አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
569 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ትንግርት


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ

ሀዋሳ

ሁሴን ወደ ሲዩዘርላንድ ከበረረ ሀያ ቀን አልፎታል፡፡ያለፉትን ሀያ ቀናት የእሱንም ቦታ ተክታ ለስራው ከላይ እታች በመሯሯጥ ብታሳልፍም ከናፍቆት ግን ማምለጥ አልቻለችም፡፡አዎ ሁሴን ባልተለመደ መልኩ በጣም ናፍቋታል፡፡እራሷን በሌላ ሰው ህልውና ላይ ይሄን ያህል መለጠፍ አትፈልግም ነበር፤ምንም ቋሚና ዘላቂ ነገር እንደሌለ ህይወት ደጋግማ አስተምራታለች፡፡የእኔ የምትለው ነገር ሁሉ አንድ ቀን በሰላምም ሆነ በአደጋ ብቻ በሆነ ምክንያት እንደሚለያትና ለዛም ዝግጁ ሆና መጠበቅ እንዳለባት የዘወትር መፈክሯና መመሪያዋ ነበር፡፡አሁን ግን መልሳ ደከመች፤እናም ባሏ ናፈቃት፡፡እለቱ ሰንበት ስለሆነ የቤቷ ሳሎን ሶፋ ላይ ጋደም ብላ ቴሌቪዢን እየተመለከተች ነው፡፡
አይድል ፕሮግራም..በሀዋሳ የሚካሄድ የማጣሪያ ውድድር እየተመለከተች ነው፡፡

በአብረሀም ወልዴ የሚመራው የዳኞች ቡድን
የዳኝነት ቦታቸውን ይዘዋል፡፡ተወዳዳሪዎች በቅደም ተከተል ወደ መድረክ እየወጡ የተዘጋጁበትን ዘፈን በመዝፈን ተፈጥሮ
የቸረቻቸውን ድምጽና በጥረታቸው ያደበሩትን
ችሎታ በማዋሀድ ዳኞቹንም ሆነ ተመልካቾችን
በማሳመን ለአዲስአበባው ውድድር ለማለፍ ይጥራሉ፡፡ጥቂቶች ይሳካላቸዋል ፤ሌሎቹ ደግሞ አንገት ደፍተውና ፈዘው ከመድረኩ
ይሰናበታሉ፡፡ትንግርት ሁሌ ይህን ፕሮግራም ስታይ ድብልቅልቅ ያለ ስሜት ነው የሚሰማት፡፡

ዘና የሚያደርገት እንዳለ ሁሉ የሚያሳዝኗትም
ተወዳዳሪዎች አሉ፡፡ከችሎታቸው በላይ
ጉጉታቸው የናረ፣ብዙ ተስፋ አድርገው መጥተው በዳኞቹ ቁርጥ ያለ ሞያዊ
አስተያየት ሽምቅቅ የሚሉ ወጣት ጨቅላዎች፤ ያሳዝኗታል፡፡ችሎታው እያላቸውም ፍራቻቸውን ብቻ ማሸነፍ ተስኗቸው ያላቸውን ነገር መግለጽ ባለመቻላቸው አጉል የሚሆኑም አሉ፤እነሱም ያሳዝኗታል፡፡

...አሁን ግን እያየች ያለቻው ድንቅና የሚያስደምም ችሎታ ነው፡፡አስር ሁለት አመት የማይበልጣቸው ሁለት ሴት ልጆች ናቸው የሚታዩት፡፡አንደኛዋ ጊታሯን ይዛ የተዘጋጀላት መቀመጫ ላይ ተቀመጠችና በጣቶቿ የጊታሩን ክሮች በመነካካት ፈታተሸች፤ሌለኛዋ ከፊት ለፊቷ በሜትሮች ርቀት ማይኩን ይዛ ::

አብረሀም ወልዴ መናገር ጀመረ....

‹‹እሺ እንኳን በሰላም መጣችሁ እያልኩ እራሳችሁን እንድታስተዋውቁ ዕድሉን ልስጣችሁ ፡፡››

‹‹ስሜ ሀሊማ ታዲዬስ ይባላል፡፡ የምጫወትላችሁ የተፈራ ካሳን ‹አባብዬ› የሚለውን ዘፈን ነው፡፡››

‹‹አሪፍ ነው፡፡ባለጊታሯስ ስምሽ ማነው ?››

‹‹ስሜ ሄለን ታዲዬስ ይባላል፤ጊታርና ፒያኖ ተጨዋች ነኝ።

<<እህት አማቾች ናችሁ ?››አረጋኸኝ መሀከል ገብቶ ጠየቀ፡፡

‹‹አዎ እህቴ ናት፡፡››

ይሄ ሁሉ ሲሆን ትንግርት ስትከታተል የነበረው በግማሽ ልቧ ነበር፡፡እህትማማቾች ነን ሲሉ ግን ትንሽ ግር አላት፡፡በእኩል ዕድሜ ላይ ናቸው፡፡የትኛዋ ታላቅ የትኛዋ ደግሞ ታናሽ ትሆን? ስትል እራሷን ጥያቄ ጠየቀች፡፡ ደግሞ ምናቸውም አይመሳሰልም <<የእናት ሆድ ዥንጉርጉር›› ይባል የለ ብላ ለራሷ መልስ ሰጠች፡፡

‹‹በሉ ቀጥሉ..መልካም ዕድል፡፡››ከዳኞቹ ፍቃድ አገኙ፡፡

ሄለን እነዛ ቀጫጭንና ለጋ ጣቶቾን የጊታሩ ክሮች ላይ ማርመስመስ ጀመረች ፡፡ የሙዚቃ መሳሪያውን ምት ተከትሎ የሀሊማ ተስረቅራቂና ማራኪ ድምጽ ይንቆረቆር ጀመር፡፡ በአዳራሹ የሞላው ተመልካች ብቻ ሳይሆን በየቤቱ በቲቪ ፕሮግራሙን የሚከታተለው ህዝብም ፀጥ የሚያሰኝ አደንዛዥ ድምጽ ነበር፡፡በዚህ ዕድሜ በእንዲህ አይነት ችሎታ? እንዴት ነው በዚህ ዕድሜ የሙዚቃ መሳሪያን ስልተ-ምት ጠብቆ ስይደናገሩና ሳይንሸራተቱ በዚህ ልክ መዝፈን የቻሉት?፡፡

ዳኞቹ ሳይቀር አፋቸውን ከፈቱ፡፡ደግሞ በሙዚቃው ሁለቱም ጉንጮች ላይ እንባ እየተንጠባጠበ ነው፡፡ሲጨርሱ የአዳራሹ ሰው ሁሉ አረንጎዴ ካርዱን እያወዛወዘ ከመቀመጨው ተነሳ፡፡ደኞቹም እያጨበጨቡ ቆሙ .. መድረክ ድረስ በመሄድ በየተራ አቅፈው ሳሟቸው፡፡

አስተያየት መስጠት ተጀመረ..የመጀመሪያው ዳኛ

‹‹በእውነት ሀዋሳ እናንተን የመሰሉ ባለድንቅ ችሎታ ሙዚቀኞችን ስላፈራች እድለኛ ነች፡፡

እኛም እዚህ መጥተን እናንተን ስላገኘን እድለኞች ነን፤በቃ ልዩ ናችሁ፡፡››

ሁለተኛው ዳኛ…..

