ስንክሳር
7.32K subscribers
825 photos
4 videos
37 files
237 links
በስንክሳር channal ስንክሳሩ ተገልጦ ቅዱሳን ይዘከራሉ፣ ወቅቱን የጠበቁ መረጃዎችን ያገኛሉ፡፡ ይከታተሉን!
Download Telegram
እንኩዋን ለካህኑ #ሰማዕት_ቅዱስ_አልዓዛር እና
ለቅዱሳን ቤተሰቡ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም
አደረሳችሁ
#ቅዱስ_አልዓዛር_ካህን
ይህ ቅዱስ #የብሉይ_ኪዳን_ሰማዕታት ተብለው
ከሚታወቁት ዋነኛው ነው:: የነበረበት ዘመንም ቅድመ ልደተ
ክርስቶስ ሲሆን " #ዓመተ_መቃብያን / #ዘመነ_ካህናት "
ይባላል::
በወቅቱ ሰሎሜ የምትባል ደግ ሴት አግብቶ ይኖር የነበረው
ቅዱስ አልዓዛር በኢየሩሳሌም ተወዳጅ ነበር:: ሐረገ ትውልዱ
ከአሮን ወገን ነውና በክህነቱ ተግቶ ያገለግል ነበር:: በዚያ
ላይ ሊቀ ካህንነትን በመመረጡ ሕዝቡን ይሠራ: ያስተምር:
ያስተዳድር ነበር::
ቅዱስ አልዓዛር ከተባረከች ሚስቱ ሰሎሜ 7 ወንዶች ልጆችን አፍርቷል:: እነርሱንም በሥርዓት አሳድጐ የቤተ እግዚአብሔር አገልጋዮች እንዲሆኑ አድርጐ ነበር:: በዚያው
ዘመን በኢየሩሳሌም አካባቢ የሚኖሩ 3 እኩያን (ክፉ) ካህናት
ነበሩ:: እነዚሁም ሕዝቡን ከማስቸገር: ፈጣሪን ከማሳዘን ቦዝነው
አያውቁም ነበር:: የክፋታቸው መጨረሻ ግን የገዛ ሃገራቸውን
ማጥፋት ሆነ:: ነገሩ እንዲህ ነው:- 3ቱም ተመካክረው
የአልዓዛርን የሊቀ ካህንነት ቦታ ሊቀሙ ወስነው ወደ እርሱ
ሔዱና እንዲህ አሉት::
"ሹመት በተርታ: ሥጋ በገበታ" ሲሆን ያምራልና እኛ
በተራችን በወንበሩ ላይ እንቀመጥ::" እርሱ ግን "ሕዝቡን ጠይቃችሁ ተሾሙ" አላቸው:: እነርሱም
ሕዝቡን ጠርተው "ሹመት ይገባናል" ቢሏቸው ሕዝቡ መልሶ
"አልዓዛርን የሾመው እግዚአብሔር ነውና እናንተም ከፈጣሪ ጠይቃችሁ ተሾሙ" አሏቸው:: በዚህ ጊዜ 3ቱ እኩያን ተቆጡ:: ምክንያቱም እግዚአብሔር እንደ ማይሰጣቸው ያውቃሉና:: ወዲያው ግን 3ቱም
ከአካባቢው ጠፉ:: ከኢየሩሳሌም ወጥተው ወደ ጨካኙ
የግሪክ ንጉሥ አንጥያኮስ ሔዱ::
+አንጥያኮስ ማለት "ቀኝ ዐይናችሁን ገብሩልኝ" የሚል ንጉሥ ነው:: እርሱን "#ኢየሩሳሌም ባለቤት የላትምና ሒደህ ውረራት" አሉት:: "አጥሩ ጥብቅ ነው:: በምን እገባለሁ?"
ቢላቸው "እኛ በመላ እናስገባሃለን" አሉት:: እርሱም
240,000 ሠራዊት አስከትቶ ወረደ:: እነርሱ ቀድመው ወደ ኢየሩሳሌም ገብተው ያስወሩ ጀመር::
"እናንተ ሹመት ብትነሱንም እኛ ግን አንጥያኮስን ያህል ንጉሥ
በእሥራኤል አምላክ አሳምነን መጣን" እያሉ ይሰብኩ ገቡ::
ቅዱስ አልዓዛር "አትስሟቸው:: በዚያም ላይ አሕዛብ
የተቀደሰውን ምድር መርገጥ የለባቸውም" ብሎ ነበር::
ነገር ግን አንዳንድ ችኩሎች አይጠፉምና ፈጥነው
የከተማዋን በር ከፈቱት:: ሠራዊቱን ደብቆ ትንሽ ራሱን የቆመ
የመሰለው አንጥያኮስ በምክንያት: በክፋትና በመላ ሁሉን
ሠራዊቱን አስገባ:: የሚገርመው በጊዜው የከተማዋ ሕዝብ
12 እልፍ (120,000) ሲሆን ንጉሡ ያስገባው ሠራዊት ግን
24 እልፍ (240,000) ሆኖ ተገኘ::
ወዲያው አንጥያኮስ ሕዝቡን ሰበሰበና አልዓዛርን ለብቻው
ጠርቶ ተናገረው:: "አንተ አምላክህን እንደምትወድ
ሰምቻለሁ:: አንተ የበጉን መስዋዕት በልተህ: #ለስዕለ_
ኪሩብ ሰግደህ: ሕዝቡን ግን እሪያ (አሳማ) እንዲበላና
ለጸፀሐይ እንዲሰግድ አድርግልኝ" አለው::
ቅዱስ አልዓዛር መለሰለት:- "እግዚአብሔር የሾመኝኮ በጐ
ሃይማኖትን ላስተምር እንጂ ለክፋት አይደለም:: ለሕዝቤ
የክፋት አብነት ፈጽሞ አልሆንም" አለው:: ያን ጊዜ ንጉሡ
በቅዱሱ ላይ ተቆጣ:: "የምልህን ካላደረግህ ብዙ ግፍ
ይደርስብሃል" ቢለው ቅዱሱ መልሶ "የፈለግኸውን አድርግ"
አለው:: በዚያን ጊዜ ንጉሡ የቅዱሱን ሚስትና 7 ልጆች
እንዲያመጡለት አዘዘ:: ቅዱሱ እያየ ከፊቱ ላይ 7ቱንም
ልጆቹን በሰይፍ አስመታቸውና 7ቱም ወደቁ:: ለአንድ አባት
ይህ የመጨረሻው መራራ ፈተና ነው:: #አልዓዛር ግን ምን
አንጀቱ በኀዘን ቢቃጠልም ከልጆቹ ለእግዚአብሔር አድልቷልና
ቻለው ታገሠው::
በዚህ ለውጥ እንዳልመጣ ያየው ንጉሡ ሌላ ፍርድ
ተናገረ:: ቅዱሱንና ሚስቱን ( #ሰሎሜን ) በፈትል ጠቅልለው
በሠም ነከሯቸው:: (ጧፍ እንደሚሠራበት መንገድ ማለት
ነው:: )
አሁንም ግን ከአምልኮታቸው ፈቀቅ ባለማለታቸው ትልቅ
ብረት ምጣድ ተጥዶ: 2ቱም ከነነፍሳቸው እንዲቃጠሉ
ተደረገ:: ቀጥሎም ሕዝቡን እንዲፈጁ አዋጅ ወጣ::
በከተማዋ ከነበረው ሕዝብ 40,000 ያህሉ ተገደሉ::
+40,000 ያህሉ ሲማረኩ 40,000 ያህሉን ደግሞ # ይሁዳ
የሚባል አርበኛ በር ሰብሮ ይዟቸው ሸሸ:: "እንሾማለን:
እንሸለማለን" ብለው ሕዝባቸውን ያስፈጁ እነዚያ ካህናትም
#እግዚአብሔር ፈርዶባቸው እነርሱም ተገደሉ:: ቅዱሱ
የአልዓዛር ቤተሰብ ግን የክብርን አክሊል አግኝተዋል::
#የእሥራኤል_አምላክ ቸሩ_እግዚአብሔር_እንዲህ ካለው_መከራ_በኪነ_ጥበቡ_ይሰውረን::_ከቅዱሳኑ_በረከትም_አይለየን::
#ቅዱሳን_ስምዖንና_ዮሐንስ
በቤተ ክርስቲያን ታሪክ አስደናቂ ታሪክ ካላቸው #ጻድቃን
እነዚህ 2ቱ ቅድሚያውን ይይዛሉ:: እርሱስ እንደ ምን ነው
ቢሉ:-
ቅዱሳኑ በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን ሶርያ አካባቢ ተወልደው
ያደጉ ክርስቲያኖች ናቸው::
ዘመዳሞች ከመሆናቸው ባሻገር አብረው ስላደጉ እጅጉን
ይፋቀሩ ነበር:: የዋሃንም ነበሩ:: ወጣት በሆኑ ጊዜ ትልቁ
#ዮሐንስ ሚስት አገባ:: ታዲያ አንድ ቀን ከጌታችን መቃብር
#ኢየሩሳሌም ደርሰው ሲመለሱ #ገዳመ_ዮርዳኖስ አካባቢ
ደረሱ:: እርስ በርሳቸውም "ይህ ገዳምኮ የመላእክት ማደሪያ
ነው" ተባባሉ::
በዚያውም መንነው ለመቅረት አሰቡ:: ፈረስና ንብረታቸውን
ለዘመዶቻቸው ልከው ጸሎት አደረሱ:: ፈቃደ እግዚአብሔርን
ሊረዱም ዕጣ ተጣጣሉ:: ዕጣውም "ወደ ገዳም ሒዱ"
የሚል ስለሆነ ተቃቅፈው ደስ አላቸው::
ወደ ገዳሙ ሲደርሱም አበ ምኔቱ #አባ_ኒቅዮስ ፈጣሪ
አዞት የገዳሙን በር ከፍቶ ጠበቃቸው:: ተቀብሎ
ሲያስገባቸውም አንድ ደግ መነኮስ ሲያልፍ: ቆቡ ቦግ ቦግ
እያለ እንደ ፋና ሲያበራ እና #መላእክት ከበውት አዩ::
ወዲያውም አበ ምኔቱን "እባክህ አመንኩሰን" አሉት::
እርሱም የአምላክ ፈቃድ ነውና በማግስቱ አመነኮሳቸው::
ፍቅረ ክርስቶስ ገዝቷቸዋልና በጥቂት ዓመታት ተጋድሎ
ከብቃት (ከጸጋ) ደረሱ:: 2ቱም ቆመው በፍቅር ሲጸልዩ
የብርሃን አክሊል በራሳቸው ላይ ይወርድ ነበር:: አካላቸውም
በሌሊት ያበራ ነበር::
እንዲህ ባለ ቅድስና ለዓመታት ቆይተው ከገዳሙ ወደ ጽኑ
በርሃ ሊሔዱ ስለ ፈለጉ የገዳሙ በር በራሱ ተከፈተ:: አበ
ምኔቱ አባ ኒቆን (ኒቅዮስ) እያነባ በጸሎት ሸኛቸው::
በበርሃም በጠባቡ መንገድ: በቅድስና ተጠምደው ለ29
ዓመታት ተጋደሉ:: በዚህ ሰዓት ግን 2ቱን የሚለያይ ምክንያት
ተፈጠረ::
#እግዚአብሔር ቅዱስ ስምዖን ወደ ከተማ እንዲገባ: ቅዱስ
ዮሐንስ ግን በዚያው እንዲቆይ አዘዘ:: 2ቱ ለረዥም ሰዓት
ተቃቅፈው ተላቅሰው ተለያዩ:: ከ50 ዓመታት በላይ
ተለያይተው አያውቁም ነበርና::
#ቅዱስ_ስምዖን ወደ ከተማ ሲገባ ክብሩን ይደብቅ ዘንድ
እንደ እብድ ሆነ:: በዚህ ምክንያትም የወቅቱ ከተሜዎች
ይንቁት: በጥፊም ይመቱት ነበር:: (እባካችሁ ብዙ
በየመንገዱ የወደቁ አባቶች አሉና እንጠንቀቅ!) ቅዱሱ ግን
ስለ እነርሱ ይጸልይ ነበር::
በከተማዋ የነበሩ እብዶችን ሁሉንም በተአምራት
ፈወሳቸው:: አንድ ቀን ግን ክርስቲያን ነን የሚሉ ሰዎች
ደብድበውት ደከመ:: የእግዚእብሔር መልአክ ወርዶ "ና
ልውሰድህ" ብሎ ዮሐንስን ከበርሃ: ስምዖንን ከከተማ
በዚህች ቀን ወሰዳቸው:: እነሆ ብርሃናቸው ዛሬም ድረስ
ለሚያምንበት ሁሉ ያበራል::
እንኩዋን ለሰማዕታት ቅዱስ #እንጣዎስ እና ቅዱስ
#ያዕቆብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ
#ቅዱስ_እንጣዎስ_አሞራዊ ይሕ ቅዱስ በቀደመ ሕይወቱ ክርስቲያኖችን የሚጠላ
አስቸጋሪ አረማዊ ነበር:: ሃገሩ #ሶርያ ( #ደማስቆ ) ሲሆን
ግብሩ ጣዖት ማምለክና መስረቅ ነበር:: በቅድስት ቤተ
ክርስቲያንና በምዕመናን ላይም ግፍን ፈጽሟል:: በሥጋዊ
ጉልበቱ ኃይለኛ ስለ ነበር የተፈራ ነው::
ሁልጊዜ በጠዋት ወደ #ቤተ_ክርስቲያን ይሔዳል::
የሚሔደው ግን ንዋያተ ቅድሳትን ለመዝረፍ: አንድም
ካህናትን ለመደብደብ ነበር:: የሚገርመው ግን የወቅቱ
ምዕመናንና ካህናት ይህን ሁሉ እያደረገባቸው አይጠሉትም::
ይልቁኑ ይጸልዩለት ነበር እንጂ:: ምክንያቱም ክርስትና ማለት
ጠላትን መውደድ ነውና:: (ማቴ. 7)
የእግዚአብሔር ትዕግስትና የምዕመናን ጸሎት ተደምሮው
አንድ ቀን ፍሬ አፈራ:: እንጣዎስ እንደ ለመደው ለክፉ ሥራ
ወደ # ቅዱስ_ቴዎድሮስ ቤተ ክርስቲያን ይሔዳል:: ከዚያም
እንደ ደረሰ ወደ ውስጥ ገብቶ: የሚማታውን ተማቶ:
የሚዘርፈውንም ዘርፎ: የተረፉትን ንዋያተ ቅድሳት በእሳት
አቃጠላቸው::
#እግዚአብሔር ከዚህም በላይ ታጋሽ ነውና አላጠፋውም::
"ዘኢይፈቅድ ለኃጥእ ሞቶ" እንዲል የኃጢአተኛውን መመለስ
እንጂ መሞቱን አይፈልግም:: ለዚያም ነው ዛሬ ይሔ ሁሉ
ግፍ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየተሠራ እግዚአብሔር
እንደማያይ ዝም የሚለው:: ለሁሉም ቀን አለውና በፈረደ ቀን
ግን በፊቱ የሚቆም አይኖርም::
እንጣዎስ ግን የሠራውን ሠርቶ እወጣለሁ ሲል
አልተሳካለትም:: ከበሩ አካባቢ ሲደርስ: ከወደ ሰማይ
አካባቢ ድምጽ ሰምቶ ቀና ሲል መላእክት እንደሱ ዓይነት
ኃጢአተኞችን አሰልፈው በጦርና በቀስት ሲወጉአቸው
ተመለከተ::
ድንገት ግን ከመላእክቱ አንዱ ዘወር ብሎ አንድ ቀስት ወደ
እንጣዎስ ወረወረ (ተኮሰ):: ቀስቷ አካሉ ውስጥ ገብታለችና
እንጣዎስ መሬት ላይ ወድቆ ለሞት ደረሰ:: ላበቱ በግንባሩ
ላይ በጭንቅ እየፈሰሰ ጮኸ::
"ጌታየ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ማረኝ? ራራልኝ? ይቅር
በለኝ? በድፍረት ባለ ማወቅም በድየሃለሁ:: ይቅር በለኝና
ላምልክህ: ስምህንም ልሸከም" ሲል በጭንቀት ውስጥ ሆኖ
አሰምቶ ጸለየ:: በዚያ የነበሩ ምዕመናን ማን: በምን እንደ
ወጋው ባያውቁም ባዩት ነገር ግን እጅግ ደስ አላቸው::
እነርሱም የፈጉትና የጸለዩለት ነገር ይሔው ነበርና::
ወዲያው ግን እንጣዎስ ከሞት ጫፍ ተመልሶ ተነሳ::
መጀመሪያ በቦታው የነበሩ ካህናትና ምዕመናንን "ይቅር
በሉኝ?" አለ:: ቀጥሎም ወደ ዻዻስ ዘንድ ሔዶ "አጥምቀኝ"
ሲል ጠየቀ:: እርሱ በሚጠመቅበት ቀን ብዙ አሕዛብና
ክርስቲያኖች ተሰብስበው ነበር::
እርሱ በከተማዋ ዝነኛ ነበር:: ሥርዓቱ ሁሉ ተደርሶ ቅዱሱ
ወደ ውሃ ገንዳው ሲገባ ሁሉ እያዩ የብርሃን ምሰሶ ከሰማይ
ወረደ:: ይህንን በገሃድ የተመለከቱ ከ10,000 በላይ አሕዛብ
ወዲያውኑ በክርስቶስ አምነው አብረውት ተጠምቀዋል::
ቅዱስ እንጣዎስ ከዚህ በሁዋላ ምስጉን ክርስቲያን ሆነ::
ስለ ቀደመ ሕይወቱ ፈንታ ጾምን: ጸሎትን: ፍቅርን: ምጽዋትን
ገንዘብ አደረገ:: ሕይወቱም ለብዙ ሰዎች መስታውት ሆነ::
#እመቤታችን ድንግል ማርያምንም ይወዳት ነበርና ወደ
ቅዱሳን ማሕበር ( #ኢየሩሳሌም ) ወስዳው በሥጋዊ አንደበት
ተከናውኖ ሊነገር የማይቻል ምሥጢርን ገልጣለታለች::
እነዚህን የቅድስና ጊዜያት በስኬት ያሳለፈው ቅዱስ
እንጣዎስ መጨረሻው ሰማዕትነት ሆነ:: አረማውያን ወገኖቹና ቀድሞ የሚያውቁት ወደ ቀደመ ክፋትና
ክህደት እንዲመለስ ጠየቁት:: "አይሆንም" አላቸው::
በአደባባይ ለፍርድ አቅርበው ደሙ እስኪፈስ ገረፉት::
ጥርሶቹን በሙሉ በድንጋይ አረገፏቸው:: ደሙና ጥርሶቹ
መሬት ላይ ተዘሩ:: ነገር ግን ይሕ ስቃይ ቅዱሱን ከፍቅረ
ክርስቶስ ሊለየው አልቻለም:: አሕዛብም ተስፋ ቆርጠው
በዚህች ቀን ገድለውታል:: ቅዱስ እንጣዎስም ከሁዋለኛው
ዘመን #ሰማዕታት እንደ አንዱ ተቆጥሯል::
ጳጉሜን ፪
#እንኩዋን_ለቅዱስ #ቲቶ_ሐዋርያ ዓመታዊ
የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞
#ቅዱስ_ቲቶ_ሐዋርያ
የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ቅዱስ ቲቶ
ከ72ቱ አርድእት አንዱ ሲሆን በተወሰነ መንገድም ቢሆን
የተዘነጋ ሐዋርያ አይደለም:: በተለይ ደግሞ ቅዱስ
ዻውሎስ ከጻፋቸው 14 መልእክታት መካከል አንዷ
የተላከችው ለዚህ ቅዱስ በመሆኗ ታሪኩ እንኩዋ
ባይነገር ስሙ አይረሳም:: ቅዱስ ዻውሎስም
በመልዕእክታቱ በጐ ስሙን እየደጋገመ ያነሳዋል::
☞ለመሆኑ ሐዋርያው ቅዱስ ቲቶ ማን ነው?
ቅዱስ ቲቶ የተወለደው በ1ኛው መቶ ክ/ዘመን እስያ
ውስጥ: #ቀርጤስ በምትባል ከተማ ነው:: የዘር ሐረጉ
ከእሥራኤልም: ከጽርእም (ግሪክ ለማለት ነው)
ይወለዳል:: አካባቢው አምልኮተ እግዚአብሔር የጠፋበት
ስለሆነ እሱም: ቤተሰቦቹም የሚያመልኩት ከዋክብትን
ነበር::
መዳን በእውቀት ይመስላቸው ስለ ነበር የአካባቢው
ሰዎች የግሪክን ፍልስፍና ጠንክረው ይማሩ ነበር:: ቅዱስ
ቲቶም በወጣትነቱ ወደ ት/ቤት ገብቶ የግሪክን
ፍልሥፍናና የዮናናውያንን ጥበበ ሥጋ ተማረ:: በጥቂት
ጊዜም የሁሉ የበላይ ሆነ::
ቅዱሱ በወቅቱ ምንም እውነተኛውን ፈጣሪ አያምልክ
እንጂ በጠባዩ እጅግ ቅንና ደግ ነበር:: ምክንያቱን
ሳያውቀው ለእኔ ቢጤዎች ያበላ: ያጠጣ:
ይንከባከባቸውም ነበር:: እግዚአብሔር ግን የዚህ ቅን
ሰው በጐነቱ እንዲሁ እንዲቀር አልወደደምና አንድ ቀን
በራዕይ ተገለጠለት::
በራዕይም አንድ ምንነቱን ያልተረዳው ነገር "ቲቶ ሆይ!
ስለ ነፍስህ ድኅነት ተጋደል:: ይህ ዓለም ኃላፊ ነው"
ሲለው ሰማ:: ከእንቅልፉ ነቅቶ በእጅጉ ደነገጠ::
የሚያደርገውንም አጣ:: ያናገራቸው ሁሉ ምንም
ሊገባቸው አልቻለም::
ለተወሰነ ጊዜም ለጉዳዩ ምላሽ ሳያገኝለት በልቡ
እየተመላለሰ ኖረ:: ድንገት ግን በዚያ ሰሞን ከወደ
#ኢየሩሳሌም አዲስ ዜና ተሰማ:: "ክርስቶስ የሚሉት
ኢየሱስ: እርሱም የባሕርይ አምላክ የሆነ ወደ ምድር
ወርዶ: ስለ እግዚአብሔር መንግስትም እየሰበከ ነው"
ሲሉ ለቲቶ ነገሩት::
"ሌላስ ምን አያችሁ?" አላቸው:: "በእጆቹ ድውያን
ይፈወሳሉ:: ሙታን ይነሳሉ:: እውራን ያያሉ:: ለምጻሞች
ይነጻሉ:: ሌሎች ብዙ ተአምራትም እየተደረጉ ነው"
አሉት:: የወቅቱ የሃገረ አክራጥስ መኮንን ፈላስፋ ነበርና
ስለ ክርስቶስ ሲሰማ ሊመራመር ወደደ::
እርሱ መሔድ ስላልተቻለው "ብልህ ጥበበኛ ሰው
ፈልጉልኝ" ብሎ ተከታዮችን ቢልካቸው ከቲቶ የተሻለ
በአካባቢው አልነበረምና እርሱኑ አመጡት:: መኮንኑ ቲቶን
"ነገሩ ትክክል ወይም ስሕተት መሆኑን በጥልቅ
መርምረህ ምላሽ አምጣልኝ" ብሎ ላከው::
ቅዱስ ቲቶም ፈጥኖ ተነስቶ ወደ ኢየሩሳሌም ገሰገሰ::
ወደ ከተማዋ እንደገባም ጌታችንን አፈላልጐ አገኘው::
1.ጌታችን ክርስቶስ በሥልጣነ ቃሉ ደዌያትን ሲያርቅ:
አጋንንትን ሲያሳድዳቸው ተመልክቶ ይህ ሥራ የፍጡር
እንዳልሆነ ተረዳ::
2.ጌታችን የሚያስተምረው ትምሕርት ከግሪክ ፍልሥፍና
እጅግ ርቆና መጥቆ አገኘው:: የግሪክ ፍልሥፍና
መነሻውም ሆነ መድረሻው ሥጋዊ ነው:: ጌታ ግን
በጣዕመ ቃሉ የሚያስተምረው ሰማያዊ: በዚያ ላይ
ዘለዓለማዊ የሆነ ትምሕርት ነው:: በራዕይ "ስለ ነፍስህ
ተጋደል" ያለው ምሥጢር አሁን ተተረጐመለት::
በዚህ ምክንያትም ጊዜ አላጠፋም:: ወዲያውኑ አምኖ
ተከታዩ ሆነ:: ጌታም ከ72ቱ # አርድእት ደመረው::
የአክራጥስ መኮንን "ምነው ዘገየህ?" ቢለው ያየውን
ሁሉ ጽፎ: እንደማይመለስም አክሎ ደብዳቤ ላከለት::
ከዚህ በሁዋላ #ቅዱስ_ቲቶ ከጌታችን እግር ለ3
ዓመታት ተምሮ: በበዓለ ሃምሳ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ:
በመላው እስያ ለ8 ዓመታት ወንጌልን ሰብኩዋል::
#ቅዱስ_ዻውሎስ ባመነ ጊዜ ደግሞ የእርሱ ደቀ
መዝሙር ሆኖ ለ25 ዓመታት አስተምሯል::
ቅዱስ ዻውሎስ ሰማዕት ከሆነ በሁዋላ ደግሞ ወደ
#አክራጥስ ተመልሶ: ሕዝቡን አሳምኖና አጥምቆ: ቤተ
ክርስቲያንን አንጿል:: ዕድሜው በደረሰ ጊዜም
መምሕራንን: ካህናትን ሹሞላቸው: ባርኩዋቸውም
በዚህች ቀን ዐርፏል::
✿አምላከ ቅዱስ ቲቶ መልካሙን የሕይወት ምሥጢር
ይግለጽልን:: ከሐዋርያውም በረከቱን ያድለን::
#ቅዱስ_አውዶኪስ_ቀሲስ
ይህ ቅዱስ ሰው ለቅዱስ መስቀሉ ከነበረው ፍቅር
የተነሳ በብዙ ድካም ወደ #ኢየሩሳሌም በእግሩ ተጉዞ
ነበር:: ከብዙ መንገደኞች ጋር በጐዳና ላይ ሳሉ ታዲያ
አንድ አይሁዳዊ (ሰማርያዊ) ተቀላቀላቸው:: በወሬ
በወሬ የት እንደሚሔዱ ሲጠይቃቸው "መካነ መስቀሉን
ለመሳለም ወደ #ጐልጐታ ነን" አሉት::
እሱ ግን ከት ብሎ ስቆ "እንዴት እንጨት
ትሳለማላችሁ" በሚል አፌዘባቸው:: የፀሐዩ ሐሩር እጅግ
ጠንቶ ነበርና ቅዱስ አውዶኪስ ኃይለ መስቀሉን ሊያሳይ
ወደደ:: በመንገድም መርዝነት ያለው ውሃ ነበርና ቅዱሱ
ቀርቦ ጸልዮ በመስቀሉ ባረከውና ፈጥኖ ወደ ጣፋጭነት
ተቀየረ::
ምዕመናኑ ደስ ብሏቸው ሲጠጡ ያ አይሁዳዊ
'እጠጣለሁ' ብሎ ቢቀርብ ወደ ነበረው ተመለሰበት::
'በኮዳ የያዝኩትን እማልጠጣ' ብሎ ቢከፍተው ደግሞ
ተልቶ አገኘው:: እጅግ ደንግጦ አለቀሰ:: በጣም
ጠማው: ግን ምኑን ይጠጣ!
አማራጭ ሲያጣ ወደ ቅዱስ አውዶኪስ ሒዶ እግሩ
ላይ ወድቆ አለቀሰ:: በመስቀሉ ቢማጸን መራራው
ጣፈጠለት:: በዚህ ምክንያትም ወደ ክርስትና
ተመልሷል:: ቅዱሱ በመልካም ሽምግልና ሲያርፍ ውሃው
የተቀየረበት ቦታ ላይ ቤተ መቅደስ ታንጾ በዚህ ቀን
ተቀድሷል::
እንኩዋን ለካህኑ #ሰማዕት_ቅዱስ_አልዓዛር እና
ለቅዱሳን ቤተሰቡ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም
አደረሳችሁ
#ቅዱስ_አልዓዛር_ካህን
ይህ ቅዱስ #የብሉይ_ኪዳን_ሰማዕታት ተብለው
ከሚታወቁት ዋነኛው ነው:: የነበረበት ዘመንም ቅድመ ልደተ
