#በምዕራብ ጎንደር ዞን ከትናንት የተሻለ መረጋጋት አለ የዞኑ #አስተዳደር
የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ መልካሙ በስልክ ባደረሱን መረጃ መሠረት ዞኑ #ከትናንት በተሻለ ሰላሙ ተመልሷል፡፡
‹‹ትናንት ሰላም ቢሆኑም ‹ስጋት ነበረባቸው› ያልኳቸው #የሽንፋና መተማ ዮሐንስ አካባቢዎች ዛሬ የተሻለ ሰላማዊ ናቸው፡፡ ከሕዝቡና ከፀጥታ አካሉ ጋር በመሆን አጥፊዎችን የመለዬት ሥራም እየሠራን ነው›› ብለዋል አቶ ሞላ፡፡
ትናንት ከገንዳ ውኃ ወደ ነጋዴ ባሕር በሚወስደው መንገድ ላይ መኪና አስቁመው ለመዝረፍ የሞከሩ #አራት ታጣቂዎችና አራት ጀሌዎች (መሳሪያ ያልታጠቁ) በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው ‹‹ባለፈው ግጭቱን ያነሳሱትን የመለዬት ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል›› ብለዋል፡፡
የምዕራብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር #ጌትነት አልታሰብ በበኩላቸው ‹‹የትራንስፖርት እንቅስቃሴው ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ገብቷል፤ አልፎ አልፎም ለተሽከርካሪዎች ድንገተኛ እጀባ እያደረግን ሰላሙን የበለጠ ለማረጋገጥ እየሠራን ነው›› ብለዋል፡፡
የፀጥታ መዋቅሩ የዞኑ ሰላም አስተማማኝ እንዲሆን ያለዕረፍት ሥራ ላይ መሆኑንም ኮማደሩ ገልጸዋል፡፡
ምንጭ ፦አብመድ
@yenetube @mycase27
የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ መልካሙ በስልክ ባደረሱን መረጃ መሠረት ዞኑ #ከትናንት በተሻለ ሰላሙ ተመልሷል፡፡
‹‹ትናንት ሰላም ቢሆኑም ‹ስጋት ነበረባቸው› ያልኳቸው #የሽንፋና መተማ ዮሐንስ አካባቢዎች ዛሬ የተሻለ ሰላማዊ ናቸው፡፡ ከሕዝቡና ከፀጥታ አካሉ ጋር በመሆን አጥፊዎችን የመለዬት ሥራም እየሠራን ነው›› ብለዋል አቶ ሞላ፡፡
ትናንት ከገንዳ ውኃ ወደ ነጋዴ ባሕር በሚወስደው መንገድ ላይ መኪና አስቁመው ለመዝረፍ የሞከሩ #አራት ታጣቂዎችና አራት ጀሌዎች (መሳሪያ ያልታጠቁ) በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው ‹‹ባለፈው ግጭቱን ያነሳሱትን የመለዬት ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል›› ብለዋል፡፡
የምዕራብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር #ጌትነት አልታሰብ በበኩላቸው ‹‹የትራንስፖርት እንቅስቃሴው ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ገብቷል፤ አልፎ አልፎም ለተሽከርካሪዎች ድንገተኛ እጀባ እያደረግን ሰላሙን የበለጠ ለማረጋገጥ እየሠራን ነው›› ብለዋል፡፡
የፀጥታ መዋቅሩ የዞኑ ሰላም አስተማማኝ እንዲሆን ያለዕረፍት ሥራ ላይ መሆኑንም ኮማደሩ ገልጸዋል፡፡
ምንጭ ፦አብመድ
@yenetube @mycase27
የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ የፈተና ውጤት ይፋ ሆነ!
ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ የፈተና ውጤትን ይፋ አደረገ።የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አርዓያ ገብረ እግዚአብሄር በ2011 ዓ.ም የ10ኛ ክፍል ፈተና ዙሪያ ከፋና ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡
ከተፈታኞቹ መካከልም #ከ10 ሺህ በላይ ተማሪዎች #አራት_ነጥብ ማምጣታቸውን ገልጸዋል።
75 ነጥብ 5 በመቶ ያህል ተፈታኞች 2.0 እና ከዚያ በላይ ነጥብ ያመጡ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል።2.0 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡት ተማሪዎች ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል። ከተፈታኞቹ መካከል ወንዶች 682 ሺህ 572 ሲሆኑ 572 ሺህ 997 ሴቶች ናቸው፡፡ከእነዚህ መካከል 894 ሺህ 318 በመደበኛ፣ 354 ሺህ 782 በግል እና 6 ሺህ 469 ደግሞ በማታው ክፈለ ጊዜ ተፈታኞች እንደነበሩ ነው የተገለጸው።
በዘንድሮው የ10ኛ ክፍል ፈተና ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ለፈተና መቀመጣቸውን የኤጀንሲ መረጃ ያመላክታል።ባለፈው አመት ሁለት እና ከዚያ በላይ ነጥብ ያስመዘገቡት ተፈታኞች 71 በመቶ መሆናቸው የሚታወስ ነው።ተማሪዎች ውጤታቸውን በኤጀንሲው ድረ ገጽ http://
app.neaea.gov.et ወይም www.neaea.gov.et እንዲሁም በአጭር የጽሁፍ መልዕክት 8181 ላይ ID- ብለው የአድሚሽን ቁጥራቸውን በማስገባት መመልከት ይችላሉ።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ የፈተና ውጤትን ይፋ አደረገ።የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አርዓያ ገብረ እግዚአብሄር በ2011 ዓ.ም የ10ኛ ክፍል ፈተና ዙሪያ ከፋና ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡
ከተፈታኞቹ መካከልም #ከ10 ሺህ በላይ ተማሪዎች #አራት_ነጥብ ማምጣታቸውን ገልጸዋል።
75 ነጥብ 5 በመቶ ያህል ተፈታኞች 2.0 እና ከዚያ በላይ ነጥብ ያመጡ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል።2.0 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡት ተማሪዎች ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል። ከተፈታኞቹ መካከል ወንዶች 682 ሺህ 572 ሲሆኑ 572 ሺህ 997 ሴቶች ናቸው፡፡ከእነዚህ መካከል 894 ሺህ 318 በመደበኛ፣ 354 ሺህ 782 በግል እና 6 ሺህ 469 ደግሞ በማታው ክፈለ ጊዜ ተፈታኞች እንደነበሩ ነው የተገለጸው።
በዘንድሮው የ10ኛ ክፍል ፈተና ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ለፈተና መቀመጣቸውን የኤጀንሲ መረጃ ያመላክታል።ባለፈው አመት ሁለት እና ከዚያ በላይ ነጥብ ያስመዘገቡት ተፈታኞች 71 በመቶ መሆናቸው የሚታወስ ነው።ተማሪዎች ውጤታቸውን በኤጀንሲው ድረ ገጽ http://
app.neaea.gov.et ወይም www.neaea.gov.et እንዲሁም በአጭር የጽሁፍ መልዕክት 8181 ላይ ID- ብለው የአድሚሽን ቁጥራቸውን በማስገባት መመልከት ይችላሉ።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa