና እናቴ የጎረቤቶቿን ወሬ በተራዋ ማዳመጥ ጀመረች፡፡

ድንቄ የምትቀመጥበትን ሶስት እግር በርጩማ እናቴ ተቀምጣበታለች። ድንቄ ስትቀመጥበት መቀመጫዋ በሁለቱም ጎን ይተርፍና ሊወድቅ የተንጠለጠለ ይመስላል። ይህን ትርፍ መቀመጫዋን አልፎ አልፎ መዳበስ ትወዳለች።

አይኔን ሳዟዙር የድንቄን ምግብ ማቅረቢያ፣ በአለላ የተሰራ ስፌት አየሁና ምራቄን ዋጥኩኝ፡፡ ለምን የጨጓራ መረቅ
እንደማያንጠባጥብ ይገርመኝ ነበር፡፡ በልቼ እስከምጨርስ መረቁን ይዞ ይቆያል። ከዚያም ማወራረጃ ውሃ አያሥፈልገኝም።

ድንቄ ጠዋት ተነስታ መተዳደሪያዋ ወደ ሆነው ወደ ልብስ አጠባ ከመሄዷ በፊት የምታደርገው ነገር ቢኖር ገብሩ ስጋ ቤት
መሄድ ነው። ድንቄ የምትፈልገውን መናገር አያሥፈልጋትም፡፡ እንደደረሰች ገብሩ የምታወራውን በፈገግታ እያዳመጠ ጨጓራ በወረቀት መጠቅለል ይጀምራል ። ድንቄ ተቀብላ በእጇ እንደ መመዘን ታደርገዋለች።

“እኔኮ የራሴ ሚዛን እያለ የእጅሽ ሚዛንነት አይገባኝም?”ይላታል፤ አታዳምጠውም፡፡

ነገ ያልቃል

ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍3
#ዘመናይ_አፍቃሪ

እሙ
እንደምወድሽ እያወቅሽ አይንህን ላፈር ብለሻል
አንድ ነገር ልንገርሽ? :
ብታፈቅሪኝ ይሻልሻል!!!

ምን መሰለሽ
የፍቅር መዝገበ ቃላት መፅሃፉ እንደሚያስረዳው
ሰውን ከማፍቀር በላይ መፈቀር ነው የሚጎዳው።

"ለምን?”
ያፈቀረ አንዴ አፍቅሯል፤
ራሱን ለፍቅር ሰጥቷል፤
ክብሩን ለሰው ሰውቷል፡፡
ለስሙ አይጨነቅም፤
ለመከተል አይሳቀቅም፡፡
ለተፈቃሪ ነው እዳው፤
ተፈቃሪ ነው የሚጎዳው፡፡

"እንዴት?”
(እንዴት ማለት ጥሩ)
ለምሳሌ እኔ (አንቺን)
በምትገቢበት እየገባሁ፣
በምትወጭበት እየወጣሁ፣
ስትበይ እያየሁሽ፣
ስትጠጭም እያየሁሽ፣
መንፈስ ሆኜ ከማሳቅቅሽ፣
ሁሌም እንደምነግርሽ፣
ብትወጅኝ ነው የሚሻልሽ!!!

እ.ደ.ግ.መ.ዋ.ለ.ሁ!

ዳናሽን እየተከተልኩ፣
ስራሽን ሁሉ እየሰለልኩ፣
የምትበያቸውን ምግቦች፣
የምትለብሻቸውን ልብሶች፣
ያወራሻቸውን ሰዎች፤
በምን ሳሙና እንደታጠብሽ
ምን አይነት 'ፓንት እንዳደረግሽ..
እየነገርኩ ከማሳቅቅሽ
ለኔ ስትይ ሳይሆን ለራስሽ
ብትወጅኝ ነው የሚሻልሽ!!!
እህስ
ምን ታስቢያለሽ!!???😳

🔘በሙሉቀን🔘
#የኔ_ነገር

የተሰበረ አጥንት የተከሰከሰ
መሬት ውስጥ ተቀብሮ አፈር የለበሰ፣
እቆጥራለሁ አጥንት
ዛሬ ላይ ቁጭ ብዬ እያሰብኩ እንደ ጥንት፡፡

አፈር ሆኖ ኖሮ ወደ አፈር የገባ
ደርቆ የሻገተ ሽታው ማያስጠጋ፣
እመትራለሁ ስጋ
ስለራሴ ሳላውቅ ስለ ሙት ሳወጋ፡፡

ወይ የደረቀ አጥንት ጋሻ ላይሰራልኝ
የሻገተ ስጋ ምግብ ላይሆንልኝ፣
ስጋየን ስመትር፣
አጥንቴን ስቆጥር፣
ተቆጠሩ አመታት ነጎዱ ዘመናት - ለራሴ ሳላድር ፤
በሙታን ሳቅራራ በሙታን ስፎክር፡፡
ዒድ ሙባረክ | Eid Mubarak 🌙

በቻናላችን ለምትገኙ የእስልምና ዕምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1442ኛው ለዒድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን በዓሉ የሰላም የመከባበር እና የአብሮነት እንዲሆን እንመኛለን።
#ተስፋ

ወቅቱ ክረምት ነው::
ዝናቡ ይዘንባል፣
በረዶ ይጥላል።
ቀኑ ብርዳማ ነው ፤
ሙቀት የናፈቀው::

በዚህ የቁር ዕለት
ሰው በማይወጣበት
ህይወት ያለው ፍጡር -
በአውራ ጎዳናው ላይ - በማይታይበት::
ቀዝቃዛ ቤቴ ውስጥ - ዱካክ ባናወዛት
የቆንጆ ሴት አምሮት - በሚወዘውዛት ፤
በበረደው ቤቴ - ትኩስ አካል ይዤ
በይሆናል ምኞት - በሃሳብ ናውዤ
በጠባብ መስኮቴ - አንገቴን መዝዤ...
ወደ ውጭ አያለሁ፡-
ምናልባት የኔ ውድ!
የእህል ውሐ ነገር
ምኑ ይታወቃል?

የፍቅር አምላክ ደጉ - ከዝናብ ሊያስጥልሽ
ወደ ተከፈተው - ወደ ባዶው ቤቴ
ያስገባሽ ይሆናል፡፡
ዝናቡ ከባድ ነው፣
ማንም የማይደፍረው፡፡
ወጨፎው ይነፍሳል፣
ውሐና በረዶ በበሬ እየገባ -ወለሌን ያርሳል፡፡
ግን መኖሪያ ቤቴ- መዋኛ ቢመስልም
ውስጤ ተስፋ አለና- በሬን አልዘጋሁም፡፡
“ምናልባት የኔ ውድ! -
የእህል ውሐ ነገር
ምኑ ይታመናል?
ወደ እኔ ስትመጭ-
በሩን ከዘጋሁት -
ሰው ያለበት መስሎሽ-
ትዘይኝ ይሆናል!
ብየ ስለማስብ
አለሁልሽ ውዴ፡-
ዝናብ እየመታኝ - ቤቴ እየበረደው
ትመጫለሽ ብዬ - ደጅ ደጁን እያየሁ፡፡
አለሁልሽ ውዴ....

🔘በሙሉቀን🔘
👍1
#የድንቄ_ኑዛዜ (መጨረሻው)


“እኔኮ የራሴ ሚዛን እያለ የእጅሽ ሚዛንነት አይገባኝም?”ይላታል፤ አታዳምጠውም፡፡

ቤቷ ገብታ እንደፊቷ ወዝ የጠገበች ማሰሮዋ ውስጥ ትጨምርና በላዩ ላይ ጨው በተን አድርጋ እሳት ትማግድበታለች።

ጠዋት ስራ ስትሄድ የጣደችው ጨጓራ በኩበትና በእንጨት ስትመጣ ገራም ሆኖ ይጠብቃታል፡፡ አሁን ጨጓራ የምትጥደው ለኔ ብቻ እስከሚመስለኝ ድረስ የምመገበው እኔ ብቻ ነኝ፡፡ ቁራጭ ጨጓራ ከበላች በአብዛኛው ለኔ
ትሰጠኛለች። በማሰሮ ውስጥ የሚቀራት ትንሽ ነው።

አናቴና ጎረቤቶቿ ከወሬ ወሬ እያፈራረቁ ስለድንቄ ንጽህና ማውራት ጀምረዋል። ንጽህናዋ ሰፈሩን ሁሉ ያስደነቀ ነው። ድንቄ እቤቷ ከሆነች የማታጥበው የማትጠርገው ነገር የለም፡፡ ብቻ ይህን
ለማድረግ በስካር ምክንያት አቅም አይነሳት እንጂ ስትጠርግ ውላ
ስትጠርግ ብታድር ደስተኛ ናት።

አዘውትራ “አምላክ ለደኸ ውሃ ባይሰጠው ጭቅቅቱም ይገለው ነበር!” ትላለች።

የእጇ አስተጣጠብ ስነ ስርአት ግዜውን ስለሚገድለው ያበሳጨኛል፡፡ መጀመሪያ በውሃ ትታጠባለች፡፡ ከዚያ ደግሞ ከቤቷ
ፊት ለፊት ወደ በቀለው ግራዋ ትሄድና ትል ያልበላውን ለምለም ቅጠል ስትበጥስ ትቆያለች። እየቀነጣጠበችና መሬት ላይ ከእጇ አምልጠው የወዳደቁ ቅጠሎች እየለቃቀመች አረፋ እስኪወጣ እጇ ላይ ትደፍቀዋለች፡፡ ውሃውን እጇ ላይ የማንቆርቆሩ ስራ ግን ለኔ ይተዋል። በሆዴ እረግማታለሁ፡፡ ምናለ ቶሎ ብላ ብትሰጠኝ እያልኩ መከረኛ ምራቄን ደጋግሜ እውጣለሁ።ጨጓራውን
ስትሰጠኝ እየተስገበገብኩ ስበላ አልፎ አልፎ፣ “አበስኩ ገበርኩ። ከነጋም ቁርስ አልሰጠችህም እናትህም ትላለች።

የአባ ምንተስኖት ድምጽ ከውጭ ሲሰማ ሁሉም ጨዋታውን አቆመ። እንደተባለው ወራሹን ልጅ ይዘው አልገቡም። ብቻቸውን
ነበሩ። ቁጭ እንዳሉ ወደዋናው ቁምነገር በቀጥታ አልገቡም፡፡ ትንሽ ሲያወሩ ከቆዩ በኋላ ከካፖርታቸው ውስጥ ወረቀት አውጥተው ጉሮሯቸውን ሲጠራርጉ አንድ ነገር ሊያነቡ እንደሆነ የገባት እናቴ፣

“ልጁ ሳይመጣ?” አለች።

አባ ምንተስኖት ሁላችንንም በፍቅር ዐይኖቻቸው ከተመለከቱ በኋላ ንግግራቸውን ጀመሩ።
“ልጆቼ! ድንቄ ይህን ኑዛዜ እናንተ ፊት እንዳነበው አስጠንቅቃ አዛኛለች። በእርግጥም ድንቄ ልጅ አላት። ልጇ ግን
እዚሁ ቅርባችን ነው ፤ እኛ ሁላችንም እናውቀዋለን፡፡

ሁላችንም በድንጋጤና በጉጉት ስናያቸው ንግግራቸውን ቀጠሉ፡፡

“ከመሞቷ በፊት አንድ ሳምንት ሲቀራት እኔና ሌሎች ሁለት ጓደኞቼን ጠራች። እኛም ያለችውን ሁሉ እዚህ ወረቀት ላይ
አሰፈርነው። ድንቄ ከዛሬ አስራ አምስት ዓመት በፊት ተቀጥራ ትሰራበት ከነበረበት ቤት ባለቤት አንድ ልጅ ወለደች፡፡”
አባ ምንተስኖት አልፎ አልፎ የሚያስላቸው ሳል የኑዛዜውን መጨረሻ በፍጥነት እንዳንሰማ ቢያደርገንም ሳላቸው አስኪያቆም ሁላችንም በያለንበት በጉጉት ጠበቅን፡፡

በመውለዷ የሚያስጠጋትና የሚረዳት ሰው ብታጣ ካለችበት ፍቼ ከተማ አክስቷ ወደ ሚኖሩበት መጣች። መውለዷ ሲነገራቸው ክፉኛ እንደተቆጡ ስትሰማ እንደማይቀበሏት ተረድታ ለረጅም ሰዓት
በለችበት ቆማ አለቀሰች፡፡ ከዚያም አክስቷ ቤት ልትደርስ ጥቂት ሲቀራት የቆመችበትን ቦታ አስተዋለች፡፡ ከአጠገቧ በግንብ የታጠረ ቤት አለ፡፡
ገርበብ ባለው አሮጌ የብረት በር ወደ ውስጥ ተመለከተች፡፡ በአካባቢውም ሆነ በግቢው አንድም ሰው አልነበረም፡፡
እንቅልፍ የወሰደውን የአንድ ወር ህጻን ከበሩ ላይ ቁጭ አድርጋው በፍጥነት ተሰወረች፡፡”

