አትሮኖስ
286K subscribers
120 photos
3 videos
41 files
569 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ጠላፊዎቹ


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#በኬንፎሌት


#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ

ሃርትማንና ጋቦን የሎርዱ ንግግር ገርሟቸው አፈጠጡባቸው:
ማርጋሬት በድንጋጤ ፊቷ የበሰለ ቲማቲም መሰለ፡፡ አባቷ የተናገሩት ጮክ ብለው ስለነበር ሰዉ ጸጥ ረጭ አለ ማርጋሬት መሬቱ ተከፍቶ ቢውጣት ወደደች፡ ይህን የተናገሩት ፊት ለፊቷ የተቀመጡት ባለጌ፣ መሆናቸውን ሰው ሁሉ ስላወቀ ተሽማቀቀች።
አስተናጋጁን ኒኪን ቀና ብላ ስታየው መሳቀቋን አይቶ ለእሷ ማዘኑን ከፊቱ አነበበች፡ ይህም የበለጠ እፍረቷን አባባሰባት"

ባሮን ጋቦን ፊታቸው በድንጋጤ አመድ መስሏል ለሎርዱ መልስ ሊሰጡ አሰቡና ትተውት ፊታቸውን ወደ ሃርትማን መለሱ፡
ሆዳቸው እያረረ በፈገግታ አለፉት፡ ነገር ግን እሳቸው ከናዚ ጀርመን አምልጠው የመጡ በመሆናቸው ከዚህ በላይ ብዙ ክፉ ነገር የደረሰባቸው ስለሆነ ይህ ስድብ ለእሳቸው እንደ ምርቃት የሚቆጠር ነው።

ማርጋሬት ባሮን ጋቦንን ተመለከተች፡ ሎርዱ ያሉትን ከምንም ባለመቁጠር ማንኪያቸውን አንስተው ሾርባቸውን መጠጣታቸውን ቢቀጥሉም እጃቸው እየተንቀጠቀጠ ስላስቸገራቸው ሰደርያቸው ላይ ሾርባው ተንጠባጠበ፡፡ውስጣቸው
የሚንተከተከው ንዴት ግን
መጠጣት ስላላስቻላቸው ማንኪያቸውን አስቀመጡት።

ማርጋሬት የባሮኑ ብስጭት ልቧን ነካው። በአባቷም ስድብ በጣም ተናደደችና ‹‹ድፍን አውሮፓ የሚያከብራቸውን ሁለት ትላልቅ ሰዎች እንደዚህ መሳደብ የለብህም›› አለቻቸው በድፍረት።

‹‹ሁለት የታወቁ ይሁዲዎች በይ›› አሉ አባቷ።

‹‹ይሁዳዊያን አያቴን ረሳሃቸው አባባ?›› አለ ፔርሲ ሁሉን ነገር ቀልድ አድርጎ።

አባት ወደ ልጃቸው ዞሩና ጣታቸውን ፔርሲ ላይ እያወዛወዙ ‹‹እንዲህ
ያለውን የማይረባ ቀልድህን ተወኝ ሰማኸኝ!›› ሲሉ አፈጠጡበት

ፔርሲ ነገሩ ስላላማረው ‹‹መጸዳጃ ቤት ልሂድ አሞኛል›› አለና ትቷቸው ሄደ፡ ማርጋሬት እሷና ፔርሲ አባታቸውን መቃወም እንደሚችሉና ምንም እንደማያመጡ አውቃለች፡ ይህም አንድ እድገት ነው ስትል አሰበች፡

‹‹ከቤታችን አባረው እንድንሰደድ ያደረጉን እነዚህ ሰዎች መሆናቸውን
እንዳትረሺ›› አሏት አባት ማርጋሬትን፡፡ ‹‹ከኛ ጋር የሚሄዱ ከሆነ ስርዓት
መማር አለባቸው›› አሉ፡

‹‹ቃ!›› ሲል ተደመጠ አንድ ድምጽ

ማርጋሬት ድምጹ ወደመጣበት አቅጣጫ ዞረች፡ ይህን ያለው ፎየንስ
ላይ የተሳፈረው መርቪን ላቭሴይ ነው፡፡ መርቪን እሳት ጎርሶ እሳት ለብሶ
የኦክሰንፎርድን ቤተሰብ ጠረጴዛ ተደግፎ ቆሟል። አስተናጋጆቹ በድንጋጤ
ደርቀው ቆመዋል፡ ጠብ ይነሳል ብለው ፈርተዋል፡ ላቭሴይ የሰማይ ስባሪ
የሚያክል፣ ዕድሜው በአርባዎቹ ውስጥ የሚገመትና ጸጉሩ ገብስማ መልከ መልካም ሰው ነው፡፡ ሲያዩት የሚፈራው ነገር ያለ አይመስልም፡ የለበስው
ልብስ ውድ መሆኑ ያስታውቃል፡

‹‹ይህን አመለካከትህን ለራስህ ያዘው›› አላቸው በሚያስፈራ ድምጽ“

‹‹አንተን አያገባህም!›› አሉ ኦክሰንፎርድ።
‹‹ያገባኛል!››
ማርጋሬት አስተናጋጁ ውልቅ ብሎ ሲሄድ አየችው፡ የአይሮፕላኑን አስተናጋጆች ሊጠራ እንደሄደ ተገንዝባለች፡፡

‹ስለ እኚህ ሰውዬ ምንም አታውቅም፡፡ ፕሮፌሰር ሃርትማን ባንተ አፍ የሚጠሩ ሰው አይደሉም፡፡ በዓለም ላይ አሉ የሚባሉ ሳይንቲስት ናቸው››
አለ ከመቆርቆር በመነጨ ብርቱ ስሜት፡

‹‹የፈለገውን ቢሆን ግድ የለኝም›› አሉ ኦክሰንፎርድ፡
‹‹አንተ ግድ ባይኖርህ እኔ ግድ ይኖረኛል፡ ስለዚህ ይህን የከረፋ አስተሳሰብህን አስተካክል›› አለ ላቭሴይ፡

እኔ የፈለኩትን ማለት እችላለሁ›› አሉና ኦክሰንፎርድ ከመቀመጫቸው ተነሱ፡
ላቭሴይ በጠንካራ እጁ የኦክሰንፎርድን ትከሻ ተጫነና አስቀመጣቸው፡፡
እንዳንተ ካሉ ሰዎች ጋር ነው ጦርነት የገጠምነው›› አለ፡፡

ኦክስንፎርድም በደከመ ድምጽ ‹‹ልቀቀኝ! ልቀቀኝ!›› ሲሉ ተወራጩ።

‹‹አፍህን የምትዘጋ ከሆነ ነው የምለቅህ››

‹ካፒቴኑን እጠራለሁ›› አሉ ኦክሰንፎርድ፡

‹‹አያስፈልግም!›› አለ ሌላ ድምጽ፡ ካፒቴን ቤከር ሙሉ ዩኒፎርሙን ለብሶ ቆሟል የአዛዥነት መንፈስ ይታይበታል፡ ‹‹ሚስተር ላቭሴይ ወደ ቦታህ ብትመለስ?›› አለ፡

‹‹እኔ ወደ ቦታዬ እመለሳለሁ›› አለ ላቭሴይ ‹‹ነገር ግን በመላው
አውሮፓ ትልቅ ክብር የሚሰጣቸው ሳይንቲስት በዚህ ሰካራም ሲሰደቡ
በዝምታ ማለፍ አልችልም፡››

‹‹ሚስተር ላቭሴይ ወደ ቦታህ›› አለ ቤከር፡

ላቭሴይ ወደ ቦታው ተመለሰ፡፡

ካፒቴኑም ወደ ኦክሰንፎርድ ዞር አለና ‹‹ሎርድ ኦክሰንፎርድ የተናገሩት
ነገር አስነዋሪ ነው፡ አንድ ተሳፋሪ ሌላውን ተሳፋሪ መስደብ አይችልም፡››

ማርጋሬት አባቷ የቤከርን ምክር እንዲቀበሉ ብትፈልግም እሳቸው ግን
ጠብ ጠብ እንዳላቸው ነው፡፡

‹‹አንተ ይሁዲ ብዬ ነው የጠራሁት፡፡ ይሁዲነቱን ሊክድ ነው!›› ሲሉ
አምባረቁ፡፡

‹‹አባባ ምነው ዝም ብትል›› ስትል ተቆጣች ማርጋሬት፡

‹‹እዚህ አይሮፕላን ውስጥ እስካለሁ ድረስ ማንንም እንዲሳደቡ አልፈቅድም›› አለ ቤከር፡

አባት ስድባቸውን ቀጠሉ ‹‹በይሁዲነቱ ያፍራል እንዴ?›› አሉ፡

ቤከር በቁጣ ገነፈለ፡፡ ‹‹ይሄ የአሜሪካ አይሮፕላን ነው ጌታዬ እኛ ደግሞ ጥብቅ የስነ ምግባር ደንብ እንከተላለን፡፡ ሌሎች ተሳፋሪዎችን መሳደብ
ካላቆሙ አይሮፕላኑ በሚቀጥለው በሚያርፍበት ቦታ ላይ ለፖሊስ አስረክቦታለሁ፡፡ ምንም እንኳን አልፎ አልፎ የሚከሰት ቢሆንም እንዲህ
አይነት ነገር ሲገጥም አየር መንገዱ ህግ የጣሱ ሰዎችን ይከሳል›››

ሎርዱ የክስ ነገር ሲነሳ ፍርሃት ፍርሃት አላቸው፡ የሚመጣውን በመፍራትም አፋቸውን ዘጉ፡፡ ማርጋሬት በእጅጉ በሃፍረት ተሽማቀቀች አባቷን ዝም ለማሰኘት ብዙ ብትጥርም የአባቷ አድራጎት አንገት
አስደፍቷታል ቅሌት ውስጥ የገቡት አባቷ ስለሆኑ::

‹‹ወደ መቀመጫችን እንመለስ›› አሉና አባት ተነሱ ወደ ሚስታቸውም ዞር ብለው ‹‹አንሄድም የኔ ውድ?›› አሏቸው።

ሁሉም ሰው ማርጋሬት ላይ አፈጠጠባት፡፡ በዚህ ጊዜ ሄሪ ከየተ መጣ ሳይባል ከመቀመጫዋ ኋላ መጥቶ ወምበሯን ያዝ አደረገላት” ሌዳ ማርጋሬት›› አለ በአክብሮት በመጠኑ አንገቱን ዝቅ አድርጎ ማርጋሬት በሄሪ አድራጎት ልቧ ተነካ፡፡

እናት ጅንን ብለው ፊታቸው ላይ ምንም የእፍረት ምልክት ሳይታይባቸው ባላቸውን አስከትለው ወጡ፡፡

ሄሪ ለማርጋሬት በጨዋ ደምብ ክንዱን ሲሰጣት ክንዷን ከክንጿ ጋ ቆላለፈች፡፡ ይሄ ትልቅ ነገር ባይሆንም ለእሷ ግን አንድ የሆነ መተማመን ፈጥሮላታል፡፡ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በእፍረት ቁንጫ አክላ የነበረችው ማርጋሬት በመጨረሻ በሄሪ እርዳታ በክብር ወደ ቦታዋ ተሸኘች፡፡ ከሄሪ ጋ ወደ መቀመጫዋ ስትመለስ ድምጹን አጥፍቶ አምባጓሮውን እንደ ትርኢት
ሲመለከት የነበረው ተሳፋሪ ከኋላ ሲንሾካሽክ ሰማች፡

‹‹አንተ ጥሩ ሰው ነህ፡፡ እንዴት እንደማመሰግንህ አላውቅም›› አለችው
ሄሪን፡፡

‹‹የተፈጠረውን አታካሮ ስመለከት ነበር፡፡ በአባትሽ አድራጎት አንገትሽን
ስትደፊ ሳይ አሳዘንሽኝ፡፡››

‹‹እንደዚህ ቀን በሃፍረት ተሸማቅቄ አላውቅም›› አለች እየተንገፈገፈች

አባቷ ግን አሁንም አደብ አልገዙም፡፡ ‹‹አንድ ቀን ይቅርታ ይጠይቁ ይሆናል እነዚህ ጅሎች!›› አሉ፡ ሚስታቸው አንድ ቃል ሳይተነፍሱ እጥግ
ተቀምጠው ባላቸውን በአግራሞት ያይዋቸዋል፡፡

‹‹ይህ ጦርነት ያበቃና! ምናለ በሉኝ›› አሉ
አባት፡፡
👍14
‹‹አባባ ከዚህ በኋላማ በቃ እባክህ›› አለች ማርጋሬት፡፡ እንዳጋጣሚ ሆኖ አጠገባቸው ሄሪ ብቻ ነው ያለው: ሚስተር መምበሪ በቦታው የለም አባቷ የልጃቸውን ውትወታ ከምንም ባለመቁጠር ‹‹የጀርመን ጦር እንደ መአበል እንግሊዝን ያጥለቀልቃታል፡፡ ከዚያም ምን ይሆናል መሰላችሁ
ሂትለር የፋሺስት መንግስት በእንግሊዝ ይተክላል» አሉ
‹‹አባባ ምነው ቀወስክ እንዴ!›› አለች፡፡
‹‹ከዚያም የፋሺዝም አራማጅ ሰው እንዲመራ ስልጣን ይሰጠዋል!›› አሉ
አባት


‹‹ወይ አምላኬ!›› አለች ማርጋሬት አባቷ ውስጣቸው የሚንቀለቀለውን አስተሳሰብ በግልጽ ሲናገሩ ስትሰማ በእጅጉ ተስፋ ቆረጠች፡

አባቷ ሂትለር የእንግሊዝ አምባገነን መሪ ያደርገኛል ብለው ያስባሉ፡፡
እንግሊዝ በጀርመን እግር ስትወድቅ እሳቸውን ከስደት አምጥቶ እንደ አሻንጉሊት ያስቀምጣቸዋል።

‹‹አንድ የፋሺስት ጠቅላይ ሚኒስቴር ቦታው ላይ ሲቀመጥ አዳሜ እሱን
ተከትላ ታሸበሽባለች!›› አሉ ኦክሰንፎርድ በድል አድራጊነት መንፈስ፤
በክርክሩ ያሸነፉ ይመስል።

ሄሪ ኦክሰንፎርድን እንደ ላንቲካ ሲመለከት ቆየና ‹‹ሂትለር ቢያሸንፍ
የፋሺስት መንግስት እንዲያቋቁሙ የሚጠራዎት ይመስሎታል?›› ሲል
ጠየቃቸው፡

‹‹ማን ያውቃል?›› አሉ ኦክሰንፎርድ ‹‹እዚህ ቦታ ላይ የሚቀመጠው
ሰው በቀድሞው መንግስት እጁ የጨቀየ መሆን የለበትም፡ እኔ አገሬን
ለማገልግል ከተጠራሁ ተመልሼ ለመምጣት አይኔን አላሽም፡፡››

ሄሪ በሰውዬው አባባል ክፉኛ ደነገጠ፡፡

ማርጋሬት በአባቷ ላይ ያላት ተስፋ ሁሉ ተሟጠጠ፡፡ ከአባቷ ተለይታ መሄድ ሊኖርባት ነው፡፡ ከዚህ ቀደም ለመጥፋት ሞክራ ሳይሳካላት ቀርቶ ቅሌት ውስጥ የከተታትን ሁኔታ ስታስታውስ ዘገነናት፡፡ አንድ ጊዜ ስላልተሳካላት ግን ተስፋ መቁረጥ አይኖርባትም፡፡ አንድ ሌላ የመጥፋት ሙከራ ለማድረግ ቆርጣ ተነስታለች፡

አሁን ግን በተለየ ሁኔታ ማድረግ ይኖርባታል፡ ከእህቷም መማር
አለባት፡፡ በጥንቃቄ አስባና አቅዳ መነሳት ይኖርባታል፡ ታዲያ ገንዘብ፣ ጓደኞችና የምታርፍበት ቦታ ያስፈልጋታል፡፡ በዚህ ጊዜ ውጤት ማምጣት
ይጠበቅባታል፡፡

ፔርሲ ከመጸዳጃ ቤት ሲመለስ ጠቅላላ ድራማው አምልጦታል፡ ሆኖም
እሱ የራሱን ድራማ ሲሰራ ስለቆየ ፊቱ በፈገግታ አብርቷል፡ ‹‹ምን እንዳ
የሁ ልንገራችሁ›› አለ አጠገቡ ላሉት ሰዎች ‹‹ሚስተር መምበሪ መታጠቢያ ቤት ውስጥ ኮቱን አውልቆ ሲታጠብ ወገቡ ላይ የሻጠውን ሽጉጥ አየሁት፡›››.....

ይቀጥላል
👍13🥰1
#ሳቤላ


#ክፍል_ሰባ_አምስት


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ


...ባርባራ ማዳም ቬንን ከኢስት ሊን ሳትወጣ እንድትቆያት አጥብቃ በለመነቻት ጊዜ በልቧ በጣም ደስ እንዳላት ባትገልጸውም ላለመቀበል አልጨከነችም "
ይህች አስተማሪ ጠባይዋ ከብዙዎቹ ብጤዎቿ ለየት ያለች ከትልቅ ቤተስብ
የተወለዶች በጨዋ ደንብ
ያደገች መሆኗን ባርባራ ጠቅላላ ሁኔታዋን በመገምግም ዐወቀቻት " ሁለተኛዉ ለሉሲ ስትል ብቻ ደሞዟን የምትፈልገውን ያህል አሳድጋላት እንድትቀመጥላት ፈለገች ነገር ግን ባርባራ ለሉሲ ስትል ብቻ እንጂ በግል ስሜቷ ማዳም ቬንን አትወዳትም ነበር በአርግጥ ሰውነቷ ቢነግራት ይሆናል እንጂ የምትጠላበት ይኸ ነው የምትለው ምክንያት አልነበራትም "

ወይም መልኳ ከሳቤላ ጋር በመመሳሰሉ ሊሆን ይችላል " ባርባራ ራሷም የማዳም ቬን መልክ ከሳቤላ ጋር መመሳሰል በድምፅ ይሁን በመልክ ይሁን በጠባይ
ይሁን ግልጽ ሊሆንላት ባይችልም ብዙ ጊዜ የሚገርም መመሳሰል ሰትል ነበር
ሳቤላ ቬን ትሆናለች ብላ ግን በጭራሽ አልጠረጠረችም እንደማትወዳትም ለማንም ተናግራ አታውቅም " የሰማይ ወፎች የየብስ እንስሶችና የባሕር ዓሦች ሁሉ አንድ ነገር ከመድረሱ በፊት የማወቅ ተሰጥኦ እንዳላቸው ሁሉ ሰውም የራሱ የሆነ ተሰጥኦ አለው " ስለዚህ በዚህ ተሰጥዎው ሰውነቷ ነግሯት ይሆናል " ከላይ እንዳልነው ባርባራ ለሉሲ ስትል ብቻ ማዳም ቬን ከኢስት ሊን እንድትለቅ ባትፈልግም ሞተች ቢባል ግን አንዲት ዘለላ እንባ እንኳን እንደማታፈስላት ታውቅ ነበር ።

እነዚህ የተለያዩ አሳቦችና ትዝታዎች በሁለቱ ሴቶች ናላዎች ሲመላለሱባቸው
ቆዩና " ማዳም ቬን ለመሔድ ከወንበሯ ተነሣች
ልጄን ለአንድ ደቂቃ ያህል ትይዥልኝ .. ማዳም ቬን ? ” አለቻት ባርባራ " ማዳም ቬን ያላሰበችው ጥያቄ ሲሆንባት ጊዜ ደነገጠችና “ ይችን ሕፃኗን ! ” ስትላት ባርባራ ሣቀች

“ ይቻትልሽ ከጎኔ ተኝታለች

ማዳም ቬን ጠጋ ብላ ልጂቱን አሣቻት " ከዚያ በፈት በክንዷ ልታቅፋት
ቀርቶ ለዐይኗም በወጉ አይታት አታውቅም " አንድ ቀን ይሁን ሁለትቀን ያህል
ሚስዝ ካርላይልን ለማየት ገብታ ወንፊት በመሰለ ልብስ የተሸፈነች ትንሽ ፊት ከህፃን አልጋዋ ላይ እንደተኛች አሳይታት ነበር » ከዚያ በቀር አይታት አታውቅም።

“ አመሰግንሻለሁ አሁን መነሣት እችላለሁ " አየሽ ልጅቱ እዚሁ እንዳለች ለመነሣት ብሞክር ኖሮ ላፍናት እችል ነበር " አለቻት ባርባራ እየሣቀች "
“ እዚህ ጋደም ካልኩ ብዙ ቆይቻለሁ አሁን ድካሜ ደኅና ወጣልኝ እንደተኙ
ስለሚታፈኑት ሕፃናት ጉዳይ ከሚስተር ካርላይል ጋር አሁን ስንጫወት ነበር "
በየሳምንቱ በሚወጣው የጤና ዜና ይህን ያህል ልጆች እንደተኙ ተደርቦ ተተኛባቸው ይህን ያህል ልጆች እንደተኙ እየታፈኑ ሞቱ እየተባለ ይገጻል" በየሳምንቱ እስከ አሥር ይደርሳሉ" ሚስተር ካርላይልማ ሆነ ተብሎ ነው የሚደረገው ይላል ”

“ ኧረ ሚስዝ ካርላይል !

እሱ አንደዚህ ብሎ ሲነግረኝ እኔም እንዳንቺ ጮኩበትና እጄን ከንፈሮቹ ላይ ጣልኩበት እሱም ሥቆብኝ ሲያበቃ የዓለምን ክፋት ግማሹን አንኳን አለማወቄን ነገረኝ " አመሰግንሻለሁ " አለቻት ሚስዝ ካርላይል ልጂቱን ከማዳም ሼን እየተቀበለች ቆንጆ ልጅ አይደለችም ? አና የሚለውን ስምስ ወደድሽው ?

ቀላል ስም ነው ቀላል ስሞች ሁልጊዜም ደስ ይላሉ” አለች ሳቤላ "
አርኪባልድ ልክ እንዳንች ረጅም ስም አልወድም አለና የኔን የእኅቱንና የራሱን ስም ምሳሌ አድርጐ ነገረኝ " አሁን “ባርባራ የሚለውን ስም እወደዋለሁ ብሎ ልጂቱን ባርባራ ብሎ ስም አወጣላት » ስለዚህ አን ባርባራ ትባላለች የመጀመሪያው መጠሪያዋ ሁለተኛው ደግሞ ሙሉ ስሟ ሲመዘገብ የምትጠቀምበት
ነው ...