‹‹ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡፡ሙዚቃው ከህይወታችሁ ጋር የሚያይዘው ጉዳይ አለ? ሁለታችሁም ስታለቅሱ ነበር፡፡እኔንም አስለቅሳችሁኛል፡፡ምከንያት ነበራችሁ?››

ሀሊማ መናገር ጀመረች‹‹አዎ ሁለታቸንም አባታችንን በጣም እንወደዋለን፡፡እርግጥ ሁሉም ሰው አባቱን በጣም ይወዳል፡፡እመኑን የእኛ አባት ግን ልዩ ሰው ነው፡፡›› አዳራሹ በሳቅና በጭብጨባ ተናጋ፡፡

ሄለን ቀጠለች‹‹ታዲያ አንተ አባታችን ባትሆን ኖሮ እኛ ዛሬ እንዲህ አምሮብን ሙዚቃ እየተጫወትን እንዲህ አዳራሽ ሙሉ ህዝብ እያጨበጨበልን አንታይም ነበር.፡፡ምክንያም እድሉም ጊዜውም አይኖረንም ነበር፡፡አዎ አባት ባትሆነን ኖሮ ይሄኔ ሁለታችንም አሞራ ገደል
አካባቢ ከሚገኝ ቆሻሻ መጣያ ገንዳ ውስጥ ተበላሽቶ የተጣለ ምግብ ከቆሻሻው በመለየት በመመገብ ላይ ነበርን፡፡…እና ከእንደገና ስለፈጠርከን አመሰግናለሁ ...ታዲ እንወድሀለን፡፡››

ዳኞቹም ታዳሚዎቹም ከልጆቹ ችሎታ በላይ በንግግራቸው ድንግርግር እንዳሉ ፊታቸውን በመመልከት ማወቅ ይቻላል፡፡

‹‹እባክህ አቶ ታዲዬስ እዚህ አዳራሽ ውስጥ ካላህ ወደ መድረክ ወጥተህ አንድ ነገር በለን››ከዳኞቹ መካከል አንድ ተናገረ፡፡ በአዳራሹ ያላው ታዳሚ እርስ በርሱ ዞር ዞር በማለት መተያየት ጀመረ፡፡ከመቀመጫው ተነስቶ ወደ መድረክ የሚወጣ ሰው ለመመልከት፡፡

‹‹ታዲ ና እንጂ››ሄለን ከመድረክ ተማፀነች፡፡

የሁለት ልጆች አባት ሳይሆን ተደባበዳቢ ቦዴ ጋርድ የሚመስል ጠይም ደንዳና ወጣት ወደ መድረኩ ወጣና ሁለቱንም ልጆቹን አቅፎ
ጉንጮቻቸውን ከሳመ በኃላ ማይኩን ተቀብሎ መናገር ጀመረ፡፡‹‹ታዴዬስ ማለት እኔ ነኝ፡፡ልጆቼ

ስለእኔ ያሉት ትንሽ ተጋኗል፡፡እውነታው በተቃራኒው ነው፡፡እነሱ ልጆቼ በመሆናቸው
በአሁኑ ወቅት በአለም በጣም እድለኛው ሰው
እኔ ነኝ፡፡ምን አልባት ችሎታቸውን አይታችሁ
ስታጨበጭቡላቸው ነበር፡፡ግን እመኑኝ መድረክ የመጀመሪያ ቀናቸው ስለሆነ የችሎታቸውን ግማሽም አላሳዮችሁም...እናም
ሁላችሁም እዚህ አዳራሹን የሞላችሁ ሁሉ ብትቀኑብኝ አይገርመኝም፡፡ምክንያቱም እኔ የእነዚህ ዕንቁ ልጆች አባት ነኝ፡፡አመሰግናለሁ፡፡>> ብሎ ወረደ፡፡ፕሮግራሙ ቢያልቅም ትንግርት
ስለልጆቹም ሆነ ስለአባትዬው ልትረሳ
አልቻለችም፡፡የሆነ ያልተለመደ ነገር ነው
የሆነባት፡፡<<አባታችን ባትሆን የቆሻሻ ገንዳ ላይ
ምግብ እንለቃቅም ነበር›› ሲሉ ምን ማለታቸው ነው?ግን የእውነት አባታቸው ነው ?

አልመሰላትም፡፡እንዴት አድርጎ ቢያሳድጋቸው
ነው በዚህ መጠን ሊወዱት የቻሉት?እውነትም
እሱ እንዳለው የሚቀናበት አባት ነው ? አለችና ቲቪውን አጥፍታ አየር ለመቀበል ቤቷን ለቃ ወደ ውጭ ወጣች፡፡

ይቀጥላል

አሁንም ዩቲዩብ ቻናል  #ሰብስክራይብ እያደረጋቹ አበረታቱን ቤተሰቦች እያደረጋቹ አደለም በየቀኑ ለመልቀቅ እየሞከርኩ ነው እናንተም ማበረታታችሁን ቀጥሉ አመሰጎናለሁ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronose
👍12214👏3🔥1
#ቤርሙዳ_ዘ_ካሳንቺስ


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ:
….

‹‹ምነው አልክ..?ፒጃማ የለህም እንዴ?››

‹‹አለኝ ግን በማሳጁ ምን ያህል ብቁ ሆነሻል.ስልጠናውስ እንዴት ነበር? የሚለውን ማወቅ እፈልጋለሁ…››

‹‹ተው… እርግጠኛ ነህ?››

‹‹አዎ ምነው ፈራሽ አንዴ.?ነው ወይስ በብቃትሽ አትተማመኝም? እንዳዛ ከሆነ ይቅር፡› ብሎ ፊቱን ወደቁምሳጥኑ መልሶ ሊራመድ ሲል እጁን ለቀም አደረገችውና‹‹መፍራት ያለብህማ አንተ ነህ…ትዝ ይልሀል ያን ቀን ቤትህ አታለህ አስገብተኸኝ የዋህነቴን ተጠቅመህ እዛ የማሳጅ ጠረጴዛ ላይ አስተኝተህ እንዴት እንደተጫወትክብኝ ያንን መበቀል መቻል አለብኝ፡፡›› ብላ እየጎተተች ወደ ማሳጅ ጠረጴዛው ወሰደችና በጀርባው እንዲተኛ አደረገችው፡፡

ከዛ በቅርብ ካለው ቅባት ወደተኮለኮለበት ጠረጴዛ በመሄድ አንዱን መርጣ አነሳችና ጀርባው ላይ አፈሰሰችበትና ከላይ ከጆሮ ግንዱ ጀምራ እስከታች የእግር ጣቶቹ ድረስ በወሰደችው ሰልጠና መሰረት የተለያዩ ቴክኒኮችን በመጠቀመ እያገለባበጠች ለአርባ ደቂቃ ካሸችው በኃላ እጅግ በሚገርም ሰመመንና መመሰጥ ውስጥ ገብቶ ከተዝለፈለፈ በኃላ እንደምንም ከጠረጴዛው ላይ አስነስታ ወለሉ ላይ ዘረረችው…. ከዛማ ቀሚሷን ወደላይ መዥርጣ አውልቃ ከጎኑ ተኛች…ከዛ በኋላ የነበረውን ለማሰብም ይከብዳታል…ያንን ሰፊ የመኝታ ቤት ወለል እየተንከባለሉበት አንዴ የአልጋው ጠርዝ ሲገጫቸው፤አንዴ ከጠረጴዛው እግር ጋር ሲላተሙ አንዴ ስትገለብጠው….ከዛም ሲገለብጣት ከ30 ደቂቃ ቆይታ በኋላ ነበር መጀመሪያ እሱ ከዛ ከ5 ደቂቃ ያህል ዘግይታ እሷ ጡዘት ላይ የደረሱት…፡፡

ከዛ እንደምንም.ተላቀው ወዲህና ወዲያ የነበሩበት ወለል ላይ የተዘረሩት.. ከ7ደቂቃ እረፍት በኋላ እሷ እንደምንም ከተዘረረችበት ተነስታ እየተሳበች ወደሻወር ቤት ሄደች….ውሀውን በላይዋ ላይ ለቀቀች…በሁሉም ነገር በጣም ረክታለች.. የዚህ ወሲባዊ ተራክቦ መሪ እሷ ነበረች.. እርግጥ ያ በግልፅ ለእሱ እንዲሰማው አላደረገችም ቢሆንም እያንዳንዷን ቅንጣት በንቃት አጣጥማታለች፡፡ ከ10 ደቂቃ በኃላ ፎጣዋን አገልድማ ወደመኝታ ቤቱ ስትመለስ ደምሳሽ ጥላው በሄደችበት ወለል ላይ ተዘርሮ እንደተኛ እንቅልፍ ወስዶታል፡፡ እየሳቀች  ወደእሱ  ቀረበችና በእግሯ ወዘወዘችው..