አባ ምንተስኖት ይህን እንደ ተናገሩ እናቴ እራሷን ይዛና ወደ መሬት አቀርቅራ እየየዋን አስነካችው። አባ ምንተስኖት እናቴ ለቅሶዋን እስክትጨርስ ይሁን አላውቅም ዝም ብለው አይዋት፡፡
ከእናቴ በቀር እንደዚያ ሆኖ ያለቀሰ አልነበረም፡፡

“ከዚያም...” ብለው ቀጠሉ አባ ምተስኖት... ከዚያም ያቺ ሴት መሐን ስለነበረችና ብቻዋን ስለምትኖር እግዜር ከሰማይ የላከላትን ልጅ በደስታ ተቀበለች፡፡ ይሄ የሆነው በፊት የድንቄ
አክስት ከሚኖሩበት ቦታ ነበር፡፡ ሰፈራቸው ፈርሶ ወደዚህ መጥተው ሲሰሩ ...”

እናቴ ለቅሶዋ እየጨመረ መጣ፡፡ አባ ምንተስኖት እናቴን በርህራሄ አይተው ጥቂት ዝም ካሉ በኋላ ። የዛሬው ሀብት ወራሽና

የድንቄ ልጅ፣ ተጥሎ የተገኘውና አሳዳጊዋ እናት ሆና ያሳደገችው
ልጅ መርሻ ነበር አሉ።”

ሁላችንም አለቀስን እኔም ሳትወልደኝ፣ እንደ እናት አድርጋ አንድም ሰው ልጂ አይደለም ብሎ ሳይጠረጥር ያሳደገችኝን እናቴን አቅፌ አለቀስኩ። እሷም እሩቅ ሀገር እንደሚሸኙት ሰው ጥብቅ
አድርጋ ይዛኝ ነበር፡፡

💫አልቋል💫
👍2
አትሮኖስ pinned «#የድንቄ_ኑዛዜ (መጨረሻው) “እኔኮ የራሴ ሚዛን እያለ የእጅሽ ሚዛንነት አይገባኝም?”ይላታል፤ አታዳምጠውም፡፡ ቤቷ ገብታ እንደፊቷ ወዝ የጠገበች ማሰሮዋ ውስጥ ትጨምርና በላዩ ላይ ጨው በተን አድርጋ እሳት ትማግድበታለች። ጠዋት ስራ ስትሄድ የጣደችው ጨጓራ በኩበትና በእንጨት ስትመጣ ገራም ሆኖ ይጠብቃታል፡፡ አሁን ጨጓራ የምትጥደው ለኔ ብቻ እስከሚመስለኝ ድረስ የምመገበው እኔ ብቻ ነኝ፡፡ ቁራጭ ጨጓራ…»
#እስካለን

#እስካለን
ክፋት ተንኮልን ትተን - ቀና አስተሳሰብ ቢኖረን፣
#እስካለን
የራሳችንን ላብ እንጂ - የሌሎችን ባያስመኘን፣
#እስካለን
ጭንቅላታችን ሩቅ ቢያስብ - የወደፊቱን ቢጠቁመን፣
#እስካለን
ከሆድ ፍቅር አስወጥቶ - የሐገር ፍቅር ቢያድለን፣
#እስካለን .....
የሰው እጅ ማየቱ ቀርቶ - ይሄኔ የት በነበርን።

🔘በሙሉቀን🔘
👍1
#እባብ_ሆይ

በምላስሽ የያዝሽው መርዝ :-
አንድም መድሐኒት ሆኖ - የታመመን ይፈውሳል
አንድም አጥፊ መርዝ ሆኖ - ጤነኛ ፍጡር ይገድላል።

እንግዲህ ምርጫው ያንቺ ነው :-
ወይ መድሐኒት ሁኝና - ተዋደን እንፍጠር ህብር
ወይንም መርዝሽን መርጠሽ -
በተገናኘን ቁጥር
ስንጨፋጨፍ እንኑር።
#እንዴት_ይሄን_አታውቂም!?

የሰው ልጅ ታሪክ ሲመረመር
እኩይና ጥሩ ሰው ነበር፡፡
እኩዮች አፈር ለብሰዋል
ጥሩዎች ሞት ድል ነስተዋል::
እንዴት ይሄን አታውቂም!?

በቅርቡ እንኳን በቅርቡ - የታየ የተነገረ
በጎረቤታችን ምድር የሰው ደም ጎርፎ ነበረ፡፡
ወንድም በወንድሙ ላይ - ስለምን ሞት አነገሰ?
ለምን የንፁሃን ደም - በየጎዳናው ፈሰሰ?
እንዴት ይሄን አታውቂም!?

የባቢሎን ስልጣኔ - ባለመግባባት ፈራርሷል
ኢያሪኮን የመሰለ ግንብ - በጩኸት ተደረማምሷል
ብቻውን የቆመ አንበሳ - በጅቦች መንጋ ተበልቷል
የተባበሩ ጉንዳኖች - የመሬትን ሆድ ቀደዋል፡፡
እንዴት ይሄን አታውቂም!?

ቂም በቀል ያረገዘች ልብ - ሰላምን ልታቅፍ አትችልም
ሰላምን ያላገኜች ነብስ - ፍቅርን አታስተምርም:
ፍቅር የራቃት ህይወት - የምትሰራው ቤት ጥላቻ
በጥላቻ የተሞላች ቤት - አማራጫ መፍረስ ብቻ::
እንዴት ይሄን አታውቂም!?

እንዴት ይሄን አታውቂም!?
ካወቅሽስ ምነው ችላ አልሽው?
ማፍረሱን ነው የናፈቅሽው?
መፍረሱን ነው የፈለግሽው?
እንዴት ይሄን አታውቂም!?
እንዴት ይሄን አታውቂም!?
እ.ን.ዴ.ት ይ.ዴ.ን ኢታ.ው.ቂ.ም!?
እንዴት!!???

🔘በሙሉቀን🔘
#ሰው_አፈር

አዕዋፍ በሰማይ ላይ ሲበሩ
በማራኪ ዜማቸው ሲዘምሩ፤
ውብ ተፈጥሯቸው ይደንቀኛል
እኔም ወፍ በሆንኩ ያሰኘኛል፡፡

እንስሳትም በየፊናቸው
ተመሳስለው ከአካባቢያቸው ፤
በጎጡ በስርጓጉጡ
ሲሽሎከሎኩ ሲሮጡ፤
ውብ ተፈጥሯቸው ይስበኛል
ፈጣሪ ስራው ይደንቀኛል፡፡

አንዱ ከዛፍዛፍ ሲዘል - ሌላው በመሬት ሲንፏቀቅ
አንዱ በሰማይ ሲበር - ሌላው ውሐ ውስጥ ሲሞላቀቅ፤
አንዱ ጮማውን ሲቆርጥ
ሌላው ደግሞ ሳሩን ሲግጥ፤
ልዩነታቸውን መመልከት - ሲሽቀዳደሙ ማየት
አቻ የሌለው ቲያትር - ተፈጥሯዊ ድንቅ ተውኔት።

ታዲያ
ከዚህ ሁሉ ውብ ተፈጥሮ - ከዚህ ሁሉ ትዕይንት
ለተመልካች የሚደንቀው - የሚገርመው አስቂኝ ትርዒት
አፈር -አፈርን ሲንቅ
አፈር - ከአፈር ሲተናነቅ፣
አፈር - በአፈር ላይ ሲያሴር
አፈር - ለአፈር ሲቆፍር..
..እንደ አፈር ቁጭ ብሎ ማየት።

🔘?🔘
#አይ እብዱ

“ሐገሬ አይዞሽ ባይ አጥታ
በራስ ወዳዶች ተሞልታ፤
እውነት ለማውራት ብቸገር
ከህግ ውጭ ሆኜ ልናገር፡፡”
አለ እብዱ::

“ወጣት በድንጋይ ስወግር - ወላጅ ስሳደብ ዝም አሉኝ
“መንግስት' ብየ ስጀምር - ሁሉም አፌን አፈነኝ፡፡”
አለ እብዱ::

“መንግስት ማለት ህዝብ ነው - አህዛብ የመሰረቱት
ስለዚህ ህዝብን ልሳደብ -
ህዝብ ሆይ ለሆድህ አትሙ........ት!!”
አለ እብዱ::

አገርህ ብዙ ልጅ ወልዳ - ጥሩ ልጅ ተርባ እያየህ
ለሆድህ እናትህን ምትሸጥ - ዳግማዊ ይሁዳ አንተ ነህ!”
አለ እብዱ፡፡

አይ እብዱ፡፡

🔘በሙሉቀን🔘
#ተይ_ማነሽ_ተይ_ማነሽ!

ተይ ማነሽ ተይ ማነሽ
ተይ ማነሽ ተይ ማነሽ
አስተውለሽ ርገጭ - ተራመጅ እያየሽ
በትዕግስት አልጋ ላይ -
የተኛ ልብ አለ ትቀሰቅሻለሽ፡፡

የራሱን ለማድመቅ - የጎረቤት መብራት እያደበዘዘ
የራሱን ለማሞቅ - የሌላውን ጎጆ እያቀዘቀዘ
ማን ወደ ፊት ሄደ? - ማን ሩቅ ተጓዘ!?
ማን ሃጃው ሞላለት? - ማን ግቡን አሳካ?
ማን ሰላም አገኜ ሰው እየነካካ!?

ተይ ማነሽ ተይ ማነሽ
ተይ ማነሽ ተይ ማነሽ
አስተውለሽ ርገጭ - ተራመጅ እያየሽ
በመቻል መስክ ላይ ~
የረጋ ቁጣ አለ ታደፈርሻለሽ፡፡

የሰው ልጅ ውድቀቱ የሰው ልጅ በሽታ
“እኛ ማለት ትተው እኔ ያሉ ለታ::
በሰፊ ምድር ላይ በጠባብ መሄጃ
“እኔ እኔ ማለትሽ ማዋጣቱን እንጃ፡፡

🔘በመሉቀን🔘
👍1
#ፉግር (እድለ-ቢስ)

ጅብ አያ ልክስክስ ፤
ካሰበው እስኪደርስ
የልቡን እስኪያደርስ፣
አንከስ
አንከስ
አንከስ....
አንክሶም አልቀረ፣
መጣ ተመልሶ
የልቡን አድርሶ፡፡

ማሙሽ እንኳ መጥቆ
በማልቀስ ፍላጎት - እንደሚሟላ አውቆ ፤
ልቡ የሻታትን - እስኪያገኛት ድረስ
ማልቀስ
ማልቀስ
ማልቀስ....
አልቅሶም አልቀረ፣
ተሳካ ምኞቱ
በየዋህ እናቱ፡፡

ልቤ ግን ፋግሩ፣
ወይ ላይዝ አንክሶ
ላያገኝ አልቅሶ
ከሄደበት ቦታ-
እያጨበጨበ መጣ ተመልሶ፡
#ከኔ_በፊት_ሙቺ

ፍቅሬ የኔ እመቤት
የኔና አንቺ መውደድ - የ'ኔና አንቺ ፍቅር
ሩቅ እንደ ሰማይ - ግዙፍ እንደ ምድር
ጥልቅ እንደ ውቂያኖስ - ጣፋጭ እንደ ቴምር::

አንቺ እኔን ስትወጂኝ፣
እኔ አንቺን ስወድሽ ፣
ዘመን ተቀይሯል፤
ሰፊው አገር ጠቧል፤
አቧራው ጨቅይቶ - የረጠበው ደርቋል፤
ምድር በጣም ግላ - ሰማይ ጥላው ሳስቷል፧
ንዋይ ተወጥሮ - የሰው ክብር ላልቷል፤
ፍቅሬና ፍቅርሽ ግን - እያደረ ጠብቋል፤
እያደር ታድሷል፤
ይኼው እዚህ ደርሷል፡፡

ታውቂያለሽ ይህች ዓለም
አንድ መንገድ ብቻ ለሷ አልተፈጠረም፡፡
ለደስታ ሐዘን አለ
ለእሳትም ውሐ አለ
ብርሐን ነው ሲሉ - ወዲያው ይጨልማል
ሰውም አለ ሲሉት - በሞት ይሽነፋል፡፡

እና የኔ ፍቅር
እውነትን መናገር - አንዳንዴ ቢመርም
የእኔና አንቺ ፍቅር - ከምድር ቢገዝፍም
ከቴምር ቢጣፍጥም
ህይወት አለንና ከሞት አናመልጥም፡፡

መሞትን ሳስበው
ካንቺ ተነጥሎ - እንዴት ነው ሚኖረው?'
ስል እጠይቃለሁ፡፡

“አንተ የሌለህበት - ለኔ ህይወት ማለት
እንደመታሰር ነው - በእጅ አሙቅ ሰንሰለት
በናፍቆት መንገብገብ - በሀዘን መሰቃየት::”

ያልሽኝን ሳስታውሰው

“ይህ ፈጣሪ ሚሉት
በፈጠራት ምድር - ፍቅርን ከፈቀደ
ጥላቻን ከጠላ - ሰላም ከወደደ
ከዓለም ጫፍ እስከ ጫፍ - የትም ይሁን የትም
የተፋቀረ ሰው - መሞት የ ለ በ ት ም!!”
እላለሁ::

ቢሆንም

ቢ ሆ ን ም
መሪር ሐቅ አይቀርም፡፡

እና የኔ እመቤት
ሞት የሚሉት ዕጣ - ቆርጦ የመጣ ዕለት
ቢቻል ሁለታችን - አንድ ላይ እንሙት፡፡
ካልሆነ ግን ውዴ
እንደ ሞት ፈጣሪ - እኔ እንደሱ አይደለሁ
ስላንቺ አስባለሁ - ለፍቅሬ እሳሳለሁ
ቀድሜሽ ከምሞት - ብትሞቺ እመርጣለሁ፡፡
ካንቺ በፊት ሞቼ - ከምትኖሪ እያዘንሽ
ስቃይሽ የኔ ይሁን -
አዝኜ ማቅ ልልበስ - ከኔ በፊት ሞተሸ፡፡

🔘በሙሉቀን🔘
#ነገር_በምሳሌ

#እንበሳ፡-
በራሱ እምነት ስላለው - ስለማይኖር ተደብቆ
ምንን ለምን እንደሚያድን - ያውቀዋልና ጠንቅቆ፣
መዳፎቹን የማይሞሉ - የአይጥ መንጋ ተሰባስበው
ቢርመሰመሱ ቢጮሁ አንበሳውን ዙሪያ ከበው፣
እንዳያመልጠው ዋናው አደን - የአይጥን መንጋ ሲያሯሩጥ
አላርፍም ቢሉም አይጦቹ - ቢጮሁ ቢሉ ሲጥ ሲጥ
ፀጥ!!!

#ውሻ፡-
እፊቱ ላይ ድመት ቆማ - እንደ ነብር ብትጮህበት
አካሏ አብጦ - ጸጉሯ ቆሞ - ተገትራ ብታፈጥበት፣
ያውቀዋልና ውሻው - ድመቷን እንደሚረታ
ጫፉን እስካልነካችው - አፍንጫው ስር ተጠግታ፣
ብትነፋፋ፣ ብትኮፈስ፣ ብትዘል፣ ብትፈርጥ፣ ብትወራጭ
ጭጭ!!!

አንዳንድ #ሰውም፡-
አንዱ በዚህ ሲቦጭቀው
አንዱ በዚያ ሲያመናጭቀው
በጆሮቹ እየሰማ - እየሳቀ ዝም የሚለው፣
አይደለም ቃላት ጠፍቶበት አይደለም ስለበሸቀው
ስራ የፈታ ቢያወራም - እሱ ራሱን ስለሚያውቀው፡፡
እሉ ራሱን ስለሚያውቀው - ሰው ስለሱ ብዙ ቢልም
ዝም!!!

🔘በሙሉቀን🔘
#ያምር_ነበር?

የውስጣችንን ብቃት
የውስጣችንን ክፋት፣

ማስመሰል የማይቀይረው
መቀላመድ የማያከስመው፣

ማንም ሰው እንደዲያነበው
ክፉ ደጉን እንዲለየው፣

ግንባራችን ላይ በአጭር ነገር
ሚፃፍ ቢሆን ያምር ነበር?

🔘በሙሉቀን🔘
#ተቃርኖ

“አንዳንዱ ያወራል
አንዳንዱ ይሰራል፤
የሰራው ሲያልፍለት
የሚያወራው ያፍራል!”
ይላል የእኛ አባባል፡፡

እውነታው ሲታይ ግን፡-
'ሚያወራው ይወራል
“ሚሰራው ይሰራል፤
በፖለቲካ ዓለም
የተገላቢጦሽ - ህይወት ይቀጥላል፡፡
#ቆንጆ_ነሽ!!!

