የ"ቶ" መስቀል
@And_Haymanot
1.ሰባተኛ ሳብዕ ፊደል ናት።ፍጹምነትን ታመላክታለች።
2.ክርስቶስ በቀራኒዮ በመስቀል ላይ መሰቀሉን የምታመለክት ናት።ክርስቶስ ሲሰቀል ፀሐይና ከዋክብት የ"ቶ" ቅርፅ ሰርተው በኢየሩሳሌም አናት ላይ ታይተዋል።
3.ቅዱስ ሚካኤል እና ቅዱስ ገብርኤል በሳጥናኤል ሁለት ጊዜ ከተሸነፉ በኋላ በሶስተኛው የ'ቶ" ቅርፅ በክንፋቸው ተቀርጾላቸው አሸንፈውት ወደ በርባኖስ ወርውረውታል።
4.'ቶ'ን ኢትዮጵያዊያን የህይወት ምልክት አድርገው ይወስዷታል።በአማራ ሕዝብ በተለይም ሴቶች ግምባራቸው ላይ
'ቶ' ፊደል መነቀስ ጥንታዊ ታሪክና ምስጢር አለው።
5.የሰው ልጅ የተፈጠረው በ"ቶ" ቀመር ነው።'ቶ' የሰው ቅርጽ ከላይ ያለውን ክብ ጭንቅላት፣አግድሙ መስመር
እጅን ትወክላለች።የተሰቀለ ሰውንም ትመስላለች።
*"ቶ" በግብፅ የዋሻ ስዕሎች፣በሳባውያን የዋሻ ላይ ስዕሎችና ማህተሞች ላይ ተገኝቷል።'ቶ"በጥንታዊ ግብጽ ሄሮግላፊክ ጽሑፎች ላይ የተለመደ ነው።
*በታሪክ "ቶ" ከክርስቶስ ልደት በፊት ግብጻውያን የአምላክ ምድር የሚሏት ቶርኔተር ወይንም ፑንት ናት።ፑንት
ምድር"ሕብስቲ፥ኽብሲ"የተባሉ በኋላም የሐበሻዎች ምድር ስትሇን የዛሬው ሶማሌላንድ መሆኗ ተረጋግጧል። ሕብስቲ፥ኽብሲ በኋላም ሐበሻዎች ንጉሥ ኤዛና በአስቀረጸው የድንጋይ ላይ ጽሁፍ ስማቸው ይገኛል።
*ፑንት በዕጣን እና በወርቅ ምርቷ ትታወቃለች። ከ2ሺህ ዓመት ቅ.ል.ክ.በቴባድ ከተማ የተሰበሰበ ግብረ ኃይል እና በቴብስ ቤተ መቅደስ ውስጥ በውብ ሁኔታ የተሳለ ስዕል በ1600 ዓመት ቅ.ል.ክ.ከፑንት ዕጣን ለማምጣት ወደ ፑንት ስለአደረጉት ጉዞ በሐማት ሸለቆ ካሉ ፍርስራሾችና አለቶች ላይ
ተቀርጾ ተገኝቷል።የግብፅ ንግሥት ሃትሼፕሰት በቀይ ባሕር በኩል የላከቻቸው መርከቦች በቤተ መቅደሷ ግድግዳ ተስሎ ይታያል።
*በግብፅ 18 ኢትዮጵያዊያን እንደነገሱ ይታወቃል።የኢትዮ-ግብፅ ንጉሥ ታዋቂው ሜምኖን በአቆመው ሐውልት ላይ ጧት ጧት ላይ ፀሐይ ሳይርፍበት የክራር ድምፅ ያሰማ እንደነበረ ሄሮዶቶስ
መዝግቦታል።ክራር ደግሞ የኛ ሀብት ነው።
*ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ቲርሐቅ ኢየሩሳሌም በአሶር ንጉሥ ሰናክሬም ስትወረር ከወታደሮቹ ጋሻ ላይ "ቶ" መስቀል እንዳስቀረጸና ራሱም በ'ቶ' የተሰራ መስቀል ማሰሩን በድንጋይ
ላይ ጽሁፍ ተረጋግጧል።
*በኢየሩሳሌም በደተረገ የአርኪኦሎጂ ቁፋሮ የአካዝ ልጅ ንጉሥ ሕዝቅያስን መንግሥት ምስል ያየዘ ሸክላ የተገኘ ሲሆን በላዩ ላይም የ'ቶ' ፊደል ተቀርጾበት ተገኝቷል።
*በጥቅሉ 'ቶ' ሰው የተፈጠረባት ቀመር፣ፍጹም፣የስቅለት
ተምሳሌት፣ህይወት፣ድል አድራጊነት ምልክት ናት።
በዲ/ን ቤርዚል
@And_Haymanot @And_Haymanot_bot
@And_Haymanot
1.ሰባተኛ ሳብዕ ፊደል ናት።ፍጹምነትን ታመላክታለች።
2.ክርስቶስ በቀራኒዮ በመስቀል ላይ መሰቀሉን የምታመለክት ናት።ክርስቶስ ሲሰቀል ፀሐይና ከዋክብት የ"ቶ" ቅርፅ ሰርተው በኢየሩሳሌም አናት ላይ ታይተዋል።
3.ቅዱስ ሚካኤል እና ቅዱስ ገብርኤል በሳጥናኤል ሁለት ጊዜ ከተሸነፉ በኋላ በሶስተኛው የ'ቶ" ቅርፅ በክንፋቸው ተቀርጾላቸው አሸንፈውት ወደ በርባኖስ ወርውረውታል።
4.'ቶ'ን ኢትዮጵያዊያን የህይወት ምልክት አድርገው ይወስዷታል።በአማራ ሕዝብ በተለይም ሴቶች ግምባራቸው ላይ
'ቶ' ፊደል መነቀስ ጥንታዊ ታሪክና ምስጢር አለው።
5.የሰው ልጅ የተፈጠረው በ"ቶ" ቀመር ነው።'ቶ' የሰው ቅርጽ ከላይ ያለውን ክብ ጭንቅላት፣አግድሙ መስመር
እጅን ትወክላለች።የተሰቀለ ሰውንም ትመስላለች።
*"ቶ" በግብፅ የዋሻ ስዕሎች፣በሳባውያን የዋሻ ላይ ስዕሎችና ማህተሞች ላይ ተገኝቷል።'ቶ"በጥንታዊ ግብጽ ሄሮግላፊክ ጽሑፎች ላይ የተለመደ ነው።
*በታሪክ "ቶ" ከክርስቶስ ልደት በፊት ግብጻውያን የአምላክ ምድር የሚሏት ቶርኔተር ወይንም ፑንት ናት።ፑንት
ምድር"ሕብስቲ፥ኽብሲ"የተባሉ በኋላም የሐበሻዎች ምድር ስትሇን የዛሬው ሶማሌላንድ መሆኗ ተረጋግጧል። ሕብስቲ፥ኽብሲ በኋላም ሐበሻዎች ንጉሥ ኤዛና በአስቀረጸው የድንጋይ ላይ ጽሁፍ ስማቸው ይገኛል።
*ፑንት በዕጣን እና በወርቅ ምርቷ ትታወቃለች። ከ2ሺህ ዓመት ቅ.ል.ክ.በቴባድ ከተማ የተሰበሰበ ግብረ ኃይል እና በቴብስ ቤተ መቅደስ ውስጥ በውብ ሁኔታ የተሳለ ስዕል በ1600 ዓመት ቅ.ል.ክ.ከፑንት ዕጣን ለማምጣት ወደ ፑንት ስለአደረጉት ጉዞ በሐማት ሸለቆ ካሉ ፍርስራሾችና አለቶች ላይ
ተቀርጾ ተገኝቷል።የግብፅ ንግሥት ሃትሼፕሰት በቀይ ባሕር በኩል የላከቻቸው መርከቦች በቤተ መቅደሷ ግድግዳ ተስሎ ይታያል።
*በግብፅ 18 ኢትዮጵያዊያን እንደነገሱ ይታወቃል።የኢትዮ-ግብፅ ንጉሥ ታዋቂው ሜምኖን በአቆመው ሐውልት ላይ ጧት ጧት ላይ ፀሐይ ሳይርፍበት የክራር ድምፅ ያሰማ እንደነበረ ሄሮዶቶስ
መዝግቦታል።ክራር ደግሞ የኛ ሀብት ነው።
*ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ቲርሐቅ ኢየሩሳሌም በአሶር ንጉሥ ሰናክሬም ስትወረር ከወታደሮቹ ጋሻ ላይ "ቶ" መስቀል እንዳስቀረጸና ራሱም በ'ቶ' የተሰራ መስቀል ማሰሩን በድንጋይ
ላይ ጽሁፍ ተረጋግጧል።
*በኢየሩሳሌም በደተረገ የአርኪኦሎጂ ቁፋሮ የአካዝ ልጅ ንጉሥ ሕዝቅያስን መንግሥት ምስል ያየዘ ሸክላ የተገኘ ሲሆን በላዩ ላይም የ'ቶ' ፊደል ተቀርጾበት ተገኝቷል።
*በጥቅሉ 'ቶ' ሰው የተፈጠረባት ቀመር፣ፍጹም፣የስቅለት
ተምሳሌት፣ህይወት፣ድል አድራጊነት ምልክት ናት።
በዲ/ን ቤርዚል
@And_Haymanot @And_Haymanot_bot
ደጅ ጠናሁ ቆይቼ
@And_Haymanot
ደጅ ጠናሁ ቆይቼ ኪዳነ ምህረትን
ተጽናናሁኝ እረሳሁ ሀዘኔን
የአምላክ እናት እመቤታችን
ሞገስ ሆኝኝ ቀሪው ዘመኔን
የመከራው ዘመን አለፈ እንደዋዛ
አንቺን ተጠግቼ የዓለምዋን ቤዛ
የልጅሽ ቸርነት የአንቺም ደግነት
ባርያሽን ሰውረኝ ከአስጨናቂ ሞት
እናቴ ስምሽን ስጠራ
አለፈ ያሁሉ መከራ
እንባዬ በፊትሽ ፈሰሰ
እምዮ በአንቺ ነው የታበሰ
ሰላም ለኪ
ልቤ በአንቺ ፀና ከፍ ከፍም አለ
በጠላቶቼም ላይ አፌ ተናገረ
በማዳንሽ ስራ ባርያሽ ደስ ብሎኛል
የኃያላንን ቀስት ልጅሽ ሰብሮልኛል
እናቴ ስምሽን ስጠራ
አለፈ ያሁሉ መከራ
እንባዬ በፊትሽ ፈሰሰ
እምዮ በአንቺ ነው የታበሰ
ሰላም ለኪ
ደጄ ባዶ ሲሆን ወዳጆቼም ሸሹ
በመርገም ምክአቸው ሊለያዩኝ ሲሹ
እሱ የሰጠኝን እርሱ ወሰደ አልኳቸው
እመቤቴ አለችኝ ብላ አሳፈርኳቸው
እናቴ ስምሽን ስጠራ
አለፈ ያሁሉ መከራ
እንባዬ በፊትሽ ፈሰሰ
እምዮ በአንቺ ነው የታበሰ
ሰላም ለኪ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
@And_Haymanot
ደጅ ጠናሁ ቆይቼ ኪዳነ ምህረትን
ተጽናናሁኝ እረሳሁ ሀዘኔን
የአምላክ እናት እመቤታችን
ሞገስ ሆኝኝ ቀሪው ዘመኔን
የመከራው ዘመን አለፈ እንደዋዛ
አንቺን ተጠግቼ የዓለምዋን ቤዛ
የልጅሽ ቸርነት የአንቺም ደግነት
ባርያሽን ሰውረኝ ከአስጨናቂ ሞት
እናቴ ስምሽን ስጠራ
አለፈ ያሁሉ መከራ
እንባዬ በፊትሽ ፈሰሰ
እምዮ በአንቺ ነው የታበሰ
ሰላም ለኪ
ልቤ በአንቺ ፀና ከፍ ከፍም አለ
በጠላቶቼም ላይ አፌ ተናገረ
በማዳንሽ ስራ ባርያሽ ደስ ብሎኛል
የኃያላንን ቀስት ልጅሽ ሰብሮልኛል
እናቴ ስምሽን ስጠራ
አለፈ ያሁሉ መከራ
እንባዬ በፊትሽ ፈሰሰ
እምዮ በአንቺ ነው የታበሰ
ሰላም ለኪ
ደጄ ባዶ ሲሆን ወዳጆቼም ሸሹ
በመርገም ምክአቸው ሊለያዩኝ ሲሹ
እሱ የሰጠኝን እርሱ ወሰደ አልኳቸው
እመቤቴ አለችኝ ብላ አሳፈርኳቸው
እናቴ ስምሽን ስጠራ
አለፈ ያሁሉ መከራ
እንባዬ በፊትሽ ፈሰሰ
እምዮ በአንቺ ነው የታበሰ
ሰላም ለኪ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ጥያቄ ነው።
*★★*
★ ጦማሩ የተጻፈው ለኦርቶዶክሳውያን
የተዋሕዶ ልጆች ስለሆነጉዳዩ የማይመለከታችሁ የገዳዩ ወሃቢያ
እስላምና የገዳዩ የኤጄቶ ጴንጤ ቡድን አስተያየት ባትሰጡ ይመከራል። ተናግሬያለሁ።
#ETHIOPIA | ~ [ ስለዚህ ጉዳይ መጀመሪያ እስቲ በየቤታችሁ ምከሩበት።]
•••
ኑሮ ተመችቷቸው የሞቀ እንቅልፍ በመተኛት የእርጅና ዘመናቸውን በሙዳየ ምጽዋት በሚገኝ ገንዘብ ፈታ ብለው
የሚኖሩትን አረጋውያኑን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትና የቤተ ክርስቲያኒቱን መሪዎችን ለጊዜው በሞቀ ፍራሻቸው ላይ እንደተኙ ትቶ በየጊዜው በማንም ወጠጤ እሳት የሚለኮስባትን
ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ከአክራሪው የጃዋር መሃመድ የወሃቢያ አክራሪ እስላምና ቡድንና ከአዲሱ አክራሪ የጴንጤ ቡድን የሚከላከላት፣ የሚጠብቃት “ በአግባቡ የሰለጠነ የተዋሕዶ ወታደር“ ወደ ማደራጀቱ ብንሄድ ምን ይመስላችኋል?
•••
መንግሥቱም በውስጡ የጴንጤና የእስላሞች ስብስብ ነው። በዓመት ውስጥ ከ30 በላይ አብያተ ክርስቲያናት ሲነዱ መከላከያው ዳር ቆሞ እንዲያይ ነው የተደረገው። ምክንያቱም
የመከላከያው ሚንስትር ለማ መገርሳ ጴንጤ ነው። ጠቅላዩ ዐቢይ አህመድ ላዩ ጴንጤ ውስጡ አክራሪ እስላም ነው።
ኤታማዦር ሹሙ ድብን ያለ አክራሪ እስላም ነው። እናም መሽኮርመሙን ትተን በጊዜ ለመፍትሄው መዘጋጀት አለብን።
•••
ያለበለዚያ አይናችን እያየ ግሸን ደብረ ከርቤ፣ ቅዱስ ላሊበላ፣ቁልቢ ገብርኤል፣ ሃዋሳ ገብርኤል። ዝቋላና ምድረከብድ አሰቦት ሥላሴም ታሪክ ይሆናሉ። ተናግሬያለሁ አስቡበት። ቅርሶችም
በጊዜ በጠንካራ ምሽጎች ውስጥ ይቀመጡ። ዘመኑ ዳግማዊ
ግራኝ አህመድ ከአክራሪ ጴንጤ ጋር ያልተቀደሰ ጋብቻ የፈጸሙበት ወቅት ነው። እናም እናስብበት።
•••
ቲሸርት የለበሱ ዐማሮች የሚታሰሩበት። ሜንጫ ይዘው የሚፎክሩ የፖሊስ ጥበቃ የሚደረግለት ለምን ይመስልሃል።
ወዳጄ ሃይማኖት ነው። አሳሪዎቹን በደንብ ተመልከታቸው። ሌላ ምንም አይነት ስምም አትስጣቸው። ሃይማኖት ነው።
•••
እነሱ ቤተ ክርስቲያን ያቃጥላሉ። እኛ ከሥር ከሥር እየተከተልን እንገነባለን። እነሱ በኢኮኖሚ ይመነደጋሉ። ባንክ እየዘረፉ ጭምር ይበለፅጋሉ። እናም መንግሥቱ ፀረ ኦርቶዶክስ ነው።
አውሬ ነው። የ666 መልእክተኛ ዘንዶ ነው። ብታምኑም ባታምኑም ወደፊት ኦሮሞው ኦርቶዶክስ፣ ደቡቡ ኦርቶዶክሳዊ፣ጉራጌ ትግሬው፣ ወላይታ ከምባታ፣ ዶርዜው ወዘተ ታራጅ ነው።
ምን አልባት ትግሬ አሁን ስላልተነካ ደስስ ብሎት ተረጋግቶ ተቀምጦ ሊሆን ይችላል። ነገ ግን አክሱም ድረስ ገብተው ሲለጠልጡት ያኔ ነገርየው ይገባዋል።
•••
እስላማዊ ባንክ፣ እስላማዊ ወታደር ሕጋዊ በሆነበት ሃገር የወደፊት ዕጣ ፈንታህን ከአሁኑ ወስን። የሰላሌ ሸዋ ኦሮሞን ቤተ ክርስቲያኑን ኦሮሞ ነህ ብለው ከማቃጠል አልተመለሱለትም።
እናም ወገኔ አስቡበት። በሕጋዊ መንገድ አስቡበት። ይሄ ምክሬ
ነው።
•••
ወዳጄ በብሄራዊ ቲአትር ስታንዳፕ ኮሜዲ የሚሠሩትን የኔታ
እሸቱ አለማየሁንና ወንድሜ ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ከጴንጤዎቹ ከለማ መገርሳና ከዐቢይ አህመድ ጋር ሲያወደለድሉ እያየህ ኦርቶዶክስ ውክልና ያላት መሶልህ አትጃጃል። እነሱ
የራሳቸው ቢዝነስ ላይ ናቸው። እነሱን እያየህ አትጃጃል። ሲቆይ እንደ ማስቲካ እንደሸንኮራም ተመጥጠው አገልግሎታቸውን ሲጨርሱ የሚጣሉ ናቸው። እናም ዳኒንና የኔታን እያየን
አንጃጃል።
••• ★ “ስለዚህ፦ አንተ የምትተኛ ንቃ ።” ኤፌ 5፥14
•••
ሻሎም ! ሰላም !
ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ሐምሌ 17/2011 ዓም
ከራየን ወንዝ ዳር።
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
*★★*
★ ጦማሩ የተጻፈው ለኦርቶዶክሳውያን
የተዋሕዶ ልጆች ስለሆነጉዳዩ የማይመለከታችሁ የገዳዩ ወሃቢያ
እስላምና የገዳዩ የኤጄቶ ጴንጤ ቡድን አስተያየት ባትሰጡ ይመከራል። ተናግሬያለሁ።
#ETHIOPIA | ~ [ ስለዚህ ጉዳይ መጀመሪያ እስቲ በየቤታችሁ ምከሩበት።]
•••
ኑሮ ተመችቷቸው የሞቀ እንቅልፍ በመተኛት የእርጅና ዘመናቸውን በሙዳየ ምጽዋት በሚገኝ ገንዘብ ፈታ ብለው
የሚኖሩትን አረጋውያኑን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትና የቤተ ክርስቲያኒቱን መሪዎችን ለጊዜው በሞቀ ፍራሻቸው ላይ እንደተኙ ትቶ በየጊዜው በማንም ወጠጤ እሳት የሚለኮስባትን
ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ከአክራሪው የጃዋር መሃመድ የወሃቢያ አክራሪ እስላምና ቡድንና ከአዲሱ አክራሪ የጴንጤ ቡድን የሚከላከላት፣ የሚጠብቃት “ በአግባቡ የሰለጠነ የተዋሕዶ ወታደር“ ወደ ማደራጀቱ ብንሄድ ምን ይመስላችኋል?
•••
መንግሥቱም በውስጡ የጴንጤና የእስላሞች ስብስብ ነው። በዓመት ውስጥ ከ30 በላይ አብያተ ክርስቲያናት ሲነዱ መከላከያው ዳር ቆሞ እንዲያይ ነው የተደረገው። ምክንያቱም
የመከላከያው ሚንስትር ለማ መገርሳ ጴንጤ ነው። ጠቅላዩ ዐቢይ አህመድ ላዩ ጴንጤ ውስጡ አክራሪ እስላም ነው።
ኤታማዦር ሹሙ ድብን ያለ አክራሪ እስላም ነው። እናም መሽኮርመሙን ትተን በጊዜ ለመፍትሄው መዘጋጀት አለብን።
•••
ያለበለዚያ አይናችን እያየ ግሸን ደብረ ከርቤ፣ ቅዱስ ላሊበላ፣ቁልቢ ገብርኤል፣ ሃዋሳ ገብርኤል። ዝቋላና ምድረከብድ አሰቦት ሥላሴም ታሪክ ይሆናሉ። ተናግሬያለሁ አስቡበት። ቅርሶችም
በጊዜ በጠንካራ ምሽጎች ውስጥ ይቀመጡ። ዘመኑ ዳግማዊ
ግራኝ አህመድ ከአክራሪ ጴንጤ ጋር ያልተቀደሰ ጋብቻ የፈጸሙበት ወቅት ነው። እናም እናስብበት።
•••
ቲሸርት የለበሱ ዐማሮች የሚታሰሩበት። ሜንጫ ይዘው የሚፎክሩ የፖሊስ ጥበቃ የሚደረግለት ለምን ይመስልሃል።
ወዳጄ ሃይማኖት ነው። አሳሪዎቹን በደንብ ተመልከታቸው። ሌላ ምንም አይነት ስምም አትስጣቸው። ሃይማኖት ነው።
•••
እነሱ ቤተ ክርስቲያን ያቃጥላሉ። እኛ ከሥር ከሥር እየተከተልን እንገነባለን። እነሱ በኢኮኖሚ ይመነደጋሉ። ባንክ እየዘረፉ ጭምር ይበለፅጋሉ። እናም መንግሥቱ ፀረ ኦርቶዶክስ ነው።
አውሬ ነው። የ666 መልእክተኛ ዘንዶ ነው። ብታምኑም ባታምኑም ወደፊት ኦሮሞው ኦርቶዶክስ፣ ደቡቡ ኦርቶዶክሳዊ፣ጉራጌ ትግሬው፣ ወላይታ ከምባታ፣ ዶርዜው ወዘተ ታራጅ ነው።
ምን አልባት ትግሬ አሁን ስላልተነካ ደስስ ብሎት ተረጋግቶ ተቀምጦ ሊሆን ይችላል። ነገ ግን አክሱም ድረስ ገብተው ሲለጠልጡት ያኔ ነገርየው ይገባዋል።
•••
እስላማዊ ባንክ፣ እስላማዊ ወታደር ሕጋዊ በሆነበት ሃገር የወደፊት ዕጣ ፈንታህን ከአሁኑ ወስን። የሰላሌ ሸዋ ኦሮሞን ቤተ ክርስቲያኑን ኦሮሞ ነህ ብለው ከማቃጠል አልተመለሱለትም።
እናም ወገኔ አስቡበት። በሕጋዊ መንገድ አስቡበት። ይሄ ምክሬ
ነው።
•••
ወዳጄ በብሄራዊ ቲአትር ስታንዳፕ ኮሜዲ የሚሠሩትን የኔታ
እሸቱ አለማየሁንና ወንድሜ ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ከጴንጤዎቹ ከለማ መገርሳና ከዐቢይ አህመድ ጋር ሲያወደለድሉ እያየህ ኦርቶዶክስ ውክልና ያላት መሶልህ አትጃጃል። እነሱ
የራሳቸው ቢዝነስ ላይ ናቸው። እነሱን እያየህ አትጃጃል። ሲቆይ እንደ ማስቲካ እንደሸንኮራም ተመጥጠው አገልግሎታቸውን ሲጨርሱ የሚጣሉ ናቸው። እናም ዳኒንና የኔታን እያየን
አንጃጃል።
••• ★ “ስለዚህ፦ አንተ የምትተኛ ንቃ ።” ኤፌ 5፥14
•••
ሻሎም ! ሰላም !
ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ሐምሌ 17/2011 ዓም
ከራየን ወንዝ ዳር።
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
፩ ሃይማኖት
ጥያቄ ነው። *★★* ★ ጦማሩ የተጻፈው ለኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች ስለሆነጉዳዩ የማይመለከታችሁ የገዳዩ ወሃቢያ እስላምና የገዳዩ የኤጄቶ ጴንጤ ቡድን አስተያየት ባትሰጡ ይመከራል። ተናግሬያለሁ። #ETHIOPIA | ~ [ ስለዚህ ጉዳይ መጀመሪያ እስቲ በየቤታችሁ ምከሩበት።] ••• ኑሮ ተመችቷቸው የሞቀ እንቅልፍ በመተኛት የእርጅና ዘመናቸውን በሙዳየ ምጽዋት በሚገኝ ገንዘብ ፈታ ብለው የሚኖሩትን አረጋውያኑን…
ሰላም ተወዳጆች ከላይ የለቀቅነው የዘመድኩን በቀለን ሃሳብ ሙሉ ለሙሉ የሚገልጽ ነው። መልዕክቱም ከናንተው የደረሰን በመሆኑ ነው የተለቀቀው።
#ከምንም_በላይ_ለቤተክርስቲያን_እንቁም የሚለውን መልዕክት ትኩረት ስጡበት እያልን በፅሑፉ ላሉት አላስፈላጊ ቃላት በቻናላችን ሥም ይቅርታን እንጠይቃለን🙏
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
#ከምንም_በላይ_ለቤተክርስቲያን_እንቁም የሚለውን መልዕክት ትኩረት ስጡበት እያልን በፅሑፉ ላሉት አላስፈላጊ ቃላት በቻናላችን ሥም ይቅርታን እንጠይቃለን🙏
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
Forwarded from መሠረተ ያሬድ ሰ/ት/ቤት ዘአሣሣ
ሐምሌ 19 ዕለት
@Meserete_Yared_Asasa
❖የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል አምላካቸው ክርስቶስን አንክድም በማለታቸው የፈላ ጋን ውስጥ የተወረወሩት ቅዱስ ቂርቆስና እናቱን ቅድስት ኢየሉጣ ተራድቶ ያዳነበት በዓል ነው።
❖ ይኸውም የቅድስት ኢየሉጣን ልጅ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ከሐዲው መኰንኑ ይዞ “ስምኽ ማነው” ብሎ በጠየቀው ጊዜ “ነቅዕ ዘእምዐዘቅት ንጹሕ ወእማይ ዘኢይማስን ክርስቲያን ስምየ” (ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውሃ የተገኘ ስሜ ክርስቲያን ነው ሞክሼ ስም ከፈለግኽ ደግሞ እናቴ የሠየመችኝ ቂርቆስ ነው) በማለት ክርስትናው መመኪያው የኾነው ይኽ ቅዱስ ሕፃን መለሰለት፡፡
❖ መኰንኑም ለአማልክት ከሠዋኽ ስታድግ እሾምኻለኊ ክርስቶስን ካድ ቢለው ቅዱስ ቂርቆስ ግን “የሰይጣን መልእክተኛ ለእውነትም ጠላቷ የኾንኽ ከእኔ ራቅ” አለው፡፡ መኰንኑም ይኽነን ሰምቶ በመቈጣት የቅዱስ ቂርቆስ ደሙ እንደ ውሃ እስኪፈስስ ድረስ እንዲጨምቁት እና ጨውና ሰናፍጭ በኹለቱ የአፍንጮቹ ቀዳዳዎች እንዲጨመሩ ቢያደርግበት፤ በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የጠነከረው ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን “ትእዛዝኽ ለጒረሮዬ ጣፋጭ ኾነ ከማርና ከሥኳርም ለአፌ ጣመኝ” እያለ አምላኩ ክርስቶስን አመሰገነ፡፡
❖ መኰንኑ በዚኽ ሳያበቃ እናትና ልጇ በክፉ አሟሟት እንዲሞቱ በማሰብ የረዘሙና የተሳሉ በእሳትም እንደ ፍም የጋሉ ዐሥራ አራት የብረት ችንካሮች እንዲመጡ አስደርጎ ሰባቱ በእናቱ አካላት፤ ሰባቱ በሕፃኑ ሰውነት ላይ እንዲሰካ ቢያስደርግም በጌታችን ትእዛዝ ግለቱ ጠፍቶ እንደ በረዶ በመቀዝቀዝ ምንም ምን ጒዳት ሳያደርስባቸው ቀረ፡፡
❖ ከዚያም ወደ ወኅኒ ቤት እንዲገቡና እንዲዘጋባቸው አደረገ፤ ከዚያም ሕፃኑና እናቱ የሚሠቃዩበት ታላቅ መንኰራኲር ለ፵ ቀናት ተሠርቶ ካለቀ በኋላ ኹለቱንም በደራቁ ራሳቸውን ላጭተው የእሳት ፍሕምን በላያቸው ላይ ቢያደርጉም የእግዚአብሔር መልአክ ሥቃዮቹን ኹሉ ከእነርሱ አራቀላቸው፡፡
❖ የሕፃኑ ምላስ እንዲቈረጥ አዝዞ ቢያስቈርጠውም ጌታችን ምላሱን መልሶለታል፡፡ “ወአዘዘ ካዕበ ያፍልሑ ማየ ውስተ ጽሕርት ዐቢይ ወይደይዎሙ ለሕፃን ቂርቆስ ወለእሙ ኢየሉጣ” ይላል በታላቅ ጋን ውሃ አፍልተው ሕፃኑንና እናቱን እንዲጨምሯቸው ሲያዝዝ ከሚፍለቀለቀው ውሃ ድምፅ የተነሣ ለጊዜው እናቱ ፍርሀት ሥጋዊ ቢያገኛትም ልጇም ወደ ጌታችን በጸለየላት ጊዜ ፍርሃቱ ርቆላት ከልጇ ጋር ስትገባ መልአከ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ውሃውን አቀዝቅዞ ሐምሌ ፲፱ አውጥቷቸዋል፡፡
❖ በመጨረሻም የሰማዕትነትን አክሊል የሚያገኝባት ጊዜ ሲደርስ ጌታችን ተገልጾለት ስሙን ለሚጠራ ኹሉ ቃል ኪዳንን ከሰጠው በኋላ ሥጋኽን በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርልኻለኊ አለው፤ ይኽነን በሰማ ጊዜ በእጅጉ ተደሰተ፤ ከዚኽም በኋላ ጥር ፲፭ በሌሊቱ እኲሌታ ከእናቱ ጋር አንገቱ ተቈረጠ የሰማዕትነትን ክብር ተቀዳጅተዋል።
✞ የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ረድኤት፣ በረከትና ምልጃ አይለየን✞✞✞ አሜን✞
@Meserete_Yared_Asasa
@Meserete_Yared_Asasa
👉 የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ከ አንቀጸ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት የ Facebook ገጽ የተወሰደ
@Meserete_Yared_Asasa
❖የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል አምላካቸው ክርስቶስን አንክድም በማለታቸው የፈላ ጋን ውስጥ የተወረወሩት ቅዱስ ቂርቆስና እናቱን ቅድስት ኢየሉጣ ተራድቶ ያዳነበት በዓል ነው።
❖ ይኸውም የቅድስት ኢየሉጣን ልጅ ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ከሐዲው መኰንኑ ይዞ “ስምኽ ማነው” ብሎ በጠየቀው ጊዜ “ነቅዕ ዘእምዐዘቅት ንጹሕ ወእማይ ዘኢይማስን ክርስቲያን ስምየ” (ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውሃ የተገኘ ስሜ ክርስቲያን ነው ሞክሼ ስም ከፈለግኽ ደግሞ እናቴ የሠየመችኝ ቂርቆስ ነው) በማለት ክርስትናው መመኪያው የኾነው ይኽ ቅዱስ ሕፃን መለሰለት፡፡
❖ መኰንኑም ለአማልክት ከሠዋኽ ስታድግ እሾምኻለኊ ክርስቶስን ካድ ቢለው ቅዱስ ቂርቆስ ግን “የሰይጣን መልእክተኛ ለእውነትም ጠላቷ የኾንኽ ከእኔ ራቅ” አለው፡፡ መኰንኑም ይኽነን ሰምቶ በመቈጣት የቅዱስ ቂርቆስ ደሙ እንደ ውሃ እስኪፈስስ ድረስ እንዲጨምቁት እና ጨውና ሰናፍጭ በኹለቱ የአፍንጮቹ ቀዳዳዎች እንዲጨመሩ ቢያደርግበት፤ በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የጠነከረው ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን “ትእዛዝኽ ለጒረሮዬ ጣፋጭ ኾነ ከማርና ከሥኳርም ለአፌ ጣመኝ” እያለ አምላኩ ክርስቶስን አመሰገነ፡፡
❖ መኰንኑ በዚኽ ሳያበቃ እናትና ልጇ በክፉ አሟሟት እንዲሞቱ በማሰብ የረዘሙና የተሳሉ በእሳትም እንደ ፍም የጋሉ ዐሥራ አራት የብረት ችንካሮች እንዲመጡ አስደርጎ ሰባቱ በእናቱ አካላት፤ ሰባቱ በሕፃኑ ሰውነት ላይ እንዲሰካ ቢያስደርግም በጌታችን ትእዛዝ ግለቱ ጠፍቶ እንደ በረዶ በመቀዝቀዝ ምንም ምን ጒዳት ሳያደርስባቸው ቀረ፡፡
❖ ከዚያም ወደ ወኅኒ ቤት እንዲገቡና እንዲዘጋባቸው አደረገ፤ ከዚያም ሕፃኑና እናቱ የሚሠቃዩበት ታላቅ መንኰራኲር ለ፵ ቀናት ተሠርቶ ካለቀ በኋላ ኹለቱንም በደራቁ ራሳቸውን ላጭተው የእሳት ፍሕምን በላያቸው ላይ ቢያደርጉም የእግዚአብሔር መልአክ ሥቃዮቹን ኹሉ ከእነርሱ አራቀላቸው፡፡
❖ የሕፃኑ ምላስ እንዲቈረጥ አዝዞ ቢያስቈርጠውም ጌታችን ምላሱን መልሶለታል፡፡ “ወአዘዘ ካዕበ ያፍልሑ ማየ ውስተ ጽሕርት ዐቢይ ወይደይዎሙ ለሕፃን ቂርቆስ ወለእሙ ኢየሉጣ” ይላል በታላቅ ጋን ውሃ አፍልተው ሕፃኑንና እናቱን እንዲጨምሯቸው ሲያዝዝ ከሚፍለቀለቀው ውሃ ድምፅ የተነሣ ለጊዜው እናቱ ፍርሀት ሥጋዊ ቢያገኛትም ልጇም ወደ ጌታችን በጸለየላት ጊዜ ፍርሃቱ ርቆላት ከልጇ ጋር ስትገባ መልአከ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ወርዶ ውሃውን አቀዝቅዞ ሐምሌ ፲፱ አውጥቷቸዋል፡፡
❖ በመጨረሻም የሰማዕትነትን አክሊል የሚያገኝባት ጊዜ ሲደርስ ጌታችን ተገልጾለት ስሙን ለሚጠራ ኹሉ ቃል ኪዳንን ከሰጠው በኋላ ሥጋኽን በኤልያስ ሠረገላ ላይ አኖርልኻለኊ አለው፤ ይኽነን በሰማ ጊዜ በእጅጉ ተደሰተ፤ ከዚኽም በኋላ ጥር ፲፭ በሌሊቱ እኲሌታ ከእናቱ ጋር አንገቱ ተቈረጠ የሰማዕትነትን ክብር ተቀዳጅተዋል።
✞ የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ረድኤት፣ በረከትና ምልጃ አይለየን✞✞✞ አሜን✞
@Meserete_Yared_Asasa
@Meserete_Yared_Asasa
👉 የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤ/ከ አንቀጸ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት የ Facebook ገጽ የተወሰደ
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
ምንፍቅና በቅዱስ ቃሉ ሲፋቅ!
#ስግደት_ለመላእክት
👉ኢያሱ ለመልአኩ ሰገደ
👉ዮሀንስ ስለምን አትስገድልኝ ተባለ?
✍ @And_Haymanot
መናፍቃን የሚያነሱትን ጥያቄ ቀለል ባለ
መንገድ ስንመልስ!!
👉1. የእስራኤል መስፍን የሆነው ኢያሱ “የምታመልኩትን ዛሬ ምረጡ እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን” ብሎ
እንዳላለ !!መጽ.ኢያሱ 5ቁ13“……እርሱም አይደለሁም እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኘ አሁን መጥቻለሁ አለ. ኢያሱም ‘ወደ ምድር በግንባሩ ተደፍቶ ሰገደና’ ጌታየ ለባሪያው
የሚነግረው ምንድር ነው አለው. የእግዚአብሔር ሰራዊት አለቃ ኢያሱን አንተ የቆምህበት ስፍራ የተቀደሰ ነውና ጫማህን አውልቅ አለው” የምታመልኩትን ምረጡ ያለው ኢያሱ ለመልአኩ በስህተት ሰገደ ብለን አናምንም!!!ለመልአኩ በግንባሩ መደፋቱም መልአኩን ለማክበር እንጅ ለማምለክ እንዳልሆነ እናውቃለን!!!ዛሬም ኢያሱን ተከትለን እንዲሁ ስናደርግ አምላክን ከመልአክ ለይተን ነው!!!የአንዱን ላንዱ ሳንሰጥ፣ሳንቀላቅል!!
👉2. ወንጌላዊው ዮሐንስ፡በራእይ 19ቁ10 እና 22ቁ8 ….በመልአኩ እግር ፊት ሰገድኩለት እሱ ግን አትስገድልኝ፣ ሁለታችንም የእግዚአብሔር ባሪያዎች ነን አለኝ….የሚለውን ጥሬ ንባብ ለመላእክት ስግደት እንደማይገባ ለማሳየት መናፍቃን ያቀርባሉ!!!ተሳስተዋል!!
✔️(ሀ)ወንጌሉን፣መልእክታቱን፣ራእዩን የጻፈው ዮሐንስ ለመልአኩ የሰገደው ባለማወቅ ነው ማለት ይሄን ሁሉ የጻፈውን ዮሐንስ ለማን መስገድ እንዳለበት እንኩዋ የማያውቅ አዲስ ምእመን ማስመሰል ነው!!!ዮሐንስ የሰገደው መስገድ ስለሚገባው ነው!!!
✔️(ለ)መልአኩ አትስገድልኝ ያለው ስግደት የበላይና የበታች መገለጫ እንደመሆኑ መጠን ዮሐንስ በክብር እደተስተካከለው አውቆ ነው!!!ለትህትና!!!
✔️(ሐ)መልአኩ በምእራፍ 19 ቁ 10 እንደተገለጸው ዮሐንስን አትስገድልኝ ቢለውም ዮሐንስ ግን በምእራፍ 22 ቁ 8’ም ዳግመኛ ለመልአኩ ሲሰግድ እናገኘዋለን!!ዮሐንስን ያህል የጌታ
ወዳጅ(ፍቁረ-እግዚእ) ተብሎ የተነገረለትና በጰራቅሊጦስ
መንፈስቅዱስ የወረደበት አባት ለመልአክ መስገድ ስህተት
መሆኑ ጠፍቶ፣ እየተነገረው ጭምር ከአንዴም ሁለቴ ሰገደ ማለት ቅድስናውን መጠራጠር ይሆናል!!!ስለሆነም መልአኩ
አትስገድልኝ ያለው ለትህትና ነው ስንል እናምናለን!!!
👉3. የሞቱ ቅዱሳን ከእኛ ጋር የሚያገናኛቸው ነገር የለም የምትሉ ሰዎች አላችሁ!!!እሺ ቅዱሳኑስ ይሁኑ ታዲያ መላእክት እኮ አይሞቱም!!!ስለታናናሾች የአብን ፊት ያያሉ እንጅ-በማቴ 18ቁ 10 እንደተጻፈው!በዘካርያስ 1 ቁ 13 የመልአኩ ምልጃ እንዲህ
ተጽፉዋል “አቤቱ የሰራዊት ጌታ ሆይ እነዚህ 70 አመት የተቆጣሀቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተማዎች የማትምራቸው እስከመቼ ነው አለው እግዚአብሔርም መልሶ ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረው መልአክ በመልካምና በሚያጽናና ቃል ተናገረው” ታዲያ ሳንለምነው እንዲህ የሚማልድልን መልአክ ብንለምነውማ ምን ያህል ይማልድልን?ሰአሉ ለነ ሚካኤል ወገብርኤል እንበላቸውማ!!!
👉4.የሞቱ ቅዱሳን በክርስቶስ ህያው ስለሆኑ ከእኛ ጋር በመንፈስ
እንደሚገናኙ ደግሞ ይሄው!!!የሞቱ ቅዱሳን “እግዚአብሔር አምላካቸው ተብሎ ሊጠራ በእነሱ እንደማያፍር” በዕብ 11 ቁ 16 ተጽፉዋል!!!የሞቱ ቅዱሳን አላዋቂዎች ሳይሆኑ ወደፍጹምነት የተሸጋገሩ ‘ፍጹማን’ መሆናቸው በዕብ 12 ቁ 22 ሰፍሮልናል!!! ጌታም ከአመታት በፊት በሞት የተለዩትን አብርሃምን፣ይስሀቅንና
ያዕቆብን ጠቅሶ “የህያዋን አምላክ ነኝ” ሲል በማቴ 22 ቁ 32 ገልጹዋል!!!ጌታችን በስጋ ስለሞተው አብርሃም በዮሀንስ 8 ቁ56 ሲናገር፡ “አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሀሴትን አደረገ፤አየም ደስ አለው” ይላል!!!በአጸደ ነፍስ ያለው አብርሃም የጌታን ቀን አይቶ የተደሰተው በሰማይ ያሉ ቅዱሳን በምድር ካለነው ጋር ህብረት ስላላቸው ነው!! ዮሐንስ በራዕዩ ምዕራፍ 8 ቁ 3 “የዕጣኑ ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚብሔር ፊት ወጣ” ይለናል!!መላእክት ጸሎታችንን ያሳርጋሉ!!!አእርጉ ጸሎተነ የምንላቸውም ለዚሁ ነው-እንደ ቅ/ያሬድ-እንደ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ!!ሙሴስ በዘጸአት 32 ቁ 13 “በራስህ የማልህላቸውን ባሪያዎችህን አብርሃምን፣ይስሀቅንና እስራኤልን አስብ” ብሎ በአጸደነፍስ ነፍስ ባሉ ቅዱሳን ስም ጌታውን ሲማጸን ከሞቱ ቅዱሳን ህብረት ስላለን አይደለምን?ነው እንጅ!!!
👉5. ይሄን ሁሉ ስንል ባለቤቱን ረስተን አይደለም!!!በቀጥታም እሱን ማረን እንለዋለን-እግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ በምህላ- መሀረነ አብ በማስታኮት!!!ስማን፣ተማለደን፣ታረቀን እንለዋለን!!! ግን እንደሌሎቹ አማልደን አንለውም!!!ሌሎቹ የሚያማልደን ጌታ ነው እያሉ ቤዛነቱን እንደአማላጅነት ስለሚወስዱት ነው እኛ ቅዱሳንን አማልዱን ስንል አምላክ ያደረግናቸው የሚመስላቸው!!! አምላካችን አንድ ነው!!!የሃይማኖታችን መሰረትም እሱ-ለዚህም ነው ሰማይንና ምድርን በፈጠረ በአንድ አምላክ እናምናለን ስንል የሃይማኖት ጸሎታችንን የምንጀምረው!!!
ይቆየን
#ኦርቶዶክሳዊ_ምላሾች_እና_መረጃ_ብቻ_የሚቀርቡበት
👇👇👇
✍ አንድ ሃይማኖት
`ተዋህዶ´´´
@And_Haymanot
JOIN
@And_Haymanot
@And_Haymanot
~~~Share~~~
@And_Haymanot
@And_Haymanot
~~~JoIN~~~
@And_Haymanot
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መልስ አላት
@And_Haymanot
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡
#ስግደት_ለመላእክት
👉ኢያሱ ለመልአኩ ሰገደ
👉ዮሀንስ ስለምን አትስገድልኝ ተባለ?
✍ @And_Haymanot
መናፍቃን የሚያነሱትን ጥያቄ ቀለል ባለ
መንገድ ስንመልስ!!
👉1. የእስራኤል መስፍን የሆነው ኢያሱ “የምታመልኩትን ዛሬ ምረጡ እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን” ብሎ
እንዳላለ !!መጽ.ኢያሱ 5ቁ13“……እርሱም አይደለሁም እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኘ አሁን መጥቻለሁ አለ. ኢያሱም ‘ወደ ምድር በግንባሩ ተደፍቶ ሰገደና’ ጌታየ ለባሪያው
የሚነግረው ምንድር ነው አለው. የእግዚአብሔር ሰራዊት አለቃ ኢያሱን አንተ የቆምህበት ስፍራ የተቀደሰ ነውና ጫማህን አውልቅ አለው” የምታመልኩትን ምረጡ ያለው ኢያሱ ለመልአኩ በስህተት ሰገደ ብለን አናምንም!!!ለመልአኩ በግንባሩ መደፋቱም መልአኩን ለማክበር እንጅ ለማምለክ እንዳልሆነ እናውቃለን!!!ዛሬም ኢያሱን ተከትለን እንዲሁ ስናደርግ አምላክን ከመልአክ ለይተን ነው!!!የአንዱን ላንዱ ሳንሰጥ፣ሳንቀላቅል!!
👉2. ወንጌላዊው ዮሐንስ፡በራእይ 19ቁ10 እና 22ቁ8 ….በመልአኩ እግር ፊት ሰገድኩለት እሱ ግን አትስገድልኝ፣ ሁለታችንም የእግዚአብሔር ባሪያዎች ነን አለኝ….የሚለውን ጥሬ ንባብ ለመላእክት ስግደት እንደማይገባ ለማሳየት መናፍቃን ያቀርባሉ!!!ተሳስተዋል!!
✔️(ሀ)ወንጌሉን፣መልእክታቱን፣ራእዩን የጻፈው ዮሐንስ ለመልአኩ የሰገደው ባለማወቅ ነው ማለት ይሄን ሁሉ የጻፈውን ዮሐንስ ለማን መስገድ እንዳለበት እንኩዋ የማያውቅ አዲስ ምእመን ማስመሰል ነው!!!ዮሐንስ የሰገደው መስገድ ስለሚገባው ነው!!!
✔️(ለ)መልአኩ አትስገድልኝ ያለው ስግደት የበላይና የበታች መገለጫ እንደመሆኑ መጠን ዮሐንስ በክብር እደተስተካከለው አውቆ ነው!!!ለትህትና!!!
✔️(ሐ)መልአኩ በምእራፍ 19 ቁ 10 እንደተገለጸው ዮሐንስን አትስገድልኝ ቢለውም ዮሐንስ ግን በምእራፍ 22 ቁ 8’ም ዳግመኛ ለመልአኩ ሲሰግድ እናገኘዋለን!!ዮሐንስን ያህል የጌታ
ወዳጅ(ፍቁረ-እግዚእ) ተብሎ የተነገረለትና በጰራቅሊጦስ
መንፈስቅዱስ የወረደበት አባት ለመልአክ መስገድ ስህተት
መሆኑ ጠፍቶ፣ እየተነገረው ጭምር ከአንዴም ሁለቴ ሰገደ ማለት ቅድስናውን መጠራጠር ይሆናል!!!ስለሆነም መልአኩ
አትስገድልኝ ያለው ለትህትና ነው ስንል እናምናለን!!!
👉3. የሞቱ ቅዱሳን ከእኛ ጋር የሚያገናኛቸው ነገር የለም የምትሉ ሰዎች አላችሁ!!!እሺ ቅዱሳኑስ ይሁኑ ታዲያ መላእክት እኮ አይሞቱም!!!ስለታናናሾች የአብን ፊት ያያሉ እንጅ-በማቴ 18ቁ 10 እንደተጻፈው!በዘካርያስ 1 ቁ 13 የመልአኩ ምልጃ እንዲህ
ተጽፉዋል “አቤቱ የሰራዊት ጌታ ሆይ እነዚህ 70 አመት የተቆጣሀቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተማዎች የማትምራቸው እስከመቼ ነው አለው እግዚአብሔርም መልሶ ከእኔ ጋር ይነጋገር ለነበረው መልአክ በመልካምና በሚያጽናና ቃል ተናገረው” ታዲያ ሳንለምነው እንዲህ የሚማልድልን መልአክ ብንለምነውማ ምን ያህል ይማልድልን?ሰአሉ ለነ ሚካኤል ወገብርኤል እንበላቸውማ!!!
👉4.የሞቱ ቅዱሳን በክርስቶስ ህያው ስለሆኑ ከእኛ ጋር በመንፈስ
እንደሚገናኙ ደግሞ ይሄው!!!የሞቱ ቅዱሳን “እግዚአብሔር አምላካቸው ተብሎ ሊጠራ በእነሱ እንደማያፍር” በዕብ 11 ቁ 16 ተጽፉዋል!!!የሞቱ ቅዱሳን አላዋቂዎች ሳይሆኑ ወደፍጹምነት የተሸጋገሩ ‘ፍጹማን’ መሆናቸው በዕብ 12 ቁ 22 ሰፍሮልናል!!! ጌታም ከአመታት በፊት በሞት የተለዩትን አብርሃምን፣ይስሀቅንና
ያዕቆብን ጠቅሶ “የህያዋን አምላክ ነኝ” ሲል በማቴ 22 ቁ 32 ገልጹዋል!!!ጌታችን በስጋ ስለሞተው አብርሃም በዮሀንስ 8 ቁ56 ሲናገር፡ “አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሀሴትን አደረገ፤አየም ደስ አለው” ይላል!!!በአጸደ ነፍስ ያለው አብርሃም የጌታን ቀን አይቶ የተደሰተው በሰማይ ያሉ ቅዱሳን በምድር ካለነው ጋር ህብረት ስላላቸው ነው!! ዮሐንስ በራዕዩ ምዕራፍ 8 ቁ 3 “የዕጣኑ ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር ከመልአኩ እጅ በእግዚብሔር ፊት ወጣ” ይለናል!!መላእክት ጸሎታችንን ያሳርጋሉ!!!አእርጉ ጸሎተነ የምንላቸውም ለዚሁ ነው-እንደ ቅ/ያሬድ-እንደ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ!!ሙሴስ በዘጸአት 32 ቁ 13 “በራስህ የማልህላቸውን ባሪያዎችህን አብርሃምን፣ይስሀቅንና እስራኤልን አስብ” ብሎ በአጸደነፍስ ነፍስ ባሉ ቅዱሳን ስም ጌታውን ሲማጸን ከሞቱ ቅዱሳን ህብረት ስላለን አይደለምን?ነው እንጅ!!!
