#አለመኖር
"መኖርም የሚጀመረው አለመኖርን ከመፍራት ነው"“
....የሰው ልጆች በመጀመሪያ በውልደት ወደዚህ አለም ስንመጣ፣ የመጀመሪያው ትግላችን ከአለመኖር ጋር መታገል ነው፡፡ እርግጠኛ ነኝ ስለ ልጅ አወላለድ ሥርዓት ያስተማሯችሁ መምህሮቻችሁ የመጀመሪያው አንድ ደቂቃ ከሚቀጥሉት አርባ አመታት በላይ የበለጠ ፋይዳ አለው ብለዋችኋል፡፡ እውነት ነው፡
ምክንያም የመጀመሪያው አንድ ደቂቃ ከመሞት በፊት ያለው ትልቁ የህይወት
ለውጥ ነው፡፡ በእርግጥ መምህሮቻችሁ ይህን ያስተማሯችሁ ህፃን ልጅ ሲወለድ
በአግባቡ አለመተንፈሱ በአንጎሉ ዕድገት ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ትኩረት በመስጠት ነው፡፡ ለኔ ግን ከዚያም በላይ ፋይዳ አለው፡፡ ማለትም ሰው ሲወለድ የለመደው በጎ ነገር በጠቅላላ ይቀየራል፡፡
በእናት ሆድ ውስጥ ጥጋብ ነው፣ ረሃብ የለም፡፡ በእናት ሆድ ውስጥ ሙቀት ነው፤
ብርድ የለም፡፡ ከሁሉም በላይ ግን በእናት ሆድ ውስጥ ጣዕር የለም፡፡ መሥራም
የለም፡፡ በምቾት መንፈላሰስ እና በለስላሳ ውሃ ውስጥ መንሳፈፍ ነው፡፡ ይህ ሁሉ
ድሎት በተወለድንበት ቅፅበት ይለወጣል፡፡ መተንፈስ ግድ ይለላ፡፡ ረሃብን
ለማስታገስ መጥባት እንጀምራለን፡፡ ይበርደናል፤ ሙቀት ለማግኘት ከሌላው
እንጠጋለን ለመኖር፡፡ አለበለዚያ መኖር የለም፡፡ መታን፣ በረሃብ አለንጋ መቆላትና
በብርድ ቆርፍዶ መሞት የፍርሃታችን ሁሉ መነሻ ይሆናሉ፡፡ በእናታችን ማህፀን
ውስጥ የምናውቀው መኖርን ብቻ ነው፡፡ መውለድ ግን አለመኖር አመላካች ነው፡፡
ይህ ስጋት ታዲያ በህይወታችን ሙሉ የሚዘልቅ ነው፡፡ በየደረጃው፣ በየእድሜያችን ለአለመኖር ስጋት እንደተጋለጥን እንዘልቃለን፡፡
የምንኖርበት አለም ደግሞ የሰው ልጅ የዘመናት የአለመኖር ስጋን ለማስወገድ
በመመኘት የገነባው የአኗኗር ስርዓት አለው፡፡ ይህም ስርዓት ከመወለዳችን
ይረከብና፡፡ በወላጆች፣ ዘመድ፣ ጎረቤት፣ ሰፈር፣ ብሄር ቋንቋ፣ ባህል፣ ሃይማኖትና
ልምድ ያሉበት ዓለም ከእኛ ቀድሞ ይጠብቀናል፡፡ ይህ ሁሉ ባለበት ዓለም
ተወልደን፣ በእኚህ ቀድመው በተዘጋጁ ስርዓቶች ውስጥ አለመኖርን ሸሽተን
ለመኖር ስንል እንታሰራለን፡፡”
ከአለመኖር መፅሀፍ የተወሰደ።
"መኖርም የሚጀመረው አለመኖርን ከመፍራት ነው"“
....የሰው ልጆች በመጀመሪያ በውልደት ወደዚህ አለም ስንመጣ፣ የመጀመሪያው ትግላችን ከአለመኖር ጋር መታገል ነው፡፡ እርግጠኛ ነኝ ስለ ልጅ አወላለድ ሥርዓት ያስተማሯችሁ መምህሮቻችሁ የመጀመሪያው አንድ ደቂቃ ከሚቀጥሉት አርባ አመታት በላይ የበለጠ ፋይዳ አለው ብለዋችኋል፡፡ እውነት ነው፡
ምክንያም የመጀመሪያው አንድ ደቂቃ ከመሞት በፊት ያለው ትልቁ የህይወት
ለውጥ ነው፡፡ በእርግጥ መምህሮቻችሁ ይህን ያስተማሯችሁ ህፃን ልጅ ሲወለድ
በአግባቡ አለመተንፈሱ በአንጎሉ ዕድገት ላይ የሚያደርሰውን ተፅዕኖ ትኩረት በመስጠት ነው፡፡ ለኔ ግን ከዚያም በላይ ፋይዳ አለው፡፡ ማለትም ሰው ሲወለድ የለመደው በጎ ነገር በጠቅላላ ይቀየራል፡፡
በእናት ሆድ ውስጥ ጥጋብ ነው፣ ረሃብ የለም፡፡ በእናት ሆድ ውስጥ ሙቀት ነው፤
ብርድ የለም፡፡ ከሁሉም በላይ ግን በእናት ሆድ ውስጥ ጣዕር የለም፡፡ መሥራም
የለም፡፡ በምቾት መንፈላሰስ እና በለስላሳ ውሃ ውስጥ መንሳፈፍ ነው፡፡ ይህ ሁሉ
ድሎት በተወለድንበት ቅፅበት ይለወጣል፡፡ መተንፈስ ግድ ይለላ፡፡ ረሃብን
ለማስታገስ መጥባት እንጀምራለን፡፡ ይበርደናል፤ ሙቀት ለማግኘት ከሌላው
እንጠጋለን ለመኖር፡፡ አለበለዚያ መኖር የለም፡፡ መታን፣ በረሃብ አለንጋ መቆላትና
በብርድ ቆርፍዶ መሞት የፍርሃታችን ሁሉ መነሻ ይሆናሉ፡፡ በእናታችን ማህፀን
ውስጥ የምናውቀው መኖርን ብቻ ነው፡፡ መውለድ ግን አለመኖር አመላካች ነው፡፡
ይህ ስጋት ታዲያ በህይወታችን ሙሉ የሚዘልቅ ነው፡፡ በየደረጃው፣ በየእድሜያችን ለአለመኖር ስጋት እንደተጋለጥን እንዘልቃለን፡፡
የምንኖርበት አለም ደግሞ የሰው ልጅ የዘመናት የአለመኖር ስጋን ለማስወገድ
በመመኘት የገነባው የአኗኗር ስርዓት አለው፡፡ ይህም ስርዓት ከመወለዳችን
ይረከብና፡፡ በወላጆች፣ ዘመድ፣ ጎረቤት፣ ሰፈር፣ ብሄር ቋንቋ፣ ባህል፣ ሃይማኖትና
ልምድ ያሉበት ዓለም ከእኛ ቀድሞ ይጠብቀናል፡፡ ይህ ሁሉ ባለበት ዓለም
ተወልደን፣ በእኚህ ቀድመው በተዘጋጁ ስርዓቶች ውስጥ አለመኖርን ሸሽተን
ለመኖር ስንል እንታሰራለን፡፡”
ከአለመኖር መፅሀፍ የተወሰደ።
👍3
#ራሳችንን #የምናይበት #አስገራሚ #ታሪክ
አንዲት ወጣት ሴት ለጉዞ ኤርፖርት ውስጥ ተቀምጣለች አውሮፕላኑ እንደሚዘገይ ባወቀች ጊዜ ኤርፓርት ውስጥ ካሉት ሱቆች ኩኪስና
መጽሐፍ ገዛች።ወደ VIP (የተመረጡ ሰዎች) ብቻ ወደ የሚስተናገዱበት ክፍል ገብታ ለንባብ ምቹ ወደ ሆነው መደገፊያ ወንበር አመራች
ተደላድላ ተቀምጣ ማንበብ ጀመረች አጠገቧ እንድ ሰው መጽሐፍ ያነባል
በሁለት መደገፊያ ወንበሮች መሐል ኩኪስ ተቀምጧል በንባቧ መካከል መተከዢያ ሆኗታል ታዲያ ከኩኪሷ አንድ ስታነሳ ሰውየውም አንድ አነሳ ገረማት ሳያስፈቅዳት መውሰዱ
አስደነቃት ግን ዝም አለች
ቀጥላ እርሷ አንድ ስትወስድ እርሱም ሌላ
ወሰደ አሁን ተበሳጨች። ድፍረቱ አናደዳት።
በዚህ አላበቃም እስከ መጨረሻው ቀጠለ።
ቅጥል አለች! ግን ንቃ ተወችው።
በአካባቢው ያሉ ሰዎችን አትኩሮት መሳብ
አልፈለገችም። ለዚህ ብቻ አይደለም በኩኪስ
ምክንያት ጸብ ረብሻ መፍጠር
አልፈለገችም።እንዲህ እንዲህ እያለ
የመጨረሻ አንድ ኩኪስ ቀረች። " ይሄ
የተረገመሰው ምን ያደርግ ይሆን? " ስትል
አሰበችና በቀስታ ማየት ጀመረች። ከዚያም
ሰውየው ኩኪሷን ሁለት ቦታ ከፈላትና ግማሹን
ወሰደ። ለድፍረቱ ጥግ አጣችለት። ከልክ ያለፈ
ስርዓት የለሽ እንደሆነ ደመደመች።ሰዓቱ
ደርሶ አውሮፕላን ላይ እንደተሳፈረች መነጽር
ለማውጣት ቦርሳዋን ስትከፍት አይኗን
ማመን አልቻለችም። ያልተከፈተው
የታሸገው ኩኪሷ ቦርሳዋ ውስጥ አለ። በጣም
አፈረች ተሸማቀቀች። ለካስ የራስዋን ኩኪስ
ቦርሳዋ ውስጥ ረስታ የሰውየውን ነበር
ስትበላ የቆየችው። ከሁሉም በላይ በጣም
ያጸጸታት ሰውየው እስከ መጨረሻው አንዲት
ኩኪስ እስክትቀር ድረስ ያካፍላት የነበረው
ምንም ሳይቆጣና ሳይመረር በደስታ መሆኑ
