#የእግዜር_የአደራ_ልጅ…
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ዶ/ር ኤልያስ ዛሬ ምን አልባትም በህይወቱ ፍፁም የሆነ ደስታ የተሰደሰተበት ቀን ስለሆነ ስሜቱን መቆጣጠር አቅቷት ጥንቅቅ ብሎ ባለቀ ውብ ቤቱ ውስጥ ከክፍል ክፍል እየተመላለሰ እንደህፃን እየቧረቀ ነው፡፡ስልኩን አነሳና ደወለ…፡፡ከአራት ጥሪ በኃላ ተነሳ፡፡
‹‹ውድ ባለቤቴ እንዴት አለሽልኝ››
‹‹አንተ ያንን ቃል መጠቀም የምትችለው እኮ ሰማንያ ፈርመህ ቤትህ ስታስገባኝ ነው››አለችው እየሳቀች፡፡፡
‹‹ያው በይው..ዜናውን አልሰማሽም እንዴ…..?ሽማግሌዎቼ እኮ ወላጆችሽ ልጃቸውን ሊሰጡኝ በደስታ መስማማታቸውን አሁን ነግረውኝ በደስታ እያበድኩ ነው፡፡››
‹‹ከአንተ ቀድሜ ሰማሁ…ምነው ይከለክሉኛል ብለህ አስበህ ነበር እንዴ?››
‹‹እንዴ ምን ይታወቃል…..ምን አልባት ቅድሞ እደጅ እየጠና ያለ ብረት መዝጊያ አማች ኖሮ ሀሳባቸው ወደእሱ ቢያጋድልስ?››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው …ለአሁኑ ግን ተርፈሀል››
‹‹እኔም መትረፍ የምፈልገው ለአሁኑ ብቻ ነው…የማገባው አንዴ ብቻ እኮ ነው…››ተሳሳቁ፡፡
‹‹እና ይሄንን ደስታ አብረን ማክበር የለብንም ትያለሽ…?››
‹‹አንተ ..ከአሁን ወዲህ እኮ እስከሰርጌ ቀን ድረስ ልታየኝ አይገባም…››
‹‹እንደዛ ከሆነማ ሰርጉን ነገውኑ ደግስ በይኛ››
‹‹አዎ ..ያን ያህል ከቸኮልክ አድርገው››
‹‹እሺ..አስበብበታለው..እውነት ግን በጣም ላገኝሽ ፈልጌለሁ…››
እሷም ከአንደበቷ አውጥታ አትናረው እንጂ በጣም ልታገኘው ፈልጋለች፡፡‹‹ ይቻላል..የትና መቼ?፡፡››
‹‹ምሳ ልጋብዝሽ …ሰባት ሰዓት ስካይ ላይት እንገናኝ፡፡››
‹‹ሰባት ሰዓት ..አሁን እኮ አራት ተኩል ሆኖል…..ለመዘጋጃጀት በቂ ጊዜ አይኖረኝም፡፡››
‹‹አንቺ ደግሞ..እንደውም ምንም መዘገጃጀት አያስፈልግሽም… እዛ ሆስፒታል በነበርሽበት ጊዜ ያለምንም ዝግጅት ምን እንደምትመስዬ እኮ አውቃለው…ለእኔ ብለሽ ለመቆነጃጀት ከሁለት ሰዓት በላይ ማጥፋት የለብሽም…ከዛሬ ወዲህ ባልሽ ነኝ፡፡ማለቴ ለጊዜው እጮኛሽ ነኝ..ግን ለጥቂት ጊዜ ብቻ ነው፡፡››
‹‹‹ይሁንልህ እሺ…..ግን ቅር ካላለህ አንድነገር ልጠይቅህ ››
‹‹ምን ጠይቂኝ››
‹‹ጸጋን ይዣት ብመጣ ቅር ይልሀል?››
‹‹አረ በፍፅም ..እንደውም በተቃራኒው ደስ ነው የሚለኝ …እሷ ከመጀመሪያው ጀምሮ የፍቅራችን ብቸኛ ምስክር ነበረች..ዛሬ መገኘት ይገባታል….ጫጉላ ቀናችን ላይ አብራን ወደመኝታ ትግባ እንዳትይ እንጂ ለዛሬው ደስ ይለኛል››
ስለጫጉላ ሲያወራ እፍረትም ሙቀትም ተሰማት‹‹አንተ ምን እያልክ ነው..?በል ቸው››ብላ ስልኩን ዘጋች፡፡
እሱም ወዲያው ወደሻወር ቤት ገባና ሰውነቱን በፍጥነት ተለቃለቀ…ከዛ ፂሙን ላጨ…ሙሉ ሱፍ ለበሰና ዝንጥ አለ…፡፡ለመውጣት ዝግጁ ሆነ…፡፡ሰዓቱን ሲያይ 5 .ከሩብ ይላል….ከራሄልና ከፀጋ ጋር ወደሚገናኝበት ቀጠሮ ከመሄዱ በፊት ማግኘት የሚገባው አንድ ሰው አለ…ከአመት በፊት በሆስፒታል አብራው ትሰራ የነበረች የህጻናት ሀኪም ነች ትናንትና ደውላ ላገኝህ እፍልጋለው ያለችው፡፡ለዚህች ዶ/ር የስራ ባለደረባው ነበር…ያለፈውን አንድ አመት ተጨማሪ ትምህርት እድል አግኝታ ኖሩዌይ ነበር ያሳለፈችው፡፡አሁንም ለሁለት ሰምንት ረፍት እንደመጣች እና መመለሻዋ እንደደረሰ እናም ከመሄዶ በፊት አንድ እቃ ልትሰጠው እንደምትፈልግ ነግራው ነው እግረመንገዱን ሊያገኛት የወሰነው፡፡
ሀያ ሁለት ነበር ቀጠሮቸው…እሷም ቸኩላ ስነበረ ቀጥታ ወደጉዳዩ ነበር የገባችው፡፡አንድ የታጠፈ ነጭ ፖስታ አውጥታ እጁ ላይ አደረገች፡፡ግራ ገብቶትም ደንግጦም‹‹ምንድነው ሲል?››ጠየቃት፡፡
‹‹ትዝ ይልሀል ከመሄዴ በፊት አብረን የምንከታተላት አንድ ታማሚ ልጅ ነበረች…እናቷ ከአንተ ጋር ትግባባለች…እንደውም የልጅነት ጓደኛዬ ነበረች ብለሀኛል››
‹‹ኦኬ ትክክል ነሽ..ስለፀጋ ነው…ማለቴ የዛን ጊዜ ስሟ ትሁት ነበር..ስለእሷ ነው የምታወሪው››
‹‹አዎ ስለእሷ ነው…ለመሆኑ እንዴት ነች…?አሁንም በህይወት አለች?››
‹‹አዎ በጣም ጥሩ ሁኔታ ላይ ነች…ግን ፖስታው ምን እንደሆነ አልገባኝም››
‹‹ፖስታውማ እናትዬው እዛ ሆስፒታል ውስጥ ህጻኗን ጥላ ከመሄዶ በፊት ይህንን ፖስታ ለአንተ እንድሰጥ አደራ ብላ ሰጥታኝ ..ነበር….እርግጥ በወቅቱ ልጇን ጥላ እንደምትሄድ አልገመትኩም እና እሺ ብዬ ተቀበልኮት….ግን በዛው ሰሞን አንተም ለሆነ ስራ ወደክፍለሀገር ወጥተህ ነበር..እኔም ውጭ ለመሄድ በጣም እየተዋከብኩ ስለነበረ እቤቴ ወስጄ እንደቀልድ እንዳስቀመጥኩት እረሳሁት እና ሳልሰጥህ ሄድኩ ..በቀደም ነው የድሮ ወረቀቶቼን ሳስተካክል ድንገት አገኘሁት..አድራሻውን ሳነብ ትዝ አለኝ….መጀመሪያ አፍሬ እንደተረሳ ልተወው ነበር›..በኃላ ሳስበው ግን ምን አልባት በጣም አስፈላጊ ነገር ቢሆንስ ብዬ…አይኔን በጨው አጥቤ አግኝቼ ልሰጥህ ወሰንኩ….ይቅርታ እሺ››
‹‹አረ ችግር ለውም…ያው ልጄን አደራ..ተከታተላት ምናምን የሚል መልዕክት ነው የሚሆነው….ያንን ደግሞ እሷ ባትለኝም አደርገዋለው››በማለት ፖስታውን ኪሱ ውስጥ ከተተና ከእሷ ተሰናብቶ መኪናው ወደ እስካይ ላይት አዞረ፡፡
ከቀጠሯቸው 10 ደቂቃ ቀድሞ ነበር የደረሰው፡፡ ወንበር ይዞ በጉጉት ይጠብቃቸው ጀመር..፡፡ድንገት ፖስታው ትዝ አለው፡፡ አወጣና አየው…፡፡ከጀርባው ለማከበርህ ደ/ር ኤልያስ ከፅጌረዳ ይላል፡፡
እነ ራሄል እስኪመጡ ቀዶ ሊያነበው ፈለገ…መቅደድ ከመጀመሩ በፊት ፖስታውን ጠራጴዛው ላይ አስቀምጦ ስልኩን ከኪሱ አወጣና ተመለከተው…ራሄል ነች፡፡አነሳው፡፡
‹‹እሺ የእኔ ፍቅር››
‹‹ቀድመንህ ደርሰናል መሰለኝ››
‹‹አረ እንዴት ተደርጎ…››አለና ያለበትን ቦታ ነገራቸውና እስኪያዩት ቆሞ ጠበቃቸው…. ራሄልን ሲያያት ልቡ ትርክክ አለ….ወደፊት ተራምዶ ፀጋን ከእቅፏ ተቀበለና..ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳሙ…. ወደ ጠረጴዛቸው ሄደው ተቀመጡ….ምሳ ታዘዘ እና እስኪመጣ ሞቅ ያለጫወታ ጀመሩ…..ራሄል ድንገት ፊት ለፊቷ የተቀመጠ ፖስታ አየችና በመገረም አነሳችና አየችው…፡፡
‹‹ፅጌረዳ ማን ነች?››ኮስተርተር አለች፡፡
‹‹ቀናሽ እንዴ?››
‹‹በኢንተርኔት ዘመን ፖስታ በምትልክልህ ሴት እንዴት ብዬ ነው የምቀናው?››
‹‹በፖስታው አድራሻ ላይ የተጠቀሰችው ፅጌረዳ ማለት የፀጋ እናት እንደሆነችና ፖስታው ከተፃፈ ከአመት በኃላ እንዴት እንዳገኘው… በእንግሊዘኛ ነገራት››ይሄንን ያደረገው ፀጋ ፊት ስለእናቷ በምትሰማው ቋንቋ ለማውራት ስላልደፈረ ነው፡፡
‹‹እና..አልተከፈተም እኮ››
‹‹አዎ…አሁን ስለፀጋ እኔን ብቻ ሳይሆን አንቺንም ስለሚመለከት አብረን እናነበዋለን››
‹‹እርግጠኛ ነህ?››
‹‹ አዎ እርግጠኛ ነኝ››
‹‹እና እናንብበዋ››ብላ ልትቀደው ስትዘጋጅ፡፡
‹‹አይ …ይሄንን ጊዜያችንማ ለሌላ ጉዳይ አንጠቀምበትም…››ብሎ ፖስታውን ከእጇ ተቀበለና ከጎኗ ካለው ወንበር ላይ የተቀመጠው የራሷ ቦርሳ ውስጥ ከተተው፡፡
‹‹በቃ አንቺ ጋር ይሁንና ..ሰሞኑን አንድ ላይ ሆነን እናነበዋለን፡፡››ተስማማች…ምሳ ቀረበላቸው በሉ…ከዛ ወጥተው ወደአለም ሲኒማ ጎራ አሉና ፊልም አዩ….አሪፍና ጣፋጭ ቀን አሳለፉ….