“ ክርስትና ገና እልተነሣችም ...አይደለም ? " አለች ማዳም ቬን "

ጥምቀት ብቻ ነው ዊልያም ባይሞት ኖሮ ቀደም ብለን እናስነሳት ነበር።
ሌላው ደግሞ የመንድሜ የሪቻርድ ጉዳይ የሊንበራው ፍርድ ቤት የሚለው እስኪ
ለይለት ስንል ነበር የቆየን " በርግጥ ለክርስትና ድግስ አናደርማፈግም ”

"ሚስተር ካርላይል ' ኮ ለክርስትና መደግስ አይወዱም ”አላች ሳቤሷ .

በምን አወቅሽ ? ” ጠየቀች ባርባራ ዐይኖን አፍጣ " ምስኪን ማዳም ቬን ፊቷ ልውጥ አለ » የኢስትሊን ባለቤትነቷ ቅዠት እንዲህ ዐልፎ ዐልፎ ልቧን ስውር ያደርገ ነበር" ለባርባራ ጥያቄ ክው ብላ ደነገጠችና " ሰዎች ሲሉ ስምቾ ነሙ ” አለች "

“እውኑት ነው አለች ባርባራ » “ ለማንኛውም ልጅ የክርስትና ድግስ አድርጎ አያሙቅም በጸሎት በሚፈጸመው ሥነ ሥርዓትኖ በአንድ ላይ ተሰባስቦ መብላት መጠጣትና ዓለማዊ ፈንጠዝያ በማድረግ ያለው ልዩነት ሊገናኝለት አልቻለም

ማዳም ቬን፡ ከባርባራ ዘንድ ወጥታ ወደ ክፍሏ ስትሔድ ወጣቱ ሎርድ ቬን
በየማእዘኑ አንገቱን እያሰገገ በመቃኘት“ ሎሲ! ሎሲ! ” እያለ የተንከለከአለ
እየተጣራ መጣ።

“ ለምን ፈለግኻት ?” አለችው ማዳም ቬን "

“እሱን ልነግርሽ አልችልም” አላት በፈረንሳይኛ „ “ የኢትን ተማሪ ስለ ነበር አጋጣሚ ሲያመቸው የፈረንሳይኛ ችሎታውን ማሳየት ደስ ይለው ነበር »

“ ሉሲ አሁን እያጠናች ስለሆነ ልትመጣ አትችልም ” አለችው " ለምን
እንደ ፈለጋት አሁንም መልሶ በፈረንሳይኛ ሲነግራት ሳትወድ ሣቅ ኤለችና “ከፈረንሳይኛ አርቲ ቡርቲ የእንግሊዝኛ ቁም ነገር? ምነው ብትናግር " አለችው

“ እንግዲያው የግድ ማወቅ ከፌለግሽ ቁም ነገሩ ሎሲን እፈልጋታለሁ እሷን ማግኘት አለብኝ " በትንሹ ሠረገላ ሽሮሽር ልወስዳት እፈልጋለሁ እሷም ተስማምታለች " ጆን ሠረገላውን እያዘጋጀ ነው ”

“ የለም አልፈቅድልሀም " አንተ ሠረገላ ላይ ከወጣች በኋላ ልታስፈራራራ
ልትረብሻት ነው የፈለግኸው ?

“ግድ የለሽም " እኔ በጣም ነው የማስብላት " ሠረገውን ዝግ አድርጌ እነዳለሁ " እሷኮ ሚስቴ ልትሆን ነው ... ታውቂያለሽ? ”

ማዳም ቬን ልጁን ክንዱን ይዛ ወደ መስኮቱ ወስዳ“ ስለ ሎሲ ካርላይል
እንደዚህ ብለህ የምትናግር እናቷ በሠራችው አጢአት እንክን እንዳለባት ረስተህው ነው?

“ እናቷ ሎሲ ማለት አይደለችም "

“ላንተ ባይመስልህም ሎርድ ማውንት እስቨርንና ወይዘሮ ማውንት እስቨርን
ቢሰሙ አይወዱልህም "

“ አባቴ ምንም አይልም !እናቴን ግን አሳምናለሁ" የእርቅ ፍልሚያ እፉለማታለሁ .... ገባሽ ጠላትን ማሳመን።

ማዳም ቬን ሰውነቷ ተረበሽ መሐረቧን አውጥታአፏ ላይ አደረግች።

ልጁም እጆቿ እንዴት እንደሚንቀጠቀ አየ "

“ሉሲን ክፉኛ ለመድኳት አብሬአት ባሳለፍኰዋቸው ጥቂት ወሮች ውስጥ
አንደ እናትና ልጅ ሆነን ነው የቆየን " ዊልያም ቬን . . እኔ በቅርቡ ምድራዊ ልዩነቶች ወደሌሉበት በደልና ኀዘን ወደማይታዩበት ዓለም እሔዳለሁ " ምናልባት እንዳሳብህ ሆኖልህ ከዘመናት በኋላ ሎሲ ካርላይል ሚስትህ ለመሆን ብትበቃ የናቷን ጥፋት እንዳታነሣባት አደራህን " ካነሳህባት ያሠቅቃታል
አለጥፋቷ ትጨነቃለች » የዚያች የዕድለ ቢስ እናቷ በደል የሷም በደል ነው » ስለዚህ የናቲቱ ኃጢአት ከናቲቱ ጋር እንደ ተቀበረ ቁጠረው » ለሎሲ ስለናቷ እንዳታነሳባት” አለችው .

"የለም ' የለም ! ሚስቴ ከሆነች በኋላ ስለናቷ ሁልጊዜ ነው የማነሣላት "
በዚህ ዓለም ከራሷ ከሉሲ በቀር እንደ መቤት ሳቤላ የምወደው ሰው እንዳልነበረ
አጫውታታለሁ " ሎሲን የምወዳት በናቷ ስለሆነ የናቷን ጥፋት የሲ መስደቢያ አላደርገውም " ይህ ቃሌ ነው ”
👍156👎1
“ በል ያባሃት እንደሆነ ውደዳት አክብራት " ይህን የምነግርህ እንደ ምሞት ሁኘ ነው " የሟቹን አደራ እንድትወጣ "

“ ግድ የለም በዚህ ቃል እገባልሻለሁ 'ግን ምን ማለትሽ ነው? ባሰብሽ
እንዴ ” አላት "

ማዳም ቬን ምንም መልስ ሳትሰጠው ሸርተት ብላ ሔደች "

ምንም እንኳን ወራቱ በጋ አየሩም ሙቀት ቢሆንም› ማታ ጊዜ የአንገት
ልብስ ደራርባም ከግራጫው ሳሎን ተቀምጣ በርዷት ስትንሰፌሰፍ በሩ ተንኳኳ“

“ ይግቡ ” አለች በግድየለሽነት ።

የገባው ሚስተር ካርላይል ነበር " ልቧ ጎኗን እየጐሸመው ከተቀመጠችበት ተነሣች » እንደዚያ ድንግርግር ብሏት እንደ ተቸገረች ወንበር አስጠጋችለት አጁን ከቀረበለት ወንበር ላይ አሳርፎ እሷንም እንድትቀመጥ አመለከታት "

“በጤንነትሽ ሁኔታ ከኛ ጋር ለመኖር ስለ አልቻልሽ ለመሔድ መፈለግሽን
ሚስዝ ካርላይል አሁን ነገረችኝ ” አላት "

“ አዎን ጌታዬ "

ምንድነው ችግርሽ ? ”

"እኔ እንደ መሰለኝ ዋናው መድከም ነው ድካም ድካም ይለኛል እያለች ተንተባተበች "

ሰዎች ዊልያምን በቅርብ ስታስታምሚ ስለ ነበር የሱ በሽታ ሳይጋባብሽ እንዳልቀረ ሲናግሩ ሰምቻለሁ " እኔ ግን አልመስለኝም ” አላት

“ ከሱ ነው የተላለፈብኝ ማለት? ” አለችና፡ “ይልቅንስ ሊመስል የሚችለው” ብላ ቀጥ አለች » ያለችበትን ሁኔታ በመዘንጋት ሊታወቅ የማትፈልገውን ነገር
እንዲታወቅ የማድረግ አባዜ አሁንም አልተዋትም ልትናገረው ጀምራው ከከንፈሯ አድርሳው የመለሰችው ቃል ከኔ ወርሶት ይሆኖል የሚል ነበር ሆኖም ቶሎ ዘወር አደረገችና የኔ መታመም ብዙ አያስገርምም » በቤተሰቤም በሽታ የተለመደ ነገር ነበር ” አለችው "

ያም ሆነ ይህ ወደ ኢስት ሊን ከመጣሽ በኋላ የኔን ልጆች ስትንከባከቢ ስለሆነ የታመምሺው ' እኛ ደግሞ ጤንነትሽን ለመመለስ የምንችለውን ሁሉ እንድናደርግ መፍቀድ አለብሽ " ለምንድነው ሐኪም እንዲያይሽ
የማትፈጊው።?

“ ሐኪም ምንም ፋይዳ አይሠራልኝም " "

በርግጥ በግንባር ቀርበሽ ችግርሽን ነግረሽ ካማhርሺው ምንም ሊያደርግልሽ አይችልም "

የለም ጌታዬ ... ሐኪሞች ከበሽታዬ ሊያድኑኝ ወይም ዕድሜዬን ሊቀጥሉልኝ አይችሉም " "

“ ግን ሁኔታሽ የሚያሠጋሽ ይመስልሻል ?

“ በርግጥ የቅርብ ሥጋት የለብኝም ይዞታዬን ስገምተው ግን ብዙ የምኖር አይመስለኝም "

' እና በዚህ ሁኔታ እያለሽ ሐኪም እንዲያይሽ አትፈልጊም ማዳም ቬን ?
እንደዚህ የመሰለ ነገር በቤቴ እንዲቀጥል እንደማልፈቅድ ማወቅ አለብሽ ። በአደገኛ በሽታ ተይዘሽ ሐኪም አልፊልግም ማለት ! ”

“ በሽታዬ ከአእምሮዬ ነው ። እሱም ከኀዘን ብዛት የመጣ ስለሆነ ማንም ሐኪም ሊረዳኝ አይችልም " ልትለው አልደፈረችም " ይኸን ተወችና ' “ ካስፈለገ ሚስተር ዌይንራይት ይየኝ ሌላ አያስፈልግም ይኸውም ለእርስዎ ደስ ይበል ብዬ ነው ” አለችው ።

“ ደኅና ነው እኔ እነግረውና ይመጣል " ሠራተኞች ሁሉ አንቺን እስኪሻልሽ
ድረስ አስፈላጊውን ሁሉ ይታዘዙሻል " ምንም ይሉኝታ እንዳይዝሽ ። የመሔድሽን ነገር ግን ሚስዝ ካርላይል እስክትመለስ ድረስ ለመቆየት መስማማትሽን ነግራኛለች የኔ ተስፋ ደግሞ እሷ እስክትመለስ ድረስ ምናልባት በጐ ትሆኝና ሐሳብሺን ለውጠሽ ከኛ ጋር ትቆዬ ይሆናል ነው በተለይ ማዳም ቬን ...ስለ ልጄ ስለ
ሉሲ ብለሽ እንደምትቀሪ አምናለሁ ” ብሎ እየተናግረ ብድግ አለና እጁን ዘረጋላት እሷም እየተጨነቀች እጅዋን ስትሰጠው ጥብቅ አድርጎ ይዞ ወደ መሬት
ያቀረቀረውን ፊቷን እያየ ' “ ውለታሺን በምን ልመልሰው ? ለዚያ ከንቱ ሆኖ ለቀረው ልጄ ለነበረሽ ፍቅርና ላደረግሽው ጥረት እንዴት አድርጌ ላመስግንሽስ?” አላት "

“ ለሱ አይዘኑ ። እሱ ዐረፈ ። ስለ አሰቡልኝ በጣም አመሰግናለሁ

”ሚስተር ካርላይል እንደገና እጅዋን ጨብጦ ወጥቶ ሔደ " እሷም የሞት መሐሪነቱ ቶሎ መምጣቱ መሆኑን እያሰበች ራሷን ከጠረጴዛ ደፍታ ተቀምጣ ቀረች።.....


💫ይቀጥላል💫
👍20🔥1
#ጠላፊዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ


#በኬንፎሌት


#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ

...አይሮፕላኑ ወደ ኋላ የማይመለስበት ቦታ ላይ ሊደርስ የቀረው ትንሽ ነው፡፡ ኤዲ አዕምሮው በጭንቀት እንደተወጠረ ከምሽቱ አራት ሰዓት ወደ ስራው ተመልሶ ገብቷል፡ በዚህ ሰዓት ፀሃይ ጠልቃ ጨለማ ነግሷል፡፡
የአየር ጠባዩም ተለውጧል፡፡ዝናቡ
የአይሮፕላኑን መስታወቶች
ይጠልዛቸዋል ኃይለኛው ነፋስ አይሮፕላኑን እንደወረቀት ስለሚወዘውዘው
ተሳፋሪዎቹን ጭንቀት ውስጥ ጥሏቸዋል፡

የአየር ጠባዩ ዝቅተኛ ቦታዎች ላይ መጥፎ ቢሆንም ካፒቴኑ
የሚያበረው ባህሩ ጋ አስጠግቶ ነው፡፡ ከምዕራብ አቅጣጫ የሚመጣው ነፋስ
ዝቅተኛ የሆነበትን ከፍታ ለማግኘት ሲል ነፋሱን እያሳደደ ነው፡፡

የአየር ጠባዩ በትንበያው ከተገመተው በላይ እየተበላሸ በመምጣቱ
ሞተሮቹ ከተጠበቀው በላይ ነዳጅ አቃጥለዋል፡ ኤዲ ነዳጁ አነስተኛ መሆኑን በማወቁ ተጨንቋል፡፡ በነዳጅ ማጠራቀሚያው ውስጥ በቀረው ነዳጅ ምን ያህል ኪሎ ሜትር ሊሄድ እንደሚችል ለማስላት የስራ ቦታው ላይ ቁጭ አለ፡፡ የቀረው ነዳጅ ኒውፋውንድ ላንድ ካናዳ የማያደርስ ከሆነ አይሮፕላኑ ወደ ኋላ መመለስ የማይችልበት ቦታ ከመድረሱ በፊት ወደኋላ መመለስ አለበት።

ታዲያ ካሮል አን ምን ሊውጣት ነው?

ቶም ሉተር ጠንቃቃ በመሆኑ አይሮፕላኑ ሊዘገይ የሚችል መሆኑን ግምት ውስጥ አስገብቶ ከጓደኞቹ ጋር ያለውን ቀጠሮ ለማስረገጥ ወይም
ለማስለወጥ መንገድ ይፈልጋል፡፡

አይሮፕላኑ ወደ ኋላ የሚመለስ ከሆነ ካሮል አን በአፋኞቿ መዳፍ ስር ለሃያ አራት ሰዓት መቆየቷ ነው፡፡ ኤዲ ከስራ ውጭ በሆነበት ጊዜ ሁሉ አስሬ በአይሮፕላኑ መስኮት ሲመለከት አመሸ፡፡ እንቅልፍ እንደማይወስደው ስላወቀ ለመተኛት እንኳ አልሞከረም፡፡ ካሮል አን በዓይነ ህሊናው እየታየችው ጭንቅ ጥብብ ብሎታል ወይ ስታለቅስ ወይ እጅ እግሯ ታስሮ ወይ በድብደባ ቆስላ ወይ ፍርሃት ፍርሃት ብሏት ወይ ተስፋ ቆርጣ ትታየዋለች፡፡ ምንም ሊያደርግላት አለመቻሉን ሲያስበው በንዴት የአይሮፕላኑን ግድግዳ በጡጫ ይጠልዘዋል፡
አንድ ሁለት ጊዜ ደግሞ ለእሱ ተተኪ ለሆነው ሚኪ ፊን ስለአይሮፕላኑ የነዳጅ ፍጆታ ለመንገር በደመነፍስ በደረጃው እየወረደ ከራሱ ጋር እየታገለ ሳይነግረው ተመልሷል፡

ኤዲ ቶም ሉተርን በመብል ክፍሉ ውስጥ በነገር የነካካው አዕምሮው
በመረበሹ ነው፡፡ ቶም ሉተር ደግሞ ብዙም አይናገርም፡፡ እድሉ ሲጠም.ደግሞ ሁለቱ አንድ ጠረጴዛ ላይ ለመብል ተገናኙና አረፉት፡፡ ከራት በኋላ ኤዲ ምን ያህል ስርዓት የጎደለው ተግባር በተሳፋሪ ላይ ሲፈጽም እንደነበረ ጃክ ሲነግረው አመሸ፡፡ ኤዲና ቶም ሉተር የተጣሉበት ነገር እንዳለ ጃክ አውቋል፡፡ ጃክ ኤዲ ብዙም ሊነግረው እንዳልፈለገ ስለገባው ለአሁኑ ያለውን ተቀብሎታል፡፡ ኤዲ ከዚህ በኋላ መጠንቀቅ እንዳለበት አምኗል፡፡ ካፒቴን ቤከር የበረራ መሀንዲሱ የተሳፋሪዎችን ደህንነት የሚጎዳ ተግባር በግዴታ
እንዲፈጽም መታዘዙን ከጠረጠረ እንኳን አይሮፕላኑን ወደ ኋላ ከመመለስ አይቆጠብም፡፡ ይህም ኤዲ ሚስቱን ከእገታው ለማውጣት የሚያደርገውን መፍጨርጨር ያደናቅፍበታል፡፡ ስለዚህ ካፒቴኑ አንድም ነገር ማወቅ የለበትም።

በመርቪን ላቭሴይና በሎርድ ኦክሰንፎርድ መካከል የተነሳው
ጠብ ትዕይንት ኤዲ በቶም ሉተር ላይ ያሳይ የነበረውን ሁኔታ
እንዲረሳ አድርጎታል፡፡ ኤዲ ሌላ የአይሮፕላኑ ክፍል ውስጥ ሆኖ በሃሳብ ተውጦ ስለነበር አላየም፡፡ በኋላ ግን አስተናጋጆቹ የነበረውን ሁኔታ አጫወቱት።ሎርድ ጨካኝ ሰው መሆኑን በመረዳቱ ካፒቴኑ አደብ እንዲገዙ ማድረጉ ኤዲን አስደስቶታል፡ ኤዲ ታዳጊው ፔርሲ በዚህ እርጉም ሰው እጅ
ማደጉ አሳዝኖታል፡

ራት ከተበላ በኋላ ተመልሶ ጸጥታ መንገሱ አይቀርም፡፡ በእድሜ የገፉት ተሳፋሪዎች በየመኝታቸው ላይ ይሰፍራሉ፡፡ ብዙዎቹ በአይሮፕላኑ ውዝዋዜ
እንቅልፍን አጥተውት
ሲያንጎላጁ ያመሻሉ፡፡ ከዚያም አንድ በአንድ እያሉ ይተኛሉ፡፡ እንቅልፍ የማይጥላቸው ተሳፋሪዎች ደግሞ ወይ ካርታ ሲጫወቱ ወይም መጠጣቸውን ሲጨልጡ ያመሻሉ፡፡

ኤዲ የአይሮፕላኑን የነዳጅ ፍጆታ በቻርቱ ላይ ይከትባል፡ በግራፉ
የተመለከተው የአይሮፕላኑ
በቀኝ በኩል የነዳጅ ፍጆታ በእርሳስ
ከተመለከተው የእሱ ትንበያ በላይ ነው፡፡ ኤዲ የሃሰት የነዳጅ ፍጆታ ትንበያ ስላሰፈረ ይህ መሆኑ አይቀርም የአየር ጠባዩ መክፋት ደግሞ በትክክለኛው ፍጆታና በትንበያው ፍጆታ መካከል ያለውን ልዩነት እንዲጎላ አድርጎታል።

በቀሪው ነዳጅ አይሮፕላኑ ሊሄድ የሚችለውን ርቀት አስልቶ ሲጨርስ
ጭንቀቱ በረታ፡፡ የአይሮፕላኑም የነዳጅ መጠን አስተማማኝነት ደንብ እንደሚያዘው የቀረውን የነዳጅ መጠን በሶስት ሞተሮች ፍጆታ ሲያሰላው እስከ ኒውፋውንድ ላንድ እንደሚያደርሰው አወቀ።

ሌላ ጊዜ ቢሆን ይህን ሲያውቅ ለካፒቴኑ ወዲያውኑ መንገር አለበት፡ አሁን ግን አልነገረውም፡፡

የነዳጅ መጠኑ በአራት ሞተር ሲሰላ የነዳጅ እጥረቱ በጣም ስለሚያንስ
ምንም አያስጨንቅም፡፡ ከዚህም በላይ የአየር ጠባዩ ከተወሰኑ ሰዓቶች በኋላ ጸጥ ያለ ይሆን ይሆናል፡ የንፋሱ ግፊት ቀለል ያለ ከሆነ አይሮፕላኑ ከተተነበየው ያነሰ ነዳጅ ስለሚጠቀም ለቀረው ጉዞ ነዳጅ ሊተርፍ ይችላል የከፋ ነገር ከመጣ ደግሞ ርቀቱን ለማሳጠር ሲሉ የጊዜ አቅጣጫቸውን
ይለውጡና በሞገደኛው ንፋስ ውስጥ ይጓዛሉ፡፡ በዚህ አይነት ጉዞ ግን የሚሰቃዩት ተሳፋሪዎች ናቸው፡፡

ከኤዲ በስተግራ የተቀመጠው ራሰ በራው ቤን ቶምሰን በሞርስ ኮድ
የተቀበለውን የሬዲዮ መልእክት ወደ ጽሑፍ እየቀየረ ነው፡፡ ኤዲ ከፊታቸው ያለው የአየር ጠባይ የተሻለ እንዲሆን በመመኘት ከቤን ኋላ ሆኖ መልእክቱን ያነባል፡

የመጣው መልእክት ግን ማስደነቅ ብቻ ሳይሆን እንቆቅልሽ ሆኖበታል፡
መልእክቱ የተላከው ኤፍ.ቢ..አይ ኦሊስ ፊልድ ለሚባል ተሳፋሪ ሲሆን

‹ብቁጥጥር ስር ያለው እስረኛ ተባባሪ ሊሆኑ የሚችሉ ከተሳፋሪዎቹ መካhል ያሉ ስለሆነ በጥብቅ ክትትል አድርግ›› ይላል፡

ምን ማለት ነው? ከካሮል አን አፈና ጋር ግንኙነት አለው ይሆን ይህ
መልእክት?› ሲል አሰበ ኤዲ፡ ይህ ሊሆን እንደሚችል ሲያስበው ራሱን
አዞረው።

ቤን የኮድ ትርጉሙን ቀዶ
«ካፒቴን ይህን መልእክት ብታየው›› ብሎ ለአለቃው አቀበለው፡፡

ጃክ አሽፎርድ የሬዲዮ መገናኛ ባለሙያው አስቸኳይ መልእክት መኖሩን ሲናገር ሰምቶ ከሚያፈጥበት ቻርቱ ላይ ቀና አለ፡፡ ኤዲ ከቤን መልእክቱን ተቀብሎ ለጃክ አሳየውና ራቱን እየበላ ላለው ካፒቴን አሳየው።

ካፒቴኑ መልእክቱን አነበበና ‹‹እንዲህ አይነት ነገር ነው የማልወደው›› አለ፡፡ ‹‹ኦሊስ ፊልድ የኤፍ.ቢ..አይ አባል ሳይሆን አይቀርም::››

‹‹ተሳፋሪ ነው?›› ሲል ጠየቀ ኤዲ፡፡

‹‹አዎ፡፡ ሰውየው እንግዳ ባህሪ ነው ያለው፡ ድብርታም ነው፡፡ የተሳፋሪ
ሁኔታ የለውም: ፎየንስ ላይ ቆይታ ሲደረግ ከአይሮፕላኑ ላይ አልወረደም›› አለ፡፡

ኤዲ ሰውየውን ባያስተውለውም ናቪጌተሩ ጃክ ግን አይቶታል፡
‹‹ያልከውን ሰው አውቄዋለሁ›› አለ ጃክ አገጬን እያከከ፡፡ ‹‹ራሰ በራ
ነው፡፡ አብሮት ልጅ እግር ሰው ተቀምጧል፡ ሰዎቹ ሲታዩ ምናቸውም አይጥምም::››
👍22
‹‹ወጣቱ ሰው እስረኛ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ስሙ ፍራንክ ጎርደን
ይመስለኛል›› አለ ካፒቴኑ።
‹‹ለዚህ ነው ፎየንስ ላይ ሁለቱ ሰዎች ከአይሮፕላኑ ያልወረዱት።
የኤፍ..ቢ.አዩ ሰው ወጣቱ ከእጁ እንዲያፈተልክ አልፈለገም›› አለ ኤዲ ካፒቴኑ ራሱን ነቀነቀና ‹‹ጎርደን ከእንግሊዝ አገር ታድኖ የመጣ እስረኛ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ከውጭ አገር ታድነው ወደ አገራቸው የሚመለሱ እስረኞች ደግሞ አደገኛ ወንጀለኞች ናቸው፡ ይህን ሳይነግሩኝ አይሮፕላኔ
ላይ ይህን ጠብደል ወንጀለኛ ጭነዋል›› አለ ካፒቴኑ።

የሬዲዮ ኦፕሬተሩ ቤን ‹‹ምን አጥፍቶ ይሆን?›› ሲል ጠየቀ።

‹‹ፍራንክ ጎርደን›› አለ ጃክ ‹‹ይሄ ስም አዲስ አይደለም እስቲ ቆዩማ
ፍራንክ ጎርዲኖ ነው ይሄ ሰውዬ››
ኤዲ ስለ ፍራንክ ጎርዲኖ ጋዜጣ ላይ ማንበቡ ትዝ አለው፡፡ በአሜሪካ
ኒው ኢንግላንድ ስቴት የማፊያ አባል ነው፡፡ የተወነጀለው አንድ ለማፊያ ቡድኑ ጉልቤዎች ገንዘብ አልከፍል ያለን የምሽት ክበብ ባለቤት ገሏል፣ውሽማውን ደፍሯል እንዲሁም የምሽት ክበቡን በእሳት አጋይቷል በሚሉ ወንጀሎች ተወንጅሏል፡ ውሽሚት ከእሳቱ ተርፋ ወንጀሉን የፈጸመው
ጎርዲኖ መሆኑን ለፖሊስ ተናግራለች፡
‹‹ወጣቱ ሰው ፍራንክ ጎርዲኖ መሆኑን እናረጋግጥ›› አለ ቤከር፡፡ ‹‹ኤዲ ሮጥ በልና ኦሊስ ፊልድን እንደምፈልገው ንገረው››

‹‹እሺ ጌታዬ›› አለና ኤዲ በደረጃው ወርዶ ወደ ተሳፋሪዎች ክፍል ገባ፡፡
ፍራንክ ጎርዲኖ ካሮል አንን ካገቷት ሰዎች ጋር የሆነ ግንኙነት ሳይኖረው
አይቀርም ሲል ገመተ፡

በአይሮፕላኑ በስተመጨረሻ ላይ አንድ እድሜው አርባ ዓመት
የሚገመት ራሰ በራ ሰው በአይሮፕላኑ መስኮት አሻግሮ ጨለማውን እያየ ሲጋራውን ያቦናል፡፡ ኤዲ ይህን ሰው ሲያየው ሽጉጡን ደግኖ ወሮበሎች
የተጠራቀሙበትን ክፍል በር በርግዶ የሚገባ ሰው አልመስልህ አለው፡ ከኦሲስ ፊልድ ፊት ለፊት ስፖርት በማቆሙ ሰውነቱ እየወፈረ የመጣ ስፖርተኛ የሚመስል ጥሩ የለበሰ ወጣት ሰው ተቀምጧል፡፡ ጎርዲኖ እሱ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ወጣቱ ሰው ሲያዩት አመለ ብልሹ ልጅ ይመስላል፡
ይህ ወጣት ሰው ጥይት ተኩሶ መግደል ይችላል?› ሲል ኤዲ ራሱን
ጠየቀ አዎ ሳይገል አይቀርም› አለ መልሶ በሆዱ፡፡

‹‹ሚስተር ፊልድ ነህ?›› አለው ትልቁን ሰው፡

‹‹አዎ›› አለ ፊልድ

ፊልድ ካፒቴኑ እንደሚፈልገው ሲነግረው ግራ ገባው: ምስጢሩ
የታወቀ መስሎት ተናደደ፡፡ ቢሆንም እሺ አለና ሲጋራውን መተርኮሻ ላይ
አጥፍቶ የመቀመጫ ቀበቶውን ፈቶ ተነሳ፡፡

‹‹ሚስተር ፊልድ ተከተለኝ›› አለ ኤዲ፡፡

ፊልድን ወደ ካፒቴኑ እየመራ ሲሄድ ከቶም ሉተር ጋር ዓይን ላይን
ግጥም ሲሉ በዚያው ቅጽበት አንድ ሃሳብ ብልጭ አለለት፡፡

የቶም ሉተር ተልዕኮ ፍራንክ ጎርዲኖ በፖሊስ እጅ እንዳይወድቅ
ማድረግ ነው፡፡

ኤዲ የገባውን ግዴታ በመተው አንድ ነገር ሊያደርግ ይችላል የሚል ስጋት ገብቶት ሉተር በድንጋጤ ኤዲ ላይ አፈጠጠ፡፡
አሁን ሁሉ ነገር ለኤዲ ግልጽ ሆነለት፡ ፍራንክ ጎርደን ከአሜሪካ
ሸሽቶ ቢወጣም ኤፍ.ቢ..አይ ዱካውን ተከታትሎ እንግሊዝ ውስጥ ያዘውና ወደ አሜሪካ ሊወስደው ነው፡፡ በአይሮፕላን እንደሚወሰድ መወሰኑን የማፊያ
ቡድኑ ማወቁ አልቀረም፡፡
አይሮፕላኑ አሜሪካ ከመድረሱ በፊት አንድ ቦታ
ላይ ጎርዲኖን ለማስመለጥ ይጥራሉ ማለት ነው፡፡

እዚህ ላይ ነው እንግዲህ ኤዲ የተፈለገው አይሮፕላኑ በካናዳና
አሜሪካ ድንበር ሜይን ስቴት ጠረፍ አጠገብ እንዲያርፍ ይደረግና እዚያም ፈጣን ጀልባ ላይ ተጋብቶ ይዘውት ጥርግ ይላሉ፡፡ ከዚያም ካናዳ ውስጥ አንድ ቦታ ይደብቁትና በመኪና ወደ መሸሸጊያው ይወሰዳል፡፡ በዚሁ ሁኔታ
ከህግ ያመልጣል፤ ለኤዲ ምስጋና ይግባውና፡፡
ፊልድን ወደ ካፒቴኑ እየወሰደ እያለ አጠቃላይ ዕቅዳቸው ምን እንደሆ
ሲረዳ እረፍት ቢሰማውም ሚስቱን ለማዳን ሲል ነፍሰ ገዳይ እንዲያመልጥ መርዳቱ በአንጻሩ አበሳጭቶታል

‹ካፒቴን ሚስተር ፊልድ ማለት እሱ ነው›› አለ ኤዲ

ካፒቴኑ ዩኒፎርሙን ለብሶ በእጅ የሬዲዮ መልእክቱን ይዞ ቁጭ
ብሏል፡ ራት በልቶ ስለጨረሰ ገበታው ከፍ ብሏል፡በኮፍያው ስር
የሚታየው ቃጫ መሳይ ጸጉሩ የአዛዥነት ክብር አጎናጽፎታል
የሚታየው በተቀመጠበት ቀና ብሎ ፊልድን ‹‹ከኤፍ.ቢ.አይ ላንተ የተላከ መልእክት ተቀብያለሁ›› አለው

ፊልድ ወረቀቱን ከካፒቴኑ ለመቀበል እጁን ቢዘረጋም ካፒቴኑ ግን አልሰጠውም፡

‹‹የኤፍ..ቢ.አይ ነጭ ለባሽ ነህ?›› ሲል ጠየቀው::
‹‹አዎ››
‹‹አሁን በግዳጅ ላይ ነህ ያለኸው?››
‹‹አዎ››
‹‹ምንድነው ግዳጅህ ሚስተር ፊልድ?››
‹‹ማወቅ ያለብህ አይመስለኝም ለኔ የተላከ ስለሆነ ወረቀቱን ብትሰጠኝ፡››

‹‹እኔ የዚህ አይሮፕላን አዛዥ በመሆኔ ግዳጅህ ምን እንደሆነ ማወቅ እፈልጋለሁ፡ ከኔ ጋር ባትከራከር ጥሩ ነው ሚስተር ፊልድ፡››

ኤዲ ፊልድን በትኩረት አየው: ፊቱ የገረጣና ድካም የሚታይበት
ሲሆን ዓይኑ እምባ አንቆርዝዟል፡ ቁመቱ ሎጋ ሲሆን በአንድ ወቅት
ሰውነቱ በስፖርት የተገነባ እንደነበር የሚያስታውቅ ቢሆንም አሁን ቆዳው ተሸብሽቧል፡ ፊልድ ጋጠወጥ እንጂ ጎበዝ እንዳልሆነ ኤዲ አውቋል፡ ይህን ማለት ያስቻለው በካፒቴኑ የተደረገበትን ግፊት መቋቋም አቅቶት ወዲያው
እጁን በመስጠቱ ነው።

‹‹ወደ አሜሪካ ሄዶ ፍርዱን የሚቀበል አንድ እስረኛ አጅቤ እየወሰድኩ ነው ፍራንክ ጎርደን ይባላል›› አለ ፊልድ፡

‹‹ፍራንክ ጎርዲኖ ነው?››

‹‹አዎ ነው››

‹‹ሰውዬ ሳትነግረኝ አደገኛ
ወንጀለኛ በአይሮፕላኔ ውስጥ ማጓጓዝ ተገቢ አይደለም››

‹‹ትክክለኛ ስሙን ብታውቅ በምን እንደሚተዳደር ታውቅ ነበር፡፡ ከሮድ
አይላንድ ስቴት እስከ ሜይን ስቴት በዘረፋ፣ በማስፈራራት፣ በአራጣ
ማበደር፣ በህገወጥ ቁማርና ሽርሙጥና በማስፋፋት ተግባር የታወቀው የሬይ ፓትሪያርካ ተቀጣሪ ነው፡፡ ሬይ ፓትሪያርካ ቁጥር አንድ ወንጀለኛ ተብሎ በመንግስት የሚፈለግ ሰው ነው: ጎርዲኖ ደግሞ በፓትሪያርካ ትዕዛዝ
ሰዎችን ያስፈራራል፣ ኢሰብዓዊ በሆነ ሁኔታ ያሰቃያል፣ ይገድላል። ላንተ አስቀድመን ያልነገርንህ ለደህንነት ጥበቃ ተብሎ ነው።››

‹‹እንዲህም ብሎ የደህንነት ጥበቃ›› ሲል ተቆናጠረ ካፒቴኑ።
ኤዲ ካፒቴኑ ተሳፋሪ ላይ ሲጮህ አይቶት አያውቅም።

‹‹የፓትሪያርካ ቡድን ሁሉን ነገር አውቆላችኋል›› አለና ወረቀቱን
ለፊልድ ሰጠው ካፒቴኑ።

ፊልድ የሬዲዮ መልእክቱን አንብቦ ሲጨርስ ፊቱ በድንጋጤ አመድ
መሰለ፡ ‹‹እንዴት ሊያውቁ ቻሉ?›› ሲል አጉተመተመ።

‹‹የትኞቹ ተሳፋሪዎች የእሱ ተባባሪዎች እንደሆኑ ማወቅ እፈልጋለሁ››አለ ካፒቴኑ። ‹‹ከተሳፋሪዎቹ መካከል የምታውቀው አለ?››

‹‹እንዴት ላውቅ እችላለሁ? አለ ፊልድ በንዴት። ባውቅ
ለኤፍ.ቢ.አይ አላሳውቅም ነበር?››

‹እነማን እንደሆኑ ቢነገረኝ አይሮፕላኑ በሚቀጥለው የሚያርፍበት ቦታ ላይ አስወርዳቸው ነበር›› አለ ካፒቴኑ፡
ኤዲ እኔ አውቄአቸዋለሁ ቶም ሉተርና እኔ ነን› አለ በሆዱ፡

ፊልድም ቀጠለና ‹‹የተሳፋሪዎቹን ስም ዝርዝር በሬዲዮ ለኤፍ.ቢ.አይ
አሳውቅና እያንዳንዱን ስም ያጣራልሃል›› አለ፡

ኤዲ ይህን ሲሰማ ፍርሃት ወረረው፡

በዚህ ማጣራት ቶም ሉተር ይጋለጥ ይሆን? እሱ ከተጋለጠ ደግሞ
ሁሉ ነገር አፈር በላው ማለት ነው። የታወቀ ወሮበላ ይሆን? ቶም ሉተርስ እውነተኛ ስሙ ነው፡ የሀሰት ስም የሚጠቀም ከሆነ የሀሰት ፓስፖርት ያስፈልገዋል፡ ከትልልቆቹ ማፍያ ቡድኖች የአንዱ አባል ከሆነ ደግሞ ይህን ማድረግ ችግር ሊሆን አይችልም። እንዲህ ያለውን ጥንቃቄ ደግሞ ማድረግ
አይቀርም፡ ሌላው ያደረገው ነገር በሙሉ በጥንቃቄ የተሰናዳ ነው።
👍13
ካፒቴን ቤከር ብልጭ አለበት።
‹‹በዚህ ምክንያት የአይሮፕላኑ
ሰራተኞች እንዲጨነቁ ማድረግ የለብንም›› አለ፡

ፊልድም ትከሻውን ነቀነቀና ‹‹እንደፈለግህ። ኤፍ ቢ.አይ የአይሮፕላኑን ሰራተኞች ስም ከፓን አሜሪካን አየር መንገድ በደቂቃ ውስጥ መውሰድ ይችላል›› አለ።

ካፒቴኑ የተሳፋሪዎቹንና የአይሮፕላኑን ሰራተኞች ስም ዝርዝር የያዘ ወረቀት ከጠረጴዛው ኪስ አውጥቶ ለሬዲዮ ኦፕሬተሩ ሰጠውና ‹‹ቤን ለኤፍ...አይ ላከው›› ሲል አዘዘው።

ቤን ቶምሰንም የስም ዝርዘሩን በኮድ መልዕክት ላከው፡

‹‹አንድ ሌላ ጉዳይ አለ›› አለው ካፒቴኑ ፊልድን፡ ‹‹መሳሪያህን ለእኛ
ታስረክባለህ››

ፊልድም ‹‹አይሆንም›› ሲል ተቃወመ::

‹‹ተሳፋሪዎች የጦር መሳሪያ እንዲይዙ አይፈቀድም፡፡ ከዚህ ክልከላ ነፄ የሚሆን ሰው የለም።
ስለዚህ ሽጉጥህን አስረክበን›› ሲል አዘዘ ካፒቴኑ፡፡

‹‹ባላስረክብስ?›› ሲል ጠየቀ ፊልድ

‹‹በሰላም ካልሰጠህ ኤዲና ጃክ በግድ እንዲነጥቁህ አደርጋለሁ፡››
ኤዲ ካፒቴኑ ባለው ቢገረምም በማስፈራራት ሁኔታ ወደ ፊልድ ጠጋ አለ፡፡ ጃክም እንዲሁ አደረገ፡፡
ካፒቴኑ ቀጠለና ‹‹ኃይል እንድጠቀም የምታስገድደኝ ከሆነ በሚቀጥለው የአይሮፕላኑ ማረፊያ ቦታ ላይ አስወርድሃለሁ፡››

ፊልድ የታጠቀ ቢሆንም ካፒቴኑ
የበላይነቱን መያዙ ኤዲን
አስደንቆታል፡፡ ይሄ ደግሞ በፊልም እንደሚታየው አይደለም፡፡ ፊልም ላይ ሽጉጥ የያዘ ሰው ነው ትዕዛዝ ሰጪው፡፡

ፊልድ ምን እንደሚያደርግ ጨነቀው፡፡ ኤፍ.ቢ.አይ ሽጉጡን የማስረከቡን ጉዳይ አይቀበለውም፡፡ በአንጻሩ ካላስረከበ ከአይሮፕላኑ ሊባረር ይችላል።

ፊልድም ‹‹እኔ አደገኛ እስረኛ አጅቤ እየወሰድኩ ነው፡፡ የግድ መታጠቅ
ይኖርብኛል፡ ሽጉጤ ከኔ መለየት የለበትም›› አለ፡፡

በጥግ በኩል ያለው በር ገርበብ ብሏል፡፡ ኤዲ በአይኑ ቂጥ አንድ ነገር ውልብ ሲል ታየው፡
ካፒቴን ቤከርም ‹‹መሳሪያውን ተቀበለው ኤዲ›› ሲል አዘዘ፡፡ ኤዲ
ፊልድ ጃኬቱ ውስጥ እጁን ሰደደ፡፡ ፊልድ ከቆመበት ንቅንቅ አላለም፡ ኤዲ ፊልድ ካነገተው የሽጉጥ ማህደር ቁልፉን አላቀቀና ሽጉጡን ላጥ አድርጎ አወጣው፡ ፊልድ ይሄን ሲያይ ፊቱን አቀጨመ ኤዲ ወዲያው ወደ አይሮፕላኑ ጥግ ሄደና በሩን ከፈተው፡፡ ፔርሲ
ኦክሰንፎርድ እዚያ ቆሟል፡፡ ኤዲ ትንሽ ቀለል አለው፡፡ ምናልባትም የጎርዲኖ ጓደኞች ማሽንገን ይዞ ይሆናል ሲል አሰበ፡፡

ካፒቴን ቤከር ፔርሲን ሲያየው ‹‹ከየት ነው የመጣኸው?›› ሲል
ጠየቀው፡፡ ‹‹የሴቶች መዋቢያ ክፍል አልፎ ያለውን መሰላል ወጥቼ
የአይሮፕላኑ ጭራ ድረስ ሄድኩ››
ኤዲ የኦሊስ ፊልድን ሽጉጥ የጠረጴዛው ኪስ ውስጥ ከተተው፡፡

ካፒቴን ቤከርም ፔርሲን ‹ወደ መቀመጫህ ተመለስ ከዚህ በኋላ
ከቦታህ እንዳትነሳ›› አለው፡፡ ፔርሲ ወደ መጣበት ለመመለስ ሲል ‹‹በዚያ አይደለም›› ሲል ተቆጣ ቤከር ‹‹በደረጃው ውረድ››

ፔርሲ የቤከር ቁጣ አስደንግጦት በደረጃው ሹክክ ብሎ ወረደ፡፡
‹‹ልጁ እዚያ ቦታ ምን ያህል ቆይቷል ኤዲ?›› ሲል ጠየቀ ቤከር፡
‹‹አላወቅሁም፡፡ የተባለውን ሁሉ ሳይሰማ አይቀርም›› አለ ኤዲ፡
‹‹ተሳፋሪዎች እንደማይሰሙ ተስፋ እናደርጋለን››

ቤከር የድካም ስሜት ይታይበታል፡፡ ኤዲ ካፒቴኑ የተሸከመው ኃላፊነት ቀላል እንዳልሆነ ተረዳ፡፡ ካፒቴኑ እንደገና ፈርጠም ብሎ ‹ሚስተር ፊልድ ወደ መቀመጫህ ተመለስ፡፡ ስለተባበርከን አመሰግናለሁ›› አለ፡፡ ኦሊስ ፊልድም ምንም መልስ ሳይሰጥ ወደ መቀመጫው ተመለሰ፡፡

ካፒቴኑም ‹ወደ ስራችን›› ሲል አዘዘ፡፡

ሰራተኞቹ ወደየስራ ቦታቸው ተመለሱ፡፡ ኤዲ አዕምሮው ቢታመስም ፊቱ የተደረደሩትን ሰዓቶች ቃኘ፡፡ በአይሮፕላኑ ክንፍ ላይ ያሉት የነዳጅ ማጠራቀሚያዎች የያዙት ነዳጅ
እየቀነሰ ስለመጣ ከዋናው ነዳጅ
ማጠራቀሚያ ወደነዚህ ጋኖች ነዳጅ ማስተላለፍ ይኖርበታል፡፡ ሀሳቡ ግን ፍራንኪ ጎርዲኖጋ ነው፡፡ ጎርዲኖ አንድ ሰው በመግደል፣ የሰውየውን ሚስት በመድፈርና የምሽት ክበብ በእሳት በመለኮስ ተከሶ ፍርዱን ሊቀበል
ቢዘጋጅም ለኤዲ ምስጋና ይግባውና ከቅጣት ሊድን ነው፡፡ ከዚህ የባሰው ደግሞ ጎርዲኖ ከህግ ካመለጠ በኋላ ሌላ ሰው መግደሉ አይቀርም፡
ከመግደል ሌላ ምን ስራ አለው? አንድ ቀን ጎርዲኖ ስለሰራው ወንጀል ጋዜጣ ላይ ያነብ ይሆናል። ጎርዲኖ ያቃጥል ይሆናል፤ ወይ ደግሞ አንዷን ሴት አግተው ለሶስት ይደፍሯት ይሆናል፡ ይህንንም ያደረጉት የፓትሪያርካ
ወሮበሎች ይሆናሉ፡፡ ኤዲም ጎርዲኖ ይሆን ይህን ያደረገው?› ብሎ ይጠይቃል፡፡ ‹ታዲያ ለዚህ ወንጀል እኔ እሆን ተጠያቂው? እነዚህ ወንጀል
የተፈፀመባቸው ሰዎች ይህን ሁሉ የሚያደርስባቸው እኔ ጎርዲኖን ከህግ እንዲያመልጥ ስለረዳሁት ነው› ብሎ ማለቱ አይቀርም፡፡