ነበር።የራሱን ኩኪስ እየበላች በሰውየው ላይ
ስትበሳጭበት በመቆየቷ እጅግ አፈረች።
አሁን ይቅርታ ለመጠየቅ እንኳን ጊዜው
አልፏል። እርሱም በሌላ አውሮፕላን ወደ
ሐገሩ አቅንቷል። እርሱን የማግኘት አንድ
ተጨማሪ እድል እንኳን የላትም። ብዙ ተመኘች ማመስገን፣ ይቅርታ መጠየቅ፣ ጉዳዩን ማብራራት፣ .....ግን ሁሉም እሷው ጋር ቀሩ አልፏል።
#አራት #የማይጠገኑ #ነገሮችን #አሰበች
👉 ድንጋይ ከተወረወረ በኋላ
👉 ቃላት ከተናገርናቸው በኋላ
👉ድርጊቶች ካመለጡን በኋላ
👉ጊዜ ካለፈ በኋላዋጋ እንደሌለው እኛም
ምንም ነገር ከመናገራችን ከመፈፀማችን
በፊት መጀመሪያ ራሳችንን እንይ
ዛሬ ልናመሰግናቸው ዋጋ ልንሰጣቸው
ልናከብራቸው የሚገባን ወዳጆቻችን የትዳር
አጋሮቻችንን ጀግኖቻችን ጊዜው ሳያልፍ
እናመስግናቸው።
#መልካም #ቀን
አንዲት ወጣት ሴት ለጉዞ ኤርፖርት ውስጥ ተቀምጣለች አውሮፕላኑ እንደሚዘገይ ባወቀች ጊዜ ኤርፓርት ውስጥ ካሉት ሱቆች ኩኪስና
መጽሐፍ ገዛች።ወደ VIP (የተመረጡ ሰዎች) ብቻ ወደ የሚስተናገዱበት ክፍል ገብታ ለንባብ ምቹ ወደ ሆነው መደገፊያ ወንበር አመራች
ተደላድላ ተቀምጣ ማንበብ ጀመረች አጠገቧ እንድ ሰው መጽሐፍ ያነባል
በሁለት መደገፊያ ወንበሮች መሐል ኩኪስ ተቀምጧል በንባቧ መካከል መተከዢያ ሆኗታል ታዲያ ከኩኪሷ አንድ ስታነሳ ሰውየውም አንድ አነሳ ገረማት ሳያስፈቅዳት መውሰዱ
አስደነቃት ግን ዝም አለች
ቀጥላ እርሷ አንድ ስትወስድ እርሱም ሌላ
ወሰደ አሁን ተበሳጨች። ድፍረቱ አናደዳት።
በዚህ አላበቃም እስከ መጨረሻው ቀጠለ።
ቅጥል አለች! ግን ንቃ ተወችው።
በአካባቢው ያሉ ሰዎችን አትኩሮት መሳብ
አልፈለገችም። ለዚህ ብቻ አይደለም በኩኪስ
ምክንያት ጸብ ረብሻ መፍጠር
አልፈለገችም።እንዲህ እንዲህ እያለ
የመጨረሻ አንድ ኩኪስ ቀረች። " ይሄ
የተረገመሰው ምን ያደርግ ይሆን? " ስትል
አሰበችና በቀስታ ማየት ጀመረች። ከዚያም
ሰውየው ኩኪሷን ሁለት ቦታ ከፈላትና ግማሹን
ወሰደ። ለድፍረቱ ጥግ አጣችለት። ከልክ ያለፈ
ስርዓት የለሽ እንደሆነ ደመደመች።ሰዓቱ
ደርሶ አውሮፕላን ላይ እንደተሳፈረች መነጽር
ለማውጣት ቦርሳዋን ስትከፍት አይኗን
ማመን አልቻለችም። ያልተከፈተው
የታሸገው ኩኪሷ ቦርሳዋ ውስጥ አለ። በጣም
አፈረች ተሸማቀቀች። ለካስ የራስዋን ኩኪስ
ቦርሳዋ ውስጥ ረስታ የሰውየውን ነበር
ስትበላ የቆየችው። ከሁሉም በላይ በጣም
ያጸጸታት ሰውየው እስከ መጨረሻው አንዲት
ኩኪስ እስክትቀር ድረስ ያካፍላት የነበረው
ምንም ሳይቆጣና ሳይመረር በደስታ መሆኑ
ነበር።የራሱን ኩኪስ እየበላች በሰውየው ላይ
ስትበሳጭበት በመቆየቷ እጅግ አፈረች።
አሁን ይቅርታ ለመጠየቅ እንኳን ጊዜው
አልፏል። እርሱም በሌላ አውሮፕላን ወደ
ሐገሩ አቅንቷል። እርሱን የማግኘት አንድ
ተጨማሪ እድል እንኳን የላትም። ብዙ ተመኘች ማመስገን፣ ይቅርታ መጠየቅ፣ ጉዳዩን ማብራራት፣ .....ግን ሁሉም እሷው ጋር ቀሩ አልፏል።
#አራት #የማይጠገኑ #ነገሮችን #አሰበች
👉 ድንጋይ ከተወረወረ በኋላ
👉 ቃላት ከተናገርናቸው በኋላ
👉ድርጊቶች ካመለጡን በኋላ
👉ጊዜ ካለፈ በኋላዋጋ እንደሌለው እኛም
ምንም ነገር ከመናገራችን ከመፈፀማችን
በፊት መጀመሪያ ራሳችንን እንይ
ዛሬ ልናመሰግናቸው ዋጋ ልንሰጣቸው
ልናከብራቸው የሚገባን ወዳጆቻችን የትዳር
አጋሮቻችንን ጀግኖቻችን ጊዜው ሳያልፍ
እናመስግናቸው።
#መልካም #ቀን
👍3❤1
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ?
መሃል አዲስአባ…ሸገር ላይ እያላችሁ..
የእንቁራሪቶች ድምፅ በደንብ ከሰማችሁ
በክር የታሰረ ጢንዚዛ ካያችሁ
የማርያም ፈረስን መንገድ ካገኛችሁ
በእፉዬ ገላ ‹‹ያዘኝ አትያዘኝ›› ከተጃጃላችሁ…
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
ሱዚ የሚዘሉ
ፔፕሲ የሚራገጡ
ሸክላ እየፈጩ በርበሬ ነው የሚሉ
ሙሽራ ሙሽራ – እቃ እቃ እቃ እቃ የሚጨዋወቱ
ጢቢ ጢቢ ሰርተው- እየተጫወቱ- የሚፈነድቁ -ሴት ልጆች ካያችሁ
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
በኮባ ጠመንጃ የሚተኳኩሱ
ኳሷን ከስልክ እንጨት ድብን አርገው አስረው ቴዘር የሚመቱ
በሽቦ መኪና የሚወዳደሩ
መሬትን ቆፋፍረው ብይ የሚጫወቱ
ልጆችን ካያችሁ
ዛፉን ተፈናጥጠው ሆምጣጤ የሚያወርዱ
ከአመት እስከ አመት እርግብ የሚያረቡ
በሌሊት ተነስተው ለእግር ኳስ ቡድን ስፖርት የሚሰሩ ፈርጣማ ጎረምሶች
ሰፈር ውስጥ ካያችሁ
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
አዲሳባ መሃል የአሞራ ክንፍ ቪላ
የቀይ ሸክላ ውብ ቤት በአይናችሁ ካያችሁ
ሰንሰልና ሃረግ አጥር ሆነው ቆመው በጎን ካለፋችሁ
ላላ ያለ ጉንጉን ሁለት ቦታ ከፍላ የተሰራች ጉብል ከገጠመቻችሁ…
‹‹አትሸኟትም ወይ መሄዷ አይደለም ወይ›› እያሉ ሲዘፍኑ ካንጀቷ ምታለቅስ ሙሽራ ካያችሁ
ፅዋ ተሸክመው እያሸበሸቡ ወይ እየዘመሩ የሚጓዙ ሴቶች
መንገድ ካገኛችሁ
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
በድፎ ዳቦና በሚሪንዳ ብቻ ልደቱን የሚያከብር ትንሽ ልጅ ካያችሁ
‹‹በሙሽራ ቀሚስ›› እየፈነደቀች ወዲህ ወዲያ የምትል ትንሽ ልጅ ካያችሁ
በሚያበራ ጫማ- ወይም በ‹‹ኦክስጅን ባግ›› ጓደኛ የሚያቀና ህፃን ልጅ ካያችሁ
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
በውይይት ታክሲ በረድፍ ተቀምጣችሁ ከተጓጓዛችሁ
ለአንዲት ነገር ብቻ መርካቶ ሸመታ ጎራ እንኳን ካላችሁ
አምስት ሳንቲምና ስሙኒ ካያችሁ
እሱ እንኳን ቢጠፋ የአንድ ብር ወረቀት ከኖረ በእጃችሁ
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
በናና የተፈላ ሻይ ፉት ካላችሁ
ሽልጦን ከወዳጅ ከተካፈላችሁ
አሹቅ አነባብሮን መክሰስ ካረጋችሁ
ቤት የተዘጋጀ- የሰነፍ ገብስ ቆሎ ዝግን ካረጋችሁ
ከጎረቤት ጋር ሰብሰብ ብላችሁ ቡና ከጠጣችሁ…
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
🔘በህይወት እምሽዉ🔘
መሃል አዲስአባ…ሸገር ላይ እያላችሁ..
