የቀድሞ የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር አምባቸው መኮንንና ጓዶቻቸው የተሰዉበት አንደኛ ዓመት በደም ባንክ አገልግሎት ቅጥር ግቢ ውስጥ ደም በመለገስ ታሰበ።
መርሃ ግብሩ "ደም እንለግሳለን እንጂ ደም አናፈስም፤ ደም ያፈሰሱትን በሕግ እንጠይቃለን" በሚል መሪ ሀሳብ ነው የተከናወነው።በዚህም ከመቶ በላይ የሚሆኑ የቀድሞ የሥራ ባልደረቦች፣ ቤተሰቦችና ሌሎች ወዳጆቻቸው የመታሰቢያ ቀኑን ምክንያት በማድረግ ደም ለግሰዋል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa
መርሃ ግብሩ "ደም እንለግሳለን እንጂ ደም አናፈስም፤ ደም ያፈሰሱትን በሕግ እንጠይቃለን" በሚል መሪ ሀሳብ ነው የተከናወነው።በዚህም ከመቶ በላይ የሚሆኑ የቀድሞ የሥራ ባልደረቦች፣ ቤተሰቦችና ሌሎች ወዳጆቻቸው የመታሰቢያ ቀኑን ምክንያት በማድረግ ደም ለግሰዋል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa
በትላንትናው ዕለት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ183 ሺህ በላይ ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የዓለም ጤና ድርጅት ገለጸ!
በትላንትናው ዕለት በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር እስካሁን ባልታየ መልኩ ዕለታዊ ጭማሪ መመዝገቡን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ።ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ የተመዘገበው አዲስ የኮሮና ቫይረስ ሕሙማን ቁጥር ዕለታዊ ሪከርድ ሆኗል ያለው የዓለም ጤና ድርጅት፣ ለዚህም የሰሜን እና ላቲን አሜሪካ ሀገራት ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚወስዱ ገልጿል።በዕለቱ ከ183 ሺህ በላይ አዲስ የኮሮና ቫይረስ ሕሙማን መመዝገባቸውን ነው ድርጅቱ ያስታወቀው።
ከእነዚህ ውስጥ ከ50 ሺህ በላይ የተመዘገበው ብራዚል ውስጥ ሲሆን፣ አሜሪካ እና ሕንድ በተከታታይ ከፍተኛ ቁጥር ያስመዘገቡ ሀገራት መሆናቸውን ጠቁሟል።ይህን ያህል ከፍተኛ ቁጥር መመዝገቡ በከፊል በዓለም ዙሪያ እየተደረገ ያለው የኮሮና ቫይረስ ምርመራ እያደገ መምጣቱን የሚያንፀባርቅ ይሆናል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።በሌላ በኩል እስካሁን በዓለም ላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ9 ሚሊዮን 51 ሺህ በላይ መድረሱን ከወርልዶሜትርስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።ከእነዚህ መካከል ከ4 ሚሊዮን 842 ሺህ በላይ ሲያገግሙ ወደ 471 ሺህ ገደማ ደግሞ ሕይወታቸው አልፏል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa
በትላንትናው ዕለት በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር እስካሁን ባልታየ መልኩ ዕለታዊ ጭማሪ መመዝገቡን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ።ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ የተመዘገበው አዲስ የኮሮና ቫይረስ ሕሙማን ቁጥር ዕለታዊ ሪከርድ ሆኗል ያለው የዓለም ጤና ድርጅት፣ ለዚህም የሰሜን እና ላቲን አሜሪካ ሀገራት ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚወስዱ ገልጿል።በዕለቱ ከ183 ሺህ በላይ አዲስ የኮሮና ቫይረስ ሕሙማን መመዝገባቸውን ነው ድርጅቱ ያስታወቀው።
ከእነዚህ ውስጥ ከ50 ሺህ በላይ የተመዘገበው ብራዚል ውስጥ ሲሆን፣ አሜሪካ እና ሕንድ በተከታታይ ከፍተኛ ቁጥር ያስመዘገቡ ሀገራት መሆናቸውን ጠቁሟል።ይህን ያህል ከፍተኛ ቁጥር መመዝገቡ በከፊል በዓለም ዙሪያ እየተደረገ ያለው የኮሮና ቫይረስ ምርመራ እያደገ መምጣቱን የሚያንፀባርቅ ይሆናል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል።በሌላ በኩል እስካሁን በዓለም ላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር ከ9 ሚሊዮን 51 ሺህ በላይ መድረሱን ከወርልዶሜትርስ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።ከእነዚህ መካከል ከ4 ሚሊዮን 842 ሺህ በላይ ሲያገግሙ ወደ 471 ሺህ ገደማ ደግሞ ሕይወታቸው አልፏል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa
YeneTube
Photo
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰሞኑን ከአልጄዚራ ጋር ቃለ ምልልስ አድርገዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በተለይ በህዳሴዉ ግድብ ዙሪያ ከአልጀዚራ አረብኛ ስርጭት ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ ትናንት ሰኔ 16 ቀን 2012 ዓም ማምሻዉን በጣቢያዉ ተላልፏል።በዚሁ መሰረት በጣቢያዉ የኢትዮጵያ ቢሮ ሃላፊ መሀመድ ጣሃ ተወኩል በኩል ለቀረበላቸው ጥያቄዎች አቶ ገዱ ምላሽ ሰጥተዋል።ግብጽ በጎረቤት አገሮች ላይ የጦር ካምፕ ለመመስረትና የኢትዮጵያን ደህንነት ለመፈታተን የምታደርገዉን ጥረት በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ ግብጽ የተለያዪ ሙከራዎችን በመጠቀም ላይ መሆኗን፤ ነገር ግን ኢትዮጵያ ከሁሉም ጎረቤት አገረቿ ጋር ማለትም ከሱዳን፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኤርትራ ጋር ጠንካራ ግንኙነት ያላት በመሆኑ ሙከራው የማይሳካ ህልም ነው ብለዋል።
ከዚህ ባለፈ የጎረቤት አገሮች ግንኙነታቸውን በማጠናከር ወደ ኢኮኖሚያዊ ትስስር እና ውህደት እያመሩ በመሆኑ በዚህ ሁኔታ ሲመዘን አገራቱ ግብጽን በመደገፍ ኢትዮጵያን ለማጥቃት ይንቀሳቀሳሉ ብለዉ እንደማያምኑም አቶ ገዱ ገልጸዋል።በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ያለዉ ግንኙነት ከመቼውም ጊዜ በተሻለ በከፍተኛ ደረጃ እየተጠናከረ እንደመጣ የገለጹት አቶ ገዱ፤ ከእርሻ መሬት ጋር በተያያዘ በድንበር አካባቢ የሚነሳው ችግር ለዘመናት የቆየ በመሆኑ ችግሩን በዘለቄታው ለመፍታት ሁለቱ አገራት በጋራ እና በትብብር እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ እና በሱዳን ድንበር አካባቢ የተከሰተውን ሰሞነኛ ክስተት የግብጽ ሚዲያዎች እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመጠቀም የሁለቱን አገራት ግንኙነት ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ እንዲያመራ በስፋት ሲሰሩ መቆየታቸውንም አቶ ገዱ አብራርተዋል።የግብጽ ሚዲያዎች ሃላይብ ትሪያንግል በመባል የሚታወቀውን የሱዳን መሬት ግብጽ በወረራ መያዟን በተመለከተ አንድም ቀን ሳይተነፍሱ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል ያለውን የድንበር ጉዳይ እንደ ትልቅ አጀንዳ አንስተው ሰፊ ሽፋን መስጠታቸው ያላቸውን ተዓማኒነት ትዝብት ውስጥ እንደሚከትም የተናገሩት።