ነገር ግን ጎርዲኖ እንዲያመልጥ ከማድረግ ውጪ ምን ምርጫ አለው? ካሮል አን ፓትሪያርካ መዳፍ ስር ወድቃለች፡ ይህን ባሰበው ቁጥር ቀዝቃዛ ላብ በጆሮ ግንዱ ይወርዳል፡፡ እንድትጎዳበት አይፈልግም፡፡ እሷን ለማዳን ሲል ከቶም ሉተር ጋር መተባበር አለበት፡

ሰዓቱን ተመለከተ እኩለ ሌሊት ሆኗል፡

ጃክ አሽፎርድ አይሮፕላኑ ያለበትን ቦታ በቻርት ላይ አመላከተው፡ ቤን
ቶምሰን ደግሞ የአየር ሁኔታ ትንበያውን ሰጠው፡፡ ከፊታቸው ንፋስ የቀላቀለ ዶፍ ዝናብ ይገጥማቸዋል፡ ኤዲ የነዳጅ መጠን አመልካቹን አነበበና የሚያስ
ፈልገውን የነዳጅ መጠን ስሌት ሰራ፡፡ ያለው ነዳጅ ኒውፋውንድ ላንድ የማያደርሳቸው ከሆነ ወደኋላ ዞረው መመለስ ይኖርባቸዋል፡፡ ይሄ ማለት ደግሞ ውጥኑ ሁሉ ውሃ በላው ማለት ነው፡፡ ግን መልሶ መላልሶ ማሰቡ ምንም ፋይዳ የለውም፡፡ ኤዲ በዕድል አያምንም፡፡ አንድ ነገር ማድረግ አለበት፡፡

ካፒቴን ቤከር ‹‹እንዴት አደረግኸው የነዳጁን ነገር?›› ሲል ኤዲን
ጠየቀው::

‹‹ስሌቱን ሰርቼ አልጨረስኩም›› ሲል መለሰ፡፡

‹በደንብ ተመልከተው ወደኋላ መመለስ የማንችልበት ቦታ እየደረስን ነው››
ኤዲ በላብ የተጠመቀውን ፊቱን ጠረገ፡፡

ስሌቱን ሰርቶ ቢያጠናቅቅም ቀሪው
ነዳጅ ኒውፋውንድ ላንድ እንደማያደርሳቸው አውቋል፡

በወረቀት ላይ የሰራው ስሌት ላይ አፈጠጠ ልክ ስሌቱን ያልጨረሰ
ለመምሰል

የቀረው ነዳጅ ጉዞውን ለማጠናቀቅ አይበቃም፡፡ ካፒቴኑ እንደውም ያለውን በእሱ ፈረቃ መቀየሪያ ጊዜ ከነበረው ሁኔታ ያሁኑ የባሰ ሆኗል
ነዳጅ መጠን በአራት ሞተር ስሌት እንዲሰራ ቢያስደርግም እንደማይበቃ ታውቋል፡ መጠባበቂያ ነዳጅ የሚባል ነገር የለም፡፡ አሁን ያላቸው ምርጫ
ጉዞውን ለማሳጠር ሲሉ በአውሎ ንፋሱ ዳር ዳር ሳይሆን በአውሎ ንፋሱ ውስጥ መብረር ሊኖርባቸው ነው፡፡ በአውሎ ንፋሱ መሀል የሚበሩ ከሆነ ደግሞ ሞተር ሊቃጠል ይችላል፡

በዚህ አደገኛ ጉዞ ምክንያት ተሳፋሪዎች ሊያልቁ ይችላሉ። እሱም ቢሆን ከሞት አይድንም፡፡ ታዲያ ካሮል አንን ምን ይውጣታል?

‹‹በል እንጂ ኤዲ›› አለ ካፒቴኑ፡ ‹‹ወደ ቦትውድ (ካናዳ) ወይስ ወደ
ፎየንስ (አየርላንድ) የምንበረው?››
ኤዲ ጥርሱ በፍርሃት ተንገጫገጨ፡፡ ካሮል አን በነዚህ ጨካኝ ወንበዴዎች እጅ ስር ላንድ ቀን እንኳን እንድትቆይ አይፈልግም::ተሳፋሪዎቹን ለአደጋም አጋልጦም ቢሆን ይደርስላታል፡

‹የጉዟችንን አቅጣጫ ለውጠን በአውሎ ንፋሱ መሐል ለመሄድ ዝግጁ ነን?›› ሲል ጠየቀው ካፒቴኑን፡፡

‹‹በአውሎ ንፋሱ መሃል ግዴታ ነው?›› ሲል ጠየቀ ካፒቴኑ በድጋሚ።
‹‹ያለን ምርጫ ወይ በአውሎ ንፋሱ መሃል መሄድ አለበለዚያ መመለስ
ነው›› አለና ኤዲ በረጅሙ ተነፈሰ፡፡
‹‹አትላንቲክ መሃል ደርሶ ወደኋላ መመለስ የሚፈልግ የለም፡››
ኤዲ የካፒቴኑን ውሳኔ በታላቅ ጉጉት ጠበቀ፡፡
👍161
‹‹የፈለገ ይምጣ!›› አለ ካፒቴን ቤከር ‹‹አውሎ ንፋሱን ሰንጥቀን
እንበራለን›› አለ፡፡...

ይቀጥላል
🥰4
አትሮኖስ pinned «#ጠላፊዎቹ ፡ ፡ #ክፍል_ሰላሳ ፡ ፡ #በኬንፎሌት ፡ ፡ #ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ ...አይሮፕላኑ ወደ ኋላ የማይመለስበት ቦታ ላይ ሊደርስ የቀረው ትንሽ ነው፡፡ ኤዲ አዕምሮው በጭንቀት እንደተወጠረ ከምሽቱ አራት ሰዓት ወደ ስራው ተመልሶ ገብቷል፡ በዚህ ሰዓት ፀሃይ ጠልቃ ጨለማ ነግሷል፡፡ የአየር ጠባዩም ተለውጧል፡፡ዝናቡ የአይሮፕላኑን መስታወቶች ይጠልዛቸዋል ኃይለኛው ነፋስ አይሮፕላኑን እንደወረቀት…»
#ሳቤላ


#ክፍል_ሰባ_ሰባት


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ


ባርባራ ለዕረፍት ወደ ባሕር ዳርቻ በሔደችበት ቀን ሳቤላ ከመኝታዋ ወድቃ መጠራሞት ጀመረች።

ለመሰናበት ካሰበች በኋላ እንደገና ባርባራ እስክትመለስ ድረስ ልትቆያት የተሰማማችው ከልጆቹ ጋር መሰንበቷን ተስፋ አድርጋ ነበር " ሚስተር ካርላይልም
በሽተኛዪቱ አስተማሪ ከልጆች ጩኸትና ውካታ ተላቃ ከማንኛውም ሥራ ርቃ የተሟላ ጸጥታና ዕረፍት አንድታገኝ በማሰብ ልጆቹን ሎሲንና አርኪባልድን ወደ ሚስ ኮርኒሊያ ዘንድ ሰደደቸው " ሳቤላ ልጆቹ ከእሷ ጋር እንዲሰነብቱ ሆዷ እየፈለገ እንዳይሔዱ ብላ ለመጠየቅ ፈራች ስለዚህ ያሰበችው ነገር
ሲበላሺባት በዝምታ ተቀበለችው የሳቤላ ሁለተኛዉ ሐሳቧ ደግሞ ማንነቷ እንዳይታወቅባት የመሞቻዋ ጊዜ ከመድረሱ በፊት ከኢስት ሊን ሹልክ ብላ ለመልቀቅ ነገር
እንዳይደርስባት የፈራችው ሰዓት ባላሰበችው ፍጥነት ቀደማት " ጊዜ ዐለፈ ልክ እንደ እናቷ እሷንም ሳይታሰብ አጣደፋት " ዊልሰን እመቤትን ተከትላ ስለ ሔደች የምታስታምማት ጆይስ ነበረች።

ባርባራ የሔደችበት ቦታ ከኢስት ሊን ሃምሳ ኪሎ ሜትር ያሀል ይርቃል
ሚስተር ካርላይል ቀን ቀን ከሥራው እየዋለ ማታ ማታ እዚያው ሔዶ ያድር ነበር " በዚህ ምክንያት ወደ ኢስት ሊን ከዘለቀ ዐሥር ቀን ዐለፈው " በነዚያ ጥቂት ቀኖች ውስጥ የሳቤላ ሁኔታ እየባሰ ሔዶ " ቀኑ ሮብ ነው ሚስተር ካርላይል
ከቤቱ ያድራል ተብሎ ይጠበቃል ።

ጆይስ የምታደርገው ነገር ጠፋት " በጣም ተጨነቀች ። ሳቤላ ተዳከመች
ራሷን መቈጣጠር አልችል አለች » ደብቃው የኖረችው ምስጢር ሊገለጽ ሆነ
የሚገለጽበት ጊዜ ደግሞ ጆይስ አስቀድማ ባለመናገሯ ከሳቤላ ጋር ተመሳጥራ አንደ ደበቀችው ተደርጎ እንዳይተረጐምባት ፈራች ባልና ሚስቱ ምን እንደሚሏት አስባው ተጨነቀች » ሚስተር ካርላይልን ጠርታ ሁሉን ነገር ልትገጽላት ብዙ
ጊዜ እያሰበች መልሳ ትተዋለች እሷ በዚህ ነገር ስትዋልል ሰዓቱ ገሠገሠ በተለይ ከእኩለ ቀን በላይ የነበረው ጊዜ ቶሎ መሸ የሳቤላ ሕይትም ከጀንበሪቷ
ጋር የመጥለቅ እሽቅድምድም የያዘች ይመስል ወደ ጥልቀት ገሠገሠች ጆይስ
ከአጠገቧ አልተለየችም
ቀኑን ሙሉ ዛል ብላ ውላ ወደ ማታ ትንሽ ዐለፍ ያለላት
መስለች ከመኝታዋ ላይ እንደ ሆነች በትራሶች ተደግፋ ትንሽ ቀና አለች " ከነጭ ሱፍ የተሠራ ያንን ልብስ ተደረበላት ደኅና አድርጋ አየር እንድታገኝ የሌት ቆቧ ወለቀላት » መስኮቶች ወለል ብለሙ ተከፈቱላት ።

ሞቃቱ የበጋ አየር ጸጥ ብሏል ጆሮዋ እንደነቃ አእምሮዋም እንዶ ሰላ ነበር
ጆይስ ” አለቻት "ዘ
እመት ” መለሰች ጆይስ
' ላየው ብችል ደሰ ብሎኝ እሞት ነበር "
“ ልየው ! " አለች ጆይስ በትክክል መስማቷን ጆሮዋን በመጠራጠር "
" እሜቴ ልየው አሎኝ ... ሚስተር ካርላይልን ?”

“ ምነው ምናለበት ? ያለሁ መስሎኝ ነው ? እኔ እኮ አሁን ሙት ማለት ነኝ "
እሱን ለማየት ብጠይቅ ነውር ሆነብኝ ? እኔ ላነጋግረው በልቤ ከተመኘሁ ብዙ ቀን ሆኖኛል " ይህ ፍላጎቴ ከሞት ፊት ተደንቅሮ አላሳልፍ አላሰቀርብ አለው .
ጣሬ በዛ ጆይስ እባክሺን ላግኘው? አንዴ ላነጋግረውና በሰላም ልሙት ”

ሊሆን አይችልም ... እሜቴ ” አለቻት ፍርጥ አድርጋ " የማይያገባ ነገር ነው " አይቃጣም !አይታሰብም”

ሳቤላ የጆይስን እምቢታ ስትሰማ እንባዋን ባራት ማዕዘን አወረደችው
ምነው ጆይስ ምን በደልኩሽ? በዚህ የተነሣ መሞት እኮ አልቻልኩም
ነፍሴ አልወጣ አለች ልጆቼን ከኔ ወሰድሽብኝ " እኔ እንዳልታወቅብሽ ስለፈራሽ እዚህ ግድም እንዳይመጡ ብለሽ ሰደድሻቸው " አሁን ደግሞ ባሌን እንዳላናግረው ትክለክይኝ ? ተይ .. ጆይስ ተይ ላግኘው! ግድ የለሺም ንግሪው ይምጣ።

ባሏ ! ምስኪን ዛሬም ባሌ ትለዋለች ጆይስ ከውሳኔዋ ፈቀቅ ባትልም ሁኔታዋ በጣም አሳዘናት ዐይኖቿ በእንባ ክድን አሉ ። ነገር ግን ሚስተር ካርላይልን ጠርታ ከዱሮ ሚስቱ ፊት ብታመጣው ባርባራ ላይ የክህደት ሥራ እንዶ
ፈጻመች እንዳይቆጠርባት ፈራች "

በፉ ተንኳኳ " ጆይስ “ ግቡ ” አለች ። ሁልጊዜ ወደዚያ ክፍል ይመጡ የነበሩት ሁሉት ሠራተኞች ሐናና ሣራ ነበሩ ሁለቱም ማዳም ቬንን ወይዘሮ ሳቤላ እንደ ነበረች አያውቁም ሣራ አንገቷን ብቅ አደረገችና
ስሚ ጆይስ ” አለቻት "
ጌቶች ይጠሩሻል .
ሚስ ጆይስ።

''እሺ መጣሁ።

“ ከመብል ቤት ናቸው " አሁን አርተር ካርላይልን ሰጥቻቸው መምጣቴ ነውኀ

“ ማዳም እንንዴት ሆነች . . . ጆይስ ? ” አላት አርተርን በትከሻው ተሸክሞ አገኘችውና ካርላይልን ።
ጆይስ ምን ብላ እንደምትመልስ ድንግር አላት " በሌላ በኩል'ደግሞ ከጥቂት ሰዓት በኋሳ በግድ የሚገለጸውን ነገር ሽፋፍና ልታልፈው አልፈለገችም

“ በጣም አሟታል , , ጌታዬ ” አለችው "

"በጣም ? ''

“ አዎን ' መሞቷ ነው መሰለኝ።

ሚስተር ካርላይል ያቀፈውን ልጅ በድንጋጤ አወረደው "

“ መሞቷ ነው ”
“ አዎን ዛሬ ማደሯንም እንጃ

“ ምነ ? ለሞት የሚያደርስ ምን ነገር አገኛት ? "

"ጆይስ አልመለሰችለትም " አሷም የምትለው ጠፍቷት ፊቷ ዐመድ መስሎ ነበር።

"ዶክተር ማርቲን አይቷት ነበር ? ”

" የለም ... ጌታዬ " ግን ምንም አይጠቅማትም ”

“ አይጠቅማትም ! " ደገመው ሚስተር ካርላይል ቆጣ ብሎ ሊሞቱ ለተቀረቡቃረቡ ሰዎች የምናደርግላቸው ይኸው ነው ? ማዳም ቬን አንቺ እንደምትይው ታማ ከሆነ ዶክተር ማርቲን በቴሌግራም ተጠርቶ ቶሎ መምጣት አለበት » እስኪ
እኔው ራሴ ሔጄ ልያት ” አለና ወደ መዝጊያው አመራ

ጆይስ ጀርባዋን ወደ መዝጊያው ሰጥታ ከበሩ መኻል ቆመችና እንዳይወጣ ከለከለችው
ጌታዬ . . ይቅርታዎን እለምናለሁ " ነገሩ ደግ አይደለም ።እባክዎን ወደሷ ክፍል መግባቱ ይቅርብዎ ”

“ ለምንድነው የማልገባው ?

“ ሚስዝ ካርላይልን ይከፋቸዋል ብላ ተንተባተበች "

“ የማታመጡት የለም " ሚስዝ ካርላይል ባትኖር የግድ አንድ ሰው ሊያያት
ያስፈልጋል። ከቤቴ ውስጥ ስትሞት ላልጠይቃት ነው ? አብደሻል መሰለኝ ጆይስ !
በይ ከራት በኋላ እጠይቃታለሁና በደንብ አዘጋጂያት ”

ራት ቀረበ ጆይስ ሕፃኑን አርተርን ይዛ ወደ ሣራ ሔደች "

ሚስተር ካርላይል ራት ሊበላ ሲጀምር እኅቱ ደረሰች " የመጣችው ከአንዳንድ ቤቶቿን ከተከራዩ ሰዎች ጋር ጭቅጭቅ ስለ ፈጠረች ለወንድሟ ለመንገር ነበር " የመጣችበትን ከመስማቱ በፊት ጆይስ የነገረችውን የማዳ ቬንን ሁኔታ ነገራትና ሔዳ እንድታያት ጠየቃት "

“ልትሞት ነው?” አለች ኮርኒሊያ እሷም ድንግጥ ብላ “ “ግድ የለህም ይህች
ጆይስ ዘንድሮ በጤናዋ አይደለችም " እስኪ አሁን ምን አገኛትና ነው ልትሞት
ነው ብላ የምታወራ ? ”

ኮርኒሊያ ላይኛው ቆቧንና ካባዋን አውልቃ ከወንበሩ ላይ ጣል አደረገች
መልኳን ከግድግዳው ላይ ከነበረው መስተዋት
ቆቧን ነካ ነካ አድርጋ አስተካከለችና በሽተኛዪቱ ወደ ነበረችበት ወደ ፎቅ ሔዳ በር መታች
ጆይስ " ይግቡ የሚል ምላሽ ሰጠቻት ወዲያው ጆይስ ማን መሆኑን ስታይ
ደነገጠችና ' “ ይተዉ እማማ አይግቡ ” አለችና ከበሩ ሒዳ ከፊቷ ተደቀነች

ማነው ደግሞ እኔን የሚከለክለኝ: ' አለች ነገሩ ስለገረማት ትንሽ ተግ ብላ ካሰበች በኋላ።በይ ዘወር በይ ሴትዮ ! ለመሆኑ ጭንቅላትሽ ደህና ነው?
ከዚህ በኋላ ደግሞ ምን ታመጪ ይሆን?

ጆይስ በሥልጣንም በጉልበትም ዐቅም እንዳልነበራት ታውቅ ነበር
ስለዚህ ሚስ ካርላይልን እንድትገባ አሳለፈቻትና ራሷ ወጣች "
👍20
ምንም የሚደበቅ ነገር አልነበረም " ቀረበች 1 አየቻት " ዐመድ ለብሶ
ጥውልግ ያለው ፊቷ ከመሸፈኛዎቿ ሁሉ ተላቅቆ ተገልጦ ከትራሱ ላይ ወድቋል ግራጫው መደረቢያዋ መነጽሯ ' ያንገቷና የሸንጎበቷ መሽፈኛ ያ ትልቅ ቆብ ሁሉ ከኖሩበት ወልቆ ተቀምጠዋል " በዚያ ሁሉ የመሸፈኛ ጓዝ ተሸፋፍኖ የነበረው ፊት ዛሬ በግልጽ ታየ በርግጥ በጣም ተለውጧል " ይሁን እንጂ የሷ የሳቤላ ቬን ፊት ለመሆኑ ትንሽም አያጠያይቅም ነበር " ሽበት ብርማ ቀለም የቀባው ጸጉሯ በሁለት ወግን ተከፍሎ የሐር ጥቅል መስሎ ካንጎቷ ተቆልሏል የሀዘን ጥላ ያረፈባቸው የሚያምሩት ዐይኖቾም አልተለወጡም " የድሮዎቹ የሳቤላ ቬን ዐይኖች እንደሆኑ ትንሽ እንኳን አያሳስቱም ።

ሁለቱም ተፋጠው ዝም አሉ " ሁለቱም እኩል ተጨነቁ ሚስ ካርላይልም እንደ በሽተኛይቱ ትቃትት ጀመር " በፊትም ቢሆን ማዳም ቬን እመቤት ሳቤላ ስለ መሰለቻት ተጠራጥራ እንደ ነበርና ኋላ ግን ሳቤላ ሙታ የመቀበሯ ጉዳይ ምንም እንደማያጠራጥር ሎርድ ማውንት እስቨርን ካረጋገጠላት በኋላ የሱን ቃል በማመን መጠራጠሯን እንደ ተወች ይታወሳል "

“ እንዴት ደፍረሽ ወደዚህ መምጣት ቻልሽ ? ” አለቻት በቁጣ ሳይሆን ልስልስ ባለ አነጋገር ሳቤላ የመነመኑት እጆቿን ከደረቷ ላይ በትሕትና አመሳቅላ ልጆቼን 'አለቻት በሹክሹክታ ከነሱ ተለይቼ መኖር አልቻልኩም " እዘኑልኝ ?ሚስ ካርላይል " እንዳይቆጡኝ ። በሠራሁት በደል ፡ በራሴ ላይ ባመጣሁት ኀዘንና መከራ ልጠየቅበት ወደፈጣሪ እየሔድኩ ነው ”

“ አልቆጣሽም ”

ወደ ዘለዓለም ዕረፍቴ በመሔዴ ደስ ይለኛል” አለች ዕንባዋ ችፍፍ ብሎ”
“እስኪ ስሚ ልጄ” አለቻት ኮርኒሊያ ወደ ሳቤላ ጠጋ ብላ በመደገፍ። “ላንቺ
ከኢስት ሊን መጥፋት ምክንያት የሆንኩኝ እኔ ነበርኩ እንዴ ? ”

ሳቤላ ራሷን በአሉታ ለመነቅነቅ ሞከረች ዐይኖቿን ስብር አድርጋ ድክም ባለ ድምፅ “እርስዎ አይደሉም ያስወጡኝ " እኔ እንድወጣም ያደረጉት ነገር የለም በእርግጥ በአርስዎ አልደሰትም ነበር። ነገር ግን የመሔዴ ምክንያት እርስዎ አይደሉም ይቅር ይበሉኝ ... ሚስ ካርላይል ይማሩኝ "

“ ተመስግን ጌታዬ ! ” አለች ኮርኒሊያ በሆዷ" ከዚያም ድምጿን ከፍ አድርጋ ' “ እኔም ቤትሺን ከዚያን ጊዜ የተሻለ የደስታ ቤት ላደርግልሽ ይገባኝ ነበር
አንቺ ከለቀቅሽ ጀምሮ እስከ ዛሬ ይቆረቁረኛል" በይ እኔንም ማሪኝ” አለቻት
አጅዋን ይዛ

ሳቤላ የሚስ ካርላይልን እጅ ወደሷ ሳብ አድርጋ ይዛ “ አርኪባልድን ለማየት እፈልጋለሁ ” አለቻት በሹክሹክታ “ ጆይስን እንድትጠራልኝ ብለምናት
አምቢ አለችኝ " እኔ ሙት ማለት ነኝ " ባገኘውና ባነጋግረው ምን አለበት?
አሁንም ለአንድ ደቂቃ ብቻ ልየውና ይቅርታ ሲያደርግልኝ ልስማው ከዚያ በኋላ በሰላም እሞታለሁ ”

ሚስ ካርላይል ነፍሷ ልትወጣ በጣር ላይ ሆና የለመነቻትን መንፈግ ስለ ከበዳት ይሁን ' ወይም ሌላ ምክንያት ይኑራት አይታወቅም " የሳቤላን ልመኖ ሰምታ ወደ በሩ ወጣች " ጆይስን ከኮሪዶሩ ውስጥ ግድግዳው ተጠግታ ዐይኖን በሽርጧ ሸፍና አየቻትና በጅዋ ጠቅሳ ወደሷ ጠራቻት "

“ ይኸን ነገር ካወቅሽው ስንት ጊዜ ሆነሽ ? "

“እንድ ጊዜ ለሊት እሳት ተነሣ ተብሎ ሁላችን ተደናግጠን ከየመኝታ
ቤታችን የወጣን ጊዜ ምንም ዐይነት መሸፈኛ ሳያደርጉ ፊታቸው በሙሉ ተገልጦ አየሁትና ዐወቅኋቸው » መጀመሪያ ግን መንፈሳቸው እንጂ እሳቸው በአካል የመጡ አልመሰለኝም ነበር ከዚያ ወዲህ እኔም ከፍራቴ የተነሣ የኖርኩት ኑሮ ኑሮ
አይበለው።

“ በይ እሺ አሁን ሒጅና ጌታሽን ወደኔ እንዲመጣ ንገሪው"

“ኧሪ ! እማማ ! መንገሩ ደግ ነው ? እንዲያዩዋቸው ነው ? ”

“ሒጅና ጌታሽን ወደኔ እንዲመጣ ንገሪው አለቻት መልሳ በማያወላወል ትእዛዝ። "አዛዥዋ አንቺ ነሽ ወይስ እኔ .. ጆይስ ? ”

ጆይስ ወረደችና ሚስተር ካርላይልን ራት ከሚበላበት አስነሥታ ይዛው መጣች

“ ማዳም ቬን ባሰባት እንዴ . . ኮርኒሊያ ? እኔን ፌለገችኝ ?

