#ሮዛ_2
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ(🔞)
፡
፡
በሁለቱ ግንኙነት ወስጥ የሆነ አንድ ያልገባኝ ነገር እንዳለ እርግጠኛ ሆንኩ።
እንዲህ እንዲህ እያልን ከማሪያ ጋር የባጥ የቆጡን ስናወራ እኔና ዶክተር ቃልአብ ከደቂቃዎች በፊት ያደረግነውን ነገር እየተረሳኝ መጣ። ሞቅ እያለን ሲመጣ ከሳሎን ባር ተነስተን ወደ ላይኛው ሰገንት
ወጣን። የቤታቸው ፎቅ ጣሪያው ሲሚንቶ ነው። በጣም የሚያምር ሰገነት አድርገው ሰርተውታል።
እዚያ ላይ ወጥተን፣ ፍራሽ ዘርግተን ብዙ ሳቅን ተጫወትን። ከማሪያ ጋር ኮከባችን ገጥሞ ነበር። በዚህ ሁሉ ጊዜ ግን የኔና የባሏ ግንኙነት ምን እንደሆነ እንድም ጊዜ ለምን እንዳልጠየቀችኝ ገርሞኛል።
እየመሸ ሲሄድ ወደቤቴ መሄድ እንዳለብኝ ነገርኳቸው።ዶክተር ቃልአብ አይኑን አሁንም ከኔሚኒስከርቴ ላይ ሊነቀል አልቻለም። በተለይ ፍራሹ ላይ ቁጭ ስል ሁሉ ነገሬ ስለተገላለጠ ተሳቀቅኩ። ይበልጥ ያስጨነቀኝ የተቀደደው ፓንቴ ቦርሳዬ ውስጥ መሆኑ ነበር። ጭኖቼን ገጥሜ ተቀመጥኩ። እሱ ግን
አይኑን አልነቅል አለኝ። ሚስቱ ሁኔታውን እንዳታስተውል ስለፈራሁ በአይኔ ተቆጣሁት። እሱ በምላሹ
ድብን አርጎ ጠቀሰኝ። ትንሽ ሞቅ ሳይለው አልቀረም። ነገሮች መልካቸውን ሳይቀይሩ ቶሎ መሄድ እንዳለብኝ አመንኩ። እስካሁንም ከቅሌት የዳንኩት በሰይጣን ትብብርና በማሪያ የዋህነት ነው። እኔና
ማሪያ ሙሉ ዋይን ስንጠጣ ስለነበር ሰውነታችን ግሏል። ሰገነቱ ላይ ያለው ንፋስ ከበድ ስለሚል ዋይኑ ብርዱን ተከላከለልን ብዙም አልተሰማንም።
መሄድ እንዳለብኝ ስነግራቸው እዚያው ማደር እችል እንደሆነ ጠየቁኝ። እናቴ ትጠብቀኛለች ብዪ ዋሸኋቸው።ከናቴ ጋር እንደምኖር ፍርጥም ብዬተናገርኩ።ዶክ ሳቁ ትን አለው ደረጃውን ወርደን ወደ ግቢው ወጣን። በኮሪደሩ ስናልፍ ዶከተር ቀለአብ «እኔ አደርሳታለሁ» ብሎ ከሰፌዱ ውስጥ የመኪና ቁልፍ ሲያነሳ ማሪያ ተቃወመች። ሀሳቡን በቁጣ ስለተቃወመችው በሁለታችን መሐል የጠረጠረችው ነገር እንዳለ አድርገን ተረዳን፤ ሁለታችንም ደነገጥን። ሆኖም እሷ የተቃወመችው ሁላችንም ስንጠጣ
ስለቆየን አልኮል ጠጥተን ማሸከርከር ተገቢ እንዳልሆነ በማመኗ ነበር። ዶክተር ቃልአብ ግን ትንሽ ነው የጠጣሁት ብሎ ተሟገታት። ሞቼ እገኛለሁ አለች። ነገሩን ለመቋጨት ተንቀሳቃሽ የሳሎን ስልኳን
አምጥታ የታክሲ ደምበኛዋን ስልክ ደውላ በፍጥነት ቤት እንዲመጣ ነገረችው።
ዶክተር ቃልአብ ለምን እኔን ካልሸኘኃት ብሎ ሙጭጭ እንዳለ ገብቶኛል። ጭኔ ውስጥ ጀምር ያልጨረሰው የቁፋሮ ፕሮጀክት አለ። እውነቱን ለመናገር እኔም በሆዴ እሱ በሸኘኝ ስል ተመኝቻለሁ።
ነግር ግን የጀመርነውን እንድንጨርስ ብዬ አልነበረም። እኔ ጣጣዬን ከጨረስኩ ቆይቻለሁ- ጭራሽ ስሜቴ ጠፍቶ ነበር፡፡ እንዲያውም ማሪያ ላይ እንደዚያ አይነት ድርጊት ማድረጌ ዉስጥ ዉስጡን
እየፀፀተኝ ነበር።ማሪያን ይበልጥ ባወራኋት ቁጥር ይበልጥ እየወደድኳት ነበር፡፡ የፍቅር ሰው ናት። እንደሷ ስለፍቅር ብቻ ብሎ የሚኖር ሰው አይቼ ማወቄንም እንጃ።
በዋናነት ዶክተር ቃልአብ አንዲሸኘኝ የፈለኩት በሁለቱ ግንኙነት ላይ አንዳች ያልገባኝ ነገር እንዳለ ስለተሰማኝና ያን ግልጽ እንዲያረግልኝ በመፈለጌ ነበር። ሆኖም እውነቱን ለመናገር ያልገባኝ ነገር
ምንእንደሆነ እኔም አልገባኝም።
እንዲያደርሰኝ የተጠራው ታክሲ መድረሱን ለማወጅ ከግቢው ዉጭ ጡሩምባውን ሲያምባረቅ በሩ
በዘበኛው ተከፈተለት። ወደ ታክሲው ተንቀሳቀስኩ። አረማመዴ አሁንም አልተስተካከለም። የሚገርም
ነገር ነው። ከዚህ ቀደም እንዲህ ሆኜ በጭራሽ አላውቅም። ረዥም ሂል ጫማ ማድረጌ ደግሞ ነገሩን አጋነብኝ መሰለኝ። እግሬ እየተብረከረከብኝ ስራመድ you see ማሬ! You and i are feeling tipsy ሃሃሃ but she is drunk! Drunk like a fish ሃሃሃ ሲል ሰማሁት።
እየሳቅኩ የታክሲውን በር ከፍቼ ገባሁ። ማሪያና ዶክተር ቃልአብ ተቃቅፈው በቆሙበት እጃቸውን አውለብልበው ሸኙኝ። የላዳ ታክሲው የኋላ ወንበር ላይ ገና ቁጭ ብዬ ወደ ግቢው ስመለከት ማሪያና ዶክተር ቃልአብ ተቃቅፈው እየተሳሳሙ ነበር። ከመቼው ከንፈራቸውን እንዳገናኙት! ደግሞ ሲሳሳሙ ወፍ እንጂ ሰው አይመስሉም። ወሲብ ለመፈጸም ተስገብግበው እንደሚሆን ገመትኩ። ቅድም ተሰምታኝ የነበረችው አይነት ስስ የሆነች ቅናት ዉስጤን ቆንጠጥ ስታደርገኝ ታወቀኝ።ለምን እንደሆነ
አላውቅም የዶክ ሚስት መሆን አምሮኝ ነበር።
#ድህረ_ታሪክ
ከሶስት ነው ከአራት ሳምንት በኋላ ዶክተር ቃልአብ «ኩል ባር» መጣ።ዝንጥ ከማለቱ የተነሳ ልዑል መስሎ ነበር። ያን ቀን እሱ ቤት ዉስጥ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ጉንጬን ሳመኝና ባለጌ ወንበር ላይ
ቁጭ አለ።ደብል ብላክ ለኔም ለሱም አዘዘና ትንሸ አቀርቅሮ ከጸለየ በኋላ ቺርስ!» ብሎኝ ተጎነጨው
ዶክ ሳይፀልይ ምንም ነገር ጀምሮ አያውቅም።
“ምን ሆነህ ነው ግን ያን ቀን?." አልኩት ከመጠጡ ትንሽ ከቀማመስኩለት በኋላ፤
I was expecting this question? አለኝ በግዴለሽነት ትከሻውን እየሰበቀ።”
ታሪኩ ምንም አይሰራልሽም! …የሆነ ጀርመን ሳለን የተፈጠረ ነገር ነው። lets forget that Roz! What happened
in Vegas stays in Vegas ይላሉ ፈረንጆች።” ንግግሩን ተፈጥሯዊ ባልሆነ ሳቅ ሊያጅበው ሞከረ።
"ይልቅ ሮዚ! ለመጀመርያ ጊዜ ቃልአብ ብለሽ በስሜ የጠራሽኝ ያን ቀን እንደሆነ ታውቂያለሽ?” አለኝ
እንደዚያ ጠራሁህ እንዴ?መቼ? የት፣ ምኑጋ” የምሬን ነበር። ዶክን ቃለአብ ብዬ መጥራቴን አላስታውስም
“ማሬ ወጥ ልታመጣ ኪችን ስትገባ ጠረጴዛው ላይ ተደፍተሸ አንገትሽን ቀብረሸው…you know እዛች ከፉ ቦታሽ ላይ በጥፍሬ ስቧጭርሽ.you were out of this world. ቃልአብ ቃልአብ ተው
በናትህ.ተውውው» እያልሽ አቃሰትሽ። በእንቅልፍ ልብሽ የምታወሪ ነበር የሚመስለው። አንድ ነገር ልንገርሽ? በሕይወቴ እንደዚያ ቀን ተደስቼ አላውቅም። "
አፈርኩኝ የሆነውን ነገር ሳስብ እሽኩርምምም አደረገኝ። ፊቴ ሁሉ ቀላ፤ መላ ሰውነቴን ውርርርር የሚያደርግ ስሜት ተሰማኝ።
“የራስህ ጉዳይ! ባለጌ ነህ ግን ዶክ! አልወድህም እሺ!”
ጉንጬን ሳመኝ።
“አንተ ቆይ ሚስትክን እንደዚያ እየወደድካት…” ጥያቄዬ ስለገባው አቋረጠኝ።
ዝም አልኩኝ። ዝም ብለን መጠጣት ጀመርን። ቆንጆ ቆንጆ ሙዚቃ ተከፍቶ ስለነበር ሁለታችንም በሀሳብ በየራሳችን የሀሳብ ሰረገላ ነጎድን። እኔ በበኩሌ ያን ቀን ዶክተር ቃልአብ ያረገኝን እያሰብኩ
ስገረም.…ስገረም ስገረም…። እንዴት አይነት ደስ የሚል እብደት ነበር!
ሳናውቀው ሰዓቱ ነጎደ። ሳናውቀው መጠጡ ሰውነታችን ውስጥ ስራውን መስራት ጀምሮ ነበር፡፡
ከብዙ ቆይታ በኋላ በዶክተርና በማሪያ የሚያስቀና የፍቅር ግንኙነት ውስጥ እስከዛሬ ያልተገለፀለኝን የነበረውን ጉዳይ ይተርክልኝ ጀመር።
ማሪያን ያገኛት ስፔሻላይዝ ለማድረግ ጀርመን ዩኒቨርስቲ ውስጥ ነው። እሷ የባዮኬሚስትሪ ተማሪ ነበረች። ብዙ ወንዶችን ንጹህ ፍቅር ፈልጋ ስትቀርባቸው ጎድተዋታል። ወንዶችን እስከናካቴው ከመጥላቷ የተነሳ ጾታዋን ወደ ወንድ ጾታ አስቀይራ ቀሪ ሕይወቷን ወንድ ሆና ለመኖር ከውሳኔ ጫፍ
ደርሳም ነበር። ሴት መሆን ማለት ደስታን በሌሎች ሰዎች ላይ እየፈለጉ መኖር ነው» የሚል ፍልስፍናን አዳብራ ቆይታለች። ስለዚህ ደስታን በራሷ ለማግኘት ቁልፉ ጉዳይ ሴት አለመሆን ነው ብላ በፅኑ ታምን ነበር። በዚህ ሁኔታ ሳለች ይህንን አስተሳሰቧን ድራሹን የሚያጠፉ ወንድ ህይወቷ ውስጥ ገባ፤
ዶክተር ቃልአብ።
፡
፡
#ክፍል_ዘጠኝ(🔞)
፡
፡
በሁለቱ ግንኙነት ወስጥ የሆነ አንድ ያልገባኝ ነገር እንዳለ እርግጠኛ ሆንኩ።
እንዲህ እንዲህ እያልን ከማሪያ ጋር የባጥ የቆጡን ስናወራ እኔና ዶክተር ቃልአብ ከደቂቃዎች በፊት ያደረግነውን ነገር እየተረሳኝ መጣ። ሞቅ እያለን ሲመጣ ከሳሎን ባር ተነስተን ወደ ላይኛው ሰገንት
ወጣን። የቤታቸው ፎቅ ጣሪያው ሲሚንቶ ነው። በጣም የሚያምር ሰገነት አድርገው ሰርተውታል።
እዚያ ላይ ወጥተን፣ ፍራሽ ዘርግተን ብዙ ሳቅን ተጫወትን። ከማሪያ ጋር ኮከባችን ገጥሞ ነበር። በዚህ ሁሉ ጊዜ ግን የኔና የባሏ ግንኙነት ምን እንደሆነ እንድም ጊዜ ለምን እንዳልጠየቀችኝ ገርሞኛል።
እየመሸ ሲሄድ ወደቤቴ መሄድ እንዳለብኝ ነገርኳቸው።ዶክተር ቃልአብ አይኑን አሁንም ከኔሚኒስከርቴ ላይ ሊነቀል አልቻለም። በተለይ ፍራሹ ላይ ቁጭ ስል ሁሉ ነገሬ ስለተገላለጠ ተሳቀቅኩ። ይበልጥ ያስጨነቀኝ የተቀደደው ፓንቴ ቦርሳዬ ውስጥ መሆኑ ነበር። ጭኖቼን ገጥሜ ተቀመጥኩ። እሱ ግን
አይኑን አልነቅል አለኝ። ሚስቱ ሁኔታውን እንዳታስተውል ስለፈራሁ በአይኔ ተቆጣሁት። እሱ በምላሹ
ድብን አርጎ ጠቀሰኝ። ትንሽ ሞቅ ሳይለው አልቀረም። ነገሮች መልካቸውን ሳይቀይሩ ቶሎ መሄድ እንዳለብኝ አመንኩ። እስካሁንም ከቅሌት የዳንኩት በሰይጣን ትብብርና በማሪያ የዋህነት ነው። እኔና
ማሪያ ሙሉ ዋይን ስንጠጣ ስለነበር ሰውነታችን ግሏል። ሰገነቱ ላይ ያለው ንፋስ ከበድ ስለሚል ዋይኑ ብርዱን ተከላከለልን ብዙም አልተሰማንም።
መሄድ እንዳለብኝ ስነግራቸው እዚያው ማደር እችል እንደሆነ ጠየቁኝ። እናቴ ትጠብቀኛለች ብዪ ዋሸኋቸው።ከናቴ ጋር እንደምኖር ፍርጥም ብዬተናገርኩ።ዶክ ሳቁ ትን አለው ደረጃውን ወርደን ወደ ግቢው ወጣን። በኮሪደሩ ስናልፍ ዶከተር ቀለአብ «እኔ አደርሳታለሁ» ብሎ ከሰፌዱ ውስጥ የመኪና ቁልፍ ሲያነሳ ማሪያ ተቃወመች። ሀሳቡን በቁጣ ስለተቃወመችው በሁለታችን መሐል የጠረጠረችው ነገር እንዳለ አድርገን ተረዳን፤ ሁለታችንም ደነገጥን። ሆኖም እሷ የተቃወመችው ሁላችንም ስንጠጣ
ስለቆየን አልኮል ጠጥተን ማሸከርከር ተገቢ እንዳልሆነ በማመኗ ነበር። ዶክተር ቃልአብ ግን ትንሽ ነው የጠጣሁት ብሎ ተሟገታት። ሞቼ እገኛለሁ አለች። ነገሩን ለመቋጨት ተንቀሳቃሽ የሳሎን ስልኳን
አምጥታ የታክሲ ደምበኛዋን ስልክ ደውላ በፍጥነት ቤት እንዲመጣ ነገረችው።
ዶክተር ቃልአብ ለምን እኔን ካልሸኘኃት ብሎ ሙጭጭ እንዳለ ገብቶኛል። ጭኔ ውስጥ ጀምር ያልጨረሰው የቁፋሮ ፕሮጀክት አለ። እውነቱን ለመናገር እኔም በሆዴ እሱ በሸኘኝ ስል ተመኝቻለሁ።
ነግር ግን የጀመርነውን እንድንጨርስ ብዬ አልነበረም። እኔ ጣጣዬን ከጨረስኩ ቆይቻለሁ- ጭራሽ ስሜቴ ጠፍቶ ነበር፡፡ እንዲያውም ማሪያ ላይ እንደዚያ አይነት ድርጊት ማድረጌ ዉስጥ ዉስጡን
እየፀፀተኝ ነበር።ማሪያን ይበልጥ ባወራኋት ቁጥር ይበልጥ እየወደድኳት ነበር፡፡ የፍቅር ሰው ናት። እንደሷ ስለፍቅር ብቻ ብሎ የሚኖር ሰው አይቼ ማወቄንም እንጃ።
በዋናነት ዶክተር ቃልአብ አንዲሸኘኝ የፈለኩት በሁለቱ ግንኙነት ላይ አንዳች ያልገባኝ ነገር እንዳለ ስለተሰማኝና ያን ግልጽ እንዲያረግልኝ በመፈለጌ ነበር። ሆኖም እውነቱን ለመናገር ያልገባኝ ነገር
ምንእንደሆነ እኔም አልገባኝም።
እንዲያደርሰኝ የተጠራው ታክሲ መድረሱን ለማወጅ ከግቢው ዉጭ ጡሩምባውን ሲያምባረቅ በሩ
በዘበኛው ተከፈተለት። ወደ ታክሲው ተንቀሳቀስኩ። አረማመዴ አሁንም አልተስተካከለም። የሚገርም
ነገር ነው። ከዚህ ቀደም እንዲህ ሆኜ በጭራሽ አላውቅም። ረዥም ሂል ጫማ ማድረጌ ደግሞ ነገሩን አጋነብኝ መሰለኝ። እግሬ እየተብረከረከብኝ ስራመድ you see ማሬ! You and i are feeling tipsy ሃሃሃ but she is drunk! Drunk like a fish ሃሃሃ ሲል ሰማሁት።
እየሳቅኩ የታክሲውን በር ከፍቼ ገባሁ። ማሪያና ዶክተር ቃልአብ ተቃቅፈው በቆሙበት እጃቸውን አውለብልበው ሸኙኝ። የላዳ ታክሲው የኋላ ወንበር ላይ ገና ቁጭ ብዬ ወደ ግቢው ስመለከት ማሪያና ዶክተር ቃልአብ ተቃቅፈው እየተሳሳሙ ነበር። ከመቼው ከንፈራቸውን እንዳገናኙት! ደግሞ ሲሳሳሙ ወፍ እንጂ ሰው አይመስሉም። ወሲብ ለመፈጸም ተስገብግበው እንደሚሆን ገመትኩ። ቅድም ተሰምታኝ የነበረችው አይነት ስስ የሆነች ቅናት ዉስጤን ቆንጠጥ ስታደርገኝ ታወቀኝ።ለምን እንደሆነ
አላውቅም የዶክ ሚስት መሆን አምሮኝ ነበር።
#ድህረ_ታሪክ
ከሶስት ነው ከአራት ሳምንት በኋላ ዶክተር ቃልአብ «ኩል ባር» መጣ።ዝንጥ ከማለቱ የተነሳ ልዑል መስሎ ነበር። ያን ቀን እሱ ቤት ዉስጥ ምንም እንዳልተፈጠረ ሁሉ ጉንጬን ሳመኝና ባለጌ ወንበር ላይ
ቁጭ አለ።ደብል ብላክ ለኔም ለሱም አዘዘና ትንሸ አቀርቅሮ ከጸለየ በኋላ ቺርስ!» ብሎኝ ተጎነጨው
ዶክ ሳይፀልይ ምንም ነገር ጀምሮ አያውቅም።
“ምን ሆነህ ነው ግን ያን ቀን?." አልኩት ከመጠጡ ትንሽ ከቀማመስኩለት በኋላ፤
I was expecting this question? አለኝ በግዴለሽነት ትከሻውን እየሰበቀ።”
ታሪኩ ምንም አይሰራልሽም! …የሆነ ጀርመን ሳለን የተፈጠረ ነገር ነው። lets forget that Roz! What happened
in Vegas stays in Vegas ይላሉ ፈረንጆች።” ንግግሩን ተፈጥሯዊ ባልሆነ ሳቅ ሊያጅበው ሞከረ።
"ይልቅ ሮዚ! ለመጀመርያ ጊዜ ቃልአብ ብለሽ በስሜ የጠራሽኝ ያን ቀን እንደሆነ ታውቂያለሽ?” አለኝ
እንደዚያ ጠራሁህ እንዴ?መቼ? የት፣ ምኑጋ” የምሬን ነበር። ዶክን ቃለአብ ብዬ መጥራቴን አላስታውስም
“ማሬ ወጥ ልታመጣ ኪችን ስትገባ ጠረጴዛው ላይ ተደፍተሸ አንገትሽን ቀብረሸው…you know እዛች ከፉ ቦታሽ ላይ በጥፍሬ ስቧጭርሽ.you were out of this world. ቃልአብ ቃልአብ ተው
በናትህ.ተውውው» እያልሽ አቃሰትሽ። በእንቅልፍ ልብሽ የምታወሪ ነበር የሚመስለው። አንድ ነገር ልንገርሽ? በሕይወቴ እንደዚያ ቀን ተደስቼ አላውቅም። "
አፈርኩኝ የሆነውን ነገር ሳስብ እሽኩርምምም አደረገኝ። ፊቴ ሁሉ ቀላ፤ መላ ሰውነቴን ውርርርር የሚያደርግ ስሜት ተሰማኝ።
“የራስህ ጉዳይ! ባለጌ ነህ ግን ዶክ! አልወድህም እሺ!”
ጉንጬን ሳመኝ።
“አንተ ቆይ ሚስትክን እንደዚያ እየወደድካት…” ጥያቄዬ ስለገባው አቋረጠኝ።
ዝም አልኩኝ። ዝም ብለን መጠጣት ጀመርን። ቆንጆ ቆንጆ ሙዚቃ ተከፍቶ ስለነበር ሁለታችንም በሀሳብ በየራሳችን የሀሳብ ሰረገላ ነጎድን። እኔ በበኩሌ ያን ቀን ዶክተር ቃልአብ ያረገኝን እያሰብኩ
ስገረም.…ስገረም ስገረም…። እንዴት አይነት ደስ የሚል እብደት ነበር!
ሳናውቀው ሰዓቱ ነጎደ። ሳናውቀው መጠጡ ሰውነታችን ውስጥ ስራውን መስራት ጀምሮ ነበር፡፡
ከብዙ ቆይታ በኋላ በዶክተርና በማሪያ የሚያስቀና የፍቅር ግንኙነት ውስጥ እስከዛሬ ያልተገለፀለኝን የነበረውን ጉዳይ ይተርክልኝ ጀመር።
ማሪያን ያገኛት ስፔሻላይዝ ለማድረግ ጀርመን ዩኒቨርስቲ ውስጥ ነው። እሷ የባዮኬሚስትሪ ተማሪ ነበረች። ብዙ ወንዶችን ንጹህ ፍቅር ፈልጋ ስትቀርባቸው ጎድተዋታል። ወንዶችን እስከናካቴው ከመጥላቷ የተነሳ ጾታዋን ወደ ወንድ ጾታ አስቀይራ ቀሪ ሕይወቷን ወንድ ሆና ለመኖር ከውሳኔ ጫፍ
ደርሳም ነበር። ሴት መሆን ማለት ደስታን በሌሎች ሰዎች ላይ እየፈለጉ መኖር ነው» የሚል ፍልስፍናን አዳብራ ቆይታለች። ስለዚህ ደስታን በራሷ ለማግኘት ቁልፉ ጉዳይ ሴት አለመሆን ነው ብላ በፅኑ ታምን ነበር። በዚህ ሁኔታ ሳለች ይህንን አስተሳሰቧን ድራሹን የሚያጠፉ ወንድ ህይወቷ ውስጥ ገባ፤
ዶክተር ቃልአብ።
👍4❤3
ከቃልአብ ጋር በፍቅር መክነፍ በጀመሩበት በመጀመሪያው ዓመት ማሪያ የአባቷን ምክር ለመተግበር
አንድ ሁለት የምትልበት አጋጣሚ ነበር። አባቷ ጾታ የመቀየሩን ሀሳብ እርግፍ አድርጋ እንድትተው የመከሯት «ወንዶች ላያቸው ላይ የምታማግጥ ሴትን ይበልጥ ያፈቅራሉ» የሚለውን አስተሳሰባቸውን በሷ ላይ በመጫን ነበር። ይህ ሁኔታ ነው የዶክተር ቃልአብን ልብ ክፉኛ የሚጎዳ ነገር እንዲከሰት
ምክንያት የሆነው።
ከማሪያ ጋር የተማሪ አፓርትመንት ተከራይተው አብረው መኖር ጀምረው ሳለ ከእለታት አንድ ቀን ያልተጠበቀ ነገር ተከሰተ። ይኸውም ዶክተር ቃልአብ የፈተና ሰሞን ስለነበር ድካም ተጫጭኖት
ከላይብረሪ መጥቶ ቤት በተኛበት ሁኔታ የሆነ እንግዳ ድምጽ ይቀሰቅሰዋል። አንሶላውን ከላዩ ላይ ገፎ መለመላውን ድምጽ ወደሰማበት ክፍል ሲሄድ ፍጹም ያልጠበቀ ነገር ተመለከተ። ማሪያ ከአንድ
አልጄሪያዊ የቀድሞ ፍቅረኛዋ ጋር የኪችን ካውንተር ጠረጴዛ ላይ ወሲብ ስትፈጽም በአይኑ በብረቱ ተመለከተ። ይህን አልጄሪያዊ ደግሞ ያውቀዋል። ሲኒየሩ ነው፤ በዚያ ላይ የተማሪዎች አፓርትመንት ዉስጥ ሳሎንና ኪችን ሼር ስለሚያደርጉ በተደጋጋሚ አይቶታል። ሆኖም የማሪያ የቀድሞ ፍቅረኛዋ
እንደነበረ ማንም ነግሮት አያውቅም። ያ ማለት ማሪያ ከዶክተር ቃልአብ ጋር ሆና ራሱ በተደጋጋሚ ከአልጄሪያዊው ጋር ወሲብ ትፈጽም ነበር ማለት ነው። የያኔው ተማሪ ቃልአብ በዐይኑ በብረቱ ያየው
ነገር አዘሮ ሊደፋው ሆነ። «በዚያች ቅጽበት ሆኜ ወደ ጌታ መጸለይ ጀመርኩ»አለኝ ዶክተር ቃልአብ
አምላኬ እባክህን ይህን የማየውን ነገር በህልሜ አድርገውና ዘላለም አንተን ሳመሰግን ልኑር"
ዶክተር ቃልአብ መለመሉን፡ እነሱ ደግሞ የኪችን ካቢኔት ጠረጴዛ ላይ መርፌና ክር እንደሆኑ ደርቀው ቀሩ።
አልጄሪያዊው ከደነዘዘበት ነቅቶ ገፍትሮኝ ወጣ። ማሪያ ጠረጴዛው ላይ ሆና ጭኖቿን ከፍታ እየተንቀጠቀጠች የሚሆነውን ነገር በጥሞና ትከታተላለች።ምን እንደሆነ የማላውቀው ዳቢሎስ ሄደህ ባለችበት እነቃት እነቃት እንደማለት ፋንታ ወስባት ወስባት ብሎ ሹክ አለኝ። የተከፈተውን እግሯን ይበልጥ ከፍቼ በከፍተኛ የአውሬ ስሜት ሴክስ አረኳት። ትዝ የሚለኝ ነገር ቢኖር እያቃሰተች ታለቅስ እንደነበረና ይቅርታ እንዳደርግላት ትለምነኝእንደነበረ ነው። ስንጨርስ ተዝለፍልፈን ወደቅን
ተቃቅፈን አለቀስን። በዚያው ቀን ልታገባኝ እንደምትፈልግ ነገረችኝ። መርፌና ክር ሆነን ሳለ would you marry me » አለችኝ። l will አልኳት።በዚያው ቅጽበት ዘላለም ከኔ መለየት እንደማትፈልግ
ገለጸችልኝ፤ በዚያው ቅጽበት ይቅርታዋንም የጋብቻ ጥያቄዋንም ተቀበልኩት። ሻወር ወስደን ተቃቅፈን |
መልሰን ተኛን። በነጋታውም ተኝተን ዋልን። ብዙ ወሲብ አደረግን። ማሪያ መውለድ ብትችል ያን ቀን ትወልድ ነበር የምናስቀና ባልና ሚስቶች ሆንን ትምህርታችንን ጨርሰን ወደ ኢትዬጵያ መጣን።
ጥያቄ ልጠይቀው አፌን ሳቆበቁብ በእጁ አስቆመኝ። ልጠይቀው ያሰብኩት ነገር ገብቶታል።
ከዚያን ቀን ጀምሮ ግን አንድ ትንሽ ዲያቢሎስ ደሜ ዉስጥ ተሰንቅሮ ቀረ። you know ማሪያን እጅግ በጣም እንደማፈቅራት። you know እሷ አንድ ነገር ብትሆንብኝ በህይወት ልቆይ የምፈልግበት አንድም ምክንያት እንደሌለ። መቼም ልለያት አልፈልግም፡፡ ልጅ መውለድ አልቻልንም። ሦስት ቡችሎችን ነው የምናሳድገው፤ ቴዎድሮስን፣ ብርቱካንና በላይን። አለመውለዳችን ግን እኛን ሊለየን የሚችል ቁም ነገር አይደለም። በሚቀጥለው አመት አንድ ሴት ልጅ በጉዲፈቻ ልናሳድግ ወስነናል። በኔና በሷ
የፍቅር ሕይወት ውስጥ ልጅ ያለመውለድ ጉዳይ ጭራሽ እንደ ችግር አይተነውም አናውቅም። እኛ የምንፈልገው እንደተፋቀርን ቶሎ ቶሎ ኖረን፣ አጠር ያለች የምትጣፍጥ ህይወት ኖረን መሞት ነው።
ችግሩ ያለው ከኔ ነው። እኔን ከያዘኝ ዲያቢሎስ ነው ችግሩ።…”
"ይህ የምነግርሽ ትንሽዬ ዲያቢሎስ ያን ሌሊት የተፈጠረውን ነገር ላለፉት 7 ዓመታት መልሶ መላልሶ ያመጣብኛል። ፀለይኩበት፤ አፀለይኩበት። ሊለቀኝ አልቻለም። ብዙ ቸርች ሄጃለው ከዚህ
ዲያቢሎስ ለመፈወስ። እየባሰብኝ መጣ። ይህ ዲያቢሎስ ስራው አንድ ነው፤ የዛን ሌሊቱን ነገር ቁልጭ
አድርጎ በአእምሮዬ እንደፊልም ያሳየኛል። አልጄሪያዊውን አልሙሳዊን ደጋግሞ ያመጣብኛል። ሮዚ አታምኚኝም ድርጊቱ ልከ ዛሬ እንደተፈጸመ አድርጎ ያሳየኛል። ኪችኑ ውስጥ የነበረውን ሹካ ሳይቀር፣
የአልሙሳዊን መቀመጫ ሳይቀር…። ያን ትዕይነት ለማጥፋት አንቺ ጋር እመጣለሁ በምወዳት ሚስቴ ላይ እባልጋለሁ-። ምን ላድርግ?? እስከመቼ ነው የዚህ እርኩስ መንፈስ መጫወቻ ሆኜ የምቀረው!?….”
ማሪያን በተመሳሳይ መልኩ ብበቀላት ይህ ችግር ለዘላለሙ እንደሚጠፋልኝ የመከሩኝ ሁለት የአሜሪካ ሳይካትሪስቶች የጻፉት መጽሐፍ ነው።ጸሐፊዎቹን ለሥራ ቨርጂኒያ በሄድኩበት ላገኛቸው
ሞከሬ አልተሳካልኝም። በኢሜይል ሁኔታውን ጻፍኩላቸው። የመከሩኝ ነገር አስደነገጠኝ። ግዴለም ሚስትህን ንገራትና ሞክረው አሉኝ። የተለመደ ቴራፒ እንደሆነ ነገሩኝ። እነሱ መፍትሄ ነው የሚሉት ቴራፒ በተመሳሳይ መንገድ እንድበቀላት ነው። እሷ ባደረገችው መንገድ ካልተበቀልካት ትዕይንቱ
ከአእምሮህ ሊወጣ አይችልም አሉኝ። ነገር ግን ፈራሁ፤ የምጎዳት መሰለኝ። በዚህ ፍርሃቴ ውስጥ ሆኜ የፈጸምኩት ድርጊት ነው የዚያ ምሽቱ ድራማ። አንቺ ዘንድ የምመጣው ይህን እርኩስ መንፈስ
ለማስታገስ ብቻ ነው፤ ሮዝ…፤እንጂ ሚስቴን ጠልቼ አይደለም።”
ዶክተር ቃልአብ አንገቴ ውስጥ ፊቱን ቀበረ። ቀና አድርጌ ሳየው የምርም እያለቀሰ ነበር። መነጽሩ ላይ የእንባ ዘለላዎች ይታያሉ። አሳዘነኝ።
የዛን ዕለት ለምን ሚስቱ ፊት ወሲብ ሊያምረው እንደቻለ አሁን ገና በደንብ ተገለጸልኝ። ያን ክስተት
በበቀል መልክ ከአእምሮው ለማጥፋት ያደረገው ከንቱ ሙከራ ነበር። አሳዘነኝ።
የምሩን ነው ማሪያን የሚወዳት። ከንፈሩን ሳምኩት። እያነባ ከንፈሬን ይስመኝ ነበር። ወደ ጓሮ ወስጄው እኛ ብቻ የምንጠቀምበት «የሴቶች ቤት» የምንላት ልብስ መቀየሪያ ክፍል ይዤው ገባው። በሩን ከውስጥ
ቀረቀርኩት። ገንዘብ የሌለበት ንጹህ ፍቅር ሰራን። የሚገርመው ከኔ ጋ ፍቅር እየሰራ ልቡ ግን ያለው ሚስቱ ጋር ነበር! ማሪያ! ማሬ! Tell me that you love me!Tell me you never see him again Tell me you never cheat » እያለ ያቃስት ነበር።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 እና #Share #Share ማድረግ እንዳይረሳ
#ለሮዚ_መልክታችሁን
#ለማስተላለፍ_ከፈለጋችሁ #ከታችያለውን_email #መጠቀም_ትችላላችሁ👇
rozachichinia@gmail.com
ለኛ ደሞ ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
አንድ ሁለት የምትልበት አጋጣሚ ነበር። አባቷ ጾታ የመቀየሩን ሀሳብ እርግፍ አድርጋ እንድትተው የመከሯት «ወንዶች ላያቸው ላይ የምታማግጥ ሴትን ይበልጥ ያፈቅራሉ» የሚለውን አስተሳሰባቸውን በሷ ላይ በመጫን ነበር። ይህ ሁኔታ ነው የዶክተር ቃልአብን ልብ ክፉኛ የሚጎዳ ነገር እንዲከሰት
ምክንያት የሆነው።
ከማሪያ ጋር የተማሪ አፓርትመንት ተከራይተው አብረው መኖር ጀምረው ሳለ ከእለታት አንድ ቀን ያልተጠበቀ ነገር ተከሰተ። ይኸውም ዶክተር ቃልአብ የፈተና ሰሞን ስለነበር ድካም ተጫጭኖት
ከላይብረሪ መጥቶ ቤት በተኛበት ሁኔታ የሆነ እንግዳ ድምጽ ይቀሰቅሰዋል። አንሶላውን ከላዩ ላይ ገፎ መለመላውን ድምጽ ወደሰማበት ክፍል ሲሄድ ፍጹም ያልጠበቀ ነገር ተመለከተ። ማሪያ ከአንድ
አልጄሪያዊ የቀድሞ ፍቅረኛዋ ጋር የኪችን ካውንተር ጠረጴዛ ላይ ወሲብ ስትፈጽም በአይኑ በብረቱ ተመለከተ። ይህን አልጄሪያዊ ደግሞ ያውቀዋል። ሲኒየሩ ነው፤ በዚያ ላይ የተማሪዎች አፓርትመንት ዉስጥ ሳሎንና ኪችን ሼር ስለሚያደርጉ በተደጋጋሚ አይቶታል። ሆኖም የማሪያ የቀድሞ ፍቅረኛዋ
እንደነበረ ማንም ነግሮት አያውቅም። ያ ማለት ማሪያ ከዶክተር ቃልአብ ጋር ሆና ራሱ በተደጋጋሚ ከአልጄሪያዊው ጋር ወሲብ ትፈጽም ነበር ማለት ነው። የያኔው ተማሪ ቃልአብ በዐይኑ በብረቱ ያየው
ነገር አዘሮ ሊደፋው ሆነ። «በዚያች ቅጽበት ሆኜ ወደ ጌታ መጸለይ ጀመርኩ»አለኝ ዶክተር ቃልአብ
አምላኬ እባክህን ይህን የማየውን ነገር በህልሜ አድርገውና ዘላለም አንተን ሳመሰግን ልኑር"
ዶክተር ቃልአብ መለመሉን፡ እነሱ ደግሞ የኪችን ካቢኔት ጠረጴዛ ላይ መርፌና ክር እንደሆኑ ደርቀው ቀሩ።
አልጄሪያዊው ከደነዘዘበት ነቅቶ ገፍትሮኝ ወጣ። ማሪያ ጠረጴዛው ላይ ሆና ጭኖቿን ከፍታ እየተንቀጠቀጠች የሚሆነውን ነገር በጥሞና ትከታተላለች።ምን እንደሆነ የማላውቀው ዳቢሎስ ሄደህ ባለችበት እነቃት እነቃት እንደማለት ፋንታ ወስባት ወስባት ብሎ ሹክ አለኝ። የተከፈተውን እግሯን ይበልጥ ከፍቼ በከፍተኛ የአውሬ ስሜት ሴክስ አረኳት። ትዝ የሚለኝ ነገር ቢኖር እያቃሰተች ታለቅስ እንደነበረና ይቅርታ እንዳደርግላት ትለምነኝእንደነበረ ነው። ስንጨርስ ተዝለፍልፈን ወደቅን
ተቃቅፈን አለቀስን። በዚያው ቀን ልታገባኝ እንደምትፈልግ ነገረችኝ። መርፌና ክር ሆነን ሳለ would you marry me » አለችኝ። l will አልኳት።በዚያው ቅጽበት ዘላለም ከኔ መለየት እንደማትፈልግ
ገለጸችልኝ፤ በዚያው ቅጽበት ይቅርታዋንም የጋብቻ ጥያቄዋንም ተቀበልኩት። ሻወር ወስደን ተቃቅፈን |
መልሰን ተኛን። በነጋታውም ተኝተን ዋልን። ብዙ ወሲብ አደረግን። ማሪያ መውለድ ብትችል ያን ቀን ትወልድ ነበር የምናስቀና ባልና ሚስቶች ሆንን ትምህርታችንን ጨርሰን ወደ ኢትዬጵያ መጣን።
ጥያቄ ልጠይቀው አፌን ሳቆበቁብ በእጁ አስቆመኝ። ልጠይቀው ያሰብኩት ነገር ገብቶታል።
ከዚያን ቀን ጀምሮ ግን አንድ ትንሽ ዲያቢሎስ ደሜ ዉስጥ ተሰንቅሮ ቀረ። you know ማሪያን እጅግ በጣም እንደማፈቅራት። you know እሷ አንድ ነገር ብትሆንብኝ በህይወት ልቆይ የምፈልግበት አንድም ምክንያት እንደሌለ። መቼም ልለያት አልፈልግም፡፡ ልጅ መውለድ አልቻልንም። ሦስት ቡችሎችን ነው የምናሳድገው፤ ቴዎድሮስን፣ ብርቱካንና በላይን። አለመውለዳችን ግን እኛን ሊለየን የሚችል ቁም ነገር አይደለም። በሚቀጥለው አመት አንድ ሴት ልጅ በጉዲፈቻ ልናሳድግ ወስነናል። በኔና በሷ
የፍቅር ሕይወት ውስጥ ልጅ ያለመውለድ ጉዳይ ጭራሽ እንደ ችግር አይተነውም አናውቅም። እኛ የምንፈልገው እንደተፋቀርን ቶሎ ቶሎ ኖረን፣ አጠር ያለች የምትጣፍጥ ህይወት ኖረን መሞት ነው።
ችግሩ ያለው ከኔ ነው። እኔን ከያዘኝ ዲያቢሎስ ነው ችግሩ።…”
"ይህ የምነግርሽ ትንሽዬ ዲያቢሎስ ያን ሌሊት የተፈጠረውን ነገር ላለፉት 7 ዓመታት መልሶ መላልሶ ያመጣብኛል። ፀለይኩበት፤ አፀለይኩበት። ሊለቀኝ አልቻለም። ብዙ ቸርች ሄጃለው ከዚህ
ዲያቢሎስ ለመፈወስ። እየባሰብኝ መጣ። ይህ ዲያቢሎስ ስራው አንድ ነው፤ የዛን ሌሊቱን ነገር ቁልጭ
አድርጎ በአእምሮዬ እንደፊልም ያሳየኛል። አልጄሪያዊውን አልሙሳዊን ደጋግሞ ያመጣብኛል። ሮዚ አታምኚኝም ድርጊቱ ልከ ዛሬ እንደተፈጸመ አድርጎ ያሳየኛል። ኪችኑ ውስጥ የነበረውን ሹካ ሳይቀር፣
የአልሙሳዊን መቀመጫ ሳይቀር…። ያን ትዕይነት ለማጥፋት አንቺ ጋር እመጣለሁ በምወዳት ሚስቴ ላይ እባልጋለሁ-። ምን ላድርግ?? እስከመቼ ነው የዚህ እርኩስ መንፈስ መጫወቻ ሆኜ የምቀረው!?….”
ማሪያን በተመሳሳይ መልኩ ብበቀላት ይህ ችግር ለዘላለሙ እንደሚጠፋልኝ የመከሩኝ ሁለት የአሜሪካ ሳይካትሪስቶች የጻፉት መጽሐፍ ነው።ጸሐፊዎቹን ለሥራ ቨርጂኒያ በሄድኩበት ላገኛቸው
ሞከሬ አልተሳካልኝም። በኢሜይል ሁኔታውን ጻፍኩላቸው። የመከሩኝ ነገር አስደነገጠኝ። ግዴለም ሚስትህን ንገራትና ሞክረው አሉኝ። የተለመደ ቴራፒ እንደሆነ ነገሩኝ። እነሱ መፍትሄ ነው የሚሉት ቴራፒ በተመሳሳይ መንገድ እንድበቀላት ነው። እሷ ባደረገችው መንገድ ካልተበቀልካት ትዕይንቱ
ከአእምሮህ ሊወጣ አይችልም አሉኝ። ነገር ግን ፈራሁ፤ የምጎዳት መሰለኝ። በዚህ ፍርሃቴ ውስጥ ሆኜ የፈጸምኩት ድርጊት ነው የዚያ ምሽቱ ድራማ። አንቺ ዘንድ የምመጣው ይህን እርኩስ መንፈስ
ለማስታገስ ብቻ ነው፤ ሮዝ…፤እንጂ ሚስቴን ጠልቼ አይደለም።”
ዶክተር ቃልአብ አንገቴ ውስጥ ፊቱን ቀበረ። ቀና አድርጌ ሳየው የምርም እያለቀሰ ነበር። መነጽሩ ላይ የእንባ ዘለላዎች ይታያሉ። አሳዘነኝ።
የዛን ዕለት ለምን ሚስቱ ፊት ወሲብ ሊያምረው እንደቻለ አሁን ገና በደንብ ተገለጸልኝ። ያን ክስተት
በበቀል መልክ ከአእምሮው ለማጥፋት ያደረገው ከንቱ ሙከራ ነበር። አሳዘነኝ።
የምሩን ነው ማሪያን የሚወዳት። ከንፈሩን ሳምኩት። እያነባ ከንፈሬን ይስመኝ ነበር። ወደ ጓሮ ወስጄው እኛ ብቻ የምንጠቀምበት «የሴቶች ቤት» የምንላት ልብስ መቀየሪያ ክፍል ይዤው ገባው። በሩን ከውስጥ
ቀረቀርኩት። ገንዘብ የሌለበት ንጹህ ፍቅር ሰራን። የሚገርመው ከኔ ጋ ፍቅር እየሰራ ልቡ ግን ያለው ሚስቱ ጋር ነበር! ማሪያ! ማሬ! Tell me that you love me!Tell me you never see him again Tell me you never cheat » እያለ ያቃስት ነበር።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 እና #Share #Share ማድረግ እንዳይረሳ
#ለሮዚ_መልክታችሁን
#ለማስተላለፍ_ከፈለጋችሁ #ከታችያለውን_email #መጠቀም_ትችላላችሁ👇
rozachichinia@gmail.com
ለኛ ደሞ ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍5❤1
#አባ_ይፍቱኝ
አባ ይፍቱኝ
ሲኦል አለ ሲሉኝ፥ የለም ብየ ክጄ
የባልቴት ተረት ነው፥ በማለት ቀልጄ
አውቄ በድፍረት፥ በድያለሁና
ያንጹኝ በንስሐ፥ ያንሱኝ በቀኖና
ሲኦል ከነጭፍራው፥ በጉም ተሸፍኖ
እንዴት ሳላየው ኖርኩ፥ ካጠገቤ ሆኖ?
#አባ_ይፍቱኝ
ሰይጣን ብሎ ነገር፥ የተጭበረበረ
ዋዛ ነው ቧልት ነው፥ ብየ አስብ ነበረ
ይሄው እውነት ሆኖ፥ ዋዛና ተረቱ
ባይኔ በብረቱ
ዲያብሎስን አየሁት፥ በሸሚዝ ዘንጦ
እልፍ ግዳይ ጥሎ፥ ቸብቸቦ ጨብጦ
#አባ
ልክ እንደ ብርሌ፥ እጥንት ሲከሰክስ
አባይን አዋሽን፥ የሚያለንቅ ደም ሲፈስ
ለምለም ፍጥረት ሁላ፥ ወደ አመድ ሲመለስ
ልክ እንደ ጧፍ ሐውልት፥ ምስኪኖች ሲጋዩ
ምድጃው ዳር ሆነው፥ ይሄንን እያዩ
ገሃነም ከላይ ነው፥ ብለው መሳትዎ
እርስዎ እንደፈቱኝ፥ እግዚሃር ይፍታዎ።
🧿በእውቀቱ ስዩም🧿
አባ ይፍቱኝ
ሲኦል አለ ሲሉኝ፥ የለም ብየ ክጄ
የባልቴት ተረት ነው፥ በማለት ቀልጄ
አውቄ በድፍረት፥ በድያለሁና
ያንጹኝ በንስሐ፥ ያንሱኝ በቀኖና
ሲኦል ከነጭፍራው፥ በጉም ተሸፍኖ
እንዴት ሳላየው ኖርኩ፥ ካጠገቤ ሆኖ?