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሁለት
፡
፡
#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
////
ዶ/ር ኤልያስ ዛሬ ምን አልባትም በህይወቱ ፍፁም የሆነ ደስታ የተሰደሰተበት ቀን ስለሆነ ስሜቱን መቆጣጠር አቅቷት ጥንቅቅ ብሎ ባለቀ ውብ ቤቱ ውስጥ ከክፍል ክፍል እየተመላለሰ እንደህፃን እየቧረቀ ነው፡፡ስልኩን አነሳና ደወለ…፡፡ከአራት ጥሪ በኃላ ተነሳ፡፡
‹‹ውድ ባለቤቴ እንዴት አለሽልኝ››
‹‹አንተ ያንን ቃል መጠቀም የምትችለው እኮ ሰማንያ ፈርመህ ቤትህ ስታስገባኝ ነው››አለችው እየሳቀች፡፡፡
‹‹ያው በይው..ዜናውን አልሰማሽም እንዴ…..?ሽማግሌዎቼ እኮ ወላጆችሽ ልጃቸውን ሊሰጡኝ በደስታ መስማማታቸውን አሁን ነግረውኝ በደስታ እያበድኩ ነው፡፡››
‹‹ከአንተ ቀድሜ ሰማሁ…ምነው ይከለክሉኛል ብለህ አስበህ ነበር እንዴ?››
‹‹እንዴ ምን ይታወቃል…..ምን አልባት ቅድሞ እደጅ እየጠና ያለ ብረት መዝጊያ አማች ኖሮ ሀሳባቸው ወደእሱ ቢያጋድልስ?››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው …ለአሁኑ ግን ተርፈሀል››
‹‹እኔም መትረፍ የምፈልገው ለአሁኑ ብቻ ነው…የማገባው አንዴ ብቻ እኮ ነው…››ተሳሳቁ፡፡
‹‹እና ይሄንን ደስታ አብረን ማክበር የለብንም ትያለሽ…?››
‹‹አንተ ..ከአሁን ወዲህ እኮ እስከሰርጌ ቀን ድረስ ልታየኝ አይገባም…››
‹‹እንደዛ ከሆነማ ሰርጉን ነገውኑ ደግስ በይኛ››
‹‹አዎ ..ያን ያህል ከቸኮልክ አድርገው››
‹‹እሺ..አስበብበታለው..እውነት ግን በጣም ላገኝሽ ፈልጌለሁ…››
እሷም ከአንደበቷ አውጥታ አትናረው እንጂ በጣም ልታገኘው ፈልጋለች፡፡‹‹ ይቻላል..የትና መቼ?፡፡››
‹‹ምሳ ልጋብዝሽ …ሰባት ሰዓት ስካይ ላይት እንገናኝ፡፡››
‹‹ሰባት ሰዓት ..አሁን እኮ አራት ተኩል ሆኖል…..ለመዘጋጃጀት በቂ ጊዜ አይኖረኝም፡፡››
‹‹አንቺ ደግሞ..እንደውም ምንም መዘገጃጀት አያስፈልግሽም… እዛ ሆስፒታል በነበርሽበት ጊዜ ያለምንም ዝግጅት ምን እንደምትመስዬ እኮ አውቃለው…ለእኔ ብለሽ ለመቆነጃጀት ከሁለት ሰዓት በላይ ማጥፋት የለብሽም…ከዛሬ ወዲህ ባልሽ ነኝ፡፡ማለቴ ለጊዜው እጮኛሽ ነኝ..ግን ለጥቂት ጊዜ ብቻ ነው፡፡››
‹‹‹ይሁንልህ እሺ…..ግን ቅር ካላለህ አንድነገር ልጠይቅህ ››
‹‹ምን ጠይቂኝ››
‹‹ጸጋን ይዣት ብመጣ ቅር ይልሀል?››
‹‹አረ በፍፅም ..እንደውም በተቃራኒው ደስ ነው የሚለኝ …እሷ ከመጀመሪያው ጀምሮ የፍቅራችን ብቸኛ ምስክር ነበረች..ዛሬ መገኘት ይገባታል….ጫጉላ ቀናችን ላይ አብራን ወደመኝታ ትግባ እንዳትይ እንጂ ለዛሬው ደስ ይለኛል››
ስለጫጉላ ሲያወራ እፍረትም ሙቀትም ተሰማት‹‹አንተ ምን እያልክ ነው..?በል ቸው››ብላ ስልኩን ዘጋች፡፡
እሱም ወዲያው ወደሻወር ቤት ገባና ሰውነቱን በፍጥነት ተለቃለቀ…ከዛ ፂሙን ላጨ…ሙሉ ሱፍ ለበሰና ዝንጥ አለ…፡፡ለመውጣት ዝግጁ ሆነ…፡፡ሰዓቱን ሲያይ 5 .ከሩብ ይላል….ከራሄልና ከፀጋ ጋር ወደሚገናኝበት ቀጠሮ ከመሄዱ በፊት ማግኘት የሚገባው አንድ ሰው አለ…ከአመት በፊት በሆስፒታል አብራው ትሰራ የነበረች የህጻናት ሀኪም ነች ትናንትና ደውላ ላገኝህ እፍልጋለው ያለችው፡፡ለዚህች ዶ/ር የስራ ባለደረባው ነበር…ያለፈውን አንድ አመት ተጨማሪ ትምህርት እድል አግኝታ ኖሩዌይ ነበር ያሳለፈችው፡፡አሁንም ለሁለት ሰምንት ረፍት እንደመጣች እና መመለሻዋ እንደደረሰ እናም ከመሄዶ በፊት አንድ እቃ ልትሰጠው እንደምትፈልግ ነግራው ነው እግረመንገዱን ሊያገኛት የወሰነው፡፡
ሀያ ሁለት ነበር ቀጠሮቸው…እሷም ቸኩላ ስነበረ ቀጥታ ወደጉዳዩ ነበር የገባችው፡፡አንድ የታጠፈ ነጭ ፖስታ አውጥታ እጁ ላይ አደረገች፡፡ግራ ገብቶትም ደንግጦም‹‹ምንድነው ሲል?››ጠየቃት፡፡
‹‹ትዝ ይልሀል ከመሄዴ በፊት አብረን የምንከታተላት አንድ ታማሚ ልጅ ነበረች…እናቷ ከአንተ ጋር ትግባባለች…እንደውም የልጅነት ጓደኛዬ ነበረች ብለሀኛል››
‹‹ኦኬ ትክክል ነሽ..ስለፀጋ ነው…ማለቴ የዛን ጊዜ ስሟ ትሁት ነበር..ስለእሷ ነው የምታወሪው››
‹‹አዎ ስለእሷ ነው…ለመሆኑ እንዴት ነች…?አሁንም በህይወት አለች?››
‹‹አዎ በጣም ጥሩ ሁኔታ ላይ ነች…ግን ፖስታው ምን እንደሆነ አልገባኝም››
‹‹ፖስታውማ እናትዬው እዛ ሆስፒታል ውስጥ ህጻኗን ጥላ ከመሄዶ በፊት ይህንን ፖስታ ለአንተ እንድሰጥ አደራ ብላ ሰጥታኝ ..ነበር….እርግጥ በወቅቱ ልጇን ጥላ እንደምትሄድ አልገመትኩም እና እሺ ብዬ ተቀበልኮት….ግን በዛው ሰሞን አንተም ለሆነ ስራ ወደክፍለሀገር ወጥተህ ነበር..እኔም ውጭ ለመሄድ በጣም እየተዋከብኩ ስለነበረ እቤቴ ወስጄ እንደቀልድ እንዳስቀመጥኩት እረሳሁት እና ሳልሰጥህ ሄድኩ ..በቀደም ነው የድሮ ወረቀቶቼን ሳስተካክል ድንገት አገኘሁት..አድራሻውን ሳነብ ትዝ አለኝ….መጀመሪያ አፍሬ እንደተረሳ ልተወው ነበር›..በኃላ ሳስበው ግን ምን አልባት በጣም አስፈላጊ ነገር ቢሆንስ ብዬ…አይኔን በጨው አጥቤ አግኝቼ ልሰጥህ ወሰንኩ….ይቅርታ እሺ››
‹‹አረ ችግር ለውም…ያው ልጄን አደራ..ተከታተላት ምናምን የሚል መልዕክት ነው የሚሆነው….ያንን ደግሞ እሷ ባትለኝም አደርገዋለው››በማለት ፖስታውን ኪሱ ውስጥ ከተተና ከእሷ ተሰናብቶ መኪናው ወደ እስካይ ላይት አዞረ፡፡
ከቀጠሯቸው 10 ደቂቃ ቀድሞ ነበር የደረሰው፡፡ ወንበር ይዞ በጉጉት ይጠብቃቸው ጀመር..፡፡ድንገት ፖስታው ትዝ አለው፡፡ አወጣና አየው…፡፡ከጀርባው ለማከበርህ ደ/ር ኤልያስ ከፅጌረዳ ይላል፡፡
እነ ራሄል እስኪመጡ ቀዶ ሊያነበው ፈለገ…መቅደድ ከመጀመሩ በፊት ፖስታውን ጠራጴዛው ላይ አስቀምጦ ስልኩን ከኪሱ አወጣና ተመለከተው…ራሄል ነች፡፡አነሳው፡፡
‹‹እሺ የእኔ ፍቅር››
‹‹ቀድመንህ ደርሰናል መሰለኝ››
‹‹አረ እንዴት ተደርጎ…››አለና ያለበትን ቦታ ነገራቸውና እስኪያዩት ቆሞ ጠበቃቸው…. ራሄልን ሲያያት ልቡ ትርክክ አለ….ወደፊት ተራምዶ ፀጋን ከእቅፏ ተቀበለና..ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳሙ…. ወደ ጠረጴዛቸው ሄደው ተቀመጡ….ምሳ ታዘዘ እና እስኪመጣ ሞቅ ያለጫወታ ጀመሩ…..ራሄል ድንገት ፊት ለፊቷ የተቀመጠ ፖስታ አየችና በመገረም አነሳችና አየችው…፡፡
‹‹ፅጌረዳ ማን ነች?››ኮስተርተር አለች፡፡
‹‹ቀናሽ እንዴ?››
‹‹በኢንተርኔት ዘመን ፖስታ በምትልክልህ ሴት እንዴት ብዬ ነው የምቀናው?››
‹‹በፖስታው አድራሻ ላይ የተጠቀሰችው ፅጌረዳ ማለት የፀጋ እናት እንደሆነችና ፖስታው ከተፃፈ ከአመት በኃላ እንዴት እንዳገኘው… በእንግሊዘኛ ነገራት››ይሄንን ያደረገው ፀጋ ፊት ስለእናቷ በምትሰማው ቋንቋ ለማውራት ስላልደፈረ ነው፡፡
‹‹እና..አልተከፈተም እኮ››
‹‹አዎ…አሁን ስለፀጋ እኔን ብቻ ሳይሆን አንቺንም ስለሚመለከት አብረን እናነበዋለን››
‹‹እርግጠኛ ነህ?››
‹‹ አዎ እርግጠኛ ነኝ››
‹‹እና እናንብበዋ››ብላ ልትቀደው ስትዘጋጅ፡፡
‹‹አይ …ይሄንን ጊዜያችንማ ለሌላ ጉዳይ አንጠቀምበትም…››ብሎ ፖስታውን ከእጇ ተቀበለና ከጎኗ ካለው ወንበር ላይ የተቀመጠው የራሷ ቦርሳ ውስጥ ከተተው፡፡
‹‹በቃ አንቺ ጋር ይሁንና ..ሰሞኑን አንድ ላይ ሆነን እናነበዋለን፡፡››ተስማማች…ምሳ ቀረበላቸው በሉ…ከዛ ወጥተው ወደአለም ሲኒማ ጎራ አሉና ፊልም አዩ….አሪፍና ጣፋጭ ቀን አሳለፉ….
❤41👍3👏1
ራሄል ደስ የሚል ቀን ብታሳልፍም ድክም ብሎታል…ገና ሁለት ሰዓት ሳይሆን ነው መተኛት እንደምትፈልግ ለወላጆቾ ተናግራና እነሱን ተሰናብታ ወደመኝታ ክፍሏ የገባቸው…የለሊት ልብሷን ቀይራ ለመተኛት አልጋዋ ላይ ከወጣች በኃላ ….የፀጋ እናት ፃፈች ተባለው ደብዳቤ ትዝ አላት….፡፡ለምን እንደሆነ ባታውቅም ውስጡ ያለውን ደብዳቤ ማንበብ ፈልጋለች….ግን ኤልያስ አብረን እናነበዋለን ነው ያለው..እራሷን ገሰጸች እና ተኛች፡፡እንቅልፍ ሊወስዳት ግን አልቻለችም…መልሳ ተነሳችና ከአልጋው ወርዳ ከቦርሳዋ ውስጥ ያለውን ፖስታ አወጣችና ወደአልጋዋ ተመለሰች….ቀደደችውና ውስጡ ያለውን ደብዳቤ አወጣችው…ማንበብ ጀመረች፡፡.
ኤሊ ይሄንን ደብዳቤ ለመጻፍ ለበርካታ ቀናት ከራሴ ጋር ስሟገት ነበር..ብዙ ቀን መፃፍ ጀምሬ ወረቀቱን ቀድጄ ጥያለው…በመጨረሻ ግን ለልጄ ስል ማድረግ እንዳለብኝ ውስጤ ስላመነ አድርጌዋለው፡፡
ኤሊ አንተ የልጅነት የሰፈር ጎደኛዬ ነህ…በጣም እወድሀለው…እርግጥ አውቃለው አንተም በጣም ትወደኛለህ..የእኔ ግን ከዛ ያለፈ ነው..አፈቅርህ ነበር…ሀይስኩል እያለን ህልሜ ወደፊት አንተን ማግባት ነበር…ከአንተ ልጅ መውለድ ነበር…አውቃለው ለአንተ ጓደኛህ ብቻ ነኝ….በእኔ ልብ ውስጥ ያለው መዝሙር ግን ሌላ ነበር….እና ምን ሆነ አንተ አሪፍ ውጤት አምጥተህ ዩኒቨርሲቲ ስትገባ እኔ ወድቄ ሰፈር ቀረሁ..እንደዛም ሆኖ በአንተ ደስተኛ ነበርኩ…እሱ ለሁለታችንም ይበቃል አልኩ…በአንተ ዲግሪ እኔ የራሴን ወደፊት ኑሮ አቀድኩ….ከአንተ ጋር የምሰራውን ቤት አለምኩ…ግን ህይወት ወራጅ ወንዝ ብቻ ሳትሆን ደራሽ ጎርፍ ጭምር ነችና…ሳላስበው ካልሆኑ ልጆች ጋር ገጠምኩ..ድህነቴና የቤተሰቦቼ የገንዘብ አቅም ደካማነት አንዳንድ ያልሆኑ ስራዎችን እንድሰራ አስገደደኝ..