“ አዎን ልታነጋግርህ ትፈልጋለች ”....

💫ይቀጥላል💫
👍19🥰4
😘 #ቃል 😘
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ

ምዕራፍ ሀያ ሰባት (27)


« ግን ሻንጣ ፤ ቅራቅንቦ የሚያስፈልጋት መሆኑን ርግጠኛ ነህ » አለች። « ይመስለኛል ። ወደ አንድ ቦታ እንድንሄድ አስቤአለሁ። ሳታስበው እንዲሆን ስለምፈልግ ፤ ቲኬቱን እሻንጣ ውስጥ ከትቼ ላስገርማት ብዬ ነው» አለ ። አንድ ትኬት ደብቆ ለመስጠት አምስት መቶ ዶላር መክፈል ይገባል ቤን ? ቤን አቭሪ እንዲህ ገንዘብ በታኝ ሆነ ? አልፎለታል ማለት ነው ። « ዕድለኛ እመቤት ናት በለኛ»
« ዕድለኛውንኳ እኔ ሳልሆን አልቀርም››
«እንዴት ? ለመጋባት አስባችኋል ማለት ነው ?»
«የለም ነገሩስ ለሥራ ነው ። የሥራ ጉብኝት አለብን»
‹‹ ያኛው ቀይ ጥብጣብ ያለው ቡናማ ከፋይ ሻንጣ ቆንጆ መሰለኝ»
«እኔም እሱ ላይ ነው ዓይኔ ያረፈው» የሜሪን ምርጫ ተቀብሎ የሱቁን ረዳት ጠራት ። ‹‹አመሰግናለሁ ሚስ…..›› አለ፡፡ ለልጅቷ ሚገዛዉን እቃ ካሳያትና እንዲጠቀለልለት ከነገራት በኋላ ሜሪን እያየ ። «አዳምሰን» ስትል ስሟን ነገረችው «ምንም ምስጋና አያስፈልግም ። ምክንያቱም እኔም ደስ ብሎኛል ። ይልቅ ትንሽ ጥያቄ ሳላበዛብህ አልቀረሁምና ይቅርታ መጠየቅ ያለብኝ እኔ ነኝ መሰል ። ዓመትባል ሲቃረብ ይኸው ነኝ ። የማይሆን የማይሆን ነገር አደርጋለሁ»
«እኔም ያው ነኝ ። ብቻ የዘንድሮው ዓመት ሲያልፍ ቢከፋኝም አይፈረድብኝም ። ደስ የሚል ዓመት ነበር ። ኒው ዮርክ እንኳ ሳይቀር»
«ኒው ዮርክ ነው እምትኖረው ? »
«ከመሄድ ስገላገል ፣ አዎ ። ግን ሥራዬ ቁጭ እሚያደርግ አይደለም ። ካንዱ ወዳንዱ መዞር ነው» ይህም ቢሆን ከማይክል ጋር አብረው እንደሚሠሩ ርግጡን የሚናገር ነገር አይደለም ። ብትጠይቀው ደስ ባላት ግን አትችልም ። ይህን ስታስብ በጣም ከፋት ። ኦመማት። ስለሌላ የሷ ስላልሆነ ሰው መጠየቅ ስላሰኛት አመማት ። መጠየቅና ማወቅ ስትችል ባለመቻሏም አመማት ።

«ነገሩ እንኳ የጅል ነገር እንደሆነ ይገባኛል ። ግን ከዚህ ወጣ ብለን አንዳንድ ነገር ይዘን መጠጥ ቢጤ ይዘን ብንጨዋወት ? ለነገሩ እቸኩላለሁ ። አውሮፕላን መያዝ አለብኝ ። ግን ቅዱስ ፍራንሲስ ሆቴል ጐራ ብለን »
«እኔም ቢሆን በራሪ ነኝ ። ያም ሆኖ ሐሳቡ የድርጊቱን ያህል ነው ። አመሰግናለሁ ሚስተር አቭሪ. . .» አለች ። ፊቱ ድንገት ቅጭም አለና ፤ «ስሜን እንዴት ልታውቂ ቻልሽ ?» ሲል ጠየቃት ። «ደረሰኝ ሲቆርጡልህ ስምህን ሲጠሩ ሰማሁ» አለች አመላለሷ ፈጣን ነበረና በጥርጣሬው ሊገፋ አልቻለም ይልቁንም እንዲህ ቶሎ ተገናኝተው ቶሎ በመለያየታቸው አዘነ ። በጣም ቆንጅዬ ልጅ ናት ፤ አለ በሐሳቡ ። ዌንዲን እወዳታለሁ ። ቢሆንም ከአንዲት ቆንጅዬ ልጅ ጋር አንድ ነገር መጠጣት ኃጢአት አልነበረም ። ድንገት አንድ ሀሳብ ብልጭ አለበት «ወዴት ነው የምትሔጂው ፤ ሚስ አዳምሰን?»
«ወደሳንታፌ ፤ ኒው ሜክሲኮ » ተስፋ ቆረጠ ።
«ምን ዓይነት ርጉም እጣ ነው ። እኔ ደሞ ወደ ኒውዮርክ የምትሔጂ ቢሆን ስል »
‹‹ሻንጣ የተገዛላት እመቤት አንድ ላይ ብታዬን እጅግ ደስ እንደምትሰኝ አይጠረጠርም ነበር ። »
«እጅ ሰጠሁ ። ደግ እንግዲህ አምሳክ ካለ ሌላ ጊዜ...»
«ሳንፍራንሲስኮ ትመጣለህ እንዴ ፣ ብዙ ጊዜ?»
«ከዚህ በፊትንኳ አልነበረም ። ወደፊት ግን እይቀርም እመጣለሁ ። ማለት እንመጣለን ። የምሠራበት ድርጅት አንድ ትልቅ ፕሮጀክት አለው» አለ ። « እዚሁ ሳንፍራንሲስኮ ማለቴ ነው ። ስለዚህ ወደፊት ከኒውዮርክ ይልቅ ይኸ ሳይሆን አይቀርም መኖሪያዬ »
«እንዲያ ከሆነ ምናልባት እንገናኝ ይሆናል » ይህን ያለችበት ድምፅ በመጠኑ መከፋትን የሚገልዕ ነበር ምንም አይደለም ። ከማይክል እንጂ ከቤን ጋር ቂም የለኝም ። ስለዚህ አዘውትረን ብንገናኝም ክፋት የለበትም። የሱቅ ረዳቷ እቃው መሰናዳቱን ገለጸችላቸው ። ቤን ጨበጣት ። ጠበቅ አድርጋ ጨበጠችው።
በመገረም ቀና ብሎ አያት በለሆሳስ ። « መልካም የገና በዓል » አለችና በፍጥነት ካጠገቡ ተሰወረች « ወዲያ ወዲህ ተገላምጦ ቢያይም ሊያገኛት እይችልም ።

ከቤን እንደተለያዩ ሰውነቷ ድክምክም አለ ።
ከሱቅ እንደ ወጣች ታክሲ ተሳፍራ ወደ ቤቷ ጉዞ ቀጠለች ከዚያ በፊት ግን ፍሬድን ለእንስሳት ህክምናና ጥበቃ ድርጅት በአደራ መልክ ሰጠችው። ምክንያቱም አያስፈልጋትም። ጉዞዋ አለና በዚያም ላይ በርከት ያለ ቦታ ማየትና ማዳረስ አለበባትና የፍሬድ መኖር አመቺ አልነበረም። ብቻዋን መሔድ አለባት ። ናንሲ ማክአሊስተር በሚል ስም የዱሮ ሰብእናዋ የምትኖርባቸውን የመጨረሻ ሳምንታት ከማንም ጋር መካፈል የለባትም። ምስክር መኖር የለበትም። የአንድ ሕይወት መደምደሚያ ፤የአዲስ ሕይወት መጀመሪያ ነውና ብቸኝነት ያስፈልጋታል። እቤቷ እንደደረሰች ተዘዋውራ ተመለከተችው በሩን ስትዘጋ አንድ ሀረግ ተናገረች ። ለቤን አቭሪ፣ ለማይክል ፤ ያውቋት ለነበሩ ፤ ይወዷት ለነበሩ ፤ ታውቃቸው ትወዳቸው ለነበሩ ሁሉ « ደህና ሁኑ » የሚል ሀረግ ተናገረች ። ደረጃውን ስትወርድ እንባ ተናነቃት ። ካሜራዋንና የዕቃ ሻንጣዋን ይዛ ነበር ።

•••••••••••••••

እረፍቷን ጨርሳ ወደ ሳንፍራንሲስኮ ስትመለስ ፒተር እየር ማረፊያ ድረስ መጥቶ እንዳይቀበላት ቃል አስገካችው ። ምክንያቱም ያለሸኚ እንደወጣች ያለተቀባይ ልትገባ ስለፈለገች ነበር ። ጉዞውን ስትጅምር ልቧን ከብዷት መንፈሷም ተሸብሮ ነበር። ያንለት ቤን አቭሪን ማግኘቷ ወዳለፈው ሕይወቷ እየተመዘዘ በመመለስ ብዙ ነገሮችን እንድታስታውስ አስገደዳት ። በዚህም የተነሳ በመጀመሪያዎቹ እለታት ከማንም ጋር ለመነጋገር ማንንም ለማዳመጥ አልተቻላትም ። ከሀሳቧ ጋር ተፋጣ ነበር ። ያ ጉዞ ግን አብነት ስለነበረው ከጭንቀቷ ፈወሳት ። የሰላም ጊዜ አሳለፈች ። እጅግ ብዙ ነገርም ሠራች ። ወደ ሳንፍራንሲስኮ ስትመለስ ፤ ከሳንፍራንሲስኮ ስትነሳ የነበረው ጭንቀት አልነበረም ። አሁን ስለቤን አቭሪ ማሰብ አያስፈራትም ። ያለፈውን ሕይወቷን መለስ ብላ ለመቃኘት አትፈራም ። ይህን ያህል በመለወጥ አዲስ ሰው ሆነች ። ለመጨረሻ ጊዜ ያለፈው ሕይወቷ የሌላ የምታውቃት ሴት ሆና ታያት ።

ናንሲ ማክአሊስተር ባዕድ ሆና እሷ ሜሪ አዳምሰንን ሆነች። ሜሪ የገናንም በአል ሆነ የዘመን መለወጫን በማታውቃቸው ሰዎች መካከል ሆና አሳለፈችው ። ሰዎች በአላትን ሲያክብሩ ናንሲ እነሱን ፎቶ ግራፎች አነሳቻቸው ። በተለይ የገናን በዓል በታአሰ አካባቢ ስታከብር የበረዶ ሸርተቴ የሚጫወቱት ብዙ ነበሩና ይህን ጨዋታ ለመሞከር ልቧ እጅግ ገፋፍቷት ነበር፡፡ እንዲህ ያለውን አደጋ ላይ ሊጥል የሚችል ጨዋታ ላለመሞከር ለፒተር ቃል ገብታለት ነበርና ለራሷም በመፍራት ፍላጎቷን መግታት ግድ ሆነባት ። ፒተር የገባውን ቃል አክብሮ ሊቀበላት እንዳልመጣ! ስትገነዘብ ደስ አላት ። እንዲሀ በማያውቅህ ሠራዊት ውስጥ ስትገባ ማንም ነህ ። ማንም ማንንም አያይም ተሰውሮ መኖርን ደግሞ ብዙ ተላምዳዋለች ። ባለፉት ሁለት ዓመታት ፊቷ በፋሻ ተደግልሎ ሥጋ ሳይሆን መልኳ ሻሽ በነበረበት ጊዜ ላለመታየት ከማድረግ ፣ ከመደበቅ በስተቀር ሌላ አማራጭ አልነበራትም ። ይምሰላት እንጂ የትም ብትሔድ ፤ የትም ብትገባ ያለመታየት ዕድል አልነበራትም ። የተዋበው መልኳ ፣ አረማመዷና አጠቃላይ እንቅስቃሴዋ አለባበስዋ ይህ ሁሉ ዓይንን በግድ ይስባሉ ። የግንባሯን ላይ ፋሻ ለመከለል ያደረገችው ኮፍያ ሳይቀር ለሷ ውበት ሆኗታል ። ይሁን እንጂ ይህን አልተገነዘበችውም ። ስለዚሀም ማንም አያውቀኝም
👍23
ማንም አያየኝም ብላ አሰበች ።

ከታክሲ ወርዳ ወደ አፓርታማው ለመግባት ደረጃዎችን ስትወጣ ርምጃዋ ፈራ ተባ ያለ ነበር ። አንድ ያልታሰበ ነገር የሚያጋጥማት ፤፡ አፓርታማው ተቀይሮ የሌላ ሰው ቤት ሆኖ የምታገኘው የመሰላት ይመስል፤ ገባች ። ፀጥ እንዳለ ምንም ነገር ሳይለወጥ አገኘችው ። ድንገተኛ ቅሬታ ተሰማት። ምን ፈልጌ ምን ጠብቄ ነበረና ቅር ተሰኘሁ ። ልክ በሩን ስከፍት የክብር ዘብ ተሰልፎ በታምቡርና በጥሩምባ እንዲቀበለኝ ፈልጌ ነበር ይሆን? ስትል አሰበች ። ሁኔታዋ አስገረማት ። አስቂኝ ሆኖ ታያት ። ወይስ ፒተር አልጋዬ ስር አድፍጦ ቆይቶ ብቅ እንዲል ምኞት ነበረኝ ? አለች ። ፒተር እንዳይቀበላት የከለከለችው ራሷ ስትሆን እንዴት ይህ ምኞት በልቧ ውስጥ ሊኖር ይችላል ? ፒተር …..

የላይ ልብሷን አውልቃ አልጋዋ ላይ ተዘረጋችና ሀሳቧን ለቀቀችው ። ፒተር . . . ፒተር የሚያደርግላት ሀክምና ወደ መፈጸሙ ተቃርቧል ። እንዲያውም ካሁን በኋላ እንደ ሀኪምና ታካሚ የሚገናኙት አንድ ቀን ብቻ ነው ። እንግዲህ ሥራዬን አከናውኜ ጨርሻለሁ ። ደህና ሁኝልኝ ቢለኝ ምን ይውጠኛል ? አይ ይህ አይሆንም ። ጅልነት ነው ። ፒተር ስለሷ ያለውን አስተሳሰብ በሚገባ ታውቀዋለች ። ሆኖም ምኑ ይታወቃል ? የለም አይሆንም ። የፎቶ ግራፎቿን ኤግዚቢሽን ያዘጋጀላት ፤ ሁሉን ነገር ያደራጀላት እሱ ሆኖ ሳለ ... በዚያም ላይ እንደታካሚ ሳይሆን እንደሰው... . ምን ያህል እንደሚወዳት እንደሚንከባከባት መች አጣችው ! ይህ ሁሉ ሀሳብ ሲተራመስባት አይዞሽ የሚላት ።፤ በኑሮ ላይ እንደጋገፋለን የሚላት ሰው ፈለገች ። አዲስ ሰው ነሽ ። ሜሪ አዳምሰን ነሽ ። ሜሪ አዳምሰን ጠንካራ ሰው ነች ። ትልቅ ደረጃ ይጠብቃታል ። ኑሮን አሳምራ ትኖራታለች የሚላት ሰው ፈለገች ። ሜሪ ጠንካራ መሆኗን አሰበች ። ነኝ አለች ። ሜረ ነኝ ጠንካራ ሰው ነኝ ። ታዲያ ምን አስፈራኝ ። አይዞሽ ባይ ለምን አስፈለገኝ… አለች በሀሳቧ ።

ከአልጋዋ ላይ ተፈናጥራ ተነስታ ምስሏን በመስታወቱ ውስጥ ተመለከተች ። በተቅበዘበዘ ሁኔታ ካሜራዋን አነሳች ። እንደለማዳ እንስሳ ዳበሰችው ። የኔ ነህ አለችው ። የሚያስፈልጋት ጓደኛ ያ ካሜራ ብቻ እንደሆነ አመነች ። ሀሳቧ ግራ አጋባት ። ምን ሆንኩ ? አለች ። ምንም ስትል ጥያቄዋን መለሰች ። ምንም አልሆንኩ ፣ ስለ ደከመኝ ነው። ሀሳቧን አቋርጣ ተኛች በማግሥቱ ጧት ወደ ፒተር መስሪያ ቤት ሄደች ። እግረመንገዷን ፍሬድን አደራ ካስቀመጠችበት የእንስሳት መጠበቂያ ሥፍራ ይዛው ሄደች ።

« አረ በስላሴ ! እንዴት አምሮብሻል እባክሽ ። ደሞ ካፖርትሽ ልክክ ብላብሻለች » አለ ፒተር እንዳያት የግንባሯን ፋሻ ለመሸሸግ የምትጠቀምበትን ኮፍያ አውልቃ በጅዋ ይዛ አይቶ በፍቅር የተነከረ ፈገግታ አሳየችው ። በደስታ ተሞላ ። ኮፍያውን አየት ካደረገች በኋላ ወደ ቢሮው የቆሻሻ መጣያ ሄደች « ከዛሬ ጀምሮ ባርኔጣ እሚሉት ነገር የማላደርግ መሆኔን በዚህ ድርጊት አስታውቃለሁ ። » ይህን ተናግራ ኮፍያውን ጭምድድ አድርጋ እቆሻሻ መጣያው ውስጥ ከተተችው ። « ፈጽሞም ባርኔጣ እንደማይነካሽ ርግጠኛ ነኝ » አለ ፒተር። « ስሜቴን ስለተረዳህልኝም ስለሌላው ሁሉ ምሥጋናዬ የላቀ ነው» አለች ሜሪ ።

የተሰማት ግን ካለችው ሁሉ የላቀ ነበር ። ፒተርን እቅፍ አድርጋ ልትስመው ፈለገች ። አላደረገችውም ። ፍላጐቷን ግን ከጠቅላላ ገፅታዋ አነበበ ። ዓይኗን ከፒተር ሳይ ሳትነቅል ተመለከተችው ። በጣም እንደናፈቃት ገባት ። ከዛሬ በኋላ ፒተር ጓደኛዋ እንጂ ሀኪሟ አይሆንም ። ከፈለገች ጓደኛዋ ፤ ከፈቀደችለት ሁሉን ነገር ይሆናል ። ፍቅረኛዬ ሁን ብትለው ደስ ይለዋል ። ባሌ ሁን ብትለውም እንደዚሁ ። ይህ ደግሞ ከንቱ አስተሳሰብ ወይም ግምት አልነበረም ። እንደሚያፈቅራት ብትፈቅድለትና ፍቅራቸውን ለመካፈል ቢችሉ ደስ እንደሚለው ደጋግሞ ገልጾላታል ።

ይቀጥላል......

ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️❤️
👍17🎉2
#ሳቤላ


#ክፍል_ሰባ_ስምንት


#ድርሰት_ሚሲስ_ሔንሪ_ውድ


ጆይስ ወረደችና ሚስተር ካርላይልን ራት ከሚበላበት አስነሥታ ይዛው መጣች

“ ማዳም ቬን ባሰባት እንዴ . . ኮርኒሊያ ? እኔን ፌለገችኝ ?

“ አዎን ልታነጋግርህ ትፈልጋለች ”

ሚስ ካርላይል እየተናገረች በሩን ከፈተችው "መጀመሪያ እሷ እንድትግባ በጁ አመለከታት “ የለም” አለችው “ ብቻህን ገብተህ ብታያት ይሻላል ”

ሊገባ ሲል ጆይስ ክንዱን ያዘችው “ ጌታዬ ተዘጋጅተው ይግቡ“ እማማ
ለምን አይነግሯቸውም ?”