👉5. ይሄን ሁሉ ስንል ባለቤቱን ረስተን አይደለም!!!በቀጥታም እሱን ማረን እንለዋለን-እግዚኦ መሀረነ ክርስቶስ በምህላ- መሀረነ አብ በማስታኮት!!!ስማን፣ተማለደን፣ታረቀን እንለዋለን!!! ግን እንደሌሎቹ አማልደን አንለውም!!!ሌሎቹ የሚያማልደን ጌታ ነው እያሉ ቤዛነቱን እንደአማላጅነት ስለሚወስዱት ነው እኛ ቅዱሳንን አማልዱን ስንል አምላክ ያደረግናቸው የሚመስላቸው!!! አምላካችን አንድ ነው!!!የሃይማኖታችን መሰረትም እሱ-ለዚህም ነው ሰማይንና ምድርን በፈጠረ በአንድ አምላክ እናምናለን ስንል የሃይማኖት ጸሎታችንን የምንጀምረው!!!
ይቆየን
#ኦርቶዶክሳዊ_ምላሾች_እና_መረጃ_ብቻ_የሚቀርቡበት
👇👇👇
✍ አንድ ሃይማኖት
`ተዋህዶ´´´
@And_Haymanot
JOIN
@And_Haymanot
@And_Haymanot
~~~Share~~~
@And_Haymanot
@And_Haymanot
~~~JoIN~~~
@And_Haymanot
@And_Haymanot
፩ ሃይማኖት
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ መልስ አላት
@And_Haymanot
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡
ደብተራ
@And_Haymanot
፠፠፠የደብተራ ትርጓሜ በመዛግበተ ቃላት ወጥበባት፠፠፠
፠ደስታ ተክለ ወልድ በመዝገበ ቃላቸው፡- ‹‹ደብተራ - ድንኳን፡፡ ደበተረ - ደብተር ዘረጋ፣ ጻፈ፣ ከተበ ፡፡ ተደበተረ - ተዘረጋ፡፡ ደብተራ - የድንኳን ስም፡፡ ደብተራ - ዜማ. ቅኔ፣ ሳታት (ሰዓታት)
የሚያውቅ፣ በደብተራ (በድንኳን) ውስጥ የሚመራ፣ የሚቀኝ፣ የሚዘምር፣ መንፈሳዊ አገልጋይ፣ ካህን፣ አወዳሽ ሳታት ቋሚ፡፡ ደብቴ - ከፊለ ስም ወይም ቁልምጫ፣ የደብተራ ወገን፣ የኔ
ደብተራ ማለት ነው፡፡›› ይሉናል፡፡
፠ግእዙም፡- ‹‹ደብተረ› ማለትን በአወራረዱ ሕግ በተንበለ ቤት
አስገብቶ ሲያበቃ ‹‹ተከለ›› ሲል ይተረጕምና ለድንኳን ይሰጠዋል፡፡ ግእዝ ድንኳን ለሚለው ቃል ከደብተራ በተጨማሪ ኀይመትና ደበና ማለትን ይጠቀማል፡፡ ደበና የንጉሥ ድንኳን
የሚጠራበት ስም ነው፡፡ ደበናንሳ (ባለእጅ) የሚለው ቃል ከዚህ
ስም ጋራ ስለመያያዝ አለመያያዙ አላውቅም!
፠የፕ/ር ሥርግው አማርኛ የቤ/ክ መዝገበ ቃላት፡- ‹‹ደብተራ የቃሉ ቀጥተኛ ትርጕም ድንኳን ማለት ነው፡፡ ግን በቤተ
ክርስቲያን ውስጥ በቅኔ ማኅሌት የያሬድን ዜማ የሚዘምር፣ የሚመረግድ እንዲሁም ቅኔን የሚቀኝ ደብተራ ይባላል፡፡›› ብሎናል፡፡
፠በኢንሳይክሎፒዲያ ኢትዮፒካ፡- ደብተራ የሚለው ቃል እንደ ወረደ ከግሪክ የተቀዳ ሲሆን ትርጓሜውም እንደ ድንኳን የሚያገለግል ውጥር ቆዳ /ሌዘር/ ማለት እንደሆነ ተገልጧል፡፡
ደባትርን በቤ/ክ ካሉ ምሁራን ሁሉ ለይቼ the most educated clerics ያልኳቸው እኔ አይደለሁም፤ እንደነ ደንጎለጥ አንጠልጥሎ ሳይሆን አንጠርጥሮ የተረዳቸው ፈረንጅ ነው፡፡ በቤ/ክ የውስጥ አገልግሎት የቅዳሴና ውዳሴ ይባላል፡፡ የውዳሴው ድርሻ የደባትር ነው፡፡ የሚያወድሱት አምላካቸውን ነው፡፡ ውዳሴ የሃይማኖት አገልግሎት ስለሆነ በመደበኛ ፍ/ቤት
እንኳ አይዳኝም፤ በመንፈሳዊ ፍ/ቤት ብቻ ነው! እኒያ እግራቸው እስኪቀበተት ቆመው የሚያነጉ አገልጋይ ምሁራን ከውጪ በድውያን መጽልማነ ስም ስማቸው ተቀረደደ፤ በውስጥም ቤተ
ክርስቲያንን እየጋጡ በሰቡና በረቡ አምስት ከለባት ተዘነጠሉ እንጂ አገልግሎታቸውስ ‹‹ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኵሎ ዓለመ - ዓለምን የፈጠረ (እርሱ) ፈጽሞ የተመሰገነ ነው›› እያሉ ማወደስ ነበር፡፡ እነርሱ ቢጽፉ ጠንቋይ፣ ቢያሸበሽቡ ደናሽ፣ በፈሊጥ ቢናገሩ ቃላቸው ‹‹ቃለ ደብተራ››፣ ቢቀኙ ሰዓት ገዳይና ምዕመን አሰልቺ፣ ሕክምና ባልነበረበት ጊዜ ቁስል በቅጠል ቢያደርቁ ‹‹ሥር ማሽ ቅጠል በጣሽ›› ተባሉ እንጂ የሙሉ ሰዓት
አገልግሎታቸውስ ውዳሴ አምላክ ነበር፡፡ ሙያዎች ሁሉ በተከበሩበት፣ የሃይማኖት ነጻነት በታወጀበት፣ የቡድን መብቶች
ሁሉ ልዕልና አግኝተዋል በተባለበት ዘመን እነሆ ‹‹ደብተራ›› የወግ ማሳመሪያ ሆነ፡፡
፠ልዩ ልዩ ሕዝባዊ ትርጕም፡- ደብተራ - ተማሪ፣ መምህር ያልሆነ አዲስ ምሩቅ፣ ቄስም መነኩሴም ወይም ዲያቆን ያልሆነ፣ ሥልጣነ ክህነት የሌለው፣ ያፈረሰ፣ የድብትርና መሬት የያዘ፣
ጸሀፊ፣ መድኃኒት ዐዋቂ፣ ጥፈት የሚጥፍ … ደግነቱ ሁሉም መማሩን አይክዱበትም፡፡ ‹‹ቃለ ደብተራ›› የተባለ እንደሁ የአሽሙርና የኵሸት ማበረታቻ (ወደ ተንኮል የሚገፋ) ንግግር ነው፡፡ ‹‹ዕፀ ደብተራ›› የምትባል የኵሸት ዕፅ አለች፤ ቀጠጥናም ትባላለች፡፡
፠መንፈሳዊ ተምሳሌት፡- እመቤታችን፣ መስቀል፣ የጌታ ሥጋ፣ ቤተ መቅደስ ሁሉም ደብተራ ይባላሉ፡፡ ቅጽል ከፊቱ እየገባና እየተዛረፈ ‹‹ደብተራ ብርሃን፣ ደብተራ ፍጽምት፣ …›› ይዜማል፤
ይመሰጠራል፡፡ ሐዋርያው በዕብራውያን 9 እና 10 ነገረ ድኅነትን ይተርክበታል፤ ሐዲስን ከብሉይ ያነጻጽርበታል ደብተራን፡፡
፠ትርጕሙ ሲጠቃለል፡- ደብተራ ማለት በመደበኛ ትርጓሜው ማኅሌታዊ ማለት ነው፡፡ መዓርጉ ‹‹ተማሪ›› የመባል ያህል
ይመስላል፤ ከማንም አይሰጥም፤ ግን ደግሞ ለማንም አይሰጥም፡፡ ዜማ፣ ቅኔና አቋቋም መሞካከርን ይጠይቃል፡፡
በመርህ ደረጃ መነኮሳት ደብተራ አይባሉም፡፡ ...ይቆየን
በአማን ነጸረ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
@And_Haymanot
፠፠፠የደብተራ ትርጓሜ በመዛግበተ ቃላት ወጥበባት፠፠፠
፠ደስታ ተክለ ወልድ በመዝገበ ቃላቸው፡- ‹‹ደብተራ - ድንኳን፡፡ ደበተረ - ደብተር ዘረጋ፣ ጻፈ፣ ከተበ ፡፡ ተደበተረ - ተዘረጋ፡፡ ደብተራ - የድንኳን ስም፡፡ ደብተራ - ዜማ. ቅኔ፣ ሳታት (ሰዓታት)
የሚያውቅ፣ በደብተራ (በድንኳን) ውስጥ የሚመራ፣ የሚቀኝ፣ የሚዘምር፣ መንፈሳዊ አገልጋይ፣ ካህን፣ አወዳሽ ሳታት ቋሚ፡፡ ደብቴ - ከፊለ ስም ወይም ቁልምጫ፣ የደብተራ ወገን፣ የኔ
ደብተራ ማለት ነው፡፡›› ይሉናል፡፡
፠ግእዙም፡- ‹‹ደብተረ› ማለትን በአወራረዱ ሕግ በተንበለ ቤት
አስገብቶ ሲያበቃ ‹‹ተከለ›› ሲል ይተረጕምና ለድንኳን ይሰጠዋል፡፡ ግእዝ ድንኳን ለሚለው ቃል ከደብተራ በተጨማሪ ኀይመትና ደበና ማለትን ይጠቀማል፡፡ ደበና የንጉሥ ድንኳን
የሚጠራበት ስም ነው፡፡ ደበናንሳ (ባለእጅ) የሚለው ቃል ከዚህ
ስም ጋራ ስለመያያዝ አለመያያዙ አላውቅም!
፠የፕ/ር ሥርግው አማርኛ የቤ/ክ መዝገበ ቃላት፡- ‹‹ደብተራ የቃሉ ቀጥተኛ ትርጕም ድንኳን ማለት ነው፡፡ ግን በቤተ
ክርስቲያን ውስጥ በቅኔ ማኅሌት የያሬድን ዜማ የሚዘምር፣ የሚመረግድ እንዲሁም ቅኔን የሚቀኝ ደብተራ ይባላል፡፡›› ብሎናል፡፡
፠በኢንሳይክሎፒዲያ ኢትዮፒካ፡- ደብተራ የሚለው ቃል እንደ ወረደ ከግሪክ የተቀዳ ሲሆን ትርጓሜውም እንደ ድንኳን የሚያገለግል ውጥር ቆዳ /ሌዘር/ ማለት እንደሆነ ተገልጧል፡፡
ደባትርን በቤ/ክ ካሉ ምሁራን ሁሉ ለይቼ the most educated clerics ያልኳቸው እኔ አይደለሁም፤ እንደነ ደንጎለጥ አንጠልጥሎ ሳይሆን አንጠርጥሮ የተረዳቸው ፈረንጅ ነው፡፡ በቤ/ክ የውስጥ አገልግሎት የቅዳሴና ውዳሴ ይባላል፡፡ የውዳሴው ድርሻ የደባትር ነው፡፡ የሚያወድሱት አምላካቸውን ነው፡፡ ውዳሴ የሃይማኖት አገልግሎት ስለሆነ በመደበኛ ፍ/ቤት
እንኳ አይዳኝም፤ በመንፈሳዊ ፍ/ቤት ብቻ ነው! እኒያ እግራቸው እስኪቀበተት ቆመው የሚያነጉ አገልጋይ ምሁራን ከውጪ በድውያን መጽልማነ ስም ስማቸው ተቀረደደ፤ በውስጥም ቤተ
ክርስቲያንን እየጋጡ በሰቡና በረቡ አምስት ከለባት ተዘነጠሉ እንጂ አገልግሎታቸውስ ‹‹ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኵሎ ዓለመ - ዓለምን የፈጠረ (እርሱ) ፈጽሞ የተመሰገነ ነው›› እያሉ ማወደስ ነበር፡፡ እነርሱ ቢጽፉ ጠንቋይ፣ ቢያሸበሽቡ ደናሽ፣ በፈሊጥ ቢናገሩ ቃላቸው ‹‹ቃለ ደብተራ››፣ ቢቀኙ ሰዓት ገዳይና ምዕመን አሰልቺ፣ ሕክምና ባልነበረበት ጊዜ ቁስል በቅጠል ቢያደርቁ ‹‹ሥር ማሽ ቅጠል በጣሽ›› ተባሉ እንጂ የሙሉ ሰዓት
አገልግሎታቸውስ ውዳሴ አምላክ ነበር፡፡ ሙያዎች ሁሉ በተከበሩበት፣ የሃይማኖት ነጻነት በታወጀበት፣ የቡድን መብቶች
ሁሉ ልዕልና አግኝተዋል በተባለበት ዘመን እነሆ ‹‹ደብተራ›› የወግ ማሳመሪያ ሆነ፡፡
፠ልዩ ልዩ ሕዝባዊ ትርጕም፡- ደብተራ - ተማሪ፣ መምህር ያልሆነ አዲስ ምሩቅ፣ ቄስም መነኩሴም ወይም ዲያቆን ያልሆነ፣ ሥልጣነ ክህነት የሌለው፣ ያፈረሰ፣ የድብትርና መሬት የያዘ፣
ጸሀፊ፣ መድኃኒት ዐዋቂ፣ ጥፈት የሚጥፍ … ደግነቱ ሁሉም መማሩን አይክዱበትም፡፡ ‹‹ቃለ ደብተራ›› የተባለ እንደሁ የአሽሙርና የኵሸት ማበረታቻ (ወደ ተንኮል የሚገፋ) ንግግር ነው፡፡ ‹‹ዕፀ ደብተራ›› የምትባል የኵሸት ዕፅ አለች፤ ቀጠጥናም ትባላለች፡፡
፠መንፈሳዊ ተምሳሌት፡- እመቤታችን፣ መስቀል፣ የጌታ ሥጋ፣ ቤተ መቅደስ ሁሉም ደብተራ ይባላሉ፡፡ ቅጽል ከፊቱ እየገባና እየተዛረፈ ‹‹ደብተራ ብርሃን፣ ደብተራ ፍጽምት፣ …›› ይዜማል፤
ይመሰጠራል፡፡ ሐዋርያው በዕብራውያን 9 እና 10 ነገረ ድኅነትን ይተርክበታል፤ ሐዲስን ከብሉይ ያነጻጽርበታል ደብተራን፡፡
፠ትርጕሙ ሲጠቃለል፡- ደብተራ ማለት በመደበኛ ትርጓሜው ማኅሌታዊ ማለት ነው፡፡ መዓርጉ ‹‹ተማሪ›› የመባል ያህል
ይመስላል፤ ከማንም አይሰጥም፤ ግን ደግሞ ለማንም አይሰጥም፡፡ ዜማ፣ ቅኔና አቋቋም መሞካከርን ይጠይቃል፡፡
በመርህ ደረጃ መነኮሳት ደብተራ አይባሉም፡፡ ...ይቆየን
በአማን ነጸረ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
አስታርቂኝ
አስታርቂኝ ድንግል ማርያም /2/
ከልጅሽ /3/ ከመድኃኔዓለም
አስታርቂኝ ኃጢአትን ሰርቼ
አስታርቂኝ ጫካ ውስጥ ቆሜአለው
አስታርቂኝ ሥራዬ አሳፍሮኝ
አስታርቂኝ ዘወትር አነባለው
አስታርቂኝ ልጄ አዳም ብሎ
አስታርቂኝ አምላኬ ሲጠራ
አስታርቂኝ እነሆኝ ለማለት
አስታርቂኝ አንደበቴ ፈራ
አዝ ------------
አስታርቂኝ ሀብትን ተካፍዬ
አስታርቂኝ ከገዛ አባቴ
አስታርቂኝ ከቤቴ ኮበለልኩ
አስታርቂኝ ይሻለኛል ብዬ
አስታርቂኝ ገፍቼ ወጥቼ
አስታርቂኝ የቤቴን ገበታ
አስታርቂኝ ልበላ ተመኘሁ
አስታርቂኝ የእንስሳት ገፈራ
አዝ---------
አስታርቂኝ ወደ አባቴ ልሂድ
አስታርቂኝ አሁን ተነሥቼ
አስታርቂኝ ይቅርታ ልጠይቅ
አስታርቂኝ እግሩ ስር ወድቄ
አስታርቂኝ ልጅነቴ ቀርቶ
አስታርቂኝ አድርገኝ ባርያህ
አስታርቂኝ ከሞያተኞችህ
አስታርቂኝ እንደ አንዱ ቆጥረህ
አዝ ------
አስታርቂኝ ገና ሩቅ ሳለው
አስታርቂኝ አባቴ አይቶኝ
አስታርቂኝ ወደእኔ ሮጦ
አስታርቂኝ አቅፎ ነው የሳመኝ
አስታርቂኝ ጠፍቶ የነበረው
አስታርቂኝ ተገኘልኝ አለ
አስታርቂኝ ሞቶ የነበረው
አስታርቂኝ ደግሞ ሕያው ሆነ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
አስታርቂኝ ድንግል ማርያም /2/
ከልጅሽ /3/ ከመድኃኔዓለም
አስታርቂኝ ኃጢአትን ሰርቼ
አስታርቂኝ ጫካ ውስጥ ቆሜአለው
አስታርቂኝ ሥራዬ አሳፍሮኝ
አስታርቂኝ ዘወትር አነባለው
አስታርቂኝ ልጄ አዳም ብሎ
አስታርቂኝ አምላኬ ሲጠራ
አስታርቂኝ እነሆኝ ለማለት
አስታርቂኝ አንደበቴ ፈራ
አዝ ------------
አስታርቂኝ ሀብትን ተካፍዬ
አስታርቂኝ ከገዛ አባቴ
አስታርቂኝ ከቤቴ ኮበለልኩ
አስታርቂኝ ይሻለኛል ብዬ
አስታርቂኝ ገፍቼ ወጥቼ
አስታርቂኝ የቤቴን ገበታ
አስታርቂኝ ልበላ ተመኘሁ
አስታርቂኝ የእንስሳት ገፈራ
አዝ---------
አስታርቂኝ ወደ አባቴ ልሂድ
አስታርቂኝ አሁን ተነሥቼ
አስታርቂኝ ይቅርታ ልጠይቅ
አስታርቂኝ እግሩ ስር ወድቄ
አስታርቂኝ ልጅነቴ ቀርቶ
አስታርቂኝ አድርገኝ ባርያህ
አስታርቂኝ ከሞያተኞችህ
አስታርቂኝ እንደ አንዱ ቆጥረህ
አዝ ------
አስታርቂኝ ገና ሩቅ ሳለው
አስታርቂኝ አባቴ አይቶኝ
አስታርቂኝ ወደእኔ ሮጦ
አስታርቂኝ አቅፎ ነው የሳመኝ
አስታርቂኝ ጠፍቶ የነበረው
አስታርቂኝ ተገኘልኝ አለ
አስታርቂኝ ሞቶ የነበረው
አስታርቂኝ ደግሞ ሕያው ሆነ
@And_Haymanot
@And_Haymanot
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
† በአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገድል ላይ የሚነሱ
አንዳንድ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
-(ለፕሮቴስታንቶችና ተሐድሶዎች የቀረበ)
፩. አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገድለ ተክለ ሃይማኖትላይ ‘ሰይጣንን አጠመቁት’ ይላል እያሉ የተሐድሶ መናፍቃን ይተቻሉ፡፡ እውን ግን ጻድቁ አባታችን
አቡነ ተክለ ሃይማኖት በቁሙ ሰይጣንን
አጥምቀዋልን?