አንተ ዶክተር ሆነህ ተመርቀህ ስትመጣ እኔ የሶስት አመት የሽርሙጥና ልምድ ነበረኝ..ያ ደግሞ በድብቅ ሳደርገው የቆየሁት ሳይሆን ሀገር ዘመድ ያንተም ቤተሰቦች ጭምር የሚያውቁት መራር ሀቅ ነበር፡፡እና በዛ ቆይታ ስለአንተ ያለኝን ህልም ገድዬው ነበር….እና ተመርቀህ መጣህ…በጣም ደስ አለኝ..የቁጭት እንባ አለቀስኩ…፡፡ አረሳሀኝም..አልተጠየፍከኝም…ቤታችሁ በተዘጋጀ የምረቃት ዝግጅት ላይ አፈላልገህ የምሰራበት ብና-ቤት ድረስ መጥተህ ጋበዝከኝ፡፡ለአንተ ስል የሰፈር ሰዎችን አይን ..ችዬ የቤተሰቦችህን ምን ይሉኛል እያልኩ እየተሸማቀቅኩ መጣሁ..ጥሩና ደስ የሚል ዝግጅት ነበር፡፡
ራሄል የምታነበውን ነገር ማመን አልቻለችም…..በጣም አጎጊና አስፈሪ ሆነባት….ማንበቧን ቀጠለች፡፡
…ከዛ መደዋወል አልፎ አልፎ መገናኘትም ጀመርን፡፡ትዝ ይልሀል ስራ ከያዝክ ከሁለት አመት በኃላ ሚዜ የሆንክበት የዶ/ር ሰለሞን ሰርግ ላይ ጋበዝከኝ….ደስ አለኝና መጣሁ…አሪፍ ሰርግ ነበር..አንተም በጣም ደስ ብሎህ ነበር…ያለወትሮህ በጣም ጥተህ ነበር… እኩለ ሊሊት ላይ ከሰርጉ ቤት ደግፌህ ተያይዘን ወጣን…ሆቴል አልጋ ያዝኩልህና እንድታርፍ አድርጌ ወደቤቴ ልሄድ ስል ትንሽ አጣጪን አልከኝ..ተው ይበቃሀል ብልህም አልሰማሀኝም..እንደውም ሶፋ ላይ ተኛለው አንቺ አልጋው ላይ ትተኚያለሽ…በለሊት ወዴትም አትሄጂም አልከኝ፡፡ከዛ ተስማማውና እዛው እልጋ ክፍል ውስጥ መጠጥ አዘን መጠጣት ጀመርን…ፈርቼ ነበር…ለእኔ ሳይሆን ለአንተ ነበር የፈራሁት…ከዛ እንዴት እንደሆነ አላውቅም መሳሳም ጀመርን… ሁሉም ነገር ሆነ …ካዛ በኃላ ነፍስህን አታውቅም ነበር…በውድቅት ለሊት ቁጭ ብዬ አሰብኩ…ጥዋት የተፈጠረውን ስታውቅ በጣም እንደምትበሳጭ አሰብኩ..ሁለተኛ ስሬ እንዳትደርሺ እንደምትለኝ እርግጠኛ ሆንኩ…ሳልመው የኖርኩትን ፍቅርህን ማግኘት ባልችልም ጓደኛነትህን ማጣት እንደሌለብኝ ወሰንኩ፡፡
ሁሉን ነገር አፀዳደው..ያወለቅከውን ፓንትና ሱሪህን በየተራ እንደምንም ብዬ መልሼ አደረኩልህ…ቀበቶህን ሳይቀር አሰርኩልህ፡፡ከዛ በስነ-ስርአት አልጋው ላይ አስተኛውህ… የራሴንም ልብስ ሙሉ በሙሉ ለብሼ አልጋ ልብሱን ተከናንቤ ሶፋ ላይ በመተኛት ስጨነቅና ስፀልይ ነጋ….ጥዋት ስትነቃ አይን አይንህን ሳይ ነበር…እግዜር የተመሰገነ ይሁን አንተ ምን እንደተፈጠረ አላወቅክም..ምንም የተቀየረ ነገር አልነበረም..ከዛ ጓደኝነታችን እንደነበረ ቀጠለ፡፡ደስ አለኝ…ከሁለት ወር በኃላ ሌላ መዘዝ መጣብኝ ..ማርገዜን አወቅኩ..ምን ላድርግ ..ከአንተ ጋር መተኛት ለአንት ማርገዝ ለእኔ የልጅነት ህልሜ ነበር እናም መደስት ነበረብኝ..ግን በዚህ አይነት ሁኔታ ላይ እያለው የሚሆን እንዳልሆነ አውቃለው…አንተ ለእኔ አዝነህ ልጅቷን ብትቀበል እንኳን ወላጆችህ ምን ይሉሀል….?ቤተሰቦችህ ምን ያህል ሀይማኖተኛ እና የተከበሩ ሰዎች እንደሆኑ አውቃለው..በአንተ ምን ያህል እንደሚኮሩብህ በደንብ አውቃለው…እና አንተ በማታውቀው ጉዳይ እንዴት እንዲያዝኑብህ ላድርግ…?ወሰንኩ…ትሁትን ላስወርዳት ወሰንኩ፡፡ብዙ መድሀኒት ተጋትኩ..እሷ ግን ጠንካራ ታጋይ ነበረች..አልወጣም አለች…በመጨረሻ የራሱ ጉዳይ ብዬ ተውኳት.. ተወለደች.. በእርግዝናዬ ወቅትም ሆነ ከወለድኩ በኃላ ከጎኔ ነበርክ…አባቷን ብዙ ጊዜ ጠይቀሀኝ ዋሽቼህ ነበር…እና እስከመጨረሻውም ላልነግርህ ነበር እቅዴ፡፡ ግን…ከስድስተ ወሯት በኃላ ታመመች… ሙሉ በሙሉ ሆስፒታል ገባች…ሳያት ህመሟ ቀጣይነት ያለውና ምናልባትም የእድሜ ልኳ እንደሆነ ተረዳው…እኔ ጋር ብትሆን ምን ላደርግላት እችላለው? ..እንዴት ልንከባከባትና እንዴት ላሳክማት እችላለሁ..?አሰብኩ..ከዛ ለአንተ እወነቱን ለመናገር ወሰንኩ፣ግን ያው ፊት ለፊትህ ተቀምጬ አይኖችህን እያየው ይሄንን ዜና ልነግርህ አልችልም..ያለኝ ምርጫ ይሄንን ደብዳቤ ፅፌ እኔ ከአካባቢው ከተሰወርኩ በኃላ እንዲደርስህ ማድረግ ነው፡፡
አንተ የትሁት አባት ነህ…ከፈለክ ዲ.ኤን.ኤ ማስመርመር ትችልህ..እኔ ማንም ሊያገኘኝ ወደማይችለው ቦታ ሄጄያለው ..ማለት ከሀገር ውጭ ነው ሄድኩት..መቼም አልመለስም….ልጅህን ወላጆችህን በሆነ መንገድ አሳምነህ ለእነሱ ብትሰጣቸው ደስ ይለኛል..እነሱ ልጅን ለማሳደግ ፍላጎቱም ፍቅሩም፣፣ ብሩም አላቸው…ብቻ የራስህ ልጅ ነች…በፈለከው መንገድ አሳድጋት፡፡
ጽጌረዳ ነኝ…..እስከመጨረሻው ደህና ሁንልኝ፡፡
ራሄል ወረቀቱን ጨመደደች ከእሷ አርቃ ወረወረችው….ከአልጋዋ ወረደችና የወለል ምንጣፉ ላይ እየተንከባለለች እስኪደክማት አለቀሰች…‹‹እሺ አሁን ምድነው የማደርገው?››እራሷን ጠየቀች፡፡‹‹‹ኤልያስ ይሄ ደብዳቤ ሲደርሰው ምንድነው የሚሆነው?››የዚህን መልስ መገመት አልቻለችም፡፡ለመረጋጋት እና ወደአልጋዋ ለመመለስ ከሁለት ሰዓት በላይ ነው የወሰደባት፡፡ ካዛ እስከንጊቱ አስራ አንድ ሰዓት ድረስ ስትገለባበጥና ስታስብ ነበር ያሰበችው፡፡ መጨረሻ የነገሩን ጥሩ ጎን ማየት ቻለች..በተለይ ለፀጋ አባት ማግኘቷ ደስ አላት..ኤልያስ አባቷ ሆነ ማለት ደግሞ እሷም እናቷ ሆነች ማለት ነው፡፡ይሄን ስታስብ ውስጧ ደስ ሚል ስሜት ወረራት፡፡
ግን ኤልያስስ ዜናውን በእንደዚህ አይነት መንገድ ይቀበለዋል…በእፍረት አንገቱን ደፍቶ ቢጠፋባትስ …?‹‹አልመጥንሽም…ጋብቻው ይቅር ቢላትስ?››ስቅጥጥ አላት..ደግሞ ኤልያስ ምን ያህል ስሜታዊ ሰው እንደሆነ ስለምታውቅ አያደርገውም ብላ በእርግጠኝነት ልትተማመንበት አልቻለችም…እና አንድ ውሳኔ ወሰነች፡፡
ኤሊ ይሄንን ደብዳቤ ለመጻፍ ለበርካታ ቀናት ከራሴ ጋር ስሟገት ነበር..ብዙ ቀን መፃፍ ጀምሬ ወረቀቱን ቀድጄ ጥያለው…በመጨረሻ ግን ለልጄ ስል ማድረግ እንዳለብኝ ውስጤ ስላመነ አድርጌዋለው፡፡
ኤሊ አንተ የልጅነት የሰፈር ጎደኛዬ ነህ…በጣም እወድሀለው…እርግጥ አውቃለው አንተም በጣም ትወደኛለህ..የእኔ ግን ከዛ ያለፈ ነው..አፈቅርህ ነበር…ሀይስኩል እያለን ህልሜ ወደፊት አንተን ማግባት ነበር…ከአንተ ልጅ መውለድ ነበር…አውቃለው ለአንተ ጓደኛህ ብቻ ነኝ….በእኔ ልብ ውስጥ ያለው መዝሙር ግን ሌላ ነበር….እና ምን ሆነ አንተ አሪፍ ውጤት አምጥተህ ዩኒቨርሲቲ ስትገባ እኔ ወድቄ ሰፈር ቀረሁ..እንደዛም ሆኖ በአንተ ደስተኛ ነበርኩ…እሱ ለሁለታችንም ይበቃል አልኩ…በአንተ ዲግሪ እኔ የራሴን ወደፊት ኑሮ አቀድኩ….ከአንተ ጋር የምሰራውን ቤት አለምኩ…ግን ህይወት ወራጅ ወንዝ ብቻ ሳትሆን ደራሽ ጎርፍ ጭምር ነችና…ሳላስበው ካልሆኑ ልጆች ጋር ገጠምኩ..ድህነቴና የቤተሰቦቼ የገንዘብ አቅም ደካማነት አንዳንድ ያልሆኑ ስራዎችን እንድሰራ አስገደደኝ..
አንተ ዶክተር ሆነህ ተመርቀህ ስትመጣ እኔ የሶስት አመት የሽርሙጥና ልምድ ነበረኝ..ያ ደግሞ በድብቅ ሳደርገው የቆየሁት ሳይሆን ሀገር ዘመድ ያንተም ቤተሰቦች ጭምር የሚያውቁት መራር ሀቅ ነበር፡፡እና በዛ ቆይታ ስለአንተ ያለኝን ህልም ገድዬው ነበር….እና ተመርቀህ መጣህ…በጣም ደስ አለኝ..የቁጭት እንባ አለቀስኩ…፡፡ አረሳሀኝም..አልተጠየፍከኝም…ቤታችሁ በተዘጋጀ የምረቃት ዝግጅት ላይ አፈላልገህ የምሰራበት ብና-ቤት ድረስ መጥተህ ጋበዝከኝ፡፡ለአንተ ስል የሰፈር ሰዎችን አይን ..ችዬ የቤተሰቦችህን ምን ይሉኛል እያልኩ እየተሸማቀቅኩ መጣሁ..ጥሩና ደስ የሚል ዝግጅት ነበር፡፡
ራሄል የምታነበውን ነገር ማመን አልቻለችም…..በጣም አጎጊና አስፈሪ ሆነባት….ማንበቧን ቀጠለች፡፡
…ከዛ መደዋወል አልፎ አልፎ መገናኘትም ጀመርን፡፡ትዝ ይልሀል ስራ ከያዝክ ከሁለት አመት በኃላ ሚዜ የሆንክበት የዶ/ር ሰለሞን ሰርግ ላይ ጋበዝከኝ….ደስ አለኝና መጣሁ…አሪፍ ሰርግ ነበር..አንተም በጣም ደስ ብሎህ ነበር…ያለወትሮህ በጣም ጥተህ ነበር… እኩለ ሊሊት ላይ ከሰርጉ ቤት ደግፌህ ተያይዘን ወጣን…ሆቴል አልጋ ያዝኩልህና እንድታርፍ አድርጌ ወደቤቴ ልሄድ ስል ትንሽ አጣጪን አልከኝ..ተው ይበቃሀል ብልህም አልሰማሀኝም..እንደውም ሶፋ ላይ ተኛለው አንቺ አልጋው ላይ ትተኚያለሽ…በለሊት ወዴትም አትሄጂም አልከኝ፡፡ከዛ ተስማማውና እዛው እልጋ ክፍል ውስጥ መጠጥ አዘን መጠጣት ጀመርን…ፈርቼ ነበር…ለእኔ ሳይሆን ለአንተ ነበር የፈራሁት…ከዛ እንዴት እንደሆነ አላውቅም መሳሳም ጀመርን… ሁሉም ነገር ሆነ …ካዛ በኃላ ነፍስህን አታውቅም ነበር…በውድቅት ለሊት ቁጭ ብዬ አሰብኩ…ጥዋት የተፈጠረውን ስታውቅ በጣም እንደምትበሳጭ አሰብኩ..ሁለተኛ ስሬ እንዳትደርሺ እንደምትለኝ እርግጠኛ ሆንኩ…ሳልመው የኖርኩትን ፍቅርህን ማግኘት ባልችልም ጓደኛነትህን ማጣት እንደሌለብኝ ወሰንኩ፡፡