ክርስቶስ ሲሆን " #ዓመተ_መቃብያን / #ዘመነ_ካህናት "
ይባላል::
በወቅቱ ሰሎሜ የምትባል ደግ ሴት አግብቶ ይኖር የነበረው
ቅዱስ አልዓዛር በኢየሩሳሌም ተወዳጅ ነበር:: ሐረገ ትውልዱ
ከአሮን ወገን ነውና በክህነቱ ተግቶ ያገለግል ነበር:: በዚያ
ላይ ሊቀ ካህንነትን በመመረጡ ሕዝቡን ይሠራ: ያስተምር:
ያስተዳድር ነበር::
ቅዱስ አልዓዛር ከተባረከች ሚስቱ ሰሎሜ 7 ወንዶች ልጆችን አፍርቷል:: እነርሱንም በሥርዓት አሳድጐ የቤተ እግዚአብሔር አገልጋዮች እንዲሆኑ አድርጐ ነበር:: በዚያው
ዘመን በኢየሩሳሌም አካባቢ የሚኖሩ 3 እኩያን (ክፉ) ካህናት
ነበሩ:: እነዚሁም ሕዝቡን ከማስቸገር: ፈጣሪን ከማሳዘን ቦዝነው
አያውቁም ነበር:: የክፋታቸው መጨረሻ ግን የገዛ ሃገራቸውን
ማጥፋት ሆነ:: ነገሩ እንዲህ ነው:- 3ቱም ተመካክረው
የአልዓዛርን የሊቀ ካህንነት ቦታ ሊቀሙ ወስነው ወደ እርሱ
ሔዱና እንዲህ አሉት::
"ሹመት በተርታ: ሥጋ በገበታ" ሲሆን ያምራልና እኛ
በተራችን በወንበሩ ላይ እንቀመጥ::" እርሱ ግን "ሕዝቡን ጠይቃችሁ ተሾሙ" አላቸው:: እነርሱም
ሕዝቡን ጠርተው "ሹመት ይገባናል" ቢሏቸው ሕዝቡ መልሶ
"አልዓዛርን የሾመው እግዚአብሔር ነውና እናንተም ከፈጣሪ ጠይቃችሁ ተሾሙ" አሏቸው:: በዚህ ጊዜ 3ቱ እኩያን ተቆጡ:: ምክንያቱም እግዚአብሔር እንደ ማይሰጣቸው ያውቃሉና:: ወዲያው ግን 3ቱም
ከአካባቢው ጠፉ:: ከኢየሩሳሌም ወጥተው ወደ ጨካኙ
የግሪክ ንጉሥ አንጥያኮስ ሔዱ::
+አንጥያኮስ ማለት "ቀኝ ዐይናችሁን ገብሩልኝ" የሚል ንጉሥ ነው:: እርሱን "#ኢየሩሳሌም ባለቤት የላትምና ሒደህ ውረራት" አሉት:: "አጥሩ ጥብቅ ነው:: በምን እገባለሁ?"
ቢላቸው "እኛ በመላ እናስገባሃለን" አሉት:: እርሱም
240,000 ሠራዊት አስከትቶ ወረደ:: እነርሱ ቀድመው ወደ ኢየሩሳሌም ገብተው ያስወሩ ጀመር::
"እናንተ ሹመት ብትነሱንም እኛ ግን አንጥያኮስን ያህል ንጉሥ
በእሥራኤል አምላክ አሳምነን መጣን" እያሉ ይሰብኩ ገቡ::
ቅዱስ አልዓዛር "አትስሟቸው:: በዚያም ላይ አሕዛብ
የተቀደሰውን ምድር መርገጥ የለባቸውም" ብሎ ነበር::
ነገር ግን አንዳንድ ችኩሎች አይጠፉምና ፈጥነው
የከተማዋን በር ከፈቱት:: ሠራዊቱን ደብቆ ትንሽ ራሱን የቆመ
የመሰለው አንጥያኮስ በምክንያት: በክፋትና በመላ ሁሉን
ሠራዊቱን አስገባ:: የሚገርመው በጊዜው የከተማዋ ሕዝብ
12 እልፍ (120,000) ሲሆን ንጉሡ ያስገባው ሠራዊት ግን
24 እልፍ (240,000) ሆኖ ተገኘ::
ወዲያው አንጥያኮስ ሕዝቡን ሰበሰበና አልዓዛርን ለብቻው
ጠርቶ ተናገረው:: "አንተ አምላክህን እንደምትወድ
ሰምቻለሁ:: አንተ የበጉን መስዋዕት በልተህ: #ለስዕለ_
ኪሩብ ሰግደህ: ሕዝቡን ግን እሪያ (አሳማ) እንዲበላና
ለጸፀሐይ እንዲሰግድ አድርግልኝ" አለው::
ቅዱስ አልዓዛር መለሰለት:- "እግዚአብሔር የሾመኝኮ በጐ
ሃይማኖትን ላስተምር እንጂ ለክፋት አይደለም:: ለሕዝቤ
የክፋት አብነት ፈጽሞ አልሆንም" አለው:: ያን ጊዜ ንጉሡ
በቅዱሱ ላይ ተቆጣ:: "የምልህን ካላደረግህ ብዙ ግፍ
ይደርስብሃል" ቢለው ቅዱሱ መልሶ "የፈለግኸውን አድርግ"
አለው:: በዚያን ጊዜ ንጉሡ የቅዱሱን ሚስትና 7 ልጆች
እንዲያመጡለት አዘዘ:: ቅዱሱ እያየ ከፊቱ ላይ 7ቱንም
ልጆቹን በሰይፍ አስመታቸውና 7ቱም ወደቁ:: ለአንድ አባት
ይህ የመጨረሻው መራራ ፈተና ነው:: #አልዓዛር ግን ምን
አንጀቱ በኀዘን ቢቃጠልም ከልጆቹ ለእግዚአብሔር አድልቷልና
ቻለው ታገሠው::
በዚህ ለውጥ እንዳልመጣ ያየው ንጉሡ ሌላ ፍርድ
ተናገረ:: ቅዱሱንና ሚስቱን ( #ሰሎሜን ) በፈትል ጠቅልለው
በሠም ነከሯቸው:: (ጧፍ እንደሚሠራበት መንገድ ማለት
ነው:: )
አሁንም ግን ከአምልኮታቸው ፈቀቅ ባለማለታቸው ትልቅ
ብረት ምጣድ ተጥዶ: 2ቱም ከነነፍሳቸው እንዲቃጠሉ
ተደረገ:: ቀጥሎም ሕዝቡን እንዲፈጁ አዋጅ ወጣ::
በከተማዋ ከነበረው ሕዝብ 40,000 ያህሉ ተገደሉ::
+40,000 ያህሉ ሲማረኩ 40,000 ያህሉን ደግሞ # ይሁዳ
የሚባል አርበኛ በር ሰብሮ ይዟቸው ሸሸ:: "እንሾማለን:
እንሸለማለን" ብለው ሕዝባቸውን ያስፈጁ እነዚያ ካህናትም
#እግዚአብሔር ፈርዶባቸው እነርሱም ተገደሉ:: ቅዱሱ
የአልዓዛር ቤተሰብ ግን የክብርን አክሊል አግኝተዋል::
#የእሥራኤል_አምላክ ቸሩ_እግዚአብሔር_እንዲህ ካለው_መከራ_በኪነ_ጥበቡ_ይሰውረን::_ከቅዱሳኑ_በረከትም_አይለየን::
💚💛ተአምረ ቅዱስ ሚካኤል💛❤️

ቅዱስ መጽሐፍ እንደ ነገረን በዚህች ዕለት የመላእክት ሁሉ አለቃቸው: የቅዱሳንም ረዳታቸው የሆነው ደጉ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል ንጉሡን ሕዝቅያስን ግሩም.በሆነ ተአምር ከከተማው #ኢየሩሳሌም ጋር ታድጐታል:: ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

ከመድኃኒታችን #ክርስቶስ ልደት 700 ዓመታት በፊት #ሕዝቅያስ የሚባል ንጉሥ በይሁዳ ላይ ነግሦ ነበር:: ደጋጉ #ዳዊትና #ሰሎሞን ካረፉ በሁዋላ የሕዝቅያስን ያክል ቅን እና የእግዚአብሔር ሰው በእሥራኤል ላይ አልነገሰም:: ንጉሡ ጣዖት አምልኮን ነቃቅሎ አጥፍቶ ሕዝቡ እግዚአብሔርን ብቻ እንዲያመልክ አድርጐም ነበር::

ነገር ግን ቅዱስ ሕዝቅያስ በነገሠ በ14ኛው ዓመት የአሕዛብ (የአሦር) ንጉሥ ሰናክሬም በጠላትነት ተነሳበት:: ወደ አካባቢውም መጥቶ: ከቦ አስጨነቀው:: ሰናክሬም በጦር እጅግ ኃይለኛ ነበር:: በዚያውም ላይ ጦር የሚመዙ ከ185,000 በላይ ብርቱ ተዋጊዎች ነበሩትና ሕዝቅያስ እንደማይችለው ተረድቶ መልእክተኛ ላከበት::

"እገብርልሃለሁ:: የፈለግከውንም እሰጥሃለሁ:: ሃገሬን ግን አታጥፋ:: ኢየሩሳሌምን አታቃጥል:: ሕዝቤንም
አትግደል" በሚል ለመነው:: እጅ መንሻ ግብሩንም ከከተማዋ የተገኘውን ወርቅና ብር ሁሉ ጭኖ ላከለት::

ሰናክሬም ግን ሰይጣን ያደረበት ነውና የሕዝቅያስን ልመና ወደ ጐን ብሎ የእሥራኤልን አምላክ : ቅዱስ ስሙንም ተገዳደረ:: ለሕዝቅያስም "ከእኔ እጅ የሚያድንህ ማነው? ሕዝቡንም #እግዚአብሔር ያድናል ብለህ አታታልላቸው" ሲል ላከበት:: ቅዱስ ሕዝቅያስ በዚህ ጊዜ የፈጣሪው ስም ሲቃለል ሰምቷልና ፈጽሞ አዘነ::

መልእክተኞችን ወደ ነቢዩ #ቅዱስ_ኢሳይያስ ልኮ እርሱ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ:: በእግዚአብሔር ፊት ልብሱን ቀድዶ ማቅ ለበሰ:: ስለ ኢየሩሳሌምና ሕዝቡም ፈጽሞ አለቀሰ:: በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር የሰናክሬምን
መገዳደርና የሕዝቅያስን ልመና ሰምቷልና በኢሳይያስ አንደበት እንዲሕ አለ:- "ስለ ባሪያየ ስለ #ዳዊት ከተማዋን አድናታለሁ::"

በዚያች ሌሊትም ድንቅ መልአክ #ቅዱስ_ሚካኤል ከሰማያት በግርማ ወረደ:: ወደ ሰናክሬም የጦር ሠፈር ደርሶ አንድ ጊዜ የእሳት ሰይፉን መዝዞ ቢያሳያቸው ከአሕዛብ ሠራዊት 185 ሺ ኃያላን እንደ ቅጠል ረገፉ:: በለኪሶ የነበረው ሰናክሬም በጧት ቢነሳ ሠራዊቱ ሁሉ ወደ አስከሬን ክምር ተቀይሯል::

በድንጋጤ ወደ #ነነዌ ሒዶ ወደ ጣዖት ቤቱ ሲገባ የራሱ ልጆች (አድራማሌክና ሳራሳር) ገደሉት:: ትዕቢተኛው ሰናክሬም ለአሕዛብ ሁሉ መዘባበቻ ሆነ:: ቅዱስ ሕዝቅያስ ግን በፈጣሪው ታምኗልና ቅዱስ ሚካኤል ሞገስ ሆኖ የዓለም ነገሥታት ሁሉ ፈሩት:: (1ነገ. 18:13, 19:1)
From:- d/n yordanos abebe
@senkesar @senkesar
💚💛 ጻድቃን እንድራኒቆስ ወአትናስያ 💛❤️
ሁለቱ ቅዱሳን ባል እና ሚስት (ባለትዳር) ናቸው:: የነበረበት ዘመን 4ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: እስኪ #እግዚአብሔር የቀደሰው ጋብቻ ምን እንደሚመስል እንመልከት::

#እንድራኒቆስና_አትናስያ በዘመናቸው ከልጅነት ጀምረው ቃለ እግዚአብሔርን የሚሰሙ : ለወላጆቻቸው የሚታዘዙ ነበሩ:: ዘመኑ ደርሶ በሚገባው የተክሊል ሥርዓት ጋብቻቸውን ፈጸሙ:: 40 ቀን ከተፈጸመ በሁዋላ ከምንም ነገር በፊት 2ቱ ቁጭ ብለው ተወያዩ::