ሁለቱንም ትክ ብሎ አያቸው ሁኔታቸውን ይኸ ነው ብሎ ለመናገር አልቻለም
አንግዳ ነገር ሆነበት " እንዲያውም ወደ ዕብደቱ ወሰድ ያደረጋቸው መሰለው
ፊቷ ምንም ቢሆን ተለውጦ የማያውቀው ኮርኒሊያ እንኳን ምንም ኮስተር ብላ
ብትቆምም ከንፈሮቿ ሲንቀጠቀጡ መቁጣጠር አልቻለችም " ሚስተር ካርላይል ግንባሩን ቋጥሮ ሲገባ እነሱ በሩን ዘጉበት "

በቀጥታ ወደ በሽተኛይቱ አልጋ ቀስ ብሎ ተጠጋና “በጣም አዝናለሁ ማዳም ቬን...” ብሎ የጀመረውን ሳይጨርስ ቀሪዎቹ ቃላት ምላሱ ላይ ተንከባለሉ"
ሊወጡ አልቻሉም . እሱም እንደ ጆይስ የሳቤላን መንፈስ ያየ መሰለው
ከአልጋው ትንሽ አፈገፈገ ወርዶ አንገቷ ላይ የተቆለለው ጸጉሯ የሚያምሩትና የኀዘን ዳመና የጣለባቸው 0ይኖቿ ሳይቀሩ የሳቤላ ቬንን መልክ ቁልጭ አድርገው አሳዩት

አርኪባልድ ! ” አለችው "

የሚንቀጠቀጠው እጅዋን ዘረጋችና እጁን ያዘችው " ትክ ብሎ አያት» ከሕልም የነቃ ይመስል ዙሪያውንም አስተውሎ አየ "

“ነፍሴ ያንተን ይቅርታ ሳታገኝ ከሥጋዋ መለየት አልቻለችም " አለችው
የሰራችውን በደል ስታስብ ዐይኖቿን ስብር አድርጋ “ ተው ' ፊትህን አታዙርብኝ " ለአንዳፍታ ታገሠኝ ይቅር ብየሻለሁ ብቻ በለኝና በሰላም ልሙት

“ ሳቤላ ! አንቺ ነሽ? አንቺ ነሽ ? ማዳም ቬን የነበርሽው ? " አለ የሚናገረውን አላወቀውም።
ይቅር በለኝ ማረኝ... አርኪባልድ | አልሞትኩም » የደረሰብኝ አደጋ ለወጠኝ እንጂ አልገደለኝም » ነገር ግን ማንም አላወቀም ስለዚህ ማዳም ቬን
ተብዬ ወደዚሁ መጣሁ " ተነጥዬና ርቄ መኖር አልቻልኩም » ማረኝ ... አር
ኪባልድ ማረኝ " "

የሚናገረው የሚያደርገው ቅጡ ጠፋው " አምሮው ጠሮ ነፋስ እንደ ገባበት
ተበጠበጠ ግራ ገብቶት ዝም ብሎ እንደ ቆመ ነገሯን ቀጠለች "

“ ከአንተና ከልጆቼ ተነጥዬ መኖር አልቻልኩም " ያንተ ናፍቆት ሊገድለኝ ሆነ ” አለችው " አነጋግሯ የትኩሳት ቅዠት ይመስል ነበር “ “ እንደዚያ አሳብዶኝ ካን† ከተለየሁ ወዲህ የአንዲት ቅጽበት እንኳን ሰላም አግኝቸ አላውቅም .
መላው ባይጠፋኝ ኖሮ ወዲያው ተመልሸ እመጣ ነበር ከቤት ከወጣሁ አንድ
ሰዓት እንኳን ሳልቆይ ጸጸት ያዘኝ እያደር እየከበደኝ እየጠናብኝ ሔደ ምን እንዳ
ስመሰለኝ ታየዋለህ ? እየው ተመልከተው " ብላ የሸበተው ጸጉሯን የመነመ
ነውን እጁዋን አሳየችው » አንተው ማረኝ ይቅር በለኝ !ጥፋቴ በጣም ከባድ ነው ! የተቀበልኩት ቅጣት ግን ይበልጣል " ለብዙ ዘመን ከባድ መከራ ከባድ
ሥቃይ ተቀብያለሁ " ሕይወቴ ረጅም ዘመን የፈጀ የጻዕረ ሞት ሕይወት ነበር ”

“ እንዲያው ሲጀመር ምን ሆነሽ ሔድሽ?”

“ ለምን እንዶ ሔድኩ አላወቅህም? ”

“ የለም አላውቅም " እስከ ዛሬ ምስጢር እንደ ሆነብኝ ነው ”

“ አንተን ከመውደዴ የተነሣ ነበር የሔድኩት " ከንፈሮቹን በንቀት ቀስቀስ አደረጋቸው " በጣር ላይ ሆናም የምትቀልድበት መሰለው

“ ተው እንደሱ አድርገህ አትየኝ " አቅም የለኝም " ያለው የሌለው ጉልበቴ አልቋል " ከሰውነት ወጥቻለሁ " ዐይንህ ያያል " የምነግርህ እውነት መሆኑን ተረዳልኝ ነገሬ ግልጽ ካልሆነ እንጃ በጣም እወድሀ ስለ ነበር ጠረጠርኩህ፤ እኔን አለሁልሽ ብለህ እያታለልክ ፍቅርህን ለሌላ የሰጠህብኝ መስለኝ » ስለዚህ በጥርጣሬ ቅናት እንደ ቆሰልኩ ከዚያ ክፉ ሰው ወጥመድ ገባሁ " እንድበቀልህ በጆሮዬ ሹክ ይለኝ ነበር ”

“እኔ ግን አንቺን በሐሳብም፡ በቃልም በተግባርም ለማታለል አልሞከርኩም"
ያንጊዜም ታውቂኝ ነበር " ከዚያ ወዲህም ሳታውቂኝ አልቀረሽም

“አርኪባልድ ... አብጀ ነበር " በዕብደት እንጂ በጤንነት እንደዚያ ያለውን ሥራ አልሠራውም ነበር " ስለዚህ እርሳው ' ይቅር በለኝ ”

“ መርሳት አልችልም " ይቅር ካልኩሽ ግን ቆይቻለሁ "

“ ከዚያ ሌሊት ወዲህ ያለፈውን የኀዘንና የብስጭት ጊዜ ለመርሳት ሞክር” አለችው ዕንባዋ በሁለት ጉንጮቿ እየወረደ " ሥጋው አልቆ አጥንቱ ብቻ ቀርቶ በትኩሳት የሚቃጠለውን ክንዷን ወደሱ ዘርግታ : “ በሱ ፈንታ የፍቅር ጊዜአችንን ላለመርሳት ሞክር "
አኔን በመጀመሪያ ወደ ዐወቅህበት ዘመን መልሰው " ከዚህ ቤት ሳቤላ ሼን አየተባልኩ ካባቴ ጋር ደስተኛ ልጅ የነበርኩበትን ዘመን አስታውስ ያኔ ለኔ ባትገልጽልኝም እንዴት ልትወደኝ እንደቻልክ አስታውስ" አባቴ በሞተ ጊዜ የተቸገርክልኝን በዚያች ምናምን ባልነበረኝ ሰዓት አንድ መቶ ፓውንድ የሰጠኸኝን ወደ ካሰል ማርሊንግ የመጣህ ዜ
ሐሳብህን ላንዳፍታ
ላገባህ ቃል የገባሁበትን ለመጀመሪያ ጊዜ ከንፌሬን የሳምከኝን ከተጋባን በኋላ የነበረን ደስታ ትዝ ይልሃል ? አብረን ያሳለፍናቸውን የፍቅር ዘመናት ታስታውሳቸዋለህ ? ሉሲ ስትወለድ ከሞት አፋፍ በመትረፌ የተሰማህን
ሁሉ ትዝ ይልሃል ? ”

“ ታዲያ አሁን እኔን ይህን አጠፋህ የምትይኝ አለሽ ” አላት አሳዛኝ እጅዋን
በእጁ ይዞ ።

አንተን ? በኔ ቀርቶ በአምላክ ዘንድም ጥፋት አይገኝብህም " ከልብህ
ወደከኝ ነበር " ለደኅንነቴ ባያሌ» ስትጨነቅልኝ ነበር » አንተ ደግሞ ምንህ ይወቀሳል? ምን አንደነበርክና ዛሬም እንዴት ያለህ ሰው እንደሆንክ ሳስበውና ከመለስኩልህ ውለታ ጋር ሳነጻጽረው በኃፍረትና በጸጸት መሬት ተከፍታ ብትውጠኝ እወድ ነበር ለራሴም ጥፋት የሚያበቃኝን ቅጣት ተቀብያለሁ ባንተና
በልጆችህ ያመጣሁባችሁን ውርደት ግን ማስለቀቅ አልችልም ”

“ የኔን ፈተና ግን አስበው " አለችው ድምጿ እየደከመ " እሱም እየራቀ የሔደውን ድምፅ ለመስማት ጆሮውን ጠጋ ለማድረግ ተገደደ ። “ በዚህ ቤት ውስጥ ከሚስትህ ጋር ተቀምጬ ምን ያህል እንደምታፈቅራት እኔን ትዳብስኝ እንደ ነበረው ስትዳብሳት እያየሁ ' በቅናት ስንገገብ ኖርኩ አሳልፌ ለሌላ ከስጠሁህ በኋላ ያፈቀርኩህን ያህል አፍቅሬህ አላውቅም ነበር " እስቲ ይታይህ' ዊልያም ልጄ ጉልበቱ እየመነመነ ሰውነቱ እያለቀ ሲሔድ እያየሁ ነፍሱ በምትወጣበት
ሰዓት ካንተ ጋር ብቻችንን ሆነን ስንጠብቀው እናቱ መሆኔን እንኳን ለመናገር
አለመቻሌ እንደ ሞተም ቤተሰቡ ሁሉ ሰምቶ ሲደናገጥ የኔን የወላጅ እናቱን ኀዘን ሳይሆን የስዋን ትንሽ መጠነኛ ኀዘን ነበር የምታጽናኑት " እኔ ባሁኑ ጊዜ ከዚህ ቤት ችየው የኖርኩት ፈተና የሞት ያህል መራራና አስጨናቂ ነበር "

“ለምን ተመልሰሽ መጣሽ ? ” አላት "

“ ነገርኩህ እኮ ካንተና ከልጆቼ ተለይቸ መኖር አልቻልኩም '

“ስሕተት ነበር ! ፍጹም ስሕተት ነበር የሠራሽው
👍10
በጣም ስሕተት ነበር እውነትህን ነው ግን ማንነቴን እንዳይታወቅ ያዶረግሁት ጥንቃቄ እስከተሳካ ድረስ የስሕተቱን ውጤት የተቀበልኩት የቅጣቱን ጽዋ የጠጣሁት እኔ ብቻ ነኝ ሞት እናቴን እንዳደረጋት እኔንም ሳላስበው ድንገት ዘሎ አነቀኝ እንጂ እኔ እስክ ሞት ድረስ ከዚህ ቤት እቆያለሁ የሚል hሳብ አልነበረኝም "
“ እንዳልከው ፍጹም ጥፋት ነው አሁን አንተን አስጠርቸ ማነጋገሬ ራሱም ከብዙዎቹ ጥፋቶች አንዱ ነው ነገር ግን እኔ ለዚህ ዓለም ሙት ማለት ስለሆንኩ ወደዚያኛው ለማለፍ አፋፍ
ላይ በማንዣበብ ላይ ስላለሁ አዲሱን ቃል ኪዳንህን የሚነካ አይመስለኝም ግን ባሌ ነበርክ " ነበር...አርኪባልድ ስለዚህ ባለፉት ጥቂት ቀኖች ውስጥ ይቅርታህን ለመለመን በጣም ስፈልግህ ነበር "
ምነው ያለፈው ነገር ሁሉ እልም ብሎ በቀረ " ምነው የፈጸምኩት ጥፋት የተቀበልኩት መከራ ሁሉ ቅዠት ሆኖ እልም ብሎ በጠፋና እንደ ዱሮ የምትወዳት ጤነኛና ደስተኛ ሚስትህ ሁኜ በነቃሁ »

"እኔ ወደ ዊልያም እየሔድኩ ነው » ሉሲና አርኪባልድ ይቀራሉ " ራራላቸው ኋላ ለተወለዱት ልጆችህ አድልተህ ፍቅርህን እንዳትቀንስባቸው " በኔ ጥፋት እነሱን አትጥላቸው
በናታቸው ዐይን አትያቸው ”

" ይህን አደራ ሊያናግርሽ የሚችል ምልክት አየሽብኝ?ልጆቹን አሁንም ልክ አንቺን እወድሽ እንደ ነበረው ያህል አወዳቸዋለሁ "
"አርኪባልድ...ወደሚቀጥው ዓለም ለመሔድ ከደፉ ላይ ቁሜአለሁ" አልፌው ከመሔዴ በፊት አንድ የፍቅር ቃል አትተነፍስሽልዥምን ? የዛሬውን ማንነቴን ለጊዜው ከአእምሮህ አውጣውና ብትችል ስለዚያች ሚስትህ ስለአደረግሃት ጠባየ ንጽሕት ለስላሳ ልጅ ለማስብ ሞክርና ፡ አንድ መልካም ቃል ብለህ ተሰናበተኝ "

“ ሳቤላ.. መጀመሪያ ጥለሽኝ የሔድሽ ጊዜ ልቤ በኀዘን ሊፈርስልሽ ምንም
አልቀረም ነበር " ሆኖም' " እኔ አሁን አንቺን በሙሉ ልቤ ይቅር እንዳልኩሽ ሁሎ እኔንም እንደዚሁ ያድርግልኝ

“ በል ዳግመኛ እንገናኛለን አብረንም እስከ ዘለዓለም እንኖራለን ዊልያም
አናቴ ከወንዙ ዳር ትፈልገኛለች ብሎ ነበር » ነገር ግን ዊልያም ነው አሁን እኔን በመፈለግ ላይ ያለው"

ሚስተር ካርላይል ሁለት እጆቹን ይዛው ስለ ነበር አንዱን አስለቅቆ ከግንባሯ ላይ ችፍፍ ያለውን የሞት ጤዛ በገዛ መሐረቡ ጠረገላት …

“ በል አርኪባልድ ቅጣቴን ከዚሀ ጨርሻለሁ ሁላችንም ከዚያ እንገናኛለን እኛም ልጆቻችንም ለዘለዓለም እንኖራለን " ይኸውም ከዚያ ሔዶ መዳር መጋባት የለምና ኃጢአት አይሆንም " አንተ ግን ለዚያች በከንቱ ለቀረችው ላንተይቱ ሳቤላ ከልብህ ውስጥ ትንሽ የትዝታ ማዕዘን ከልለህ ያዝላት። ”

'' እሺ እሺ !” አለ በሹክሹክታ "

“ መሔድህ ነው ? ” አለች እየቃተተች"

“ በጣም እየደከመሽ ነው ' ዕርዳታ መፈለግ አለብኝ „ ”

"በል እንግዲያው ደኅና ሁን እስከ መረሻው ደኀና ሁን” አለችው በረጅሙ ተንፍሳ ዕንባዋ ሳያቋርጥ እንደ ዝናብ መውረዱን ቀጠለ “ነገሩ የሞት አንጂ የዝለት አይመስለኝም " አዬ ጉድ መለያየት ጭንቅ ነው " ደኅና ሁን...ደኅና ሁን የዱሮው ውድ ባሌ "

ደግፏት የነበረውን ትራስ ለቃ ቀና አለች » የመንፈሷ መሸበር ብርታትን ሰጣት - ከክንዱ ተጠመጠመችበትና ናፍቆት የጎዳውን ፊቱን ቀና አድርጋ አየችው ሚስተር ካርላይል ቀስ አድርጎ መልሶ አስተኛትና ከንፈሮቹን በከንፈሮቿ ላይ ማረፋቸውን ቻለ።

“ እስከ ዘለዓለም ” አለ በሹክሹክታ ።

ምልስ ብሎ ከክፍሉ እስኪወጣ ድረስ በዐይኗ ስትከተለው ቆየችና ፊቷ
ወደ ግድግዳው አዞረች “ በቃ አለቀ ” አለች "
ሚስተር ካርይል እንደ ወጣ ከደረጃው ላይ ቁሞ ከራሱ ጋር ትንሽ መከሪና ጆይስን ወደ በሽተኛይቱ እንድትሔድላት ጠቀሳት " እኀቱ ከበራፍ ቁማ ነበር

“ ኮርኒሊያ ” ብሎ ጠራትና ወደ ምግብ ቤት ተከትላው ገባች "

“ ዛሬ ከዚህ ታድሪያለሽ ? ከሷ ጋር ''

" ደግሞ ለዚህ ትጠራጠር ኖረሃል ? አሁን ወዴት ልትሔድ ነው ?” አለችው

“ሎርድ ማውንት እስቨርንን ለመጥራት ወደ ቴሌግራፍ ቤት መሔዴነው…”

“ ምነው ሌላ ሰው አትልክም? ራትህ እንደ ቀረበ ሳትቀምስለት እንዳለ
ይጠብቅሃል።

ወደ ጠረጴዛው ያለ ልቡ ዞር ብሎ አየና፡ ለኮርኒሊያም ያልተሰማ መልስ አልጎምጉሞ ወቶ ሔደ ።

ሊመለስ እኅቱ ከመተላለፊያው ጠብቃ ካጠገቧ ከነበረው አንድ ክፍል ይዛው ገባች » በሩን ዘጋች ሳቤላ ከዐሥር ደቂቃ በፊት ሕይወቷ ማለፉን ነገረችው

“ አንተ ከወጣህ አንድም ቃል አልተናገረችም አርኪባልድ " መጨረሻ
ላይ ትንፋቯ ሲዘጋ ትንሽ ተወራጨች እንጂ በሰላም ሔደች "

ሎርድ ማውንት እስቨርን በአስቸኳይ የተጠራበት ምክንያት ለምን እንደሆነ
እያሰበ ምንም ጊዜ ሳያባክን ገሥግሶ በበነጋታው ጧት ደረስ ሚስተር ካርላይል
ዝግ ሠረገላውን ይዞ ከጣቢያ ጠብቆ ተቀበለው ወደ ኢስትሊን ሲመጡ በመንገድ አረዳው ኧርሉ ነገሩ ሊገባው አልቻለም " ሲገባው ደግሞ ማመን አቃተው።

" ከቤትህ ለመሞት ነው የመጣችው ? አንተስ አስገባሃት ? እኔ ነገሩ ምንም አልገባኝም ” አለው

ሚስተር ካርላይል ሁኔታውን ጨምሮ አብራራለትና በመጨረሻ ገባው „

“ ምን የሚሉት ዕብደት ነው? እዚህ መምጣት ? ማዳም ቬን እንዴት
ሳትታወቅ ቀረች ? ”

"አልታወቀችም አለ ሚስተር ካርላይል " ማዳም ቬን ከመጀመሪያ ሚስቴ ጋር በመመሳሰሏ ገርሞኝ ነበር" ግን እሷ ትሆናለች ብዬ አልጠረጠርኩም።
መመሳሰሉም ቢሆን መመሳሰል አይባልም " ፊቷ ሁሉ ተለውጦ ነበር " ያልትለወጡት ዐይኖቿንም ያለ መነጽር ዐይቻቸው አላውቅም "

ሎርድ ማውንት እስቨርን ያተኮሰውን ፊቱን ጠረገ " መርዶውን ከምንም
አልቆጠረውም " መሞቷን ቢያውቅም በአድራጐቷ ተናደዶ ሚስዝ ካርላይል ባለመኖሯም ደስ አለው "

“ አሁን ሊያዩዋት ይፈልጋሉ ? " አለው ሚስተር ካርላይል ገና ወደ ቤት ሲገቡ "

“ አዎን"

ሚስተር ካርላይል በሩን ከፈተውና ገቡ " ጆይስና ኮርኒሊያ አስፈላጊውን
ሁሉ አድርገውላታል " ሎርድ ማውንት እስሸርን ጠጋ ብሎ መልኳን አነጻጸረና
ባየው መመሳሰል ተደነቀ

ምን ገደላት ? ” አለው "

እሷ ጎዘን ነው ትል ነበር

“በዚህ ከሆነ ገና ዱሮ ባለመሞቷም ያስደንቃል" ጎዘኗማ ምን ልክ አለው! ”
አዬ ያልታደልሺው ሳቤላ” አለ እጂዋን እየነካ » “ የገዛ ደስታሽን አበላሸሽው ካርላይል ይህ የጋብቻ ቀለበትሀ መሰለኝ "

ሚስተር ካርላይል ወደ ቀለበቱ አየት አድርጎ “ ሳይሆን አይቀርም ' አለ"

“ ምንም ሳታወልቀው መኖሯም የሚገርም ነው ” አለና ይዞት የነበረውን
የ በረዶ እጅዋን ለቀቀው “እኔ ይሀን ታሪክ ማን ይቸግረኛል "

ይኸንንእየተናገረ ከክፍሉ ወጣ " ሚስተር ካርላይል ግንባሯን በጣቶቹ እየነካ ፊቷን ለአንድ ሁለት ደቂቃ ያህል ትክ ብሎ ሲመለከታት ቆናና የገለጠውን ፊት መልሶ ሸፍኖት ወጣ "

ሎርድ ማውንት እስቨርንና ሚስተር ካርላይል ወደ ቁርስ ቤት ወረዱ ሚስ
ካርላይልን ተቀምጣ ስትጠብቃቸው አገኙዋት " " ዐይኖቻቸሁ የት ሔዶው ነው ኧረ ያላወቃችሁዋት ? ” አለ ኧርሉ "

“ የእርስዎ ዐይኖች ከሔዱበት ” አለችው ኮርኒሊያ “ እርስዎ ማዳም ቬንን እኛ እንዳየናት አድርገው አይተዋታል

እኔ ከሁለትና ከሦስት ጊዜ የበለጠ አላየኋትም " ለዚያው ቆቧንና ዐይነ ርግቧን አውጥታ አይቻት አላውቅም ። ካርላይል ግን ለምን ሳያውቃት እንደ ቀረ
ይገርማል ።
👍19
“ መናገር ካስፈለገ ሐቅ ምን ጊዜም ሐቅ ነው " ከዚህ በሔደች ጊዜ ገና ወጣት ፊተ ብሩህ ንቁ ጸጉረ ጥቁርና ረጅም ቁመናዋ እንደ ቀስት ቀጥ ያለ
በጠቅላላው በጣም የምታምር ልጅ ነበረች አሁን ደግሞ ማዳም ቬን ተብላ ስትመጣ ፊቷ ገርጥቶ ጐብጣ ' አንክሳ ከእመቤት ሳቤላ አጥራ ልዩ ልዩ የማሳሳቻ ልብስ ደራርባ ተሸፋፍና ፡ ጸጉሯ ሸብቶና ከቆቡ ውስጥ ተጠቅልሎ አፏ ተለዋውጦ ፥ የፊት ጥርሶቿ ወልቀው ንግግሯ ተኮላትፎ ከፍተኛ ለውጥ ደርሶባት ነበር" ይህን ሁሉ አጠቃልለን ስንመለከተው” አለች ሚስ ካርላይል ስታጠቃልል፡
“ያቺ ከዚህ የጠፋችውን ሳቤላ ጨርሳ አትመስልም ነበር። አሁን እርስዎ ..ጌታ
በጣም የሚወዱት ጓደኛዎ በአደጋ ተሰባብሮ እንደሷ ሆኖ ተለዋውጦ ቢያዩት
በቀላሉ ሊያውቁት ይችላሉ ? ” አለችው "