ሁሉን ነገር አፀዳደው..ያወለቅከውን ፓንትና ሱሪህን በየተራ እንደምንም ብዬ መልሼ አደረኩልህ…ቀበቶህን ሳይቀር አሰርኩልህ፡፡ከዛ በስነ-ስርአት አልጋው ላይ አስተኛውህ… የራሴንም ልብስ ሙሉ በሙሉ ለብሼ አልጋ ልብሱን ተከናንቤ ሶፋ ላይ በመተኛት ስጨነቅና ስፀልይ ነጋ….ጥዋት ስትነቃ አይን አይንህን ሳይ ነበር…እግዜር የተመሰገነ ይሁን አንተ ምን እንደተፈጠረ አላወቅክም..ምንም የተቀየረ ነገር አልነበረም..ከዛ ጓደኝነታችን እንደነበረ ቀጠለ፡፡ደስ አለኝ…ከሁለት ወር በኃላ ሌላ መዘዝ መጣብኝ ..ማርገዜን አወቅኩ..ምን ላድርግ ..ከአንተ ጋር መተኛት ለአንት ማርገዝ ለእኔ የልጅነት ህልሜ ነበር እናም መደስት ነበረብኝ..ግን በዚህ አይነት ሁኔታ ላይ እያለው የሚሆን እንዳልሆነ አውቃለው…አንተ ለእኔ አዝነህ ልጅቷን ብትቀበል እንኳን ወላጆችህ ምን ይሉሀል….?ቤተሰቦችህ ምን ያህል ሀይማኖተኛ እና የተከበሩ ሰዎች እንደሆኑ አውቃለው..በአንተ ምን ያህል እንደሚኮሩብህ በደንብ አውቃለው…እና አንተ በማታውቀው ጉዳይ እንዴት እንዲያዝኑብህ ላድርግ…?ወሰንኩ…ትሁትን ላስወርዳት ወሰንኩ፡፡ብዙ መድሀኒት ተጋትኩ..እሷ ግን ጠንካራ ታጋይ ነበረች..አልወጣም አለች…በመጨረሻ የራሱ ጉዳይ ብዬ ተውኳት.. ተወለደች.. በእርግዝናዬ ወቅትም ሆነ ከወለድኩ በኃላ ከጎኔ ነበርክ…አባቷን ብዙ ጊዜ ጠይቀሀኝ ዋሽቼህ ነበር…እና እስከመጨረሻውም ላልነግርህ ነበር እቅዴ፡፡ ግን…ከስድስተ ወሯት በኃላ ታመመች… ሙሉ በሙሉ ሆስፒታል ገባች…ሳያት ህመሟ ቀጣይነት ያለውና ምናልባትም የእድሜ ልኳ እንደሆነ ተረዳው…እኔ ጋር ብትሆን ምን ላደርግላት እችላለው? ..እንዴት ልንከባከባትና እንዴት ላሳክማት እችላለሁ..?አሰብኩ..ከዛ ለአንተ እወነቱን ለመናገር ወሰንኩ፣ግን ያው ፊት ለፊትህ ተቀምጬ አይኖችህን እያየው ይሄንን ዜና ልነግርህ አልችልም..ያለኝ ምርጫ ይሄንን ደብዳቤ ፅፌ እኔ ከአካባቢው ከተሰወርኩ በኃላ እንዲደርስህ ማድረግ ነው፡፡
አንተ የትሁት አባት ነህ…ከፈለክ ዲ.ኤን.ኤ ማስመርመር ትችልህ..እኔ ማንም ሊያገኘኝ ወደማይችለው ቦታ ሄጄያለው ..ማለት ከሀገር ውጭ ነው ሄድኩት..መቼም አልመለስም….ልጅህን ወላጆችህን በሆነ መንገድ አሳምነህ ለእነሱ ብትሰጣቸው ደስ ይለኛል..እነሱ ልጅን ለማሳደግ ፍላጎቱም ፍቅሩም፣፣ ብሩም አላቸው…ብቻ የራስህ ልጅ ነች…በፈለከው መንገድ አሳድጋት፡፡
ጽጌረዳ ነኝ…..እስከመጨረሻው ደህና ሁንልኝ፡፡
ራሄል ወረቀቱን ጨመደደች ከእሷ አርቃ ወረወረችው….ከአልጋዋ ወረደችና የወለል ምንጣፉ ላይ እየተንከባለለች እስኪደክማት አለቀሰች…‹‹እሺ አሁን ምድነው የማደርገው?››እራሷን ጠየቀች፡፡‹‹‹ኤልያስ ይሄ ደብዳቤ ሲደርሰው ምንድነው የሚሆነው?››የዚህን መልስ መገመት አልቻለችም፡፡ለመረጋጋት እና ወደአልጋዋ ለመመለስ ከሁለት ሰዓት በላይ ነው የወሰደባት፡፡ ካዛ እስከንጊቱ አስራ አንድ ሰዓት ድረስ ስትገለባበጥና ስታስብ ነበር ያሰበችው፡፡ መጨረሻ የነገሩን ጥሩ ጎን ማየት ቻለች..በተለይ ለፀጋ አባት ማግኘቷ ደስ አላት..ኤልያስ አባቷ ሆነ ማለት ደግሞ እሷም እናቷ ሆነች ማለት ነው፡፡ይሄን ስታስብ ውስጧ ደስ ሚል ስሜት ወረራት፡፡
ግን ኤልያስስ ዜናውን በእንደዚህ አይነት መንገድ ይቀበለዋል…በእፍረት አንገቱን ደፍቶ ቢጠፋባትስ …?‹‹አልመጥንሽም…ጋብቻው ይቅር ቢላትስ?››ስቅጥጥ አላት..ደግሞ ኤልያስ ምን ያህል ስሜታዊ ሰው እንደሆነ ስለምታውቅ አያደርገውም ብላ በእርግጠኝነት ልትተማመንበት አልቻለችም…እና አንድ ውሳኔ ወሰነች፡፡
❤39
አንደኛ ሰርጋቸውን ከሁለት ወር ባነሰ ጊዜ እንዲደረግ ማድረግ፡፡ሁለተኛ ደግሞ ሰርጋቸው ተደግሶ ባል እና ሚስት ተብለው አንድ ቤት ተጠቃለው እስኪገቡ ድረስ ይሄንን ፀጋ ልጁ እንደሆነች የሚገልፀውን ደብዳቤ እንዳያገኘው ማድረግ፡፡
እነዚህን ውሳኔዎች ከወሰነች በኃላ ነው የተወሰነ መረጋጋት ስለተሰማት እንቅልፍ የወሰዳት፡፡
✨ተፈፀመ✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እነዚህን ውሳኔዎች ከወሰነች በኃላ ነው የተወሰነ መረጋጋት ስለተሰማት እንቅልፍ የወሰዳት፡፡
✨ተፈፀመ✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤35👍10🤔5
#የፀሎት_ፉክክር ፩
.
ለረጅም ዘመናት
እግዚአብሔር ይስጥልኝ እየተባለበት፤
በእያንዳንዱ ሠው አፍ እግዜር ዕዳ አለበት፤
እያሉ ሠምቼ
ይኸው መጥቻለሁ
እሱ ይስጥህ እያሉ ሲልኩኝ ወዳንተ፤
በል እግዜር መፅውተኝ
ምሰፍርበት አጣሁ
ምድሩን ዘር ዘርተውት
እንኳን ለኔ ቀርቶ ቦታ የለም ላንተ፤
.
ብዛ ተባዛባት
ምድሪቱንም ሙላት ብለህ ስትልከኝ፤
ምን አስበህ ይሆን?
እንደሚታነቅ ሰው ባዶ ኪስ የላክከኝ?፤
.
ፍቃድ ትዕዛዝህን
ላከብር ልበዛ ኑሮ ልጀምር ስል፤
እንዳልከው አልሆነም
አብስትራክት ሆኗል የዚህች ምድር ምስል፤
.
ፈጣሪ ሆይ ፍረድ!
በደላቸው በዛ ትዕግስትህን አይተው፤
የገዛ መሬትህን
እየሸጡልኝ ነው በስንዝር ለክተው፤
.
ወይ ምድርህን ስጠኝ
ወይ ስንዝሩን ቀማ፤
መሬቴን ብቻ ሆኗል
የዚህች ምድር ዜማ፤
እኔ አላማረኝም
መሬትህን ውሰድ በሠው ሳትቀማ፤
🔘ልዑል ሐይሌ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
.
ለረጅም ዘመናት
እግዚአብሔር ይስጥልኝ እየተባለበት፤
በእያንዳንዱ ሠው አፍ እግዜር ዕዳ አለበት፤
እያሉ ሠምቼ
ይኸው መጥቻለሁ
እሱ ይስጥህ እያሉ ሲልኩኝ ወዳንተ፤
በል እግዜር መፅውተኝ
ምሰፍርበት አጣሁ
ምድሩን ዘር ዘርተውት
እንኳን ለኔ ቀርቶ ቦታ የለም ላንተ፤
.
ብዛ ተባዛባት
ምድሪቱንም ሙላት ብለህ ስትልከኝ፤
ምን አስበህ ይሆን?
እንደሚታነቅ ሰው ባዶ ኪስ የላክከኝ?፤
.
ፍቃድ ትዕዛዝህን
ላከብር ልበዛ ኑሮ ልጀምር ስል፤
እንዳልከው አልሆነም
አብስትራክት ሆኗል የዚህች ምድር ምስል፤
.
ፈጣሪ ሆይ ፍረድ!
በደላቸው በዛ ትዕግስትህን አይተው፤
የገዛ መሬትህን
እየሸጡልኝ ነው በስንዝር ለክተው፤
.
ወይ ምድርህን ስጠኝ
ወይ ስንዝሩን ቀማ፤
መሬቴን ብቻ ሆኗል
የዚህች ምድር ዜማ፤
እኔ አላማረኝም
መሬትህን ውሰድ በሠው ሳትቀማ፤
🔘ልዑል ሐይሌ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍21❤10
#እናትነት
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//////
የእኔ ቅንዝርነት የልጅቷ ድህነት፤እናትነት እና ተስፋ ቢስነት
ስሟ ግን ማን ነበር?
ምን አይነት ችግር ላይ እንዳለሁ ልትገምቱ አትችሉም፡፡ ሀገር አማን ነው ብዬ በእንቅልፍ ዓለም ከተዋጥኩ በኋላ በእኩለ ለሊት ላይ ለመንገድ መብራት ማቆሚያ እደተተከለ የእንጨት ምሰሶ ቀጥ ይላል፡፡ ቀጥ ማለቱ ብቻ አይደለም እኮ የሚያበሳጨኝ ቀጥ በማለቱ ውስጥ ጥዝጣዜ ነገር አለው፡፡ የመነዝነዝ ዓይነት እና ለመግለፅ የሚያስቸግር ግራ አጋቢ ህመም ከእቅልፍ እስከማባበነን ድረስ የሚደርስ ኃይል ያለው ህመም ፡፡እስከአሁን ስለምን እንደማወራችሁ አልገባችሁም አይደል?
እንጠራራ እና ከእንቅልፌ ጋር እየታገልኩ ዓይኔን እያሻሸው በዳበሳ ወደ ሽንት ቤት ሄዳለው… ምን አልባት ሽንቴ ወጥሮኝ እንደሆነ ብዬ…ግን ብጨምቀው ባልበው ጠብ አይለኝም ፡፡
በንጭንጭ ወደ አልጋዬ እመለስና እያተገላበጥኩ እንቅልፍ እስኪያሸንፈኝ እሰቃያለው፡፡ከሰዓታት በኃላ እንደምንም እንቅልፍ ያሸንፈኛል፡፡ሊነጋጋ ሲል መለልሶ ይቀሰቅሰኛል፡፡የዚህኛውን ጊዜ እንኳን ፊት አልሰጠውም …ከነ ተረቱ ‹ የጥዋት ቁ› ይባል የለ …ሽንት እንዲወጠር እድርጎት ይሆን ትክክለኛ አምሮት ይሁን መለየት አይቻልም…ሀሰተኛ መሲ ነገር ነው፡፡
ይሄ ነገር እየተደጋገመ ሲያስቸግረኝ ህልሜን ሁሉ የከተማዋ ቆነጃጅቶች እና በአካልም በምናብም የማውቃቸው ሴቶች ሲሞሉት የሆነ ነገር ማድረግ እንዳለብኝ ወሰንኩ…፡፡ በእኔ ምክር ሳይሆን በተፈጥሮ ህግ የሚመራውን ቅንዝሬን የሆነ ዘዴ ፈጥሬ ማቀዝቀዝ አለብኝ..ስለዚህ ግዢ ልወጣ ወሰንኩ፡፡
ሰፈሩን ባልነግራችሁም …ለግዢ ምቹ ናቸው ሲባሉ ከሰማዋቸው የከተማዋ ጉድ ሰፈሮች መካከል ወደ አንዱ ነው የሄድኩት…ቺቺኒያ አይተንሀል አላችሁኝ…..?ምን አልባት እኔን የመሰለ ሰው አይታችሁ ይሆናል እንጂ እኔ ወደ እዛ ሰፈር ዝር አላልኩም…ደግሞስ እናንተ ራሳችሁ እዛ ሰፈር ምን ስትሰሩ ነበር? ለማንኛውም ያልኳችሁ ቦታ ሄድኩ …ቀድሜ አልጋ ተከራየው….