የእንቁራሪቶች ድምፅ በደንብ ከሰማችሁ
በክር የታሰረ ጢንዚዛ ካያችሁ
የማርያም ፈረስን መንገድ ካገኛችሁ
በእፉዬ ገላ ‹‹ያዘኝ አትያዘኝ›› ከተጃጃላችሁ…
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
ሱዚ የሚዘሉ
ፔፕሲ የሚራገጡ
ሸክላ እየፈጩ በርበሬ ነው የሚሉ
ሙሽራ ሙሽራ – እቃ እቃ እቃ እቃ የሚጨዋወቱ
ጢቢ ጢቢ ሰርተው- እየተጫወቱ- የሚፈነድቁ -ሴት ልጆች ካያችሁ
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
በኮባ ጠመንጃ የሚተኳኩሱ
ኳሷን ከስልክ እንጨት ድብን አርገው አስረው ቴዘር የሚመቱ
በሽቦ መኪና የሚወዳደሩ
መሬትን ቆፋፍረው ብይ የሚጫወቱ
ልጆችን ካያችሁ
ዛፉን ተፈናጥጠው ሆምጣጤ የሚያወርዱ
ከአመት እስከ አመት እርግብ የሚያረቡ
በሌሊት ተነስተው ለእግር ኳስ ቡድን ስፖርት የሚሰሩ ፈርጣማ ጎረምሶች
ሰፈር ውስጥ ካያችሁ
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
አዲሳባ መሃል የአሞራ ክንፍ ቪላ
የቀይ ሸክላ ውብ ቤት በአይናችሁ ካያችሁ
ሰንሰልና ሃረግ አጥር ሆነው ቆመው በጎን ካለፋችሁ
ላላ ያለ ጉንጉን ሁለት ቦታ ከፍላ የተሰራች ጉብል ከገጠመቻችሁ…
‹‹አትሸኟትም ወይ መሄዷ አይደለም ወይ›› እያሉ ሲዘፍኑ ካንጀቷ ምታለቅስ ሙሽራ ካያችሁ
ፅዋ ተሸክመው እያሸበሸቡ ወይ እየዘመሩ የሚጓዙ ሴቶች
መንገድ ካገኛችሁ
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
በድፎ ዳቦና በሚሪንዳ ብቻ ልደቱን የሚያከብር ትንሽ ልጅ ካያችሁ
‹‹በሙሽራ ቀሚስ›› እየፈነደቀች ወዲህ ወዲያ የምትል ትንሽ ልጅ ካያችሁ
በሚያበራ ጫማ- ወይም በ‹‹ኦክስጅን ባግ›› ጓደኛ የሚያቀና ህፃን ልጅ ካያችሁ
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
በውይይት ታክሲ በረድፍ ተቀምጣችሁ ከተጓጓዛችሁ
ለአንዲት ነገር ብቻ መርካቶ ሸመታ ጎራ እንኳን ካላችሁ
አምስት ሳንቲምና ስሙኒ ካያችሁ
እሱ እንኳን ቢጠፋ የአንድ ብር ወረቀት ከኖረ በእጃችሁ
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
በናና የተፈላ ሻይ ፉት ካላችሁ
ሽልጦን ከወዳጅ ከተካፈላችሁ
አሹቅ አነባብሮን መክሰስ ካረጋችሁ
ቤት የተዘጋጀ- የሰነፍ ገብስ ቆሎ ዝግን ካረጋችሁ
ከጎረቤት ጋር ሰብሰብ ብላችሁ ቡና ከጠጣችሁ…
#ስንት #ጊዜ #ሆናችሁ ?
🔘በህይወት እምሽዉ🔘
👍4
#ለቃልህ #ታምኜ
በአንዲት እርጉም ቀን ልቤ ፅድቅ ሻተ
ከመፅሐፍህ መሃል “ግራህን ቢመቱ ቀኝ ስጥ” የሚል ቃል ለነብሴ ሸተተ
እልፍ ጠላቶቼ መንገዴን ተረዱ
በእፀድቃለሁ ሰበብ መስከኔን ወደዱ
መጡ ተሰልፈው
ግራዬን ነገሉ
ከቀኙም አንድ አሉ
ወገሩኝ ደጋግመው ክንዳቸው እስኪዝል
ሁሉን ዝም አልክዋቸው ፅድቅህ ይበልጣል ስል
እነሱ ቀጠሉ
የሩቅ ጠላቶቼም እየተጠራሩ
የድል ፈገግታና ቡጢ ሰነዘሩ
በዚህ ሁሉ መሀል አንተ ዝም ብለሀል
በልቤ መሀል ላይ ቃልህ ይንገዋላል
…ቡጢያቸው በረታ ዝምታህ አየለ
እልቦናዬ ውስጥ ትዕዛዝህ ዋለለ
‘…ቀኝህን ስጣቸው’ ይል ቃልህ ተነቅሮ
ግራህን ሲመቱ ቀኛቸውን አንግል ሆነ ተቀይሮ
ዝም ብሎ መጠፍጠፍ መነረቱን ትቼ
እጥፍ ቡጢዎችን ሰነዘሩ እጆቼ
በዙሪያዬ ሆነው ሲያሹኝ የነበሩ
ጠላቶቼ ሁሉ ደንብረው በረሩ
ታዲያ ይህን ጊዜ አንድ ነገር ገባኝ
እፀድቃለሁ ብሎ ፊትን ከመሰዋት
ቀድመው እየመቱ መቺን ካገር ማጥፋት
🔘በ አገኘሁ አሰግድ🔘
በአንዲት እርጉም ቀን ልቤ ፅድቅ ሻተ
ከመፅሐፍህ መሃል “ግራህን ቢመቱ ቀኝ ስጥ” የሚል ቃል ለነብሴ ሸተተ
እልፍ ጠላቶቼ መንገዴን ተረዱ
በእፀድቃለሁ ሰበብ መስከኔን ወደዱ
መጡ ተሰልፈው
ግራዬን ነገሉ
ከቀኙም አንድ አሉ
ወገሩኝ ደጋግመው ክንዳቸው እስኪዝል
ሁሉን ዝም አልክዋቸው ፅድቅህ ይበልጣል ስል
እነሱ ቀጠሉ
የሩቅ ጠላቶቼም እየተጠራሩ
የድል ፈገግታና ቡጢ ሰነዘሩ
በዚህ ሁሉ መሀል አንተ ዝም ብለሀል
በልቤ መሀል ላይ ቃልህ ይንገዋላል
…ቡጢያቸው በረታ ዝምታህ አየለ
እልቦናዬ ውስጥ ትዕዛዝህ ዋለለ
‘…ቀኝህን ስጣቸው’ ይል ቃልህ ተነቅሮ
ግራህን ሲመቱ ቀኛቸውን አንግል ሆነ ተቀይሮ
ዝም ብሎ መጠፍጠፍ መነረቱን ትቼ
እጥፍ ቡጢዎችን ሰነዘሩ እጆቼ
በዙሪያዬ ሆነው ሲያሹኝ የነበሩ
ጠላቶቼ ሁሉ ደንብረው በረሩ
ታዲያ ይህን ጊዜ አንድ ነገር ገባኝ
እፀድቃለሁ ብሎ ፊትን ከመሰዋት
ቀድመው እየመቱ መቺን ካገር ማጥፋት
🔘በ አገኘሁ አሰግድ🔘
#ቫላታይንስ #ደይ *(ሳሙኤል አዳነ)
ፍቅር ነው...
ስትስቂ አሳስቄሽ፣
ስትሄጅ ናፍቄሽ፣
ስትመጭ መርቄሽ፣
ስትከፊ ደግም የአይኖችሽ እንባ
በልቤ እየገባ፡እኔም አነባለሁ፤
በአንች መታመም ታማሚ እሆናለሁ፡፡
ታሪክ ነው ፣
ድምፅሽን ሣልሰማ ልቤ እየጨነቀው፤
የሞባይል ካርዴ ባንች ነው የሚያልቀው።
አንችን ስወድሽ ቀን ፡እኔን ስለተውኩኝ፤
ጊዜህን ብትይኝ፡ሁሉን ነገር ትቼ ካንችጋራ ሆንኩኝ
ታሪክ ነው፣
አንች ሪሞት ሆነሽ፡እኔ ደሞ ቻናል፤
play pause ስትይኝ ፡የስንቱ መዝናኛ ሚዲያ ሆነናል።
ደሞ ከሰሞኑ...