አባባሏ ሎርድ ማውንት እስቨርንን አንድ ነገር አስገነዘበው አንድ በቅርብ
የሚያውቀው ሰውዬ አሠቃቂ አደጋ ደረሰበትና የድሮ መልኩ ጨርሶ ተለዋወጠ" አንደ ሳቤላ እንኳን ተጨማሪ ማሳሳቻ አላደረገም " ነገር ግን የገዛ ቤተሰቦቹም ሊያውቁት አልቻሉም " ይህ በርግጥ የደረሰ እውነተኛ ታሪክ ነው "
“የመልኳን መመሳሰል እንኳን እንደ ተባለው ለመጠርጠር ያስቸግር ይሆናል።ነገር ግን ያንን ሁሉ መሸፋፈኛ ስትደራርብ መንቃት ነበረብን” አለ ሚስተር ካርላይል

እሱንማ ገና እዚህ ቤት እንደገባች ” አለች ሚስ ኮርኒሊያ የገለጠች እንደሆን ራሷን አይኗን ፊቷን ሳይቀር እንደሚያማት ስትናገር ጊዜ ሁሉም አመናት በዚህ በኩል እንዳትጠረጠር በሩን ዘጋችው ከዚህም ሌላ እንድ
ሎርድ ማውንት እስቨርን የዱሲ ቤተሰቦችም
ጀርመን ሳለች አብረዋት ነበሩ » ግን እሷ ትሆናለች ብለው አልጠረጠሩም ሌላው መረሳት የሌለበት ነገር አለ በጣም ከፍተኛ ያሆነ መመሳሰል ብናይባትም አንሥተን አልተነጋገርንበትም " የእመቤት ሳቤላን ስም በሹክክታ እንኳን አንሥተነው አናውቅም " "

እውነት ነው ! ” አለ ሎርድ ማውንት እስቨርን " " የምትይው ሁሉ እውነት ነው።

ሚስተር ካርላይል ዓርብ የሚከተለውን ደብዳቤ ወደ ሚሲዝ ካርላይል ላከ

· የኔፍቅር እሑድ ከሰዓት በኋላ አንቺ ዘንድ እደርሳለሁ ብየሽ የነበረው የማይሳካልኝ ስለሆነ በእሑድ ሌሊት ባቡር እነሰለሁ » ስለዚህ እንዳትጠብቂኝ ሎርድ ማውንት እስቨርን ለጥቂት ቀኖች ወደዚህ መጥተው አብረውኝ አሉ”
መልካም ምኞታቸውን ያቀርቡልሻል "

“ በይ ባርባራ .. አሁን ለአንድ አስደንጋጭ ወሬ ተዘጋጂ' ማዳም ቬን ዐረፈች እኛ እንደሔድን ባንድ ጊዜ አጣድፎ ለሞት አደረሳት ብለው ነገሩኝ። ረቡዕ
ሌሊት ሞተች። ባለመኖርሽ ደስ ብሎኛል . . ምን ጊዜም ያንቺው ነኝ የኔ ፍቅር

አርኪባልድ ካርላይል”

የዌስትሊን ሕዝብ ምስጢሩ አልገባውም" የሎርድ ማውንት እስቨርንና የሚስተር ካርላይል ኀዘንተኞች ሆነው አስከሬኑን አጅበው ሊቀብሩ መምጣት የመጀመሪያው ከቤቱ ሬሳ ስለ ወጣ ሁለተኛው ደግሞ በእንግድነት እንደ ወጣ ለሚስተር ካርላይል ከበሬታ ሲል ያደረገው መስሎ ታየው ።

አስከሬኑ በሠረገላዎች ታጅቦ ክብር ባለው ሁኔታ መጥቶ ሲቀበርም አስተማሪቱ ለቀብሯ ማስፈጸሚያ በቂ ግንዘብ አጠራቅማ ስለተወች ነው ተባለ እሑድ ጧት ካባቷ ጐን ተቀበረች" ለዚሁም የዌስት ሊን ስው ምክንያት አላጣም አጋጣሚ ሆኖ ከኧርል ዊልያም ሼን መቃብር አጠግብ ባዶ ቦታ ስለ ተገኘ ነው ተባለ "

ከዚያም አስቀብረው ሲያበቁ ኧርሎና ሚስተር ካርላይል በጎዘኑ ሠረገላ ተሳፍረው ወደ ኢስት ሊን ተመለሱ "

ከመቃብሯ ላይ ሁለት ጫማ በአንድ ጫማ ተኩል የሆነ ነጭ ዕብነ በረድ
እንዲቆምላትና ሳ. ሜ . ቬ ( ሳቤላ ሜሪ ቬን ) የሚሉ ቀለሞችና ዘመንም እንዲ
ቀረፅበት ወደ ቤት በመመለስ ላይ እያሉ ከመንገድ ተስማሙ "

የቀብሩ ሥነ ሥርዓት ተፈጽሞ በመመለስ ላይ እንዳሉ የአንድ ሌላ ቤተክርስቲያን ደወሎች ማስተጋባት ጀመሩ " ደወሎቹ አንድ ሥርዓተ ተክሊል ሲፈጸም አብሣሪዎች ነበሩ" አፊ ሆሊጆን በሁለት ካህናትና በስድስት የሴት ሚዜዎች
ረዳትነት • ሚስዝ ጂፊን ተብላ ተሠየመች » በመጨረሻ ሚስተር ጂፊን የልቡ ደረሰ "

ኧርሉ ከሰዓት በኋላ ወደ አጀሩ ተመለሰ " ጥቂት ቆይታ ባርባራ ደረሰች
ዊልሰን እመቤቷ ከቤት እስክትገባ ለመቆየት እንኳን ቸኮለች » እንዲያውም ሕፃኒቱን ከሠረገላ ውስጥ ትታት ልትሔድ ምንም አልቀራትም ነበር ያቺ ፈረንሳዊት አስተማሪ ምን እንደ ገደላት ወሬ ለማግኘት ነበር የዊሰን ጥድፊያ ሚስተር ካርላይል ደግሞ ካስበው ጊዜ ቀድመው መምጣታቸው ድንገተኛ ነገር ሆነበት "

“ አንተ ወሬውን ከነገርከኝ በኋላ እንዴት ብዬ እስከ ሰኞ ልሰንብት አርኪባልድ ? ለመሆኑ በምን ሞተች ? መቸም ድንገተኛ ነገር መሆን አለበት 'አለችው "

“ ይመስለኛል” አላት ያለልቡ ሐሳቡ በሌላ ተይዞበት ስለ ነበር እንዴት
እንደሚገልጽላት ማንስ ቢገልጽላት አንደሚሻል ያወጣ ያወርድ ጀመር በመጨረሻ ግን ከሌላ ሰው ከምትሰማ ጊዜ ሳይወስድ ወዲያውኑ እሱ ቢነግራት መሻሉን መረጠ "

“ ግን ምን ሆንክ .. አርኪባልድ ! አመመህ እንዴ ? " አለችው የፊቱን
መለወጥ አይታ "
" አንድ የምነግርሽ ነገር አለኝ . . ባርባራ ” አላት አብረው እንደቆሙ እጂዋን ወደሱ ሳብ አድርጎ " ከሷ መልበሻ ክፍል ነበሩ : “ ረቡዕ ማታ ከቤት ገብቼ
ራት ልበላ ስል ማዳም ቬን በሞት አፋፍ መሆኗን ጆይስ ነገረችኝ "

እኔም ሔጄ መጠየቅ ይገባኛል ብዬ አሰብኩ „

እንዴታ” አለች ባርባራ“ ልክ ነህ !እንዴት ታርጋለህ?”
“ ተነሳሁና ብሔድ እውነትም ደክማ አገኘኋት ግን የጠበቀኝ ሌላ ነገር ነበር ባርባራ ሴትዮይቱ ማዳም ቬን አልነበረችም "

“ማዳም ቬን አልነበረችም ? " አለች ባርባራ ድንግጥ ብላ።

" የድሮዋ ሚስቴ ነበረች ሳቤላ ቬን ”

የባርባራ ፊት መጀመሪያ ደም መሰለ። ቀጠለና ነጭ ዕብነ በረድ መስሎነጣ "
ይዞት የነበረው እጂዋን አስለቀቀችና ስበሰበች ሆኖም የታየባትን መለዋወጥና ያደረገችውን መቁነጥነጥ ልብ ብሎ ያስተዋለ አልመሰለም " ክርኑን ከአሳት መሞቂያው ምድጃ ላይ አስደግፎ ባጭሩ ማብራራቱን ቀጠለ።

“ ከልጆቹ ተለይታ መኖር ስላልቻለች ፈረንሳይ ሳለች የደረሰባት የባቡር አደጋ በጣም ስለ ለወጣትና በተጨማሪም ከጸጉሯ ሽበት ሌላ መነጽሯንና ያለባበሷን
ሁኔታ ቀያይራ እንደማትታወቅ በማመን ማዳም ቬን ተብላ መጣች አለመታወቋን ሳስበው ይገርመኛል እንደዚህ ያለ ታሪክ ከሌላ ብሰማው በጭራሽ አላምንም ነበር «

" አንተስ ጠርጥረህ ነበር ? ” አለችው ብዙ ከተጨነቀች በኋላ "

ባርባራ!ብጠረጥር ኖሮ መቸ ዝም እል ነበር?እሷ ግን ስለ ዐለፈው ድርጊቷና እንደገናም ተመልሳ ስለ መምጣቷ ይቅርታ ለመነችኝ እኔም ከልቤ አልኳት። ለማውንት እስቨርን ቴሌግራፍ ለማድረግ ዌስት ሊን ሔጄ ስመለስ ሙታ
ቆየችኝ " ኀዘን ነው የገደለኝ አለችኝ ግን ባርባራ...በዚህ አንደነቅም "

ሚስተር ካርላይል ዝም አለ። ሚስቱ ፊቷን እንዳያይባት ስትዞር አያት እሱ ግን አሷ ሳታስተውለው ቀስ ብሎ አስተውሉ ተመለከታት አውነትም የመታወክ ምልክት አየባት "
አጆቹን ትከሻዋ ላይ ጣል አድርጎ ቀና ብላ እንድታየው አደረገ "

“ የኔ ፍቅር . . ምንድነው ? "

አርኪባልድ !” አለች ዕንባዋን እያወረደች “እና'ይህ ነር ፍቅርህን
ወስዶብኝ ይሆን ?

ሁለቱን እጆን በአንድ እጁ ይዞ ሌላዉን እጁን ሽንጧ ላይ ጠምጥሞ ከፊቱ
ይዟት ቆመ » አንድም ነገር ሳይናገር ዝም ብሎ ዐይን ዐይኗን ሲያያት ቆየና በመጨረሻ“ እኔስ ሚስቴ በሙሉ ልቧ የምታምነኝ ይመስለኝ ነበር ” አላት።
👍12
አዎን አምንሃለሁ እንደማምንህ አንተም ታቃለህ . . አርኪባልድ”
ይቅርታ አድርግልኝ ” ብላ ከደረቱ ተደግፋ ቀስ ብላ አለቃቀስችና ቀና ብላ አየችው።

“ የኔ ሚስት " የኔ ፍቅር • አሁንም ሁልጊዜም "

“ ልቤን በዚህ በማሻከሬ አዝናለሁ የማይረባ አስተሳሰብ ነው. .
አርኪባልድ አሁን ግን ዐለፈ

" እንደዚህ ያለ ስሜት ዳግመኛ እንዳይመጣ
... ባርባራ “ ስሟም ሁለተኛ በመኻላችን መነሣት ኢያስፈልገውም እስከ ዛሬም እንዳይወሳ የተከለከለ ነበር " እንግዲህም ቢሆን አይነሣም "

" አንተ ያልከው ሁሉ ይሁን " ዋናው ምኞቴ አንተን በማስደስት ለፍቅርህና
ለአክብሮትህ ብቁ ሁኘ ለመገኘት ነው አርኪባልድ . . .በልጆችህ እንኳን ዐይነት ስሜት አድሮብኝ ነበር ገባህ አስተሳሰቤ ምን ያህል የተሳሳተ እንደ ነበር አውቄዋለሁ » ለማረም ከልቤ ጥሬአለሁ ። በሚገባ ሞክሬአለሁ " አሁን
ጨርሶ ሊለወጥ ምንም አልቀረውም " ልክ እንደ ልጆቼ ልወዳቸው ' ልንከባከባቸው ' እንዲረዳኝ ሁልጊዜ እጸልያለሁ " "

እንድናገኘው ከልባችን የምንመኘውና የምንታገልለት መልካም ነገር ሁሉ ጊዜውን ጠብቆ ይደርሳል” አለ ሚስተር ካርላይል ” ሰማሽ ባርባራ . .ምንም ቢሆን መርሳት የማይገባሽ አንድ ነገር አለ " በመጨረሻ የተረጋገጠ ሰላም ለማግኘት ሳይስገበገቡ መልካም ሥራ ለመሥራት ያለ ማቋረጥ መታገል ማስፈለጉን አትርሺ።

💫ተ..ፈ..ፀ..መ💫

አሰተያየታችሁን እጠብቃለሁ።
👏23👍20🔥2😁2😢1
#ጠላፊዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_አንድ


#በኬንፎሌት


#ትርጉም_ወንዳየሁ_ንጉሴ


ከመሐል አትላንቲክ ወደ ቦትውድ (ካናዳ)


ዳያና ላቭሴይ ባሏ ፎየንስ ላይ አይሮፕላኑን መሳፈሩ በእጅጉ አስቆጥቷታል፡ በመጀመሪያ ዱካዋን እግር በእግር ተከታትሎ በመምጣት መሳቂያ መሳለቂያ ስላደረጋት አፍረት ውስጥ ከቷታል፡ ባሏ እቤታችን እንሂድ ቢላትም ሀሳቧን መለወጥ አትፈልግም ከማርክ ጋር ወደ አሜሪካ ለመሄድ የወሰነች ብትሆንም መርቪን ግን የመጨረሻ ውሳኔዋ ነው ብሎ መቀበል አልቻለም፡፡ ይሄ ደግሞ በቁርጠኝነቷ ላይ ጥላ አጥልቶበታል፡፡እሱም ውሳኔዋን እንደገና እንድታጤነው ደጋግሞ ስላሳሰባት ውሳኔዋን
በተደጋጋሚ ገልጻለታለች፡፡ በመጨረሻ ግን የአየር ጉዞዋ የሰጣትን ደስታ
ነጥቋታል፡፡

በህይወት አንዴ ብቻ የሚገጥም ከፍቅረኛ ጋር የሚደረግ ጉዞ፡፡

ከሳውዝ ሃምፕተን ሲነሱ የነበረው የነጻነትና የደስታ ስሜት አሁን የለም: መርቪን ከመጣ ወዲህ ምቹው አይሮፕላን፣ ከተለያዩ ተሳፋሪዎች ጋር መቀላቀሉና እጅ የሚያስቆረጥመው ምግብ ደስታ እየሰጣት አይደለም፡መርቪን ባጋጣሚ ሲያልፍ ያየኛል ብላ ስለፈራች ከማርክ ጋር መላፋት፣መተሻሸትና መሳሳም አልቻለችም፡፡ መርቪን የት እንደተቀመጠ አታውቅም፡፡ካሁን አሁን ይመጣ ይሆን እያለች ትበረግጋለች። ማርክ ካሊፎርኒያ ስለሚጠብቃቸው ኑሮ በተስፋ ሲያወራና ሲቀልድ ቆይቶ ጣውንቱ ከሰማይ
እንደወደቀ ሁሉ ድንገት አይሮፕላኑ ውስጥ ጥልቅ ካለ ወዲህ ግን ቀልቡ
ግፍፍ ብሏል፡ አሁን የተነፈሰ ፊኛ መስሏል፡፡ ዳያና አጠገብ ቁጭ ብሎ
አንድም ቃል ሳያነብ የመጽሔቱን ገጾች ያገላብጣል፡፡ ስሜቱ መጎዳቱን ዳያና አይታለች፡፡ አንድ ወቅት ላይ ይዟት እንዲጠፋ ከቆረጠች በኋላ ሃሳቧን ለውጣ ነበር፡፡ አሁን ባሏ ስለመጣ ከእሱ ጋር እሄዳለሁ ብላ ሃሳቧን
የማትለውጥ መሆኗን እርግጠኛ መሆን አልቻለም፡፡
የአየሩ ሁኔታ እየከፋ መምጣቱ ደግሞ ሌላ ራስ ምታት ሆኖባታል

አይሮፕላኑ ልክ ኮረኮንች ላይ እንደሚሄድ መኪና ይንገጫገጫል፡፡ በየሰዉ
ፊት ላይ ፍርሃት ይነበባል፡፡ ተሳፋሪው ሁሉ የሚያወራው ይህንኑ ነው፡

ዳያና ባሏ የት እንደተቀመጠ ማወቅ ፈለገች፡፡ እግረ መንገዴን ባየው እየተዘዋወረች ብትቃኝም መርቪንን የበላው ጅብ አልጮህ አለ፡፡ በመጨረሻ የቀራት ክፍል የሙሽሮቹ ክፍል ብቻ ነው፡፡

የሴቶች መዋቢያ ክፍል ገባች። ክፍሉ ውስጥ ሁለት ወምበሮች ያሉ ሲሆን አንዱ ወንበር ላይ አንዲት ሴት ተቀምጣ ትኳኳላለች፡፡ ዳያና በሩን ልትዘጋ ስትል አይሮፕላኑ ዘጭ ሲል ሚዛኗን ስታ ልትወድቅ ምንም አልቀራትም፡፡ እንደምንም ተንገዳግዳ ሄዳ ባዶው ወምበር ላይ ዘፍ አለች።

‹‹ተረፍሽ?›› ስትል ጠየቀች ሴትየዋ፡፡

‹‹አዎ፣ አመሰግናለሁ›› አለች ዳያና ‹‹አይሮፕላን እንዲህ ሲሆን አልወድም››

‹‹እኔም አልወድም፡ ከዚህ በኋላ ጉዟችን የከፋ እንደሚሆን አንድ ሰው
ነግሮኛል፡ ዶፍ ዝናብ ይጠብቀናል›› አለች፡፡

የአይሮፕላኑ ውዝዋዜ ጋብ ሲል ዳያና ጸጉሯን ማበጠር ጀመረች።

‹‹ሚስስ ላቭሴይ ነሽ አይደለም?›› ስትል ጠየቀች

‹‹አዎ ዳያና በይኝ››
‹‹እኔ ናንሲ ሌኔሃን እባላለሁ:: ፎየንስ ላይ ነው የተሳፈርኩት”
ከሊቨርፑል ካንቺ. . . ከሚስተር ላቭሴይ ጋር ነው የመጣሁት››
‹‹ኦ!›› ዳያና ይህን ስትሰማ ፊቷ በእፍረት ቲማቲም መሰለ፡፡ ‹‹ጓደኛ እንዳገኘ አላወቅሁም ነበር›› አለች በምጸት፡፡

‹‹ይህን አይሮፕላን ለመሳፈር ወደ ሳውዝ ሃምፕተን ለመሄድ ፈልጌ
ሊቨርፑል ላይ መውጫ አጥቼ ስጨነቅ ባለቤትሽን አየር ማረፊያ ላይ
አገኘሁትና እንዲወስደኝ ለመንኩት››

‹‹እንኳን ቀናሽ›› አለች ዳያና፡፡ ‹‹የእሱ መምጣት እኔን እፍረት ውስጥ
ከቶኛል፡፡››

‹‹ማፈር የለብሽም፡፡ ሁለት ወንዶችን በፍቅር ማጥመድሽ ደስ የሚል
ነገር ነው፡፡ እኔ አንድ እንኳን ፍቅረኛ የለኝም፡፡››

ዳያና ናንሲን በመስታወት አየቻት፡፡ ሴትየዋ ቆንጆ ባትባልም የደስ ደስ አላት፡ ጸጉረ ጥቁር ስትሆን ከሰውነቷ ጋር የሚሄድ ልብስ ለብሳለች።
ስትታይ በራሷ የምትተማመን ትመስላለች፡ መርቪን ሊፍት ቢሰጥሽ
አያስገርምም፡ እሱ እንዳንቺ ያለች ሴት ነው የሚፈልገው አለች ዳያና በሆዷ፡፡
‹‹እንዴት ነው ያሳየሽ ባህሪ ጥሩ ነበር?›› ስትል ጠየቀቻት ናንሲን፡፡
‹‹ብዙም ጥሩ አልነበረም›› አለች በቅሬታ ፈገግታ፡
‹‹አዝናለሁ፡ ይህ ባህሪው ነው የሚያስጠቃው›› አለችና ሊፒስቲኳን ጨረገች

‹‹ሆኖም በችግሬ ጊዜ ስለደረሰልኝ ባለውለታዬ ነው›› አለችና ናንሲ
ተናፈጠች፡ ናንሲ ቀለበት ማሰሯን ዳያና አጤነች፡፡ ‹‹ትህትና ባይኖረውም
ጥሩ ሰው ይመስላል፡፡ ራትም ጋብዞኛል፡ ጨዋታ ያውቃል፡፡ የሴት ልጅን
ልብ የሚሰርቅ ቁመናና መልክ አለው›› አለች፡፡

ጥሩ ሰው ቢሆንም….... አለች ዳያና ‹‹ሰው ይንቃል፡፡ ትዕግስትም የሚባል ነገር ፈጽሞ አልፈጠረበትም፡፡››
ናንሲ ጥቁር ጥቅጥቅ ያለውን ጸጉሯን ታበጥራለች ሽበቷን ለመደበቅ ቀለም ትቀባ ይሆን?› አለች ዳያና በሆዷ።

