#በምዕራብ ጎንደር ዞን ከትናንት የተሻለ መረጋጋት አለ የዞኑ #አስተዳደር
የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ መልካሙ በስልክ ባደረሱን መረጃ መሠረት ዞኑ #ከትናንት በተሻለ ሰላሙ ተመልሷል፡፡
‹‹ትናንት ሰላም ቢሆኑም ‹ስጋት ነበረባቸው› ያልኳቸው #የሽንፋና መተማ ዮሐንስ አካባቢዎች ዛሬ የተሻለ ሰላማዊ ናቸው፡፡ ከሕዝቡና ከፀጥታ አካሉ ጋር በመሆን አጥፊዎችን የመለዬት ሥራም እየሠራን ነው›› ብለዋል አቶ ሞላ፡፡
ትናንት ከገንዳ ውኃ ወደ ነጋዴ ባሕር በሚወስደው መንገድ ላይ መኪና አስቁመው ለመዝረፍ የሞከሩ #አራት ታጣቂዎችና አራት ጀሌዎች (መሳሪያ ያልታጠቁ) በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው ‹‹ባለፈው ግጭቱን ያነሳሱትን የመለዬት ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል›› ብለዋል፡፡
የምዕራብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር #ጌትነት አልታሰብ በበኩላቸው ‹‹የትራንስፖርት እንቅስቃሴው ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ገብቷል፤ አልፎ አልፎም ለተሽከርካሪዎች ድንገተኛ እጀባ እያደረግን ሰላሙን የበለጠ ለማረጋገጥ እየሠራን ነው›› ብለዋል፡፡
የፀጥታ መዋቅሩ የዞኑ ሰላም አስተማማኝ እንዲሆን ያለዕረፍት ሥራ ላይ መሆኑንም ኮማደሩ ገልጸዋል፡፡
ምንጭ ፦አብመድ
@yenetube @mycase27
የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሞላ መልካሙ በስልክ ባደረሱን መረጃ መሠረት ዞኑ #ከትናንት በተሻለ ሰላሙ ተመልሷል፡፡
‹‹ትናንት ሰላም ቢሆኑም ‹ስጋት ነበረባቸው› ያልኳቸው #የሽንፋና መተማ ዮሐንስ አካባቢዎች ዛሬ የተሻለ ሰላማዊ ናቸው፡፡ ከሕዝቡና ከፀጥታ አካሉ ጋር በመሆን አጥፊዎችን የመለዬት ሥራም እየሠራን ነው›› ብለዋል አቶ ሞላ፡፡
ትናንት ከገንዳ ውኃ ወደ ነጋዴ ባሕር በሚወስደው መንገድ ላይ መኪና አስቁመው ለመዝረፍ የሞከሩ #አራት ታጣቂዎችና አራት ጀሌዎች (መሳሪያ ያልታጠቁ) በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው ‹‹ባለፈው ግጭቱን ያነሳሱትን የመለዬት ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል›› ብለዋል፡፡
የምዕራብ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር #ጌትነት አልታሰብ በበኩላቸው ‹‹የትራንስፖርት እንቅስቃሴው ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ገብቷል፤ አልፎ አልፎም ለተሽከርካሪዎች ድንገተኛ እጀባ እያደረግን ሰላሙን የበለጠ ለማረጋገጥ እየሠራን ነው›› ብለዋል፡፡
የፀጥታ መዋቅሩ የዞኑ ሰላም አስተማማኝ እንዲሆን ያለዕረፍት ሥራ ላይ መሆኑንም ኮማደሩ ገልጸዋል፡፡
ምንጭ ፦አብመድ
@yenetube @mycase27
#በምዕራብ_ጎንደር ዞን ቋራ እና #በባሕር _ዳር ዙሪያ ወረዳ በኮሌራ ወረርሽኝ የተያዙ ሰዎች ቁጥር መጨመሩን ኢንስቲትዩቱ አስታወቀ
