የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ የፈተና ውጤት ይፋ ሆነ!
ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ የፈተና ውጤትን ይፋ አደረገ።የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አርዓያ ገብረ እግዚአብሄር በ2011 ዓ.ም የ10ኛ ክፍል ፈተና ዙሪያ ከፋና ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡
ከተፈታኞቹ መካከልም #ከ10 ሺህ በላይ ተማሪዎች #አራት_ነጥብ ማምጣታቸውን ገልጸዋል።
75 ነጥብ 5 በመቶ ያህል ተፈታኞች 2.0 እና ከዚያ በላይ ነጥብ ያመጡ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል።2.0 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡት ተማሪዎች ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል። ከተፈታኞቹ መካከል ወንዶች 682 ሺህ 572 ሲሆኑ 572 ሺህ 997 ሴቶች ናቸው፡፡ከእነዚህ መካከል 894 ሺህ 318 በመደበኛ፣ 354 ሺህ 782 በግል እና 6 ሺህ 469 ደግሞ በማታው ክፈለ ጊዜ ተፈታኞች እንደነበሩ ነው የተገለጸው።
በዘንድሮው የ10ኛ ክፍል ፈተና ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ለፈተና መቀመጣቸውን የኤጀንሲ መረጃ ያመላክታል።ባለፈው አመት ሁለት እና ከዚያ በላይ ነጥብ ያስመዘገቡት ተፈታኞች 71 በመቶ መሆናቸው የሚታወስ ነው።ተማሪዎች ውጤታቸውን በኤጀንሲው ድረ ገጽ http://
app.neaea.gov.et ወይም www.neaea.gov.et እንዲሁም በአጭር የጽሁፍ መልዕክት 8181 ላይ ID- ብለው የአድሚሽን ቁጥራቸውን በማስገባት መመልከት ይችላሉ።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa
ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ የፈተና ውጤትን ይፋ አደረገ።የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አርዓያ ገብረ እግዚአብሄር በ2011 ዓ.ም የ10ኛ ክፍል ፈተና ዙሪያ ከፋና ጋር ቆይታ አድርገዋል፡፡
ከተፈታኞቹ መካከልም #ከ10 ሺህ በላይ ተማሪዎች #አራት_ነጥብ ማምጣታቸውን ገልጸዋል።
75 ነጥብ 5 በመቶ ያህል ተፈታኞች 2.0 እና ከዚያ በላይ ነጥብ ያመጡ መሆናቸውን ዳይሬክተሩ ጠቅሰዋል።2.0 እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡት ተማሪዎች ቁጥር ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር ብልጫ እንዳለው ተናግረዋል። ከተፈታኞቹ መካከል ወንዶች 682 ሺህ 572 ሲሆኑ 572 ሺህ 997 ሴቶች ናቸው፡፡ከእነዚህ መካከል 894 ሺህ 318 በመደበኛ፣ 354 ሺህ 782 በግል እና 6 ሺህ 469 ደግሞ በማታው ክፈለ ጊዜ ተፈታኞች እንደነበሩ ነው የተገለጸው።
በዘንድሮው የ10ኛ ክፍል ፈተና ከ1 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ ተማሪዎች ለፈተና መቀመጣቸውን የኤጀንሲ መረጃ ያመላክታል።ባለፈው አመት ሁለት እና ከዚያ በላይ ነጥብ ያስመዘገቡት ተፈታኞች 71 በመቶ መሆናቸው የሚታወስ ነው።ተማሪዎች ውጤታቸውን በኤጀንሲው ድረ ገጽ http://
app.neaea.gov.et ወይም www.neaea.gov.et እንዲሁም በአጭር የጽሁፍ መልዕክት 8181 ላይ ID- ብለው የአድሚሽን ቁጥራቸውን በማስገባት መመልከት ይችላሉ።
Via FBC
@YeneTube @FikerAssefa