የውይይታቸው ርዕስ ደግሞ "ፈጣሪያችን በምን እናስደስተው" የሚል ነበር:: ውይይታቸው የጠናቀቀው በእነዚህ ውሳኔዎች ነው::
1.ሁልጊዜም እንግዳ መቀበል አለብን::
2.ነዳያን ከቤታችን ሊጠፉ አይገባም::
3.ጸሎት : ጾምና ስግደት በቤት ውስጥ አይቁዋረጥም::
4.አብሮ ለመተኛት መቸኮል የለብንም::

እነርሱ መልካምን አስበዋልና አምላክ የሰጣቸውን ሃብት ሲመጸውቱ ኖሩ:: ከዘመናት የቅድስና ጉዞ በሁዋላ በፈቃደ እግዚአብሔር 2 ልጆችን አከታትለው ወለዱ:: ወንዱን "#ዮሐንስ" : ሴቷን ደግሞ "#ማርያም" አሏት::

እነርሱን ከወለዱ በሁዋላ እንደ ገና ሌላ ውሳኔ አሳለፉ:: "ይህንን ላደረገልን ጌታ ከዚህ በሁዋላ አልጋ እንለያለን" ብለው ለ12 ዓመታት በጾምና በጸሎት ተወሰኑ::
+ሕጻናቱ ዮሐንስና ማርያም በቅንነት አድገው እድሜአቸው 12 ሲሆን 2ቱም በአንድ ቀን ታመው ሞቱ:: ይህ ለአንድ ወላጅ የመጨረሻው አሰቃቂ ፈተና ነው:: ሁሉቱም (እንድራኒቆስና ሚስቱ አትናስያ) ልጆቻቸውን ታቅፈው ወስደው ቀበሩ::

#እንድራኒቆስ ከቀብር በሁዋላ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብቶ ምርር ብሎ አለቀሰ:: ግን እንዲህ አለ:-
"አምላከ #ኢዮብ! አንተ ሰጠኸኝ:: አንተም ነሳኸኝ:: ስምህ ለዘለዓለም ይባረክ" ብሎ ሔደ:: እናት #አትናስያ ግን ከሐዘን ብዛት ልቡናዋ ሊሠወር ጥቂት ቀረው::

የልጆቿ መቃብር ላይ ተደፍታ ስታለቅስ ቅዱስ መልአክ ልቡናዋን ወደ ሰማይ አሳረገው:: ልጆቿ ዮሐንስና ማርያም በገነት ውስጥ ከቅዱሳን ጋር ሐሴትን ሲያደርጉም ተመለከተች:: ወዲያው ወደ ቤት ተመልሳ ለባሏ እንድራኒቆስ ያየችውን ነገረችውና ደስ አላቸው::

እዛው ላይ "ለዚህ ውለታው ከነፍሳችን ውጪ የምንሰጠው የለም" ብለው ሊመንኑ ተስማሙ:: እጅግ ሃብታሞች ነበሩና ነዳያንን ሰብስበው : ሃብት ንብረታቸውን : ቤት ርስታቸውን አካፍለው ወደ ገዳመ አስቄጥስ ሔዱ::

እርሷ ከሴቶች ገዳም : እርሱ ደግሞ ከወንዶቹ ገቡ:: ለ12 ዓመታት በፍጹም ተጋድሎ ለፈጣሪያቸው ተገዙ:: በእነዚህ ዘመናት ተያይተው : አንዱ ስለ ሌላው ሰምቶ አያውቅም:: በጸሎት ግን ያለማቁዋረጥ ይተሣሠቡ ነበር::

ከ12 ዓመታት በሁዋላ የፍቅር አምላክ በሁለቱም ልቡና በተመሳሳይ ሰዓት : ተመሳሳይ ሐሳብን አመጣ:: እርሱ ከአበ ምኔቱ (#ታላቁ_አባ_ዳንኤል) : እርሷም ከእመ ምኔቷ አስፈቅደው ወደ #ኢየሩሳሌም ከቅዱሳት መካናት ለመባረክ ጉዞ ጀመሩ:: በየፊናቸው ጥቂት እንደተጉዋዙ እርስ በርስ ተያዩ::
+እርሷ ለየችው:: እርሱ ግን ጭራሽ ሊለያት አልቻለም:: ይህም ጥበበ እግዚአብሔር ነው:: 2ቱም እየተጫወቱ : እየጸለዩ በሰላም ተባርከው ወደ ግብጽ ተመለሱ:: በእነዚህ ጊዜያት ቅድስት አትናስያን የሚለያት አልነበረም:: አካሏ በገድል ከመለወጡ ባሻገር የለበሰችው እንደ ወንድ መነኮሳት ነበር::

ወደ #ገዳመ_አስቄጥስ ሲደርሱ ጸጋው ተሰጥቶታልና #አባ_ዳንኤል ባልና ሚስት መሆናቸውን አወቀ:: "ለምን አብራችሁ አትኖሩም?" አላቸው:: "እኛ ደስ ይለናል" አሉት:: ከዚያ እርሷ እያወቀችው: እርሱ ሳያውቃት ለ12 ዓመታት አብረው በቅድስና ኖሩ::

ከእነዚህ ዘመናት በሁዋላ ግን ሐምሌ 28 ቀን ቅድስት #አትናስያ ታመመች:: አባ ዳንኤል ሥጋውን ደሙን አቀብሏትም ዐረፈች:: ሊገንዟት ሲቀርቡ ቅዱስ #እንድራኒቆስ መልኩዋን ልብ ቢለው ሚስቱ ናት::

በአንድ ጊዜ ሚስቱንና የሚወደውን ባልንጀራ በማጣቱ አለቀሰ:: እርሷን ቀብረው ወደ በዓቱ ተመልሶ "ጌታ ሆይ! ውሰደኝ?" አለ:: እርሱም ተከትሏት ዐረፈ:: አባ ዳንኤል እርሱንም ቀብሮ ጥዑም ዜናቸውን ጻፈ::
From:- dn yordanos abebe
@senkesar @senkesar