ሚዲያ የሚሉት መረጃ ማይርቀው፣
የፍቅረኛሞች ቀን ብሎ እያከበረ ልቤን አስጨነቀዉ።
እህህ...
valantines day በእኔው እይታ፤
የሞኞች ዕብደት ነው፤የሞኞች ጨዋታ፤
አድማጭ የሌለበት የስብሰባ ቦታ ።
ለምን ብትይ...
ዛሬ የፍቅር ቀን ነገ የጥላቻ፣
ፍቅርና ውሸት ቀን ቆጠራ ብቻ።
እውነቱን ልንገርሽ፣
ፍቅር በባህሪው ቀን ቆጠራ አያውቅም።
አበባ እያሳየ የሰው ልብ አይሠርቅም።
ዛሬ እያስደሰተ ነገ አያስለቅስም።
እሡን ተይውና
ይሄውልሽ ፍቅሬ
አንች ብጠይኝም እኔ ወድሻለሁ፣
መልሰሽ ከመጣሽ፤
በልቤ ዙፍን ላይ
አስቀምጥሻለሁ።
ቦታ አገኘሁ ብሎ
መጤ ሳያርፍበት፣
ንግስናሽን ይዘሽ
ነይና ተኝበት።
እንደዛ ከሆነ፡፤
ፍቅራችን አይሎ
እውነት እንሆናለን፣
እኔ ባሪያ ሆኘ አንች ደግሞ ንግስት
valantines day ሁሌ እናከብራለን።
*
27/07/08
8:00pm
ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ
ከቻናሉ ተከታታይ የተላከ የተመቸዉ 👍
ፍቅር ነው...
ስትስቂ አሳስቄሽ፣
ስትሄጅ ናፍቄሽ፣
ስትመጭ መርቄሽ፣
ስትከፊ ደግም የአይኖችሽ እንባ
በልቤ እየገባ፡እኔም አነባለሁ፤
በአንች መታመም ታማሚ እሆናለሁ፡፡
ታሪክ ነው ፣
ድምፅሽን ሣልሰማ ልቤ እየጨነቀው፤
የሞባይል ካርዴ ባንች ነው የሚያልቀው።
አንችን ስወድሽ ቀን ፡እኔን ስለተውኩኝ፤
ጊዜህን ብትይኝ፡ሁሉን ነገር ትቼ ካንችጋራ ሆንኩኝ
ታሪክ ነው፣
አንች ሪሞት ሆነሽ፡እኔ ደሞ ቻናል፤
play pause ስትይኝ ፡የስንቱ መዝናኛ ሚዲያ ሆነናል።
ደሞ ከሰሞኑ...
ሚዲያ የሚሉት መረጃ ማይርቀው፣
የፍቅረኛሞች ቀን ብሎ እያከበረ ልቤን አስጨነቀዉ።
እህህ...
valantines day በእኔው እይታ፤
የሞኞች ዕብደት ነው፤የሞኞች ጨዋታ፤
አድማጭ የሌለበት የስብሰባ ቦታ ።
ለምን ብትይ...
ዛሬ የፍቅር ቀን ነገ የጥላቻ፣
ፍቅርና ውሸት ቀን ቆጠራ ብቻ።
እውነቱን ልንገርሽ፣
ፍቅር በባህሪው ቀን ቆጠራ አያውቅም።
አበባ እያሳየ የሰው ልብ አይሠርቅም።
ዛሬ እያስደሰተ ነገ አያስለቅስም።
እሡን ተይውና
ይሄውልሽ ፍቅሬ
አንች ብጠይኝም እኔ ወድሻለሁ፣
መልሰሽ ከመጣሽ፤
በልቤ ዙፍን ላይ
አስቀምጥሻለሁ።
ቦታ አገኘሁ ብሎ
መጤ ሳያርፍበት፣
ንግስናሽን ይዘሽ
ነይና ተኝበት።
እንደዛ ከሆነ፡፤
ፍቅራችን አይሎ
እውነት እንሆናለን፣
እኔ ባሪያ ሆኘ አንች ደግሞ ንግስት
valantines day ሁሌ እናከብራለን።
*
27/07/08
8:00pm
ወልዲያ ዩኒቨርሲቲ
ከቻናሉ ተከታታይ የተላከ የተመቸዉ 👍
👍3
#ሲጨልም
ወደ ሰባዎቹ የሚጠጉ የሚመስሉ አንድ አረጋዊ “ልጄ” አሉት አስተናጋጁን፡፡ “የወሰድኩትን መድኃኒት ይዤብህ መጣሁ፣ እባክህን የሰጠኸኝን ወስደህ . . .”
አላስጨርሳቸውም፡፡ ግርግዳው ላይ ወደተለጠፈው ጽሑፍ አመለከታቸው፡፡‘የተሸጠ መድኃኒት አይመለስም አረጋዊው’ በለሰለሱ ቃላት መማፀን ያዙ፡፡
“ሰውዬ ዞር በል! ስራ ልስራበት! ለእንቶ ፈንቶ ጉዳይ የማባክነው ጊዜ የለኝም. . .” አለ ቁጣው እየተወለደ፡፡
“ዛሬ በዚህ ሰውዬ እንድጨቀጨቅ ተፈርዶብኛል ልበል?”
“እባክህን ልጄ አሳፋሪ ነገር ደርሶብኝ ነው ዘመድና ዕድር የለለኝ በመሆኑ እንጂ . . . ” አሉ ትሁት በሆነች ፈገግታ ሊያባብሉት እየሞከሩ፡፡
“ቅናሽ ዋጋ ብትከፍለኝም . . .”
“ይሄ ሰውዬ ነካ ያረገዋል ልበል?” አለና ሌሎች መድኃኒት ገዥዎችን ያስተናግድ ገባ፡፡ “ከያዙ አይለቁ”
“ድህነት ቢፈትነኝ ነው ልጄ” አለ¸ያደፈና የነተበ ነጠላቸውን እያሳዩት፡፡ ነጠላው ከሰውነታቸው በከፋ ሁኔታ ያረጀውን ኮታቸውን ደብቆላቸዋል፡፡
“አቅሜ የደከመ ባይሆን ኖሮ . . . ” ጫማ ካገኘ የከረመ እግራቸውን እያዩ፡፡ አንዲት ተስተናጋጅ “አልመልስም ካለ አልመልስም ነው፡፡ ለምንድነው የሚነዘንዙት?” አለች በሚነጫነጭ ድምጽ “ይሄኮ ፋርማሲ እንጂ አዛውንቶች የሚጦሩበት የድኩማን መርጃ ድርጅት አይደለም”
አነጋገሯን ያልወደደው የሚመስል ሌላኛው ጎልማሳ ደግሞ “መድኃኒቱን ሙሉ በሙሉ የገዙት ከዚሁ መደብር ነው?” የሚል ጥያቄ አመጣ፡፡
“አዎ ዶክተሩ ፅፎ በሰጠኝ መሠረት”
“ምን ያሕል ፈጀብዎት?”
“ሰባ ሁለት ብር ከሰማኒያ አምስት ሳንቲም፡፡ መድኃኒቱን ወስደው ግማሹን እንኳን ቢሰጡኝ ምን አለበት?” አሉ በሃዘኔታ፤ “የሁለታችንንም የጋብቻ ቀለበት አስይዤ ነው ከማምነው ሰው የተበደርኩት”
“መድኃኒቱን ለምን መመለስ ፈለጉ?” ዘንቢል ያንጠለጠሉ ያንዲት ምስኪን እናት ጥያቄ፡፡
በዚህ ጊዜ አስተናጋጁ ጣልቃ ገባ፡፡ “ባህላዊ ሕክምና ብትከታተል ኪስ እንደማታራቁት ገብቷቸው ይሆናላ! ወይ ፀበል ሊያጠምቋት! ወይ . . .”
“ኧይ ልጄ! ጉዳዩን ብታውቀው ኖሮ ያፌዝክበት ምላስህን ታፍርበት ነበር . . .” አሉ እንባ እየተናነቃቸው፡፡
“መድኃኒቱን ምን ላድርገው? ልዋጠው ወይስ ሽንት ቤት ልጨምረው?”
“ለባለቤቴ ነው የምገዛላት ብለው አልነበር? በጠና ታማብኛለች የእድሜዬ ጀምበር እየጠለቀ ባበት ሰዓት ለእህል ያላነሱና ለትምህርት ያልደረሱ ሦስት ልጆች በትናብኝ እንዳትሄድ ፀልይልኝ ብለውኝ አልነበር?”
“ማለቱንስ ብዬህ ነበር ልጄ! . . . ብዬ ነበር”
“እና ሩብ ሰዓት ያህል እንኳን ሳይቆዩ ሃሳብዎን አስሰርዞ የገዙትን መድኃኒት የሚያስመልስ ምን ተአምር ተፈጠረ?! ቅድም የማይመለከተኝን ነገር ሲዘላብዱልኝ ነበር እኮ” አረጋዊው አንገታቸውን ደፉ፡፡ “እኮ ምን ቢፈጠር ነው . . . ?”