#አባ_ይፍቱኝ
ሰይጣን ብሎ ነገር፥ የተጭበረበረ
ዋዛ ነው ቧልት ነው፥ ብየ አስብ ነበረ
ይሄው እውነት ሆኖ፥ ዋዛና ተረቱ
ባይኔ በብረቱ
ዲያብሎስን አየሁት፥ በሸሚዝ ዘንጦ
እልፍ ግዳይ ጥሎ፥ ቸብቸቦ ጨብጦ
#አባ
ልክ እንደ ብርሌ፥ እጥንት ሲከሰክስ
አባይን አዋሽን፥ የሚያለንቅ ደም ሲፈስ
ለምለም ፍጥረት ሁላ፥ ወደ አመድ ሲመለስ
ልክ እንደ ጧፍ ሐውልት፥ ምስኪኖች ሲጋዩ
ምድጃው ዳር ሆነው፥ ይሄንን እያዩ
ገሃነም ከላይ ነው፥ ብለው መሳትዎ
እርስዎ እንደፈቱኝ፥ እግዚሃር ይፍታዎ።
🧿በእውቀቱ ስዩም🧿
#እየጠበቀችው_ነው !
#በናትናኤል
የሆነ ቀን…
ከቤተክርስትያን ስትመለስ እንቅፋት መታት ። ነጠላ ጫማዋ ተገነጠለ ። መሀል መንገድ ላይ ስለነበረች ተጨነቀች ። እያነከሰች ወደ መንገዱ ዳር ሂዳ ስትቀመጥ አንድ ጀለቢያ የለበሰ ወጣት አንዲት ሱቅ ተደግፎ ተመለከታት። ወዲያው ከሱቁ መርፌ ገዝቶ ተከተላት ።
እንደ ደረሰ ፈገግታውን ለግሷት ከስሯ ተንበረከከ ። ምንም አልተነጋገሩም ።
እግሯ እየደማ መሆኑን ሲመለከት ሳያመንታ የለበሰውን ቀደደው ። ፊቱ ላይ ፅንፍ የለሽ ርህራሄ ይነበባል ። በቅዳጁ አውራ ጣቷን አሰረላት ። የገዛውን መርፌ በስር አስገብቶ ነጠላ ጫማዋን ጠገነው ።
እሷ እንባ ባቀረዘዙ አይኖቿ በግርምት እያየችው ነው ። ሲጨርስ አመሰግናለሁ እንኳ ሳትለው ወደ ቤቷ ገሰገሰች ። መፍጠን አለባት ።
…
በሌላ ቀን …
ያኔ ከቤተ ክርስትያን መልስ በመዘግየቷ ቁጡው የእንጀራ አባቷ በሽቦ ገርፈዋታል ። ጠበል እንድታመጣላቸው ከሰጧት ሰአት አንዲት ደቂቃ እንኳ እንድታረፍድ አይፈቅዱላትም ። ጀርባዋ ላይ የተጋደመው ሰንበር ትንንሽ የቆዳ መስኮቶችን ሰርቷል ። እንዲህ በሽቦ ተገርፋ ጀርባዋ ላይ ምልክት ሲወጣባት አክሱምን የተደገፈች ይመስላታል ። የአክሱም መስኮቶች ጀርባዋ ላይ የወጡ ይመስላታል። አሁንም ላለመገረፍ ከቤተክርስትያን ስትመለስ እየፈጠነች ነበር ። በሁለት ሊትሩ ሀይላንድ ጠበል ይዛለች ። ሱቁ አካባቢ ስትደርስ ግን ቆም አለች ። ጫማዋን ቀስ ብላ ገነጠለችው ። ልጁ በድጋሚ መጣ !
ጫማዋን ሲጠግንላት አሁንም ምንም አላወሩም ። እንደ ትንግርት ያያታል ። በፍቅር ታየዋለች ። ሲጨርስ አመሰግናለሁ እንኳ ሳትለው መንገዷን ቀጠለች… ከሄደች በኋላ ግን ዙራ ተመለከተችው ።
…
በሌ..ላ ቀን
ልጁ ሱቁን ተደግፎ እየጠበቃት ነው ። እንደምትመጣ ያውቃል ። ሱቁጋ ስትደርስ ጫማዋ እንደሚገነጠል ያውቃል ። እስከዛው እየሰገደ ይጠብቃታል ። ሱቁ ሱቅ ብቻ አይደለም። መስጊድም ጭምር ነው ። አክሱም ከተማ ውስጥ መስጊድ ስለሌለ ከሱቁ ጋር ከተያያዘው ጠባብ ቤት ውስጥ ብዙዎች ይሰግዳሉ ።
ድንገት የታመሙት አጎቱን አሰበ ። በጠና ደዌ ተመቶ ችፍ ያለ ፊታቸው ትውስ አለው ። ፊታቸው መስኮት በሚመስሉ ፍርግርጎች የተሞላ ነው። አጎቱ ተዳክመዋል ። እያንዳንዱን ቀን በስቃይ ነው የሚያሳልፉት ። ሀሳብ ውስጥ እያለ ልጅቷ መጣች ። ሄደ… ጫማዋን ለመጠገንና አይኖቿን ለማየት …ሄደ ።
…
ሁል ቀን :
ግርፋት ያሻከረው ጀርባዋ ከኋላ በነጠላ ተሸፍኖ ሲያዩት አያስታውቅም።
ባጎቱ ህመም የተጨነቀው ልቡ ለስግደት ሲደፋ አያስታውቅም ።
እንደተለመደው ስትፈጥን ትመጣና ሱቁ አካባቢ ስትደርስ ቆም ትላለች…
እንደተለመደው ሰግዶ ሲጨርስ ሱቁን ተደግፎ ባይኑ ይማትራል።
የተገነጠለ ጫማዋን አንጠልጥላ ከመንገዱ ዳር ትቀመጣለች ።
ፈገግ እያለ ይቀርባታል ። ምንም ሳያወሩ ጫማዋን ብቻ ጠግኖላት ይለያያሉ ።
…
የሆነ ቀን
ድክምክም ያለ ጀርባዋን በስስ ነጠላ እንደሸፈነች መጓዟን ቀጠለች ። ከቤተ/ክ እየተመለሰች ነው ። ሱቁ አካባቢ ስትደርስ እንደ ሁልጊዜው ነጠላ ጫማዋን ሆን ብላ ገነጠለችው ።
ከመንገዱ ዳር ተቀምጣ ልጁን መጠበቅ ጀመረች ።
ልጁ :
ታመው የነበሩት አጎቱ ስለሞቱ የቀብር ስነስርአታቸውን ለማስፈፀም ጉዞ ላይ ነው ። እዚያ አባካባቢ ሙስሊሞች መቀበር አይችሉም ። የመቀበርያ ቦታ የላቸውም ። ለዚህ ሲባል ረጅም ጉዞ ማድረግ አለባቸው ።
የእንጀራ አባቷ: እሷን ለመግረፍ እጅግ በቋመጠ ሁኔታ ሽቦ ይዘው እየጠበቋት ነው ። ዛሬ በጣም አርፍዳለች ። በተለየ ሁኔታ ነው የሚገርፏት ። ሽቧቸውን እየደራረቡ ከመጠን በላይ አወፈሩት ። ከወዲያ ወዲህ እየተንጎራደዱ እሳት አይናቸውን ማንቀልቀል ቀጠሉ ።
ልጁ ግን በጣም ዘገየ ። ለነገሩ ከዚያም በላይ ይዘገያል ። ምክንያቱም አጎቱን ለመቅበር ከሰአታት በላይ በእግሩ መጓዝ አለበት ።
እሬሳውን የተሸከሙ አራት ሰዎች ከፊት ሲመሩ እሱ ከኋላ ይከተላል ። በሀዘኑም ውስጥ ሁኖ እያሰባት ነው ። ለቅፅበት ህይወት የአክሱም ሀውልት መስኮቶችን መስላ ታየችው… የማያስገቡ ደግሞም የማያወስወጡ መስኮቶች ።
አባቷ የቅጣት ደረጃቸውን ከፍ ሊያደርጉት አስበዋል። ቀበቷቸውን እያላሉ አልጋቸውን ተመለከቱ ።
ልጁ ገና ያረፍዳል ምናልባትም ደግሞ ያመሻል ። ልጅቷ ግን እየጠበቀችው ነው…
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ቀን። 🙏
#በናትናኤል
የሆነ ቀን…
ከቤተክርስትያን ስትመለስ እንቅፋት መታት ። ነጠላ ጫማዋ ተገነጠለ ። መሀል መንገድ ላይ ስለነበረች ተጨነቀች ። እያነከሰች ወደ መንገዱ ዳር ሂዳ ስትቀመጥ አንድ ጀለቢያ የለበሰ ወጣት አንዲት ሱቅ ተደግፎ ተመለከታት። ወዲያው ከሱቁ መርፌ ገዝቶ ተከተላት ።
እንደ ደረሰ ፈገግታውን ለግሷት ከስሯ ተንበረከከ ። ምንም አልተነጋገሩም ።
እግሯ እየደማ መሆኑን ሲመለከት ሳያመንታ የለበሰውን ቀደደው ። ፊቱ ላይ ፅንፍ የለሽ ርህራሄ ይነበባል ። በቅዳጁ አውራ ጣቷን አሰረላት ። የገዛውን መርፌ በስር አስገብቶ ነጠላ ጫማዋን ጠገነው ።
እሷ እንባ ባቀረዘዙ አይኖቿ በግርምት እያየችው ነው ። ሲጨርስ አመሰግናለሁ እንኳ ሳትለው ወደ ቤቷ ገሰገሰች ። መፍጠን አለባት ።
…
በሌላ ቀን …
ያኔ ከቤተ ክርስትያን መልስ በመዘግየቷ ቁጡው የእንጀራ አባቷ በሽቦ ገርፈዋታል ። ጠበል እንድታመጣላቸው ከሰጧት ሰአት አንዲት ደቂቃ እንኳ እንድታረፍድ አይፈቅዱላትም ። ጀርባዋ ላይ የተጋደመው ሰንበር ትንንሽ የቆዳ መስኮቶችን ሰርቷል ። እንዲህ በሽቦ ተገርፋ ጀርባዋ ላይ ምልክት ሲወጣባት አክሱምን የተደገፈች ይመስላታል ። የአክሱም መስኮቶች ጀርባዋ ላይ የወጡ ይመስላታል። አሁንም ላለመገረፍ ከቤተክርስትያን ስትመለስ እየፈጠነች ነበር ። በሁለት ሊትሩ ሀይላንድ ጠበል ይዛለች ። ሱቁ አካባቢ ስትደርስ ግን ቆም አለች ። ጫማዋን ቀስ ብላ ገነጠለችው ። ልጁ በድጋሚ መጣ !
ጫማዋን ሲጠግንላት አሁንም ምንም አላወሩም ። እንደ ትንግርት ያያታል ። በፍቅር ታየዋለች ። ሲጨርስ አመሰግናለሁ እንኳ ሳትለው መንገዷን ቀጠለች… ከሄደች በኋላ ግን ዙራ ተመለከተችው ።
…
በሌ..ላ ቀን
ልጁ ሱቁን ተደግፎ እየጠበቃት ነው ። እንደምትመጣ ያውቃል ። ሱቁጋ ስትደርስ ጫማዋ እንደሚገነጠል ያውቃል ። እስከዛው እየሰገደ ይጠብቃታል ። ሱቁ ሱቅ ብቻ አይደለም። መስጊድም ጭምር ነው ። አክሱም ከተማ ውስጥ መስጊድ ስለሌለ ከሱቁ ጋር ከተያያዘው ጠባብ ቤት ውስጥ ብዙዎች ይሰግዳሉ ።
ድንገት የታመሙት አጎቱን አሰበ ። በጠና ደዌ ተመቶ ችፍ ያለ ፊታቸው ትውስ አለው ። ፊታቸው መስኮት በሚመስሉ ፍርግርጎች የተሞላ ነው። አጎቱ ተዳክመዋል ። እያንዳንዱን ቀን በስቃይ ነው የሚያሳልፉት ። ሀሳብ ውስጥ እያለ ልጅቷ መጣች ። ሄደ… ጫማዋን ለመጠገንና አይኖቿን ለማየት …ሄደ ።
…
ሁል ቀን :
ግርፋት ያሻከረው ጀርባዋ ከኋላ በነጠላ ተሸፍኖ ሲያዩት አያስታውቅም።
ባጎቱ ህመም የተጨነቀው ልቡ ለስግደት ሲደፋ አያስታውቅም ።
እንደተለመደው ስትፈጥን ትመጣና ሱቁ አካባቢ ስትደርስ ቆም ትላለች…
እንደተለመደው ሰግዶ ሲጨርስ ሱቁን ተደግፎ ባይኑ ይማትራል።
የተገነጠለ ጫማዋን አንጠልጥላ ከመንገዱ ዳር ትቀመጣለች ።
ፈገግ እያለ ይቀርባታል ። ምንም ሳያወሩ ጫማዋን ብቻ ጠግኖላት ይለያያሉ ።
…
የሆነ ቀን
ድክምክም ያለ ጀርባዋን በስስ ነጠላ እንደሸፈነች መጓዟን ቀጠለች ። ከቤተ/ክ እየተመለሰች ነው ። ሱቁ አካባቢ ስትደርስ እንደ ሁልጊዜው ነጠላ ጫማዋን ሆን ብላ ገነጠለችው ።
ከመንገዱ ዳር ተቀምጣ ልጁን መጠበቅ ጀመረች ።
ልጁ :
ታመው የነበሩት አጎቱ ስለሞቱ የቀብር ስነስርአታቸውን ለማስፈፀም ጉዞ ላይ ነው ። እዚያ አባካባቢ ሙስሊሞች መቀበር አይችሉም ። የመቀበርያ ቦታ የላቸውም ። ለዚህ ሲባል ረጅም ጉዞ ማድረግ አለባቸው ።
የእንጀራ አባቷ: እሷን ለመግረፍ እጅግ በቋመጠ ሁኔታ ሽቦ ይዘው እየጠበቋት ነው ። ዛሬ በጣም አርፍዳለች ። በተለየ ሁኔታ ነው የሚገርፏት ። ሽቧቸውን እየደራረቡ ከመጠን በላይ አወፈሩት ። ከወዲያ ወዲህ እየተንጎራደዱ እሳት አይናቸውን ማንቀልቀል ቀጠሉ ።
ልጁ ግን በጣም ዘገየ ። ለነገሩ ከዚያም በላይ ይዘገያል ። ምክንያቱም አጎቱን ለመቅበር ከሰአታት በላይ በእግሩ መጓዝ አለበት ።
እሬሳውን የተሸከሙ አራት ሰዎች ከፊት ሲመሩ እሱ ከኋላ ይከተላል ። በሀዘኑም ውስጥ ሁኖ እያሰባት ነው ። ለቅፅበት ህይወት የአክሱም ሀውልት መስኮቶችን መስላ ታየችው… የማያስገቡ ደግሞም የማያወስወጡ መስኮቶች ።
አባቷ የቅጣት ደረጃቸውን ከፍ ሊያደርጉት አስበዋል። ቀበቷቸውን እያላሉ አልጋቸውን ተመለከቱ ።
ልጁ ገና ያረፍዳል ምናልባትም ደግሞ ያመሻል ። ልጅቷ ግን እየጠበቀችው ነው…
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ቀን። 🙏
👍2😁1
#የእሷ_እንቆቅልሽ !
#በናትናኤል
አፍቅራው ከሆነ ለምን እንዳፈቀረችው አይገባኝም። ሰው በበዛበት አካባቢ ሳይቀር በጥፊ ሲያጠናግራት ምንም አይመስለውም። የአፍንጫዋን ደም በሶፍት እየጠረገች ፀጥ ትላለች።
«ቱ! ሴት አይደለሽም አንቺ ዝፍዝፍ! እበት ነገር ነሽ! !ጥንብ!!» …እንደዚህ ከሰው ፊት ሲሰድባት ቅሬታዋን ውጣ አንገቷን ትሰብራለች እንጂ ምንም አትናገረውም።
.
ብዙ ጊዜ እየገላገልኩ ከደንዳና መዳፉ ላተርፋት ጥሬያለሁ። እየቆየ ሳስተውላት ግን ህይወቷ ላይ ለውጥ የሚያስከትል ምንም አይነት ውሳኔ አትወስንም። በዚህ ስለተገረምኩ ፣ ትዕግስቷ ምን ያህል እንደሆነ ለማየት ስለጓጓሁ፤ በጠፈጠፋትና ባሸማቀቃት ቁጥር እንደ ፊልም ተረጋግቼ ማየት ጀመርሁ።
.
ግን የያዛት ፍቅር ነው ? ለምን አፈቀረችው ?
እሱ ዝና አለው። ደራሲ ነኝ ይላል። ማህበራዊ ሚድያ ላይ እንደምንም ተንደፋድፎ ስሙን ሰቅሏል። ግን ስለ ሴት መከበር ይፅፋል እንጂ ሴትን የሚያከብር ቅንጣት ስብዕና እንደሌለው በአካል የምናውቀው እናውቀዋለን።
የገንዘብ ችግር ኑሮባት ይሆን ? ስል አስቤ አውቃለሁ። ከእሱ ጋር እንደዛ የሚያላትማት የሆዷ ጉዳይ ይሆንን? ግን አይደለም። አንዳንዴ ሲጣሉ ለቀናት ወደ ቤቷ ትሄዳለች። እሷ አኩርፋው ሳይሆን የእሱ ኩርፊያ እስኪለቀው። እና ምን ሁና ነው ? እንቆቅልሹን ልፈታ እታገላለሁ።
.
አንድ ቀን አምሽታ መጣች። ሲደውልላት «ቤት ነኝ» ብላው ነበር። ቤት እንዳልነበረች ግን አውቆባታል። ፀጉሯን ጨምድዶ ከግድግዳ ጋር ያጋጫት ጀመር።
«ልቀቀኝ ! ኡ ! ኡ !ኡ! …ኸረ ገደለኝ !» ጮኸች!
«አንቺም ሰው ሁነሽ እኔን ትዋሻለሽ ? አንቺ ጋለሞታ ! አንቺ ጥንብ አንሳ! »
« ኸረ ገደለኝ! ውውውውውውውይ!»
«ፀጥ በይ አህያ የአህያ ልጅ! ልጅሽን በስነ ስርአት አታሳድጊም ከመንዘላዘል? ሸርሙጣ!»
ጎረቤት መጥቶ እስኪገላግላት የተወሰኑ ደቂቃዎችን በስቃይ አሳለፈች።
« እሄዳለሁ» አለች።
«ሂጂ ጥርግ በይ !» …ሌሊት ስለነበር ማደር ግድ ይላታል። አደረች።
የመጨረሻዋ ነው ብዬ አሰብኩ። ወሲብ መፈፀማቸው ያስታውቃል። የመሰነባበቻ ይሆናል ወሲቡ። እንዲቆርጥላት !
.
ለ ሁለት ቀናት ከሱ ቤት ሳትመጣ ቀረች። በመጨረሻም ወሰነች ስል አሰብኩ። ግን ተሳስቼ ነበር። በሶስተኛው ቀን ማታ አቅፏት ሲገባ አየሁ።
« ልጅ አላት። ቤተሰቦቿ እያሳደጉላት ይሆናል። ለልጇ አታስብም? ከእሱ ጋር የምታባክነው ከንቱ ጊዜ ለልጇ የሚያስፈልግ ወርቃማ ሰአት አይደለም? ምን ሁና ነው ? » እላለሁ። እንቆቅልሹ ይገዝፍብኛል።
ብዙ ጊዜ ሲጣሉ የሚገላግላቸው ፣ ሁላችንንም የሚያውቀን ዮሀንስ ጋር ስንገናኝ እንዲህ አለኝ።
«ሴት ልጅ ታዋቂ ሰው ስታይ ብዙ ነገሯን ትረሳለች ። ከማይታወቅ ወርቅ ይልቅ የሚታወቅ መዳብ ለሴት ልጅ ትልቅ ዋጋ አለው። »
« ተው እንደሱ አትበል። ሀይለኛ ፍቅር ነው የያዛት! »
« ሃሃሃሃ! ባክህ ፍቅር አልያዛትም። ከእሱ ጋር መታየት የሚያስከብራት መስሏት ነው። ብታፈቅረው ኑሮ ላዩ ላይ አትደርብም። እኔም ጋር አድረናል» ሲለኝ በድንጋጤ እየጠጣሁ የነበረውን ሻይ ጠረንጴዛው ላይ ለቀኩት።
.
ከሁለት አመት በኋላ፤ ዛሬ ጠዋት የምሰራበት ድርጅት ውስጥ ፀሀፊ ለመቅጠር የቃል ፈተና እያደረኩ እያለ ፣ አንዲት ሴት መጣች። ራሷ ናት ፤ ብሩክቲ!
ስታየኝ ጥቂት እንደማፈር አለች። እንድትረጋጋ ነግሬያት ቃለመጠይቁን ጀመርኩ። የምጠይቃትን ጥያቄዎች ከግማሽ በላይ በትክክል መልሳለች። በዚያ ላይ ታሳዝናለች። የማውቃት ሰው ናት። ከእሷ የተሻሉ ቢኖሩም ያ የማውቀው ታሪክ ተፅዕኖ አሳድሮብኝ ላሳልፋት አሰብኩ።
«እሺ እንደውልልሻለን» ብያት መውጣት ጀመረች። በሩ ላይ ስትደርስ ዘወር ብላ በድጋሚ አየችኝ። ፊቷ ላይ የበለዘ ነገር ያየሁ መሰለኝ። ማመን አልቻልኩም። አሁንም በዚያ ሁኔታ ውስጥ ናት። የምሰራበት ድርጅት ጠንካራ ሴቶችን መቅጠር ይፈልጋል። ራሷን የማታከብር ሴት ለምንም አትሆንም ስል አሰብኩ። ጣልኳት !! ስለጣልኳት አዝናለሁ። ግን የወደቀችው በራሷ መሰለኝ!!
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ። 🙏
#በናትናኤል
አፍቅራው ከሆነ ለምን እንዳፈቀረችው አይገባኝም። ሰው በበዛበት አካባቢ ሳይቀር በጥፊ ሲያጠናግራት ምንም አይመስለውም። የአፍንጫዋን ደም በሶፍት እየጠረገች ፀጥ ትላለች።
«ቱ! ሴት አይደለሽም አንቺ ዝፍዝፍ! እበት ነገር ነሽ! !ጥንብ!!» …እንደዚህ ከሰው ፊት ሲሰድባት ቅሬታዋን ውጣ አንገቷን ትሰብራለች እንጂ ምንም አትናገረውም።
.
ብዙ ጊዜ እየገላገልኩ ከደንዳና መዳፉ ላተርፋት ጥሬያለሁ። እየቆየ ሳስተውላት ግን ህይወቷ ላይ ለውጥ የሚያስከትል ምንም አይነት ውሳኔ አትወስንም። በዚህ ስለተገረምኩ ፣ ትዕግስቷ ምን ያህል እንደሆነ ለማየት ስለጓጓሁ፤ በጠፈጠፋትና ባሸማቀቃት ቁጥር እንደ ፊልም ተረጋግቼ ማየት ጀመርሁ።
.
ግን የያዛት ፍቅር ነው ? ለምን አፈቀረችው ?
እሱ ዝና አለው። ደራሲ ነኝ ይላል። ማህበራዊ ሚድያ ላይ እንደምንም ተንደፋድፎ ስሙን ሰቅሏል። ግን ስለ ሴት መከበር ይፅፋል እንጂ ሴትን የሚያከብር ቅንጣት ስብዕና እንደሌለው በአካል የምናውቀው እናውቀዋለን።
የገንዘብ ችግር ኑሮባት ይሆን ? ስል አስቤ አውቃለሁ። ከእሱ ጋር እንደዛ የሚያላትማት የሆዷ ጉዳይ ይሆንን? ግን አይደለም። አንዳንዴ ሲጣሉ ለቀናት ወደ ቤቷ ትሄዳለች። እሷ አኩርፋው ሳይሆን የእሱ ኩርፊያ እስኪለቀው። እና ምን ሁና ነው ? እንቆቅልሹን ልፈታ እታገላለሁ።
.
አንድ ቀን አምሽታ መጣች። ሲደውልላት «ቤት ነኝ» ብላው ነበር። ቤት እንዳልነበረች ግን አውቆባታል። ፀጉሯን ጨምድዶ ከግድግዳ ጋር ያጋጫት ጀመር።
«ልቀቀኝ ! ኡ ! ኡ !ኡ! …ኸረ ገደለኝ !» ጮኸች!
«አንቺም ሰው ሁነሽ እኔን ትዋሻለሽ ? አንቺ ጋለሞታ ! አንቺ ጥንብ አንሳ! »
« ኸረ ገደለኝ! ውውውውውውውይ!»
«ፀጥ በይ አህያ የአህያ ልጅ! ልጅሽን በስነ ስርአት አታሳድጊም ከመንዘላዘል? ሸርሙጣ!»
ጎረቤት መጥቶ እስኪገላግላት የተወሰኑ ደቂቃዎችን በስቃይ አሳለፈች።
« እሄዳለሁ» አለች።
«ሂጂ ጥርግ በይ !» …ሌሊት ስለነበር ማደር ግድ ይላታል። አደረች።
የመጨረሻዋ ነው ብዬ አሰብኩ። ወሲብ መፈፀማቸው ያስታውቃል። የመሰነባበቻ ይሆናል ወሲቡ። እንዲቆርጥላት !
.
ለ ሁለት ቀናት ከሱ ቤት ሳትመጣ ቀረች። በመጨረሻም ወሰነች ስል አሰብኩ። ግን ተሳስቼ ነበር። በሶስተኛው ቀን ማታ አቅፏት ሲገባ አየሁ።
« ልጅ አላት። ቤተሰቦቿ እያሳደጉላት ይሆናል። ለልጇ አታስብም? ከእሱ ጋር የምታባክነው ከንቱ ጊዜ ለልጇ የሚያስፈልግ ወርቃማ ሰአት አይደለም? ምን ሁና ነው ? » እላለሁ። እንቆቅልሹ ይገዝፍብኛል።
ብዙ ጊዜ ሲጣሉ የሚገላግላቸው ፣ ሁላችንንም የሚያውቀን ዮሀንስ ጋር ስንገናኝ እንዲህ አለኝ።
«ሴት ልጅ ታዋቂ ሰው ስታይ ብዙ ነገሯን ትረሳለች ። ከማይታወቅ ወርቅ ይልቅ የሚታወቅ መዳብ ለሴት ልጅ ትልቅ ዋጋ አለው። »
« ተው እንደሱ አትበል። ሀይለኛ ፍቅር ነው የያዛት! »
« ሃሃሃሃ! ባክህ ፍቅር አልያዛትም። ከእሱ ጋር መታየት የሚያስከብራት መስሏት ነው። ብታፈቅረው ኑሮ ላዩ ላይ አትደርብም። እኔም ጋር አድረናል» ሲለኝ በድንጋጤ እየጠጣሁ የነበረውን ሻይ ጠረንጴዛው ላይ ለቀኩት።
.
ከሁለት አመት በኋላ፤ ዛሬ ጠዋት የምሰራበት ድርጅት ውስጥ ፀሀፊ ለመቅጠር የቃል ፈተና እያደረኩ እያለ ፣ አንዲት ሴት መጣች። ራሷ ናት ፤ ብሩክቲ!
ስታየኝ ጥቂት እንደማፈር አለች። እንድትረጋጋ ነግሬያት ቃለመጠይቁን ጀመርኩ። የምጠይቃትን ጥያቄዎች ከግማሽ በላይ በትክክል መልሳለች። በዚያ ላይ ታሳዝናለች። የማውቃት ሰው ናት። ከእሷ የተሻሉ ቢኖሩም ያ የማውቀው ታሪክ ተፅዕኖ አሳድሮብኝ ላሳልፋት አሰብኩ።
«እሺ እንደውልልሻለን» ብያት መውጣት ጀመረች። በሩ ላይ ስትደርስ ዘወር ብላ በድጋሚ አየችኝ። ፊቷ ላይ የበለዘ ነገር ያየሁ መሰለኝ። ማመን አልቻልኩም። አሁንም በዚያ ሁኔታ ውስጥ ናት። የምሰራበት ድርጅት ጠንካራ ሴቶችን መቅጠር ይፈልጋል። ራሷን የማታከብር ሴት ለምንም አትሆንም ስል አሰብኩ። ጣልኳት !! ስለጣልኳት አዝናለሁ። ግን የወደቀችው በራሷ መሰለኝ!!
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ። 🙏
👍3
#ከአንዲት_ቦንቦሊኖ_መሀል
፡
፡
#በናትናኤል
.
የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ በነበርኩበት ሰአት ከተማሪዎች ተገንጥዬ ብቻዬን መሆንን እመርጥ ነበር ። በተለይ ከሴቶች ጋር ምንም አይነት ቀረቤታ የለኝም ።
.
ሁሌም የእረፍት ሰአት ሲደወል ...ከግቢው መሀል ሜዳ ላይ የተጎነጎነ ሳር ተደግፌ እቀመጣለሁ ። የሚንጫጩ ተማሪዎች፣ ፈንጠር ብለው ለብቻቸው የሚቀመጡ ጥንዶች ፣ክብ ሰርተው የሚያወሩ ጉዋደኞች...ሜዳውን ይሞሉታል ። ከዚህ ሁሉ ግርግር መሀል ለብቻዬ ተቀምጬ አረንጓዴውን ሳር በተመስጦ እያየሁ የምተክዘው እኔ ነኝ ።
.
ዘወትር ከተማሪዎች ግርግር የሚመጣውን ጫጫታ ትኩረት ነፍጌ ወደ ሳሩ አቀረቅራለሁ ። ሜዳው ሰፊ ሲሆን ዙሪያውን በእንጨትና በሽቦ አጥር የተከበበ ነው ። ግቢው ውስጥ አዳዲስ ግንባታዎች በመጀመራቸው ፣ ከተማሪዎች ሌላ የቀን ሰራተኞችም በሜዳው ጥግ ሲርመሠመሡ ይስተዋላሉ ። ይሄ ሁሉ ነገር ግን ትኩረቴን አይስበኝም ። አቀርቅሬ ሳሩን እመለከታለሁ ። ብዙ ጊዜ አቀርቅሬ መተከዝና አይኔን ሳሩ ላይ መትከል ከጀመርኩ ቀና አልልም ።
.
ብቻዬን ስሆን ለብቻዬ የማውቀው እውነት ያለ ያህል ይሰማኛል ።ለብቻዬ የሚሰማኝ ስሜት ያለ ያህል ይሰማኛል ።... አንድ ቀን ተክዤ ካቀረቀርኩበት ቀና ስል አንዲት ሴት ወደ እኔ አተኩራ እያየች ሰብሰብ ወዳሉት ጉዋደኞቿ ስታንሾካሹክና በህብረት ጩኸው ሲስቁ አስተዋልኩ ። ምን እንዳለቻቸው መስማት ባልችልም እንዳፌዘችብኝ ግን ውስጤ ነገረኝ ። መጀመሪያ ነገሩን በቁም ነገር ስላላየሁት ይሁን ወይም ሳሩ ስለሚስበኝ አላውቅም... አንገቴን ወደ ሳሩ መልሼ አቀረቀርኩ ። በኃላ ግን እንደ አዲስ ይቆረቁረኝ ጀመር ።
.
ነገሩን እንደ አጋጣሚ ልቆጥረው ብፈልግም በቀጣዮቹ ቀናቶች ተደጋገመ...በተደጋጋሚ በእረፍት ሰአት እዛ እንደሚቀመጡና እንደዛ እንደሚያደርጉም አስተዋልኩ ። ሁሌ እንሚያሾፉብኝ ገባኝ ።..... አመቱን በሙሉ የትምህርት ቤቱ ሜዳ ላይ የተጎነጎነ ሳር እየተደግፍኩ ስቀመጥና ፊትለፊቴ የሚስቁብኝን ተማሪዎች ስታዘብ አሳለፍኩ ። በጣም እናደድና በጉዳዩ ከውስጤ ጋር እከራከር ነበር ።
የትምህርት ሰአት አልቆ ወደ ቤት ስሄድ በእኔ ላይ ለምን እንደሚያሾፉ ራሴን እጠይቅና መልስ አጣለሁ ። በአለባበሴ ይሆን የሚስቁብኝ?..ብቻዬን ስለምሆን እንደ ጅል ቆጥረውኝ ይሆን ?ወይስ ሰለ ራሴ ያላወኩት ነገር አለ?. እኔንጃ!
..
እየቆየ የትምህርት ቤቱ ግቢ ሳር ቀስ በቀስ እየጠፋና በአቧራ እየተተካ መሄድ ጀመረ ። ግቢው ውስጥ ያልነበሩ የተማሪ መገልገያ ካፌዎች ተከሰቱ ። የመማሪያ ክፍሎች ግድግዳ በሌላ ቀለም አሸበረቀ ። አጥሩ እየፈረሰ እንደገና ታጠረ... ትምህርት ቤቱ ሰፋ ። የትምህርት ቤቱ ብዙ ነገሮች ተለዋወጡ...እኔም ከትምህርት ቤቱ ይሄንን መጥፎ ትዝታ ብቻ ይዤ ተሰናበትኩ ።
.
ከተወሰኑ አመታት በኃላ ትምህርት ቤቱን አልፎ በሚገኝ በሚገኝ አንድ ህንጻ ውስጥ ስራ ተቀጠርኩ ። ህንጻው ትልቅ ሲሆን ሰፊ ቦታ የያዘና ዙሪያውን በሽቦ የታጠረ የመንግስት መስሪያ ቤት ነው ። ስራ መጀመሬን ተከትሎ በህይወቴና በአኗኗሬ ላይ ብዙ ለውጦች ተከስተዋል ። ትምህርት ቤት የነበረኝን መጥፎ ትዝታ ግን መርሳት አልቻልኩም ። ነገሮች አልሳካልኝ ብለው የውድቀትና የሽንፈት ስሜት ሲሰማኝ እንኳን...አንዲት ሴት ስታንሾካሹክና ሌሎቹም ተከትለዋት ሲስቁ በአይመሮዬ ይመጣብኛል። የተሳቀብኝ ይመስለኛል ። ተጽእኖው ቀላል አልነበረም ። መስሪያ ቤቴ ውስጥ ብዙ ሴት ጸሀፊዎችና ተላላኪዎች ሲኖሩ ከአንዳቸውም ጋር አልነጋገርም ነበር ።
ስድስት ሰአት ሲሆን የመስሪያ ቤቱ አባላት ለምሳ ወደ ቤታቸው ሲጣደፉ ፣ እኔ አንድ ወንበር ወደ ውጭ እስብና ከመስሪያ ቤቱ ቅጽር ውስጥ የበቀለውን ለምለም ሳር እየታዘብኩ የስራ ሰአት እስኪጀምር በትካዜ አሳልፋለሁ ።
.
በዚህ ሁኔታ ...የበጋው ወር ገፍቶ ክረምቱ እየገባ ...እኔ የምታዘበው ሳርም እያደገ መጣ ። አንድ ቀን ምሳ ሰአት ላይ ወንበር አውጥቼ ያደገውን ሳር እየታዘብኩ ያስመጣሁትን ቦንቦሊኖ እየበላሁ ነው ፥ ድንገት " ይቅርታ ..." የሚል የሴት ድምፅ ትዝብቴን አቋረጠኝና ቀና አልኩ ። ሳያት የሆነ ስሜት ወረረኝ....ደምስሬ ሲወጣጠርና የልብ ምቴ ሲፈጥን ታወቀኝ......ያኔ ዘጠነኛ ክፍል ለጉዋደኞቿ ስታስቅብኝ የነበረቺዋ ሴት ናት ። ጺሜ በጣም ስላደገና ፊቴ ስለጠቆረ ያወቀቺኝ አልመሠለኝም ። ታኮ የለለው ጫማ የለበሰች ሲሆን ሰፊ የእርጉዝ ልብስ ለብሳለች ።
.
አንድ ጉዳይ ልታስፈፅም እንደመጣችና ሰራተኞች እስኪገቡ እየጠበቀች እንደሆነ ነገረቺኝ ።..የማላውቀው ስሜት ውስጤን እየናጠኝ ተቋቁሜ ጸጥ ብዬ አየሇት። በጣቷ ወደ ሆዷ እየጠቆመችና ፈገግ እያለች..." እርጉዝ ነኝ ...እባክህ ቦንቦሊኖው ሸቶኝ ነው..ቆርሰህ ስጠኝ" አለቺኝ ። ..አይኖቿን እያየሁ አስተዋልኳት ። ግራ በመጋባት አየችኝ ። በመገረም ለጥቂት ሰከንዶች ካስተዋልኳት በኃላ ....እንቢታዬን ገለጽኩላት ። ፊቷ ሲቀላና ቅይርይር ሲል ግራ የሚያጋባ ስሜት ሲፈጠርባት በዝምታ እያየሇት ነበር ። ከአይኔ እየሸሸች እስክትሰወር ድረስ አስተዋልኳት ።...ምንድን ነው ግን ያደረኩት?...
.
ጥቂት አመታቶች እንደ ቀልድ አለፉ...ክረምቱ ያሳረፈው የዝናብ አለንጋ ተረሳ ፥መስሪያ ቤቱ ግቢ ውስጥ የነበረው ሳር ደረቀ ። እኔም ተንጨባሮ የነበረው ጸጉሬንና ጺሜን ስቆረጥ ሌላ ሰው መሠልኩ ። ....ምሳ ሰአት ላይ ወንበሬን ስቤ ከውጭ የተቀመጥኩ ቢሆንም በትዝታ ወደ ሁዋላ ተወርውሬአለሁ......ወደ ዘጠነኛ ክፍል ። ብቻውን ሳር ላይ ቁጭ የሚልና..ሴቶች የሚስቁበት ሁኖ አገኘሁት ራሴን ።ለምን እንደሆነ ባላውቅም ከጉዋደኞቿ ጋር ለምን ታሾፍብኝ እንደነበር ማወቅ ፈለኩ ። ምን ያደርግልሀል?...አልኩት ራሴን ። ለአሁን ሂዎትህ ይጠቅምሀል?..ለምን ማወቅ ፈለክ...ነው ወይስ ዘጠነኛ ክፍል ያሳቀብህ ጉዳይ አሁንም በስራ ባልደረባዎችህ እያሳቀብህ ነው ?...ጉጉቴ እየናረ ራሷን እንድጠይቃት ተማጸነኝ ።ብዙ አመነታሁ....ምንም አይጠቅመኝም አልኩ ።በኃላ ግን ላገኛት ወሰንኩ ።
.
እንደምንም ስልኳን አፈላልጌ አገኘሁና ስደውልላት በሁለተኛው ጥሪ አነሳችው ። ቀዝቀዝ ያለ ሰላምታ ሰጥቻት...ዘጠነኛ ክፍል አብረን እንደተማርንና...ምን አይነት ልጅ እንደሆንኩ ደግሞ ብቸኝነቴን ምልክት አድርጌ ስነግራት ሞቅ ያለ ሰላምታ ሰታኝ ስታበቃ ልታገኘኝ ተስማማች ።
.
ወደ ተቀጣጠርንበት ካፌ ስትመጣ ትልቅ የነበረው ሆዷ ወደ ውስጥ መግባቱን አስተዋልኩ ። እንደበፊቱ ሰፊ ልብስ አለበሰችም ። አንድ ህጻን ልጅ ከስሯ አስከትላለች ። አብዝሀኛዎቹ የከተማ እናቶች የሚለብሱትን አለባበስ የለበሰች ሲሆን ፤ አንገቷ ላይ ስካርፕ ጣል አድርጋለች።
.
እንዳየችኝ ደንግጣ የምትመለስ መስሎኝ ነበር ። እሷ ግን ጸጉሬንና ጺሜን ስለተስተካከልኩ ከዚ በፊት ያገኘችኝ አልመሰላትም ።
ለመጀመሪያ ጊዜ እንደተገናኘ ሰው ሞቅ ያለ ሰላምታ ሰጥታኝ ከፊት ለፊቴ ተቀመጠች ። ከጠበኩት በላይ ተግባቢ ሁና አገኘሇት ። ትምህርት ቤት ውስጥ ስለነበሩአት ጉዋደኞችና አሁን የት እንደ ደረሱ አወራን ። ስትስቅ ጉንጮቿ ይሰረጎዳሉ ። ለብዙ ደቂቃ በጨዋታ ይዛኝ እየሳኩ ጥያቄዬን የምጠይቅበትን አጋጣሚ በመጠበቅ ላይ ነበርኩ ........በመሀል እንደ ድንገት ጠየኳት ።
" ለምን ነበር የምታሾፉብኝ..?...ብዙ ጊዜ እያየሺኝ ታንሾካሽኪ ነበር"
.
በድንጋጤ ፊቷ ተቀያይሮ አስተዋለችኝ ።.አይን አይኗን እያየሁ ነው ። ጸጥታ በመሀከላችን ለጥቂት ደቂቃዎች ነገሰ ። የሚያስፈራ ጸጥታ
፡
፡
#በናትናኤል
.
የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ በነበርኩበት ሰአት ከተማሪዎች ተገንጥዬ ብቻዬን መሆንን እመርጥ ነበር ። በተለይ ከሴቶች ጋር ምንም አይነት ቀረቤታ የለኝም ።
.
ሁሌም የእረፍት ሰአት ሲደወል ...ከግቢው መሀል ሜዳ ላይ የተጎነጎነ ሳር ተደግፌ እቀመጣለሁ ። የሚንጫጩ ተማሪዎች፣ ፈንጠር ብለው ለብቻቸው የሚቀመጡ ጥንዶች ፣ክብ ሰርተው የሚያወሩ ጉዋደኞች...ሜዳውን ይሞሉታል ። ከዚህ ሁሉ ግርግር መሀል ለብቻዬ ተቀምጬ አረንጓዴውን ሳር በተመስጦ እያየሁ የምተክዘው እኔ ነኝ ።
.
ዘወትር ከተማሪዎች ግርግር የሚመጣውን ጫጫታ ትኩረት ነፍጌ ወደ ሳሩ አቀረቅራለሁ ። ሜዳው ሰፊ ሲሆን ዙሪያውን በእንጨትና በሽቦ አጥር የተከበበ ነው ። ግቢው ውስጥ አዳዲስ ግንባታዎች በመጀመራቸው ፣ ከተማሪዎች ሌላ የቀን ሰራተኞችም በሜዳው ጥግ ሲርመሠመሡ ይስተዋላሉ ። ይሄ ሁሉ ነገር ግን ትኩረቴን አይስበኝም ። አቀርቅሬ ሳሩን እመለከታለሁ ። ብዙ ጊዜ አቀርቅሬ መተከዝና አይኔን ሳሩ ላይ መትከል ከጀመርኩ ቀና አልልም ።
.
ብቻዬን ስሆን ለብቻዬ የማውቀው እውነት ያለ ያህል ይሰማኛል ።ለብቻዬ የሚሰማኝ ስሜት ያለ ያህል ይሰማኛል ።... አንድ ቀን ተክዤ ካቀረቀርኩበት ቀና ስል አንዲት ሴት ወደ እኔ አተኩራ እያየች ሰብሰብ ወዳሉት ጉዋደኞቿ ስታንሾካሹክና በህብረት ጩኸው ሲስቁ አስተዋልኩ ። ምን እንዳለቻቸው መስማት ባልችልም እንዳፌዘችብኝ ግን ውስጤ ነገረኝ ። መጀመሪያ ነገሩን በቁም ነገር ስላላየሁት ይሁን ወይም ሳሩ ስለሚስበኝ አላውቅም... አንገቴን ወደ ሳሩ መልሼ አቀረቀርኩ ። በኃላ ግን እንደ አዲስ ይቆረቁረኝ ጀመር ።
.
ነገሩን እንደ አጋጣሚ ልቆጥረው ብፈልግም በቀጣዮቹ ቀናቶች ተደጋገመ...በተደጋጋሚ በእረፍት ሰአት እዛ እንደሚቀመጡና እንደዛ እንደሚያደርጉም አስተዋልኩ ። ሁሌ እንሚያሾፉብኝ ገባኝ ።..... አመቱን በሙሉ የትምህርት ቤቱ ሜዳ ላይ የተጎነጎነ ሳር እየተደግፍኩ ስቀመጥና ፊትለፊቴ የሚስቁብኝን ተማሪዎች ስታዘብ አሳለፍኩ ። በጣም እናደድና በጉዳዩ ከውስጤ ጋር እከራከር ነበር ።
የትምህርት ሰአት አልቆ ወደ ቤት ስሄድ በእኔ ላይ ለምን እንደሚያሾፉ ራሴን እጠይቅና መልስ አጣለሁ ። በአለባበሴ ይሆን የሚስቁብኝ?..ብቻዬን ስለምሆን እንደ ጅል ቆጥረውኝ ይሆን ?ወይስ ሰለ ራሴ ያላወኩት ነገር አለ?. እኔንጃ!
..
እየቆየ የትምህርት ቤቱ ግቢ ሳር ቀስ በቀስ እየጠፋና በአቧራ እየተተካ መሄድ ጀመረ ። ግቢው ውስጥ ያልነበሩ የተማሪ መገልገያ ካፌዎች ተከሰቱ ። የመማሪያ ክፍሎች ግድግዳ በሌላ ቀለም አሸበረቀ ። አጥሩ እየፈረሰ እንደገና ታጠረ... ትምህርት ቤቱ ሰፋ ። የትምህርት ቤቱ ብዙ ነገሮች ተለዋወጡ...እኔም ከትምህርት ቤቱ ይሄንን መጥፎ ትዝታ ብቻ ይዤ ተሰናበትኩ ።
.
ከተወሰኑ አመታት በኃላ ትምህርት ቤቱን አልፎ በሚገኝ በሚገኝ አንድ ህንጻ ውስጥ ስራ ተቀጠርኩ ። ህንጻው ትልቅ ሲሆን ሰፊ ቦታ የያዘና ዙሪያውን በሽቦ የታጠረ የመንግስት መስሪያ ቤት ነው ። ስራ መጀመሬን ተከትሎ በህይወቴና በአኗኗሬ ላይ ብዙ ለውጦች ተከስተዋል ። ትምህርት ቤት የነበረኝን መጥፎ ትዝታ ግን መርሳት አልቻልኩም ። ነገሮች አልሳካልኝ ብለው የውድቀትና የሽንፈት ስሜት ሲሰማኝ እንኳን...አንዲት ሴት ስታንሾካሹክና ሌሎቹም ተከትለዋት ሲስቁ በአይመሮዬ ይመጣብኛል። የተሳቀብኝ ይመስለኛል ። ተጽእኖው ቀላል አልነበረም ። መስሪያ ቤቴ ውስጥ ብዙ ሴት ጸሀፊዎችና ተላላኪዎች ሲኖሩ ከአንዳቸውም ጋር አልነጋገርም ነበር ።
ስድስት ሰአት ሲሆን የመስሪያ ቤቱ አባላት ለምሳ ወደ ቤታቸው ሲጣደፉ ፣ እኔ አንድ ወንበር ወደ ውጭ እስብና ከመስሪያ ቤቱ ቅጽር ውስጥ የበቀለውን ለምለም ሳር እየታዘብኩ የስራ ሰአት እስኪጀምር በትካዜ አሳልፋለሁ ።
.
በዚህ ሁኔታ ...የበጋው ወር ገፍቶ ክረምቱ እየገባ ...እኔ የምታዘበው ሳርም እያደገ መጣ ። አንድ ቀን ምሳ ሰአት ላይ ወንበር አውጥቼ ያደገውን ሳር እየታዘብኩ ያስመጣሁትን ቦንቦሊኖ እየበላሁ ነው ፥ ድንገት " ይቅርታ ..." የሚል የሴት ድምፅ ትዝብቴን አቋረጠኝና ቀና አልኩ ። ሳያት የሆነ ስሜት ወረረኝ....ደምስሬ ሲወጣጠርና የልብ ምቴ ሲፈጥን ታወቀኝ......ያኔ ዘጠነኛ ክፍል ለጉዋደኞቿ ስታስቅብኝ የነበረቺዋ ሴት ናት ። ጺሜ በጣም ስላደገና ፊቴ ስለጠቆረ ያወቀቺኝ አልመሠለኝም ። ታኮ የለለው ጫማ የለበሰች ሲሆን ሰፊ የእርጉዝ ልብስ ለብሳለች ።
.