ከዛ ወደ ቡና ቤቶቹ ወይም ወደ ጭፈራ ቤቶቹ አልነበረም ጎራ ያልኩት፡፡ ከምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ወደ ጎዳናው ነው የወጣሁት…፡፡ከቤት ውስጥ ግዢ የውጩን ለምን እንደመረጥኩ አልገባኝም…. ብቻ ስሜቴ ወደ እዛ ነው የገፋኝ ፡፡ዞሬ ለመምረጥ… መርጬ ለማነጋገር እና ለመስማማት..ተስማምቶም ይዞ ለመሄድ ..አንድ ሰዓት ገደማ ፈጀብኝ፡፡
ልጅቷ የተከራየሁት ቤርጎ ገብታ አልጋው ጠርዝ ላይ እንደተቀመጠች ፊቷን ለማንበብ ሞከርኩ..፡፡ፊቷ ሜካፕ የነከካው ቢሆንም በስርዓቱ አልተዳረሰም… የሆነ መዝረክረክ ይታይበታል፡፡ከቀይ ዳማ መልክ ወደ ግራጫ የተቀየረ የፊት ቀለም ይታየኛል..፡፡የዓይኖቾ ቅንድቦች ቀና ማለት ደክሟቸው መሰለኝ ተደፍተዋል፡፡ጉንጮቾ ወደ ውስጥ ስርጉድ ብለው በረሀ ላይ ውሃ እንዲወጣባቸው የተቆፈሩ ጉድጓዶች ነው የሚመስሉት ...፡፡ከንፈሮቾ ቁርፍድፍድ ብለው የመሰነጣጠቅ ምልክት ይታይባቸዋል፡፡ግን በተቀባችው ቀይ ሊፒስቲክ ልትሸፍነው ሞክራለች፡፡ውጭ ከመብራቱ ፖል አቅራቢያ ከሚገኝ ግንብ አጥር ጋር ተጣብቃ ግማሽ ብርሀን እና ግማሽ ጨለማ ከቧት ሳነጋግራት ይሄ ሁሉ አሁን የዘረዘርኩላችሁን የመልኳ ሁኔታ አልተገለፀልኝ ነበር.፡፡አቋሟን እና የፊቷን ቅርጽ በከፊል ነበር የገመገምኩት….፡፡ገምግሜም አስፓልቱ ላይ ከተኰለኰሉት መሀከል እሷን የመረጥኳት…መርጬም ያነጋገርኳት …አነጋሬም የተሰመመማነው… ተስማምተን ወደ ተከራየውት ቤርጎ ይዤት የገባሁት፡፡
አሁን ..ከገባችና በመጠኑም ፈንጠር ብላ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጣ ሳስተውላት ግን አሁን ከላይ እንደዘረዘርኩላችሁ የተለየች ሆና ነው ያገኘኋት፡፡ ገና ያልበሰለች የ16 ዓመት አካባቢ ጨቅላ ወጣት ነች ፡፡ቢሆንም ውስጧ የ60 ዓመት …የጎበጠች እና የጨረጨሰች አሮጊት በእሷነቷ ውስጥ ተደብቃ ትታያለች፡፡ ወጣትነቷ በፍጥነት ወደ መጠውለግ ሲንደረደር ይታያል፡፡
‹‹ተጫወቺ እንጂ …ምነው ከእኔ ጋር ማደሩ ደስ አላለሽም እንዴ? ››አልኳት፡፡
ፊቷን እንዳጨማደደች አላስፈላጊ ጥያቄ እንደጠየቀ ሰው በግርምት እያየችኝ
‹‹መደሰት እና አለመደሰት እዚህ ጋር ምን አመጣው›ስትል መለሰችልኝ፡፡
‹‹አልገባኝም››
‹‹እንዴት አይገባህም..እኔ ገንዘብህን ነው የምፈልገው፡፡ ከፍለኸኛል….ከከፈልከኝ ደግሞ ደስ አለኝም አላለኝም አብሬህ ማደር ግዴታዬ ነው››አለችኝ እና ልብሶቾን ማወላለቅ ጀመረች፡፡
እኔም አወላለቅኩና ተከተልኳት..ተያይዘን አንድ አንሶላና ፍራሽ ከስር..አንድ አንሶላና ብርድ ልብስ ከላይ አድርገን ከመሀከል ገባን…፡፡
‹‹እዛ ባዶ ቤት ብቻውን በነበረበት ሰዓት ዘራፍ እያለ እረፍት ይነሳኝ የነበረው አጅሬን‹‹ አሁን እስቲ ጉዱህን እየዋለው….ሜዳውም ፈረሱንም ያው አመቻችቼለታለው… ›› አልኩት.፡፡
ግን ለእኔም ሆነ ለአጅሬው እንደአሰብነውና እደጓጓነው የሆነልን አይመስለኝም ….የሆነ ደስ የማይል ስሜት እየተሰማኝ ነው…እሱም አንዴ ቀጥ ከዛ መልሶ እንደመልፈስፈስ እያለ ፈራ ተባ ውስጥ ገብቷል፡፡ወደ እሷ ፊቴን አዞርኩና እጄን ትከሻዋ ላይ ጣል አደረግኩ..ስጠጋት ከሰውነቷ የሚረጨው ጠረን ተምዘግዝጎ ወደ አፍንጫዬ ሲገባ ደስ የማይል ስሜት ነው የተሰማኝ..እርግጥ ከለበሰችው ልብስ አልፎ ሰውነቷ ላይ የቀረ የሽቶ ሽታ አለ ..፡፡ግን ከሽቶው ተደባልቆ ና ተዋህዶ የሚበተን ሌላ ጠረን አለ..ምንነቱን ልለየው ያልቻልኩት ትንሽ የሚረብሽ ጠረን….፡፡
እንደዛም ሆኖ በደንብ ተጠጋኋት ..ሰውነቴን ከሰውነቷ አጣበቅኩ…እዳብሳት እና አሻሻት ጀመርኩ፡፡..ቀስ በቀስ ሰውነቴ እየጋለ እየሞቀ ቢመጣም ከእሷ ወደ እኔ እየተላለፈ ያለ ምንም አይነት ሙቀት ሊሰማኝ አልቻለም…. አሁንም በረዶ እንደሆነችና ሰውነቷ ከፍሪጅ እደወጣ ስጋ እንደደረ ነው፡፡ማሻሸቴ ቀጥሎ ጡቶቾ ጋር ደረሰ ....ጨመቅ ለቀቅ.. ጨመቅ ለቀቅ ሳደርግ አስደንጋጭ ፈሳሽ ከጡቶቾ ፊን ብሎ ደረቴ ላይ ተረጨ..ደነገጥኩ ፡፡
በደነገጥኩበት ፍጥነት አሷም ይበልጥ በመበሳጨት ጮኸችብኝ፡፡
‹‹በናትህ ዝም ብለህ ማሻሻቱን ጥለህ ..ማድረግ አትችልም ?››
‹‹ምድነው ከጡትሽ የወጣው?››
‹‹ምን እንዲወጣ ትፈልጋለህ… ነዳጅ…››.በማሾፍ መለሰችልኝ፡፡
‹‹እሱማ ወተት ነው…ግን እንዴት...?እንዲህ ይሆናል እንዴ?››
‹‹እመጫት ስለሆንኩ እና ስለማጠባ ነው››ግዴለሽ እና ስሜት አልባ በሆነ ስሜት መለሰችልኝ፡፡
‹‹ማ….? አንቺ?››
‹‹አዎ …የሁለት ወር አራስ ልጅ ቤት ጥዬ ነው የመጣሁት››
በድንጋጤ ከመኝታዬ ተስፈንጥሬ በመነሳት ቁጭ አልኩ
‹‹ አቤት ጭካኔ ..የሁለት ወር አራስ ቤት አስተኝቶ ለሽርሙጥና መሰማራት ሀጥያት ብቻ ስይሆን ወንጀልም ነው..ምን አይነጠቷ አውሬ ነሽ በእግዚያብሄር…!!!!››አልኳት፡፡
ተንፈቅፍቃ የሹፈት ሳቅ ሳቀችብኝ‹‹ሀጥያት አልክ ..?ማነው እኔን ወንጀለኛ እና ሀጥያተኛ ነሽ ብሎ ሊፈርድብኝ የሞራል ብቃት ያለው..?ያሳደገኝ ማበረሰብ…? ሚያስተዳድረኝ መንግስት …?ቄሱ..?ፓስተሩ…? አንተ ..
፡
፡
#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
//////
የእኔ ቅንዝርነት የልጅቷ ድህነት፤እናትነት እና ተስፋ ቢስነት
ስሟ ግን ማን ነበር?
ምን አይነት ችግር ላይ እንዳለሁ ልትገምቱ አትችሉም፡፡ ሀገር አማን ነው ብዬ በእንቅልፍ ዓለም ከተዋጥኩ በኋላ በእኩለ ለሊት ላይ ለመንገድ መብራት ማቆሚያ እደተተከለ የእንጨት ምሰሶ ቀጥ ይላል፡፡ ቀጥ ማለቱ ብቻ አይደለም እኮ የሚያበሳጨኝ ቀጥ በማለቱ ውስጥ ጥዝጣዜ ነገር አለው፡፡ የመነዝነዝ ዓይነት እና ለመግለፅ የሚያስቸግር ግራ አጋቢ ህመም ከእቅልፍ እስከማባበነን ድረስ የሚደርስ ኃይል ያለው ህመም ፡፡እስከአሁን ስለምን እንደማወራችሁ አልገባችሁም አይደል?
እንጠራራ እና ከእንቅልፌ ጋር እየታገልኩ ዓይኔን እያሻሸው በዳበሳ ወደ ሽንት ቤት ሄዳለው… ምን አልባት ሽንቴ ወጥሮኝ እንደሆነ ብዬ…ግን ብጨምቀው ባልበው ጠብ አይለኝም ፡፡
በንጭንጭ ወደ አልጋዬ እመለስና እያተገላበጥኩ እንቅልፍ እስኪያሸንፈኝ እሰቃያለው፡፡ከሰዓታት በኃላ እንደምንም እንቅልፍ ያሸንፈኛል፡፡ሊነጋጋ ሲል መለልሶ ይቀሰቅሰኛል፡፡የዚህኛውን ጊዜ እንኳን ፊት አልሰጠውም …ከነ ተረቱ ‹ የጥዋት ቁ› ይባል የለ …ሽንት እንዲወጠር እድርጎት ይሆን ትክክለኛ አምሮት ይሁን መለየት አይቻልም…ሀሰተኛ መሲ ነገር ነው፡፡
ይሄ ነገር እየተደጋገመ ሲያስቸግረኝ ህልሜን ሁሉ የከተማዋ ቆነጃጅቶች እና በአካልም በምናብም የማውቃቸው ሴቶች ሲሞሉት የሆነ ነገር ማድረግ እንዳለብኝ ወሰንኩ…፡፡ በእኔ ምክር ሳይሆን በተፈጥሮ ህግ የሚመራውን ቅንዝሬን የሆነ ዘዴ ፈጥሬ ማቀዝቀዝ አለብኝ..ስለዚህ ግዢ ልወጣ ወሰንኩ፡፡
ሰፈሩን ባልነግራችሁም …ለግዢ ምቹ ናቸው ሲባሉ ከሰማዋቸው የከተማዋ ጉድ ሰፈሮች መካከል ወደ አንዱ ነው የሄድኩት…ቺቺኒያ አይተንሀል አላችሁኝ…..?ምን አልባት እኔን የመሰለ ሰው አይታችሁ ይሆናል እንጂ እኔ ወደ እዛ ሰፈር ዝር አላልኩም…ደግሞስ እናንተ ራሳችሁ እዛ ሰፈር ምን ስትሰሩ ነበር? ለማንኛውም ያልኳችሁ ቦታ ሄድኩ …ቀድሜ አልጋ ተከራየው….