‹‹ደምሳሽ…እረ ተነስ ሻወር ውሰድና እንተኛ››

‹‹እንዴ... አንቺ ምን አደረግሺኝ?›› እያለ እደምንም ተነሳና ወደ ሻወር ቤት ገባ፡፡

እሷ ሰውነቷን በሎሺን አባበሰችና  አልጋ  ላይ  ወጥታ  ከአንገቷ  ቀና  በማለት ትራስ ተደግፋ ታጥቦ እስኪመጣ በንቃት ትጠብቀው ጀመር….እሱ 5 ደቂቃ አልፈጀበትም፡፡ፎጣውን አገልድሞ ወጣ…

ቁጭ ብላ ሲያያት ‹‹እንዴ ምነው አተኚም እንዴ?››

‹‹ምነው? አንዴ አንደግምም?››አለችው እየሳቀች፡፡

ሰውነቱን የጠቀለለበትን ፎጣ ከላዩ አነሳና የረጠበ ጸገሩን እያደራረቀ‹‹ምነው በቀል ቢሉሽ እንዲህ በአንድ ቀን ሙሉ በሙሉ ማውደም ነው እንዴ.? ቀስ እያልሽ አይሻልም?››አለና እሱም እንደእሷ አልጋ ላይ ወጣ…ከውስጥ ገብቶ ተኛ፡፡
‹‹ችግር  የለም …ዋናው እጅ መስጠትህ ነው››

‹እረ እጅ ሰጥቼያለሁ…በነገራችን ላይ የማሳጅ ችሎታሽ በጣም አስገራሚ ነው የሆነብኝ….ለረጅም አመት በስራው ላይ የቆየሽ እኮ ነው የምትመስይው… በራስሽ ካላበላሸሽው በስተቀር በቀላሉ ውጤታማ እንደምትሆኚ በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ››

‹‹ይሄን ያህል?››

‹‹የምሬን ነው በጣም ነው ያስደመምሺኝ.. ሶስትና  አራት  አመት  በስራው  የቆዩ እንኳን ያንቺን ያህል በጥበብ እና በእውቀት አይሰሩም….አንቺ በዚህ ላይ  ሶስት አራት ወር ልምድ ካከልሺበት በቃ ልዩ ነው የምትሆኚው፡››

‹‹ለአድናቆትህ በጣም ነው የማመሰግነው..ግን ምነው አድናቆትህ ማሳጁ   ላይ ብቻ ሆነ ..ሌላው እስከዚህም ሆነብህ ማለት ነው?፡፡››

‹‹ትቀልጂያለሽ አይደል…? በወሲብ ልምዴ እንዲህ አቅሌን ስቼ ስዘረር የመጀመሪያ ገጠመኜ ነው…ብቻ  ድንቅ ተማሪ ነሽ.. የመጀመሪያ  ጊዜ ወሲብ  ስናደርግ..ትኩስ እና ሞቃት ነበርሸ ቢሆንም አብዛኛውን ነገር ለእኔ ነበር አሳልፈሽ የሰጠሸው…ዛሬ ግን እኔ ባሪያሽ ሆኜ ነበር፡፡ በአጠቃላይ በሁሉም ዘርፍ ነው የተቀየርሽው….ምን አልባት ተሰጥኦሽን ይሆናል ያገኘሽው፡፡

‹አንተ እየሰደብከኝ ነው እንዴ…? የታደሉት በስዕል ችሎታቸውና በሙዚቃ ብቃታቸው የተፈጥሮ ታለንታቸውን አገኙ ይባላል…እኔን በወሲብ?፡፡›

ሁሉን ነገር በጥበብና በእውቀት ከከወንሽው አርት ነው…ተሰጥኦ ነው፡፡ እንዴ ትቀለጂያለሽ እንዴ ለአንድ ሴት አርክቶ በእኩል ሰዓት  መርካት  መቻል  እራሱ ድንቅ መሆንን ይጠይቃል፡፡ ብዙ ጊዜ አንዱ አንዱን ለማስደሰት ምን ይህል እንደሚሰቃይ አታውቂም፡፡ ወንድ ልጅ ደግሞ አንዲትን ሴት ሲቀርብ  እሷም ሴትነቷን በሚፈልገው መጠን እንዲህ እንደ አንቺ በገለጠችለትና ይበልጥ በእሷ እየተደሰተና እየረካ በሄደ መጠን ነው ቀን ከቀን ይበልጥ በእሷ እየተሳበ እና በአካሏ ብቻ ሳይሆን መላ እሷነቷን እየወደዳትና እየተቀበላት የሚሄደው፡፡

‹‹እሺ ለማንኛውም ነገ ወደ ወሳኙ ተግባራዊ ፈተና የምሰማራበት ቀን  ስለሆነ ደክሜ  መገኘት አልፈልግም፤ እንተኛ  ለዚህ  ድንቅ  ልብ  አቅልጥ  አስተያየትህ ግን አልፎ አልፎ ያው እቸገርልሀለሁ›› አለችው፡፡

ተንጠራርቶ መብራቱን እያጠፋ‹‹በነገራችን ላይ የዛሬው አዳራችን ምን አልባት የስንብት ሊሆን ይችላል?››ሲል ነበር ያረዳት፡

የእውነት ከልቧ ደንግጣ ተነስታ ቁጭ አለች‹‹ምን ማለት ነው?››

‹‹ከዚህ በፊት ነግሬሽ የለ…ልጄን ፍለጋ ወደአሜሪካ እንደምሄድ አሁን ፕሮሰሱ ሁሉ.አልቆልኛል...ቪዛም አግኝቼያለሁ….ከአራት ቀን በኋላ እበራለሁ››

‹‹ምን አይነት ጨካኝ ሰው ነህ ግን…? እንዴት አራት ቀን እስኪቀረው ድረስ ሳትነግረኝ?››

‹‹ከባድ ስልጠና ላይ ስለነበርሽ ልረብሽሽ አልፈለኩም ነበር…››አላት፡፡

‹‹በፈጣሪ…ግን  ቶሎ ተመልሰህ ትመጣልህ አይደል?››

‹‹ስለእሱ ምንም የማወራው ነገር የለም….ልጄን ካገኘሁ በኋላ በቀጣይ ባለው ሁኔታ ላይ የተመሰረተ ነው፡፡››
‹‹ያ ማለት አስከወዲያኛውም ላትመጣ ትችላለህ ማለት ነው?››
       ቁዝዝ ብሎ‹‹አዎ ላልመለስ እችላለሁ››አላት፡፡
ተመልሳ ተኛች…እሱም ተኛ…ተቃቅፈው ….እሷ  ይሄን  የመሰለ  መከታ  የሆነ ወዳጅ እንዲህ በድንገት እብስ ብሎ ከእጇ ሊያመልጥ መሆኑን ስታውቅ ሆዷን ባር  ባር  አላት… በጣም  ከፋት…ሰሰተችው….ገና  ከመሄዱ   በፊት ከአሁኑ ናፈቃት... ግን እርቃኑ ከእርቃኗ ተጣብቆ እቅፉ ወስጥ  ገብታ  ትንፋሿ ሲገርፈው ዝም ብሎ መተኛት አልፈለገም … እሷም  በተመሳሳይ…  ለሁለተኛ  ዙር  ፍልሚያ ገቡ፡፡

ጠዋት 12 ሰዓት ነበር ከእንቅልፉ ነቅቶ መኝታውን በመልቀቅ ወደ ኪችን የገባው፤ጥሩ ቁርስ ሰራና አንድ ሰዓት ሲሆን ቀሰቀሳት…ሶስት ሰዓት ስልጠና የምትወስድበት ቪላ ቤት ጋር አድርሷት አንኳኩታ ወደውስጥ ስትገባ…እሱ ወደሌላ ስራው ሄደ፡፡

ስልጠና ቦታዋ ስትደርስ ማንም አልነበረም።ግራ ገባት...አብረዋት የሚሠለጥኑት ተፎካካሪዎቿን ደውላ መጠየቅ አትችልም። ስልክ ቁጥራቸው  አልነበራትም። አሰልጣኟ  ጋር  ደወለች። አይሰራም። ምን  ተፈጠረ?"ሰገን  ጋር ደወለች። ጎሽ ይጠራል "አለችና ጆሮዋ ላይ ለጠፈች። ዝም ብሎ ይጠራል አይነሳም።

ሊዘጋ ሲል። "ምነው ፈለግሺኝ እዚህ ነኝ" የሚል  ድምፅ  ከጀርባዋ  ሰማች። በፈገግታ ዞር አለች።

"ግቢው ባዶ ሲሆንብኝ ግራ ገብቶኝ ነው"
👍727👏2
#ጉዞ_በፀሎት
(አቃቂ እና ቦሌ)


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#በዘሪሁን_ገመቹ_ዋቤ
፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧፧

ጨጓራው ሲለበልበው ይታወቀዋል…በቃ ውስጡ እየነደደ ነው…አሁን ምንም የማያውቀውን አዲስ ነገር አልነገረችውም…ምን እንዳበሳጨው ለራሱም አልገባውም….ሌላ ቢራ ከፈተና አንደቀደቀው…ስልኩን ደግመኛ አነሳና ደወለ…

‹‹ሄሎ ሶል ምነው?››

‹‹እባክሽ ስለሆነ ነገር ላማክርሽ ነበር… እኔ ክፍል ድረስ መምጣት ትችያለሽ?››

‹‹መቼ አሁን?››በመገረም ጠየቀችው፡፡

‹‹አዎ አሁን››

‹‹እሺ በቃ መጣሁ››

‹‹ስልኩን ዘጋና ከተቀመጠበት ተነሳ…መልሶ ቁጭ አለ‹‹ሰለሞን ምን እያደረክ ነው…?በዚህ ሰአት ስለምን ጉዳይነው የምታወራት.?›እራሱን በብስጭት ጠየቀ፡‹‹፡መልሼ ደውዬ በቃ ተይው ነገ ይደርሳል ማለት አለብኝ..››ወሰነና ስልኩን አነሳ….ቁጥሩን ከመጫኑ በፊት የመኝታ ቤቱ በራፍ ተቆረቆረ…..

ስልኩን ወደ አልጋው ወረወረና ተንደርድሮ ሄዶ ከፈተላት…በፀሎት ሮዝ ቀለም ያለው ስስና ልስልስ ቢጃማ ቀሚስ ለብሳለች… ፀጉሯን ወደላይ ጠቅልላ በሻሽ አንድ ላይ ጠፍራ አስራዋለች…ውብና መራኪ ሆና ነው እየመጣችው …ወደውስጥ ዘልቃ ገባች‹‹….ምነው በሰላም ነው…?አስደነገጥከኝ እኮ››

ፊት ለፊቷ ተገትሮ ቆመ….ግራ ገባት
‹‹ሶል ምን ሆነሀል…?.ምንድነው የምትነግረኝ?››ጉጉትና ፍራቻ በተቀየጠበት ስሜት ጠየቀችው፡፡

ተንደረደረና በሁለት እጆቹ አገጯን ግራና ቀኝ ክንዶን ይዞ ወደእሱ አስጠጋት… ከንፈሯ ላይ ተጣበቀ….በቀላሉ አለቀቃትም…ምን ይህል ደቂቃ እንደተሳሳሙ ሁለቱም አያቁም …ምን አልባት አንድ ደቂቃ ሊሆን ይችላል …ምን አልባትም ዘላለምም ሊሆን ይችላል….ግን የሁለቱም ልብ በየውስጣቸው ሲንፈራፈር ታውቋቸዋል…ሁለቱም በአየር ላይ የሚንሳፈፉበት ክንፍ እንዳበቀሉ አይነት ስሜት ተሰምቷቸዋል….ለሁለቱም ያልተጠበቀና ልዩ ክስተት ነበር….ሁለቱም ደግሞ ከገዛ ራሳቸው ጋር እንኳን ተነጋግረው ሳይወስኑ በነገሩ መሆን ተስማምተው በደስታ ፈንጥዘዋል፡፡በፀሎት አራት ተኩል ላይ ሰለሞን ክፍል የሄደች ስድስት ሰዓት ሲሆን ነበር ወደክፍሏ የተመለሰችው፡፡እሱንም ለሊሴ ምን ትለኛለች የሚል ይሉኝታ ቀፍድዷት እንጂ እዛው እቅፉ ውስጥ ሟሙታ እየቀለጠች ቢነጋ ደስ ይላት ነበር፡፡እሱም እንደዛው፡፡
በማግስቱ እስከአራት ሰዓት ከአልጋቸው መውረድ አልቻሉም ነበር፡፡

‹‹ልጁ ምን ይለናል ብዬ ነው እንጂ ቀኑን ሙሉ ከዚህ አልጋ ባልወርድ ደስ ይለኝ ነበር››ወ.ሮ ስንዱ ተናገሩ
‹‹ከአልጋው መውረድ ነው ወይስ ከእኔ እቅፍ መውጣት ነው ያስጠላሽ?››

‹‹አንተ ደግሞ…ለምን ታሳፍራኛለህ?››
‹‹ይሄውልሽ ነገ ወደአዲስአበባ እንመለስ የለ ..የልጃችንን የንቅለተከላ የተደረገላትን አመታዊ የመታሰቢያ በአል ድል አድርገን ከደገስን እና አንዳንድ ነገሮችን ካስተካከልን በኃላ..ለአንድ ወር ሲዊዘርላንድ እንሄዳለን፡፡›

‹ማ እና ማ?››

‹‹እኔ እና አንቺ..፡፡ያው አሁን ዳግመኛ እንደተጋባን እና ጉዞውንም ልክ እንደጫጉላ ሽርሽር ቁጠሪው››

‹‹በጣም አጓጓኸኝ ..ግን እኮ ይሄ ያለንበትም ስፍራ ከሲዊዘርላንድ አይተናነስም››

‹‹ገባኝ… ግን ራቅ ብዬ ካንቺ ጋር መጥፋት ነው የምፈልገው…››

‹‹ውይ የፍቅር ግርሻ እኮ መጥፎ ነገር ነው…ግን እንደምታየው ከልጄ ጋር ላለፈው አንድ ወር አልተገናኘሁም…እኔ ለሌላ አንድ ወር ከእሷ ውጭ ማሳለፍ አልችልም››