በ #አማራ ክልል በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ እና በባሕር ዳር ዙሪያ ወረዳ በኮሌራ ወረርሽኝ በርካታ ሰዎች እየተያዙ መሆኑን የክልሉ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የአማራ ክልል ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የበሽታዎች እና የጤና ሁኔታዎች ምላሽ አሰጣጥ ባለሙያ ሲስተር ሰፊ ደርብ እንደገለጹት ወረርሽኙ ከተከሰተበት ቀን ጀምሮ በየቀኑ የሚደርሰው የበሽተኛ ቁጥር እየጨመረ ነው፡፡ በተለይ በባሕር ዳር ዙሪያ ወረዳ በቀን ውስጥ በርካታ ሰዎች በበሽታው እየተጠቁ ነው ብለዋል።
አጣዳፊ ተቅማጥ እና ትውከት በማስከተል ለሞት የሚዳርገው በሽታው በክልሉ ከየካቲት ወር መጨረሻ ጀምሮ መከሰቱን አስረድተዋል ሲል አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።
ሲስተር ሰፊ ደርብ የኮሌራ የተበከለ ውኃ እና ምግብን በመጠቀም የሚከሰት ሲኾን ሰዎች በብዛት በሚሠባሠቡባቸው ቦታዎች በተለይም ንጹህ የመጠጥ ውኃ እና ንጹህ የመጸዳጃ ቦታ በሌለበት አካባቢ በቀላሉ የሚተላለፍ በመሆኑ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስበዋል።
በሽታውን ለመከላከል ከበሽተኛ ጋር ንክኪ ከተደረገ በኋላ እጅን በሳሙና መታጠብ፣ ውኃን በኬሚካል አክሞ እና አፍልቶ መጠቀም እንዲሁም የበሽታው ምልክቶች ከታዩ በአቅራቢያ ወደሚገኝ የጤና ተቋም በመሄድ የሕክምና አገልግሎት ማግኘት ያስፈልጋል ብለዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
በ #አማራ ክልል በምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ እና በባሕር ዳር ዙሪያ ወረዳ በኮሌራ ወረርሽኝ በርካታ ሰዎች እየተያዙ መሆኑን የክልሉ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የአማራ ክልል ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የበሽታዎች እና የጤና ሁኔታዎች ምላሽ አሰጣጥ ባለሙያ ሲስተር ሰፊ ደርብ እንደገለጹት ወረርሽኙ ከተከሰተበት ቀን ጀምሮ በየቀኑ የሚደርሰው የበሽተኛ ቁጥር እየጨመረ ነው፡፡ በተለይ በባሕር ዳር ዙሪያ ወረዳ በቀን ውስጥ በርካታ ሰዎች በበሽታው እየተጠቁ ነው ብለዋል።
አጣዳፊ ተቅማጥ እና ትውከት በማስከተል ለሞት የሚዳርገው በሽታው በክልሉ ከየካቲት ወር መጨረሻ ጀምሮ መከሰቱን አስረድተዋል ሲል አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘግቧል።
ሲስተር ሰፊ ደርብ የኮሌራ የተበከለ ውኃ እና ምግብን በመጠቀም የሚከሰት ሲኾን ሰዎች በብዛት በሚሠባሠቡባቸው ቦታዎች በተለይም ንጹህ የመጠጥ ውኃ እና ንጹህ የመጸዳጃ ቦታ በሌለበት አካባቢ በቀላሉ የሚተላለፍ በመሆኑ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስበዋል።
በሽታውን ለመከላከል ከበሽተኛ ጋር ንክኪ ከተደረገ በኋላ እጅን በሳሙና መታጠብ፣ ውኃን በኬሚካል አክሞ እና አፍልቶ መጠቀም እንዲሁም የበሽታው ምልክቶች ከታዩ በአቅራቢያ ወደሚገኝ የጤና ተቋም በመሄድ የሕክምና አገልግሎት ማግኘት ያስፈልጋል ብለዋል።
@Yenetube @Fikerassefa
👍8❤3😭3😁1