አንቺን መልሶ በእጁ ለማስገባት ሲል የሚደርስበትን መከራ ለመቀበል ቆርጧል››

‹‹አይደለም ክብሩ ስለተነካ ነው›› አለች ዳያና ‹‹ሌላ ወንድ ስለወሰደኝ ነው ያንጨረጨረው፡፡ ተጋፊ ስለመጣበት ነው ተከትሎኝ የመጣው፡ ጥዬው
እህቴ ቤት ሄጄ ቢሆን ኖሮ እኔን ለመፈለግ እግሩን አያነሳም ነበር››

ናንሲ ሳቀችና ‹‹እንዳነጋገርሽ አንቺን ለማስመለስ ተስፋ ያለው
አይመስልም›› አለች፡፡

‹‹ምንም ተስፋ የለውም›› አለች ዳያና፡፡ ዳያና ድንገት ስሜቷ ስለተረበሸ ከናንሲ ጋር ከዚህ በላይ ማውራት አልፈለገችም፡፡ ሜክአፕና ማበጠሪያዋን ቦርሳዋ ውስጥ ከታታ ለናንሲ ያላት ጥላቻ እንዳይታወቅባት የውሽት ፈገግታ አሳየቻትና ‹‹ወደ ቦታዬ ልሂድ›› ብላ ተነሳች፡፡

‹‹መልካም ዕድል!››

ከሴቶች መዋቢያ ክፍል ስትወጣ ሉሉ ቤልንና ልዕልት ላቪኒያ የመዋቢያ ዕቃዎቻቸውን ያጨቁበትን ቦርሳዎቻቸውን አንጠልጥለው ገቡ፡፡
ወደ ቦታዋ ስትመለስ አስተናጋጁ ዴቭ መቀመጫቸውን ወደ ታጣፊ አልጋ ሲቀይር አየች፡፡ ዳያና አንድ ተራ ሶፋ እንዴት ወደ ተደራራቢ አልጋ ሊቀየር
እንደሚችል ገርሟታል። ዴቭ ከወምበሩ ስር አንሶላና ብርድ ልብስ አወጣና
አነጠፈ፡፡

ተደራራቢ አልጋዎቹ ምቹ ቢሆኑም ከሰው እይታ ውጭ ባለመሆናቸው
ዴቭ መጋረጃ አመጣና ጋረዳቸው፡ ከዚያም በአልጋዎቹ ጎን ትንሽ ታጣፊ
መሰላል አያያዘባቸው፡፡ ዴቭ ይህን የሰራው በሚያስደንቅ ቅልጥፍና ነው፡፡

ዴቭ ወደ ዳያናና ማርክ ዞሮ ፈገግታ ሳይለየው መኝታችሁ እንዲዘጋጅላችሁ ከፈለጋችሁ ንገሩኝና አዘጋጅላችኋለሁ›› አላቸው፡፡

‹‹ተደራራቢ አልጋዎቹ ውስጥ ሲተኙ ሰዎች አይታፈኑም?››
‹‹እያንዳንዱ አልጋ የራሱ አየር ማስገቢያ አለው›› ሲል መለሰ ‹ቀና ብለሽ ብታዪ ያንቺ አልጋ አየር ማስገቢያ አለው፡›› ዳያና ቀና ስትል መስቀያና መዝጊያና መክፈቻ ያለው በብረት ፍርግርግ የተሰራ አየር ማስገቢያ አየች:: "ከዚህ በተጨማሪ›› ሲል ቀጠለ ዴቭ ‹‹የራስሽ መስኮት፣ መብራት፣ የልብስ መስቀያና የመፀሐፍ ማስቀመጫ አለሽ።ከዚህ በተረፈ የምትፈልጊው ነገር
እንዲመጣልሽ ስትፈልጊረመ ይህን ቁልፍ ብትጫኚው ከተፍ እልልሻለሁ›› አላት።
👍10
ዴቭ ፍራንክ ጎርደንና ራስ በራው ኦሊስ ፊልድ ወደ መታጠቢያ ቤት ሲሄዱ አየና የእነሱንም መኝታ ማበጃት ጀመረ።
።።።።።።።።።።።።
ልዕልት ላቪኒያ መሬት የሚጠርግ ፒጃማ ለብሰውና ከእሱ ጋር
የሚሄድ ሻሽ ራሳቸው ላይ ጠምጥመው ከመታጠቢያ ቤት ተመለሱ።
በፒጃማ ሰው ፊት መታየታቸው ምቾት የነሳቸው በመሆኑ ፊታቸውን
ክረምት አስመስለውና ተጀንነው ተኮፍሰዋል። ድፍን የአይሮፕላኑን ሰው በፍርሃት ነው የሚያዩት:
‹‹እዚህ እፍግፍግ ያለ ቦታ ተቀምጬ መሞቴ
ነው›› ሲሉ አማረሩ። ነገር ግን ነገሬ ያላቸው ሰው የለም። ነጠላ ጫማቸውን
አወለቁና ታችኛው አልጋ ላይ ወጡ አጠገባቸው ያሉትን ሰዎች ደህና እደሩ
እንኳን ሳይሉ መጋረጃቸውን ዘጉና ብርድ ልብስ ውስጥ ገብተው ጥቅልል አሉ።

ብዙም ሳይቆዩ ሉሉ ቤል ገላዋን ወለል አድርጎ የሚያሳይ የመኝታ
ልብስ ለብሳ እየተውረገረገች ብቅ አለች: ከፎየንስ ከተሳፈሩ ወዲህ ከዳያናና ከማርክ ጋር የነበራትን መቀራረብ በድርበቡ አድርጋ ከቆየች በኋላ ማርክና ዳያና አጠገብ ቁጭ ብላ ወግ መጠረቅ ጀመረች።

‹‹አጠገባችን ስላሉት ተሳፋሪዎች አንድ ወሬ አግኝቻለሁ›› አለች ወደ
ፊልድና ጎርደን ቦታ እያመለከተች።

ማርክ በፍርሃት ወደ ዳያና አማተረና ‹‹ምን ሰማሽ ሉሉ?›› ሲል ጠየቀ፡

‹‹ሚስተር ፊልድ የኤፍ.ቢ.አይ አባል ነው››

ይሄ ታዲያ ምን ያስደንቃል የኤፍቢ.አይ አባል እኮ ፖሊስ ነው አለች ዳያና በሆዷ።

ሉሉ ወሬዋን ቀጠለች ‹‹ሌላው ጉዳይ ደግሞ ፍራንክ ጎርደን እስረኛ
ነው»

ማርክም ቀጠለና ‹‹ማን ነገረሽ?›› ሊል ጠየቃት፡
‹‹መታጠቢያ ቤት ሁሉም የሚያወራው ይህንኑ ነው››
‹‹ታዲያ ሁሉም ስላወራው እውነት ይሆናል?›› አለ ማርክ።
‹‹እንደማታምኑኝ እኮ አውቃለሁ›› አለች ሉሉ ያ ትንሹ ልጅ ካፒቴኑና ፊልድ ሲጨቃጨቁ ሰምቷል፡ ኤፍ.ቢ.አይ የፓን አሜሪካንን አየር መንገድ ሳያሳውቅ አደገኛ ወንጀለኛ አይሮፕላኑ ላይ ማሳፈሩ ካፒቴኑን እብድ
አድርጎታል፡ በኋላ የፊልድን ትጥቅ የአይሮፕላኑ ሰራተኞች አስፈቱት…››

ዳያና ፊልድ የጎርደን አንጋች መስሏት ነበር፡ ‹‹ጎርደን ጥፋቱ ምንድነው?›› ስትል ጠየቀች፡:

‹‹ማፊያ ነው፡፡ አንድ ሰው ገድሎ፣ አንዲት ሴት አስገድዶ ደፍሮ የምሽት ክበብ በእሳት አጋይቷል፡››
ዳያና የሉሉ ቤልን ወሬ አምና መቀበል ተቸገረች፡ ወጣቱን ሰው ራሷ
አናግራው ነበር፡፡ በእርግጥ ንግግሩ ብዙም የታረመ አይደለም፡፡ ይሄ እውነት
ነው: መልከ መልካምና አለባበሱ ያማረ ነው፡፡ አንድ ጊዜ ልትዳራው ሞክራ
ነበር፡ ምናልባት አጭበርባሪ ይሆናል ወይም በህገወጥ ቁማር ጨዋታ ተይዞ ይሆናል፡ ነገር ግን ሰው ገድሏል የተባለው ሊታመን አይችልም› አለች በሀሳቧ ሉሉ ደግሞ ትልቁንም ትንሹንም ታምናለች፡

‹‹ማመን ያስቸግራል›› አለ ማርክ፡፡

‹‹በሉ ፍቅረኞች›› አለች ሉሉ እጇን በንዴት አወናጭፋ ‹‹ልተኛ ነው፡፡ጎርደን ሴቶችን አስገድዶ የሚደፍር ከሆነ ቀስቅሱኝ›› አለችና ላይኛው አልጋ ላይ በመሰላል ወጣች፡ መጋረጃውን ከፈተችና ዳያናን ‹‹የኔ ማር አየርላንድ ውስጥ ለምን እንደተናደድሽብኝ ገብቶኛል፡ አውጥቼ አውርጄ ተገልጾልኛል ማርክ ላይ ስላንዣበብኩኝ ነው፡ ከፍቅረኛሽ ጋር እንዳትጫወቺ በወሬ
ጠምጄው አቆይቼዋለሁ፡ ነገር ቶሎ የማይገባኝ ሰው ነኝ፡ ጥፋቴን አርማለሁ፡ አንቺም ቂም አትያዥብኝ፡ ደህና እደሩ›› አለች።

የሉሉ ቤል ንግግር ይቅርታ እንደመጠየቅ ይቆጠራል፡ ዳያናም ይቅር ላለማለት ምክንያት አላገኘችም፡፡ ‹‹ደህና እደሪ ሉሉ›› አለች ዳያና፡፡

ሉሉም መጋረጃዋን ዘጋች፡፡
‹‹እሷ ብቻ አይደለችም፡ እኔም ጥፋተኛ ነኝ፡፡ እኔንም ይቅር በይኝ፡፡ የኔ ፍቅር›› አላት ማርክ፡፡

ዳያና መልስ የመስጠት ያህል ከንፈሩን መጠጠችው፡
ከዚያማ ምን ይወራል! ቀለል እያላት ሲመጣ መላ ሰውነቷ ዘና አለ፡፡
እየሳመችው ወንበሩን ተደገፈች፡፡ እየሳመችው ጡቷ ደረቱን ሲታከክ
ተሰማት፡ እንደገና ገላ ለገላ መተሻሸት መቻሏ ደስታ ፈጥሮላታል፡ በከንፈሩ
ጫፍ ከንፈሯን ሲዳስስ ስሜት ውስጥ ገብታ አፏን ከፍታ ተቀበለችው፡፡ ጫን
ጫን መተንፈስ ጀመረች፡ በእርግጥ የሚያደርጉት ነገር መረን የለቀቀ
መሆኑ ታውቋታል፡ ዓይኗን ስትከፍት መርቪንን አየችው:
በመጀመሪያ እያለፈ ስለነበር አላስተዋላትም ነበር፡ ድንገት ወዳለችበት
ፊቱን ዞር ሲያደርግ ያየው ነገር ከእርምጃው ገታው፡ እሷም ስታየው ፊቷ
በድንጋጤ አመድ ለበሰ፡፡....

ይቀጥላል
👍17
😘 #ቃል 😘
#ዳንኤላ_ስቴል
ትርጉም፣ ባሴ ሐብቴ

ምዕራፍ ሀያ ስምንት (28)

እንደሚያፈቅራት ብትፈቅድለትና ፍቅራቸውን ለመካፈል ቢችሉ ደስ እንደሚለው ደጋግሞ ገልጾላታል ። ግን እሷ ልቧን ትጠራጠረዋለች ። በይመስለኛል ስሜት ተገፋፍታ ሳይሆንላት ቢቀር ፒተርን ማስቀየም
ይሆናል ። ይህንን ደግሞ ፈፅሞ አትፈልገውም ። ስለዚህ የፒተር ጥያቄ የኣሺታም የእምቢታም መልስ ሳያገኝ በውዝፍ ዶሴ ተይዞ ቀርቷል ። መዋደዳቸው ፤ መተሳሰባቸው ፤ ጓደኝነታቸው ግን አሌ የሚባል ነገር አይደለም ። «በጣም ናፍቀኸኝ ኖሯል ፒተር» አለች ሜሪ ። ይህን ብላ ህክምና በሚደረግላት ጊዜ እምትቀመጥበት ወንበር ላይ ተቀምጣ ሥራውን እንዲቀጥል ዝግጁ ሆነች ። ዓይኗን ገርበብ አደረገች ። ከወንበሩ ላይ ተነስቶ ትንሽ ከተመለከታት በኋላ « ዛሬ ደግሞ ለመታከም ጥድፊያ በጥድፈያ ሆነሻል » አላት በተለመደው ብርጩማው ላይ ፊት ለፊቷ ተቀመጠ፡፡ « ሁለት ዓመት ሙሉ በፋሻ ስትሸፈን ፤ ፋሻ ሲላጥልክ ብታሳልፍና የመጨረሻው ቀን ቢመጣ አንተ ራስህስ ብትሆን ያንለት ለመገላገል መቻኮልህ ይቀር ነበር ? »

«አይቀርም ፤ እንዲሁ ለማለት ያህል አልኩ እንጂ ነገሩስ ይገባኛል ። ... በደንብ ይገባኛል የኔ መቤት» እግንባሯ ላይ ያለውን ፋሻ ካነሳላት በኋላ ፤ «አሁን አይንሽን መግለጥና ፊትሽን በመስታወት ማየት ትችያለሽ ፣ ሜሪ» አለ ። ሜሪ ግን ካለችበት ላይ ንቅንቅ አላለችም ። ብዙ ዓለም አይታ መጥታለች ። ሆኖም የአዲስ እሷን ፊት ሙሉውን አታውቀውም ። አንደኛው ጐን ቢገለጥ ሌላኛው ወይ በፋሻ ተሸፍኖ ወይ ፕላስተር ተለጥፎበት ወይም ተደርቶ ነበር የምታየው። «በያ ብድግ በይና ወደ መስታወቱ ቅረቢ» አለ ፒተር ያን አዲስ ፊት ፤ ያን ናንሲ ማክአሊስተር የነበረችውን የቀድሞ እሷን ሳይሆን ሜሪ አዳምሰን የተባለችውን አዲስ እሷን ለማየት ፍርሃት ተጫናት ። ምን ያለ የማይረባ ፍርሃት ነው አለች በሐሳቧ። ፍርሃቷን እሸንፋ ተነሳች ። ፊቷን በመስታወቱ ውስጥ ስታይ ፊቷ በሳቅ ቧ ብሎ ተከፈተ ። በጉንጯ ላይ ግን እንባዋ ይጐርፍ ነበር ። ይህ የስሜት ግንፈላ ተግ እስኪልላት ድረስ አልተጠጋትም ። አላነገራትም ። ያ ጊዜ የግሏ የሆነ ማንም ሊጋራት የማይገባ ጊዜ እንደሆነ በመገንዘብ ። «ፒተር ፤ እረ የፈጣሪ ያለህ ! እንዴት ቆንጆ ነው አለች ። «አይ አንቺ ቂል ፍጡር» አለ ፒተር በለሆሳስ እየሳቀ «እንዴት ቆንጆ ነው ሳይሆን እንዴት ቆንጆ ነኝ በይ… ያቺ የምታያት ሌላ ሰው ወይ ሌላ ነገር አይደለችም ። አንቺ ነሽ ራስሽ ነሽ›› ዞራ አየችው ። የተናገረው ትክክል እንደሆነ በቃላት መግለጽ አቃታት ። ራሷን በአዎንታ ነቀነቀች ። ልክ ነው ። ሙሉ በሙሉ ተቀይራለች ። ከምታውቀው መልኳ የቀረ ቅንጣት ምልክት የለም ። አሁን ያላንዳች ማወላወል ሜሪ አዳምሰን ነኝ ስትል አመነች

«ፒተር !...» አለች ውለታ በበዛበት ድምጽ ። ሄዳ ተጠመጠመችበት ። ተቃቅፈው ብዙ ጊዜ ቆዩ ። በመጨረሻ ፊቷን ለማየት እስኪችል ድረስ በክንዶቿ ይዞ ራቅ አደረጋት ። ፈቷ በእንባ ርሷል ። በጣቶቹ ጠረገላት ። «ፒተር. . . አየህ እንባየ እንኳ ፊቱን አላሟሟውም ! » አለች ። «ያ ብቻ ሳይሆን በትንሽ በትንሹ ይሁን እንጂ ፀሐይም መሞቅ ትችያለሽ» አላት ። ከዚያ በኋላ ግን ዕድሜሽን በሙሉ የፈለግሽውን ነገር ማድረግ ትችያለሽ ። ደስ ያለሽን ብትሆኝ ምንም አደጋ አይኖርም ። በነገራችን ላይ ምን ለማድረግ ነው እቅድሽ ? »

ይህን ብላ እተሽከርካሪው ወንበር ላይ ተቀምጣ ፤ እግሯ ጉንጯን ነክቶ ከራሷ በላይ እስኪሆን ሽቅብ አንስታ ከወንበሩ ጋር መሽከርከር ጀመፎች ። «አምላኬ እስቲ ይኸን ምን ትለዋለህ ? ሴትዮዋ እቢሮዬ ውስጥ ገብታ አንድ አካሏ ቢጐድል ሰው ምን ይለኛል ። አበጀህ እንኳን ይለኝ ይሆን ?»
«አትፍራ እኔ እንደሆነ ዛሬ የመጣው ቢመጣ ጥርሴ እረገፈ ፤ እግሬ ተሰበረ ... ካሣ ምናምን እንደማልል ይግባህ ።የማከብረው እንጂ የምጨቃጨቅበት ቀን አይደለም»
«እንዲያም ከሆነ መልካም ። ይህ ቀን ዓመት ባልሽ መሆኑን መስማቴ ደሞ በጣም ደስ አስኝቶኛል » ፒተር ብቻ ሳይሆን ፍሬድም (ውሻው) በሆነው ነገር ደስ ያለው ይመስላል ። ይዘላል ፤ ይቧርቃል ፤ ጭራውን ይቆላል። የተናገርኩት ስለገባው ነው አለች ውሻውን እያሰበች ። ከዚያም ጨብጠኝ እንደማለት እጅዋን እየዘረጋችለት ፣ «አላወክም ነበር ማለት ነው ጅሎ !. ይህን ዕለት ለማክበር ለራሳችን ጢን ያለ የምሳ ግብዣ እናደርጋለን ፒተር›› አለች ። ስሙን ከጠራችው በኋላ ሙሉ በሙሉ እያየችው «ፒተር ውለታህን ልከፍልህ የምችል አይመስለኝም ። ግን ደግሞ እስከመቃብር ከልቤ አትጠፋም ። መቼም ቢሆን የትም ቢሆን አስታውስሃለሁ ። በበድን አካሌ ነፍስ የዘራህባት አንተ ነህ» አለች ።

«አ…እ… እኔ ሳልሆን ሌላ ሰው ነው» አለ ፒተር ። አዎ ማሪዮን ሂልያርድ ፤ የማይክል እናት ናት ፤ ይህ ሁሉ እንዲሆን ያደረገችው። ግን ደግሞ ሜሪ ማሪዮንን ምን ያህል እንደምትጠላት ስለሚያውቅ ስሟን ሊጠራ አልፈላገም ። ሌላ ሰው ብሎ ጠራት ።
ቀጥሎም...
«እኔ. .. እኔ በበኩሌ ግን ሜሪ… ያደረግኩልሽን ሁሉ ስላደረኩልሽ ደስ ይለኛል ። ለወደፊቱም ላደርግልሽ የምትፈልጊውን ሁሉ ለማድረግ ዝግጁ ነኝ» አለ ። «ነው?... ቀልድ መስሎሃል ፤ አደል ? እንዲያውም ከዛሬ እንጀምራለን ፤ ዛሬ በስድስት ሰዓት ተኩል ተገናኝተን ምሳዬን እንድታጐርሰኝ እፈልጋለሁ ። እሺ?»
«ደስ ይለኛል»
«የት እንገናኝ ? » አንድ በቅርብ የተከፈተ ምግብ ቤት ጠቀሰላትና ታውቀው እንደሆነ ጠየቃት ።
«በሚገባ !» አለች ።
«ይስማማሻል ?››
«አሳምሮ ። እንዲያውም ካሁን ጀምሬ ወደዚያው አካባቢ ሄጂ ሰዓቱ እስኪደርስ ፎቶግራፍ ሳነሳ እቆያለሁ፡፡ አይን የሚገባ ነገር ከተገኘ»
«አሁን የልቤን ምኞት ነገርሺኝ ። ገበያ ሄጄ አዲስ ልብስ ስመርጥ ወይም ሌላ ብትይኝ ኖር ይከፋኝ ነበር» ተሰነባብተው ተለያዩ ፤ እስከምሳ ሰዓት ።

••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

በምሳ ሰዓት ሲገናኙ ልብሷን ቀይራ ሽክ ብላ አገኛት ። «በእውነት ይቺ ሴት አንቺው ራስሽ ነሽ ?»
«ባለወርቅ ጫማዋ ልዕልት እነሆኝ ፡። እንዴት ነው ፤ አምሮብኛል ?»
«አምሮብኛል !? እንደ ቅዱሳን አንፀባርቀሻል እንጂ ፤ ምንማማር ብቻ! ... እንደፈራሁት ፎቶ ግራፍ ማነሳሳቱን ትተሽ ቀሚስ መረጣ ላይ ዋልሽ ልበል?»
«ምን ይደረግ ትላለህ ። ሳስበው ለካ ይህ ቀን የሚከበር ፌስታ የሚደረግበት እንጂ የሚሠራበት አይደለም» ድንገት አቅፈህ ሳማት የሚል ሐሳብ መጣበት ፤ እምግብ ቤቱ ውስጥ ያ ሁሉ ሰው እያዬ ። ሐሳቡን ገታና እጅዋን ጥብቅ አድርጐ ያዛት ። «ውዴ ይህን ያህል ደስ ብሎሽ ስላየሁ እኔንም እጅግ ደስ አለኝ» ኣለ ። «ፒተር በጣም ደስ ብሎኛል ። የዛሬዋ ቀን ለኔ ልዩ ናት። ስለገጽታዬ ብቻ አይምሰልህ ። የዛሬ ቀን. . . ነገ የፎቶግራፍ ተርኢት የማቀርብበት ፤ ኤግዚቢሽኔ የሚከፈትበት ቀንም ስለሆነ... አዲስ ሕይወት መጀመሬም ነው።... አንተም አጠገቤ እንዳለህና ድንቅ እንደሆንክ ስለማውቅ»
👍141