‹‹አንቺ ደግ…በቃ ይዘናት እንሄዳለን…ሶስታችን እንደቤተሰብ ከእንደገና አብርን በፍቅር እንቆማለት….›

‹‹እሱ ያስማማኛል፡፡››አሉና ከአልጋቸው ላይ ወረዱ…ተጣጥበውና ተዘጋጅተው ከክፍላቸው ሲወጡ አምስት  ሠዓት ሆኖ ነበር፡፡የሰለሞንን ክፍል ሲያንኳኩ አልነበረም…ደወሉለት

..በደቂቃዎች መጣላቸው፡፡

‹‹እንዴት ነበር አዳር?››

‹‹ዕድሜ ላንተ ሁሉ ነገር ውብና ማራኪ ነበር››አቶ ኃይለልኡል መለሱ፡፡

‹‹ጥሩ …አሁን እርግጠኛ ነኝ እርቦችኃላ?››

‹‹አዎ …የራበን ይመስለኛል›››

‹‹በሉ ተከተሉኝ …ቆንጆ ቁርስና ምሳ አንድ ላይ እንዲዘጋጅላችሁ አድርጌለው…››ብሎ ይዟቸው ሄደ..፡፡

በቀይ መንጣፍ ያሸበረቀ ግዙፍ የሞጃ ሳሎን የመሰለ ክፍል ውስጥ ነው ይዞቸው የገባው….ልክ አዲስ ሙሽሮች እንደሚስተናገዱበት አዳራሽ ውብና ልዩ ተደርጎ ዲኮር ተደርጓል….ግዙፉ ጠረጴዛና ጠረጴዛውን የከበቡት ወንበሮች ከቆዳ የተለበጡ ውብና ልዩ ናቸው…ልዩ ልዩ ባህላዊ ቅርሶች ግድግዳው ሞልተውታል፡፡እየመራ ወሰደና ወንበሩን እየሳበ ሁለቱንም አስቀመጣቸውና ..ከፊት ለፊታቸው ዞሮ ቆመ….
‹‹አቶ ኃይለልኡልና ወ.ሮ ስንዱ…ዛሬ የመጨረሻ ቀናችን ነው፡፡ማለቴ ከአሁን በኃላ ያለውን ቤታችሁ ተመልሳችሁ መደበኛ ስራችሁን እየሰራችሁ የምናከናውነው ይሆናል፡፡እስከአሁን ላለው ግን በእውነት እናንተ ለእኔ ትልቅ ውለታ ስለዋላችሁልኝ ላመሰግናችሁ እወዳለው..ይሄንን ስራ ከልጃችሁ ከበፀሎት ስቀበል በከፍተኛ ፍራቻና በወረደ የራስ መተማመን ነበር…እናንተ ግን ለልጃችሁ ስትሉ ጠንክራችሁ አጠነከራችሁኝ….በሶስት ወርና በአራት ወር እፈተዋላው ያላልኩትን በመሀከላችሁ ያለውን ውስብስብ ችግር በአንድ ወር አዚህ ደረጃ እንዲደርስ አድርጋችሁ አስደመማችሁኝ..ይህ አንድ ወር ለእኔ ታላቅ ትምህርት

ያገኘሁበት ነው..በሀገራችን የማህበራዊ ስሪትና ባህል የጋብቻ አማካሪ ብሎ ዘመናዊ አሰራር ተግባራዊ ማድረግ ውጤታማ አይሆንም ተጠቃሚም አይኖርም ብዬ ተስፋ ቆርጬ ድርጅቴን ልዘጋ እያሰብኩ ባለሁበት ወቅት ነው የእናንተን ስራ ያገኘሁት…አሁን ግን ዘመናዊውን ሳይንስ በሀገራችን ተጫባች ሁኔታ አንፃር ቃኝተን በጥበብ ከተጠቀምነው የብዙ ውስብስብ ጋብቻዎችን ችግር ለመቅረፍ እንደሚቻልና ስራዬም ለማህበረሰቡ ጠቃሚ እንደሆነ እንድረዳ አድርጋችሁኛልና አመሰግናለው….በአጭር ቀናት ውስጥ ባሳያችሁት ውጤት ልጃችሁ ብቻ ሳትሆን እኔም ደስተኛ ነኝ፡፡
‹‹ልጄ ..አንተም እንደምትረዳው ወደእዚህ ጉዳይ ስንገባ ..አንተ ስለምትለው በእኔና ስንዱ መሀከል ስላለው ግንኙነት ማሻሻል ምንም አይነት ፍላጎትም ሆነ እምነት የለኝም ነበር…ልጄን ለማግኘት ስል ነበር ሳልወድ በግዴ የተስማማሁት…እያደረ ግን ሀሳቤን ሙሉ በሙሉ እንድቀይር አድርገሐኛል…ጋብቻዬ ጥሩ ባለመሆኑ ሕይወቴም ምን ያህል የተዛባ እና በጭንቀትና በሀዘን የተሞላ እንደሆነ እንዳስተውል አድርገሐኛል…እኔ ምን የህል አጥቼ ቤተሰቦቼንም ምን ያህል እንዳሳጣኋቸው እንዳስብና ወደቀልቤ እንድመለስ አድርገኀኛል..እኔ ነኝ አንተንም ሆነ ስንዱን ማመስገን አያለብኝ…በእውነት የእድሜ ልክ ባለውለታዬ ነህ…አንተ ከአሁን ወዲያ ልክ እንደልጄ ነህ….በማንኛውም ህይወት ጉዞህ እኔም ሆንኩ ቤተሰቦቼ ከጎንህ እንደሆን ልታውቅ ይገባል፡፡እርግጠኛ ነኝ ነገ ተነጋ ወዲያ አዲስአበባ እንደተመለስን ልጃችንም ወደቤቷ ትመለሰላች ብዬ ተስፋ አደርጋለው…እሷ ስትመለስ የተቀረውን ነገር እናወራለን፡፡››

ሰለሞን‹‹እሺ ጥሩ አሁን ስለራባችሁ …ከዚህ በላይ በወሬ አልያዛችው ››እጁን ሲያጨበጭብ ነጭ ዩኒፎርም የለበሰ አስተናጋጅ መጣ…..‹‹ምግብ ይቅረብ…መጀመሪያ የእጅ ውሀ አምጡ በላቸው››ሲል አዘዘው…ልጁ በቆመበት በራፍ ላይ ላሉት ልጆች ምልክት ሰጠው፡፡ውብ የሆነ ባህላዊ ነጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ወጣት ሴቶች ውብ የሆነ ወርቅ ቅብ ማስታጠቢያ በእጃቸው ይዘው መጡና….አንደኛዋ አቶ ኃይለልኡልን ሌለኛዋ ወ.ሮ ስንደን ለማስታጠብ ጎንበስ አሉ…ሁለቱም ታጥበው..ቀና ሲሉ በተመሳሳይ ቅፅበት ነው የአንደኛዋ ፊት
👍8415
#የድንግሊቷ_አፍቃሪዎች
:
:
#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ
================

‹‹እሺ ቻው ሁሴን…››ስልኩን ዘጋ፡፡ፈጽሞ ያልጠበቀው ነገር ነው፡፡ድብልቅልቅ የሆነ የሚረብሽ አይነት ስሜት ነው እየተሰማው ያለው፡፡ደስታም መረበሽም ….አሁንም ሶስቱም  አንድ ላይ ተገናኝተው  ሰሎሜን ከበው ሲቀመጡ ምን እንደሚሰማቸውና ምንስ ሊፈጠር እንደሚችል መገመት አልቻለም፡፡