ከዛ ወደ ቡና ቤቶቹ ወይም ወደ ጭፈራ ቤቶቹ አልነበረም ጎራ ያልኩት፡፡ ከምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ወደ ጎዳናው ነው የወጣሁት…፡፡ከቤት ውስጥ ግዢ የውጩን ለምን እንደመረጥኩ አልገባኝም…. ብቻ ስሜቴ ወደ እዛ ነው የገፋኝ ፡፡ዞሬ ለመምረጥ… መርጬ ለማነጋገር እና ለመስማማት..ተስማምቶም ይዞ ለመሄድ ..አንድ ሰዓት ገደማ ፈጀብኝ፡፡
ልጅቷ የተከራየሁት ቤርጎ ገብታ አልጋው ጠርዝ ላይ እንደተቀመጠች ፊቷን ለማንበብ ሞከርኩ..፡፡ፊቷ ሜካፕ የነከካው ቢሆንም በስርዓቱ አልተዳረሰም… የሆነ መዝረክረክ ይታይበታል፡፡ከቀይ ዳማ መልክ ወደ ግራጫ የተቀየረ የፊት ቀለም ይታየኛል..፡፡የዓይኖቾ ቅንድቦች ቀና ማለት ደክሟቸው መሰለኝ ተደፍተዋል፡፡ጉንጮቾ ወደ ውስጥ ስርጉድ ብለው በረሀ ላይ ውሃ እንዲወጣባቸው የተቆፈሩ ጉድጓዶች ነው የሚመስሉት ...፡፡ከንፈሮቾ ቁርፍድፍድ ብለው የመሰነጣጠቅ ምልክት ይታይባቸዋል፡፡ግን በተቀባችው ቀይ ሊፒስቲክ ልትሸፍነው ሞክራለች፡፡ውጭ ከመብራቱ ፖል አቅራቢያ ከሚገኝ ግንብ አጥር ጋር ተጣብቃ ግማሽ ብርሀን እና ግማሽ ጨለማ ከቧት ሳነጋግራት ይሄ ሁሉ አሁን የዘረዘርኩላችሁን የመልኳ ሁኔታ አልተገለፀልኝ ነበር.፡፡አቋሟን እና የፊቷን ቅርጽ በከፊል ነበር የገመገምኩት….፡፡ገምግሜም አስፓልቱ ላይ ከተኰለኰሉት መሀከል እሷን የመረጥኳት…መርጬም ያነጋገርኳት …አነጋሬም የተሰመመማነው… ተስማምተን ወደ ተከራየውት ቤርጎ ይዤት የገባሁት፡፡
አሁን ..ከገባችና በመጠኑም ፈንጠር ብላ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀምጣ ሳስተውላት ግን አሁን ከላይ እንደዘረዘርኩላችሁ የተለየች ሆና ነው ያገኘኋት፡፡ ገና ያልበሰለች የ16 ዓመት አካባቢ ጨቅላ ወጣት ነች ፡፡ቢሆንም ውስጧ የ60 ዓመት …የጎበጠች እና የጨረጨሰች አሮጊት በእሷነቷ ውስጥ ተደብቃ ትታያለች፡፡ ወጣትነቷ በፍጥነት ወደ መጠውለግ ሲንደረደር ይታያል፡፡
‹‹ተጫወቺ እንጂ …ምነው ከእኔ ጋር ማደሩ ደስ አላለሽም እንዴ? ››አልኳት፡፡
ፊቷን እንዳጨማደደች አላስፈላጊ ጥያቄ እንደጠየቀ ሰው በግርምት እያየችኝ
‹‹መደሰት እና አለመደሰት እዚህ ጋር ምን አመጣው›ስትል መለሰችልኝ፡፡
‹‹አልገባኝም››
‹‹እንዴት አይገባህም..እኔ ገንዘብህን ነው የምፈልገው፡፡ ከፍለኸኛል….ከከፈልከኝ ደግሞ ደስ አለኝም አላለኝም አብሬህ ማደር ግዴታዬ ነው››አለችኝ እና ልብሶቾን ማወላለቅ ጀመረች፡፡
እኔም አወላለቅኩና ተከተልኳት..ተያይዘን አንድ አንሶላና ፍራሽ ከስር..አንድ አንሶላና ብርድ ልብስ ከላይ አድርገን ከመሀከል ገባን…፡፡
‹‹እዛ ባዶ ቤት ብቻውን በነበረበት ሰዓት ዘራፍ እያለ እረፍት ይነሳኝ የነበረው አጅሬን‹‹ አሁን እስቲ ጉዱህን እየዋለው….ሜዳውም ፈረሱንም ያው አመቻችቼለታለው… ›› አልኩት.፡፡
ግን ለእኔም ሆነ ለአጅሬው እንደአሰብነውና እደጓጓነው የሆነልን አይመስለኝም ….የሆነ ደስ የማይል ስሜት እየተሰማኝ ነው…እሱም አንዴ ቀጥ ከዛ መልሶ እንደመልፈስፈስ እያለ ፈራ ተባ ውስጥ ገብቷል፡፡ወደ እሷ ፊቴን አዞርኩና እጄን ትከሻዋ ላይ ጣል አደረግኩ..ስጠጋት ከሰውነቷ የሚረጨው ጠረን ተምዘግዝጎ ወደ አፍንጫዬ ሲገባ ደስ የማይል ስሜት ነው የተሰማኝ..እርግጥ ከለበሰችው ልብስ አልፎ ሰውነቷ ላይ የቀረ የሽቶ ሽታ አለ ..፡፡ግን ከሽቶው ተደባልቆ ና ተዋህዶ የሚበተን ሌላ ጠረን አለ..ምንነቱን ልለየው ያልቻልኩት ትንሽ የሚረብሽ ጠረን….፡፡
እንደዛም ሆኖ በደንብ ተጠጋኋት ..ሰውነቴን ከሰውነቷ አጣበቅኩ…እዳብሳት እና አሻሻት ጀመርኩ፡፡..ቀስ በቀስ ሰውነቴ እየጋለ እየሞቀ ቢመጣም ከእሷ ወደ እኔ እየተላለፈ ያለ ምንም አይነት ሙቀት ሊሰማኝ አልቻለም…. አሁንም በረዶ እንደሆነችና ሰውነቷ ከፍሪጅ እደወጣ ስጋ እንደደረ ነው፡፡ማሻሸቴ ቀጥሎ ጡቶቾ ጋር ደረሰ ....ጨመቅ ለቀቅ.. ጨመቅ ለቀቅ ሳደርግ አስደንጋጭ ፈሳሽ ከጡቶቾ ፊን ብሎ ደረቴ ላይ ተረጨ..ደነገጥኩ ፡፡
በደነገጥኩበት ፍጥነት አሷም ይበልጥ በመበሳጨት ጮኸችብኝ፡፡
‹‹በናትህ ዝም ብለህ ማሻሻቱን ጥለህ ..ማድረግ አትችልም ?››
‹‹ምድነው ከጡትሽ የወጣው?››
‹‹ምን እንዲወጣ ትፈልጋለህ… ነዳጅ…››.በማሾፍ መለሰችልኝ፡፡
‹‹እሱማ ወተት ነው…ግን እንዴት...?እንዲህ ይሆናል እንዴ?››
‹‹እመጫት ስለሆንኩ እና ስለማጠባ ነው››ግዴለሽ እና ስሜት አልባ በሆነ ስሜት መለሰችልኝ፡፡
‹‹ማ….? አንቺ?››
‹‹አዎ …የሁለት ወር አራስ ልጅ ቤት ጥዬ ነው የመጣሁት››
በድንጋጤ ከመኝታዬ ተስፈንጥሬ በመነሳት ቁጭ አልኩ
‹‹ አቤት ጭካኔ ..የሁለት ወር አራስ ቤት አስተኝቶ ለሽርሙጥና መሰማራት ሀጥያት ብቻ ስይሆን ወንጀልም ነው..ምን አይነጠቷ አውሬ ነሽ በእግዚያብሄር…!!!!››አልኳት፡፡
ተንፈቅፍቃ የሹፈት ሳቅ ሳቀችብኝ‹‹ሀጥያት አልክ ..?ማነው እኔን ወንጀለኛ እና ሀጥያተኛ ነሽ ብሎ ሊፈርድብኝ የሞራል ብቃት ያለው..?ያሳደገኝ ማበረሰብ…? ሚያስተዳድረኝ መንግስት …?ቄሱ..?ፓስተሩ…? አንተ ..
❤37😢3
?ወይስ እግዚያብሄር…?›› ትንፋሽ ወሰደችና ንግግሯን ቀጠለች….‹‹….ልጄ ወተት ያስፈልጋታል...እኔም መብላት ባልችልም ቀምሼም ቢሆን ማደር አለብኝ...እናቴም አየር ስባ ብቻ አይደለም የምትኖረው….አንገታችን የምናስገባበትን እና ጎናችንን የምናሳርፍበት ደሳሳ ጎጆም ከመንግስት በችሮታ የተሰጠን ሳይሆን በ6000 ብር የተከራሁት ነው..ነው ወይስ አራስ ልጄን እና ደህነት እና በሽታ ተባብረው ያደቀቋትን እናትኔን ይዤ ጎዳና በመውጣት መንገድ ጠርዝ ጨርቅ አንጥፌ ልለምን?ለተቀማጭ ሰማይ ቅርቡ ነው አሉ….ዳሩ ወንድ አይደለህ.. ማስታቀፍ አንጂ መታቀፍ ምን እንደሆነ ጣጣውን እና መዓቱን የት ታውቃለህ?፡፡››
በንግግሯ ደነዘዝኩ ..ጭንቅላቴን ራስምታት ሲወቅረኝ ይታወቀኛል‹‹ይቅርታ ..ስሜታዊ ሆኜ ነው… አሁን ልጅሽን ማን ነው የሚጠብቀልሽ?››ስል ቀዝቀዝ ብዬ ለስለስ ባለ የድምፅ ቃና ጠየቅኳት፡፡
‹‹እናቴ››
‹‹አይቸገሩም?››
‹‹ታስቸግራለች..ግን ብዙ ጊዜ አዳር አልሰራም… ሁለትም ሆነ ሶስት ሰዎችን አግኝቼ ሾርት ከሳራው በኋላ ያገኘኋትን ብር ይዤ ስድስትም ሳባትም ሰዓት ወደቤቴ እገባ ነበር… ዛሬ ግን እንደዛ ስላልቀናኝ ነገ ደግሞ የግድ የቤት ኪራዬን መክፈል ስላለብኝ እና ለዛ የሚሆን በቂ ብር እጄ ላይ ስለሌለ ነው አዳር ለመስራት የወሰንኩት፡፡››
‹‹ሞባይሌን አወጣሁና ሰዓቴን አየው 5፡25 ይላል..ኪሶቼን በረበርኩና ጥዋት ለታክሲ ይሆነኛል ብዬ ሀምሳ ብር ብቻ አስቀረሁና ሌላውን መዳፎ ላይ አስጨበጥኳት.. ከተስማማንበት ሂሳብ ቢያንስ በእጥፍ ይበልጣል….
‹‹በቃ… ለልጅሽ ሂጂላት››
‹‹ለምን?››
‹‹በቃ ሂጂላት››
‹‹ቢያንስ አንዴ ተጠቀምና ልሂድ››
‹‹አይ አልችልም ስሜቴ ደፈራርሷል››
ለመጀመሪያ ጊዜ ፈገግ አለች..ለሽርፍራፊ ሰከንድ ቢሆንም ውስጧ ያለችው አሮጊት ስትከሳ እና ከውጭ የሚታየው ወጣትነቷ ሲፈካ ታዘብኩ‹‹ በጣም ነው ማመሰግነው..በእውነት ከጭንቀት እና ከስጋት ነው የገላገልከኝ….፡፡በድኔ ብቻ ነበር እዚ ያለው…፡፡ ስጋዬም ነፍሴም ልጄ ጋ ነበር፡፡››እየመረቀችኝ ልብሶቾን ለበሰች… ሞባይሌን ተቀብላ ቁጥሯን መዘገበች ና መለሰችልኝ‹‹ቁጥሬ ነው ብትደውልልኝ ደስ ይለኛል›› አለችኝ፡፡
‹‹እሺ እደውልልሻለው.. ለማንኛውም አንቺ በርቺ››
‹‹ወድጄ እበረታለው..››አለችኝና ንግግሯን ቀጠለች‹‹በጣም ይገርማል ››አለችኝ፡፡
‹‹ምኑ?››
‹‹ወንዶች ስትባሉ እንደየመልካችሁ ባህሪያችሁም ብዛቱ ..ስንቱ አውሬ እና ማሰብ የተሳነው የአእምሮ ድኩማን አለ መሰለህ… እነሱን አስበህ በአዳም ልጆች ተስፋ ልትቆርጥ ስትል ደግሞ እንደ አንተ አይነት በግ ያጋጥማሀል፡፡››
‹‹በግ?››አልኰኳት … ደንግጬም ተገርሜም፡፡
‹‹ይቅርታ በግ ስልህ ሞኝ ለማለት ፈልጌ አይደለም… ፡፡የዋህ እና መልካም ሰው ለማለት ነው ..ለማኛውም ብትደውልልኝ ደስ ይለኛል ፡፡ቆንጆ እና የምታምር ልጄንም አሳይሀለው››
‹‹እሺ አይልሻለሁ..››
‹‹እሺ ቻው››ብላኝ በራፉን ከፋታ በመውጣት መልሳ ዘጋችልኝና ሄደች፡፡እርምጃዋ ቀስ እያለ እየደበዘዘ..እየደበዘዘ ለጆሮ እየሳሳ በስተመጨረሻ ጭልም ብሎ ሲጠፋ ተሰማኝ…፡፡
ግን ነገ ወይ በማግስቱ እደውልላት ይሆን? በውስጤ የተጫረ ጥርጣሬ የወለደው ጥያቄ ነበር፡፡ልደውልላትማ ይገባል….ስለዚህች ልጅ ታሪክ ጠለቅ ብዬ ባውቅ ደስ ይለኛል.. ?እንደዛ አይነት ጉጉት በውስጤ ተፀንሷል፡፡
✨ተፈፀመ✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በንግግሯ ደነዘዝኩ ..ጭንቅላቴን ራስምታት ሲወቅረኝ ይታወቀኛል‹‹ይቅርታ ..ስሜታዊ ሆኜ ነው… አሁን ልጅሽን ማን ነው የሚጠብቀልሽ?››ስል ቀዝቀዝ ብዬ ለስለስ ባለ የድምፅ ቃና ጠየቅኳት፡፡
‹‹እናቴ››
‹‹አይቸገሩም?››
‹‹ታስቸግራለች..ግን ብዙ ጊዜ አዳር አልሰራም… ሁለትም ሆነ ሶስት ሰዎችን አግኝቼ ሾርት ከሳራው በኋላ ያገኘኋትን ብር ይዤ ስድስትም ሳባትም ሰዓት ወደቤቴ እገባ ነበር… ዛሬ ግን እንደዛ ስላልቀናኝ ነገ ደግሞ የግድ የቤት ኪራዬን መክፈል ስላለብኝ እና ለዛ የሚሆን በቂ ብር እጄ ላይ ስለሌለ ነው አዳር ለመስራት የወሰንኩት፡፡››
‹‹ሞባይሌን አወጣሁና ሰዓቴን አየው 5፡25 ይላል..ኪሶቼን በረበርኩና ጥዋት ለታክሲ ይሆነኛል ብዬ ሀምሳ ብር ብቻ አስቀረሁና ሌላውን መዳፎ ላይ አስጨበጥኳት.. ከተስማማንበት ሂሳብ ቢያንስ በእጥፍ ይበልጣል….
‹‹በቃ… ለልጅሽ ሂጂላት››
‹‹ለምን?››
‹‹በቃ ሂጂላት››
‹‹ቢያንስ አንዴ ተጠቀምና ልሂድ››
‹‹አይ አልችልም ስሜቴ ደፈራርሷል››
ለመጀመሪያ ጊዜ ፈገግ አለች..ለሽርፍራፊ ሰከንድ ቢሆንም ውስጧ ያለችው አሮጊት ስትከሳ እና ከውጭ የሚታየው ወጣትነቷ ሲፈካ ታዘብኩ‹‹ በጣም ነው ማመሰግነው..በእውነት ከጭንቀት እና ከስጋት ነው የገላገልከኝ….፡፡በድኔ ብቻ ነበር እዚ ያለው…፡፡ ስጋዬም ነፍሴም ልጄ ጋ ነበር፡፡››እየመረቀችኝ ልብሶቾን ለበሰች… ሞባይሌን ተቀብላ ቁጥሯን መዘገበች ና መለሰችልኝ‹‹ቁጥሬ ነው ብትደውልልኝ ደስ ይለኛል›› አለችኝ፡፡
‹‹እሺ እደውልልሻለው.. ለማንኛውም አንቺ በርቺ››
‹‹ወድጄ እበረታለው..››አለችኝና ንግግሯን ቀጠለች‹‹በጣም ይገርማል ››አለችኝ፡፡
‹‹ምኑ?››
‹‹ወንዶች ስትባሉ እንደየመልካችሁ ባህሪያችሁም ብዛቱ ..ስንቱ አውሬ እና ማሰብ የተሳነው የአእምሮ ድኩማን አለ መሰለህ… እነሱን አስበህ በአዳም ልጆች ተስፋ ልትቆርጥ ስትል ደግሞ እንደ አንተ አይነት በግ ያጋጥማሀል፡፡››
‹‹በግ?››አልኰኳት … ደንግጬም ተገርሜም፡፡
‹‹ይቅርታ በግ ስልህ ሞኝ ለማለት ፈልጌ አይደለም… ፡፡የዋህ እና መልካም ሰው ለማለት ነው ..ለማኛውም ብትደውልልኝ ደስ ይለኛል ፡፡ቆንጆ እና የምታምር ልጄንም አሳይሀለው››
‹‹እሺ አይልሻለሁ..››
‹‹እሺ ቻው››ብላኝ በራፉን ከፋታ በመውጣት መልሳ ዘጋችልኝና ሄደች፡፡እርምጃዋ ቀስ እያለ እየደበዘዘ..እየደበዘዘ ለጆሮ እየሳሳ በስተመጨረሻ ጭልም ብሎ ሲጠፋ ተሰማኝ…፡፡
ግን ነገ ወይ በማግስቱ እደውልላት ይሆን? በውስጤ የተጫረ ጥርጣሬ የወለደው ጥያቄ ነበር፡፡ልደውልላትማ ይገባል….ስለዚህች ልጅ ታሪክ ጠለቅ ብዬ ባውቅ ደስ ይለኛል.. ?እንደዛ አይነት ጉጉት በውስጤ ተፀንሷል፡፡
✨ተፈፀመ✨
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍32❤29
#ሞት_አያምም!!!
