ስንክሳር
7.32K subscribers
825 photos
4 videos
37 files
237 links
በስንክሳር channal ስንክሳሩ ተገልጦ ቅዱሳን ይዘከራሉ፣ ወቅቱን የጠበቁ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡ ይከታተሉን!
Download Telegram
እንኩዋን ለጌታችን ቅዱስ #ዕፀ_መስቀል የተአምር በዓል በሰላም አደረሳችሁ
#ቅዱስ_ዕፀ_መስቀል +"+
የዕፀዋት ሁሉ ንጉሣቸው የሚሆን ቅዱስ ዕፀ መስቀል
ለእኛም #ኃይላችን: #ቤዛችን: #መዳኛችን: #የድል_
ምልክታችን ነው:: መስቀል #በደመ_ክርስቶስ ተቀድሷልና
አንክሮ: ስግደት ክብርና ምስጋና በፀጋ ይገባዋል::
#ቅዱስ_መስቀለ_ክርስቶስ ላለፉት 2,000 ዓመታት ብዙ
ተአምራትን ሠርቷል:: ከእነዚህ መካከልም አንዱን በዚህ
ዕለት እናዘክራለን:: ታሪኩ: ምሥጢሩስ እንደ ምን ነው
ቢሉ:- በ400 ዓ/ም አካባቢ በግብፅ #አባ_ቴዎፍሎስ ፓትርያርክ
ሳለ: #ቅዱስ_ቄርሎስም በሊቀ ዲቁና ሲያገለግል ሳለ
በእስክንድርያ ከተማ 2 ደሃ ክርስቲያኖች ይኖሩ ነበር:: የቀን
ሠራተኞች በመሆናቸው ከዕለት ምግብ አይተርፋቸውም
ነበር::
ከ2ቱ አንዱ ፍጹም አማኝ ሲሆን ሌላኛው ግን ተጠራጣሪ
ነበር:: ስለ ምን ነው ቢሉ:- በከተማዋ ብዙ ሃብታም አይሁድ
ነበሩና እነሱን እየተመለከተ ነው:: ለእርሱ #ክርስትና ማለት
ገንዘብ መስሎታልና ዘወትር "ለምን ክርስቶስን እያመለክን ድሃ
እንሆናለን?" እያለ ያማርር ነበር::
"ያዛቆነ ሰይጣን . . . " እንደሚባለው አንድ ቀን ባልጀራውን "ለምን ክርስቶስን አንክደውም? (ሎቱ ስብሐት!) እርሱን ከማምለክ የተረፈን ድህነት ብቻ ነው" አለው:: ባልንጀራው ሊመክረው ሞከረ:-
"እግዚአብሔር አምላከ-ነዳያን ነው:: ቅዱሳን #ነቢያት :
#ሐዋርያት : #ጻድቃን: #ሰማዕታትም በሥጋዊ ሃብት ነዳያን
ነበሩ" ብሎ ቢለውም ሰይጣን ሠልጥኖበታልና
አልሰማውም:: ያ ስሑት ደሃ ወዲያው ወጥቶ ወደ ማሕበረ አይሁድ ሔደ::
እነርሱ በቁጥር ብዙ ሁነው በአንድነት ይኖሩ ነበር::
"ሥራ ቅጠሩኝ" አላቸው:: "በእምነት አትመስለንምና
አይሆንም" አሉት:: ያን ጊዜ ለአለቃቸው ( #ፈለስኪኖስ)
"አንተ ሥራ ቅጠረኝ እንጂ እኔ ክርስቶስን እክዳለሁ" (ሎቱ
ስብሐት!) አለው::
ወዲያው የከተማው ሕዝብ ተጠርቶ: በጉባኤ መካከል
ሊያስክዱት ተዘጋጁ:: በፍጥነትም #መስቀል: ጦር: ሐሞት
አዘጋጁ:: ስዕለ ስቅለቱንም አመጡ:: ያን ደሃ ከሃዲም
"በል-ክርስቶስ ሆይ! ካድኩህ ብለህ ምራቅህን ትፋበት:
ሐሞቱን አፍስበት: በጦርም ውጋው" (ሎቱ ስብሐት!)
አሉት::
ያ ልቡ የደነቆረ መስቀለ ክርስቶስ ላይ ተፋ:: ሐሞትም
አፈሰሰበት:: በመጨረሻ በጦር ሲወጋው ግን ድንቅ ተአምር
ተገለጠ:: በጦር ከተወጋው ከመስቀሉ ጐን ብዙ ደም
ፈሰሰ:: ለረዥም ሰዓትም አላቁዋረጠም:: በዚህች ሰዓት
በአካባቢው የነበሩ ሁሉም አይሁድ በግንባራቸው ተደፍተው
ለክርስቶስና ቅዱስ መስቀሉ ሰገዱ::
ሁሉም በአንድነት "#ክርስቶስ_የአብርሃም_አምላክ_ነው
:: #መድኃኒትም_ነው " ሲሉ እየጮሁ ተናገሩ:: ባለማወቅ
ስላደረጉት እነርሱ ምሕረትን ሲያገኙ ያ አዕምሮ የጐደለውን
ደሃ ግን ዘወር ብለው ሲያዩት ወደ ድንጋይነት ተቀይሮ ነበር::
ነፍሱንም: ሥጋውንም በፈቃዱ አጠፋ::
የአይሁድ አለቃም ዐይነ ሥውር ዘመድ ነበረውና ወዲያው
አምጥቶ ከደሙ ቢቀባው ዐይኑ በራ:: ታላቅ ደስታም በዚያ
ሥፍራ ተደረገ:: ነገሩን የሰሙት #ቅዱሳን #ቴዎፍሎስ እና
#ቄርሎስ ሲመጡ ደሙ ከመፍሰስ አላቆመም ነበር::
በተአምሩ ደስ ተሰኝተው: ከደመ ክርስቶስ ለበረከት ተቀቡ::
የፈሰሰውን #ቅዱስ_ደም ከነ አፈሩ አንስተው: መስቀሉን
በትከሻ ተሸክመው: በፍፁም እልልታና ዝማሬ ወስደው በቤተ
መቅደስ አኑረውታል:: የከተማዋ ሁሉም አይሁድም
በክርስቶስ አምነው ተጠምቀዋል::
#ቅዱስ_ዕፀ_መስቀል
ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ቸር አምላካችንና
መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን ከሰማያዊ
ክብሩ ወደ ምድር ወርዶ: በማሕጸነ #ማርያም_እግዝእት
በኪነ ጥበቡ ተጸንሶ: በኅቱም ድንግልና ተወልዶ: በፈቃዱ
መከራ መስቀልን ተቀብሎ:
ከግራ ቁመት:
ከገሃነመ እሳት:
ከሰይጣን ባርነት:
ከኃጢአት ቁራኝነትም አድኖናል::
እምእቶነ እሳት ዘይነድድ አንገፈነ እንዳለ
ሊቁ::
ምንም መስቀል በብሉይ የወንጀለኞች መቅጫ ሆኖ
ቢቆይም እግዚአብሔር ለዓለም መዳኛነት የመረጠው
ነውና ሕብረ ትንቢቶች ሲነገሩለት: በብዙ ሕብረ
አምሳልም ሲመሰል ኑሯል:: ከተፈጥሯችን ጀምሮ ዓለም
ራሷ አርአያ #ትዕምርተ_መስቀል ናት::
እግዚአብሔር ለቃየን እንዳይገድሉት ከሰጠው ምልክት
(ዘፍ. 4:15) ጀምሮ
#ይስሐቅ ሊሰዋ የተሸከመው እንጨት (ዘፍ. 22:6):
#ቅዱስ_ያዕቆብ ያያት የወርቅ መሰላል (ዘፍ. 28:12):
ያዕቆብ የዮሴፍን ልጆች የባረከበት መንገድ (ዘፍ.
48:14):
ባሕረ ኤርትራን የከፈለችው #የሙሴ_በትር (ዘጸ.
14:15):
# የናሱ_ዕባብ የተሰቀለበት እንጨት (ዘኁ. 21:8)
ጨምሮ በርካታ ምሳሌዎች ለቅዱስ መስቀሉ
መኖራቸውን መተርጉማን ተናግረዋል::
# ቅዱስ_ዳዊትን የመሰሉ ነቢያት ደግሞ "ለሚፈሩሕ
ከቀስት ያመልጡ ዘንድ ምልክትን ሰጠሃቸው" እያሉ
መስቀሉን ከርቀት ተመልክተዋል:: (መዝ. 59:4)
በሐዲስ ኪዳን ግን ምሳሌው ገሃድ ሆኖ: ጌታ በዕፀ
መስቀል ላይ ተሰቅሎ ሥጋውን ቆረሰበት: ደሙን
አፈሰሰበት: ዓለምንም አዳነበት::
ስለዚህም "#መስቀል_ብርሃን_ለኩሉ_ዓለም :
#መሠረተ_ቤተ_ክርስቲያን " ተብሎ የሚመሰገን ሆኗል::
#ቅዱስ_ያሬድ ሊቁ አክሎ "መስቀል መልዕልተ ኩሉ
ነገር: ያድኅነነ እምጸር" ብሎ ጠላትን ማሳፈሪያ መሆኑን
ይነግረናል:: #ብርሃነ_ዓለም #ቅዱስ_ዻውሎስም ስለ
መስቀሉ አምልቶ አጉልቶ አስተምሯል:: መመኪያችን
ነውና:: (1ቆሮ. 1:18, ገላ. 6:14)
አንዳንዶቹ እኛን 'የተሰቀለውን ትታቹሃል' ይሉናል::
የተሰቀለውማ የጌቶች ጌታ: የነገሥታት ንጉሥ:
የአማልክት አምላክ: ሁሉ በእጁ የተያዘ:
#ኢየሱስ_ክርስቶስ ነውና ከኦርቶዶክስ በላይ የሚያመልክ
በወዴት አለና::
ነገር ግን መስቀሉን ንቆ የተሰቀለውን ማክበር
አይቻልምና እኛ ለመስቀሉ የጸጋ ስግደትን እንሰግዳለን:
እናመሰግነዋለን: እናከብረዋለን: ቤዛ: ጽንዕ: መድኃኒት:
ኃይል እያልንም እንጠራዋለን:: አባቶቻችን በመስቀሉ
ምርኩዝነት ማዕበለ ኃጢአትን: ባሕረ እሳትን
ተሻግረዋል::
በመስቀሉ ቢመኩ አጋንንትን ድል ነስተዋል:: ጠላትንም
አሳፍረዋል:: እኛም በመስቀሉ አምነን ከብረን: ገነን
እንኖራለን:: ተጠቅመንበታልና ከራሳችን ሕይወት በላይ
ምስክርን አንፈልግም::