እርግጥ አሁን እንደድሮው አይደለም ሰሎሜ የአላዛር ህጋዊ ሚስት ሆናለች፡፡ግን ደግሞ በመሀከላቸው ያለው ሸለቆ ስምጥና  እሩቅ ነው፡፡እና አላዛር ከበሽታው ማገገም ተስኖት ሁለቱ ከተፋቱ ሰሎሜን መልሶ ለማግኘት ሁለቱ ይፎካከራሉ ማለት ነው…አለማየሁና  ሁሴን…..‹‹ምን አልባት እሱ እስካሁን ባለበት ሀገር አንዷን ወዶና አጭቶ ወይንም አግብቶ ሊሆን ይችላል… እንደዛ ከሆነ ግልግል ››ሲል አሰበና እራሱን እንደምንም ለማረጋጋት ጥረት ማድረግ ጀመረ፡፡
የሁሴንን ድምፅ በስልክ ከሰማ በኃላ  የአላዛርን የህክምና ውጤት ለማወቅ በጣም ነው የጓጓው…ደውሎ ሊጠይቀው አስበና ደግሞ ምን ብሎ እንደሚጠይቀው ስላልገባው  ሀሳቡን ሰረዘ፡፡

…‹‹እራሱን ወይም ልቡን አሞት ቢሆን ኖሮ በቀላሉ ደውዬ የድሮ ጎደኛዬ ልብህን እንዴት ሆንክ ..?አሁን ምን ይሰማሀል…?ምርመራው ምን ውጤት አስገኘ….?ምናምን እያልኩ በዝርዝር እጠይቀው ነበር፡፡››ሲል ተነጫነጨ…ድንገት ብልጭ አለለትና ከተኛበት አልጋ ተነሳና ቁጭ አለ.. ስልኩን ከተቀመጠበት አነሳና ዳታ አበራ…..
ስንፈተ ወሲብ ብሎ ሰርች ሲያደርግ ብዛት ያላቸው መረጃዎች ተዘረገፉለት…የመጀመሪያውን ከፈተ፡፡
ስንፈተ ወሲብ ወይም የወንድ ብልት አለመቆም ችግር ለወንዶች አሳሳቢ ከሆኑ ጉዳዮች ውስጥ አንዱ ነው። ይህ ችግር የወንዶችን በራስ መተማመን የሚቀንስና ፍርሃት የሚያሳድር ነው። ስንፈተ ወሲብ ማለት በፆታዊ ግንኙነት ወቅት የወንድ ልጅ ብልት በደንብ መቆም አለመቻል ነው።
ንባቡን አቆመና ማሰብ ጀመረ..‹‹የእሱ ግን ያለመቆም ችግር ነው እንዴ..?ነው ወይስ ሙሉ በሙሉ ፍላጎት ማጣት…?.››መረጃው ስለሌለው ማሰቡን አቁሞ ንባቡን ቀጠለ፡፡
ስንፈተ ወሲብን ማከም የምንችልባቸው ብዙ መንገዶች አሉ።
•  ስኳር የበዛባቸው ምግቦች የወሲብ መነሳሳትን ወይም የወሲብ ፍላጎትን ሊቀንሱ ስለሚችሉ ብዙ ስኳርንና ከፍተኛ ካርቦሀይድሬት ያላቸውን ምግቦች ማስወገድ።
•  የኮሌስትሮል መጠናችን ጤነኛ በሚባለው ደረጃ መቆጣጠር።
•  የደም ፍሰትን ለመጨመር ከፍተኛ አሚኖ አሲድ ያላችው ምግቦችን መጠቀም።
•  በዚንክ የበለፀጉ ምግቦችን መጠቀም እንዲሁም የቴስቴስትሮን ሆርሞን እንዲመረት የሚረዱ ሰፕልመንቶችን መውሰድ።
እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት መፍትሄዎች ቀለል ያለ የስንፈተ ወሲብ ችግር ላለባቸው ሰዎች እንደመፍትሄ የተቀመጠ ሲሆን ከዛ ከፍ ያለና አሳሳቢ የሆነ ስንፈተ ወሲብ ችግር ካለብዎ የሜዲካል ህክምና ማግኘት እንደ  ኤክስትራኮርፖራል ሾክዌቭ ህክም ማግኘት ይገባል ይላል፡፡የኤክስትራኮርፖራል ሾክዌቭ ህክምና የታካሚው ብልት ውግት አድርጎ በመያዝ ዝቅተኛ ኢንተንሲቲ ባለው ግፊት ሞገድ ወደ 4000 ሾክ በወንዱ ብልት 4 ቦታ ላይ የብልት የደምስሮችን ለማነቃቃት ይሰጣል። በዚህ ህክምና ታካሚው በሳምንት ከ1-2 ጊዜ በተከታታይ ለ12 ሳምንት ህክምናውን መውሰድ አለበት።
የሚያነበው ነገር ሁሉ ምንም እየገባው አይደለም…ልክ ያንቀላፋ ያለን ልብ በኤልኬትሪክ ሾክ መንጭቆ እንደማስነሳት አይነት ህክምና ይሆን እንዴ..?ልክ እንደዛ በብልት ዙሪያ  የኤሌክትሪክ ንዝረት በመልቀቅ ተመንጭቆ እንዲነሳና እንዲያቆም ማድረግ ይሆን እንዴ….?ተመንጭቆ ተነስቶ አልተኛም ቢልስ?››በራሱ ጥያቄ እራሱ ሳቀ፡፡

እግዚያብሄር ከዚህ አይነት በሽታ አንዲሰውረው  በመፀለይ ስልኩን አጠፋና መልሶ ተኛ፡፡

በሶስተኛው ቀን ከስራ ወደቤት እየተመለሰ  መንገድ ላይ እያለ  አላዛር ደወለለት፡፡

‹‹ሄሎ አላዛር እንዴት ነህ?››

‹‹ምንም አልል ሰላም ነኝ››
ምን ሊነግረው እንደደወለለት  ለማወቅ በከፍተኛ ጉጉት ‹‹አይ ጥሩ ነው…ምነው ፈለከኝ….?.››ሲል ጠየቀው፡፡

‹‹አዎ …ነገ ማታ እራት ብጋብዝህ ብዬ አሰብኩ››

‹‹ይቻላል….የትና በስንት ሰዓት እንደምንገኛኝ ንገረኝ..እገኛለሁ››

‹‹ጥሩ …ቴክስት አደርግልሀለው››

‹‹እሺ እጠብቃለሁ….ግን ሰላም ነው አይደል…?ማለቴ የተነጋገርነው ህክምና በተመለከተ አዲስ ነገር አለ?››በመከራና በጭንቀት ጥያቄውን አፈረጠው…
እስከነገ እንዴት  ብሎ አምቆ ይያዘው…?‹‹የእራት ግብዣው ሙሉ በሙሉ ተፈወስኩ ብሎ የምስራች ሊለኝ ቢሆንስ?.››ሲል አሰበና ተጨነቀ፡፡ የእሱ የምስራች ማለት ለእሱ በተዘዋወሪ  መርዶ ነው….