“ቤቴ ሳልደርስ ነው አንተ ዘንድ የመጣሁት”
“ለምን?” የሌሎቹ ጥያቄ፡፡
“ሰፈርተኞቼ ደጄ ላይ ሲጯጯሁ አየሁ፡፡ ባቤቴን በህይወቷ ልደርስላት አልቻልኩም!” አሉ አረጋዊው ድምጻቸው እየሻከረ፡፡ እንባቸው እየወረደ፡፡ በመድኃኒት ሻጩ ፊት ላይ ፀፀት ድንጋጤ እየታየ ድፍን መቶ ብር አውጥቶ በሻካራ እጆቻቸው ላይ አኖረው፡፡ ሌሎቹም ኪሶቻቸውን ይፈታትሹ ጀምር፡፡
“ይባርካችሁ ልጆቼ! ከፈን መግዣ ስላልነበረኝ እንጂ . . . ” አንባ ተናነቃቸው፡፡
መንሰቅሰቃቸውን እየቀጠሉ ወጡ፡፡
ፀጥታ!😔😔
ወደ ሰባዎቹ የሚጠጉ የሚመስሉ አንድ አረጋዊ “ልጄ” አሉት አስተናጋጁን፡፡ “የወሰድኩትን መድኃኒት ይዤብህ መጣሁ፣ እባክህን የሰጠኸኝን ወስደህ . . .”
አላስጨርሳቸውም፡፡ ግርግዳው ላይ ወደተለጠፈው ጽሑፍ አመለከታቸው፡፡‘የተሸጠ መድኃኒት አይመለስም አረጋዊው’ በለሰለሱ ቃላት መማፀን ያዙ፡፡
“ሰውዬ ዞር በል! ስራ ልስራበት! ለእንቶ ፈንቶ ጉዳይ የማባክነው ጊዜ የለኝም. . .” አለ ቁጣው እየተወለደ፡፡
“ዛሬ በዚህ ሰውዬ እንድጨቀጨቅ ተፈርዶብኛል ልበል?”
“እባክህን ልጄ አሳፋሪ ነገር ደርሶብኝ ነው ዘመድና ዕድር የለለኝ በመሆኑ እንጂ . . . ” አሉ ትሁት በሆነች ፈገግታ ሊያባብሉት እየሞከሩ፡፡
“ቅናሽ ዋጋ ብትከፍለኝም . . .”
“ይሄ ሰውዬ ነካ ያረገዋል ልበል?” አለና ሌሎች መድኃኒት ገዥዎችን ያስተናግድ ገባ፡፡ “ከያዙ አይለቁ”
“ድህነት ቢፈትነኝ ነው ልጄ” አለ¸ያደፈና የነተበ ነጠላቸውን እያሳዩት፡፡ ነጠላው ከሰውነታቸው በከፋ ሁኔታ ያረጀውን ኮታቸውን ደብቆላቸዋል፡፡
“አቅሜ የደከመ ባይሆን ኖሮ . . . ” ጫማ ካገኘ የከረመ እግራቸውን እያዩ፡፡ አንዲት ተስተናጋጅ “አልመልስም ካለ አልመልስም ነው፡፡ ለምንድነው የሚነዘንዙት?” አለች በሚነጫነጭ ድምጽ “ይሄኮ ፋርማሲ እንጂ አዛውንቶች የሚጦሩበት የድኩማን መርጃ ድርጅት አይደለም”
አነጋገሯን ያልወደደው የሚመስል ሌላኛው ጎልማሳ ደግሞ “መድኃኒቱን ሙሉ በሙሉ የገዙት ከዚሁ መደብር ነው?” የሚል ጥያቄ አመጣ፡፡
“አዎ ዶክተሩ ፅፎ በሰጠኝ መሠረት”
“ምን ያሕል ፈጀብዎት?”
“ሰባ ሁለት ብር ከሰማኒያ አምስት ሳንቲም፡፡ መድኃኒቱን ወስደው ግማሹን እንኳን ቢሰጡኝ ምን አለበት?” አሉ በሃዘኔታ፤ “የሁለታችንንም የጋብቻ ቀለበት አስይዤ ነው ከማምነው ሰው የተበደርኩት”
“መድኃኒቱን ለምን መመለስ ፈለጉ?” ዘንቢል ያንጠለጠሉ ያንዲት ምስኪን እናት ጥያቄ፡፡
በዚህ ጊዜ አስተናጋጁ ጣልቃ ገባ፡፡ “ባህላዊ ሕክምና ብትከታተል ኪስ እንደማታራቁት ገብቷቸው ይሆናላ! ወይ ፀበል ሊያጠምቋት! ወይ . . .”
“ኧይ ልጄ! ጉዳዩን ብታውቀው ኖሮ ያፌዝክበት ምላስህን ታፍርበት ነበር . . .” አሉ እንባ እየተናነቃቸው፡፡
“መድኃኒቱን ምን ላድርገው? ልዋጠው ወይስ ሽንት ቤት ልጨምረው?”
“ለባለቤቴ ነው የምገዛላት ብለው አልነበር? በጠና ታማብኛለች የእድሜዬ ጀምበር እየጠለቀ ባበት ሰዓት ለእህል ያላነሱና ለትምህርት ያልደረሱ ሦስት ልጆች በትናብኝ እንዳትሄድ ፀልይልኝ ብለውኝ አልነበር?”
“ማለቱንስ ብዬህ ነበር ልጄ! . . . ብዬ ነበር”
“እና ሩብ ሰዓት ያህል እንኳን ሳይቆዩ ሃሳብዎን አስሰርዞ የገዙትን መድኃኒት የሚያስመልስ ምን ተአምር ተፈጠረ?! ቅድም የማይመለከተኝን ነገር ሲዘላብዱልኝ ነበር እኮ” አረጋዊው አንገታቸውን ደፉ፡፡ “እኮ ምን ቢፈጠር ነው . . . ?”
“ቤቴ ሳልደርስ ነው አንተ ዘንድ የመጣሁት”
“ለምን?” የሌሎቹ ጥያቄ፡፡
“ሰፈርተኞቼ ደጄ ላይ ሲጯጯሁ አየሁ፡፡ ባቤቴን በህይወቷ ልደርስላት አልቻልኩም!” አሉ አረጋዊው ድምጻቸው እየሻከረ፡፡ እንባቸው እየወረደ፡፡ በመድኃኒት ሻጩ ፊት ላይ ፀፀት ድንጋጤ እየታየ ድፍን መቶ ብር አውጥቶ በሻካራ እጆቻቸው ላይ አኖረው፡፡ ሌሎቹም ኪሶቻቸውን ይፈታትሹ ጀምር፡፡
“ይባርካችሁ ልጆቼ! ከፈን መግዣ ስላልነበረኝ እንጂ . . . ” አንባ ተናነቃቸው፡፡
መንሰቅሰቃቸውን እየቀጠሉ ወጡ፡፡
ፀጥታ!😔😔
👍3
#ፍቅር ነው #የራበኝ
ደህና ነኝ እንዳልል
ደህንነቴ ጠፍቷል ፣
አሞኛል እንዳልል
ይሄው ፊቴ ፈክቷል ።
ሰው ሲያየኝ ጤነኛ ፣
ውስጤ በሽተኛ ፣
ቆይ ምን ብየ ላውራ
ሰሚ ሰው አግኝቼ ፣
በልቤ ጠራ ውስጥ
የትኛውን ትቼ ፣
*
አይቶ በሚፈርድ
ጆሮ ጠቢ ምላስ በሞላበት ሀገር ፣
ለየትኛው ሰሚ
ለየትኛው ሀኪም ህመሜን ልናገር ።
ከማንነት በላይ ፣
ከምንነት በላይ ፣
ምን ቃል ሊተነፈስ ?
በሽፋን መለኪያ
ምን እውነት ሊታፈስ ?
*
ፍቅር ነው የራበኝ..
እሱ ነው ያመመኝ ..
የሀገሬ መሬት ሰው እያካሰሰ ፣
ሰው እያናከሰ፣
የሀገሬ ቋንቋ
ዘር እያስቆጠረ ፣
ክልል እያጠረ ፣
ያዳም የ አብራክ ክፋይ
ሰውነት ቀረና ፣
በጎሳ በብሄር
ታጥሮ ህልውና ፣
በሽብር አይምሮ
ሀገር ይታመሳል ።
ለማይጠቅም አለም
ንጹህ ደም ይፈሳል ።
ክብር የ ሰው ስጋ
በግፍ ይቆረሳል ።
አፍ አየቀደመ
የህሊና ደወል
መሰማት ተስኖት ፣
የአምላክ ቃል ይፈርሳል ።
*
ይሔው ነው ህመሜ
የእድሜያችን ጣሪያ
ሰማኒያ ላይሞላ ፣
በሳር በቅጠሉ
ባፈር ስንባላ ፣
እኔ ነኝ የኔ ነው ፣
ማንነቴ እንትን ነው ፣
የሚል እድር ፈላ ።
በሉ እስኪ ንገሩኝ
ማንነት ምንድን ነው?
ምንነት የቱ ነው ?
*
ሰው ከመባል ወዲያ
ምን ትርጉም ተገኝቶ ?
ከአምላክ ፍጡር ውጭ
ምን ጠላት መጥቶ ?
*
ምንድን ነው ነገሩ ፣
ዝንትአለም መናከስ
ደምበር እያጠሩ ፣
በመግባቢያ ቋንቋ
በትውልድ ቀየ ዘር እየቆጠሩ ፣
ምንድን ነው ?ዘር መቁጠር
ዘር ማሳለይ እንጅ
ሰው ላይ ምን ያደርጋል ፣
ማን በሀሩር ደርቆ
ማን በዝናብ ያድጋል?
*
አመሉ ነው እንጅ ፣
ሞኝነት ነው እንጅ፣
ጥንትም ተፈጥሮውን
ሰው በአምላክ ካመነ፣
ማን ሀባሻን መርጦ
ማን ፈረንጅ ሆነ ?
ከግዜሩ ሆኖ አንጅ
ፍጥረት የተሰጠ ፣
ይሁንልኝ ብሎ
ማን ፆታ መረጠ ።
*
ከአፈር ተፈጥሮ
አፈር የሚሆን ሰው ፣
ከአፈር ጋር ታግሎ
አፈር የሚቆርሰው ፣
ምነው? ይሄ ትውልድ
ከራስ የዘለለ ማስተዋል አነሰው ።
*
ይገርማል ...
በማለዳ ፀሀይ
በምሽት ከዋክብት ቀን እየተዋጀ፣
ህዝቤ አንደጎበጠ
ቅን ሆኖ ቀን ሳያይ ሰማኒያውን ፈጀ ።
ፍቅር ነው የራበኝ ...........
*
03/02/2011
2:00pm
ከ 🔘ሳሙኤል አዳነ🔘
ከቻናሉ ተከታታይ የተላከ
ስለግጥሙ ያሎትን አስተያየት @Sam2127 አድርሱት
ደህና ነኝ እንዳልል
ደህንነቴ ጠፍቷል ፣
አሞኛል እንዳልል
ይሄው ፊቴ ፈክቷል ።
ሰው ሲያየኝ ጤነኛ ፣
ውስጤ በሽተኛ ፣
ቆይ ምን ብየ ላውራ
ሰሚ ሰው አግኝቼ ፣
በልቤ ጠራ ውስጥ
የትኛውን ትቼ ፣
*
አይቶ በሚፈርድ
ጆሮ ጠቢ ምላስ በሞላበት ሀገር ፣
ለየትኛው ሰሚ
ለየትኛው ሀኪም ህመሜን ልናገር ።
ከማንነት በላይ ፣
ከምንነት በላይ ፣
ምን ቃል ሊተነፈስ ?
በሽፋን መለኪያ
ምን እውነት ሊታፈስ ?
*
ፍቅር ነው የራበኝ..
እሱ ነው ያመመኝ ..
የሀገሬ መሬት ሰው እያካሰሰ ፣
ሰው እያናከሰ፣
የሀገሬ ቋንቋ
ዘር እያስቆጠረ ፣
ክልል እያጠረ ፣
ያዳም የ አብራክ ክፋይ
ሰውነት ቀረና ፣
በጎሳ በብሄር
ታጥሮ ህልውና ፣
በሽብር አይምሮ
ሀገር ይታመሳል ።
ለማይጠቅም አለም
ንጹህ ደም ይፈሳል ።
ክብር የ ሰው ስጋ
በግፍ ይቆረሳል ።
አፍ አየቀደመ
የህሊና ደወል
መሰማት ተስኖት ፣
የአምላክ ቃል ይፈርሳል ።
*
ይሔው ነው ህመሜ
የእድሜያችን ጣሪያ
ሰማኒያ ላይሞላ ፣
በሳር በቅጠሉ
ባፈር ስንባላ ፣
እኔ ነኝ የኔ ነው ፣
ማንነቴ እንትን ነው ፣
የሚል እድር ፈላ ።
በሉ እስኪ ንገሩኝ
ማንነት ምንድን ነው?
ምንነት የቱ ነው ?
*
ሰው ከመባል ወዲያ
ምን ትርጉም ተገኝቶ ?
ከአምላክ ፍጡር ውጭ
ምን ጠላት መጥቶ ?
*
ምንድን ነው ነገሩ ፣
ዝንትአለም መናከስ
ደምበር እያጠሩ ፣
በመግባቢያ ቋንቋ
በትውልድ ቀየ ዘር እየቆጠሩ ፣
ምንድን ነው ?ዘር መቁጠር
ዘር ማሳለይ እንጅ
ሰው ላይ ምን ያደርጋል ፣
ማን በሀሩር ደርቆ
ማን በዝናብ ያድጋል?
*
አመሉ ነው እንጅ ፣
ሞኝነት ነው እንጅ፣
ጥንትም ተፈጥሮውን
ሰው በአምላክ ካመነ፣
ማን ሀባሻን መርጦ
ማን ፈረንጅ ሆነ ?
ከግዜሩ ሆኖ አንጅ
ፍጥረት የተሰጠ ፣
ይሁንልኝ ብሎ
ማን ፆታ መረጠ ።
*
ከአፈር ተፈጥሮ
አፈር የሚሆን ሰው ፣
ከአፈር ጋር ታግሎ
አፈር የሚቆርሰው ፣
ምነው? ይሄ ትውልድ
ከራስ የዘለለ ማስተዋል አነሰው ።
*
ይገርማል ...
በማለዳ ፀሀይ
በምሽት ከዋክብት ቀን እየተዋጀ፣
ህዝቤ አንደጎበጠ
ቅን ሆኖ ቀን ሳያይ ሰማኒያውን ፈጀ ።
ፍቅር ነው የራበኝ ...........
*
03/02/2011
2:00pm
ከ 🔘ሳሙኤል አዳነ🔘
ከቻናሉ ተከታታይ የተላከ
ስለግጥሙ ያሎትን አስተያየት @Sam2127 አድርሱት
በዚያ ቀን፣ ልክ የዛሬ 82 ዓመት፣ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም. በተካሄደው ጭፍጨፋ አዲስ አበባና አካባቢዋ ውስጥ ብቻ ወደ 30 ሺህ ኢትዮጵያውያን ተገድለዋል። የየካቲት 12 ሰማዕታት ቀን፣ ዘንድሮ 82ኛ ዓመቱ ላይ ነው። የካቲት 1929 ዓ.ም.የሚያክል ለኢትዮጵያ የመከራና የጽልመት ወራት ኖሮ አያውቁም። በጣም የሚገርመው፣ በዚሁ በወርኃ የካቲት 1888 ዓመተ ምህረትም ከሰባ ሺህ በላይ ወገኖቻችንን መሥዋዕት አድርገናል። ግፈኛው የንጉሥ ኡምቤርቶ ጦር፣ በጄኔራል ባራቴሪ እየተመራ ሃይማኖት ሊቀለብስ፣ መሬት ሊቆርስ፣ ነፃነታችንን ሊገስ መጥቶ ማጭድና ጎራዴ፣ ጦርና ጋሻ የያዙትን በመድፍና በዘመኑ መሳሪያዎች ፈጃቸው።
ከአርባ አንድ ዓመታት በኋላ ተመልሶ ለወረራ የመጣው በማርሻል ሩዶልፍ ግራዚያኒ የሚመራው የፋሺስትም ጦር፣ ከየካቲት 12 ቀን እስከ የካቲት 14 ድረስ ባሉት ሦስት ቀናት ከሠላሳ ሺህ በላይ ሰላማዊ ኢትዮጵያውያንን ገደላቸው።
#የመታሰቢያ #ሐውልታቸው
ሀውልቱ የወራሪው የጣሊያን ወታደሮች በግፍ የጨፈጨፏቸውን 30ሺ ያህል ሰዎች ለመዘከር የቆመ ነው፡፡ ግራዚያኒ ሰራዊቱን እና መኳንንቱን ጠርቶ ፣ ህዝቡን ሰብስቦ የአሁኑ አዲሰ አበባ ዩኒቨርስቲ ቀደም ሲል ገነተ ልዑል በሚል ይታወቅ በነበረው በአፄ ኃይለስላሴ ቤተ መንግስት ውስጥ የተለመደ የእብሪት ንግግሩን በማሰማት ላይ ነበር፡፡ ግራዚያኒን ለመግደል አመቺ ቦታ እና ጊዜ ሲጠባበቁ የነበሩት አብርሐም ደቦጭ እና ሞገስ አሰግዶም የያዙትን ቦምብ አከታትለው ወረወሩበት፤ ግራዚያኒም ቆሰለ፡፡ ከዚያች ቅፅበት በኋላ በማንኛውም ሁኔታ የተገኘ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በግፍ ተጨፈጨፈ፡፡ አዲሰ አበባም በንፁሀን የደም ጎርፍ ተጥለቀለቀች፡፡ በህፃናት ለቅሶ በእናቶች ዋይታ ተዋጠች፡፡ በወቅቱ የተፈጠረው ሁኔታም ኢትዮጵያውያን በድፍረት እና በወኔ ጠላትን እንዲፋለሙ ብርታት ሆናቸው፡፡ እነዚህን ያለርህራሄ የተጨፈጨፉ ንፁሀን ዜጎች ለማሰታወስም ዛሬ በየካቲት 12 ሆስፒታል ፣ በአዲሰ አበባ ዩኒቨርስቲ እና በቀድሞዉ በአንበሳ ግቢ መካከል 6ኪሎ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ የሰማዕታቱ ሃውልት ቆሟል፡፡
በዚህ ሀውልት ቀረፃ ላይ ኢትዮጳያውያን ባለሙያዎችም ተሳትፈዋል፡፡ ሀውልቱ 28 ሜትር ቁመት ያለው ሲሆን ባለ ሶስት ማዕዘንም ነው፡፡ ሀውልቱ የተሰራው በሁለት የዩጎዝላቪያ ዜግነት ያላቸው ባለሙያተኞች ሲሆን በሀውልቱ ላይ ኢትዮጵያውያን በጣሊያን ወታደሮች በግፍ ሲገደሉ የሚያሳዩ ቅርፃ ቅርፆችም ይስተዋላሉ፡፡ ሀውልቱ ከቅርፃ ቅርፆቹ ባሻገር የተለያዩ ፅሁፎችም አሉት፡፡
እባክዎን ካለዎት ጊዜ ላይ ደቂቃዎች ወስደው ይህን ፒቲሽን በመፈረም ለየካቲት 12/1929 ዓ.ም ጭፍጨፋ ሰማእታት ያሎትን አጋርነት ያሳዩ።
ቫቲካንና የጣሊያን መንግስተም ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠይቅና ተገቢውን ካሳ እንዲከፍሉ ያድርጉ።
100,000 ፊርማ ነዉ የሚያስፈልገዉ ግን እስካሁን 6558 ብቻ ነው ማግኘት የተቻለው የሁላችንም ጉዳይ ነው ትንሽ ደቂቃ ወስደን እንፈርም
https://www.gopetition.com/petitions/vatican-apology-for-ethiopian-holocaust.html
#ክብር #ለተሰውት #ሰማዕታት……..!!!