ግብጾች ግድቡን ከእስራኤል ጋር ለማገናኘት መሞከራቸው ስህተት ብቻ ሳይሆን ወንጀል መሆኑንም አቶ ገዱ በነበራቸው ቃለ ምልልስ መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በተለይ በህዳሴዉ ግድብ ዙሪያ ከአልጀዚራ አረብኛ ስርጭት ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ ትናንት ሰኔ 16 ቀን 2012 ዓም ማምሻዉን በጣቢያዉ ተላልፏል።በዚሁ መሰረት በጣቢያዉ የኢትዮጵያ ቢሮ ሃላፊ መሀመድ ጣሃ ተወኩል በኩል ለቀረበላቸው ጥያቄዎች አቶ ገዱ ምላሽ ሰጥተዋል።ግብጽ በጎረቤት አገሮች ላይ የጦር ካምፕ ለመመስረትና የኢትዮጵያን ደህንነት ለመፈታተን የምታደርገዉን ጥረት በተመለከተ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሚኒስትሩ በሰጡት ምላሽ ግብጽ የተለያዪ ሙከራዎችን በመጠቀም ላይ መሆኗን፤ ነገር ግን ኢትዮጵያ ከሁሉም ጎረቤት አገረቿ ጋር ማለትም ከሱዳን፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን እና ኤርትራ ጋር ጠንካራ ግንኙነት ያላት በመሆኑ ሙከራው የማይሳካ ህልም ነው ብለዋል።
ከዚህ ባለፈ የጎረቤት አገሮች ግንኙነታቸውን በማጠናከር ወደ ኢኮኖሚያዊ ትስስር እና ውህደት እያመሩ በመሆኑ በዚህ ሁኔታ ሲመዘን አገራቱ ግብጽን በመደገፍ ኢትዮጵያን ለማጥቃት ይንቀሳቀሳሉ ብለዉ እንደማያምኑም አቶ ገዱ ገልጸዋል።በኢትዮጵያ እና በሱዳን መካከል ያለዉ ግንኙነት ከመቼውም ጊዜ በተሻለ በከፍተኛ ደረጃ እየተጠናከረ እንደመጣ የገለጹት አቶ ገዱ፤ ከእርሻ መሬት ጋር በተያያዘ በድንበር አካባቢ የሚነሳው ችግር ለዘመናት የቆየ በመሆኑ ችግሩን በዘለቄታው ለመፍታት ሁለቱ አገራት በጋራ እና በትብብር እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል።
በኢትዮጵያ እና በሱዳን ድንበር አካባቢ የተከሰተውን ሰሞነኛ ክስተት የግብጽ ሚዲያዎች እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመጠቀም የሁለቱን አገራት ግንኙነት ወደ አልተፈለገ አቅጣጫ እንዲያመራ በስፋት ሲሰሩ መቆየታቸውንም አቶ ገዱ አብራርተዋል።የግብጽ ሚዲያዎች ሃላይብ ትሪያንግል በመባል የሚታወቀውን የሱዳን መሬት ግብጽ በወረራ መያዟን በተመለከተ አንድም ቀን ሳይተነፍሱ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል ያለውን የድንበር ጉዳይ እንደ ትልቅ አጀንዳ አንስተው ሰፊ ሽፋን መስጠታቸው ያላቸውን ተዓማኒነት ትዝብት ውስጥ እንደሚከትም የተናገሩት።ግብጾች ግድቡን ከእስራኤል ጋር ለማገናኘት መሞከራቸው ስህተት ብቻ ሳይሆን ወንጀል መሆኑንም አቶ ገዱ በነበራቸው ቃለ ምልልስ መግለጻቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa
በቦሌ ክፍለ ከተማ ከዘራፊዎች ጋር በተደረገ የተኩስ ልውውጥ የሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን ፖሊስ አስታወቀ!
በቦሌ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ሩዋንዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኝ አንድ የቻይናዊያን መኖሪያ ቤት ላይ የዘረፋ ወንጀል ፈጽመው ለማምለጥ የሞከሩ በቁጥር 8 ግለሰቦች ከፖሊስ ጋር በከፈቱት ተኩስ ሞትና ጉዳት መድረሱን የፌዴራል ፖሊስ አስታውቋል። ተጠረጣሪዎቹ በፖሊስ ኢንተለጀንስ አባላት ክትትል እየተደረገባቸው ሳለ ወደ ቻይናውያኑ ቅጥር ጊቢ መግባታቸውን የጠቆመው መረጃው፥ ዘረፋውን ፈጽመው ሲወጡ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ቢጠየቁም አሻፈረኝ ብለው ተኩስ መክፈታቸው በተደረገው የተኩስ ልውውጥ ሂደት ሊያመልጡ የሞከሩ ሁለት ግለሰቦች አንዱ ህይወቱ ሲያልፍ ሌላኛው ቆሰሎ ለህክምና ወደ ሆስፒታል ሲወሰድ ስድስቱ በቁጥጥር ሰር እንዲውሉ ተደርጓል።
ግለሰቦቹ ቀደም ሲልም የተለያዩ የጸጥታ አካላትን የደንብ ልብሶች በመልበስ እና የጦር መሳሪያ በመታጠቅ እንዲሁም የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን በመጠቀም በተለያዩ ስፍራዎች የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶችን ሲፈጽሙ ለመቆየታቸው ከህብረተሰቡ በተለያዩ ጊዜ የደረሱ ጥቆማዎች የሚያመላክቱ ሲሆን በዛሬው ዕለትም በተለመደው ሁኔታ የወንጀል ድርጊታቸውን ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ ህብረተሰቡ በሰጠው ጥቆማ በቁጥጥር ስር ውለው በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል።ህብረተሰቡ የጸጥታ ኃይሎችን የደንብ ልብስ በመልበስ፣ የጦር መሳሪያ በመታጠቅ እና ህግ አስከባሪ በመምሰል ወደ መኖሪያ ቤቱ የሚመጡ ግለሰቦች ሁኔታ አጠራጣሪ ሆኖ ሲያገኝ ለአካባቢው ፖሊስ በመጠቆም ወይም በ987 ነፃ የስልክ መስመር በመጠቀም የወንጀል ድርጊቱ እንዲገታ ለፖሊስ የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪውን አቅርቧል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa
በቦሌ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ሩዋንዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኝ አንድ የቻይናዊያን መኖሪያ ቤት ላይ የዘረፋ ወንጀል ፈጽመው ለማምለጥ የሞከሩ በቁጥር 8 ግለሰቦች ከፖሊስ ጋር በከፈቱት ተኩስ ሞትና ጉዳት መድረሱን የፌዴራል ፖሊስ አስታውቋል። ተጠረጣሪዎቹ በፖሊስ ኢንተለጀንስ አባላት ክትትል እየተደረገባቸው ሳለ ወደ ቻይናውያኑ ቅጥር ጊቢ መግባታቸውን የጠቆመው መረጃው፥ ዘረፋውን ፈጽመው ሲወጡ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ቢጠየቁም አሻፈረኝ ብለው ተኩስ መክፈታቸው በተደረገው የተኩስ ልውውጥ ሂደት ሊያመልጡ የሞከሩ ሁለት ግለሰቦች አንዱ ህይወቱ ሲያልፍ ሌላኛው ቆሰሎ ለህክምና ወደ ሆስፒታል ሲወሰድ ስድስቱ በቁጥጥር ሰር እንዲውሉ ተደርጓል።
ግለሰቦቹ ቀደም ሲልም የተለያዩ የጸጥታ አካላትን የደንብ ልብሶች በመልበስ እና የጦር መሳሪያ በመታጠቅ እንዲሁም የተለያዩ ተሽከርካሪዎችን በመጠቀም በተለያዩ ስፍራዎች የተለያዩ የወንጀል ድርጊቶችን ሲፈጽሙ ለመቆየታቸው ከህብረተሰቡ በተለያዩ ጊዜ የደረሱ ጥቆማዎች የሚያመላክቱ ሲሆን በዛሬው ዕለትም በተለመደው ሁኔታ የወንጀል ድርጊታቸውን ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ ህብረተሰቡ በሰጠው ጥቆማ በቁጥጥር ስር ውለው በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ እየተጣራባቸው ይገኛል።ህብረተሰቡ የጸጥታ ኃይሎችን የደንብ ልብስ በመልበስ፣ የጦር መሳሪያ በመታጠቅ እና ህግ አስከባሪ በመምሰል ወደ መኖሪያ ቤቱ የሚመጡ ግለሰቦች ሁኔታ አጠራጣሪ ሆኖ ሲያገኝ ለአካባቢው ፖሊስ በመጠቆም ወይም በ987 ነፃ የስልክ መስመር በመጠቀም የወንጀል ድርጊቱ እንዲገታ ለፖሊስ የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪውን አቅርቧል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa
ወላጆች ከ9 ወር ጀምሮ ያሉ ህፃናትን የኩፍኝ ክትባት እንዲያስከትቡ ጥሪ ቀረበ!
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ እድሜያቸው ከ9 ወር እስከ 5 አመት ለሆናቸው ህፃናት ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 2/ 2012 ዓ.ም የኩፍኝ በሽታ ዘመቻ እንደሚያካሂድ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል፡ክትባቱ ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 2/ 2012 ዓ.ም በሁሉም ጤና ተቋማት እና ጊዜያዊ የክትባት መስጫ ጣቢያዎች እንደሚሰጥ መግለጫውን የሰጡት የቢሮው ኃላፊ ዶ/ር ዮሐንስ ጫላ አስታውቀዋል።በክትባቱ ወቅት ህፃናት ለኮሮና ቫይረስ ተጋላጭ እንዳይሆኑ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጂት የተደረገ መሆኑንም ነው ኃላፊው የገለፁት፡፡ወላጆች እና አሳዳጊዎች ልጆቻቸውን በማስከተብ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ቢሮ ኃላፊው አሳስበዋል፡፡
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ እድሜያቸው ከ9 ወር እስከ 5 አመት ለሆናቸው ህፃናት ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 2/ 2012 ዓ.ም የኩፍኝ በሽታ ዘመቻ እንደሚያካሂድ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል፡ክትባቱ ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 2/ 2012 ዓ.ም በሁሉም ጤና ተቋማት እና ጊዜያዊ የክትባት መስጫ ጣቢያዎች እንደሚሰጥ መግለጫውን የሰጡት የቢሮው ኃላፊ ዶ/ር ዮሐንስ ጫላ አስታውቀዋል።በክትባቱ ወቅት ህፃናት ለኮሮና ቫይረስ ተጋላጭ እንዳይሆኑ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጂት የተደረገ መሆኑንም ነው ኃላፊው የገለፁት፡፡ወላጆች እና አሳዳጊዎች ልጆቻቸውን በማስከተብ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ቢሮ ኃላፊው አሳስበዋል፡፡
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa
በአራዳ ክፍለ ከተማ በህንፃ ግንባታ ላይ በደረሰው የመደርመስ አደጋ የ1 ሰው ህይወት ሲያልፍ በ3 ሰዎች ላይ ጉዳት ደረሰ!
በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚደረግ የማስፋፊያ ግንባታ ስራ ላይ በተሰማሩ ሰራተኞች ጉርጓድ በመደርመሱ የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ፡፡ በሁለት ሰራተኞች ላይ ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡የአራዳ ቅ/ጽ/ቤት ኦፕሬሽን ዘርፍ ኃላፊ ኮማንደር መስፍን እሽቱ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው ዛሬ ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት ገደማ ነው፡፡በዕለቱ በግንባታ ስራ ላይ ከተሰማሩት 16 ሰራተኞች ውስጥ ሶስቱ ጉርጓድ ቁፋሮ ላይ ተሰማርተው በስራ ሂደት ላይ እንደነበሩ የመደርመስ አደጋው እንደደረሰባቸው ኮማንደር መስፍን ለኢቢሲ ተናግረዋል፡፡ፖሊስና የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች 7 ሰዓታትን በፈጀው የህይወት አድን ስራ ሁለት ሰራተኞችን በህይወት ማግኘት የተቻለ ሲሆን ወደ አቤት ሆስፒታል ለህክምና መወሰዳቸውን ኮማንደር መስፍን ተናግረዋል፡፡አንድ ሰራተኛ ግን ህይወቱ ማለፉን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ወደ ተደረመሰው ህንጻ ገብተው የህወት አድን ስራውን ለመስራት መግቢያ መንገድ አለመኖሩ የህይወት አድን ስራውን አደጋች እንዳደረገውም አመልክተዋል፡፡
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚደረግ የማስፋፊያ ግንባታ ስራ ላይ በተሰማሩ ሰራተኞች ጉርጓድ በመደርመሱ የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ፡፡ በሁለት ሰራተኞች ላይ ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡የአራዳ ቅ/ጽ/ቤት ኦፕሬሽን ዘርፍ ኃላፊ ኮማንደር መስፍን እሽቱ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው ዛሬ ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት ገደማ ነው፡፡በዕለቱ በግንባታ ስራ ላይ ከተሰማሩት 16 ሰራተኞች ውስጥ ሶስቱ ጉርጓድ ቁፋሮ ላይ ተሰማርተው በስራ ሂደት ላይ እንደነበሩ የመደርመስ አደጋው እንደደረሰባቸው ኮማንደር መስፍን ለኢቢሲ ተናግረዋል፡፡ፖሊስና የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች 7 ሰዓታትን በፈጀው የህይወት አድን ስራ ሁለት ሰራተኞችን በህይወት ማግኘት የተቻለ ሲሆን ወደ አቤት ሆስፒታል ለህክምና መወሰዳቸውን ኮማንደር መስፍን ተናግረዋል፡፡አንድ ሰራተኛ ግን ህይወቱ ማለፉን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ወደ ተደረመሰው ህንጻ ገብተው የህወት አድን ስራውን ለመስራት መግቢያ መንገድ አለመኖሩ የህይወት አድን ስራውን አደጋች እንዳደረገውም አመልክተዋል፡፡
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
ጨፌ ኦሮሚያ 12ኛ መደበኛ፣ 5ኛ ዓመት 5ኛ የሥራ ዘመን ጉባዔውን ሐምሌ 18 እና 19 እንደሚያካሂድ የጨፌው አፈ-ጉባዔ ወ/ሮ ሎሚ በዶ አስታወቁ።
አፈ-ጉባዔዋ በዛሬው ዕለት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ጨፌው በሁለት ቀን ውሎው የ2012 ዓ.ም የሥራ አፈፃፀም እንደሚገመግም እና የ2013 በጀት እንደሚያፀድቅ ጠቁመዋል። በተጨማሪም የሕግ ማርቀቅ እና በተጓደሉ አመራች ቦታ ሹመት ማፅደቅ ሥራ የሚሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
አፈ-ጉባዔዋ በዛሬው ዕለት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ ጨፌው በሁለት ቀን ውሎው የ2012 ዓ.ም የሥራ አፈፃፀም እንደሚገመግም እና የ2013 በጀት እንደሚያፀድቅ ጠቁመዋል። በተጨማሪም የሕግ ማርቀቅ እና በተጓደሉ አመራች ቦታ ሹመት ማፅደቅ ሥራ የሚሠራ መሆኑን አብራርተዋል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
በኢትዮጵያ የብሔራዊ ሎጂስቲክስ ምክር ቤት ተቋቋመ!
በኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ሥርዓትን ለማሻሻል እና ተወዳዳሪ ለማድረግ በዘርፉ ቁልፍ ሚና ያላቸውን ተቋማት በጋራ ማቀናጀት የሚያስችል የብሔራዊ ሎጂስቲክስ ምክር ቤት ማቋቋሙን የትራንስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ምክር ቤቱ የትራንስፖርት ሚኒስቴር እና የሎጂስቲክስ ትራንስፎርሜሽን ጽ/ቤትን ጨምሮ 11 አባላት ያሉት ሆኖ በዛሬው ዕለት ተመሥርቷል። በዛሬው ዕለት የተቋቋመው ምክር ቤት የዕቃ እና የሰነድ ፍሰት፣ የመሠረተ-ልማት አጠቃቀም፣ አሠራር እና የሰው ኃይልን ለመምራት ያስችላል ተብሏል። ከዚህ በተጨማሪም የሎጂስቲክስ ስትራቴጂ ውጤታማነት ላይ ግልጽ አመራር ለመስጠት እንዲሁም በዘርፉ ላይ ያሉ ማነቆዎችን በመለየት እና መፍትሔ በማመላከት ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተጠቁሟል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
በኢትዮጵያ የሎጂስቲክስ ሥርዓትን ለማሻሻል እና ተወዳዳሪ ለማድረግ በዘርፉ ቁልፍ ሚና ያላቸውን ተቋማት በጋራ ማቀናጀት የሚያስችል የብሔራዊ ሎጂስቲክስ ምክር ቤት ማቋቋሙን የትራንስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ምክር ቤቱ የትራንስፖርት ሚኒስቴር እና የሎጂስቲክስ ትራንስፎርሜሽን ጽ/ቤትን ጨምሮ 11 አባላት ያሉት ሆኖ በዛሬው ዕለት ተመሥርቷል። በዛሬው ዕለት የተቋቋመው ምክር ቤት የዕቃ እና የሰነድ ፍሰት፣ የመሠረተ-ልማት አጠቃቀም፣ አሠራር እና የሰው ኃይልን ለመምራት ያስችላል ተብሏል። ከዚህ በተጨማሪም የሎጂስቲክስ ስትራቴጂ ውጤታማነት ላይ ግልጽ አመራር ለመስጠት እንዲሁም በዘርፉ ላይ ያሉ ማነቆዎችን በመለየት እና መፍትሔ በማመላከት ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው ተጠቁሟል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ጋር እየተወያዩ ነው።
ውይይቱ በመንግሥት እና በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በወቅታዊ የአገሪቱ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው።በቀጣይም አገራዊ ምርጫን በሚመለከት ከዚህ በፊት ከተደረው ምክክር የቀጠለ ውይይት እንደሚደረግም ተገልጿል።በዚህም እስከ ሰባት በሚደርሱ አጀንዳዎች ላይ ምክክር ለማድረግ ስምምነት ተደርሷል፣ በቅድሚያ ግን ውይይት የሚደረግባቸው አራት አጀንዳዎችም ተለይተዋል።በቅድሚያ አገራዊ መግባባት ላይ ውይይት ለማድረግ የተስማሙ ሲሆን፣ በዚህም ጉዳይ ላይ ገለጻ ለማድረግ እና ለማወያየት ከተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ሰዎች ተመርጠዋል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
ውይይቱ በመንግሥት እና በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በወቅታዊ የአገሪቱ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው።በቀጣይም አገራዊ ምርጫን በሚመለከት ከዚህ በፊት ከተደረው ምክክር የቀጠለ ውይይት እንደሚደረግም ተገልጿል።በዚህም እስከ ሰባት በሚደርሱ አጀንዳዎች ላይ ምክክር ለማድረግ ስምምነት ተደርሷል፣ በቅድሚያ ግን ውይይት የሚደረግባቸው አራት አጀንዳዎችም ተለይተዋል።በቅድሚያ አገራዊ መግባባት ላይ ውይይት ለማድረግ የተስማሙ ሲሆን፣ በዚህም ጉዳይ ላይ ገለጻ ለማድረግ እና ለማወያየት ከተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ሰዎች ተመርጠዋል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
በአቶ ጃዋር መሐመድ ላይ ለነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጠ!
የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በአቶ ጃዋር መሐመድ ላይ ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ በማየት 12 ቀን ፈቅዶ ለነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።ሁከት እና ብጥብጥ በተከሰተባቸው የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች የተሰማራው የምርመራ ቡድን በርካታ የሰው ሞት እና የንብረት ውድመት የተመለከተ መረጃ መላኩንም ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።አቶ ጃዋር በበኩሉ የተከሰተው ወንጀል እሱን እንደማይመለከት እና ሚዲያዎች ችሎቱን እንዳይዘግቡ ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።ተጠርጣሪው አቶ ጃዋር ያቆማቸው 9 ጠበቆች የምርመራ ሥራው አዲስ አለመሆኑንና ፖሊስ የጠየቀው የጊዜ ቀጠሮ ውድቅ እንዲሆን ወይም ጥቂት ቀን እንዲሆንም ጠይቀዋል።ፍርድ ቤቱም ፖሊስ ቀደም ሲል በተሰጠው 13 ቀናት ውስጥ ምርመራውን በአግባቡ በማከናወኑ እና ቀሪ ሥራዎችን ለማጠናቀቅ የጠየቀውን ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ አይቶ 12 ቀን በመፍቀድ ለነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
የፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በአቶ ጃዋር መሐመድ ላይ ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ በማየት 12 ቀን ፈቅዶ ለነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።ሁከት እና ብጥብጥ በተከሰተባቸው የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች የተሰማራው የምርመራ ቡድን በርካታ የሰው ሞት እና የንብረት ውድመት የተመለከተ መረጃ መላኩንም ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል።አቶ ጃዋር በበኩሉ የተከሰተው ወንጀል እሱን እንደማይመለከት እና ሚዲያዎች ችሎቱን እንዳይዘግቡ ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።ተጠርጣሪው አቶ ጃዋር ያቆማቸው 9 ጠበቆች የምርመራ ሥራው አዲስ አለመሆኑንና ፖሊስ የጠየቀው የጊዜ ቀጠሮ ውድቅ እንዲሆን ወይም ጥቂት ቀን እንዲሆንም ጠይቀዋል።ፍርድ ቤቱም ፖሊስ ቀደም ሲል በተሰጠው 13 ቀናት ውስጥ ምርመራውን በአግባቡ በማከናወኑ እና ቀሪ ሥራዎችን ለማጠናቀቅ የጠየቀውን ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ አይቶ 12 ቀን በመፍቀድ ለነሐሴ 5 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
በአማራ ክልል 1 ሺህ 244 የህግ ታራሚዎች በይቅርታ ተለቀቁ!
በአማራ ክልል 1 ሺህ 244 የህግ ታራሚዎች በይቅርታ መለቀቃቸውን የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታወቀ። የአቃቤ ሕጉ ህዝብ ግንኙነት ጉዳዮች ኃላፊ አቶ አለምሸት ምህረቴ ለኢዜአ እንደገለጹት የህግ ታራሚዎቹ በይቅርታ የተለቀቁት ከሐምሌ 21/2012 ዓ.ም ጀምሮ ነው።ይቅርታ የተደረላቸውም በመደበኛው የይቅርታ አዋጅ ቁጥር 136/1998 መሰረት እና በልዩ ይቅርታ ቦርድ ጉዳያቸው ተጣርቶ የቀረቡ ናቸው ብለዋል።
የዕድሉ ተጠቃሚ ከሆኑት መካከልም ዕድሜያቸው የገፋ፣ የጤና ችግር ያለባቸው፣ አንድ ሶስተኛውን እስር ጊዜያቸውን ያጠናቀቁና የባህሪ ለውጥ ያመጡ ይገኙበታል።በይቅርታ ከተለቀቁት ውስጥ 22 ሴቶች መሆናቸውንም አመልክተዋል።
በሙስና ፣ በጠለፋና አስገድዶ መድፈር ወንጀል የተፈረደባቸው በይቅርታው አለመካተታቸውን ነው ኃላፊው ያሰረዱት።ይቅርታ የተደረገላቸው የህግ ታራሚዎች ወደ ህብረተሰቡ ሲቀላቀሉ የበደሉትን ህዝብ በልማት ለመካስ ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው ያሳሰቡት ደግሞ የክልሉ ይቅርታ ቦርድ ጽህፈት ቤት ተወካይ ኃላፊ አቶ አምባው አስረስ ናቸው።ህብረተሰቡም በጥፋታቸው የተፀፀቱና ታርመው የተለቀቁ መሆኑን ተገንዝቦ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሊደግፋቸውና ሊያግዛቸው እንደሚገባም አመልክተዋል።በክልሉ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በመጋቢት ወር 2012 ዓ.ም መንግስት በልዩ ሁኔታ ባደረገው ይቅርታ ከ7 ሺህ የሚበልጡ የህግ ታራሚዎች እንዲለቀቁ መደረጉ ይታወቃል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
በአማራ ክልል 1 ሺህ 244 የህግ ታራሚዎች በይቅርታ መለቀቃቸውን የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታወቀ። የአቃቤ ሕጉ ህዝብ ግንኙነት ጉዳዮች ኃላፊ አቶ አለምሸት ምህረቴ ለኢዜአ እንደገለጹት የህግ ታራሚዎቹ በይቅርታ የተለቀቁት ከሐምሌ 21/2012 ዓ.ም ጀምሮ ነው።ይቅርታ የተደረላቸውም በመደበኛው የይቅርታ አዋጅ ቁጥር 136/1998 መሰረት እና በልዩ ይቅርታ ቦርድ ጉዳያቸው ተጣርቶ የቀረቡ ናቸው ብለዋል።
የዕድሉ ተጠቃሚ ከሆኑት መካከልም ዕድሜያቸው የገፋ፣ የጤና ችግር ያለባቸው፣ አንድ ሶስተኛውን እስር ጊዜያቸውን ያጠናቀቁና የባህሪ ለውጥ ያመጡ ይገኙበታል።በይቅርታ ከተለቀቁት ውስጥ 22 ሴቶች መሆናቸውንም አመልክተዋል።
በሙስና ፣ በጠለፋና አስገድዶ መድፈር ወንጀል የተፈረደባቸው በይቅርታው አለመካተታቸውን ነው ኃላፊው ያሰረዱት።ይቅርታ የተደረገላቸው የህግ ታራሚዎች ወደ ህብረተሰቡ ሲቀላቀሉ የበደሉትን ህዝብ በልማት ለመካስ ጠንክረው መስራት እንዳለባቸው ያሳሰቡት ደግሞ የክልሉ ይቅርታ ቦርድ ጽህፈት ቤት ተወካይ ኃላፊ አቶ አምባው አስረስ ናቸው።ህብረተሰቡም በጥፋታቸው የተፀፀቱና ታርመው የተለቀቁ መሆኑን ተገንዝቦ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሊደግፋቸውና ሊያግዛቸው እንደሚገባም አመልክተዋል።በክልሉ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በመጋቢት ወር 2012 ዓ.ም መንግስት በልዩ ሁኔታ ባደረገው ይቅርታ ከ7 ሺህ የሚበልጡ የህግ ታራሚዎች እንዲለቀቁ መደረጉ ይታወቃል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
በ750 ሚሊዮን ብር ወጪ የተገነባው የፌዴራል ዳኞች የጋራ መኖሪያ ቤት ተመረቀ!
በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የፌዴራል መንግስት ህንጻዎች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በ750 ሚሊዮን ብር ወጪ ተገንብቶ የተጠናቀቀው የፌዴራል ዳኞች የጋራ መኖሪያ ቤት ተመርቋል።በምርቃት ስነ-ስርአቱ ላይ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የጋራ መኖሪያ ቤቱን ቁልፍ ከከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትሯ ኢ/ር አይሻ መሀመድ ተረክበዋል።ግንባታው ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞለት የተጀመረ ቢሆንም ከታሰበለት በታች 750 ሚሊዮን ብር ባልበለጠ በጀት ለማጠናቀቅ እንደተቻለ ተነግሯል፡፡በዛሬው ዕለት 80 ቤቶች የተላለፉ ሲሆን የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ግንባታ ፕሮጀክት በልዩ ልዩ ምክንያቶች መጠናቀቅ ከነበረበት ጊዜ ዘግይቶ የተጠናቀቀ ቢሆንም በጥራትና በበጀት አፈፃፀም በኩል በስኬት የተጠናቀቀ ነው ማለታቸውን የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር በማህበራዊ ገጹ ዘግቧል፡፡
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የፌዴራል መንግስት ህንጻዎች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በ750 ሚሊዮን ብር ወጪ ተገንብቶ የተጠናቀቀው የፌዴራል ዳኞች የጋራ መኖሪያ ቤት ተመርቋል።በምርቃት ስነ-ስርአቱ ላይ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መዓዛ አሸናፊ የጋራ መኖሪያ ቤቱን ቁልፍ ከከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትሯ ኢ/ር አይሻ መሀመድ ተረክበዋል።ግንባታው ከ900 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞለት የተጀመረ ቢሆንም ከታሰበለት በታች 750 ሚሊዮን ብር ባልበለጠ በጀት ለማጠናቀቅ እንደተቻለ ተነግሯል፡፡በዛሬው ዕለት 80 ቤቶች የተላለፉ ሲሆን የጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ግንባታ ፕሮጀክት በልዩ ልዩ ምክንያቶች መጠናቀቅ ከነበረበት ጊዜ ዘግይቶ የተጠናቀቀ ቢሆንም በጥራትና በበጀት አፈፃፀም በኩል በስኬት የተጠናቀቀ ነው ማለታቸውን የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር በማህበራዊ ገጹ ዘግቧል፡፡
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
“ድምፃችን ለግድባችን” በሚል ለሕዳሴው ግድብ ኢትዮጵያውያን ድምፅ የሚያሰሙበት መርሐ ግብር እየተከናወነ ነው!
“ድምፃችን ለግድባችን” የተሰኘ እና በመላው ዓለም ያሉ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ውኃ ሙሌትን በተመለከተ ደስታቸውን እንዲገልጹ ለማድረግ ያለመው ዝግጅት በመከናወን ላይ ይገኛል።ዝግጅቱን ሊፍት ኢትዮጵያ የተሰኘ ድርጅት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል።በአዲስ አበባ ከተማ በመካሄድ ላይ በሚገኘው መርሐ ግብር ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር በት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ ወ/ሮ ሮማን ገብረ ሥላሴን ጨምሮ በርካታ የመንግሥት ባለሥልጣናት እና የክብር እንግዶች በመታደም ላይ ናቸው።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
“ድምፃችን ለግድባችን” የተሰኘ እና በመላው ዓለም ያሉ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ውኃ ሙሌትን በተመለከተ ደስታቸውን እንዲገልጹ ለማድረግ ያለመው ዝግጅት በመከናወን ላይ ይገኛል።ዝግጅቱን ሊፍት ኢትዮጵያ የተሰኘ ድርጅት ከታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ሕዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽ/ቤት ጋር በመተባበር አዘጋጅተውታል።በአዲስ አበባ ከተማ በመካሄድ ላይ በሚገኘው መርሐ ግብር ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገዱ አንዳርጋቸው፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር በት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ ወ/ሮ ሮማን ገብረ ሥላሴን ጨምሮ በርካታ የመንግሥት ባለሥልጣናት እና የክብር እንግዶች በመታደም ላይ ናቸው።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ በአፍሪካ ኅብረት ማዕቀፍ የሚደረገው ድርድር እንደገና መቀጠሉ ተገለጸ!
የኢፌዴሪ ውኃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን ውኃ ሀብት ሚኒስቴሮች መካከል በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ በአፍሪካ ኅብረት ማዕቀፍ የሚያደርጉትን ድርድር በቪዲዮ ኮንፈረንስ አማካኝነት መቀጠሉን አስታወቋል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
የኢፌዴሪ ውኃ፣ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በኢትዮጵያ፣ ግብጽ እና ሱዳን ውኃ ሀብት ሚኒስቴሮች መካከል በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ላይ በአፍሪካ ኅብረት ማዕቀፍ የሚያደርጉትን ድርድር በቪዲዮ ኮንፈረንስ አማካኝነት መቀጠሉን አስታወቋል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
በአቶ በቀለ ገርባ ላይ ሲያካሂድ የነበረውን የምርመራ ሥራ ማጠናቀቁን የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ ቡድን አስታወቀ!
የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ ቡድን በአቶ በቀለ ገርባ ላይ ሲያካሂድ የነበረውን የምርመራ ሥራ ማጠናቀቁን አስታወቀ።ምርመራው መጠናቀቁን ተከትሎ እስካሁን ሲታይ የነበረው የጊዜ ቀጠሮ የምርመራ ሰነድ ተዘግቶ አዲስ ወደተከፈተው ቀዳሚ ምርመራ እንዲዛወርለት ጠይቋል። የቀዳሚ ምርመራ ችሎት የሚባለው ዐቃቤ ሕግ የምርመራ መዝገቡን ከፖሊስ ተቀብሎ ተጠርጣሪው ላይ የተደረገው ምርመራ ተአማኒ መሆኑን ሲያረጋግጥ የማስረጃ ጥበቃ ለማድረግ የሚከተለው ሥርዓት ነው።