‹‹አሌክስ  ያው በተነጋገርነው መሰረት ቀናቶች አሉኝ አይደል?››

‹‹አዎ ..20 ቀን አለህ…እንዲሁ ሂደቱ እንዴት እየሄደልህ ነው የሚለውን ለማወቅ ነው››

‹‹ለጊዜው ሁሉ ነገር በሂደት ላይ ስላለ መጨራሻውን በእርግጠኝነት አላውቅም ..ሀኪሞቹም የሚያውቁ አይመስለኝም››

‹‹ጥሩ ..በእኔ በኩል ላግዝህ የምትፈልገው ነገር ካለ ሁሉ ጊዜ አለሁልህ…አሁን መራራቃችንን ሳይሆን የልጅነት ቅርበታችንን  አስበህ ምንም ነገር ልትጠይቀኝ ትችላለህ….ይሄ ነገር ተስተካክሎ ሁለት የልጅነት ጓደኞቼ ደስተኛ የሆነ ትዳራቸውን እንዲያስቀጥሉ እፈልጋለው…ሁለታችሁንም ስል ማድረግ ያለብኝን ሁሉ አደርጋለሁ››አለው…ንግግሩ ለራሱ  ጆሮ እንግዳ ስሜት ነው የፈጠረበት፡፡
‹‹በእውነት አሌክስ ይህንን መስማቴ ደስ ብሎኛል…በቀደም ቢሮህ ተገናኝተን  በጉዳዩ  ላይ ስንወያይ ንግግርህ ጨከን ያለ ነበር…ይቅርታ አድርግልኝና እንደውም…የሄ ልጅ የእኛን መለያየት ይፈልጋል እንዴ?ብዬ እንዳስብ ነበር ያደረከኝ..ያንን ስሜቴን ደግሞ በእለቱ ነግሬሀለው››ሲል እውነቱን አፍርጦ ነገረው፡፡

እንደዛ ሲለው ዛሬም መደንገጡ አልቀረም….ያን ያህል እስከሚያስታውቅበት እንደዘባረቀ አልተሰማውም ነበር…..ማስተባበሉን ቀጠለ‹‹እንዴ ምን ነካህ ?ለምንድነው እንድትለያዩ የምፈልገው?››

‹‹ያው ታውቃለህ አይደል…..?››

‹‹ምኑን ነው የማውቀው?››

‹‹ያው ልጅ ሆነን ጀምሮ ሶስታችንም ነበር የምናፈቅራት››

‹‹ልጅ ሆነን ነበራ ››

‹‹አሁን እንደውም በይበልጥ ውብና ማራኪ ሆናለች እኮ…እንደውም በበለጠ በፍቅር የምታማልለው አሁን ነው…ማለቴ ስሜቱን በራሴ አውቀዋለው..በየጊዜው ትንሽ ባደገችና እድሜ በጨመረች ቁጥር ውብና ማሪኪ እየሆነች እኔም አምርሬ እያፈቀርኳት ነው እየሄድኩ ያለሁት››

‹‹አላአዛር…አንተ እኮ እንደዛ ቢሰማህ ሚስትህ ስለሆነች ነው…..እኛን በተመለከተ የምታወራው ግን የልጅነትና ያለፈ ታሪክ ነው››

‹‹ለማንኛውም እንደዛ ስላሰብኩህ ይቅርታ…በእውነት ያንተን እገዛና ማበረታቻ በጣም ነው የሚያስፈልገኝ…በዚህ ጉዳይ ላይ ከአንተ በተሻለ የሚረዳኝና የሚያግዘኝ ሰው እደሌለ እኔም  አምናለው››

‹‹አዎ እንደዛ ጥሩ ነው..በል አሁን ቻው …ነገ እንገናኛለን፡፡››
‹‹.ቻው እሺ ..አመሰግናለሁ፡፡››
👍559
#ቋጠሮ_ሲፈታ


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#ድርሰት_በዘሪሁን_ገመቹ

///
እሷ እንደጠረጠረችው…ልክ ግቢዋን ከፍታ እንደገባች በተጠንቀቅ ሲጠብቃት የነበረው ኩማንደር ያስቀመጠው ሰው ወዲያው ነበር ያያት…ስልኩን አንስቶ ኩማንደሩ ጋር ለመደወል ያባከነው ደቂቃ አልነበረም….

ኩማንደሩ ስልኩ ሲደወልለት ዳኛው ቤት ቁጭ ብሎ ማድረግ ስለሚገባቸው አንዳንድ ነገሮች እየተወያዩ ነበር….

‹‹በቃ ታክሲ ያዝና ተከታተላት..ከእይታህ እንዳትሰወር…ያለህበት ድረስ እመጣለው››የሚል ትዕዛዝ ነገረውና ስልኩን ዘግቶ ለዳኛው አለም እንደተገኘች ሲነግራቸው ዳግመኛ እንደተወለዱ አይነት እፎይታ ነው የተሰማቸው…

‹‹.እንዲከተሏት አድርጌያለው…አሁን መሄድ አለብኝ….. ››አለና ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡

‹‹ለምን ሪስክ ትወስዳለህ..?ወዲያው እንዲይዞት ማድረግ ነበረብህ››ሲሉ አካሄዱ ላይ ያላቸውን ተቃውሟ አሰሙ፡፡

‹‹ይዘናትስ….?ምንም የሰራችው ወንጀል የለም እኮ…ዝም ብለን አንጠልጥለን ልናስራት አንችልም››

‹‹እስከዛሬ የምታስሯቸውን ሰዎች ሁሉ ወንጀል ሰርተው ነው?››ዳኛው ስትሰሩ የኖራችሁትን ማላውቅ መሰላችሁ የሚል ቃና ባለው ንግግር ታቃወሙ፡፡
‹‹ልጅቷ እኮ የዞኑ ምክትል አቃቢ ህግ የነበረች የህግ ባለሞያ ነች….ሌላ ሰው ላይ የምናደርገውን ሁሉ እሷ ላይ በቀላሉ ማድረግ አንችልም…በዛ ላይ መከተላችን…የትነው የምትሄደው…?አጋዥ አላት ወይስ ብቻዋን ነች?››የሚለውን ለማጥናት ይረዳናል….ምን
አልባት ከሌሎች ጠላቶቻችን ጋር ህብረት ፈጥራ የምትንቀሳቀስ ከሆነም እሷን ብቻ ነጥለን መያዝ ከምንም አያተርፈንም…..››

‹‹ጥሩ አስበሀል ..እንግዲያው እኔም አብሬህ መሆን ፈልጋለው….››

‹‹አረ በዚህ ምሽት ይቅርብህ…ባይሆን ሁኔታውን በየጊዜው እየደወልኩ አሳውቅሀለው…››

‹‹አረ እኔም ከእናንት ጋር እሄዳለው››

ፎቅ ላይ ሆና ንግግሯቸውን ስታዳምጥ የነበረችው ስርጉት የአለምን መገኘት ዜና ስትሰማ በደስታ ጃኬቷን ደርባ አምርራ የምትጠላትን ሴት መያዝ በቀጥታ በአይኗ ለመከታተል ዝግጁ ሆና ወደእነሱ ስትመጣ ተመለከተ…ብዙ ቢከራከራቸውም ሁለቱም ለመቅረት ፍላጎት ስላላሳዩ ምን አገባኝ በሚል መንፈስ አብረውት እንዲሄዱ ፈቀደላቸው፡፡በኩማንደሩ ሹፌርነት አባትና ልጅ ከኋላ ሆነው አለምን ለመከታል ወጡ ..አለምን የሚከታተላትን ታክሲ አዲሱ መነኸሪያ ካለፈ በኃላ ነበር የደረሱበት…ከዛ የአለምን መኪና ካሳያቸው በኃላ እሱ እንዲመለስ ነገረውና አነሱ የአለምን መኪና መከታተሉን ቀጠሉ..እሷ ቀጥታ ለዛ ምሽት ፈጣን በሚባል አነዳድ የቦሌን የአስፓልት መንገድ ይዛ እየነዳችው ነው፡፡