ከአርባ አንድ ዓመታት በኋላ ተመልሶ ለወረራ የመጣው በማርሻል ሩዶልፍ ግራዚያኒ የሚመራው የፋሺስትም ጦር፣ ከየካቲት 12 ቀን እስከ የካቲት 14 ድረስ ባሉት ሦስት ቀናት ከሠላሳ ሺህ በላይ ሰላማዊ ኢትዮጵያውያንን ገደላቸው።
#የመታሰቢያ #ሐውልታቸው
ሀውልቱ የወራሪው የጣሊያን ወታደሮች በግፍ የጨፈጨፏቸውን 30ሺ ያህል ሰዎች ለመዘከር የቆመ ነው፡፡ ግራዚያኒ ሰራዊቱን እና መኳንንቱን ጠርቶ ፣ ህዝቡን ሰብስቦ የአሁኑ አዲሰ አበባ ዩኒቨርስቲ ቀደም ሲል ገነተ ልዑል በሚል ይታወቅ በነበረው በአፄ ኃይለስላሴ ቤተ መንግስት ውስጥ የተለመደ የእብሪት ንግግሩን በማሰማት ላይ ነበር፡፡ ግራዚያኒን ለመግደል አመቺ ቦታ እና ጊዜ ሲጠባበቁ የነበሩት አብርሐም ደቦጭ እና ሞገስ አሰግዶም የያዙትን ቦምብ አከታትለው ወረወሩበት፤ ግራዚያኒም ቆሰለ፡፡ ከዚያች ቅፅበት በኋላ በማንኛውም ሁኔታ የተገኘ ኢትዮጵያዊ ሁሉ በግፍ ተጨፈጨፈ፡፡ አዲሰ አበባም በንፁሀን የደም ጎርፍ ተጥለቀለቀች፡፡ በህፃናት ለቅሶ በእናቶች ዋይታ ተዋጠች፡፡ በወቅቱ የተፈጠረው ሁኔታም ኢትዮጵያውያን በድፍረት እና በወኔ ጠላትን እንዲፋለሙ ብርታት ሆናቸው፡፡ እነዚህን ያለርህራሄ የተጨፈጨፉ ንፁሀን ዜጎች ለማሰታወስም ዛሬ በየካቲት 12 ሆስፒታል ፣ በአዲሰ አበባ ዩኒቨርስቲ እና በቀድሞዉ በአንበሳ ግቢ መካከል 6ኪሎ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ የሰማዕታቱ ሃውልት ቆሟል፡፡
በዚህ ሀውልት ቀረፃ ላይ ኢትዮጳያውያን ባለሙያዎችም ተሳትፈዋል፡፡ ሀውልቱ 28 ሜትር ቁመት ያለው ሲሆን ባለ ሶስት ማዕዘንም ነው፡፡ ሀውልቱ የተሰራው በሁለት የዩጎዝላቪያ ዜግነት ያላቸው ባለሙያተኞች ሲሆን በሀውልቱ ላይ ኢትዮጵያውያን በጣሊያን ወታደሮች በግፍ ሲገደሉ የሚያሳዩ ቅርፃ ቅርፆችም ይስተዋላሉ፡፡ ሀውልቱ ከቅርፃ ቅርፆቹ ባሻገር የተለያዩ ፅሁፎችም አሉት፡፡
እባክዎን ካለዎት ጊዜ ላይ ደቂቃዎች ወስደው ይህን ፒቲሽን በመፈረም ለየካቲት 12/1929 ዓ.ም ጭፍጨፋ ሰማእታት ያሎትን አጋርነት ያሳዩ።
ቫቲካንና የጣሊያን መንግስተም ይፋዊ ይቅርታ እንዲጠይቅና ተገቢውን ካሳ እንዲከፍሉ ያድርጉ።
100,000 ፊርማ ነዉ የሚያስፈልገዉ ግን እስካሁን 6558 ብቻ ነው ማግኘት የተቻለው የሁላችንም ጉዳይ ነው ትንሽ ደቂቃ ወስደን እንፈርም
https://www.gopetition.com/petitions/vatican-apology-for-ethiopian-holocaust.html
#ክብር #ለተሰውት #ሰማዕታት……..!!!
GoPetition
Ethiopian Genocide 1935-1941 and Vatican Complicities
We, the undersigned, appeal to the international community...all Governments, the United Nations, the European Union,…
👍1
#የጀርባ #ነገር
አንድ ጊዜ የመንደራችን ልጅ በምግብ ዝግጅት ተመርቃ እራት ግብዣ ጠራችን .... ሴቱ ሁሉ እራሱን እስኪስት ዘንጦ ይገባል....(ያው ሴቶች ሰንበቴም ቢጠሩ የእራት ልብስ መልበስ ይወዱ የለ) !
ያልተለበሰ አይነት ልብስ የለም የሚበዛው የተራቆተ ነው ! አጭር ቀሚስ ጫፉ መሬትን እንደመንግስተ ሰማየት የናፈቀ ........ደረቱ ተከፍቶ ከግራና ከቀኝ በጡት ማስያዣ አነሳሽነት ደረት ላይ ለአመፅ የተሰበሰበ ጡት .... ከተመልካች አይን ጋር በእትብት የተያያዘ ይመሰል መሸፈን የጠላ እንብርት ..... ብቻ እራት ተባልን እንጅ የተራቆተ ጅስም እነድናይ የተጠራን ነበር የሚመስለው (ለፍትፍት ተጠርተን ፊት ስናይ አመሸን ቢባል ....ሂሂሂ)
አጠገቤ የተቀመጡት ሰውየ ታዲያ መነፅራቸውን እያስተካከሉ አላፊ አግዳሚወቹን እንደፔንዱለም አንገታቸው እስኪቀጭ እየተወዛወዙ ሲያዮ የሜዳ ቴንስ የሚያዩ ይመስሉ ነበር ...
አንዷ በገባች ቁጥር ‹‹በስማም...እንደው እግዜርን ባትፈራ ብርድ አትፈራም ›› ይላሉ
ትንሽ ቆይተው ደግሞ ሌላኛዋን ያዩና‹‹ ትፍ አሁን ይሄ ተገቢ ነው ...እንደፈጠራት እርቃኗን .....›› ይላሉ ግን ምራቃቸውን ሲውጡ በጉሮሯቸው ላይ እንቅርታቸው ሲያወጣና ሲወርድ በግልፅ ይታይ ነበር
በመጨረሻ የሚያምር ረዥም የእራት ቀሚስ የለበሰች ልጅ ገባች.... ሰውየው ደስ አላቸው እስከአንገቷ የሚደርሰው ቀሚስ ከእጆቿ በቀር ሙሉ ነበር .....እንደውም ባለተረከዝ ጫማ ባታደርግ ቀሚሷ መሬት ይነካ ነበር
‹‹ ተባረኪ! እንዲህ ነው ባህላችን ወጋችን ጨዋ ያሳደጋት...እግዜር ለቁም ነገር ያብቃሽ ››.....እያሉ ማሞገሳቸውን ሳይጨርሱ ልጅቱ እኛ በተቀመጥንበት አለፈች .......ሰውየው ድንገት ሙገሳቸውን አቁመው ‹‹ በስመ አብ›› አሉ ከኋላዋ እያፈጠጡባት .... የልጅቱ ጀርባ ከመቀመጫዋ ከፍ ብሎ ጀምሮ ራቁት ነበር ...
‹‹ ጀርባ ሳናጠና እየሾምን . እና እየባረክን እኮ ነው ትውልድና አገር ሆድና ጀርባ እንዲሆን ምናደርገው ›› አሉና እስከመድረሻዋ በአይናቸው ሸኟት ቆንጆዋን !!
🔘አሌክስ🔘
〰አብሮነታችሁን በዚ 👍 አሳዩን〰
አንድ ጊዜ የመንደራችን ልጅ በምግብ ዝግጅት ተመርቃ እራት ግብዣ ጠራችን .... ሴቱ ሁሉ እራሱን እስኪስት ዘንጦ ይገባል....(ያው ሴቶች ሰንበቴም ቢጠሩ የእራት ልብስ መልበስ ይወዱ የለ) !
ያልተለበሰ አይነት ልብስ የለም የሚበዛው የተራቆተ ነው ! አጭር ቀሚስ ጫፉ መሬትን እንደመንግስተ ሰማየት የናፈቀ ........ደረቱ ተከፍቶ ከግራና ከቀኝ በጡት ማስያዣ አነሳሽነት ደረት ላይ ለአመፅ የተሰበሰበ ጡት .... ከተመልካች አይን ጋር በእትብት የተያያዘ ይመሰል መሸፈን የጠላ እንብርት ..... ብቻ እራት ተባልን እንጅ የተራቆተ ጅስም እነድናይ የተጠራን ነበር የሚመስለው (ለፍትፍት ተጠርተን ፊት ስናይ አመሸን ቢባል ....ሂሂሂ)
አጠገቤ የተቀመጡት ሰውየ ታዲያ መነፅራቸውን እያስተካከሉ አላፊ አግዳሚወቹን እንደፔንዱለም አንገታቸው እስኪቀጭ እየተወዛወዙ ሲያዮ የሜዳ ቴንስ የሚያዩ ይመስሉ ነበር ...
አንዷ በገባች ቁጥር ‹‹በስማም...እንደው እግዜርን ባትፈራ ብርድ አትፈራም ›› ይላሉ
ትንሽ ቆይተው ደግሞ ሌላኛዋን ያዩና‹‹ ትፍ አሁን ይሄ ተገቢ ነው ...እንደፈጠራት እርቃኗን .....›› ይላሉ ግን ምራቃቸውን ሲውጡ በጉሮሯቸው ላይ እንቅርታቸው ሲያወጣና ሲወርድ በግልፅ ይታይ ነበር
በመጨረሻ የሚያምር ረዥም የእራት ቀሚስ የለበሰች ልጅ ገባች.... ሰውየው ደስ አላቸው እስከአንገቷ የሚደርሰው ቀሚስ ከእጆቿ በቀር ሙሉ ነበር .....እንደውም ባለተረከዝ ጫማ ባታደርግ ቀሚሷ መሬት ይነካ ነበር
‹‹ ተባረኪ! እንዲህ ነው ባህላችን ወጋችን ጨዋ ያሳደጋት...እግዜር ለቁም ነገር ያብቃሽ ››.....እያሉ ማሞገሳቸውን ሳይጨርሱ ልጅቱ እኛ በተቀመጥንበት አለፈች .......ሰውየው ድንገት ሙገሳቸውን አቁመው ‹‹ በስመ አብ›› አሉ ከኋላዋ እያፈጠጡባት .... የልጅቱ ጀርባ ከመቀመጫዋ ከፍ ብሎ ጀምሮ ራቁት ነበር ...
‹‹ ጀርባ ሳናጠና እየሾምን . እና እየባረክን እኮ ነው ትውልድና አገር ሆድና ጀርባ እንዲሆን ምናደርገው ›› አሉና እስከመድረሻዋ በአይናቸው ሸኟት ቆንጆዋን !!
🔘አሌክስ🔘
〰አብሮነታችሁን በዚ 👍 አሳዩን〰
👍3
#ከንፈር #ግን #ሲገርም !
እኔ የምልሽ ውዴ
የጀነት በር ማለት ከንፈርሽ ነው እንዴ ?
ምናባቴ ልበል .....!
ስትስሚኝ ጊዜ
ፊቴ የነበረው ፎከታም ግድግዳ የት አባቱ ሄደ ?
ውስጤ የተገነባው የጭንቀት ባቢሎን
ከምኔው ተናደ ?
ስትስሚኝ ጊዜ
በሂሊናየ ውስጥ ያንን ሁሉ አበባ
ማን ተክሎት በቀለ ?
ይሄስ ሁሉ ደስታ
ከየት ተጠራርቶ
ውስጤ ተቆለለ ?
ተፈጥሮን ገልብጦ አናቴን በጥብጦ
ፀሃይን በምራብ አወጣት ከንፈርሽ
መገን አሳሳምሽ !!
ብትስሚኝ ጊዜ
ዝሆኖች በረሩ
እባቦች ጋለቡ
በባዶ ልቤ ውስጥ
እልፍ ሰርጎች ገቡ
አይሆንም ያልኩት ቀን
ይሄው ዛሬ ሆነ
እግርሽ እያስቃዠው ልቤ ልብ ሲያልም
ህልሜን ከሃቂቃው ያደበላለቀው
ከንፈር ግን አይገርምም ! ?
እኔ የምልሽ ውዴ
ስንት ጉድ ፀያፍ ቃል
አልፎ የሚወጣው
ይሄን ጉድ ነው እንዴ
ኧረ ጉዴ !
ማጀት ተገን አርጎ
ለፍቅር ባይሳሳም
አሁንም እላለሁ
ሳይሳም ያሳመኝ አገሬው ይሳሳም
🔘አሌክስ አብረሃም🔘
እኔ የምልሽ ውዴ
የጀነት በር ማለት ከንፈርሽ ነው እንዴ ?
ምናባቴ ልበል .....!
ስትስሚኝ ጊዜ
ፊቴ የነበረው ፎከታም ግድግዳ የት አባቱ ሄደ ?
ውስጤ የተገነባው የጭንቀት ባቢሎን
ከምኔው ተናደ ?
ስትስሚኝ ጊዜ
በሂሊናየ ውስጥ ያንን ሁሉ አበባ
ማን ተክሎት በቀለ ?
ይሄስ ሁሉ ደስታ
ከየት ተጠራርቶ
ውስጤ ተቆለለ ?
ተፈጥሮን ገልብጦ አናቴን በጥብጦ
ፀሃይን በምራብ አወጣት ከንፈርሽ
መገን አሳሳምሽ !!
ብትስሚኝ ጊዜ
ዝሆኖች በረሩ
እባቦች ጋለቡ
በባዶ ልቤ ውስጥ
እልፍ ሰርጎች ገቡ
አይሆንም ያልኩት ቀን
ይሄው ዛሬ ሆነ
እግርሽ እያስቃዠው ልቤ ልብ ሲያልም
ህልሜን ከሃቂቃው ያደበላለቀው
ከንፈር ግን አይገርምም ! ?
እኔ የምልሽ ውዴ
ስንት ጉድ ፀያፍ ቃል
አልፎ የሚወጣው
ይሄን ጉድ ነው እንዴ
ኧረ ጉዴ !
ማጀት ተገን አርጎ
ለፍቅር ባይሳሳም
አሁንም እላለሁ
ሳይሳም ያሳመኝ አገሬው ይሳሳም
🔘አሌክስ አብረሃም🔘
👍1
#አይደለም #ምኞቴ
አይደለም ምኞቴ
ለምለም አንገትሽ ላይ : ክንዶቼን መጠምጠም
ዳሌሽ ላይ መንሳፈፍ: ጭንሽ ማሃል መስጠም
እይደለም ምኞቴ
ከንፈርሽን ማለብ
ቀሚስሽን መግለብ
ከገላሽ ቆርሼ :ገላየን መቀለብ
ደረትሽን ማለም
ጡትሽን መሳለም
በቁንጅናሽ ጅረት : ገነቴን ማለምለም
አላማየ አይደለም::
ምኞቴን ልንገርሽ?
ካለሺበት ቦታ: ቀልቤን ማሰማራት
ወትሮ ካንቺ ጋራ: ቡና መጠራራት
ሰላም መገባበዝ: ትዝታ መጋራት
የጨለመ ፊቴን : ባይንሽ ጮራ ማድመቅ
በቃላትሽ መስከን: በሳቅሽ መጠመቅ
በጎ መንፈስሽን :ካይንሽ ላይ መሻማት
ርጋታሽን ማጥመድ : ዝምታሽን መስማት::
ከ🔘በውቄ🔘
አይደለም ምኞቴ
ለምለም አንገትሽ ላይ : ክንዶቼን መጠምጠም
ዳሌሽ ላይ መንሳፈፍ: ጭንሽ ማሃል መስጠም
እይደለም ምኞቴ
ከንፈርሽን ማለብ
ቀሚስሽን መግለብ
ከገላሽ ቆርሼ :ገላየን መቀለብ
ደረትሽን ማለም
ጡትሽን መሳለም
በቁንጅናሽ ጅረት : ገነቴን ማለምለም
አላማየ አይደለም::
ምኞቴን ልንገርሽ?
ካለሺበት ቦታ: ቀልቤን ማሰማራት
ወትሮ ካንቺ ጋራ: ቡና መጠራራት
ሰላም መገባበዝ: ትዝታ መጋራት
የጨለመ ፊቴን : ባይንሽ ጮራ ማድመቅ
በቃላትሽ መስከን: በሳቅሽ መጠመቅ
በጎ መንፈስሽን :ካይንሽ ላይ መሻማት
ርጋታሽን ማጥመድ : ዝምታሽን መስማት::
ከ🔘በውቄ🔘