በዚህ መሠረት ሕጉን ተከትሎ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ያስከፈለ በመሆኑ፣ ይህ የጊዜ ቀጠሮ ሲመለከት የነበረው ችሎት መዝገቡን ዘግቶ ወደ ቀዳሚ ምርመራ ችሎት እንዲመራው የምርመራ ቡድኑ እና ዐቃቤ ሕግ ጠይቋል። የምርመራ ቡድኑ በአቶ በቀለ ገርባ በተሰጠው ጊዜ የተለያዩ የምርመራ ሥራዎች ማከናወኑን ለአራዳ ምድብ ችሎት አስታውቋል።
በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ እና አካባቢዋ እንዲሁም በሻሸመኔ ሰኔ 23 እና 24 ቀን 2012 ዓ.ም በነበረው ብጥብጥ የደረሰውን ውድመት አስመልክቶ የትራንስፖርት ሚኒስቴር ዘርፉን የተመለከተ 45 ገጽ ያካተተ ማስረጃ ማቅረቡን ጠቅሷል።ተጠርጣሪው የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ አስከሬን በአስገዳጅ መልኩ ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ 10 ቀናት በማስለቀስ የምኒልክ ሐውልት ማፍረስ እና ቤተ መንግሥቱን መቆጣጠር ይቻላል የሚል ትእዛዝ መስጠቱን በማስረጃ ማረጋገጡን ፖሊስ ገልጿል።
ከተጠርጣሪው የተገኙት ሁለት ሽጉጦች ሕገ ወጥ መሆናቸውንም ፖሊስ ጠቅሷል።የተጠርጣሪው ጠበቆች ደንበኛቸው ፈጸሙ የተባለው ወንጀል አመላካች ነገር አልሰማንም፤ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ የምርመራ መዝገቡን አቅርቦ እንዲመረምር እና ይህ የምርመራ መዝገብ ተዘግቶ ጉዳዩ በቀዳሚ ምርመራ ይታይ ቢባል እንኳን ተጠርጣሪው የዋስ መብታቸው እንዲከበር አመልክተዋል። አቶ በቀለ ገርባ በበኩላቸው የፈጸምኩት ወንጀል የለም፤ እኔ የፖለቲካ መሪ እንጂ የምመራው ሠራዊት የለም፤ በመሆኑም በብሔር እና በሃይማኖት ግጭት የተከፈተብኝ ወንጀል እኔን የሚመለከት አይደለም ብለዋል።
ዐቃቤ ሕግ በበከሉ በተጠርጣሪው ላይ የሕዝብ ለሕዝብ ግጭት በመቀስቀስ እና በሌሎች ወንጀሎች ተጨባጭ ማስረጃ ማግኘቱን በማስታወቅ፣ ይህንን ማድረግ የሚቻለው በጊዜ ቀጠሮ ችሎት ሳይሆን በመደበኛ ክርክር ነው ብሏል።አቶ በቀለ የተጠረጠሩበትም ወንጀል የሰው ሕይወት የጠፋበት እና ከባድ በመሆኑ የዋስትና መብታቸው ሊጠበቅ አይገባም ሲል ለፍርድ ቤቱ አመልክቷል።ፍርድ ቤቱ በበኩሉ የፖሊስን የምርመራ መዝገብ መርምሮ ትእዛዝ ለመስጠት ለሐምሌ 29 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።በሌላ በኩል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አቶ ጃዋር መሐመድን ጨምሮ በ14 ተጠርጣሪዎች ላይ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል በሌላ ችሎት ማስከፈቱን ገልጿል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ ቡድን በአቶ በቀለ ገርባ ላይ ሲያካሂድ የነበረውን የምርመራ ሥራ ማጠናቀቁን አስታወቀ።ምርመራው መጠናቀቁን ተከትሎ እስካሁን ሲታይ የነበረው የጊዜ ቀጠሮ የምርመራ ሰነድ ተዘግቶ አዲስ ወደተከፈተው ቀዳሚ ምርመራ እንዲዛወርለት ጠይቋል። የቀዳሚ ምርመራ ችሎት የሚባለው ዐቃቤ ሕግ የምርመራ መዝገቡን ከፖሊስ ተቀብሎ ተጠርጣሪው ላይ የተደረገው ምርመራ ተአማኒ መሆኑን ሲያረጋግጥ የማስረጃ ጥበቃ ለማድረግ የሚከተለው ሥርዓት ነው።
በዚህ መሠረት ሕጉን ተከትሎ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ያስከፈለ በመሆኑ፣ ይህ የጊዜ ቀጠሮ ሲመለከት የነበረው ችሎት መዝገቡን ዘግቶ ወደ ቀዳሚ ምርመራ ችሎት እንዲመራው የምርመራ ቡድኑ እና ዐቃቤ ሕግ ጠይቋል። የምርመራ ቡድኑ በአቶ በቀለ ገርባ በተሰጠው ጊዜ የተለያዩ የምርመራ ሥራዎች ማከናወኑን ለአራዳ ምድብ ችሎት አስታውቋል።
በዚህም በአዲስ አበባ ከተማ እና አካባቢዋ እንዲሁም በሻሸመኔ ሰኔ 23 እና 24 ቀን 2012 ዓ.ም በነበረው ብጥብጥ የደረሰውን ውድመት አስመልክቶ የትራንስፖርት ሚኒስቴር ዘርፉን የተመለከተ 45 ገጽ ያካተተ ማስረጃ ማቅረቡን ጠቅሷል።ተጠርጣሪው የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ አስከሬን በአስገዳጅ መልኩ ወደ አዲስ አበባ ተመልሶ 10 ቀናት በማስለቀስ የምኒልክ ሐውልት ማፍረስ እና ቤተ መንግሥቱን መቆጣጠር ይቻላል የሚል ትእዛዝ መስጠቱን በማስረጃ ማረጋገጡን ፖሊስ ገልጿል።
ከተጠርጣሪው የተገኙት ሁለት ሽጉጦች ሕገ ወጥ መሆናቸውንም ፖሊስ ጠቅሷል።የተጠርጣሪው ጠበቆች ደንበኛቸው ፈጸሙ የተባለው ወንጀል አመላካች ነገር አልሰማንም፤ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ የምርመራ መዝገቡን አቅርቦ እንዲመረምር እና ይህ የምርመራ መዝገብ ተዘግቶ ጉዳዩ በቀዳሚ ምርመራ ይታይ ቢባል እንኳን ተጠርጣሪው የዋስ መብታቸው እንዲከበር አመልክተዋል። አቶ በቀለ ገርባ በበኩላቸው የፈጸምኩት ወንጀል የለም፤ እኔ የፖለቲካ መሪ እንጂ የምመራው ሠራዊት የለም፤ በመሆኑም በብሔር እና በሃይማኖት ግጭት የተከፈተብኝ ወንጀል እኔን የሚመለከት አይደለም ብለዋል።
ዐቃቤ ሕግ በበከሉ በተጠርጣሪው ላይ የሕዝብ ለሕዝብ ግጭት በመቀስቀስ እና በሌሎች ወንጀሎች ተጨባጭ ማስረጃ ማግኘቱን በማስታወቅ፣ ይህንን ማድረግ የሚቻለው በጊዜ ቀጠሮ ችሎት ሳይሆን በመደበኛ ክርክር ነው ብሏል።አቶ በቀለ የተጠረጠሩበትም ወንጀል የሰው ሕይወት የጠፋበት እና ከባድ በመሆኑ የዋስትና መብታቸው ሊጠበቅ አይገባም ሲል ለፍርድ ቤቱ አመልክቷል።ፍርድ ቤቱ በበኩሉ የፖሊስን የምርመራ መዝገብ መርምሮ ትእዛዝ ለመስጠት ለሐምሌ 29 ቀን 2012 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።በሌላ በኩል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አቶ ጃዋር መሐመድን ጨምሮ በ14 ተጠርጣሪዎች ላይ የቀዳሚ ምርመራ ፋይል በሌላ ችሎት ማስከፈቱን ገልጿል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
በባሕር ዳር ከተማ ነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓ.ም ለተሠው 'ሠማእታት' መታሠቢያ ዝግጅት ተካሄደ!
ለአማራ ሕዝብ ነፃነት፣ ፍትሕ፣ እኩልነት እና ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ሲታገሉ ነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓ.ም በባሕር ዳር ከተማ ለተሠው 'ሠማእታት' የመታሠቢያ ዝግጅት ተካሂዷል።ለእነዚህ 'ሠማእታት' ከሐምሌ 28 ጀምሮ መታሠቢያ ዝግጅት እየተከናወነ ሲሆን፣ በዚህም የችግኝ ተከላ፣ ደም ልገሳ እና የፅዳት ዘመቻ መርሐ-ግብሮች ተካሂደዋል። ዛሬ በተካሄደው የማጠቃለያ ፕሮግራም ለሠማእታቱ መንገድ የመሠየም እና የመታሠቢያ ሐውልት የመሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓት ተከናውኗል።
ሠማእታቱን ለመዘከር በባሕር ዳር ከተማ ከቤዛዊት ቤተ መንግሥት መገንጠያ መንገድ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ-ክርስቲያን መንገድ ድረስ ያለው 1.5 ኪሎ ሜትር "የነሐሴ ሠማእታት ጎዳና" በሚል ተሰይሟል። ወደ ባሕር ዳር አውሮፕላን ማረፊያ የሚወስደው እና ገጠር መንገድ ተብሎ የሚጠራው ቦታ ባለው አደባባይ ላይም የመታሰቢያ ሐውልት ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦላቸዋል። በመታሠቢያ ዝግጅቱ ላይ የአማራ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አገኘሁ ተሻገር፣ የባሕር ዳር ከተማ ም/ከንቲባ አቶ አማረ ዓለሙ፣ የክልሉ እና የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የከተማው ወጣቶች ታድመዋል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
ለአማራ ሕዝብ ነፃነት፣ ፍትሕ፣ እኩልነት እና ፍትሐዊ ተጠቃሚነት ሲታገሉ ነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓ.ም በባሕር ዳር ከተማ ለተሠው 'ሠማእታት' የመታሠቢያ ዝግጅት ተካሂዷል።ለእነዚህ 'ሠማእታት' ከሐምሌ 28 ጀምሮ መታሠቢያ ዝግጅት እየተከናወነ ሲሆን፣ በዚህም የችግኝ ተከላ፣ ደም ልገሳ እና የፅዳት ዘመቻ መርሐ-ግብሮች ተካሂደዋል። ዛሬ በተካሄደው የማጠቃለያ ፕሮግራም ለሠማእታቱ መንገድ የመሠየም እና የመታሠቢያ ሐውልት የመሠረት ድንጋይ የማስቀመጥ ሥነ-ሥርዓት ተከናውኗል።
ሠማእታቱን ለመዘከር በባሕር ዳር ከተማ ከቤዛዊት ቤተ መንግሥት መገንጠያ መንገድ ጀምሮ እስከ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ-ክርስቲያን መንገድ ድረስ ያለው 1.5 ኪሎ ሜትር "የነሐሴ ሠማእታት ጎዳና" በሚል ተሰይሟል። ወደ ባሕር ዳር አውሮፕላን ማረፊያ የሚወስደው እና ገጠር መንገድ ተብሎ የሚጠራው ቦታ ባለው አደባባይ ላይም የመታሰቢያ ሐውልት ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦላቸዋል። በመታሠቢያ ዝግጅቱ ላይ የአማራ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አገኘሁ ተሻገር፣ የባሕር ዳር ከተማ ም/ከንቲባ አቶ አማረ ዓለሙ፣ የክልሉ እና የከተማ አስተዳደሩ የሥራ ኃላፊዎችን ጨምሮ የከተማው ወጣቶች ታድመዋል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
ከሃይማኖት በዳዳ ግድያ ጋር በተያያዘ ፖሊስ ተጨማሪ ተጠርጣሪዎችን ፍርድ ቤት አቀረበ!
በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የጤና ኮሌጅ የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪ ከነበረችው ሃይማኖት በዳዳ ግድያ ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ተጨማሪ ተጠርጣሪዎችን ዛሬ ፍርድ ቤት አቀረበ።በዋና ወንጀል አድራጊነት ተጠርጥሮ በቁጥጥር ሥር ከዋለው ደግነት ወርቁ ከተባለ ግለሰብ ባሻጋር ፖሊስ ከጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ስምንት ግለሰቦችን በቁጥጥር አውሎ ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት አቅርቧል። ከስምንቱ ግለሰቦች አብዛኛዎቹ በሆስፒታሉ በጥበቃ ሥራ ላይ የተሰማሩ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ የሃይማኖት በዳዳ የትምህርት አማካሪ (አድቫይዘር) የነበሩ ሰው መሆኑም ታውቋል።
ዛሬ ችሎቱ ፊት የቀረቡት የሆስፒታሉ ጥበቃዎች የሃይማኖት በዳዳ ግድያ በተፈፀመት ወቅት ሟቿ የነበረችበት ሕንፃ አጥር ያልነበረው መሆኑን ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል።ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸውም ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል።ፖሊስ ግን ከሟች ጋር የተደረጉ የስልክ ልውውጦችን ለመመርመር እንዲሁም የጥበቃ ሠራተኞች ዋናው ወንጀል በመፈፀም የተጠረጠረው ግለሰብ ድምፅ አልባ የጦር መሣሪያ ይዞ ወደ ሆስፒታሉ ሲገባ ያደረጉት ቁጥጥር እንዴት እንደነበር እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ምርመራ ለማካሄድ የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።ፍርድ ቤቱ በቀጣይ ቀጠሮ የእያንዳንዱ ተጠርጣሪ በወንጀሉ ላይ የነበራቸው ተሳትፎ ለይቶ እንዲያቀርብ ለፖሊስ የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል።ባለፈው ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ሕይወቷ ካለፈው ሃይማኖት በዳዳ ግድያ ጋር በተያያዘ ደግነት ወርቁ የተባለ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር መዋሉ ይታወሳል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የጤና ኮሌጅ የሁለተኛ ዲግሪ ተማሪ ከነበረችው ሃይማኖት በዳዳ ግድያ ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ተጨማሪ ተጠርጣሪዎችን ዛሬ ፍርድ ቤት አቀረበ።በዋና ወንጀል አድራጊነት ተጠርጥሮ በቁጥጥር ሥር ከዋለው ደግነት ወርቁ ከተባለ ግለሰብ ባሻጋር ፖሊስ ከጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ስምንት ግለሰቦችን በቁጥጥር አውሎ ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት አቅርቧል። ከስምንቱ ግለሰቦች አብዛኛዎቹ በሆስፒታሉ በጥበቃ ሥራ ላይ የተሰማሩ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ የሃይማኖት በዳዳ የትምህርት አማካሪ (አድቫይዘር) የነበሩ ሰው መሆኑም ታውቋል።
ዛሬ ችሎቱ ፊት የቀረቡት የሆስፒታሉ ጥበቃዎች የሃይማኖት በዳዳ ግድያ በተፈፀመት ወቅት ሟቿ የነበረችበት ሕንፃ አጥር ያልነበረው መሆኑን ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል።ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸውም ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል።ፖሊስ ግን ከሟች ጋር የተደረጉ የስልክ ልውውጦችን ለመመርመር እንዲሁም የጥበቃ ሠራተኞች ዋናው ወንጀል በመፈፀም የተጠረጠረው ግለሰብ ድምፅ አልባ የጦር መሣሪያ ይዞ ወደ ሆስፒታሉ ሲገባ ያደረጉት ቁጥጥር እንዴት እንደነበር እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ቀጣይ ምርመራ ለማካሄድ የ14 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።ፍርድ ቤቱ በቀጣይ ቀጠሮ የእያንዳንዱ ተጠርጣሪ በወንጀሉ ላይ የነበራቸው ተሳትፎ ለይቶ እንዲያቀርብ ለፖሊስ የ7 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል።ባለፈው ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም ