#ከኔ_በፊት_ሙቺ
ፍቅሬ የኔ እመቤት
የኔና አንቺ መውደድ - የ'ኔና አንቺ ፍቅር
ሩቅ እንደ ሰማይ - ግዙፍ እንደ ምድር
ጥልቅ እንደ ውቂያኖስ - ጣፋጭ እንደ ቴምር::
አንቺ እኔን ስትወጂኝ፣
እኔ አንቺን ስወድሽ ፣
ዘመን ተቀይሯል፤
ሰፊው አገር ጠቧል፤
አቧራው ጨቅይቶ - የረጠበው ደርቋል፤
ምድር በጣም ግላ - ሰማይ ጥላው ሳስቷል፧
ንዋይ ተወጥሮ - የሰው ክብር ላልቷል፤
ፍቅሬና ፍቅርሽ ግን - እያደረ ጠብቋል፤
እያደር ታድሷል፤
ይኼው እዚህ ደርሷል፡፡
ታውቂያለሽ ይህች ዓለም
አንድ መንገድ ብቻ ለሷ አልተፈጠረም፡፡
ለደስታ ሐዘን አለ
ለእሳትም ውሐ አለ
ብርሐን ነው ሲሉ - ወዲያው ይጨልማል
ሰውም አለ ሲሉት - በሞት ይሽነፋል፡፡
እና የኔ ፍቅር
እውነትን መናገር - አንዳንዴ ቢመርም
የእኔና አንቺ ፍቅር - ከምድር ቢገዝፍም
ከቴምር ቢጣፍጥም
ህይወት አለንና ከሞት አናመልጥም፡፡
መሞትን ሳስበው
ካንቺ ተነጥሎ - እንዴት ነው ሚኖረው?'
ስል እጠይቃለሁ፡፡
“አንተ የሌለህበት - ለኔ ህይወት ማለት
እንደመታሰር ነው - በእጅ አሙቅ ሰንሰለት
በናፍቆት መንገብገብ - በሀዘን መሰቃየት::”
ያልሽኝን ሳስታውሰው
“ይህ ፈጣሪ ሚሉት
በፈጠራት ምድር - ፍቅርን ከፈቀደ
ጥላቻን ከጠላ - ሰላም ከወደደ
ከዓለም ጫፍ እስከ ጫፍ - የትም ይሁን የትም
የተፋቀረ ሰው - መሞት የ ለ በ ት ም!!”
እላለሁ::
ቢሆንም
ቢ ሆ ን ም
መሪር ሐቅ አይቀርም፡፡
እና የኔ እመቤት
ሞት የሚሉት ዕጣ - ቆርጦ የመጣ ዕለት
ቢቻል ሁለታችን - አንድ ላይ እንሙት፡፡
ካልሆነ ግን ውዴ
እንደ ሞት ፈጣሪ - እኔ እንደሱ አይደለሁ
ስላንቺ አስባለሁ - ለፍቅሬ እሳሳለሁ
ቀድሜሽ ከምሞት - ብትሞቺ እመርጣለሁ፡፡
ካንቺ በፊት ሞቼ - ከምትኖሪ እያዘንሽ
ስቃይሽ የኔ ይሁን -
አዝኜ ማቅ ልልበስ - ከኔ በፊት ሞተሸ፡፡
🔘በሙሉቀን🔘
ፍቅሬ የኔ እመቤት
የኔና አንቺ መውደድ - የ'ኔና አንቺ ፍቅር
ሩቅ እንደ ሰማይ - ግዙፍ እንደ ምድር
ጥልቅ እንደ ውቂያኖስ - ጣፋጭ እንደ ቴምር::
አንቺ እኔን ስትወጂኝ፣
እኔ አንቺን ስወድሽ ፣
ዘመን ተቀይሯል፤
ሰፊው አገር ጠቧል፤
አቧራው ጨቅይቶ - የረጠበው ደርቋል፤
ምድር በጣም ግላ - ሰማይ ጥላው ሳስቷል፧
ንዋይ ተወጥሮ - የሰው ክብር ላልቷል፤
ፍቅሬና ፍቅርሽ ግን - እያደረ ጠብቋል፤
እያደር ታድሷል፤
ይኼው እዚህ ደርሷል፡፡
ታውቂያለሽ ይህች ዓለም
አንድ መንገድ ብቻ ለሷ አልተፈጠረም፡፡
ለደስታ ሐዘን አለ
ለእሳትም ውሐ አለ
ብርሐን ነው ሲሉ - ወዲያው ይጨልማል
ሰውም አለ ሲሉት - በሞት ይሽነፋል፡፡
እና የኔ ፍቅር
እውነትን መናገር - አንዳንዴ ቢመርም
የእኔና አንቺ ፍቅር - ከምድር ቢገዝፍም
ከቴምር ቢጣፍጥም
ህይወት አለንና ከሞት አናመልጥም፡፡
መሞትን ሳስበው
ካንቺ ተነጥሎ - እንዴት ነው ሚኖረው?'
ስል እጠይቃለሁ፡፡
“አንተ የሌለህበት - ለኔ ህይወት ማለት
እንደመታሰር ነው - በእጅ አሙቅ ሰንሰለት
በናፍቆት መንገብገብ - በሀዘን መሰቃየት::”
ያልሽኝን ሳስታውሰው
“ይህ ፈጣሪ ሚሉት
በፈጠራት ምድር - ፍቅርን ከፈቀደ
ጥላቻን ከጠላ - ሰላም ከወደደ
ከዓለም ጫፍ እስከ ጫፍ - የትም ይሁን የትም
የተፋቀረ ሰው - መሞት የ ለ በ ት ም!!”
እላለሁ::
ቢሆንም
ቢ ሆ ን ም
መሪር ሐቅ አይቀርም፡፡
እና የኔ እመቤት
ሞት የሚሉት ዕጣ - ቆርጦ የመጣ ዕለት
ቢቻል ሁለታችን - አንድ ላይ እንሙት፡፡
ካልሆነ ግን ውዴ
እንደ ሞት ፈጣሪ - እኔ እንደሱ አይደለሁ
ስላንቺ አስባለሁ - ለፍቅሬ እሳሳለሁ
ቀድሜሽ ከምሞት - ብትሞቺ እመርጣለሁ፡፡
ካንቺ በፊት ሞቼ - ከምትኖሪ እያዘንሽ
ስቃይሽ የኔ ይሁን -
አዝኜ ማቅ ልልበስ - ከኔ በፊት ሞተሸ፡፡
🔘በሙሉቀን🔘