አንድ ጉዳይ ልታስፈፅም እንደመጣችና ሰራተኞች እስኪገቡ እየጠበቀች እንደሆነ ነገረቺኝ ።..የማላውቀው ስሜት ውስጤን እየናጠኝ ተቋቁሜ ጸጥ ብዬ አየሇት። በጣቷ ወደ ሆዷ እየጠቆመችና ፈገግ እያለች..." እርጉዝ ነኝ ...እባክህ ቦንቦሊኖው ሸቶኝ ነው..ቆርሰህ ስጠኝ" አለቺኝ ። ..አይኖቿን እያየሁ አስተዋልኳት ። ግራ በመጋባት አየችኝ ። በመገረም ለጥቂት ሰከንዶች ካስተዋልኳት በኃላ ....እንቢታዬን ገለጽኩላት ። ፊቷ ሲቀላና ቅይርይር ሲል ግራ የሚያጋባ ስሜት ሲፈጠርባት በዝምታ እያየሇት ነበር ። ከአይኔ እየሸሸች እስክትሰወር ድረስ አስተዋልኳት ።...ምንድን ነው ግን ያደረኩት?...
.
ጥቂት አመታቶች እንደ ቀልድ አለፉ...ክረምቱ ያሳረፈው የዝናብ አለንጋ ተረሳ ፥መስሪያ ቤቱ ግቢ ውስጥ የነበረው ሳር ደረቀ ። እኔም ተንጨባሮ የነበረው ጸጉሬንና ጺሜን ስቆረጥ ሌላ ሰው መሠልኩ ። ....ምሳ ሰአት ላይ ወንበሬን ስቤ ከውጭ የተቀመጥኩ ቢሆንም በትዝታ ወደ ሁዋላ ተወርውሬአለሁ......ወደ ዘጠነኛ ክፍል ። ብቻውን ሳር ላይ ቁጭ የሚልና..ሴቶች የሚስቁበት ሁኖ አገኘሁት ራሴን ።ለምን እንደሆነ ባላውቅም ከጉዋደኞቿ ጋር ለምን ታሾፍብኝ እንደነበር ማወቅ ፈለኩ ። ምን ያደርግልሀል?...አልኩት ራሴን ። ለአሁን ሂዎትህ ይጠቅምሀል?..ለምን ማወቅ ፈለክ...ነው ወይስ ዘጠነኛ ክፍል ያሳቀብህ ጉዳይ አሁንም በስራ ባልደረባዎችህ እያሳቀብህ ነው ?...ጉጉቴ እየናረ ራሷን እንድጠይቃት ተማጸነኝ ።ብዙ አመነታሁ....ምንም አይጠቅመኝም አልኩ ።በኃላ ግን ላገኛት ወሰንኩ ።
.
እንደምንም ስልኳን አፈላልጌ አገኘሁና ስደውልላት በሁለተኛው ጥሪ አነሳችው ። ቀዝቀዝ ያለ ሰላምታ ሰጥቻት...ዘጠነኛ ክፍል አብረን እንደተማርንና...ምን አይነት ልጅ እንደሆንኩ ደግሞ ብቸኝነቴን ምልክት አድርጌ ስነግራት ሞቅ ያለ ሰላምታ ሰታኝ ስታበቃ ልታገኘኝ ተስማማች ።
.
ወደ ተቀጣጠርንበት ካፌ ስትመጣ ትልቅ የነበረው ሆዷ ወደ ውስጥ መግባቱን አስተዋልኩ ። እንደበፊቱ ሰፊ ልብስ አለበሰችም ። አንድ ህጻን ልጅ ከስሯ አስከትላለች ። አብዝሀኛዎቹ የከተማ እናቶች የሚለብሱትን አለባበስ የለበሰች ሲሆን ፤ አንገቷ ላይ ስካርፕ ጣል አድርጋለች።
.
እንዳየችኝ ደንግጣ የምትመለስ መስሎኝ ነበር ። እሷ ግን ጸጉሬንና ጺሜን ስለተስተካከልኩ ከዚ በፊት ያገኘችኝ አልመሰላትም ።
ለመጀመሪያ ጊዜ እንደተገናኘ ሰው ሞቅ ያለ ሰላምታ ሰጥታኝ ከፊት ለፊቴ ተቀመጠች ። ከጠበኩት በላይ ተግባቢ ሁና አገኘሇት ። ትምህርት ቤት ውስጥ ስለነበሩአት ጉዋደኞችና አሁን የት እንደ ደረሱ አወራን ። ስትስቅ ጉንጮቿ ይሰረጎዳሉ ። ለብዙ ደቂቃ በጨዋታ ይዛኝ እየሳኩ ጥያቄዬን የምጠይቅበትን አጋጣሚ በመጠበቅ ላይ ነበርኩ ........በመሀል እንደ ድንገት ጠየኳት ።
" ለምን ነበር የምታሾፉብኝ..?...ብዙ ጊዜ እያየሺኝ ታንሾካሽኪ ነበር"
.
በድንጋጤ ፊቷ ተቀያይሮ አስተዋለችኝ ።.አይን አይኗን እያየሁ ነው ። ጸጥታ በመሀከላችን ለጥቂት ደቂቃዎች ነገሰ ። የሚያስፈራ ጸጥታ
👍3
ትንሽ ቆይታ በመገረም እያየችኝ
" ጸጋዬን ታውቀዋለህኣ ? " አለችኝ ድክም ባለ ድምፅ
" አዎ " አልኳት በጥያቄዋ ግራ እየተጋባሁ ።
" ሁሌ በእረፍት ሰአት የሚቀመጠው ካንተ ጀርባ ነበር ። ስለምወደው እከታተለው ነበር ። ከጉዋደኞቼ ጋር ሁነን እየነገርኳቸው እንስቅ ነበር ። " ስትለኝ ድንግጥ አልኩ ። ጸጋዬን በአይምሮዬ ሳልኩት ...ድምጹ ስልል ያለ ልጅ...ሁሌ በእረፍት ሰአት ...ከኔ ጀርባ ነበር የሚቀመጠው ።
.
ስሜቴ ተቀያየረ....ድንጋጤ ዋጠኝ ።..ትኩስ ላብ ወደ ጀርባዬ እየወረደ ሲቀዘቅዝ ይታወቀኛል ። የምናገረው ጠፍቶብኝ አንገቴን ወደ ውስጥ ስቀብር ልጇን አስተዋልኩት ። አንገቱ አካባቢ ላይ ምልክት አለበት ።
" አንገቱን ምን ሆኖ ነው ..." ስል ጠየኳት ወሬ ለመቀየር
"...እ...ሽታ ነው .." አለችኝ ፈገግ እያለች ..."
" ሽታ ነው........እርጉዝ እያለው ቦንቦሊኖ አምሮኝ........."
.......ብዙ መቀመጥ አልቻልኩም። ..ቶሎ ተሰናብቻት ወደ ቢሮዬ ስመለስ ብዙ ነገሮችን እያወጣሁና እያወረድኩ ነው ። ህይወቴን ምን ያህል በተሳሳተ ስሜት እንደሞላሁት ሳስብ አዘንኩ ።.....ወይኔ ደግሞ..ልጇ!..ልጇ!... ቢሮዬ ስደርስ እንዲህ እያልኩ ይመስለኛል ። ከእያንዳንዷ ሽታ(ጠባሳ) ጀርባ የሆነ ስህተት አለ ። ከእያንዳንዱ ቦንቦሊኖ መሀል የሆነ ክፍተት አለ ...የሆነ ስህተት... ህይወቴ ከአንዲት ቦንቦሊኖ መሀል ያለው ክፍተት ሁኖ ተሰማኝ...
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ቀን። 🙏
" ጸጋዬን ታውቀዋለህኣ ? " አለችኝ ድክም ባለ ድምፅ
" አዎ " አልኳት በጥያቄዋ ግራ እየተጋባሁ ።
" ሁሌ በእረፍት ሰአት የሚቀመጠው ካንተ ጀርባ ነበር ። ስለምወደው እከታተለው ነበር ። ከጉዋደኞቼ ጋር ሁነን እየነገርኳቸው እንስቅ ነበር ። " ስትለኝ ድንግጥ አልኩ ። ጸጋዬን በአይምሮዬ ሳልኩት ...ድምጹ ስልል ያለ ልጅ...ሁሌ በእረፍት ሰአት ...ከኔ ጀርባ ነበር የሚቀመጠው ።
.
ስሜቴ ተቀያየረ....ድንጋጤ ዋጠኝ ።..ትኩስ ላብ ወደ ጀርባዬ እየወረደ ሲቀዘቅዝ ይታወቀኛል ። የምናገረው ጠፍቶብኝ አንገቴን ወደ ውስጥ ስቀብር ልጇን አስተዋልኩት ። አንገቱ አካባቢ ላይ ምልክት አለበት ።
" አንገቱን ምን ሆኖ ነው ..." ስል ጠየኳት ወሬ ለመቀየር
"...እ...ሽታ ነው .." አለችኝ ፈገግ እያለች ..."
" ሽታ ነው........እርጉዝ እያለው ቦንቦሊኖ አምሮኝ........."
.......ብዙ መቀመጥ አልቻልኩም። ..ቶሎ ተሰናብቻት ወደ ቢሮዬ ስመለስ ብዙ ነገሮችን እያወጣሁና እያወረድኩ ነው ። ህይወቴን ምን ያህል በተሳሳተ ስሜት እንደሞላሁት ሳስብ አዘንኩ ።.....ወይኔ ደግሞ..ልጇ!..ልጇ!... ቢሮዬ ስደርስ እንዲህ እያልኩ ይመስለኛል ። ከእያንዳንዷ ሽታ(ጠባሳ) ጀርባ የሆነ ስህተት አለ ። ከእያንዳንዱ ቦንቦሊኖ መሀል የሆነ ክፍተት አለ ...የሆነ ስህተት... ህይወቴ ከአንዲት ቦንቦሊኖ መሀል ያለው ክፍተት ሁኖ ተሰማኝ...
💫አለቀ💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ መልካም ቀን። 🙏
👍3
#ሮዛ_2
፡
፡
#ክፍል_አስር(🔞)
፡
፡
#ከለብ_አሪዞና
ክለብ አሪዞና ሮማን ሕንጻ ስር የሚገኝ ቀውጢ ጭፈራ ቤት ነበር። በሩ ጠባብ ነው።ዉስጡ ግን በጣም ሰፊ ነው። ልክ እንደትዝታ “ባብሽ”።በአንድ ወቅት የትዙን “ባብሽ” ጠባብ ነው እያሉ ብዙ
ወንዶች ተዋደቁለት። እውነት ለመናገር ያን ሰሞን ከኛ ፊት ይልቅ የሷ ባብሽ ይበልጥ ዝነኛ ነበር።ዘልቀው እስኪያዩ ድረስ ነው ታድያ።
ስለሺ ዘ ጎንደር የትዙን ባብሽ ካልቀመስኩ ብሎ እሪ አለ። ተው ቢባል ምን ቢባል! በቃ እሷ ጭን ውስጥ
ቅበሩኝና ታፍኜ ልሙት አለ። እግር ስሞ፣ ደጅ ጠንቶ፣እጥፍ ከፍሎ፣ በስንት መከራ፣ከምሽታት በአንዱ ሌሊት ከፍታ ሰጠችው። አጥብባ ሰጠችው። አስነከሰችው። ስለሺ ደስ አለው። ደስታው ግን ብዙ አልዘለቀም። ዕቃው ገብቶ ጠፋ። ቢባል ቢፈለግ ከየት ይገኝ? የስለሺ ዕቃ የትዙ ባብሽ ውስጥ ገብቶ በቃ ጠፋ ጠፋ። በስንት ፍለጋ ለፖሊስ አመልክቶ ነው ያገኘው እየተባለ ተቀለደ።
በሌላ ቀን ስለሺን አግኝተነው “ምን ሆንክ?” ስንለው “ዉስጥ ገብታችሁ እኔ ያየሁትን ብታዩ እንዳሁኑ አትቀልዱም ነበር” አለን። እሱ እንደሚለው ባብሽዋ ውስጥ ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች አሉ-
በእኩልነት እየጨፈሩ ይኖራሉ። ብቻ በትዙ “ባብሽ” ዙርያ አንድ ዓመት ተቀለደ። ትዙ ከፋት። ይሄ ክፉ ጎንደሬ! ምነው ባልሰጠሁት ኖሮ” ብላ ተጸጸተች።
በርግጥ የትዙ “ባብሽ” በተፈጥሮ ሰፊ ነው፤ እሷም ይህንንም ስለምታውቅ ነው ዮጋ የጀመረችው። ዮጋ የምታሰራት አንዲት ህንዳዊት መነኩሲት ነበረች፡፡ ሳር ቤት አካባቢ። ትዙ ደንበኞቿ እቃሽ ሰፉብን እያሉ ሲነጫነጩባት ብድግ ብላ ህንዷ ሴትዮ ጋር ሄደችና ሰላም እንኳ ሳትላት “ይቅርታ ባብሼ"
ማስጠበብ ፈልጌ ነበር” አለቻት። ህንዷ እንገቷን በአዎንታ ነቅንቃው ዮጋ ከላስ መዘገበቻት። በደንብ እንዲጠብላት ብላ Pussy Contraction and Relaxation የሚባል ኮርስ ሰጠቻት።
ኮርሱ ለትዝታ ከባድ አልነበረም። ትልቅ የሚነፉ የፕላስቲክ ኳስ በእግሮቿ መሐል አድርጋ ቁጭ ትልበትና ትንፉሽ ወደ ውስጥና ወደ ዉጭ በማስገባትና በማስወጣት የባብሽዋን ጡንቻ መቆጣጠር ተማረች። ዘዴው ለተወሰነ ጊዜ ሰራላት። በአጭሩ ቁላ ሲገባባት በባብሿ ጡንቻ ነክሳ መያዝ ቻለችበት።
ወንዱን ሁሉ አሰለፈችው። ዋጋ እየቆለለችባቸው እንኳን ብዙ ወንዶች ከሷ ባብሽ ሌላ ወይ ፍንክች አሉ። እሷ ባብሽ ውስጥ ገብተን ስንወጣ ሌላ መቃብር ቆፍራችሁ ብትቀብሩን አይቆጨንም አሉ።
ትዝታ ቢዝነስ ቆመላት። በተማረችው መሰረት ሴክስ ማድረግ ስትጀምር ቶሎ ብላ ትንፋሽዋን ስባ ትይዘዋለች። ባብሽዋ ይጠብላታል። ይህን ጊዜ ወንዶቹ እቃቸውን ታግለው ስለሚከቱባት በደስታ ማበድ ይጀምራሉ"እቃዬ ትልቀቱን መቋቋም አቅቷት ልትሞት እሪ ነው ያለችው እያሉ ለወንድ ጓደኞቻቸው ጉራቸውን ይቸረችራሉ። ብለው ብለው ደግሞ 6 ዓመት ያለመታከት በሸሌነት ያገለገለችውን ትዙን “ድንግል ናት” ብለው መማል ያምራቸዋል። ወንድ ሲባል ጉረኛና ወረኛ ነው።
ኾኖም ትዙ በዚህ ጥበብ ብዙም አልዘለቀችም። ሴክስ የጉልበት ሥራ ሆነባት። ከወንድ በተኛች ቁጥር
ትንፋሽዋን ወደ ውስጥ ስባ ማቆየት ያቅታትና ትለቀው ጀመር። በዚህን ጊዜ ባብሸዋ ወደ ተፈጥሯዊ ስፋቱ ይመለሳል። ወንዶቹ ይሄኔ መደናገጥ ጀመሩ። አንዳንዶቹ የነሱ ዕቃ የተኮማተረ እንጂ የሷ ባብሽ የሰፋ ስለማይመስላቸው አፍረው ቢዝነስ ጨምረውላት ዉልቅ ይላሉ።
እንዲህ እንዲህ እያለች ለተወሰነ ጊዜ ሸቀለች፤ ቢያንስ ለዮጋ ክላስ ያወጣችውን ብር አስመልሳለች።አይቆጫትም።
#አሪዞና
ክለብ አሪዞናም እንዲሁ ነው፤ እንደትዙ ባብሽ። በሩ ጠባብ፤ ዉስጡ ሰፊ። ደግነቱ ስፋቱ ብዙም አያስታውቅም። በመስታወት ተከፋፍሏል። ለተራ ጠጪ(open Bar)፣ ለቋሚ ደምበኛ (Customefs Bar)፣ ለልዩ ደምበኛ (VP Bar)ና ለዲፕሎማቶች (Ambassador Bar) ተብለው ክፍሎቹ
ተሸንሽነዋል። አንድ ምንም የማይከፈት ሌላ ክፍልም አለ። ሁለት እጅግ የናጠጡ ባለሐብቶች ብቻ ሲመጡ ነው የሚከፈተው። ከነሱ ሌላ ማንም ሰው እዚያ መግባት አይችልም። እነሱ በዓመት አንዴ
ወይም ሁለቴ ሊሆን ይችላል የሚመጡት። ወይም ምንም ላይመጡ ይችላሉ። ቢኾንሞ በቀን በቀን ይፀዳል በቀን በቀን ይወለወላል።
የሁሉም ክፍሎች መስታወቶች በልዩ ትዕዛዝ የተሰሩና Tinted የተደረጉ በመሆናቸው አንዱ ሌላውን ክፍል እንዲያይ አያስቻሉም። ለምሳሌ የዲፕሎማቶች ከፍል ውስጥ የሚዝናኑ ሰዎች በልዩ ደምበኛ ክፍል VIP Bar) ያሉትን ሰዎች ማየት ይችላሉ። ነገር ግን VIP Bar ያሉ ደምበኞች
Arabassador bar ማን እንዳለ ማየት አይቻሉም። ሁሉም የበታቹን ማየት ግን ይችላል የብላዩን ማየት ነው የማይችለው ደስ የሚለው ግን ሁሉም ሰው ካለበት ቁጭ ብሎ ዋናውን የዳንስ ፍሎር ቁልቁል መመልከት መቻሉ ነው።
በክለብ አሪዞና “መኝታ ቤት” የሚባል ነገር የለም። ነገር ግን ለሾርት ብቻ የሚያገለግል ምድር ቤት የሚባል ቦታ አለ። አንድ አጭር ሶፋ፣ አንድ የብረት ምሶሶ፣ አንድ ደረቅ ወንበርና አንድ ጠረጴዛ ብቻ ነው ያለው። ፍራሽም ኾነ አልጋ የለውም። ልዩ ደምበኞች ብቻ ናቸው ከዚህ ከፍል መግባት የሚፈቀድላቸው። በፈለጉት ፖዚሽን ቶሎ ጣጣቸውን ጨርሰው እንዲወጡ ነው ዲዛይን የተደረገው ዲፕሎማቶች 50 ዶላር ይከፍላሉ። ሀበሻ በየ 15 ደቂቃው የሚጨምር 500 መቶ ብር ይከፍላል። ተራ ጠጪዎች ግን ይህን አያውቁም። ስለዚህ ምድር ቤት ምን እንደሆነ አያውቁም። ምን እንደሚሰራ
አያውቁም። ቢያውቁም መግባት አይችሉም፡፡ ለነሱ አልጋ የለም!” እንላቸዋለን፤ ሲጠይቁን። ከፍሉ
በር ላይ የተጻፈውም እነሱን ለማደናገር ኾን ተብሎ ነው- Warehouse!” ይላል በትላልቅ ፊደል።
#እዮኤል_ማነው?
ትዝ ይለኛል ለዚህ ቤት እንድንሰራ መጀመርያ የመለመለን እዮኤል ነበር። አንድ ምሸት ሴቶች ብቻ ሆነን ሜሞ ፐብ በግል እየተዝናናን አስተናጋጁ ሂሳብ ተከፍሏል!” አለን። ገርሞን ስንዞር አንድ ቀይ ጎልማሳ ሰው ወደኛ ሲመለከት አየን ። መላጣ ነው። ስናየው ፈገግ አለ። ፈገግታው ደስ ይላል። ተዋወቀን ። እዮኤል እባላለሁ፤I don't know why ሴቶች ብቻቸውን ሲዝናኑ ይማርኩኛል አለ
ከዚህ በፊት አይተነው ባናውቅም ወደድነው። አብሮን ትንሽ ደነሰ። የማይከብድ፣ ጫወታ አዋቂ ይመስላል። ትንሽ ቆይቶ “Ladies night ነው መሰለኝ፤ እንዳልረብሻችሁ ተዝናኑ” ብሎን ቢዝነስ ካርዱን ሰጥቶን ወጣ። ከሜሞ ወጥተን ላዳ ውስጥ ስንገባ ቶሎ ብለን ቢዝነስ ካርዱን አየነው። ሰሙ
የስልክ አድራሻው ብቻ ነበር የተጻፈው ። ካርዱን ገልብጠን ስናየው Private Consulart to Happiness ይላል። ነገሩ በጣም አሳቀኝ። ቆይ ግን እዮኤል ማን ነው?
መጀመርያ እንደ ኡስማን ዘ ፒምፕ ዓይነት ሰው መስሎን ነበር። ሦስታችንም ማንነቱን ለማወቅ ጉጉት ስላደረብን በሌላ ቀን ደወልንለት። ያለንበት ለንደን ካፌ ድረስ መጣ። እኛ በረንዳው ላይ ቁጭ ብለን ነበር። ሰማያዊ ግራንድ ቪታራ መኪናውን ፓርክ ሲያደርግ ለየነው። ቀይ መላጣ ነው። መላጣው የችጋር ሳይሆን የምቾት ነው። ያብረቀርቃል። ምቾት ያንገላታውን መላጣ ሲያብረቀርቅ ብዙም ሰው ላይ እያንጸባርቅም መሰለኝ። የመኪናውን ቁልፍ በቄንጥ እያሽከረከረ ወደኛ ጠረጴዛ መጥቶ ወንበር
ስቦ ተቀማጠ። ለሁላችንም ኬክ በምርጫችን ጋበዘን። ስናወራ ለብዙ ዓመት አብሮን የኖረ ጓደኛችን እንጂ ሁለተኛ ቀናችን አይመስልም ነበር።
የፈለኳችሁ ለአንድ ቀላል የቢዝነስ ስራ ነው ብሎ ጀመረ።አንድ የልብ
፡
፡
#ክፍል_አስር(🔞)
፡
፡
#ከለብ_አሪዞና
ክለብ አሪዞና ሮማን ሕንጻ ስር የሚገኝ ቀውጢ ጭፈራ ቤት ነበር። በሩ ጠባብ ነው።ዉስጡ ግን በጣም ሰፊ ነው። ልክ እንደትዝታ “ባብሽ”።በአንድ ወቅት የትዙን “ባብሽ” ጠባብ ነው እያሉ ብዙ
ወንዶች ተዋደቁለት። እውነት ለመናገር ያን ሰሞን ከኛ ፊት ይልቅ የሷ ባብሽ ይበልጥ ዝነኛ ነበር።ዘልቀው እስኪያዩ ድረስ ነው ታድያ።
ስለሺ ዘ ጎንደር የትዙን ባብሽ ካልቀመስኩ ብሎ እሪ አለ። ተው ቢባል ምን ቢባል! በቃ እሷ ጭን ውስጥ
ቅበሩኝና ታፍኜ ልሙት አለ። እግር ስሞ፣ ደጅ ጠንቶ፣እጥፍ ከፍሎ፣ በስንት መከራ፣ከምሽታት በአንዱ ሌሊት ከፍታ ሰጠችው። አጥብባ ሰጠችው። አስነከሰችው። ስለሺ ደስ አለው። ደስታው ግን ብዙ አልዘለቀም። ዕቃው ገብቶ ጠፋ። ቢባል ቢፈለግ ከየት ይገኝ? የስለሺ ዕቃ የትዙ ባብሽ ውስጥ ገብቶ በቃ ጠፋ ጠፋ። በስንት ፍለጋ ለፖሊስ አመልክቶ ነው ያገኘው እየተባለ ተቀለደ።
በሌላ ቀን ስለሺን አግኝተነው “ምን ሆንክ?” ስንለው “ዉስጥ ገብታችሁ እኔ ያየሁትን ብታዩ እንዳሁኑ አትቀልዱም ነበር” አለን። እሱ እንደሚለው ባብሽዋ ውስጥ ሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች አሉ-
በእኩልነት እየጨፈሩ ይኖራሉ። ብቻ በትዙ “ባብሽ” ዙርያ አንድ ዓመት ተቀለደ። ትዙ ከፋት። ይሄ ክፉ ጎንደሬ! ምነው ባልሰጠሁት ኖሮ” ብላ ተጸጸተች።
በርግጥ የትዙ “ባብሽ” በተፈጥሮ ሰፊ ነው፤ እሷም ይህንንም ስለምታውቅ ነው ዮጋ የጀመረችው። ዮጋ የምታሰራት አንዲት ህንዳዊት መነኩሲት ነበረች፡፡ ሳር ቤት አካባቢ። ትዙ ደንበኞቿ እቃሽ ሰፉብን እያሉ ሲነጫነጩባት ብድግ ብላ ህንዷ ሴትዮ ጋር ሄደችና ሰላም እንኳ ሳትላት “ይቅርታ ባብሼ"
ማስጠበብ ፈልጌ ነበር” አለቻት። ህንዷ እንገቷን በአዎንታ ነቅንቃው ዮጋ ከላስ መዘገበቻት። በደንብ እንዲጠብላት ብላ Pussy Contraction and Relaxation የሚባል ኮርስ ሰጠቻት።
ኮርሱ ለትዝታ ከባድ አልነበረም። ትልቅ የሚነፉ የፕላስቲክ ኳስ በእግሮቿ መሐል አድርጋ ቁጭ ትልበትና ትንፉሽ ወደ ውስጥና ወደ ዉጭ በማስገባትና በማስወጣት የባብሽዋን ጡንቻ መቆጣጠር ተማረች። ዘዴው ለተወሰነ ጊዜ ሰራላት። በአጭሩ ቁላ ሲገባባት በባብሿ ጡንቻ ነክሳ መያዝ ቻለችበት።
ወንዱን ሁሉ አሰለፈችው። ዋጋ እየቆለለችባቸው እንኳን ብዙ ወንዶች ከሷ ባብሽ ሌላ ወይ ፍንክች አሉ። እሷ ባብሽ ውስጥ ገብተን ስንወጣ ሌላ መቃብር ቆፍራችሁ ብትቀብሩን አይቆጨንም አሉ።
ትዝታ ቢዝነስ ቆመላት። በተማረችው መሰረት ሴክስ ማድረግ ስትጀምር ቶሎ ብላ ትንፋሽዋን ስባ ትይዘዋለች። ባብሽዋ ይጠብላታል። ይህን ጊዜ ወንዶቹ እቃቸውን ታግለው ስለሚከቱባት በደስታ ማበድ ይጀምራሉ"እቃዬ ትልቀቱን መቋቋም አቅቷት ልትሞት እሪ ነው ያለችው እያሉ ለወንድ ጓደኞቻቸው ጉራቸውን ይቸረችራሉ። ብለው ብለው ደግሞ 6 ዓመት ያለመታከት በሸሌነት ያገለገለችውን ትዙን “ድንግል ናት” ብለው መማል ያምራቸዋል። ወንድ ሲባል ጉረኛና ወረኛ ነው።
ኾኖም ትዙ በዚህ ጥበብ ብዙም አልዘለቀችም። ሴክስ የጉልበት ሥራ ሆነባት። ከወንድ በተኛች ቁጥር
ትንፋሽዋን ወደ ውስጥ ስባ ማቆየት ያቅታትና ትለቀው ጀመር። በዚህን ጊዜ ባብሸዋ ወደ ተፈጥሯዊ ስፋቱ ይመለሳል። ወንዶቹ ይሄኔ መደናገጥ ጀመሩ። አንዳንዶቹ የነሱ ዕቃ የተኮማተረ እንጂ የሷ ባብሽ የሰፋ ስለማይመስላቸው አፍረው ቢዝነስ ጨምረውላት ዉልቅ ይላሉ።
እንዲህ እንዲህ እያለች ለተወሰነ ጊዜ ሸቀለች፤ ቢያንስ ለዮጋ ክላስ ያወጣችውን ብር አስመልሳለች።አይቆጫትም።
#አሪዞና
ክለብ አሪዞናም እንዲሁ ነው፤ እንደትዙ ባብሽ። በሩ ጠባብ፤ ዉስጡ ሰፊ። ደግነቱ ስፋቱ ብዙም አያስታውቅም። በመስታወት ተከፋፍሏል። ለተራ ጠጪ(open Bar)፣ ለቋሚ ደምበኛ (Customefs Bar)፣ ለልዩ ደምበኛ (VP Bar)ና ለዲፕሎማቶች (Ambassador Bar) ተብለው ክፍሎቹ
ተሸንሽነዋል። አንድ ምንም የማይከፈት ሌላ ክፍልም አለ። ሁለት እጅግ የናጠጡ ባለሐብቶች ብቻ ሲመጡ ነው የሚከፈተው። ከነሱ ሌላ ማንም ሰው እዚያ መግባት አይችልም። እነሱ በዓመት አንዴ
ወይም ሁለቴ ሊሆን ይችላል የሚመጡት። ወይም ምንም ላይመጡ ይችላሉ። ቢኾንሞ በቀን በቀን ይፀዳል በቀን በቀን ይወለወላል።
የሁሉም ክፍሎች መስታወቶች በልዩ ትዕዛዝ የተሰሩና Tinted የተደረጉ በመሆናቸው አንዱ ሌላውን ክፍል እንዲያይ አያስቻሉም። ለምሳሌ የዲፕሎማቶች ከፍል ውስጥ የሚዝናኑ ሰዎች በልዩ ደምበኛ ክፍል VIP Bar) ያሉትን ሰዎች ማየት ይችላሉ። ነገር ግን VIP Bar ያሉ ደምበኞች
Arabassador bar ማን እንዳለ ማየት አይቻሉም። ሁሉም የበታቹን ማየት ግን ይችላል የብላዩን ማየት ነው የማይችለው ደስ የሚለው ግን ሁሉም ሰው ካለበት ቁጭ ብሎ ዋናውን የዳንስ ፍሎር ቁልቁል መመልከት መቻሉ ነው።
በክለብ አሪዞና “መኝታ ቤት” የሚባል ነገር የለም። ነገር ግን ለሾርት ብቻ የሚያገለግል ምድር ቤት የሚባል ቦታ አለ። አንድ አጭር ሶፋ፣ አንድ የብረት ምሶሶ፣ አንድ ደረቅ ወንበርና አንድ ጠረጴዛ ብቻ ነው ያለው። ፍራሽም ኾነ አልጋ የለውም። ልዩ ደምበኞች ብቻ ናቸው ከዚህ ከፍል መግባት የሚፈቀድላቸው። በፈለጉት ፖዚሽን ቶሎ ጣጣቸውን ጨርሰው እንዲወጡ ነው ዲዛይን የተደረገው ዲፕሎማቶች 50 ዶላር ይከፍላሉ። ሀበሻ በየ 15 ደቂቃው የሚጨምር 500 መቶ ብር ይከፍላል። ተራ ጠጪዎች ግን ይህን አያውቁም። ስለዚህ ምድር ቤት ምን እንደሆነ አያውቁም። ምን እንደሚሰራ
አያውቁም። ቢያውቁም መግባት አይችሉም፡፡ ለነሱ አልጋ የለም!” እንላቸዋለን፤ ሲጠይቁን። ከፍሉ
በር ላይ የተጻፈውም እነሱን ለማደናገር ኾን ተብሎ ነው- Warehouse!” ይላል በትላልቅ ፊደል።
#እዮኤል_ማነው?
ትዝ ይለኛል ለዚህ ቤት እንድንሰራ መጀመርያ የመለመለን እዮኤል ነበር። አንድ ምሸት ሴቶች ብቻ ሆነን ሜሞ ፐብ በግል እየተዝናናን አስተናጋጁ ሂሳብ ተከፍሏል!” አለን። ገርሞን ስንዞር አንድ ቀይ ጎልማሳ ሰው ወደኛ ሲመለከት አየን ። መላጣ ነው። ስናየው ፈገግ አለ። ፈገግታው ደስ ይላል። ተዋወቀን ። እዮኤል እባላለሁ፤I don't know why ሴቶች ብቻቸውን ሲዝናኑ ይማርኩኛል አለ
ከዚህ በፊት አይተነው ባናውቅም ወደድነው። አብሮን ትንሽ ደነሰ። የማይከብድ፣ ጫወታ አዋቂ ይመስላል። ትንሽ ቆይቶ “Ladies night ነው መሰለኝ፤ እንዳልረብሻችሁ ተዝናኑ” ብሎን ቢዝነስ ካርዱን ሰጥቶን ወጣ። ከሜሞ ወጥተን ላዳ ውስጥ ስንገባ ቶሎ ብለን ቢዝነስ ካርዱን አየነው። ሰሙ
የስልክ አድራሻው ብቻ ነበር የተጻፈው ። ካርዱን ገልብጠን ስናየው Private Consulart to Happiness ይላል። ነገሩ በጣም አሳቀኝ። ቆይ ግን እዮኤል ማን ነው?
መጀመርያ እንደ ኡስማን ዘ ፒምፕ ዓይነት ሰው መስሎን ነበር። ሦስታችንም ማንነቱን ለማወቅ ጉጉት ስላደረብን በሌላ ቀን ደወልንለት። ያለንበት ለንደን ካፌ ድረስ መጣ። እኛ በረንዳው ላይ ቁጭ ብለን ነበር። ሰማያዊ ግራንድ ቪታራ መኪናውን ፓርክ ሲያደርግ ለየነው። ቀይ መላጣ ነው። መላጣው የችጋር ሳይሆን የምቾት ነው። ያብረቀርቃል። ምቾት ያንገላታውን መላጣ ሲያብረቀርቅ ብዙም ሰው ላይ እያንጸባርቅም መሰለኝ። የመኪናውን ቁልፍ በቄንጥ እያሽከረከረ ወደኛ ጠረጴዛ መጥቶ ወንበር
ስቦ ተቀማጠ። ለሁላችንም ኬክ በምርጫችን ጋበዘን። ስናወራ ለብዙ ዓመት አብሮን የኖረ ጓደኛችን እንጂ ሁለተኛ ቀናችን አይመስልም ነበር።
የፈለኳችሁ ለአንድ ቀላል የቢዝነስ ስራ ነው ብሎ ጀመረ።አንድ የልብ
👍7❤2
ጓደኛዬ ቆንጆ ክለብ ከፍቷል።ደመቀ ይባላል። እና እሱን እንድታግዙት አስቤ ነው…ምን ይመስላችኋል?” አለን። ሸሌነት ሊያስቀጥረን እየሞከረ ስለመሰለን ሦስታችንም ፊታችንን ከሰከስነው። እሱም ያስብነው ገባው መሰለኝ ሳቀ። “ኖኖ ፈፅሞ እንደዛ አይነት ነገር አይደለም ያሰብኩት። እ…ምን መሰላችሁ…እንደናንተ ዓይነት ቆንጆ ሴቶች አዲስ ክለብ ውስጥ ሲታዩ ደምበኞችን መሳባቸው አይቀርም። እኛ ደግሞ ታርጌት ያደረግናቸው ከስተመሮች ከፍ ያሉትን ብቻ ነው if you know what mean እና በማንኛውም ጊዜ መዝናናት
ስትፈልጉ ወደ ክለብ አሪዞና ትመጣላችሁ…የምትበሉት፣የምትጠጡት በሙሉ ይሸፈንላችኋል። እ…እያልኳችሁ ያለሁት እኛ ክለብ ተዝናኑ ነው ሌላ አይደለም፣ Alas! End of the story።”
ነገሩ ገርሞን እሺ ጣጣ የለውም” ብለነው ለጊዜው ተለያየን፡፡ እኔ ስምረት ቤቲና ትምኒት ነበርን ያን ቀን። ስምረት… "ለማየት ያብቃችሁ የሆነ ነገር ሊሸቅልብን አስቦ ነው.…እንዲያውም ኮፊ አናን ነው የላከው” አለችን። አልሰማናትም።
በቀጣዩ ዕሁድ እስኪ ይታይለት” ብለን ክለብ አሪዞና” ሄድን። በቤቱ ስፋትና ጥራት በጣም ተገረምን። ዱባይ እንጂ አዲስ አበባ ዉስጥ ያለን አይመስልም። ይሄን ቤት እስከዛሬ ባለማወቃችን
አፈርን። ለማንኛውም በላን፣ ጠጣን፣ ጨፈርን…እሱ ግን የለም። ሂሳብ ተባልን…ሂሳቡን ስናየው ሦስታችንም አፋችንን ከፍተንቀረን። ጉድ ፈላ! ሳምሪ ቢዝነስ ካርዱን ከቦርሳዋ አውጥታ ደወለችለት…፤
ከፎቅ እየከነፈ ወረደ። ሂሳቡን ያቀረበልን አስተናጋጅ ከእዮኤል ጋር ሲያየን ጭራውን እየቆላ መጥቶ ተከፍሏል! ይቅርታ፤ ልዩ እንግዳ እንደሆናቹ አላወቅኩም” ብሎን ቱር ብሎ ሄደ።
ያን ሌሊት ወደቤታችን ከመመለሳችን በፊት እዮኤል ፎቁ ላይ ወደሚገኘው ቢሮው በላፍት ይዞን ወጣ። የአይሪሾች ቸኮሌት ለሁላችንም አንድ አንድ ከሰጠን በኋላ ከደሜ ጋር አስተዋወቀን። "የምወደው ወንድሜ ነው ተንከባከቡልኝ ብሎ አደራ አለን እሺ ብለነው ልንወጣ ስንል እንዲያውም ልሽኛችሁ” ብሎን ተከትሎን ወጣ። ከዚያ እሱ ግራንድ ቪታራ ዉስጥ ተስገብግበን ከገባን በኋላ
ያልጠበቅነው ነገር ነገረን።
ሌዲስ! Now lets talk business! እዚህ ቤት በማንኛውም ቀንና ሰዓት መጥታችሁ በነጻ መዝናናታችሁ እንዳለ ኾኖ አልፎ አልፎ ግን ቅር ካላላችሁ ለአንዳንድ ወጪ የሚሆን ሳንቲም ልንሰጣችሁ እንፈልጋለን።እና ምን ይመስላችኋል..?
“ኸረ እንክብካቤ በዛብን! ሙድ የለውም” አለች ሳምሪ። እሷ ሁልጊዜም አፏ እንዳመጣላት ነው የምታወራው መሀላችን ስለነበረች ከስር ቆነጠጥናት እዩኤል አነዳዱ ሲያስፈራ!
"ኖ ኖ! መብዛት እንኳ አይበዛባችሁም፤ ለናንተ እንዲያውም ሲያንስ ነው። ባይኾን በምላሹ አንዳንድ ነገር ታግዙናላችሁ..." አለን ኮስተር ብሎ።
Like ምን አይነት ነገር?” አልነው።
እ..ዊል ብዙ አይደለም…ላይክ…ጥሩ ገቢ ያላቸውን ወንዶች ጥሩ ክለብ ተከፍቷል እያላችሁ እዚህ ይዛችኋቸው ብትመጡ፣ ማለቴ...ለናንተ እምቢ አይሏችሁም። እንደናንተ አይነት ቆንጆ ልጆችን
እምቢ የሚል ወንድ ይኖራል ብላችሁ ነው? እና ባመጣችሁት ሰው ልክ እንከፍላለን. ፤ ምን ይመስላችኋል?”
“Deal!”
"Deal!"
ከዚያን ቀን ጀምሮ ገንዘብ ያሰከረው ወንድ ስናገኝ…አንጠልጥለን “ክለብ አሪዞና” እያመጣን ማሳረድ ሆነ
ስራችን፡፡ አንድ ወንድ “አለሁ አለሁ” ካበዛ “ቄራ ይወሰድ” እንላለን በኮድ። ፋራ ከሆነ ቄራ አካባቢ ናይት ክለብ አለ እንዴ? ይላል። እንስቅበታለም። ክለብ አሪዞናን ማለታችን ነው እንለዋለን። በክለብ አሪዞና ከወንድ ጋር ስንጠቃጠቅ ብናድር የማናገኘውን አዱኛ በልተን፣ ጠጥተን፣ ተዝናንተን ማግኘት
ጀመርን። እዮኤል በሂደት አንዳንድ መከተል ያለብንን መመሪያዎች ነገረን።
እውነት ለመናገር ስራችን መተወን ነው። ልክ ፊልም ቀረጻ ላይ እንዳለ አክተር መተወን። ወይም በሌላ ቋንቋ በቀን አንድ በብር የሰከረ ወንድ እያመጡ ለካራ አንገቱን እንዲሰጥ ማድረግ።
መጀመርያ የምናመጣውን ወንድ እየካብን ገና አሪዞናን ሳይረግጥ አቅሉን እናስተዋለን። እዮኤል በነገረን መሠረት ያመጣነውን ወንድ ልዩ ደምበኞ ወደሚለው ክፍል እናስገባዋለን። ምንም ጥያቄ የለውም እዚያ ክፍል ሲገባ የሚደረግለት እከብካቤ ብቻ ልቡን ያጠፋዋል። የምታስተናግደው አንዲት ረዥም የኤምሬት ሆስተሶችን የሚመስል ዩኒፎርም የለበሰች ሴት ናት። የምትለብሰው ሚኒ ስከርት ብቻ ነው።
ጀርባዋ ሙሉ በሙሉ ክፍት ነው። ካፈነደደች ቂጧ ሦስት አራተኛ ይታያል። ጎንበስ ካለች የጡቷ ሁለት ሦስተኛ ይታያል። ምንም ጥያቄ የለውም እንግዳው ትኩሳቱ ይጨምራል። በሚያየው ነገር ሁሉ ዐይኑ ይጥበረበራል…ያኔ ሆስተሷን እንጠቅሳታለን።
ስውር ብላ ተመልሳ ትመጣና ብላክ ታወርዳለች። ዉስኪው የሚመጣው እንደ ፈረንጅ ሕጻን በትሮሊ እየተገፉ ነው። እንግዳው ገና የሚፈልገውን የመጠጥ ዓይነት ማሰብ ሳይጀምር “ሆስተሷ” ዉስኪውን በሚደንቅ ፍጥነት ከፍታ በቄንጥ ለቅምሻ መቅዳት ትጀምራለች። ጡቷን እያስከለመችው። ይሄን ጊዜ
የእንግዳው ለሀጭ መዝረክረክ ይጀምራል።
ክለብ አሪዞና ዉስጥ አንድም የረገበ ጡት የለም፤ አንድም። እዚያ በቋሚነት የምትሰራ አንዲት የሳምሪ ጓደኛ እንደነገረችን ሁሏም ሴት ስትቀጠር ጡቶቿን ያለምንም ማስያዣ ገልጣ እንድትንቀሳቀስ ይደረጋል። ጡቷ ያልተወደረ ሴት አትቀጠርም። ወዝወዝ የሚል ዳሌ የሌላት ሴትም አትቀጠርም።
እዩኤል ቂጥና ጡት የሌላትን ሴት ከሚቀጥር ቆንጆ ወንድ ቢቀጥር ይመርጣል።
ሆስተሷ አስተናጋጇ ዞር ስትል በተሰጠን ስክሪፕት መሠረት መተወን እንጀምራለን። ለምሳሌ ሰውየው ለሚናገረው ነገር በሙሉ እንስቅለታለን። ለካ መድረክ አላገኘሁም እንጂ ኮሜዲያን ነበርኩ” እስኪል ድረስ። ከስውነት ከፍሉ አንድ የሚያምር ነገር ፈልገን አቅሉን እስኪስት አድናቆት እናዘንብበታለን። እኔ በበኩሌ የሰው ልጅ እጅግ ደካማ ፍጡር መኾኑን ያየሁት በዚህ አጋጣሚ ነው። አድናቆት
ለካ ያሳውራል። አቅልን ያስታል። መላጣ የሆነውን ሰውዬ “አይገርምም? ጸጉርህ ሉጫ እንደነበር ያስታውቃል! ” ስንለው ፊቱ ይፈካል። “.እንዴት አወቃችሁ? ድሮ ሰፈር “ፍሪዛሙ ልጅ” እያሉ ነበር
የሚጠሩኝ፣ ማርያምን!” ይላል፤ በስሜት ተውጦ። ወይም ደግሞ አንድን የሚታረድ ወንድ "seriously መላጣህ ግን ከሰውነትህ ጋር ይሄዳል፣ አንዳንድ ወንድ ግን መላጣ ያምርበታል! ካልነው አያናችን እያየ ግንባሩ ጥርስ ይሆናል።መላጣው ሁሉ ያስቃል።
አድናቆት የሁሉም የሰው ልጅ ደካማ ጎን እንደሆነ ተረዳሁ። “አድናቆት የሰው ልጅን በቁሙ የሚያስከር ኦፒየም ነው ብዬ ጥቅስ የሚመስል ነገር ፃፍኩ።
ከኛ የአድናቆት ኦፒየም ሌላ…ሆስተሷ እየመጣች በላይ በላዩ ትቀዳለታለች። በዚህን ጊዜ ሞቅታ ይመጣል። እዮኤል ይቺን ሰዓት ጠብቆ በኛ ክፍል በኩል እኛን እንዳላየ ኾኖ ሲያልፍ ለእንግዳው
እየጠቆምነው “የዚህ ፎቅ ባለቤት እሱ ነው!” እንለዋለን። የኾነ የአውሮፓ አገር እንጠራና እዛም አገር የሐበሻ ሬስቶራንት አለው፤ አታውቀውም” እንለዋለን። ምንም ሀብታም ቢሆን በሰማው ነገር በርገግ ማለት ይጀምራል።ትንሽ ቆይቶ ደግሞ እዮኤል ይመጣና እንደምን አመሻትሁ! ምን አነሰ ታዲያ? ምን ይጨመር ብሎ ተራ በተራ ይጨብጠናል አቤት ሲችልበት!!
ሰውየው ብርክ ይይዘዋል።
እኛ ደግሞ ቀልጠፍ ብለን " አቶ እዮኤል! እሱ ታዋቂ የመርካቶ ነጋዴ ነው…የምንወደው ወንድማችን ነው…ምናምን” እንላለን። ወይም ደግሞ ስለሰውየው የምናውቀውን ተናግረን በገገማ እናስተዋውቃቸዋለን እዩኤል
ስትፈልጉ ወደ ክለብ አሪዞና ትመጣላችሁ…የምትበሉት፣የምትጠጡት በሙሉ ይሸፈንላችኋል። እ…እያልኳችሁ ያለሁት እኛ ክለብ ተዝናኑ ነው ሌላ አይደለም፣ Alas! End of the story።”
ነገሩ ገርሞን እሺ ጣጣ የለውም” ብለነው ለጊዜው ተለያየን፡፡ እኔ ስምረት ቤቲና ትምኒት ነበርን ያን ቀን። ስምረት… "ለማየት ያብቃችሁ የሆነ ነገር ሊሸቅልብን አስቦ ነው.…እንዲያውም ኮፊ አናን ነው የላከው” አለችን። አልሰማናትም።
በቀጣዩ ዕሁድ እስኪ ይታይለት” ብለን ክለብ አሪዞና” ሄድን። በቤቱ ስፋትና ጥራት በጣም ተገረምን። ዱባይ እንጂ አዲስ አበባ ዉስጥ ያለን አይመስልም። ይሄን ቤት እስከዛሬ ባለማወቃችን
አፈርን። ለማንኛውም በላን፣ ጠጣን፣ ጨፈርን…እሱ ግን የለም። ሂሳብ ተባልን…ሂሳቡን ስናየው ሦስታችንም አፋችንን ከፍተንቀረን። ጉድ ፈላ! ሳምሪ ቢዝነስ ካርዱን ከቦርሳዋ አውጥታ ደወለችለት…፤
ከፎቅ እየከነፈ ወረደ። ሂሳቡን ያቀረበልን አስተናጋጅ ከእዮኤል ጋር ሲያየን ጭራውን እየቆላ መጥቶ ተከፍሏል! ይቅርታ፤ ልዩ እንግዳ እንደሆናቹ አላወቅኩም” ብሎን ቱር ብሎ ሄደ።
ያን ሌሊት ወደቤታችን ከመመለሳችን በፊት እዮኤል ፎቁ ላይ ወደሚገኘው ቢሮው በላፍት ይዞን ወጣ። የአይሪሾች ቸኮሌት ለሁላችንም አንድ አንድ ከሰጠን በኋላ ከደሜ ጋር አስተዋወቀን። "የምወደው ወንድሜ ነው ተንከባከቡልኝ ብሎ አደራ አለን እሺ ብለነው ልንወጣ ስንል እንዲያውም ልሽኛችሁ” ብሎን ተከትሎን ወጣ። ከዚያ እሱ ግራንድ ቪታራ ዉስጥ ተስገብግበን ከገባን በኋላ
ያልጠበቅነው ነገር ነገረን።
ሌዲስ! Now lets talk business! እዚህ ቤት በማንኛውም ቀንና ሰዓት መጥታችሁ በነጻ መዝናናታችሁ እንዳለ ኾኖ አልፎ አልፎ ግን ቅር ካላላችሁ ለአንዳንድ ወጪ የሚሆን ሳንቲም ልንሰጣችሁ እንፈልጋለን።እና ምን ይመስላችኋል..?
“ኸረ እንክብካቤ በዛብን! ሙድ የለውም” አለች ሳምሪ። እሷ ሁልጊዜም አፏ እንዳመጣላት ነው የምታወራው መሀላችን ስለነበረች ከስር ቆነጠጥናት እዩኤል አነዳዱ ሲያስፈራ!
"ኖ ኖ! መብዛት እንኳ አይበዛባችሁም፤ ለናንተ እንዲያውም ሲያንስ ነው። ባይኾን በምላሹ አንዳንድ ነገር ታግዙናላችሁ..." አለን ኮስተር ብሎ።
Like ምን አይነት ነገር?” አልነው።
እ..ዊል ብዙ አይደለም…ላይክ…ጥሩ ገቢ ያላቸውን ወንዶች ጥሩ ክለብ ተከፍቷል እያላችሁ እዚህ ይዛችኋቸው ብትመጡ፣ ማለቴ...ለናንተ እምቢ አይሏችሁም። እንደናንተ አይነት ቆንጆ ልጆችን
እምቢ የሚል ወንድ ይኖራል ብላችሁ ነው? እና ባመጣችሁት ሰው ልክ እንከፍላለን. ፤ ምን ይመስላችኋል?”
“Deal!”
"Deal!"
ከዚያን ቀን ጀምሮ ገንዘብ ያሰከረው ወንድ ስናገኝ…አንጠልጥለን “ክለብ አሪዞና” እያመጣን ማሳረድ ሆነ
ስራችን፡፡ አንድ ወንድ “አለሁ አለሁ” ካበዛ “ቄራ ይወሰድ” እንላለን በኮድ። ፋራ ከሆነ ቄራ አካባቢ ናይት ክለብ አለ እንዴ? ይላል። እንስቅበታለም። ክለብ አሪዞናን ማለታችን ነው እንለዋለን። በክለብ አሪዞና ከወንድ ጋር ስንጠቃጠቅ ብናድር የማናገኘውን አዱኛ በልተን፣ ጠጥተን፣ ተዝናንተን ማግኘት
ጀመርን። እዮኤል በሂደት አንዳንድ መከተል ያለብንን መመሪያዎች ነገረን።
እውነት ለመናገር ስራችን መተወን ነው። ልክ ፊልም ቀረጻ ላይ እንዳለ አክተር መተወን። ወይም በሌላ ቋንቋ በቀን አንድ በብር የሰከረ ወንድ እያመጡ ለካራ አንገቱን እንዲሰጥ ማድረግ።
መጀመርያ የምናመጣውን ወንድ እየካብን ገና አሪዞናን ሳይረግጥ አቅሉን እናስተዋለን። እዮኤል በነገረን መሠረት ያመጣነውን ወንድ ልዩ ደምበኞ ወደሚለው ክፍል እናስገባዋለን። ምንም ጥያቄ የለውም እዚያ ክፍል ሲገባ የሚደረግለት እከብካቤ ብቻ ልቡን ያጠፋዋል። የምታስተናግደው አንዲት ረዥም የኤምሬት ሆስተሶችን የሚመስል ዩኒፎርም የለበሰች ሴት ናት። የምትለብሰው ሚኒ ስከርት ብቻ ነው።
ጀርባዋ ሙሉ በሙሉ ክፍት ነው። ካፈነደደች ቂጧ ሦስት አራተኛ ይታያል። ጎንበስ ካለች የጡቷ ሁለት ሦስተኛ ይታያል። ምንም ጥያቄ የለውም እንግዳው ትኩሳቱ ይጨምራል። በሚያየው ነገር ሁሉ ዐይኑ ይጥበረበራል…ያኔ ሆስተሷን እንጠቅሳታለን።
ስውር ብላ ተመልሳ ትመጣና ብላክ ታወርዳለች። ዉስኪው የሚመጣው እንደ ፈረንጅ ሕጻን በትሮሊ እየተገፉ ነው። እንግዳው ገና የሚፈልገውን የመጠጥ ዓይነት ማሰብ ሳይጀምር “ሆስተሷ” ዉስኪውን በሚደንቅ ፍጥነት ከፍታ በቄንጥ ለቅምሻ መቅዳት ትጀምራለች። ጡቷን እያስከለመችው። ይሄን ጊዜ
የእንግዳው ለሀጭ መዝረክረክ ይጀምራል።
ክለብ አሪዞና ዉስጥ አንድም የረገበ ጡት የለም፤ አንድም። እዚያ በቋሚነት የምትሰራ አንዲት የሳምሪ ጓደኛ እንደነገረችን ሁሏም ሴት ስትቀጠር ጡቶቿን ያለምንም ማስያዣ ገልጣ እንድትንቀሳቀስ ይደረጋል። ጡቷ ያልተወደረ ሴት አትቀጠርም። ወዝወዝ የሚል ዳሌ የሌላት ሴትም አትቀጠርም።
እዩኤል ቂጥና ጡት የሌላትን ሴት ከሚቀጥር ቆንጆ ወንድ ቢቀጥር ይመርጣል።
ሆስተሷ አስተናጋጇ ዞር ስትል በተሰጠን ስክሪፕት መሠረት መተወን እንጀምራለን። ለምሳሌ ሰውየው ለሚናገረው ነገር በሙሉ እንስቅለታለን። ለካ መድረክ አላገኘሁም እንጂ ኮሜዲያን ነበርኩ” እስኪል ድረስ። ከስውነት ከፍሉ አንድ የሚያምር ነገር ፈልገን አቅሉን እስኪስት አድናቆት እናዘንብበታለን። እኔ በበኩሌ የሰው ልጅ እጅግ ደካማ ፍጡር መኾኑን ያየሁት በዚህ አጋጣሚ ነው። አድናቆት
ለካ ያሳውራል። አቅልን ያስታል። መላጣ የሆነውን ሰውዬ “አይገርምም? ጸጉርህ ሉጫ እንደነበር ያስታውቃል! ” ስንለው ፊቱ ይፈካል። “.እንዴት አወቃችሁ? ድሮ ሰፈር “ፍሪዛሙ ልጅ” እያሉ ነበር
የሚጠሩኝ፣ ማርያምን!” ይላል፤ በስሜት ተውጦ። ወይም ደግሞ አንድን የሚታረድ ወንድ "seriously መላጣህ ግን ከሰውነትህ ጋር ይሄዳል፣ አንዳንድ ወንድ ግን መላጣ ያምርበታል! ካልነው አያናችን እያየ ግንባሩ ጥርስ ይሆናል።መላጣው ሁሉ ያስቃል።
አድናቆት የሁሉም የሰው ልጅ ደካማ ጎን እንደሆነ ተረዳሁ። “አድናቆት የሰው ልጅን በቁሙ የሚያስከር ኦፒየም ነው ብዬ ጥቅስ የሚመስል ነገር ፃፍኩ።
ከኛ የአድናቆት ኦፒየም ሌላ…ሆስተሷ እየመጣች በላይ በላዩ ትቀዳለታለች። በዚህን ጊዜ ሞቅታ ይመጣል። እዮኤል ይቺን ሰዓት ጠብቆ በኛ ክፍል በኩል እኛን እንዳላየ ኾኖ ሲያልፍ ለእንግዳው
እየጠቆምነው “የዚህ ፎቅ ባለቤት እሱ ነው!” እንለዋለን። የኾነ የአውሮፓ አገር እንጠራና እዛም አገር የሐበሻ ሬስቶራንት አለው፤ አታውቀውም” እንለዋለን። ምንም ሀብታም ቢሆን በሰማው ነገር በርገግ ማለት ይጀምራል።ትንሽ ቆይቶ ደግሞ እዮኤል ይመጣና እንደምን አመሻትሁ! ምን አነሰ ታዲያ? ምን ይጨመር ብሎ ተራ በተራ ይጨብጠናል አቤት ሲችልበት!!
ሰውየው ብርክ ይይዘዋል።
እኛ ደግሞ ቀልጠፍ ብለን " አቶ እዮኤል! እሱ ታዋቂ የመርካቶ ነጋዴ ነው…የምንወደው ወንድማችን ነው…ምናምን” እንላለን። ወይም ደግሞ ስለሰውየው የምናውቀውን ተናግረን በገገማ እናስተዋውቃቸዋለን እዩኤል
👍8
በአድናቆት "Oh Oh Great! Great! አንተን በማወቄ ታላቅ ኩራት ይሰማኛል! Nice meeting you!”፣ አብረን የምንሰራባቸው ዘርፎች ሊኖሩ እንደሚችሉ እገምታለሁ ምናምን እያለ ይቀበጣጥራል። አቤት እዮኤል ማስመሰል ሲችልበት!!
ይሄኔ እንግዳው ሰው መርበትበት ይጀምራል። እዮኤል ለትውውቃችን” ብሎ ግማሽ ውስኪ ያስወርዳል። " For meeting such a great guy! ሂሳቡ በኔ ነው፤ ኦኬ!" ብሎ ሥራ እንደበዛበት ሰው ተጣድፎ ይሄዳል።
ይሄን ጊዜ ሰውዬያችን ሰማይ ምድሩ ይደበላለቅበታል። ከዚህች ቅጽበት ጀምሮ ራሱን ከፍ ያለ ዋጋ ያለው
ሰው አድርጎ ያስባል። ስለዚህ በምንም መልኩ ክብሩን ላለማስደፈር ይሟሟታል። አድናቆታችን በላይ በላይ እናዘንብለታለን። ሰማይ ምድሩ ይደበላለቅበታል። ሌሎች የቤቱ ቆንጆ ቆንጆ ሴቶች አውቀው እኛ በምንጠጣበት ክፍል ወዝወዝ እያሉ ያልፋሉ። ወይም መጥተው ሰላም ይሉናል። ከእንግዳው ጋር
አስተዋውቀን እንዲጠጡ እንጋብዛቸዋለን። ብዙዎቹ ሆን ብለው ፍቃደኛ አይሆኑም፡፡ አንዷ ብቻ ደስ
ያላትን ማጠጥ አመስግና ታዝና ወንበር ስባ ትንሽ ትቀመጥና ለበዓል ከውጭ እንደመጣች፣ እንዲህ የመገባበዝ ባህል በምዕራቡ አለም እየጠፋ እንደሆነ ጠቅሳ ጓደኞቿ ሌላ ሩም እየጠበቋት እንደሆነ
ጠቀሳ ያዘዘችውን ትንሽ ቀምሳለት ትሄዳለች። የምታዘው ሁልጊዜም የቤቱን ዉድ መጠጥ ነው ታዲያ።
ልክ እዚህ ደረጃ ሲደረስ “ሆስተሷን” እንጠቅሳታለን። ሂሳብ አምጪ ማለታችን ነው። የሂሳቡን ወረቀት በሚያማምሩ ጡቶቿ መሐል ወሽቃ ታመጣለች። ይሄ የቤቱ ስታይል ነው። VIP room ዉስጥ
የሚከፍለው!” ብሎ ለመናገር የሚያስችል አቅም አይኖረውም፡፡ ሼም ስለሚይዘው የተባለውን ሁሉ
ይከፍላል። የዋጋ ዝርዝሩን ማንበብ ሁሉ ያሳፍረዋል። ቶሎ ብሎ ድምሩን ነው የሚያየው። ድምሩ ላይ ደግሞ ሆን ተብሎ በእስክሪብቶ ይከበብበታል የቤቱ ስታይል ነው።
ሌላ ቦታ በ2500 ብር ብር የሚሸጥ ቦትል እዚህ አምስት ሺ ብር ያስከፍሉታል። ለምን አይልም፣
ምከንያቱም ሲጀመር አእምሮው ተጭበርብሯል። የሕንጻውን ባለቤት ተዋውቆ እንዴት ለአምስት ሺ
ብር ይከራከራል? ታዋቂ ነጋዴ ነው ተብሎ እንዴት ለአምስት ሺ ብር ይጨነቃል? ይህን ከሚያደርግ
ቢሞት ይሻለዋል። ስለዚህ ዉርደቱን ዋጥ አድርጎ ኪሱን ይበረብራል። ዐይናችን እያየ ከ5 እስከ 10 ሺ ብር ከፍሎ ይወጣል። በኪሱ ካልያዘም “መጣሁ ባዝሩም ደርሼ” ብሎ ከሽንት ቤት ደውሎ በሠራተኛ ወይም በጓደኛው በፍጥነት ብር ያስመጣል። ይሄ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው።
እንግዳውን አብረነው በመውጣት እስከመንገድ ድረስ እንሸኘውና ታጥፈን መጥተን ሼራችንን ከደመቀ ቢሮ እንወስዳለን።
በዚህ መንገድ ስንቱን አረስነው። ስንቱን አሳረድነው። በተለይ ምድረ ጢባራም ዲያስፖራ! ምድረ ጡሩምባ ዲያስፖራ…ለነሱ ምህረት ኖሮን አያውቅም። አጭደን አጭደን ነው የምንለቃቸው። ሁሉንም
ሰው ደንቆሮ እነሱ ብቻ አዋቂ አድርገው ስለሚቆጥሩ አንወዳቸውም። ሦስት ወር ሳህን ያጠቡበትን
ዶላር በአንድ ሌሊት ዱቅ አድርገውት ሹልከ ይላሉ።
#የአሪዞና_ጋርዶች
ክለብ አሪዞና ሁለት በረኞች አሉት ተሺና ሳሚ ባርያው የሚባሉ። እውቅ ጋርዶች ናቸው ሳሚ የ 24 ቀበሌ ልጅ ነው። ድሮ ከሰፈሩ ልጆች ከሁሉም ተደባድቦ የሚችለው ስለጠፋ ከሌላ ሰፈር ጎበዝ ተደባዳቢ ላመጣለት ሰው 50 ብር ቲፕ ይሰጥ ነበር ይባላል። በቀን አንድ ሰው ሳይደበድብ ቤት ከገባ ልክ ቡና
ሳትጠጣ እንደዋለች ባልቴት ሲያዛጋ ይውላል። እንቅልፍ አይወስደውም። ቢገላበጥ፣ የእንቅልፍ ኪኒን ቢወስድ፣ ምን ቢል በቀን አንድ ሰው ካልደበደበ እንቅልፍ በዓይኑ ሳይዞር ሌሊቱ ይጋመሳል። ስለዚህ ከብርድ ልብሱም ቢኾን ወጥቶ ጎረቤትም ቢኾን ሄዶ፣ የተኛ ጎረምሳም ቢኾን ቀስቅሶ ይደበድበውና፣
“ይቅርታ እንቅልፍ እምቢ ስላለኝ ነው” ብሎት ቤቱ ተመልሶ ገብቶ ይተኛ ነበር ይባላል።
ህልሙ በኦሎምፒክ ኢትዮጵያን የሚወክል ቦክሰኛ ሆኖ አውስትራሊያ የሚባል አገር ሄዶ መጥፋት ነበር። ለዚህም ሲል ተከታታይ የቦክስ ስልጠና ወስዷል። ለምሳሌ በአንድ ምት ሰውን እንዴት ከመሬት ጋር ማደባየት እንደሚቻል፣ አፍንጫን የመስበርና የማጣመም ቴክኒኮት፣ በአንድ ቦክስ የኋላ ጥርስን ማርገፍ፣ በሁለት ቡጢ መንጋጋን ማጣመም፣ ወዘተ... ከወሰዳቸው ጥቂት ኮርሶች የሚጠቀሱለት ናቸው።ነገር ግን እሱ አውስትራሊያ ኦሎምፒክ እስከታዘጋጅ ሲጠብቅ እድሜው ቆሞ አልጠበቀውም
ለመካከለኛ ክብደት ቡጢኛ እድሜህ ገፍቷል ተብሎ ከክለብ ተቀነሰ። በንዴት የክለቡን ፕሬዝዳንት ሁለት የፊት ጥርስ ቀንሶ ጓንቱን ሰቀለ።
ከዚያ በኋላ ሁለት ዓመት ታስሮ ሲፈታ የቀድሞ አሰልጣኙ “ከሙያህ ጋር የሚሄድ ሥራ አግኝቼልካለዉ ብለው “ክለብ አሪዞና” አስቀጠሩት። እዚህ ጋርድ ኾኖ ተቀጠረ።
ችግሩ አሪዞና ብዙም ወጠጤ ስለማይመጣ ሳሚ ሥራ ፈታ። እንዲያውም መጀመርያ አካባቢ “ወይኔ
ሳሚ! ባጣ ባጣ የምደበድበው ወንድ ልጣ!” ብሎ በጣም ይብሰለሰል ነበር ብለውኛል ጓደኞቹ። የኋላ የኋላ በአሪዞና ያለአቅማቸው ጠጥተው የሰከሩ ሴቶችን አንከብክቦ አቅፎ መኪናቸው ዉስጥ መከተት ሲጀምር፣ መኪናቸውን እየነዳላቸው እነሱን ቤት ማድረስ ሲጀምር ምናምን ሥራውን እየወደደው መጣ። ያም ኾኖ ግን አገሬ ተሰጥኦዬን በሙሉ አቅሟ አልተጠቀመችበትም” እያለ መተከዙ አልቀረም።
አንዳንዴ ዉልፍ ሲልበት ሰው ሳያየው ጸብ የሚበዛባቸው ቤቶች እየሄደ አንድ አፍንጫ ሰብሮና ሁለት የፊት ጥርስ አውልቆ መምጣት ጀመረ። ከተማው ውስጥ ብዙ የጥርስ ክሊኒኮች የበዙት ሳሚ ባሪያው ባደረገላቸው አስተዋጽኦ ሳይሆን አይቀርም እየተባለ ተቀለደ።
ሳሚ ከጊዜ በኋላ እየሰከነ መጣ መሰለኝ ትሁት መኾን ጀመረ። ኾኖም አሁንም ድረስ ሥራ መፍታቱ ያብከነክነዋል ወንዱ ምን ነካው!” እያለ ይተክዛል።አሪዞና ዳንስ ፍሎር ላይ ደስ የማይል አደናነስ የሚደንስ ጎረምሳ ሲያጋጥመው ደስ ይለዋል። እንዳገለገለ ሶፍት በአንድ እጁ አንጠልጥሎ ያስወጣዋል።በዚህ ሁኔታ አንድ ወቅት ላይ አንድ ታዋቂ የሬጌ ዘፋኝን ከጭፈራ መድረክ አስወጥቶት ብዙ ጣጣ አምቶብን ነበር።
ሳሚ ባሪያው በተፈጥሮ ረዥም ስለሆነና ወንዳወንድ ሰውነቱ ስለሚያምር ሀብታም አሮጊት ሴቶች ከባላቸው እየደስቁ አንዳንድ የትርፍ ሰዓት ሥራ ያሠሩት ጀመር። ከሚያሰሩት ጥቃቅንና አነስተኛ ሥራዎት እንዱ እነሱ እላዩ ላይ ወጥተው፣ እሱ ደግሞ ከስር ሆኖ ፣ ዥዋዥዌ መጫወት ነበር።
ሳሚ ባሪያው በዚህ መልኩ ገቢውን ማሳደግ ጀመረ። ከዚህ ሌላ ደግሞ እጅግ ሞጃ የኾኑ የከተማዋ ኢንቨስተሮት እዚያው አሪዞና ውስጥ ተጨማሪ ሥራ እያሰሩት ጠቀም ያለ ሳንቲም ይሰጡት ነበር። ምን ያሰሩት እንደነበር መግለጽ ግን ትንሽ ሳይከብድ አይቀርም።
አሱ፣ እንደነገረኝ እኔም በከፊል እንዳየሁት Top VIP Room ውስጥ የሚጠጡ የመጨረሻዎቹ የከተማዋ ሀብታሞች ብዙዉን ጊዜ ጥሩ ተዝናናን የሚሉት ጥሩ ሲደንሱ ወይም ጥሩ በልተው ጥሩ.ሲጠጡ አይደለም። ያንንማ ማንም በሬ ያደርገዋል። ያንንማ የመኪና ደላላም ያደርገዋል። እነሱ
የሚዝናኑት ትንንሽ ሀብታሞችን በማንጓጠጥ ነው። ለምሳሌ ትንንሽ ሀብታሞች ኪስ ዉስጥ በትንሽ
ጠርሙስ ዉስኪ በማፍሰስ ሰውየው ሲደነግጥ መሳቅ አንዱ መዝናኛቸው ነው። ሁለተኛው ደግሞ የትንንሽ ሀብታሞችን ሚስቶች ወይም የያዟትን ሴት በገንዘብ ኃይል ማስከዳት ያስደስታቸዋል።
ከሚዝናናው “ተራ ሀብታም” ውስጥ ደስ ያላላቸውን ሰው “በባለሙያዎች” አማካኝነት እንዲዋረድ በማድረግ በሱ ላይ ቦርጫቸው እስኪረግፍ መሳቅ አጅግ
ይሄኔ እንግዳው ሰው መርበትበት ይጀምራል። እዮኤል ለትውውቃችን” ብሎ ግማሽ ውስኪ ያስወርዳል። " For meeting such a great guy! ሂሳቡ በኔ ነው፤ ኦኬ!" ብሎ ሥራ እንደበዛበት ሰው ተጣድፎ ይሄዳል።
ይሄን ጊዜ ሰውዬያችን ሰማይ ምድሩ ይደበላለቅበታል። ከዚህች ቅጽበት ጀምሮ ራሱን ከፍ ያለ ዋጋ ያለው
ሰው አድርጎ ያስባል። ስለዚህ በምንም መልኩ ክብሩን ላለማስደፈር ይሟሟታል። አድናቆታችን በላይ በላይ እናዘንብለታለን። ሰማይ ምድሩ ይደበላለቅበታል። ሌሎች የቤቱ ቆንጆ ቆንጆ ሴቶች አውቀው እኛ በምንጠጣበት ክፍል ወዝወዝ እያሉ ያልፋሉ። ወይም መጥተው ሰላም ይሉናል። ከእንግዳው ጋር
አስተዋውቀን እንዲጠጡ እንጋብዛቸዋለን። ብዙዎቹ ሆን ብለው ፍቃደኛ አይሆኑም፡፡ አንዷ ብቻ ደስ
ያላትን ማጠጥ አመስግና ታዝና ወንበር ስባ ትንሽ ትቀመጥና ለበዓል ከውጭ እንደመጣች፣ እንዲህ የመገባበዝ ባህል በምዕራቡ አለም እየጠፋ እንደሆነ ጠቅሳ ጓደኞቿ ሌላ ሩም እየጠበቋት እንደሆነ
ጠቀሳ ያዘዘችውን ትንሽ ቀምሳለት ትሄዳለች። የምታዘው ሁልጊዜም የቤቱን ዉድ መጠጥ ነው ታዲያ።
ልክ እዚህ ደረጃ ሲደረስ “ሆስተሷን” እንጠቅሳታለን። ሂሳብ አምጪ ማለታችን ነው። የሂሳቡን ወረቀት በሚያማምሩ ጡቶቿ መሐል ወሽቃ ታመጣለች። ይሄ የቤቱ ስታይል ነው። VIP room ዉስጥ
የሚከፍለው!” ብሎ ለመናገር የሚያስችል አቅም አይኖረውም፡፡ ሼም ስለሚይዘው የተባለውን ሁሉ
ይከፍላል። የዋጋ ዝርዝሩን ማንበብ ሁሉ ያሳፍረዋል። ቶሎ ብሎ ድምሩን ነው የሚያየው። ድምሩ ላይ ደግሞ ሆን ተብሎ በእስክሪብቶ ይከበብበታል የቤቱ ስታይል ነው።
ሌላ ቦታ በ2500 ብር ብር የሚሸጥ ቦትል እዚህ አምስት ሺ ብር ያስከፍሉታል። ለምን አይልም፣
ምከንያቱም ሲጀመር አእምሮው ተጭበርብሯል። የሕንጻውን ባለቤት ተዋውቆ እንዴት ለአምስት ሺ
ብር ይከራከራል? ታዋቂ ነጋዴ ነው ተብሎ እንዴት ለአምስት ሺ ብር ይጨነቃል? ይህን ከሚያደርግ
ቢሞት ይሻለዋል። ስለዚህ ዉርደቱን ዋጥ አድርጎ ኪሱን ይበረብራል። ዐይናችን እያየ ከ5 እስከ 10 ሺ ብር ከፍሎ ይወጣል። በኪሱ ካልያዘም “መጣሁ ባዝሩም ደርሼ” ብሎ ከሽንት ቤት ደውሎ በሠራተኛ ወይም በጓደኛው በፍጥነት ብር ያስመጣል። ይሄ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው።
እንግዳውን አብረነው በመውጣት እስከመንገድ ድረስ እንሸኘውና ታጥፈን መጥተን ሼራችንን ከደመቀ ቢሮ እንወስዳለን።
በዚህ መንገድ ስንቱን አረስነው። ስንቱን አሳረድነው። በተለይ ምድረ ጢባራም ዲያስፖራ! ምድረ ጡሩምባ ዲያስፖራ…ለነሱ ምህረት ኖሮን አያውቅም። አጭደን አጭደን ነው የምንለቃቸው። ሁሉንም
ሰው ደንቆሮ እነሱ ብቻ አዋቂ አድርገው ስለሚቆጥሩ አንወዳቸውም። ሦስት ወር ሳህን ያጠቡበትን
ዶላር በአንድ ሌሊት ዱቅ አድርገውት ሹልከ ይላሉ።
#የአሪዞና_ጋርዶች
ክለብ አሪዞና ሁለት በረኞች አሉት ተሺና ሳሚ ባርያው የሚባሉ። እውቅ ጋርዶች ናቸው ሳሚ የ 24 ቀበሌ ልጅ ነው። ድሮ ከሰፈሩ ልጆች ከሁሉም ተደባድቦ የሚችለው ስለጠፋ ከሌላ ሰፈር ጎበዝ ተደባዳቢ ላመጣለት ሰው 50 ብር ቲፕ ይሰጥ ነበር ይባላል። በቀን አንድ ሰው ሳይደበድብ ቤት ከገባ ልክ ቡና
ሳትጠጣ እንደዋለች ባልቴት ሲያዛጋ ይውላል። እንቅልፍ አይወስደውም። ቢገላበጥ፣ የእንቅልፍ ኪኒን ቢወስድ፣ ምን ቢል በቀን አንድ ሰው ካልደበደበ እንቅልፍ በዓይኑ ሳይዞር ሌሊቱ ይጋመሳል። ስለዚህ ከብርድ ልብሱም ቢኾን ወጥቶ ጎረቤትም ቢኾን ሄዶ፣ የተኛ ጎረምሳም ቢኾን ቀስቅሶ ይደበድበውና፣
“ይቅርታ እንቅልፍ እምቢ ስላለኝ ነው” ብሎት ቤቱ ተመልሶ ገብቶ ይተኛ ነበር ይባላል።
ህልሙ በኦሎምፒክ ኢትዮጵያን የሚወክል ቦክሰኛ ሆኖ አውስትራሊያ የሚባል አገር ሄዶ መጥፋት ነበር። ለዚህም ሲል ተከታታይ የቦክስ ስልጠና ወስዷል። ለምሳሌ በአንድ ምት ሰውን እንዴት ከመሬት ጋር ማደባየት እንደሚቻል፣ አፍንጫን የመስበርና የማጣመም ቴክኒኮት፣ በአንድ ቦክስ የኋላ ጥርስን ማርገፍ፣ በሁለት ቡጢ መንጋጋን ማጣመም፣ ወዘተ... ከወሰዳቸው ጥቂት ኮርሶች የሚጠቀሱለት ናቸው።ነገር ግን እሱ አውስትራሊያ ኦሎምፒክ እስከታዘጋጅ ሲጠብቅ እድሜው ቆሞ አልጠበቀውም
ለመካከለኛ ክብደት ቡጢኛ እድሜህ ገፍቷል ተብሎ ከክለብ ተቀነሰ። በንዴት የክለቡን ፕሬዝዳንት ሁለት የፊት ጥርስ ቀንሶ ጓንቱን ሰቀለ።
ከዚያ በኋላ ሁለት ዓመት ታስሮ ሲፈታ የቀድሞ አሰልጣኙ “ከሙያህ ጋር የሚሄድ ሥራ አግኝቼልካለዉ ብለው “ክለብ አሪዞና” አስቀጠሩት። እዚህ ጋርድ ኾኖ ተቀጠረ።
ችግሩ አሪዞና ብዙም ወጠጤ ስለማይመጣ ሳሚ ሥራ ፈታ። እንዲያውም መጀመርያ አካባቢ “ወይኔ
ሳሚ! ባጣ ባጣ የምደበድበው ወንድ ልጣ!” ብሎ በጣም ይብሰለሰል ነበር ብለውኛል ጓደኞቹ። የኋላ የኋላ በአሪዞና ያለአቅማቸው ጠጥተው የሰከሩ ሴቶችን አንከብክቦ አቅፎ መኪናቸው ዉስጥ መከተት ሲጀምር፣ መኪናቸውን እየነዳላቸው እነሱን ቤት ማድረስ ሲጀምር ምናምን ሥራውን እየወደደው መጣ። ያም ኾኖ ግን አገሬ ተሰጥኦዬን በሙሉ አቅሟ አልተጠቀመችበትም” እያለ መተከዙ አልቀረም።
አንዳንዴ ዉልፍ ሲልበት ሰው ሳያየው ጸብ የሚበዛባቸው ቤቶች እየሄደ አንድ አፍንጫ ሰብሮና ሁለት የፊት ጥርስ አውልቆ መምጣት ጀመረ። ከተማው ውስጥ ብዙ የጥርስ ክሊኒኮች የበዙት ሳሚ ባሪያው ባደረገላቸው አስተዋጽኦ ሳይሆን አይቀርም እየተባለ ተቀለደ።
ሳሚ ከጊዜ በኋላ እየሰከነ መጣ መሰለኝ ትሁት መኾን ጀመረ። ኾኖም አሁንም ድረስ ሥራ መፍታቱ ያብከነክነዋል ወንዱ ምን ነካው!” እያለ ይተክዛል።አሪዞና ዳንስ ፍሎር ላይ ደስ የማይል አደናነስ የሚደንስ ጎረምሳ ሲያጋጥመው ደስ ይለዋል። እንዳገለገለ ሶፍት በአንድ እጁ አንጠልጥሎ ያስወጣዋል።በዚህ ሁኔታ አንድ ወቅት ላይ አንድ ታዋቂ የሬጌ ዘፋኝን ከጭፈራ መድረክ አስወጥቶት ብዙ ጣጣ አምቶብን ነበር።
ሳሚ ባሪያው በተፈጥሮ ረዥም ስለሆነና ወንዳወንድ ሰውነቱ ስለሚያምር ሀብታም አሮጊት ሴቶች ከባላቸው እየደስቁ አንዳንድ የትርፍ ሰዓት ሥራ ያሠሩት ጀመር። ከሚያሰሩት ጥቃቅንና አነስተኛ ሥራዎት እንዱ እነሱ እላዩ ላይ ወጥተው፣ እሱ ደግሞ ከስር ሆኖ ፣ ዥዋዥዌ መጫወት ነበር።
ሳሚ ባሪያው በዚህ መልኩ ገቢውን ማሳደግ ጀመረ። ከዚህ ሌላ ደግሞ እጅግ ሞጃ የኾኑ የከተማዋ ኢንቨስተሮት እዚያው አሪዞና ውስጥ ተጨማሪ ሥራ እያሰሩት ጠቀም ያለ ሳንቲም ይሰጡት ነበር። ምን ያሰሩት እንደነበር መግለጽ ግን ትንሽ ሳይከብድ አይቀርም።
አሱ፣ እንደነገረኝ እኔም በከፊል እንዳየሁት Top VIP Room ውስጥ የሚጠጡ የመጨረሻዎቹ የከተማዋ ሀብታሞች ብዙዉን ጊዜ ጥሩ ተዝናናን የሚሉት ጥሩ ሲደንሱ ወይም ጥሩ በልተው ጥሩ.ሲጠጡ አይደለም። ያንንማ ማንም በሬ ያደርገዋል። ያንንማ የመኪና ደላላም ያደርገዋል። እነሱ
የሚዝናኑት ትንንሽ ሀብታሞችን በማንጓጠጥ ነው። ለምሳሌ ትንንሽ ሀብታሞች ኪስ ዉስጥ በትንሽ
ጠርሙስ ዉስኪ በማፍሰስ ሰውየው ሲደነግጥ መሳቅ አንዱ መዝናኛቸው ነው። ሁለተኛው ደግሞ የትንንሽ ሀብታሞችን ሚስቶች ወይም የያዟትን ሴት በገንዘብ ኃይል ማስከዳት ያስደስታቸዋል።
ከሚዝናናው “ተራ ሀብታም” ውስጥ ደስ ያላላቸውን ሰው “በባለሙያዎች” አማካኝነት እንዲዋረድ በማድረግ በሱ ላይ ቦርጫቸው እስኪረግፍ መሳቅ አጅግ
👍3❤1
ያስደስተቻው። ባለሙያዎች ማለት በነዚህ ሀብታሞች ቋንቋ “ጋርዶች ማለት ነው።
የዳንስ ፍሎ ካሉበት Top VIP Room ቁልጭ ብሎ ስለሚታይ እንዲህ አይነት ድርጊቶችን ሞቅ ባላቸው ቁጥር ማድረግ ደስ ይላቸዋል።ለምሳሌ በምሽቱ ቀሽት የምትባል ሴት ይዞ የመጣ ወንድ ካለ
እሱን ታርጌት ውስጥ ያስገቡታል። ከዚያ ልጁ በደስታ ሰክሮ እየጨፈረ ሲያብድ ሀብታሙ ሰውዬ
“ይሄን ልጅ ቀልቤ አልወደደውም” ካለ አጃቢዎቹ ቶሎ ብለው፣ ችግር የለም በ“ባለሙያ” እንዲወጣ ይደረጋል” ይሉታል። ይሄኔ ሳሚ ባሪያው በልዩ ረዳቶቻቸው በኩል ይጠራና በጆሮው የኾነ ነገር ሹክ ይሉታል።
ሳሚ ልጁ ጋር ሄዶ "ወንድሜ በስነስርአት ተዝናና ይለዋል።ልጁ ጥፋቱ ግር ብሎት ምን አጠፋው ይላል።ሳሚ ኮስተር ብሎ በቃ ሥርአት ይዘህ ጠጣ ጠርሙስ አያያዝህ ቤቱን የሚመጥን መሆን አለበት ይሄ ጠላ ቤት አይደለም ይገባሃል? ይለዋል።በገርል ፍሬንዱ ፊት እንደዚህ መባሉ ያንገበገበዉ ወጣት በጣም ደፋር ከሆነ ሳሚን ካልደበደብኩ ይላል።ይሄን ግዜ ሳሚ ባርያው ጆሮውን ይዞ ውጭ አውጥቶ እንደ ጅራፍ ያስጮህዋል።
TOP VIP Room ቁጭ ብለው ይሄ እንዲሆን ያዘዙት ሀብታሞች "ካካካካ...ካካካካ..ካካካካ እያሉ ረጅም የሃብታም ሳቃቸውን ይለቁታል።ቦርጫቸው ለምን በሳቅ ብዛት ረግፎ እንደማይጠፋ አይገባኝም።የተዋረደውን ልጅ ገረል ፍሬንድ ከተቻለ "አንቺን መጋበዝ የሚፈልጉ ባለሀብቶች አሉ ፍቃድሽ ከሆነ .." ተብላ ትጠራለች።እምቢ ካለች ማንም አይነካትም በሰላም የጠጣችበት ተከፍሎላት ትሄዳለች።እሺ ካለችና ዕድለኛ ከሆነች ግን አንድ ኬክ ቤት ሊከፈትላት ይችላል ደግነቱ እነዚህ የናጠጡ ሃብታሞች ለሴት ልጅ ያላቸው ክብር ደስ ይላል።ፍቃደኛ ያልሆነች ሴት በፍፁም አይነኩም
ሳሚ እንደነገረኝ የሞጃዎቹ ፍላጎት ከሆነ ባለትዳርም ቢሆን በዚህ መልኩ ከቤቱ ተዋርዶ ሊወጣ ይችላል።ዋናው ነገር ድርጊቱ እነወዚያ ባለሃብቶች ያዝናናል ወይስ አያዝናናም የሚለው ነው።
አንድ ቅዳሜ ማታ ባለሃብቶቹ ከሚቀመጡበት ክፍል ቀጥሎ ባለው የዲፕሎማቶች ክፍል ነበር ከሁለት የአረብ ሊግ ዲፕሎማቶችና ከእዩኤል ጋር። አረቦቹ ይህን ሪያል ስለሚረጩት ነበር እዩኤል አብሮን ተቀምጦ የነበረው። ሳሚ ባርያው መጥቶ በጆሮው የሆነ ነገር ሹክ አለው። እዩኤል ቱር ብሎ ተነስቶ ለሁሉም ሰው ትእዛዝ መስጠት ጀመረ።ዲጄው በፍጥነት ሙዚቃዎቹን እንዲቀይር ተደረገ።በተለይ የሚመጡት ሁለቱ ባለሃብቶች የሚወዷቸው ቆየት ያሉ አማርኛ ዘፈኖች አሏቸው በቃ እነሱ ተደጋግመው መከፈት ጀመሩ።ቤቱ በአንድ ጊዜ በአንድ እግሩ ቆመ።
ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ሰዎቹ ከአጃቢዎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ልዩ ክፍላቸው አመሩ ይህ ክፍል ከነሱ ውጪ ማንም አይገባበትም።ለአንድ አመት ከፍለውበታል።ቢኖሩም ባይኖሩም በቀን በቀን እየተፀዳ ሽቶ ይርከፈከፍበታል።እኔ ገብቼበትም አላቅ።ገባን የሚሉ ሴቶች ግን አሉ በወርቅ የተለበጠ ጠረጴዛና ሶፋ ወንበር አለ ብለው ይ ነግሩናል።
እዩኤል ባለሐብቶቹ ገብተው ቦታቸውን እንደያዙና ነገሮች መልክ መልክ እንደያዙ ሲያረጋግጥ ተልሶ መጣ። ግርማ ነው ያለኝ። ሪያል እንደጠበል እየረጩ ከነበሩ ሁለት የአረብ ዲፕሎማቶች በላይ የሚያንቀጠቅጡት ምን እይነት ሀብታም ቢኾኑ ነው ብዬ አሰብኩ።
ተማልሶ መጥቶ እኛን ከተቀላቀለን በኋላ አንድ ሁለቴ ከመጠጡ ተጎነጨለት። ከዚያ ትንፋሹን ሰብስቦ እኝዲህ አለኝ።
ይሄ ሚስኪን ሕዝብ አዲስአባ የኔ ናት፣ የኔ ናት እያለ ይፋጃል፤ ልንገርሽ አይደል? ፊንፊኔ የኦሮሞም የኢትዮጵያም አይደለችም። የዚህ ሰውዬ ናት" አለ በአፍንጫው ጫፍ Top VIP Room እያመለከተኝ።
ያን ሰምን በአዲስ አበባ የባለቤትነት ጉዳይ ላይ በየዩኒቨርስቲው ረብሻ ተከስቶ ነበር።
የተናገረው ነገር ፖለቲካ ስለመሰለኝ ምንም አላልኩም። እሱም ቀልቡ ሁሉ ሁለቱ ባለሐብቶች ጋር ስለነበረ ተነስቶ ሄደ።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 እና #Share ማድረግ እንዳይረሳ
#ለሮዚ_መልክታችሁን
#ለማስተላለፍ_ከፈለጋችሁ #ከታችያለውን_email #መጠቀም_ትችላላችሁ👇
rozachichinia@gmail.com
ለኛ ደሞ ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
የዳንስ ፍሎ ካሉበት Top VIP Room ቁልጭ ብሎ ስለሚታይ እንዲህ አይነት ድርጊቶችን ሞቅ ባላቸው ቁጥር ማድረግ ደስ ይላቸዋል።ለምሳሌ በምሽቱ ቀሽት የምትባል ሴት ይዞ የመጣ ወንድ ካለ
እሱን ታርጌት ውስጥ ያስገቡታል። ከዚያ ልጁ በደስታ ሰክሮ እየጨፈረ ሲያብድ ሀብታሙ ሰውዬ
“ይሄን ልጅ ቀልቤ አልወደደውም” ካለ አጃቢዎቹ ቶሎ ብለው፣ ችግር የለም በ“ባለሙያ” እንዲወጣ ይደረጋል” ይሉታል። ይሄኔ ሳሚ ባሪያው በልዩ ረዳቶቻቸው በኩል ይጠራና በጆሮው የኾነ ነገር ሹክ ይሉታል።
ሳሚ ልጁ ጋር ሄዶ "ወንድሜ በስነስርአት ተዝናና ይለዋል።ልጁ ጥፋቱ ግር ብሎት ምን አጠፋው ይላል።ሳሚ ኮስተር ብሎ በቃ ሥርአት ይዘህ ጠጣ ጠርሙስ አያያዝህ ቤቱን የሚመጥን መሆን አለበት ይሄ ጠላ ቤት አይደለም ይገባሃል? ይለዋል።በገርል ፍሬንዱ ፊት እንደዚህ መባሉ ያንገበገበዉ ወጣት በጣም ደፋር ከሆነ ሳሚን ካልደበደብኩ ይላል።ይሄን ግዜ ሳሚ ባርያው ጆሮውን ይዞ ውጭ አውጥቶ እንደ ጅራፍ ያስጮህዋል።
TOP VIP Room ቁጭ ብለው ይሄ እንዲሆን ያዘዙት ሀብታሞች "ካካካካ...ካካካካ..ካካካካ እያሉ ረጅም የሃብታም ሳቃቸውን ይለቁታል።ቦርጫቸው ለምን በሳቅ ብዛት ረግፎ እንደማይጠፋ አይገባኝም።የተዋረደውን ልጅ ገረል ፍሬንድ ከተቻለ "አንቺን መጋበዝ የሚፈልጉ ባለሀብቶች አሉ ፍቃድሽ ከሆነ .." ተብላ ትጠራለች።እምቢ ካለች ማንም አይነካትም በሰላም የጠጣችበት ተከፍሎላት ትሄዳለች።እሺ ካለችና ዕድለኛ ከሆነች ግን አንድ ኬክ ቤት ሊከፈትላት ይችላል ደግነቱ እነዚህ የናጠጡ ሃብታሞች ለሴት ልጅ ያላቸው ክብር ደስ ይላል።ፍቃደኛ ያልሆነች ሴት በፍፁም አይነኩም
ሳሚ እንደነገረኝ የሞጃዎቹ ፍላጎት ከሆነ ባለትዳርም ቢሆን በዚህ መልኩ ከቤቱ ተዋርዶ ሊወጣ ይችላል።ዋናው ነገር ድርጊቱ እነወዚያ ባለሃብቶች ያዝናናል ወይስ አያዝናናም የሚለው ነው።
አንድ ቅዳሜ ማታ ባለሃብቶቹ ከሚቀመጡበት ክፍል ቀጥሎ ባለው የዲፕሎማቶች ክፍል ነበር ከሁለት የአረብ ሊግ ዲፕሎማቶችና ከእዩኤል ጋር። አረቦቹ ይህን ሪያል ስለሚረጩት ነበር እዩኤል አብሮን ተቀምጦ የነበረው። ሳሚ ባርያው መጥቶ በጆሮው የሆነ ነገር ሹክ አለው። እዩኤል ቱር ብሎ ተነስቶ ለሁሉም ሰው ትእዛዝ መስጠት ጀመረ።ዲጄው በፍጥነት ሙዚቃዎቹን እንዲቀይር ተደረገ።በተለይ የሚመጡት ሁለቱ ባለሃብቶች የሚወዷቸው ቆየት ያሉ አማርኛ ዘፈኖች አሏቸው በቃ እነሱ ተደጋግመው መከፈት ጀመሩ።ቤቱ በአንድ ጊዜ በአንድ እግሩ ቆመ።
ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላ ሰዎቹ ከአጃቢዎቻቸው ጋር ሆነው ወደ ልዩ ክፍላቸው አመሩ ይህ ክፍል ከነሱ ውጪ ማንም አይገባበትም።ለአንድ አመት ከፍለውበታል።ቢኖሩም ባይኖሩም በቀን በቀን እየተፀዳ ሽቶ ይርከፈከፍበታል።እኔ ገብቼበትም አላቅ።ገባን የሚሉ ሴቶች ግን አሉ በወርቅ የተለበጠ ጠረጴዛና ሶፋ ወንበር አለ ብለው ይ ነግሩናል።
እዩኤል ባለሐብቶቹ ገብተው ቦታቸውን እንደያዙና ነገሮች መልክ መልክ እንደያዙ ሲያረጋግጥ ተልሶ መጣ። ግርማ ነው ያለኝ። ሪያል እንደጠበል እየረጩ ከነበሩ ሁለት የአረብ ዲፕሎማቶች በላይ የሚያንቀጠቅጡት ምን እይነት ሀብታም ቢኾኑ ነው ብዬ አሰብኩ።
ተማልሶ መጥቶ እኛን ከተቀላቀለን በኋላ አንድ ሁለቴ ከመጠጡ ተጎነጨለት። ከዚያ ትንፋሹን ሰብስቦ እኝዲህ አለኝ።
ይሄ ሚስኪን ሕዝብ አዲስአባ የኔ ናት፣ የኔ ናት እያለ ይፋጃል፤ ልንገርሽ አይደል? ፊንፊኔ የኦሮሞም የኢትዮጵያም አይደለችም። የዚህ ሰውዬ ናት" አለ በአፍንጫው ጫፍ Top VIP Room እያመለከተኝ።
ያን ሰምን በአዲስ አበባ የባለቤትነት ጉዳይ ላይ በየዩኒቨርስቲው ረብሻ ተከስቶ ነበር።
የተናገረው ነገር ፖለቲካ ስለመሰለኝ ምንም አላልኩም። እሱም ቀልቡ ሁሉ ሁለቱ ባለሐብቶች ጋር ስለነበረ ተነስቶ ሄደ።
💫ይቀጥላል💫
Like 👍 እና #Share ማድረግ እንዳይረሳ
#ለሮዚ_መልክታችሁን
#ለማስተላለፍ_ከፈለጋችሁ #ከታችያለውን_email #መጠቀም_ትችላላችሁ👇
rozachichinia@gmail.com
ለኛ ደሞ ማንኛዉንም አስተያየት በ @atronosebot አድርሱን
👍4
#ወድሽ_ነበር_አለሁ
አሁን ደረስኩ ሲል ፥ ጓዙን አንጠልጥሎ
ቅድም ተብሎ ሊሸኝ ፥ ሊሄድ ተገንጥሎ፣
አሁን ከአሁን በፊት ፥ ከአፌ ላይ ቢበርም
በሚመጣው አሁን ፥ ሳልወድሽ አልቀርም።
አሁን ደረስኩ ሲል ፥ ጓዙን አንጠልጥሎ
ቅድም ተብሎ ሊሸኝ ፥ ሊሄድ ተገንጥሎ፣
አሁን ከአሁን በፊት ፥ ከአፌ ላይ ቢበርም
በሚመጣው አሁን ፥ ሳልወድሽ አልቀርም።