ውብዬ
ውቢቷ!
መልከ መልካሚቷ!
ልቤ በጣም መታ - አንቺን አንቺን አለኝ
እኔ አላማረኝም - ወደድኩሽ መሰለኝ::
ወድጀሽ ወድጀሽ
ውበትሽን ለማድነቅ - ብዕር አንስቻለሁ
ምን ብየ ልጀምር?
ሁለመናሽ ያምራል - ቃላት አጥቻለሁ፡፡

ግን የማውቀው ነገር
አንቺን የሚያወድስ - አንቺን የሚዘክር
ሺህ ጊዜ ቃል ባጣ - ሺህ ጊዜ ብቸገር፣
“በውበትሽ ፈዘው - ወፎች አዜሙልሽ
ስምሽን እየጠሩ - ቅኔ ተቀኙልሽ፡፡”
ብየስ አልክብሽም
ወፎች ወፍን እንጂ - አንቺን አያውቁሽም፡፡

ውሸት ምን ያደርጋል:-
ሺህ ጊዜ ብወድሽ
ሺህ ጊዜ ባደንቅሽ
“ውበትሽን እንዳዩ - እየተገረሙ
እንስሳት ስገዱ - እፅዋት ዘመሙ
ንቦች ተከተሉሽ - ጠረንሽን ሊቀስሙ:: ”
እያልኩ አልዋሽሽም
አላወድስሽም::
ታውቂያለሽ
አውቃለሁ
ውበትሽ ልዩ ነው::
ግን ምንም ብደነቅ
አንቺን ለማዳነቅ
ውበትሽን እንዳየ - ሰማይ ዝቅ አለልሽ
ጨረቃ ደመቀች - ፀሐይ አጀበችሽ
ክዋክብት ቦረቁ - እየተከተሉሽ፡፡”
እያልኩ ያለ ህጉ - ያለ ተፈጥሯቸው- አንቺን አልክብሽም
እንዲያውም እንዲያውም
ክዋክብት ጨረቃ
ፀሐይና ሰማይ
ከነመፈጠርሽም አያስታውሱሽም፡፡

ግን አንድ እውነት አለ:-
አንቺ ባለፍሽበት - በሄድሽበት ሁሉ
ሰዎች ስራ ፈትተው - ወደ አንቺ ያያሉ፡፡

ሐቅ ነው
እውነት ነው
በመንገድ የሚያዩሽ - የአዳም ዘሮች ሁሉ
አንቺን ያደንቃሉ
አንቺን ይመኛሉ፡፡

ነገር ግን ውቢቷ!
መልከ መልካሚቷ!
የሰውን ስብዕና - የሰውን ቁንጂና
እንስሳት እፅዋት - አያውቁትምና፣
ጨረቃ ብትወጣ - ፀሐይ ብታበራ
ክዋክብት ሲያደምቁት - ውበትሽን በጋራ፣
በሰማይ በምድር -
ያንቺን ቆንጆ መሆን - ግዑዝ አያውቀውም
ሰውን ሰው ብቻ እንጂ - ሌላ አያደንቀውም፡፡
እናም ተቀበይኝ
ውበትሽ ማርኮኛል - ውበትሽን ላድንቀው
መልክሽ እንደሚስብ -
ዛላሽ እንደሚያምር፣
የውበትሽ ነገር -
እንደሚያነጋግር፣
እኔ ብቻ ሳልሆን - ሁሉም ነው የሚያውቀው::
ቆንጆ ነሽl!

🔘በሙሉቀን🔘
#የአንድ_አውሮጳዊ_ምኞት

ትኑር እንጂ አፍሪካ!
ይኑር እንጂ ደሃ!
ዛፎች ተጨፍጭፈው - አፈሩ ቢፋቅም
ወንዞች ሁሉ ደርቀው - መሬት ብትነጥፍም፣

ትኑር እንጂ አፍሪካ!
ይኑር እንጂ ደሃ!
ምድረ በዳ ቢሆን - ጫካ የነበረው
የውቂያኖስን ግት - ውሐ ቢናፍቀው፣

ወይናደጋው አየር - በሐሩር ቢተካ
ለምለሙ መሬቴ - ቢደርቅ በፋብሪካ፣
ይኑር እንጂ ደሃ!
ትኑር እንጂ አፍሪካ!
ለኔ ሚስማማኝን - አየር እገዛለሁ፤
በድልቡ ገንዘቤ - ነብስ እለውጣለሁ፣
አፍሪካ አትደጊ - ኑሪልኝ አፍሪካ
ተስማሚ መሬትሽን - አይንካው ፋብሪካ፡፡