YeneTube
118K subscribers
31.4K photos
485 videos
79 files
3.87K links
መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa
Download Telegram
6 ዩኒቨርስቲዎች የጉና ተራራ አከባቢን ለማልማት ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

ዛሬ ደብረታቦር፣ ጎንደር፣ ባህር ዳር፣ ደብረ ማርቆስ፣ እንጅባራ እና ደባርቅ ዩኒቨርሲቲዎች  "ጣናን ለመታደግ የጋራ፣ የትብብርና የፍቅር አረንጓዴ አሻራ - ዘመቻ ወደ ጉና" በሚል መሪ ቃል  የጉና-ጣና ተፋሰስ  ቦታዎች ላይ ችግኝ የተከሉ ሲሆን ከችግኝ ተከላው በኃላም የጉና ተራራ አከባቢን ለማልማት፣ በአካባቢ እንክብካቤና ሌሎች ሁለንተናዊ ጉዳዮች ላይ አብሮ ለመስራት ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ የጉና ተራራ የ41 ወንዞችና የ77 ምንጮች መገኛ ሲሆን የጣናና የአባይ ገባሮች በሙሉ የሚነሱበት እና የምስራቅ አፍሪካ የውሃ ማማ ተብሎ የሚጠቀስ ስፍራ ነው።የጉና ተራራን ማልማት ጣና ሃይቅን ከእንቦጭ ለመጠበቅ ወሳኝ መሆኑና ጣና ከደለል በሚጠበቅበት ጊዜ የእምቦጭ አደጋውን መከላከል እንደሚቻል እና ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አስተማማኝ የውሃ አቅርቦት ለማግኘት እንደሚረዳ ተገልጿል።

#MoSHE
@YeneTube @FikerAssefa
በቦሌ ክፍለ ከተማ ከዘራፊዎች ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ የሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን ፖሊስ አስታወቀ!

በቦሌ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ሩዋንዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኝ አንድ የቻይናዊያን መኖሪያ ቤት ላይ የዘረፋ ወንጀል ፈጽመው ለማምለጥ የሞከሩ በቁጥር 8 ግለሰቦች ከፖሊስ ጋር በከፈቱት ተኩስ ሞትና ጉዳት መድረሱን የፌዴራል ፖሊስ አስታውቋል። ተጠረጣሪዎቹ በፖሊስ ኢንተለጀንስ አባላት ክትትል እየተደረገባቸው ሳለ ወደ ቻይናውያኑ ቅጥር ጊቢ መግባታቸውን የጠቆመው መረጃው፥ ዘረፋውን ፈጽመው ሲወጡ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ቢጠየቁም አሻፈረኝ ብለው ተኩስ መክፈታቸው በተደረገው የተኩስ ልውውጥ ሂደት ሊያመልጡ የሞከሩ ሁለት ግለሰቦች አንዱ ህይወቱ ሲያልፍ ሌላኛው ቆሰሎ ለህክምና ወደ ሆስፒታል ሲወሰድ ስድስቱ በቁጥጥር ሰር እንዲውሉ ተደርጓል።

ግለሰቦቹ ቀደም ሲልም የተለያዩ የጸጥታ አካላትን የደንብ ልብሶች በመልበስ እና የጦር መሳሪያ በመታጠቅ እንዲሁም የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን በመጠቀም በተለያዩ ስፍራዎች የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶችን ሲፈጽሙ ለመቆየታቸው ከህብረተሰቡ በተለያዩ ጊዜ የደረሱ ጥቆማዎች የሚያመላክቱ ሲሆን በዛሬው ዕለትም በተለመደው ሁኔታ የወንጀል ድርጊታቸውን ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ ህብረተሰቡ በሰጠው ጥቆማ በቁጥጥር ስር ውለው በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል።ህብረተሰቡ የጸጥታ ኃይሎችን የደንብ ልብስ በመልበስ፣ የጦር መሳሪያ በመታጠቅ እና ህግ አስከባሪ በመምሰል ወደ መኖሪያ ቤቱ የሚመጡ ግለሰቦች ሁኔታ አጠራጣሪ ሆኖ ሲያገኝ ለአካባቢው ፖሊስ በመጠቆም ወይም በ987 ነፃ የስልክ መስመር በመጠቀም የወንጀል ድርጊቱ እንዲገታ ለፖሊስ የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪውን አቅርቧል።

#ETV
@YeneTube @FikerAssefa
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 250 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የ8 ሰዎች ህይወት አልፏል።

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5414 የላብራቶሪ ምርመራ 250 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 5425 ደርሷል።

ከጠቅላላው የላብራቶሪ ምርምራ ውስጥ 32 (11 ከጤና ተቋም እና 21 ከማህበረሰብ በተወሰደ ናሙና) ናሙናዎች በአስክሬን ላይ የተደረገ የላብራቶሪ ምርምራ ሲሆን 6 ናሙናዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። ከዚህ ባለፈ ሁለት በህክምና ማዕከል ውስጥ በህክምና ላይ የነበሩ ሰዎች ህይወት አልፏል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 89 ደርሷል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
ዛሬ ቫይረሱ የተገኘባቸው 250 ሰዎች ሲሆኑ ከአስሩ በስተቀር ሁሉም ኢትዮጵያውያን ናቸው። በፆታ ሲታይ ደግሞ ወንድ(158) ሴት(92) ናቸው!

➡️ዕድሜያቸው ከ3 ወር-90 አመት የሆኑ

➡️ተጨማሪ 144 ሰዎች (124 ከአዲስ አበባ፣ 7 ከትግራይ ክልል፣ 5 ከሶማሊ ክልል፣ 2 ከኦሮሚያ ክልል እና 7 ከአማራ ክልል) ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1688 ነው።

➡️የተገኙት ከአዲስ አበባ(177)፣ ከትግራይ ክልል(21)፣ ከኦሮሚያ ክልል(8)፣ከሶማሊ ክልል(4)፣ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል(1)፣ ከጋምቤላ ክልል(18)፣ ከአማራ ክልል(20) እና ከድሬዳዋ(1) በድምር 250 ሰዎች ናቸው።

➡️በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 5425 ደርሷል።

➡️በጠና የታመሙት ቁጥር ደግሞ 27 ነው።

➡️በ24 ሰዓት ውስጥ 8 ሞት የተመዘገበ ሲሆን፣ እስካሁን በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 89 ነው።

@YeneTube @FikerAssefa
12 ድርጅቶች በቴሌኮም ዘርፍ ለመሰማራት ፍላጎት አሳዩ!

ባሳለፍነው ሰኞ እኩለ ቀን በተዘጋው የፍላጎት መጠይቅ 12 ድርጅቶች ፍላጎታቸውን መግለፃቸውን የኢትዮጵያ የኮሚኒኬሽን ባለስልጣን ለካፒታል ጋዜጣ በላከው መግለጫ አስታወቀ፡፡ከ12ቱ ድርጅቶች ዘጠኙ የቴሌኮም ድርጅቶች ሁለቱ በሌላ ዘርፍ ያሉ እና አንድ ድርጅት ያልተሟላ ሰነድ ያስገቡ እደሆኑ ታውቋል፡፡የቴሌኮም ድርጅቶቹ Vodafone, Vodacom, and Safaricom (በጋራ) Etisalat, Axian, MTN, Orange, Saudi Telecom Company, Telkom SA, Liquid Telecom እና Snail Mobile ሲሆኑ፡፡ ሁለቱ የቴሌኮም አንቀሳቃሽ ያልሆኑት ድርጅቶች ደግሞ Kandu Global Telecommunications እና Electromecha International Projects የተባሉ ናቸው፡፡ከሁለት አመት በፊት የቀድሞው ገዥ ፓርቲ ኢህአዴግ ማእከላዊ ኮሚቴ የመንግስት ግዙፍ ድርጅቶችን በከፊል ወይም በሙሉ ለመሸጥ እንዲሁም በመንግስት ሙሉ ድርሻ ተይዘው የነበሩ ዘርፎችን ለተጨማሪ አንቀሳቃሾች በከፊል እንዲከፈቱ በወሰነው መሰረት የቴሌኮም ዘርፉ ቀዳሚ ሆኗል፡፡ለአንድ ወር የቆየው የፍላጎት መጠይቅ ሁለት ተጨማሪ የቴሌኮም አንቀሳቃሾችን በአገሪቱ ለማስገባት ያለመ ነው፡፡

#Capital
@YeneTube @FikerAssefa
ለጤና ተቋማት የሕክምና ግብዓቶችና የኢንፌክሽን መከላከያ ቁሳቁስ ለሟሟላት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ገለጹ።

የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ዛሬ በሰጡት መግለጫ፤ ለጤና ተቋማቱ በግዥ አልያም በዕርዳታ የሚገኙ የሕክምና መሳሪያዎችና ግብዓቶችን የማሰባሰብ ሥራው ተጠናክሯል ብለዋል።በተለይም በጽኑ ሕሙማን ክትትል ለሚገኙ የኮቪድ-19 ታካሚዎች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ የሕክምና ግብዓቶችን ለማሟላት አጽንኦት መሰጠቱን ገልጸዋል።ያም ሆኖ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው የግብዓት እጥረትና አንዳንድ አምራች አገራት ምርታቸውን ወደ ሌሎች አገራት መላክ ማቆማቸው ጫና አሳድሯል ነው ያሉት።ይህን ክፍተት ለመሙላት በተለይም የአገር ውስጥ አምራች ኩባንያዎች በስፋት ወደ ምርት ሥራ እንዲገቡ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ምንጭ: ኢዜአ
@YeneTube @FikerAssefa
ከሰኔ 15ቱ የአማራ ክልል አመራሮች እና የጸጥታ አካላት ግድያ ጋር ተጠርጥሮ በእስር የቆየው መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ የወንጀል ድርጊቱን ስለመፈጸሙ የሚያስረዳ የሰውም ሆነ የጽሁፍ ማስረጃ ባለማግኘቱ መዝገቡን መዝጋቱን የክልሉ ዐቃቤ ሕግ አስታወቀ።

Via ELU
@YeneTube @FikerAssefa
በአዲስ አበባ በ 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 177 ሰዎች ኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ እስከ ዛሬ ድረስ በተደረጉ የላቦራቶሪ ምርመራዎች አድራሻቸው አዲስ አበባ የሆኑ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 3545 ደርሷል፡፡ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ በከተማዋ የ7 ኢትዮጵያውያን ህይወት አልፏል።በሌላ በኩል ደግሞ በትላንትናው እለት 123 ሰዎች ከኮሮና በሽታ ማገገማቸውን የጤና ቢሮ አስታውቋል፡፡

አዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓታት ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች በክፍለ ከተማ፤-

👉አዲስ ከተማ 24
👉ቦሌ 4
👉ጉለሌ 11
👉ልደታ 26
👉ኮልፌ ቀራንዮ 12
👉ቂርቆስ 6
👉አራዳ 9
👉የካ 4
👉ንፋስ ስልክ ላፍቶ 4
👉አቃቂ ቃሊቲ 7
👉አድራሻቸው በመጣራት ላይ ያለ 4

@YeneTube @FikerAssefa
የኢትዮጵያ የ10 ዓመት መሪ የልማት ዕቅድ መነሻ ሰነድ ለሕዝብ ውይይት እንደሚቀርብ የፕላንና ልማት ኮሚሽን አስታወቀ።

ኮሚሽኑ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የመነሻ ሰነዱ ውይይት ከመጪው ሰኞ ጀምሮ ለ11 ቀናት ይካሄዳል።የውይይቱ ዓላማ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በዕቅድ ዝግጅቱ እንዲሳተፉ ማስቻል፣ ከኅብረተሰቡ በሚገኝ ግብዓት ዕቅዱን ማዳበርና ግልጽ ባልሆኑ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ መስጠት መሆኑን ጠቁሟል።የተቋማት የ10 ዓመት መሪ የልማት ዕቅድ መነሻ ሰነድ በሃላፊዎቻቸው በተሰጣቸው የጊዜ ሰሌዳ ለውይይት እንደሚቀርብም ተገልጿል።ዝግጅቱ በተቋሙ የፌስ ቡክ ገጽ፣ በዩቲዩብ ቻናልና በፋና ቴሌቪዥን በቀጥታ ለሕዝብ ይቀርባል።

ምንጭ:ኢዜአ
@YeneTube @FikerAssefa
የሲዳማ ክልል በጀት ለብቻ እንዲቀርብ ተወሰነ!

ዛሬ በገቢ፣ በጀት እና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ በተጠራው እና በ2013 ዓ/ም በጀት አመት ረቂቅ በጀት ላይ በተደረገው ውይይት በቅርቡ በክልልነት ለተደራጀው የሲዳማ ክልል በጀት ለብቻ መቅረብ እንዳለበት የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወ/ሮ ለምለም ሃድጉ አሳሰቡ፡፡ክልሉ እንደ ክልል እንዲደራጅ መወሰኑን ያስታወሱት የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የክልሉ በጀት ለብቻ የማይቀርብበት ምንም ምክንያት የለም በመሆኑም ከደቡብ ክልል ተነጥሎ ለብቻ ይቅረብ ብለዋል፡፡በሰኔ 4 የበጀት መግለጫቸው ወቅት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የሲዳማን በጀት ለምን ለብቻ አልቀረበበም ለሚል ተደጋጋሚ የፓርላማ አባላት ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ የአዲሱን ክልል በጀት ለብቻ ማቅረብ በቀላሉ የመነጠል ስራ ነው ማለታቸው ይታወሳል፡፡ ወ/ሮ ለምለምም ዛሬ በነበረው ከባለድርሻዎች እና ከህዝብ ለሚቀርቡ ጥያቄዎች በሚመክረው የረቂቅ በጀት መድረክ የክልሉ በጀት ለብቻ እንደሚቀርብ ገልፀዋል፡፡

Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
በሐይማኖት በዳዳ ግድያ ወንጀል የተጠረጠረው ወጣት "ተገድጄ ነው ወንጀሉን የፈፅምኩት" ሲል ለፍርድ ቤት ዛሬ ቃሉን ሰጥቷል።

በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የጤና ኮሌጅ የሁለተኛ ድግሪ ተማሪ የነበረችው እና ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ/ም በኮሌጁ አስተዳደር ህንፃ ላይ በሚገኘው የላቦራቶሪ ቤተ ሙከራ ክፍል ለምርምር በገባችበት ሁኔታ ህይወቷ ያለፈው ሀይማኖት በዳዳ በመግደል የተጠረጠረው ደግነት ወርቁ የተባለው ወጣት ዛሬ ፒያሳ በሚገኘው አራዳ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን ወንጀሉን የፈፀመው ተገዶ አንደሆነ ቢናገረም ማን እንዳስገደደው ግን አልተናገረም።ፖሊስ በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ምርመራ ለማድረግ 14 ቀናትን የጠየቀ ሲሆን ቀጣዩም ችሎት ለሐምሌ 3/2012 ዓ.ም ቀጠሮ ይዟል።

Via Fidelpost
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን "ታላቁ የኅዳሴ ግድብን በውኃ መሙላትን ጨምሮ አንዳች ስምምነት ሳይደረስ የተናጠል እርምጃ ላለመውሰድ መስማማታቸውን" የግብጽ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ቃል አቀባይ ባሳም ራዲ በጽሁፍ ባወጡት መግለጫ አስታወቁ።ባሳም እንዳሉት ሶስቱ አገሮች የግድቡን የውኃ አሞላል እና አስተዳደር የተመለከተ የመጨረሻ ስምምነት ለማዘጋጀት የቴክኒክና የሕግ ባለሙያዎች ኮሚቴ እንዲዋቀር ተስማምተዋል።የደቡብ አፍሪካ፣ የአውሮፓ ኅብረት፣ የአሜሪካ እና የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጽህፈት ቤት ታዛቢዎች የኮሚቴው አባል ይሆናሉ።አገራቱ በግድቡ ድርድር ላይ በመጪው ሰኞ ሊመክር ለቀጠረው የጸጥታ ጥበቃው ምክር ቤት ስለ ጉዳዩ ደብዳቤ ይጽፋሉ።

Via Eshete Bekele
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
ኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን "ታላቁ የኅዳሴ ግድብን በውኃ መሙላትን ጨምሮ አንዳች ስምምነት ሳይደረስ የተናጠል እርምጃ ላለመውሰድ መስማማታቸውን" የግብጽ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ቃል አቀባይ ባሳም ራዲ በጽሁፍ ባወጡት መግለጫ አስታወቁ።ባሳም እንዳሉት ሶስቱ አገሮች የግድቡን የውኃ አሞላል እና አስተዳደር የተመለከተ የመጨረሻ ስምምነት ለማዘጋጀት የቴክኒክና የሕግ ባለሙያዎች ኮሚቴ እንዲዋቀር ተስማምተዋል።የደቡብ…
የውሃ ኢነርጂና መስኖ ሚንስትር አቶ ስለሺ በቀለ በዚህ ዙሪያ በትዊተር ገጻቸው እንዳሰፈሩት በወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት በተመራው ስብሰባ የሶስቱ ሀገራት መሪዎች በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ከ2-3 ሳምንታት ባለው ጊዜ ውስጥ ስምምነት ላይ ለመድረስ ተግባብተዋል።

የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂ መሃመት በበኩላቸው ሶስቱ ሀገራት የአፍሪካ ህብረት እንዲያደራድራቸው መስማማታቸውን ተናግረዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ ሊሰጥ የነበረውን ጋዜጣዊ መግለጫ "በፕሮግራም መጣበብ" ምክንያት ለሌላ ጊዜ መተላለፉ ተገልጿል።

@YeneTube @FikerAssefa
የጠ/ሚር ጽ/ቤት አሁን ባወጣው መግለጫ ኢትዮጵያ ግድቡን በሚቀጥሉት 2 ሳምንት ጊዜ ውስጥ ለመሙላት ያቀደች ሲሆን በዚሁ ጊዜ ውስጥ በአፍሪካ ህብረት መሪነት የሶስትዮሽ ድርድሩን ለማጠናቀቅ ስምምነት ላይ ተደርሷል፣ ውሃ ለመሙላት ያላለቁ የግንባታ ስራዎችም በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ይከናወናሉ ተብሏል።

@YeneTube @FikerAssefa
"ኢትዮጵያ በመጭዎቹ ሁለት ሳምንታት የግድቡን ቀሪ የግንባታ ስራዎች በማጠናቀቅ ሙሌት ትጀምራለች፣ በነዚህ ሁለት ሳምንታት ሀገራቱ ስምምነት ላይ ለመድረስ ወስነዋል።"

#PMOEthiopia
@YeneTube @FikerAssefa
የህዳሴ ግድብ ውሀ ሙሌት ተራዝሟል ተብሎ የሚፃፈው እና የሚነገረው ስህተት እንደሆነ የውሀ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ዛሬ አሳውቀውኛል!

"ትክክል አይደለም! በሁለት ሳምንት ግዜ ውስጥ ስምምነት ላይ እንድንደርስ፣ እስከዛውም ለውሀ ሙሌት ዝግጅት እንድናደርግ ነው ያለን አካሄድ" ብለውኛል።

Via Elias Meseret
@YeneTube @FikerAssefa
ከጀሞ 2 እስከ ጀነራል ዊንጌት የሚገነባው የፈጣን ከተማ አውቶብስ መንገድ ግንባታ ተጀመረ!

የመንገዱን ግንባታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድና ኢ/ር ታከለ ኡማ አስጀምረውታል።መንገዱ በአጠቃላይ 20 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን ወደ ሁለት አቅጣጫ የሚዘረጋ ነው ተብሏል።የፈጣን አውቶብስ መንገዱ አዲስ ከተማ፣ልደታ፣ቂርቆስና ኮልፌ በመሳሰሉ ቦታዎች የአውቶብስ መቆሚያዎች ይኖሩታል መባሉን ከከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።

@YeneTube @FikerAssefa