እኖር ብዬ ብታረድም
ለመኖር ስል ብሰደድም
እኖር ብዬ ብዋረድም
ዘጠኜ ሞቴን ብሞተው…
አንዴ እንደመኖር አይከብድም!
መኖር ከመምት አይልቅም
ሞት እንደሕይወት አይጨንቅም፡፡
………………………………
የሞተ ‹‹እሞታለሁ›› ሲል…
በጭራሽ አያውቅም ፈርቶ፡፡
ያልኖረ አያውቅም ሞቶ።
።።።።
መኖር እንጂ የሚያስፈራኝ
መኖር እንጂ የሚያስገፋኝ
መኖር እንጂ የገደለኝ
መኖር እንጂ የበደለኝ
ሞት አያምም ካቆሰለኝ
ምት አያምም ከገደለኝ!
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እኖር ብዬ ብታረድም
ለመኖር ስል ብሰደድም
እኖር ብዬ ብዋረድም
ዘጠኜ ሞቴን ብሞተው…
አንዴ እንደመኖር አይከብድም!
መኖር ከመምት አይልቅም
ሞት እንደሕይወት አይጨንቅም፡፡
………………………………
የሞተ ‹‹እሞታለሁ›› ሲል…
በጭራሽ አያውቅም ፈርቶ፡፡
ያልኖረ አያውቅም ሞቶ።
።።።።
መኖር እንጂ የሚያስፈራኝ
መኖር እንጂ የሚያስገፋኝ
መኖር እንጂ የገደለኝ
መኖር እንጂ የበደለኝ
ሞት አያምም ካቆሰለኝ
ምት አያምም ከገደለኝ!
🔘በላይ በቀለ ወያ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍12❤6🔥2
#ቀረሽ_እንደዋዛ
እንደ ድመቶቹ
የትም እንደሚያድሩት
እንደ ስልክ እንጨቶች
እንደ ዛፍ ሀረጎች
እንደ ቤት ክዳኖች
ብርድ አቆራመደኝ
ስጠብቅ ስጠብቅ
˝ትመጫለሽ ብዬ ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ
የልጅነት አይኔ ሟሟ እንደ በረዶ˝
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስቆጥር
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስቆጥር
ትመጫለሽ ብዬ ባዝን ባንጎራጉር
ትወጫለሽ ብዬ በበራፍሽ ብዞር
ብርድ አቆራመደኝ
የመንገድ መብራቶች አይተው አፌዙብኝ
ውርጩ ቀለደብኝ
ጨለማው ሳቀብኝ
አለመምጣትሽን አውቀዋል ያውቃሉ
መስኮቶች ጨልመው
ቤቶች ተቆልፈው
ከተማው ሲተኛ
አይተዋል ያያሉ
አለመምጣትሽን
አውቀዋል ያውቃሉ፡፡
🔘ገብረ ክርስቶስ ደስታ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እንደ ድመቶቹ
የትም እንደሚያድሩት
እንደ ስልክ እንጨቶች
እንደ ዛፍ ሀረጎች
እንደ ቤት ክዳኖች
ብርድ አቆራመደኝ
ስጠብቅ ስጠብቅ
˝ትመጫለሽ ብዬ ሳይ ማዶ ሳይ ማዶ
የልጅነት አይኔ ሟሟ እንደ በረዶ˝
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስቆጥር
ትመጫለሽ ብዬ ደቂቃ ስቆጥር
ትመጫለሽ ብዬ ባዝን ባንጎራጉር
ትወጫለሽ ብዬ በበራፍሽ ብዞር
ብርድ አቆራመደኝ
የመንገድ መብራቶች አይተው አፌዙብኝ
ውርጩ ቀለደብኝ
ጨለማው ሳቀብኝ
አለመምጣትሽን አውቀዋል ያውቃሉ
መስኮቶች ጨልመው
ቤቶች ተቆልፈው
ከተማው ሲተኛ
አይተዋል ያያሉ
አለመምጣትሽን
አውቀዋል ያውቃሉ፡፡
🔘ገብረ ክርስቶስ ደስታ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍12❤3
አለም ትዞራለች የተባለው ሳይንስ
አሁን የለው ዋጋ፣
አለም ዛሬ ቆማ ሰው እየዞራት ነው
እንጀራ ፍለጋ።
🔘ስፍራዬ ጥላዬ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አሁን የለው ዋጋ፣
አለም ዛሬ ቆማ ሰው እየዞራት ነው
እንጀራ ፍለጋ።
🔘ስፍራዬ ጥላዬ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
🔥12❤4
ስትመጪ
ክንዴ በስተራስጌ ክንፍ አቆጠቆጠ
የደጅ አፌ ዳገት፣ ዐይኔ ፊት ቀለጠ
ስትሄጂ
ጸሐዩ ፈረጠ፣ ቁልቁለቱ አበጠ
የቀዬው አብሪ ትል በጽልመት ተዋጠ።
በዳፍንታም አለም፣ ጠባቂ ሲተጋ
እንኳን ቀን ጨልሞ፣ ሌሊቱ ሲነጋ...
መምጣትና መሄድ ቀን ይቀያይራል፥
ምላስሽ ያጎድፋል፣ ምላስሽ ያጠራል
ትንፋሽሽ ያጠፋል፣ ትንፋሽሽ ያበራል።
🔘ዮሐንስ ሞላ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ክንዴ በስተራስጌ ክንፍ አቆጠቆጠ
የደጅ አፌ ዳገት፣ ዐይኔ ፊት ቀለጠ
ስትሄጂ
ጸሐዩ ፈረጠ፣ ቁልቁለቱ አበጠ
የቀዬው አብሪ ትል በጽልመት ተዋጠ።
በዳፍንታም አለም፣ ጠባቂ ሲተጋ
እንኳን ቀን ጨልሞ፣ ሌሊቱ ሲነጋ...
መምጣትና መሄድ ቀን ይቀያይራል፥
ምላስሽ ያጎድፋል፣ ምላስሽ ያጠራል
ትንፋሽሽ ያጠፋል፣ ትንፋሽሽ ያበራል።
🔘ዮሐንስ ሞላ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍6
#ወህኒ
ካቻምና በመስቀል ድፎ ባርኬአለሁ።
ዘንድሮ በጩቤ አጥንት ወግቻለሁ።
ለምን እንዳትሉ፤
በቃ ሆነ በሉ፤
የሰው ልጅ ጠባዩ የሰው ልጅ አመሉ ።
አምና ደግ ነበርኩ ፣ ክፉ ሰው ዘንድሮ
ትናንትና ምሁር ፣ ዛሬ ግን ደንቆሮ ።
ለምን እንዳትሉ ፤
በቃ ሆነ በሉ ፤
የሰው ልጅ ጠባዩ የሰው ልጅ አመሉ ።
መሆን አምሮኝ ያውቃል፤ ፖለቲከኛ ሰው ፣ ኃያል የጦር መሪ ፤
ተመኝቼም ነበር ለመሆን አዝማሪ ፤
ገጣሚ ለመሆን ስንኝ ቋጥሬአለሁ ፤
ደራሲ ለመሆን ተስዬም አውቃለሁ ፤
ሞዴል አርሶአደርም ለመሆን ፈልጌ ፣
አስጠምጄ ነበር ከ 4 ኪሎ ግርጌ ።
ኢንጂነር ዶክተርም ልሆን ነበር እኮ ፤
እንደዚህ ሆንኩ እንጂ ነገር ሌላ ታኮ ።
ለምን እንዳትሉ፤
በቃ ሆነ በሉ ፤
የሰው ልጅ ጠባዩ የሰው ልጅ አመሉ ።
አንድ ሰው አንድ ነው ከንግዲህ አትበሉ ፤
የሰው ልጅ ወህኒ ነው ፤
እልፍ አዕላፍ ሰዎች ታስረው የተጣሉ ፣
መውጫ አጥተው ነው እንጂ፣አንድ ሰው ውስጥ አሉ።
🔘ይስማዕከ ወርቁ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ካቻምና በመስቀል ድፎ ባርኬአለሁ።
ዘንድሮ በጩቤ አጥንት ወግቻለሁ።
ለምን እንዳትሉ፤
በቃ ሆነ በሉ፤
የሰው ልጅ ጠባዩ የሰው ልጅ አመሉ ።
አምና ደግ ነበርኩ ፣ ክፉ ሰው ዘንድሮ
ትናንትና ምሁር ፣ ዛሬ ግን ደንቆሮ ።
ለምን እንዳትሉ ፤
በቃ ሆነ በሉ ፤
የሰው ልጅ ጠባዩ የሰው ልጅ አመሉ ።
መሆን አምሮኝ ያውቃል፤ ፖለቲከኛ ሰው ፣ ኃያል የጦር መሪ ፤
ተመኝቼም ነበር ለመሆን አዝማሪ ፤
ገጣሚ ለመሆን ስንኝ ቋጥሬአለሁ ፤
ደራሲ ለመሆን ተስዬም አውቃለሁ ፤
ሞዴል አርሶአደርም ለመሆን ፈልጌ ፣
አስጠምጄ ነበር ከ 4 ኪሎ ግርጌ ።
ኢንጂነር ዶክተርም ልሆን ነበር እኮ ፤
እንደዚህ ሆንኩ እንጂ ነገር ሌላ ታኮ ።
ለምን እንዳትሉ፤
በቃ ሆነ በሉ ፤
የሰው ልጅ ጠባዩ የሰው ልጅ አመሉ ።
አንድ ሰው አንድ ነው ከንግዲህ አትበሉ ፤
የሰው ልጅ ወህኒ ነው ፤
እልፍ አዕላፍ ሰዎች ታስረው የተጣሉ ፣
መውጫ አጥተው ነው እንጂ፣አንድ ሰው ውስጥ አሉ።
🔘ይስማዕከ ወርቁ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍12
#እውነት_ወደ_ኋላ
ገንዘብ ካለው ጋራ
ፍቅር አይኖርም ወይ ብለሽ ጠይቀሻል!?
እኔ ያንቺን እንጂ
የሌላን አላልኩም እጅግ ተሳስተሻል
አይኖርም አላልኩም...አይጠፋም ይኖራል
ይኖራል
ይኖራል
ግን?...
ከባለሐብት ጋር
ተፋቅራ 'ምናያት የቷም አይነት እንስት...
'ምን ' ትሁንም 'ምንም '
የሕይወት ታሪኳን ወደኋላ ሄደን ....ጥቂት ብንገመግም
አንድ ቡና ለሁለት ....
አብራ የጠጣችው አንድ አፍቃሪ አታጣም ።
🔘ኤፍሬም ስዩም🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ገንዘብ ካለው ጋራ
ፍቅር አይኖርም ወይ ብለሽ ጠይቀሻል!?
እኔ ያንቺን እንጂ
የሌላን አላልኩም እጅግ ተሳስተሻል
አይኖርም አላልኩም...አይጠፋም ይኖራል
ይኖራል
ይኖራል
ግን?...
ከባለሐብት ጋር
ተፋቅራ 'ምናያት የቷም አይነት እንስት...
'ምን ' ትሁንም 'ምንም '
የሕይወት ታሪኳን ወደኋላ ሄደን ....ጥቂት ብንገመግም
አንድ ቡና ለሁለት ....
አብራ የጠጣችው አንድ አፍቃሪ አታጣም ።
🔘ኤፍሬም ስዩም🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍7❤1
#ያገሬ_መንታ_ገፅ
ውዷ ባለቤቴ፤
እኔም ወግ ይድረሰኝ፤
ወፍራም ሳግ ይውረሰኝ፤
አባት ልሁናቸው ውለጂልኝ መንታ፣
አንድ ሀገር የሚያድን አንዱ የሚፈታ፣
አንዱ ቤት ሚያፈርስ አንዱ 'ሚሆን ዋልታ፡፡
.
.
እንዲያ ነው እንግዲህ፤
በውላ'ጅ አካልሽ፤
መገፋት ቢተርፍሽ፣
ቢጠልዝሽ ደርሶ አካልሽን ቢያጎነው፣
ከቶ አትገረሚ፤
አንዱ ሲንድሽ ነው "ሌላ"ሽ 'ሚጠግነው፡፡
እናልሽ አለሜ፤
እናልሽ ህመሜ፤
እንዲያ ነው ዘመንሽ እንዲያ ነው ዘመኔ፣
አንቺን ሲነኩሽ ግን ታምሜያለሁ እኔ፡፡
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ውዷ ባለቤቴ፤
እኔም ወግ ይድረሰኝ፤
ወፍራም ሳግ ይውረሰኝ፤
አባት ልሁናቸው ውለጂልኝ መንታ፣
አንድ ሀገር የሚያድን አንዱ የሚፈታ፣
አንዱ ቤት ሚያፈርስ አንዱ 'ሚሆን ዋልታ፡፡
.
.
እንዲያ ነው እንግዲህ፤
በውላ'ጅ አካልሽ፤
መገፋት ቢተርፍሽ፣
ቢጠልዝሽ ደርሶ አካልሽን ቢያጎነው፣
ከቶ አትገረሚ፤
አንዱ ሲንድሽ ነው "ሌላ"ሽ 'ሚጠግነው፡፡
እናልሽ አለሜ፤
እናልሽ ህመሜ፤
እንዲያ ነው ዘመንሽ እንዲያ ነው ዘመኔ፣
አንቺን ሲነኩሽ ግን ታምሜያለሁ እኔ፡፡
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍9❤1
#የኔ_ዓለም!
እንዳንቺ ሚጣፍጥ - አንጀት የሚያረካ
ጣፋጭ የለም ለካ!
ጥዑም ናቸው ያሉኝ ማርና ቸኮሌት
ካንቺ ሲነፃፀር መረሩኝ እንደ ሬት።
#ማርያምን !
ከድምፀትሽ ልቆ - 'ሚሰማ ሙዚቃ
ከአንባሰል ከባቲ ከብሉዝ ትዝታ
ወድያም ከብሉዙ ደግሞም ከአፍሪቃ
አንድም የለም በቃ !
#ማርያምን!
ካገኘሽ ጠቁሚኝ
ከሄድሽ ብትነግሪኝ.. .
ካንቺ ጋራ ስሆን ሀዘን ጭንቄን ሽሮ
የደስታ ወሰኔን አለቅጥ አንሮ
የሚገርመኝ የለም ከዓለሟ ተፈጥሮ!
ምንድናት ጨረቃ?
ምንድናትስ ፀሀይ ?
ካንቺ አንፃር ስትታይ.. .
ሀዋሳ ላንጋኖ.. . ቢሾፍቱ ሪዞርት
እውን ካንቺ በልጠው እኔን ሊያስደስቱኝ
ኸረ በማዬ ሞት !
#ማርያምን...
የቱ ኮሜዲ ነው የትኛው ቀልደኛ
እኔን የሚያደርገኝ የወሬው ምርኮኛ?
ደግሞ ካንቺ በላይ
እኔን ለማሳሳቅ ማነው የሚደፍረው ?
ባንቺ ጨዋታ ነው
የተደበቀውን.. . ጥርሴን የምገልጠው።
#ማርያምን !
እንደውም ባጭሩ.. .
አሁን ይሄ ግጥም
የቃላት ጥርቅም
እጅግ መሳጭ ሆኖ አንባቢው ቢያደንቅም
ካንቺ ግን አይበልጥም።
ማርያምን...
🔘ሚካኤል አስጨናቂ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
እንዳንቺ ሚጣፍጥ - አንጀት የሚያረካ
ጣፋጭ የለም ለካ!
ጥዑም ናቸው ያሉኝ ማርና ቸኮሌት
ካንቺ ሲነፃፀር መረሩኝ እንደ ሬት።
#ማርያምን !
ከድምፀትሽ ልቆ - 'ሚሰማ ሙዚቃ
ከአንባሰል ከባቲ ከብሉዝ ትዝታ
ወድያም ከብሉዙ ደግሞም ከአፍሪቃ
አንድም የለም በቃ !
#ማርያምን!
ካገኘሽ ጠቁሚኝ
ከሄድሽ ብትነግሪኝ.. .
ካንቺ ጋራ ስሆን ሀዘን ጭንቄን ሽሮ
የደስታ ወሰኔን አለቅጥ አንሮ
የሚገርመኝ የለም ከዓለሟ ተፈጥሮ!
ምንድናት ጨረቃ?
ምንድናትስ ፀሀይ ?
ካንቺ አንፃር ስትታይ.. .
ሀዋሳ ላንጋኖ.. . ቢሾፍቱ ሪዞርት
እውን ካንቺ በልጠው እኔን ሊያስደስቱኝ
ኸረ በማዬ ሞት !
#ማርያምን...
የቱ ኮሜዲ ነው የትኛው ቀልደኛ
እኔን የሚያደርገኝ የወሬው ምርኮኛ?
ደግሞ ካንቺ በላይ
እኔን ለማሳሳቅ ማነው የሚደፍረው ?
ባንቺ ጨዋታ ነው
የተደበቀውን.. . ጥርሴን የምገልጠው።
#ማርያምን !
እንደውም ባጭሩ.. .
አሁን ይሄ ግጥም
የቃላት ጥርቅም
እጅግ መሳጭ ሆኖ አንባቢው ቢያደንቅም
ካንቺ ግን አይበልጥም።
ማርያምን...
🔘ሚካኤል አስጨናቂ🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍10❤3
#የተጀመረ_አንጀት
በደል ያሰለለው
ጥቃት የበዛበት
የተገዘገዘ
የተጀመረ አንጀት
ባልጎለደፈ ቃል
ባልገረጀፈ ጣት
በስሱ ካልነኩት
በፍቅር ካልዳሰሱት
በስስት ካልያዙት
በእውቀት ካላገሙት
በበደል ፣ በጥቃት
ዳግም ከደፈቁት
ደፍቀው ከጓጎጡት
የተብሰከሰከ ፣ የተጀመረ አንጀት
እንኳንስ ሊቀጥል
ጥቂት ይበቃዋል ቆርጦ ለመለየት ።
🔘ጌትነት እንየው🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በደል ያሰለለው
ጥቃት የበዛበት
የተገዘገዘ
የተጀመረ አንጀት
ባልጎለደፈ ቃል
ባልገረጀፈ ጣት
በስሱ ካልነኩት
በፍቅር ካልዳሰሱት
በስስት ካልያዙት
በእውቀት ካላገሙት
በበደል ፣ በጥቃት
ዳግም ከደፈቁት
ደፍቀው ከጓጎጡት
የተብሰከሰከ ፣ የተጀመረ አንጀት
እንኳንስ ሊቀጥል
ጥቂት ይበቃዋል ቆርጦ ለመለየት ።
🔘ጌትነት እንየው🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍7❤6
#ፍሰሽ
ፍሰሽ በአካላቴ እንደ ወንዙ ፍሳሽ
ወስዶ እንደሚሄደው ልክ እንደ ደራሽ
ውሰጂኝ ውሰጂኝ አስምጪኝ በሞቴ
ይነከር በፍቅርሽ ይራስ ሰውነቴ።
✍??
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ፍሰሽ በአካላቴ እንደ ወንዙ ፍሳሽ
ወስዶ እንደሚሄደው ልክ እንደ ደራሽ
ውሰጂኝ ውሰጂኝ አስምጪኝ በሞቴ
ይነከር በፍቅርሽ ይራስ ሰውነቴ።
✍??
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤5👍3
#ይቅር_ታ
በትንሽ ጭንቅላት
በእንጭጭ ልቦና ፥የተጣሉ ለታ፤
ዳግም ለመመለስ
ከሰማይ ከፍ ያለ፥ዳገት ነው ይቅርታ!
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
በትንሽ ጭንቅላት
በእንጭጭ ልቦና ፥የተጣሉ ለታ፤
ዳግም ለመመለስ
ከሰማይ ከፍ ያለ፥ዳገት ነው ይቅርታ!
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍8❤3
#ላምላክህ_ላምላኬ!
ጀሊሉ ይዳብስህ - ይበርቱ ክንዶችህ
የማርያም ልጅ ደርሶ - ያቁምህ በእግሮችህ!
እግዜር በሽታህን - ይንቀለው ከገላህ
ፈውስ ያውርድልህ - የታመንከው አላህ!
ያደከመህ ይድከም - ይራገፍ በሽታህ
በገጽህ ላይ ይፍሰስ - ይመለስ ፈገግታህ!
ታሞ ተኛ ሲሉኝ - ላፍታ ተንበርክኬ
እንዲህ ነው የጸለይኩ - ላምላክህ ላምላኬ!!
🔘ዘውድአለም ታደሰ 🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
ጀሊሉ ይዳብስህ - ይበርቱ ክንዶችህ
የማርያም ልጅ ደርሶ - ያቁምህ በእግሮችህ!
እግዜር በሽታህን - ይንቀለው ከገላህ
ፈውስ ያውርድልህ - የታመንከው አላህ!
ያደከመህ ይድከም - ይራገፍ በሽታህ
በገጽህ ላይ ይፍሰስ - ይመለስ ፈገግታህ!
ታሞ ተኛ ሲሉኝ - ላፍታ ተንበርክኬ
እንዲህ ነው የጸለይኩ - ላምላክህ ላምላኬ!!
🔘ዘውድአለም ታደሰ 🔘
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤15👍1
#የፍርሃት_ሽንቁር
በስግብግብ ህይወት
የባርያ ዓለም ግዞት፤
ስንቱን አፍሪቃዊ
ሀሳቡን ገንዞት፤
ገመናው ተገልጦ
ጠመንጃ አሳርዞት!
ከኖረ ከኖረ ከኖረ በኋላ
ጨቁኖ ከያዘው የባሪያነት ዱላ፤
ሂድ ወደአለምክበት
ተብሎ በገዢው ከተፈታ ኋላ፤
በእንግዳ ነፃነት
መድረሻው ጠፍቶበት
ይኸው ይኳትናል ነፍሱን እየበላ!
ይሄ አፍሪቃዊ
በዘመን ባርነት
በአስተሳሰብ ውጥረት ተፍቆ ቀለሙ፤
በበርሃ ቀርቶ
በባህር ውስጥ ገብቶ ለሚጠፋ ስሙ፤
በህልም ዓለም ትብታብ
ወድቆና ቆሽሾ ተሰባብሮ ቅስሙ፤
ታሪኩ ቆንጥጦት
ፍርሃት ሸምቅቆት
ተገልጦ አይቆምም ሽንቁር ነው ዓለሙ!
🔘አብርሃም ፍቅሬ🔘
በስግብግብ ህይወት
የባርያ ዓለም ግዞት፤
ስንቱን አፍሪቃዊ
ሀሳቡን ገንዞት፤
ገመናው ተገልጦ
ጠመንጃ አሳርዞት!
ከኖረ ከኖረ ከኖረ በኋላ
ጨቁኖ ከያዘው የባሪያነት ዱላ፤
ሂድ ወደአለምክበት
ተብሎ በገዢው ከተፈታ ኋላ፤
በእንግዳ ነፃነት
መድረሻው ጠፍቶበት
ይኸው ይኳትናል ነፍሱን እየበላ!
ይሄ አፍሪቃዊ
በዘመን ባርነት
በአስተሳሰብ ውጥረት ተፍቆ ቀለሙ፤
በበርሃ ቀርቶ
በባህር ውስጥ ገብቶ ለሚጠፋ ስሙ፤
በህልም ዓለም ትብታብ
ወድቆና ቆሽሾ ተሰባብሮ ቅስሙ፤
ታሪኩ ቆንጥጦት
ፍርሃት ሸምቅቆት
ተገልጦ አይቆምም ሽንቁር ነው ዓለሙ!
🔘አብርሃም ፍቅሬ🔘
❤5🔥2
#ሳንመጣ_ለመቅረት
አቤት የኛ ነገር
ዳገት ስንሻማ ከቁልቁለት ገባን
ቀኙን ስንፈልገው ከግራ ተጋባን
ማን መቶ ያግባባን?
በቃል አልባ ቅኝት በተስፋ ቃል ኪዳን
ከደገስነው ድግስ መራራ ሬት ቀዳን
ድግሱም አልቀና
አልጠገብን አልጠጣን ከቀዳነው እሬት
ይኸው ነጋ ጠባ
ማር ማር እንላለን ሳንወጣ ከምሬት
አቤት የኛ ነገር
ስንፈልግ ተጣጣን
ስንሸሽ ተቀጣን
ከመስከረም ጡቶች መከራ እየጠባን
በተራበ አንጀት ስንት በቀል አባን?
በታወረ አይናችን ስን ጊዜ አነባን?
የሆነውን ሁሉ
ያየነውን ሁሉ በማይችለው ቁጥር
አንድ ነን ሁልጊዜ ለዜሮ ስንጥር
መሰንበት ስንሻ ለመኖር ስንቃትት
በወጉ መሞትም ሆኖ አረፈው የክት
አሟሟቴን ይመር
የሚል ተረታችን ያኔ እናዳልተናቀ
ዘመን ቢቀያየር ዛሬ ተናፈቀ
ከዘመኑ በልጦ ቢንቀለቀል ግርሻት
ነገር ላይገናኝ ደጋግሞ በመሻት
ልክ እንደሁልጊዜው
በለመድነው ሙሾ በምናውቀው ተረት
መጣን ብለን እንሂድ ሳንመጣ ለመቅረት
✍ ??
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
አቤት የኛ ነገር
ዳገት ስንሻማ ከቁልቁለት ገባን
ቀኙን ስንፈልገው ከግራ ተጋባን
ማን መቶ ያግባባን?
በቃል አልባ ቅኝት በተስፋ ቃል ኪዳን
ከደገስነው ድግስ መራራ ሬት ቀዳን
ድግሱም አልቀና
አልጠገብን አልጠጣን ከቀዳነው እሬት
ይኸው ነጋ ጠባ
ማር ማር እንላለን ሳንወጣ ከምሬት
አቤት የኛ ነገር
ስንፈልግ ተጣጣን
ስንሸሽ ተቀጣን
ከመስከረም ጡቶች መከራ እየጠባን
በተራበ አንጀት ስንት በቀል አባን?
በታወረ አይናችን ስን ጊዜ አነባን?
የሆነውን ሁሉ
ያየነውን ሁሉ በማይችለው ቁጥር
አንድ ነን ሁልጊዜ ለዜሮ ስንጥር
መሰንበት ስንሻ ለመኖር ስንቃትት
በወጉ መሞትም ሆኖ አረፈው የክት
አሟሟቴን ይመር
የሚል ተረታችን ያኔ እናዳልተናቀ
ዘመን ቢቀያየር ዛሬ ተናፈቀ
ከዘመኑ በልጦ ቢንቀለቀል ግርሻት
ነገር ላይገናኝ ደጋግሞ በመሻት
ልክ እንደሁልጊዜው
በለመድነው ሙሾ በምናውቀው ተረት
መጣን ብለን እንሂድ ሳንመጣ ለመቅረት
✍ ??
#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።
👇Sebscribe
YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
❤11🔥1