መልስ፡- በቀድሞ መጻሕፍት ሥጋ ለበስ የሆኑ አጋንንት ታሪክ የታወቀ ነው፡፡ እነዚህ ሥጋ ለበስ አጋንንት የአጋንንትን ሥራ የሚሠሩ ቢሆኑም
የሚዳሰስ ሥጋ ግን አላቸው፡፡ ለምሳሌ ድርሳነ ሚካኤል ዘጥር ላይ እንደ ተገለጠው እነዚህ በሽታዎችን ሁሉ የሚያመጡ ሥጋ ለበስ አጋንንት
እንደ ሰው ሁሉ ይታመማሉ፤ ይራባሉ፤ ይሞታሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ
በበረሐ ውስጥ አንዳንድ ጊዜም በውኃ ውስጥ ይኖራሉ፡፡
+ በገድለ ተክለ ሃይማኖትና በልደተ አበው ላይ እንዲህ ይላል “አቡነ ተክለ ሃይማኖት በእነዚህ አውራጃዎች ሲመላለስ አንድ ቀን በውኃ ዳር ዐረፍ አለ፡፡ ጋኔንም ከውኃው ወጣና ደቀ መዛሙሩን ያዘው፡፡ አሳመመውም፡፡ እርሱም ጋኔን መሆኑን ዐወቀ፡፡ በረድኡ ላይም በመስቀል ምልክት አማተበበት፡፡ ጋኔኑም ፈጥኖ ወጣ ሸሸ፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም በእጁ ያዘው፡፡ ሥራዩንም አወጣበት፡፡ ያን ጊዜም ለሁሉ ታየ፡፡ እርሱም “ማነው ስምህ?” አለው፡፡ ጋኔኑም “ባሕር አልቀም” አለው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም “ከኔ ጋር ትኖራለህን?” አለው፡፡ እርሱም ገዘረውና ወደ ታላቁ የቤተ ክርስቲያን ምሥጢረ ጥምቀት አገባው፡፡ ስሙንም ክርስቶስ ኀረዮ(ክርስቶስ መረጠው ማለት ነው) አለው፡፡ ረድእም አደረገው፡፡ ወደ በኣቱም አስገባው፡፡ እርሷም አስቦ ናት፡፡ እርሱም እግዚአብሔርን የሚወድና ወንድሞቹንም ሁሉ የሚያስደስት ሆነ፡፡” (ገድለ ተክለ ሃይማኖት፤ነሐሴ 1989 ዓ.ም፤ ምዕራፍ ፶፩፤ ገጽ. 177-178፤ Getachew Haile, Geneaology, P.11&12)
+ በጥንታውያን ሰዎች ዘንድ በአጋንንት አሠራር ተጠምደው የሚኖሩ ጣዖት አምላኪ ሰዎችን ባደሩባቸው አጋንንት ስም መጥራት የተለመደ ነው፡፡ ሰው በውስጡ ባለው ነገር ይጠራልና፡፡ ልክ ጌታ ጴጥሮስን “አንተ ሰይጣን ከኋላየ ሒድ” (ማቴ.16፡23) እንዳለው ማለት ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ታሪኮች በብዙ ጥንታውያን መጻሕፍት አሉ፡፡ ሥጋ ለበስ አጋንንት የሚሏቸው እነርሱን ነው፡፡ የተለያዩ የምትሐት ነገሮችን ይሠራሉ፡፡ በባሕር ይኖራሉ፣ በእሳት ውስጥም ገብተው በደኅና ይወጣሉ፡፡ ዋሊስ ባጅ ባሰተመው የደብረ ሊባኖስ ገድለ ተክለ ሃይማኖት ላይ ጸሐፊው ከሌሎቹ የአካባቢው ቅጅዎች ለየት ብሎ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ያጠመቁት ክፉ መንፈስ
ያለበትን ሰው እንጂ መንፈስ የሆነውን ሰይጣን አለመሆኑን በቅዱሳት መጻሕፍት ማስረጃዎች ያብራራል፡፡ (E.A.W. Budge, The Life and Miracles of Takla Hay-manot, (London,1906), P. 80).
የተሐድሶ መናፍቃን ገድለ ተክለ ሃይማኖት‘የተክለ ሃይማኖት ተቅማጥ ከክርስቶስ ደም ጋር እኩል ነው’ ይላል ይላሉ፡፡ በውኑ ይላልን?
መልስ፡- ሙሉ ገጸ ንባቡ “ክቡር አባታችንም ጌታዬ ወደ ሰማዕትነት ዐደባባይ ሄጄ በስምህ እንድሞት እዘዘኝ አለው፤ ጌታም መጋደልስ ፈጸምክ ከሞት በቀር ምንም አልቀረህም፡፡” አለው ነው የሚለው፡፡ [ገድለ ተክለ ሃይማኖት፤ነሐሴ 1989 ዓ.ም፤ ምዕራፍ ፶፯፤ ገጽ. 195] ከዚህም በኋላ፡- “ወናሁ ትመውት በሕማመ ብድብድ በእኩይ ሞት ወእሬሲ ለከ ኪያሃ ከመ ስቅለትየ በከመ ደመ ሰማዕት እለ እምቅድሜከ አኮ ለባሕቲትከ አላ ደቂቅከኒ እለ ይመውቱ በሕማመ ብድብድ በውስተ ዛቲ ገዳም እኌልቆሙ ምስለ ሰማዕታት ወአወፍዮሙ ለከ በመንግሥተ ሰማያት፡፡”[ዝኒ ከማሁ] ነው ያለው፡፡ + የቃሉ የግእዝ ትርጒም ሕማመ ብድብድ ማለት ቸነፈር ማለት ነው፡፡ ጻድቁ ተክለ ሃይማኖት የሞቱት በቸነፈር በሽታ ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በዕለተ ዐርብ እንደ ተቀበልኩት መከራ መስቀል አደርግልሃለሁ ያለው፤ ገድላቸውንና በደዌ የተቀበሉትን መከራ ነው፡፡
በመልክዐ ጊዮርጊስ ላይም እንዲህ የሚል አብነት ይገኛል፡፡ ሰላም ለሰኳንዊከ ምስለ ክልኤሆን መከየድ፡፡ ለአጻብዒከ ሰላም ወለአጽፋረ እግርከ አምሳለ መረግድ፡፡ ገባሬ መንክራት ጊዮርጊስ በአቊጽሎ ይቡስ ዐምድ፡፡ አድኅነኒ በጸሎትከ እምነ መከራ ክቡድ፡፡ እስመ እምኔሁ ይወጽእ ቀታሊ ብድብድ፡፡ (መልክዐ ጊዮርጊስ) ትርጓሜውም፡- ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ በሁለቱ ተረከዞችህ ጋር ለጫሞችህ ሰላም እላለሁ፡፡ እንደ ከበረ ዕንቊ ለሚያበሩት ለእግር ጽፍሮችህና ጣቶችህም ሰላም እላለሁ፡፡ ተአምር አድራጊው ሰማዕት ሆይ! ደረቁን ምሰሶ ለምለም ተአምራትህን ገልጸሃልና፡፡ ከጽኑ መከራ በጸሎትህ አድነኝ፡፡ ሰውስ ለሥቃይ የሚዳርጉ ረኀብ ቸነፈር ከእሱ ይፈልቃሉና፡፡ ማለት ነው፡፡ ስለሆነም "ብድብድ" የሚለው ረኀብ፤ ቸነፈር
ተብሎ ይተረጎማል፡፡
+ የተሐድሶ መናፍቃኑ እንደ ሚሉት ‘ተቅማጥህ እንደ ስቅላቴ ደም ነው’ የሚል ሐረግም ከገድሉ ላይ አይገኝም፡፡ “… እሷንም እንደ ስቅላቴና ካንተ በፊት እንደ ነበሩ ሰማዕታት ደም እቆጥርልሃለሁ፤” [ዝኒ ከማሁ(Ibid)] ነው ያለው፡፡ ይህም ማለት የተክለ ሃይማኖት ሕማም ከሰማዕታት ደም ጋር እኩል እንደሆነ እንጂ ከክርስቶስ ደም ጋር እኩል እንደሆነ አያስረዳም፡፡
ይህም የሆነበት ምክንያት ከገድሉ ላይ እንደምንረዳው መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አባ ተክለ ሃይማኖት ብዙ ተጋድለሃል ከእንግዲህ ይበቃሃል ነፍስህ ከመከራ ተለይታ ወደ እረፍት መሄጃህ ጊዜ ደርሷል ባላቸው ጊዜ አባ ተክለ
ሃይማኖት በሰማዕትነት እንድሞት አድርገኝ ብለው ስለለመኑት ነው፡፡ + በሚሞቱበት ጊዜ የሚደርስባቸውን
ሕማም እንደ ራሱ መከራና በጦር ተወግተው በስለት ተቆርጠው ደማቸው እንደ ፈሰሰው ሰማዕታት ደም ሲቆጠርላቸው ነው፡፡ ሰማዕታት ለክርስቶስ ሲሉ በጦር ተወግተው በስለት ተቆርጠው ደማቸው እንደሚፈስ አባ ተክለ ሃይማኖትም ለክርስቶስ ሲሉ
ሃገር ለሃገር ጫካ ለጫካ ሲንከራተቱ ሕማመ ብድብድን (ቸነፈርን) በጦር ተወግተው ደማቸው እንደፈሰሰው ሰማዕታት ቆጠረላቸው፡፡ ስለዚህ የአባ ተክለ ሃይማኖት ሕማመ ብድብድ (ቸነፈር) እንደ ሰማዕታት ደም
ሆኖ ቢቆጠር ሃይማኖት ላለውና ለሚያስተውል ሰው አያደንቅም፡፡
፫. “ከሩቅም ከቅርብም ቢመጣ ወደ መቃብርህ የሄደውን እኔ ወደ መቃብሬ ኢየሩሳሌም እንደ ሄደ አደርገዋለሁ፤ በመታሰቢያህ ቀን ሥጋውን ደሙን የተቀበለውንም ስማቸው ከተጠራው ገድላቸው ከተነገረው ልጆችህ ጋራ እኔ እቈጥረዋለሁ፡፡” [ገድለ ተክለ
ሃይማኖት፤ነሐሴ 1989 ዓ.ም፤ ምዕራፍ ፶፯፤ ገጽ. 193] ማለት ምን
ማለት ነው?
+ መልስ፡- ወደ መቃብርህ የመጣውን ወደ መቃብሬ እንደመጣ አደርገዋለሁ ማለት በአንተ አማላጅነት በእኔ በርነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባል ማለት
ነው፡፡ ይህም እናንተን የተቀበለ
እኔን ተቀበለ ያለው የወንጌል ቃል በተግባር ሲተረጎም ነው፡፡ + በተክለ ሃይማኖት በመቃብር ላይ በተክለ
ሃይማኖት ስም በተሠራው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ወደ ሚገኝበት በመምጣት በመጸለይ ወደ
መንግሥተ ሰማያት መግባት ነው፡፡ የእግዚአብሔር በረከት ወደሚገኝበት ቦታ በመሄድ ዋጋ እንደሚገኝም መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምረናል፡፡ 2ኛ.ነገ.5፡1፤
ዕብ. 11፡23፤ ሩት. 1፡16-18፡፡
+ “በመታሰቢያህ ቀን ሥጋውን ደሙን
የተቀበለውንም ስማቸው ከተጠራው ገድላቸው ከተጻፈው ልጆችህ ጋር እኔ አኖራቸዋለሁ፡፡” የሚለውም ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን መግቢያ
በርነት የበለጠ ያስተምራል እንጂ
አንዳንድ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
-(ለፕሮቴስታንቶችና ተሐድሶዎች የቀረበ)
፩. አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገድለ ተክለ ሃይማኖትላይ ‘ሰይጣንን አጠመቁት’ ይላል እያሉ የተሐድሶ መናፍቃን ይተቻሉ፡፡ እውን ግን ጻድቁ አባታችን
አቡነ ተክለ ሃይማኖት በቁሙ ሰይጣንን
አጥምቀዋልን?
መልስ፡- በቀድሞ መጻሕፍት ሥጋ ለበስ የሆኑ አጋንንት ታሪክ የታወቀ ነው፡፡ እነዚህ ሥጋ ለበስ አጋንንት የአጋንንትን ሥራ የሚሠሩ ቢሆኑም
የሚዳሰስ ሥጋ ግን አላቸው፡፡ ለምሳሌ ድርሳነ ሚካኤል ዘጥር ላይ እንደ ተገለጠው እነዚህ በሽታዎችን ሁሉ የሚያመጡ ሥጋ ለበስ አጋንንት
እንደ ሰው ሁሉ ይታመማሉ፤ ይራባሉ፤ ይሞታሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ
በበረሐ ውስጥ አንዳንድ ጊዜም በውኃ ውስጥ ይኖራሉ፡፡
+ በገድለ ተክለ ሃይማኖትና በልደተ አበው ላይ እንዲህ ይላል “አቡነ ተክለ ሃይማኖት በእነዚህ አውራጃዎች ሲመላለስ አንድ ቀን በውኃ ዳር ዐረፍ አለ፡፡ ጋኔንም ከውኃው ወጣና ደቀ መዛሙሩን ያዘው፡፡ አሳመመውም፡፡ እርሱም ጋኔን መሆኑን ዐወቀ፡፡ በረድኡ ላይም በመስቀል ምልክት አማተበበት፡፡ ጋኔኑም ፈጥኖ ወጣ ሸሸ፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም በእጁ ያዘው፡፡ ሥራዩንም አወጣበት፡፡ ያን ጊዜም ለሁሉ ታየ፡፡ እርሱም “ማነው ስምህ?” አለው፡፡ ጋኔኑም “ባሕር አልቀም” አለው፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም “ከኔ ጋር ትኖራለህን?” አለው፡፡ እርሱም ገዘረውና ወደ ታላቁ የቤተ ክርስቲያን ምሥጢረ ጥምቀት አገባው፡፡ ስሙንም ክርስቶስ ኀረዮ(ክርስቶስ መረጠው ማለት ነው) አለው፡፡ ረድእም አደረገው፡፡ ወደ በኣቱም አስገባው፡፡ እርሷም አስቦ ናት፡፡ እርሱም እግዚአብሔርን የሚወድና ወንድሞቹንም ሁሉ የሚያስደስት ሆነ፡፡” (ገድለ ተክለ ሃይማኖት፤ነሐሴ 1989 ዓ.ም፤ ምዕራፍ ፶፩፤ ገጽ. 177-178፤ Getachew Haile, Geneaology, P.11&12)
+ በጥንታውያን ሰዎች ዘንድ በአጋንንት አሠራር ተጠምደው የሚኖሩ ጣዖት አምላኪ ሰዎችን ባደሩባቸው አጋንንት ስም መጥራት የተለመደ ነው፡፡ ሰው በውስጡ ባለው ነገር ይጠራልና፡፡ ልክ ጌታ ጴጥሮስን “አንተ ሰይጣን ከኋላየ ሒድ” (ማቴ.16፡23) እንዳለው ማለት ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ታሪኮች በብዙ ጥንታውያን መጻሕፍት አሉ፡፡ ሥጋ ለበስ አጋንንት የሚሏቸው እነርሱን ነው፡፡ የተለያዩ የምትሐት ነገሮችን ይሠራሉ፡፡ በባሕር ይኖራሉ፣ በእሳት ውስጥም ገብተው በደኅና ይወጣሉ፡፡ ዋሊስ ባጅ ባሰተመው የደብረ ሊባኖስ ገድለ ተክለ ሃይማኖት ላይ ጸሐፊው ከሌሎቹ የአካባቢው ቅጅዎች ለየት ብሎ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ያጠመቁት ክፉ መንፈስ
ያለበትን ሰው እንጂ መንፈስ የሆነውን ሰይጣን አለመሆኑን በቅዱሳት መጻሕፍት ማስረጃዎች ያብራራል፡፡ (E.A.W. Budge, The Life and Miracles of Takla Hay-manot, (London,1906), P. 80).
የተሐድሶ መናፍቃን ገድለ ተክለ ሃይማኖት‘የተክለ ሃይማኖት ተቅማጥ ከክርስቶስ ደም ጋር እኩል ነው’ ይላል ይላሉ፡፡ በውኑ ይላልን?
መልስ፡- ሙሉ ገጸ ንባቡ “ክቡር አባታችንም ጌታዬ ወደ ሰማዕትነት ዐደባባይ ሄጄ በስምህ እንድሞት እዘዘኝ አለው፤ ጌታም መጋደልስ ፈጸምክ ከሞት በቀር ምንም አልቀረህም፡፡” አለው ነው የሚለው፡፡ [ገድለ ተክለ ሃይማኖት፤ነሐሴ 1989 ዓ.ም፤ ምዕራፍ ፶፯፤ ገጽ. 195] ከዚህም በኋላ፡- “ወናሁ ትመውት በሕማመ ብድብድ በእኩይ ሞት ወእሬሲ ለከ ኪያሃ ከመ ስቅለትየ በከመ ደመ ሰማዕት እለ እምቅድሜከ አኮ ለባሕቲትከ አላ ደቂቅከኒ እለ ይመውቱ በሕማመ ብድብድ በውስተ ዛቲ ገዳም እኌልቆሙ ምስለ ሰማዕታት ወአወፍዮሙ ለከ በመንግሥተ ሰማያት፡፡”[ዝኒ ከማሁ] ነው ያለው፡፡ + የቃሉ የግእዝ ትርጒም ሕማመ ብድብድ ማለት ቸነፈር ማለት ነው፡፡ ጻድቁ ተክለ ሃይማኖት የሞቱት በቸነፈር በሽታ ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በዕለተ ዐርብ እንደ ተቀበልኩት መከራ መስቀል አደርግልሃለሁ ያለው፤ ገድላቸውንና በደዌ የተቀበሉትን መከራ ነው፡፡
በመልክዐ ጊዮርጊስ ላይም እንዲህ የሚል አብነት ይገኛል፡፡ ሰላም ለሰኳንዊከ ምስለ ክልኤሆን መከየድ፡፡ ለአጻብዒከ ሰላም ወለአጽፋረ እግርከ አምሳለ መረግድ፡፡ ገባሬ መንክራት ጊዮርጊስ በአቊጽሎ ይቡስ ዐምድ፡፡ አድኅነኒ በጸሎትከ እምነ መከራ ክቡድ፡፡ እስመ እምኔሁ ይወጽእ ቀታሊ ብድብድ፡፡ (መልክዐ ጊዮርጊስ) ትርጓሜውም፡- ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ በሁለቱ ተረከዞችህ ጋር ለጫሞችህ ሰላም እላለሁ፡፡ እንደ ከበረ ዕንቊ ለሚያበሩት ለእግር ጽፍሮችህና ጣቶችህም ሰላም እላለሁ፡፡ ተአምር አድራጊው ሰማዕት ሆይ! ደረቁን ምሰሶ ለምለም ተአምራትህን ገልጸሃልና፡፡ ከጽኑ መከራ በጸሎትህ አድነኝ፡፡ ሰውስ ለሥቃይ የሚዳርጉ ረኀብ ቸነፈር ከእሱ ይፈልቃሉና፡፡ ማለት ነው፡፡ ስለሆነም "ብድብድ" የሚለው ረኀብ፤ ቸነፈር
ተብሎ ይተረጎማል፡፡
+ የተሐድሶ መናፍቃኑ እንደ ሚሉት ‘ተቅማጥህ እንደ ስቅላቴ ደም ነው’ የሚል ሐረግም ከገድሉ ላይ አይገኝም፡፡ “… እሷንም እንደ ስቅላቴና ካንተ በፊት እንደ ነበሩ ሰማዕታት ደም እቆጥርልሃለሁ፤” [ዝኒ ከማሁ(Ibid)] ነው ያለው፡፡ ይህም ማለት የተክለ ሃይማኖት ሕማም ከሰማዕታት ደም ጋር እኩል እንደሆነ እንጂ ከክርስቶስ ደም ጋር እኩል እንደሆነ አያስረዳም፡፡
ይህም የሆነበት ምክንያት ከገድሉ ላይ እንደምንረዳው መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አባ ተክለ ሃይማኖት ብዙ ተጋድለሃል ከእንግዲህ ይበቃሃል ነፍስህ ከመከራ ተለይታ ወደ እረፍት መሄጃህ ጊዜ ደርሷል ባላቸው ጊዜ አባ ተክለ
ሃይማኖት በሰማዕትነት እንድሞት አድርገኝ ብለው ስለለመኑት ነው፡፡ + በሚሞቱበት ጊዜ የሚደርስባቸውን
ሕማም እንደ ራሱ መከራና በጦር ተወግተው በስለት ተቆርጠው ደማቸው እንደ ፈሰሰው ሰማዕታት ደም ሲቆጠርላቸው ነው፡፡ ሰማዕታት ለክርስቶስ ሲሉ በጦር ተወግተው በስለት ተቆርጠው ደማቸው እንደሚፈስ አባ ተክለ ሃይማኖትም ለክርስቶስ ሲሉ
ሃገር ለሃገር ጫካ ለጫካ ሲንከራተቱ ሕማመ ብድብድን (ቸነፈርን) በጦር ተወግተው ደማቸው እንደፈሰሰው ሰማዕታት ቆጠረላቸው፡፡ ስለዚህ የአባ ተክለ ሃይማኖት ሕማመ ብድብድ (ቸነፈር) እንደ ሰማዕታት ደም
ሆኖ ቢቆጠር ሃይማኖት ላለውና ለሚያስተውል ሰው አያደንቅም፡፡
፫. “ከሩቅም ከቅርብም ቢመጣ ወደ መቃብርህ የሄደውን እኔ ወደ መቃብሬ ኢየሩሳሌም እንደ ሄደ አደርገዋለሁ፤ በመታሰቢያህ ቀን ሥጋውን ደሙን የተቀበለውንም ስማቸው ከተጠራው ገድላቸው ከተነገረው ልጆችህ ጋራ እኔ እቈጥረዋለሁ፡፡” [ገድለ ተክለ
ሃይማኖት፤ነሐሴ 1989 ዓ.ም፤ ምዕራፍ ፶፯፤ ገጽ. 193] ማለት ምን
ማለት ነው?
+ መልስ፡- ወደ መቃብርህ የመጣውን ወደ መቃብሬ እንደመጣ አደርገዋለሁ ማለት በአንተ አማላጅነት በእኔ በርነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባል ማለት
ነው፡፡ ይህም እናንተን የተቀበለ
እኔን ተቀበለ ያለው የወንጌል ቃል በተግባር ሲተረጎም ነው፡፡ + በተክለ ሃይማኖት በመቃብር ላይ በተክለ
ሃይማኖት ስም በተሠራው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ወደ ሚገኝበት በመምጣት በመጸለይ ወደ
መንግሥተ ሰማያት መግባት ነው፡፡ የእግዚአብሔር በረከት ወደሚገኝበት ቦታ በመሄድ ዋጋ እንደሚገኝም መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምረናል፡፡ 2ኛ.ነገ.5፡1፤
ዕብ. 11፡23፤ ሩት. 1፡16-18፡፡
+ “በመታሰቢያህ ቀን ሥጋውን ደሙን
የተቀበለውንም ስማቸው ከተጠራው ገድላቸው ከተጻፈው ልጆችህ ጋር እኔ አኖራቸዋለሁ፡፡” የሚለውም ቃል የኢየሱስ ክርስቶስን መግቢያ
በርነት የበለጠ ያስተምራል እንጂ
Forwarded from ፩ ሃይማኖት
አያስቀርም፡፡ በአንተ መታሰቢያ
ዕለት የእኔን ሥጋና ደም ተቀብሎ በአንተ አስተማሪነት በእኔ በርነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባል ማለት ነው፡፡
፬ የመናፍቃን ጥያቄ ከገድለ ተክለሐይማኖት ውስጥ: "እባብን የገደለ ይጽድቃል" ይላል፡፡ ስለዚህ ሰዎች ሁሉ እባብን እየፈለጉ ለመጽደቅ እባብን መግደል አለባቸው ወይ የሚል ነው። አይ ይህቺ የመናፍቃን ጭንቅላት ትንሽ ብትሰፋ! ወገኖቼ መጸሐፍ ቅዱስ እውርን እውር ቢመራው ተያይዞ ገደል መግባት ነው ይላል:: አንዱ ብርሃን መሆን አለበት:: ዛሬ ብዙ ሰዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ታውረዋል፡፡ አባታችን ተክለ ሐይማኖት ይፈውሱዋቸው
አሜን :: ወገኖቼ እባብን የገደለ
ይጸድቃል ማለት እባብ የተባለ ዲያቢሎስ ነው:: ለምሳሌ ያህል በመዝሙር ምህራፍ 73 ቁጥር 14
እንዲህ ይላል “አንተም የዘንዶውን እራስ
ቀጠቀጥክ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው፤” ይላል :: ታዲያ አንተ የዘንዶውን እራስ ቀጠቀጥክ
ሲል ታዲያ እግዚአብሔር ዘንዶ
ያለበትን እየሔደ እራስ እራሱን ቀጠቀጠው ማለት ነውን? አይደለም :: ዘንዶ የተባለው ሰይጣን ነው:: ሰይጣንን ደግሞ እግዚአብሔር በመስቀሉ
ቀጥቅጦታል ::
እንዲሁም ገድለ ተክለ ሐይማኖት
ላይም እባብን የገደለ ይጽድቃል ሲል ሰይጣንን የገደለ ይጸድቃል
ማለቱ ነው :: ሰይጣንን የምንገለው ደግሞ በጾም በጸሎት እና በስግደት
ነው:: በነዚህ እባብ (ዲያቢሎስን ) መግደል እንችላለን:: በተጨማሪም ደግሞ ራእይ ዮሐንስ ምህራፍ 12 ቁጥር 7 እንዲህ ይላል፡- “በሰማይም
ሰልፍ ሆነ ሚካኤልና ሰራዊቱ ዘንዶውን ተዋጉት :: ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ አልቻላቸውም፤ ከዚያም ወዲያ በሰማይ ስፍራ አልተገኘላቸውም::
ዓለሙን ሁሉ የሚያስት ዲያቢሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፡፡ ወደ ምድርም ተጣለ፤ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ፤” ይላል:: ታዲያ ሚካኤልና ቅዱሳን መላእክቱ ከዘንዶው ጋር ተዋጉ ሲል ከእንስሳ ጋር ተዋጉ ማለት ነውን? አይደለም፡፡ ዘንዶ የተባለው የቀደመው ሰይጣን እርሱ ዲያቢሎስ ነው ይለናል:፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
Join
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡
ዕለት የእኔን ሥጋና ደም ተቀብሎ በአንተ አስተማሪነት በእኔ በርነት ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባል ማለት ነው፡፡
፬ የመናፍቃን ጥያቄ ከገድለ ተክለሐይማኖት ውስጥ: "እባብን የገደለ ይጽድቃል" ይላል፡፡ ስለዚህ ሰዎች ሁሉ እባብን እየፈለጉ ለመጽደቅ እባብን መግደል አለባቸው ወይ የሚል ነው። አይ ይህቺ የመናፍቃን ጭንቅላት ትንሽ ብትሰፋ! ወገኖቼ መጸሐፍ ቅዱስ እውርን እውር ቢመራው ተያይዞ ገደል መግባት ነው ይላል:: አንዱ ብርሃን መሆን አለበት:: ዛሬ ብዙ ሰዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ቃል ታውረዋል፡፡ አባታችን ተክለ ሐይማኖት ይፈውሱዋቸው
አሜን :: ወገኖቼ እባብን የገደለ
ይጸድቃል ማለት እባብ የተባለ ዲያቢሎስ ነው:: ለምሳሌ ያህል በመዝሙር ምህራፍ 73 ቁጥር 14
እንዲህ ይላል “አንተም የዘንዶውን እራስ
ቀጠቀጥክ ለኢትዮጵያ ሰዎችም ምግባቸውን ሰጠሃቸው፤” ይላል :: ታዲያ አንተ የዘንዶውን እራስ ቀጠቀጥክ
ሲል ታዲያ እግዚአብሔር ዘንዶ
ያለበትን እየሔደ እራስ እራሱን ቀጠቀጠው ማለት ነውን? አይደለም :: ዘንዶ የተባለው ሰይጣን ነው:: ሰይጣንን ደግሞ እግዚአብሔር በመስቀሉ
ቀጥቅጦታል ::
እንዲሁም ገድለ ተክለ ሐይማኖት
ላይም እባብን የገደለ ይጽድቃል ሲል ሰይጣንን የገደለ ይጸድቃል
ማለቱ ነው :: ሰይጣንን የምንገለው ደግሞ በጾም በጸሎት እና በስግደት
ነው:: በነዚህ እባብ (ዲያቢሎስን ) መግደል እንችላለን:: በተጨማሪም ደግሞ ራእይ ዮሐንስ ምህራፍ 12 ቁጥር 7 እንዲህ ይላል፡- “በሰማይም
ሰልፍ ሆነ ሚካኤልና ሰራዊቱ ዘንዶውን ተዋጉት :: ዘንዶውም ከመላእክቱ ጋር ተዋጋ አልቻላቸውም፤ ከዚያም ወዲያ በሰማይ ስፍራ አልተገኘላቸውም::
ዓለሙን ሁሉ የሚያስት ዲያቢሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፡፡ ወደ ምድርም ተጣለ፤ መላእክቱም ከእርሱ ጋር ተጣሉ፤” ይላል:: ታዲያ ሚካኤልና ቅዱሳን መላእክቱ ከዘንዶው ጋር ተዋጉ ሲል ከእንስሳ ጋር ተዋጉ ማለት ነውን? አይደለም፡፡ ዘንዶ የተባለው የቀደመው ሰይጣን እርሱ ዲያቢሎስ ነው ይለናል:፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ኦርቶዶክስ መልስ አላት፡፡
Join
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
የአበው ሃይማኖት አትታደስም፡፡
Forwarded from መሠረተ ያሬድ ሰ/ት/ቤት ዘአሣሣ
[የሕሙማን እናት የተባለችው ሐምሌ 25 ያረፈችው በብዙ ሊቃውንት የተወደሰችው የቅድስት ቴክላ ድንቅ ታሪክ]
✍ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
@Meserete_Yared_Asasa
❖ በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረችው ብዙዎች አበው በድርሳናቸው የመሰከሩላትን በድንግልናዋ ጸንታ የኖረችውን ቅድስት ቴክላ ናት፤ ይኽቺ ቅድስት ሴት፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን ከተከተሉት ቅዱሳን ሴቶች አንዷ ስትኾን እጅግ ውብ፣ ሀብታምና የተማረች ነበረች ፤ በዚኽም ከልዑላኑ ታሚሪስ የሚባል ወጣት ሰው አጭቷት ነበር፤ ቅዱስ ጳውሎስ በ45 ዓ.ም. ከአንጾኪያ ከተማ ወደ ኒቆምድያ ከተማ ኼዶ ወንጌልን ሲሰብክ በተመስጦ ኾና ትምህርቱን ትከታተል እንደነበር ከሊቃውንት ቅዱስ አምብሮስና ቅዱስ አውግስጢኖስ ጽፈዋል።
❖ በሐዋርያውም ትምህርት ልቧ በመነካቱ የድንግልና ሕይወትን በመምረጥ ለእናቷ የታሚሪስ እጮኝነቷን ማፍረሷንና ክርስቲያን እንደምትኾን ነገረች፤ ወላጆቿ ግን ርሱን እንዳትሰማ ቢያግባቧትም ርሷ ግን እነርሱን አልሰማቻቸውም፤ በዚኽ ምክንያት አባቷ ዲማኖስና ርምጋኖስ ከሚባሉ ዳኞች ኺዶ ከሰሳት፤ እነርሱም ሊያስገድዷ ቢሞክሩም አልቻሉም፤ ከዚያም የቀደመ ልብሷንና ጌጦቿን ኹሉ ትታ ከቅዱስ ጳውሎስ ጉባኤ ተቀመጠች፡፡
❖ በዚኽ ተበሳጭተው በመኰንኑ ዘንድ እንደገና ከሰዋት፤ ርሱም ሌሎቹ ፈርተው ወደ ቅዱስ ጳውሎስ እንዳይኼዱ በእሳት እንዲያቃጥሏት አዘዘ፤ ርሷ ግን በሚያቃጥሏት ጊዜ ልቧን አጽንታ ቅዱስ ጳውሎስን ተመለከተችው፤ ያን ጊዜ ሐዋርያው በመስቀል ምልክት ባማተበ ጊዜ ወደ እሳቱ ምድጃ ተወረወረች፡፡
❖ “ፈነወ እግዚአብሔር ዝናመ ብዙኀ ወበረደ ወመብረቀ ወኮነ ዕቶነ እሳት ከመ ጠል ቈሪር ወሮጸት ቴክላ ወበጽሐት ኀበ ቅዱስ ጳውሎስ ኀበ ኀሎ መካነ ኅቡአ” ይላል፤ ያን ጊዜ እግዚአብሔር ብዙ ዝናብን፣ በረድን፣ መብረቅን ላከ፤ የእሳቱም ምድጃ እንደ ቀዝቃዛ ጠል ኾነ፤ ቴክላም ሩጣ ቅዱስ ጳውሎስ ተሰዉሮ ወደ አለበት ቦታ በመድረስ፤ ወንጌልን ለመማር በኼደበት ኹሉ ትከተለው ዘንድ ለመነችው፡፡
❖ ከዚያም ከርሱ ጋር አንጾኪያ ከተማ በመኼድ ለዐዲስ አማኞች የእግዚአብሔርን ቃል ትነግራቸው ነበር፤ ከመልኳ ውበትም የተነሣ ከመኳንንቶቹ አንዱ ሊአገባት ፈለገ፤ ርሷ ግን ዘለፈችው፤ ከዚያም ለአንበሶች እንድትጣል ቢደረግም ልክ እንደ ነቢዩ ዳንኤል አንበሶቹ ሳይነኳት በነርሱ መኻከል ኹለት ቀናት ቆየች፤ ከዚኽም በኋላ በኹለት በሬዎች መኻከል አስረው በከተማው ውስጥ አስጐተቷት፤ ነገር ግን ምንም ክፉ ነገር አልደረሰባትም፤ ከዚያም በኋላ ለቀቁዋት፡፡
❖ ርሷም ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ኼደች ርሱም አጽንቶና አረጋግቶ የሰማችውን እንድትመሰክር አዘዛት፡፡ ርሷም ወደ ወላጆቿ ሀገር በመኼድ ስለ ክርስቶስ መሰከረች፤ አባትና እናቷም አምነው ክርስቲያን ኾኑ፤ ሀብተ ፈውስም ተሰጥቷት ብዙዎችን ትፈውሳቸው ነበር በዚኽም “የሕሙማን እናት” በመባል ትታወቃለች፤ በመጨረሻም ተጋድሎዋን ፈጽማ ሐምሌ ፳፭ ዐረፈች፤ መስከረም ፳፯ም ትታሰባለች፤ ሥጋዋም በግብጽ ደቡብ ሰንጋር በሚባል ቦታ ተቀመጠ፤ በዚያም ከሥጋዋ የተነሣ ብዙ ድንቅ ተአምር ተገልጧል፡፡
❖ በርካቶች ቅዱሳን አበው በየድርሳናቸው የቅድስት ቴክላን ቅድስናና ተጋድሎ ጽፈውላታል፤ በተለይ ቅዱስ ሜቶዲየስ ቅድስት ቴክላ ከቅዱስ ጳውሎስ በተማረችው ትምህርት ምን ያኽል ጠንካራ እንደነበረች፤ በጊዜው ከነበሩት የደናግል ኅብረት ከፍ ከፍ ያለች፤ ድንግልናቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ በዝማሬም ትመራቸው እንደነበር ይገልጣል ፡፡
❖ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅም ስለ ርሷ ክብር ሲጽፍላት፡- የተባረከች ድንግል ቴክላ ንጽሕናዋን ሰማዕትነቷን ለልዑል እግዚአብሔር በማቅረብ በአንድ እጇ በሥጋው በደማዊ ፈቃድ ላይ የድል ዘውድን ስትይዝ፤ በሌላኛው እጇ በአደገኛ ሥቃይና መከራ ላይ የክብር አክሊሏን እንደያዘች ዐውቃለኊ” ብሏል፡፡
❖ ቅዱስ ጀሮምም በደብዳቤው ላይ “የጌታ እናት ቅድስት ድንግል ማርያም የደናግልን ማኅበር አስከትላ እናንተን ለመገናኘት የምትመጣባት የዚያቺ ቀን ክብር እንደምን ያለ ነው!... ያን ጊዜ ቴክላ እናንተን ለማቀፍ በደስታ ትበርራለች” ብሏል፡፡
❖ ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያም የድንግልና ሕይወቷን አብነት እንዲያደርጉ ሲያስተምር “የንጽሕና አምሳል ከምትኾን ወደር ከሌላት ከአምላክ እናት በመቀጠል ከሴቶች አስቀድማ ሰማዕት የኾነች ቴክላን ምሳሌ አድርጌ አነሣለኊ፤ እናንተም የርሷን መንፈሳዊ ውበት ተላብሳችኊ ሰማያዊ ጸጋን ለማግኘት ነፍሳኹን በተለያዩ መንፈሳዊ መልካሞች ሥራዎች ታስጌጧት ዘንድ ይገባል” በማለት አስተምሯል፡፡
❖ ኢትዮጵያዊዉ ሊቅ አርከ ሥሉስም ተጋድሎዋን በማዘከር፡-
“ሰላም እብል ለሐዋርያዊት ቴክላ
እግዚአብሔር ዘአኀየላ
ኢያቊስልዋ አናብስት ወእሳተ ዕቶን ኢያሕልላ
እስመ አምነት ትምህርተ ጽድቅ ከመ ጳውሎስ ይቤላ
እስከ ኀደገት አበዊሃ ወገደፈት ብዕላ”
(አንበሶች እንዳያቈስሏት የእሳት ምድጃም እንዳያቃጥላት እግዚአብሔር ያበረታት ሐዋርያዊት ለኾነች ለቴክላ ሰላምታ ይገባል፤ አባቶቿን እስክትተውና ሀብቷን እስክትጥል ድረስ ደርሳ ጳውሎስ እንዳላት የእውነት ትምህርትን አምናለችና) እያለ የተቀደሰ ሕይወቷን በአድናቆት ጽፎላታል፡፡
❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ፦
“ሰላም ለጤቅላ (ቴክላ)
ዘሞአቶ ለተኲላ በገድል
ንጽሕት ድንግል”፡፡
(ንጽሕት ድንግል በገድል ተኲላውን ያሸነፈችው ለኾነች ለጤቅላ ሰላምታ ይገባል)እያለ ያወድሳታል።
✍ የጽሑፉ ምንጭ [አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የጻፈው ተአምኆ ቅዱሳን ንባቡና ትርጓሜው፤ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ የተተረጎመ]
[የቅድስት ቴክላ በረከት ይደርብን]
[ከቅድስት ቴክላ ሕይወት ምን ተማርን? በተለይ እኅቶች]
@Meserete_Yared_Asasa
@Meserete_Yared_Asasa
✍ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ
@Meserete_Yared_Asasa
❖ በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረችው ብዙዎች አበው በድርሳናቸው የመሰከሩላትን በድንግልናዋ ጸንታ የኖረችውን ቅድስት ቴክላ ናት፤ ይኽቺ ቅድስት ሴት፤ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን ከተከተሉት ቅዱሳን ሴቶች አንዷ ስትኾን እጅግ ውብ፣ ሀብታምና የተማረች ነበረች ፤ በዚኽም ከልዑላኑ ታሚሪስ የሚባል ወጣት ሰው አጭቷት ነበር፤ ቅዱስ ጳውሎስ በ45 ዓ.ም. ከአንጾኪያ ከተማ ወደ ኒቆምድያ ከተማ ኼዶ ወንጌልን ሲሰብክ በተመስጦ ኾና ትምህርቱን ትከታተል እንደነበር ከሊቃውንት ቅዱስ አምብሮስና ቅዱስ አውግስጢኖስ ጽፈዋል።
❖ በሐዋርያውም ትምህርት ልቧ በመነካቱ የድንግልና ሕይወትን በመምረጥ ለእናቷ የታሚሪስ እጮኝነቷን ማፍረሷንና ክርስቲያን እንደምትኾን ነገረች፤ ወላጆቿ ግን ርሱን እንዳትሰማ ቢያግባቧትም ርሷ ግን እነርሱን አልሰማቻቸውም፤ በዚኽ ምክንያት አባቷ ዲማኖስና ርምጋኖስ ከሚባሉ ዳኞች ኺዶ ከሰሳት፤ እነርሱም ሊያስገድዷ ቢሞክሩም አልቻሉም፤ ከዚያም የቀደመ ልብሷንና ጌጦቿን ኹሉ ትታ ከቅዱስ ጳውሎስ ጉባኤ ተቀመጠች፡፡
❖ በዚኽ ተበሳጭተው በመኰንኑ ዘንድ እንደገና ከሰዋት፤ ርሱም ሌሎቹ ፈርተው ወደ ቅዱስ ጳውሎስ እንዳይኼዱ በእሳት እንዲያቃጥሏት አዘዘ፤ ርሷ ግን በሚያቃጥሏት ጊዜ ልቧን አጽንታ ቅዱስ ጳውሎስን ተመለከተችው፤ ያን ጊዜ ሐዋርያው በመስቀል ምልክት ባማተበ ጊዜ ወደ እሳቱ ምድጃ ተወረወረች፡፡
❖ “ፈነወ እግዚአብሔር ዝናመ ብዙኀ ወበረደ ወመብረቀ ወኮነ ዕቶነ እሳት ከመ ጠል ቈሪር ወሮጸት ቴክላ ወበጽሐት ኀበ ቅዱስ ጳውሎስ ኀበ ኀሎ መካነ ኅቡአ” ይላል፤ ያን ጊዜ እግዚአብሔር ብዙ ዝናብን፣ በረድን፣ መብረቅን ላከ፤ የእሳቱም ምድጃ እንደ ቀዝቃዛ ጠል ኾነ፤ ቴክላም ሩጣ ቅዱስ ጳውሎስ ተሰዉሮ ወደ አለበት ቦታ በመድረስ፤ ወንጌልን ለመማር በኼደበት ኹሉ ትከተለው ዘንድ ለመነችው፡፡
❖ ከዚያም ከርሱ ጋር አንጾኪያ ከተማ በመኼድ ለዐዲስ አማኞች የእግዚአብሔርን ቃል ትነግራቸው ነበር፤ ከመልኳ ውበትም የተነሣ ከመኳንንቶቹ አንዱ ሊአገባት ፈለገ፤ ርሷ ግን ዘለፈችው፤ ከዚያም ለአንበሶች እንድትጣል ቢደረግም ልክ እንደ ነቢዩ ዳንኤል አንበሶቹ ሳይነኳት በነርሱ መኻከል ኹለት ቀናት ቆየች፤ ከዚኽም በኋላ በኹለት በሬዎች መኻከል አስረው በከተማው ውስጥ አስጐተቷት፤ ነገር ግን ምንም ክፉ ነገር አልደረሰባትም፤ ከዚያም በኋላ ለቀቁዋት፡፡
❖ ርሷም ወደ ቅዱስ ጳውሎስ ኼደች ርሱም አጽንቶና አረጋግቶ የሰማችውን እንድትመሰክር አዘዛት፡፡ ርሷም ወደ ወላጆቿ ሀገር በመኼድ ስለ ክርስቶስ መሰከረች፤ አባትና እናቷም አምነው ክርስቲያን ኾኑ፤ ሀብተ ፈውስም ተሰጥቷት ብዙዎችን ትፈውሳቸው ነበር በዚኽም “የሕሙማን እናት” በመባል ትታወቃለች፤ በመጨረሻም ተጋድሎዋን ፈጽማ ሐምሌ ፳፭ ዐረፈች፤ መስከረም ፳፯ም ትታሰባለች፤ ሥጋዋም በግብጽ ደቡብ ሰንጋር በሚባል ቦታ ተቀመጠ፤ በዚያም ከሥጋዋ የተነሣ ብዙ ድንቅ ተአምር ተገልጧል፡፡
❖ በርካቶች ቅዱሳን አበው በየድርሳናቸው የቅድስት ቴክላን ቅድስናና ተጋድሎ ጽፈውላታል፤ በተለይ ቅዱስ ሜቶዲየስ ቅድስት ቴክላ ከቅዱስ ጳውሎስ በተማረችው ትምህርት ምን ያኽል ጠንካራ እንደነበረች፤ በጊዜው ከነበሩት የደናግል ኅብረት ከፍ ከፍ ያለች፤ ድንግልናቸውን ጠብቀው እንዲኖሩ በዝማሬም ትመራቸው እንደነበር ይገልጣል ፡፡
❖ ሊቁ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅም ስለ ርሷ ክብር ሲጽፍላት፡- የተባረከች ድንግል ቴክላ ንጽሕናዋን ሰማዕትነቷን ለልዑል እግዚአብሔር በማቅረብ በአንድ እጇ በሥጋው በደማዊ ፈቃድ ላይ የድል ዘውድን ስትይዝ፤ በሌላኛው እጇ በአደገኛ ሥቃይና መከራ ላይ የክብር አክሊሏን እንደያዘች ዐውቃለኊ” ብሏል፡፡
❖ ቅዱስ ጀሮምም በደብዳቤው ላይ “የጌታ እናት ቅድስት ድንግል ማርያም የደናግልን ማኅበር አስከትላ እናንተን ለመገናኘት የምትመጣባት የዚያቺ ቀን ክብር እንደምን ያለ ነው!... ያን ጊዜ ቴክላ እናንተን ለማቀፍ በደስታ ትበርራለች” ብሏል፡፡
❖ ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያም የድንግልና ሕይወቷን አብነት እንዲያደርጉ ሲያስተምር “የንጽሕና አምሳል ከምትኾን ወደር ከሌላት ከአምላክ እናት በመቀጠል ከሴቶች አስቀድማ ሰማዕት የኾነች ቴክላን ምሳሌ አድርጌ አነሣለኊ፤ እናንተም የርሷን መንፈሳዊ ውበት ተላብሳችኊ ሰማያዊ ጸጋን ለማግኘት ነፍሳኹን በተለያዩ መንፈሳዊ መልካሞች ሥራዎች ታስጌጧት ዘንድ ይገባል” በማለት አስተምሯል፡፡
❖ ኢትዮጵያዊዉ ሊቅ አርከ ሥሉስም ተጋድሎዋን በማዘከር፡-
“ሰላም እብል ለሐዋርያዊት ቴክላ
እግዚአብሔር ዘአኀየላ
ኢያቊስልዋ አናብስት ወእሳተ ዕቶን ኢያሕልላ
እስመ አምነት ትምህርተ ጽድቅ ከመ ጳውሎስ ይቤላ
እስከ ኀደገት አበዊሃ ወገደፈት ብዕላ”
(አንበሶች እንዳያቈስሏት የእሳት ምድጃም እንዳያቃጥላት እግዚአብሔር ያበረታት ሐዋርያዊት ለኾነች ለቴክላ ሰላምታ ይገባል፤ አባቶቿን እስክትተውና ሀብቷን እስክትጥል ድረስ ደርሳ ጳውሎስ እንዳላት የእውነት ትምህርትን አምናለችና) እያለ የተቀደሰ ሕይወቷን በአድናቆት ጽፎላታል፡፡
❖ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ፦
“ሰላም ለጤቅላ (ቴክላ)
ዘሞአቶ ለተኲላ በገድል
ንጽሕት ድንግል”፡፡
(ንጽሕት ድንግል በገድል ተኲላውን ያሸነፈችው ለኾነች ለጤቅላ ሰላምታ ይገባል)እያለ ያወድሳታል።
✍ የጽሑፉ ምንጭ [አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ የጻፈው ተአምኆ ቅዱሳን ንባቡና ትርጓሜው፤ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ የተተረጎመ]
[የቅድስት ቴክላ በረከት ይደርብን]
[ከቅድስት ቴክላ ሕይወት ምን ተማርን? በተለይ እኅቶች]
@Meserete_Yared_Asasa
@Meserete_Yared_Asasa
#መልአካይ_ሰይጣን ~ ሰባሪ ዜና
@And_Haymanot
👉 "ኦርቶዶክስ" የሚለው ስም የኦርቶዶክሳውያን ብቻ ነው!!!!!
√Share √Share √Share
«ውሉደ ብርሃን የክርስቶስ ቤ/ክ» ብሎ ራሱን ሲጠራ የነበረው የውጉዙ አሰግድ ሣህሉ (?) የተሐድሶ መናፍቃን ቡድን ያሰበውን ያህል በጎችን ከበረት ማውጣት ስላልቻለ ስሙን «ቃለ ዐዋዲ ዘኦርቶዶክስ የክርስቶስ ቤ/ክ» ብሎ ቀይሮ የኦርቶዶክስ ቤ/ክ ነኝ በማለት ፈቃድ እንዲሰጠው ጠይቋል። ይህ በእምነታችን ኃጢአት፣ በባህላችን ነውር፣ በሕጋችንም ወንጀል የሆነ ቅጥፈት ነው። መንግስትም የሌላን ቤተ እምነት ስም በመጠቀምህ ፍቃድ አልሰጥም ማለት እየቻለ "ተቃዋሚ ካለ ሰኞ ሐምሌ 29 3:00 ሰዓት በሰላም ምኒስቴር የሃይማኖት ድርጅቶችና ማሕበራት ምዝገባ ዳይሪክቶሬት ይቅረብ" ብሎ የማርያም መንገድ የሰጠ ይመስላል።
ሰይጣን ሰዎችን ሲያታልል መልአክን እንጂ ራሱን መስሎ አይደለም። የራሱን ኃይልና ብርታት በመግለጥ፣ ከመልአክነት ይልቅ ሰይጣናዊነት እንደሚልቅ በማስረጃ በማስረገጥ አይቀርብም። ስለ ራሱ የሚያቀርበው ነገር የሌለው ባዶ ነውና፣ ሌላን መምሰል እንጂ ራስን መሆን አይሆንለትምና መልአክ-መሳይ (መልአካይ) ሆኖ ይቅበዘበዛል። ተሐድሶዎችም እንዲሁ በመብከን ተሐድሶነታቸውን ሳይሆን ኦርቶዶክስ-መሳይነታቸውን ሊነግሩን ሽሩገድ ይላሉ። 2 ቀናት ብቻ ቀርተውናል! ይህ የብሔርህ አልያም የፖለቲካ ወሬ አይደለም፣ የእውነትም የእምነትም ጉዳይ ነው! ይህንን መልዕክት በውስጥ መስመር ለመምህራን፣ ለሕግ ባለሞያዎች፣ ለባለሥልጣናትና ለብጹዓን አባቶች በማካፈልና በመላክ በቤ/ክ ጉዳይ ለውጥ እንፍጠር! ዳይ ወደ ስራ [©Binyam ZeChristos ሐምለ 26 - 2011]
፪ኛ ቆሮ ፲፩
26 “ብዙ ጊዜ በመንገድ ኼድኹ፤ በወንዝ ፍርኃት፥ በወንበዴዎች ፍርኃት፥ በወገኔ በኩል ፍርኃት፥ በአሕዛብ በኩል ፍርኃት፥ በከተማ ፍርኃት፥ በምድረ በዳ ፍርኃት፥ በባሕር ፍርኃት፥ በውሸተኞች ወንድሞች በኩል ፍርኃት ነበረብኝ፤
27 በድካምና በጥረት ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት፥ በራብና በጥም ብዙ ጊዜም በመጦም፥ በብርድና በራቁትነት ነበርኹ።
28 የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ኹሉ ዐሳብ ነው።”
@And_Haymanot
@And_Haymanot
@And_Haymanot
👉 "ኦርቶዶክስ" የሚለው ስም የኦርቶዶክሳውያን ብቻ ነው!!!!!
√Share √Share √Share
«ውሉደ ብርሃን የክርስቶስ ቤ/ክ» ብሎ ራሱን ሲጠራ የነበረው የውጉዙ አሰግድ ሣህሉ (?) የተሐድሶ መናፍቃን ቡድን ያሰበውን ያህል በጎችን ከበረት ማውጣት ስላልቻለ ስሙን «ቃለ ዐዋዲ ዘኦርቶዶክስ የክርስቶስ ቤ/ክ» ብሎ ቀይሮ የኦርቶዶክስ ቤ/ክ ነኝ በማለት ፈቃድ እንዲሰጠው ጠይቋል። ይህ በእምነታችን ኃጢአት፣ በባህላችን ነውር፣ በሕጋችንም ወንጀል የሆነ ቅጥፈት ነው። መንግስትም የሌላን ቤተ እምነት ስም በመጠቀምህ ፍቃድ አልሰጥም ማለት እየቻለ "ተቃዋሚ ካለ ሰኞ ሐምሌ 29 3:00 ሰዓት በሰላም ምኒስቴር የሃይማኖት ድርጅቶችና ማሕበራት ምዝገባ ዳይሪክቶሬት ይቅረብ" ብሎ የማርያም መንገድ የሰጠ ይመስላል።
ሰይጣን ሰዎችን ሲያታልል መልአክን እንጂ ራሱን መስሎ አይደለም። የራሱን ኃይልና ብርታት በመግለጥ፣ ከመልአክነት ይልቅ ሰይጣናዊነት እንደሚልቅ በማስረጃ በማስረገጥ አይቀርብም። ስለ ራሱ የሚያቀርበው ነገር የሌለው ባዶ ነውና፣ ሌላን መምሰል እንጂ ራስን መሆን አይሆንለትምና መልአክ-መሳይ (መልአካይ) ሆኖ ይቅበዘበዛል። ተሐድሶዎችም እንዲሁ በመብከን ተሐድሶነታቸውን ሳይሆን ኦርቶዶክስ-መሳይነታቸውን ሊነግሩን ሽሩገድ ይላሉ። 2 ቀናት ብቻ ቀርተውናል! ይህ የብሔርህ አልያም የፖለቲካ ወሬ አይደለም፣ የእውነትም የእምነትም ጉዳይ ነው! ይህንን መልዕክት በውስጥ መስመር ለመምህራን፣ ለሕግ ባለሞያዎች፣ ለባለሥልጣናትና ለብጹዓን አባቶች በማካፈልና በመላክ በቤ/ክ ጉዳይ ለውጥ እንፍጠር! ዳይ ወደ ስራ [©Binyam ZeChristos ሐምለ 26 - 2011]
፪ኛ ቆሮ ፲፩
26 “ብዙ ጊዜ በመንገድ ኼድኹ፤ በወንዝ ፍርኃት፥ በወንበዴዎች ፍርኃት፥ በወገኔ በኩል ፍርኃት፥ በአሕዛብ በኩል ፍርኃት፥ በከተማ ፍርኃት፥ በምድረ በዳ ፍርኃት፥ በባሕር ፍርኃት፥ በውሸተኞች ወንድሞች በኩል ፍርኃት ነበረብኝ፤
27 በድካምና በጥረት ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት፥ በራብና በጥም ብዙ ጊዜም በመጦም፥ በብርድና በራቁትነት ነበርኹ።
28 የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ኹሉ ዐሳብ ነው።”
@And_Haymanot
@And_Haymanot
“ግርግር ለሌባ ያመቻል” እንዲሉ አበው አሁንም መዘናጋታችንን እና በሌሎች ሥጋዊ ተግባራት መጠመዳችንን
ያዩ ተግባራቸውን አንድ እርምጃ ከፍ በማድረግ ከንዋያተ ቅድሳት ዘረፋ ወደ ስያሜ እና መጠርያ ዘረፋ ተሸጋግረዋል፡፡ እኛም ተኝተናል!
መናፍቃን ስማቸውን ከ"ውሉደ ብርሃን የክርስቶስ ቤተክርስትያን" ወደ "ቃለ ዘአዋዲ ዘ ኦርቶዶክስ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን" ሊያስለውጡ ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል፡፡ እውነተኛ የኦርቶዶክስ ልጆች ከሆንን እና ስለቅድስት ቤተክርስቲያናችን የሚገድደን ከሆነ ይህንን መቃወም ግድ ይለናል! በቤተክርስቲያን ነዋያት
እና ስያሜ መጠቀም ይብቃ!
²⁶ “ብዙ ጊዜ በመንገድ ኼድኹ፤ በወንዝ ፍርኃት፥ በወንበዴዎች
ፍርኃት፥ በወገኔ በኩል ፍርኃት፥ በአሕዛብ በኩል ፍርኃት፥ በከተማ
ፍርኃት፥ በምድረ በዳ ፍርኃት፥ በባሕር ፍርኃት፥ በውሸተኞች ወንድሞች በኩል ፍርኃት ነበረብኝ፤
²⁷ በድካምና በጥረት ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት፥ በራብና
በጥም ብዙ ጊዜም በመጦም፥ በብርድና በራቁትነት ነበርኹ።
28 የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ
የአብያተ ክርስቲያናት ኹሉ ዐሳብ ነው።” ፪ኛ ቆሮ ፲፩
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ያዩ ተግባራቸውን አንድ እርምጃ ከፍ በማድረግ ከንዋያተ ቅድሳት ዘረፋ ወደ ስያሜ እና መጠርያ ዘረፋ ተሸጋግረዋል፡፡ እኛም ተኝተናል!
መናፍቃን ስማቸውን ከ"ውሉደ ብርሃን የክርስቶስ ቤተክርስትያን" ወደ "ቃለ ዘአዋዲ ዘ ኦርቶዶክስ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን" ሊያስለውጡ ዝግጅታቸውን ጨርሰዋል፡፡ እውነተኛ የኦርቶዶክስ ልጆች ከሆንን እና ስለቅድስት ቤተክርስቲያናችን የሚገድደን ከሆነ ይህንን መቃወም ግድ ይለናል! በቤተክርስቲያን ነዋያት
እና ስያሜ መጠቀም ይብቃ!
²⁶ “ብዙ ጊዜ በመንገድ ኼድኹ፤ በወንዝ ፍርኃት፥ በወንበዴዎች
ፍርኃት፥ በወገኔ በኩል ፍርኃት፥ በአሕዛብ በኩል ፍርኃት፥ በከተማ
ፍርኃት፥ በምድረ በዳ ፍርኃት፥ በባሕር ፍርኃት፥ በውሸተኞች ወንድሞች በኩል ፍርኃት ነበረብኝ፤
²⁷ በድካምና በጥረት ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት፥ በራብና
በጥም ብዙ ጊዜም በመጦም፥ በብርድና በራቁትነት ነበርኹ።
28 የቀረውንም ነገር ሳልቆጥር፥ ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ
የአብያተ ክርስቲያናት ኹሉ ዐሳብ ነው።” ፪ኛ ቆሮ ፲፩
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
ሰበር ዜና
እንኳን ደስ አላችሁ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስም "ውሉደ ብርሃን የክርስቶስ ቤተክርስቲያን" እያለ ራሱን የሚጠራው ጸረ ወንጌል ድርጅት ሕዝብን ለማወናበድ እንዲመችው በማቀድ የስም ለውጥ እንዲሰጠው ማለትም ቃለ አዋዲ ዘኦርቶዶክስ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ተብሎ እንዲጠራ ለኢትዮጵያ ፌድራላዊ ዴሞክራሳዊ ሪፐብሊክ የሰላም ሚኒስተር ቢያመለክትም ተቃዋሚ ካለ እንዲቀርብ በሚንስትሩ ጽ/ቤት የሃይማኖት ድርጅቶችና ማህበራት ምዝገባ ዳሬክትሬት ሐምሌ 29 ቀን 2011 ዓም ከጠዋቱ 3:00 እንዲቀርብ ትእዛዝ መሥጠቱ በጋዜጦች እና በማህበራዊ ሚድያ ሰዘገብ ቆይቷል በዚህም ይህንን የተዋህዶ ልጆችን ድምፅ ችል ባለማለት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሕግ መምሪያ ክፍል ኃላፊ የሆኑት አባ ገብረ ስላሴ እና የስብከተ ወንጌል መምሪያ ኃላፊ መላአከ ሰላም ቀሲስ ሰሎሞን ቶልቻ ዝግጅታቸውን አጠናቀው ሐምሌ 29 ቀን በቀጠሮው ሰአት ተቃውሞአቸውን ይዘው እንደሚቀርቡ ከታመኑ ምንጭ ታሰምቷል ድል በክርስቶስ ደም ለተዋጀች ለኦርቶዶክስዊት ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን በጸሎት አስቧቸው፡፡
መረጃው ከማህበራዊ ድህረ ገፅ ተገኘ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot
እንኳን ደስ አላችሁ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ስም "ውሉደ ብርሃን የክርስቶስ ቤተክርስቲያን" እያለ ራሱን የሚጠራው ጸረ ወንጌል ድርጅት ሕዝብን ለማወናበድ እንዲመችው በማቀድ የስም ለውጥ እንዲሰጠው ማለትም ቃለ አዋዲ ዘኦርቶዶክስ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ተብሎ እንዲጠራ ለኢትዮጵያ ፌድራላዊ ዴሞክራሳዊ ሪፐብሊክ የሰላም ሚኒስተር ቢያመለክትም ተቃዋሚ ካለ እንዲቀርብ በሚንስትሩ ጽ/ቤት የሃይማኖት ድርጅቶችና ማህበራት ምዝገባ ዳሬክትሬት ሐምሌ 29 ቀን 2011 ዓም ከጠዋቱ 3:00 እንዲቀርብ ትእዛዝ መሥጠቱ በጋዜጦች እና በማህበራዊ ሚድያ ሰዘገብ ቆይቷል በዚህም ይህንን የተዋህዶ ልጆችን ድምፅ ችል ባለማለት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የሕግ መምሪያ ክፍል ኃላፊ የሆኑት አባ ገብረ ስላሴ እና የስብከተ ወንጌል መምሪያ ኃላፊ መላአከ ሰላም ቀሲስ ሰሎሞን ቶልቻ ዝግጅታቸውን አጠናቀው ሐምሌ 29 ቀን በቀጠሮው ሰአት ተቃውሞአቸውን ይዘው እንደሚቀርቡ ከታመኑ ምንጭ ታሰምቷል ድል በክርስቶስ ደም ለተዋጀች ለኦርቶዶክስዊት ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ምእመናን በጸሎት አስቧቸው፡፡
መረጃው ከማህበራዊ ድህረ ገፅ ተገኘ
@And_Haymanot
@And_Haymanot_bot