‹‹ልጅቷ ወደየት እየሄደች ነው?፡፡››ስርጉት ግራ በመጋባት ውስጥ ሆና ጠየቀች፡፡
‹‹ይመስለኛል…ግብረ አበሮቾ ጋር የምትገናኘው ከከተማው ውጭ ነው፡፡››አባቷ የመሰላቸውን ተናገሩ፡፡

‹‹አይመስለኝም››ኩማንደር ነው ተናጋሪው፡፡

‹‹ማለት…ምን አሰብክ?››

‹‹ትዝ ይላችኃላ እናቷ ኮፈሌ ዘመዶች ነበሯት…የአባቷም ዘመዶች እዛው ናቸው..እኛ በማናውቅበት መንገድ ከዘመዶቾ ጋር መገናኘት ጀምራ ነበር ማለት ነው..እና አሁን እነሱን ለማግኘት እየሄደች ያለ ይመስለኛል..››ሲል መላምቱን አስቀመጠ፡፡

‹‹እና ኮፈሌ ድረስ ልንከተላት ነው ማለት ነው?፡፡››

‹‹እንግዲህ ቀድሞውንም አትከተሉኝ ያልኩት ለዚህ ነው…እኔ እንኳን እዚህች ኮፈሌ ድረስ ይቅርና ሱማሌም ድረስ ከነዳችው ከመከተል ወደኃላ አልልም››ሲል ፍርጥም ያለ ውሳኔውን ነገራቸው፡፡
//

አለም መኪናዋን በፍጥነት እያበረረች እንኳን ደጋግማ አቶ ፍሰሀ ስልክ ላይ ከመደወል አልታቀበችም…ግን አሁንም ስልኩ ይጠራል እንጂ አይነሳም…‹‹ይሄ ማለት ሰውዬው ከባድ አደጋ ደርሶበታል ማለት ነው..?››ስትል አሰበችና ዝግንን አላት….በእሱ ላይ በሚደርስ አደጋ እንደዚህ አይነት ሽብር ውስጥ እገባለሁ ብላ አስባ አታውቅም ነበር….እርግጥ እንዲህ በድሎኛል ብላ አንድም ቀን አካላዊ ጉዳቱን ወይም ሞቱን ተመኝታለት አታውቅም
…ቢሆንም ደህንነቱ በዚህ መጠን እንዲህ ያሳስበኛል ብላም ግምቱ አልነበራትም፡፡እና የራሷ ሁኔታ በጣም ነው ያስገረማት፡፡

‹‹ፈጣሪ ሆይ እባክህ..ህይወቱን ጠብቃት››ከልቧ ፀለየች፡፡ለቤተሰቦቹ መሳወቅ እንዳለባት ትዝ ያላት ወደባሌ የሚያመራውን የአስፓልት መንገድ ለቃ ወደቀኝ በመታጠፋ ወደ  ሶሌ ደን የሚወስደውን ጥርጊያ መንገድ ከያዘች በኃላ ነበር፡፡የጂኒዬርን ቁጥር ፈለገችና ደወችለት፡፡

‹‹ሄሎ ጁኒዬር…. አለም ነኝ››

‹‹አለም ..ደህና ነሽ…?የት ነሽ….?እንዴት ነሽ?››የእሷን ድምፅ ሲሰማ የሚይዘው የሚጨብጠው ጠፋበት፡፡ስልኩ ሲደወልለት ቤት ከእናቱ ጋር ሳሎን ቁጭ ብሎ እየተጫወተ ነበር፡፡እሷ ለእሱ መርበትበት ቁብም ሳትሰጥ ንግግሯን ቀጠለች‹‹ጂኒዬር ልብ ብለህ አድምጠኝ…ከ30 ደቂቃ በፊት ከአባትህ ጋር በስልክ እያወራሁ ነበር…መኪና እየነዳ ሳያስበው ከከተማ እንደወጣ እና ወደሶሌ ደን እየተቃረበ መሆኑንና ከአሁን በኃላ ስለመሸ ወደከተማ እንደማይመለስና ማረፊያ ጎጆ ስላለው እዛው እንደሚያድር እየነገረኝ ነበር፡፡›

‹‹አዎ እዛ አልፎ አልፎ የምናርፍበት ጎጆ አለን….››

‹‹እና..ምን መሰለህ?››

‹‹እያስደነገጥሺኝ ነው..ስለምን ነበር እያወራችሁ የነበረው?››

‹‹እሱ ምን ይሰራልሀል…ለማንኛውም ንግግራችንን ሳንጨርስ አውሬ ገባብኝ የሚል ድምፅ እና ከፈተኛ ፍንዳታ የመሰለ ነገር ሰማው..እና ስልኩ ተቋረጠ.. መልሼ ደጋግሜ ብደውል ስልኩ ይጠራል… አይነሳም..፡፡››

‹‹ወይኔ ፈጣሪ…ምን እያልሺኝ ነው?››አጠገቡ የነበረችው እናቱ ሳራ የልጇ ጭንቀት በእሷም ላይ ተጋብቶባት…ስሩ ቆማ ትንቆራጠጥ ጀመር፡፡.

‹‹ለምንኛውም አሁን ቦታው ላይ እየደረስኩ ነው.. እንዳገኘሁትና ሁኔታውን እንዳየው እደውልልሀለው…ምን አልባት አንብላንስ ያስፈልግ ይሆናል››ስልኩ ተቋረጠ
‹‹ምንድ ነው ልጄ..?ፍሰሀ ምን ሆነ?››ሳራ ጠየቀች፡፡

‹‹አባዬ አደጋ ደርሶበታል መሰለኝ..ሶሌ ያለው ደን ውስጥ ነው…መሄዴ ነው››

‹‹እኔም አብሬህ እሔዳለው››

‹‹እማዬ አንቺ እዚሁ ሆነሽ ጠብቂ….››

‹‹እሔደለው..አልኩህ እሔዳው›› አጉረጠረጠችበት፡፡ምንም አላለም…በክርክር ጊዜ ማባከን ስላልፈለገ ቀጥታ ወደሳሎኑ መውጫ መራመድ ጀመረ… እናቱም ከኃላው ተከተለችው… መኪና ውስጥ ገቡ ..ወደባሌ ጎባ የሚወስደውን የአስፓልት መንገድ ይዘው ወደ ሶሌ ጉዞ ጀመሩ
///
አቶ ፍሰሀ አውሬውን አድናለው ብሎ መሪውን ሲጠመዝ ሙሉ በሙሉ ከመንገዱ ወጥቶ በግራ በኩል ባለው ገደል መሰል ጉድጓድ ውስጥ ነበር ጎማው ተንሸራቷ የገባው…ከዛ ፍሬኑን ለመያዝ ቢሞክርም የመኪናዋን ፍጥነትም ሆነ ባላንስ መቆጣጠር አቅቶት አንድ ዙር ተገለበጠና አንድ የብሳና ዛፍ ተደግፎ ቆመ….ለአምስት ደቂቃ ራሱን አያውቅም ነበር፡፡ከገባበት መደንዘዝ ሲወጣ ወንበሩ ስር ተወሽቆ ነው ራሱን ያገኘው…እንደምንም ታግሎ ቀበቶውን ከአንገቱ አወጣና በራፍን በእግሮቹ ገፍቶ ለመክፈት ሞከር..ቀላል ስራ እልሆነለትም፡፡እግሮቹ  ምን  እንደነካቸው  ባያውቅም  የሚያሰበውን  ያህል  ጥንካሬ
37👍4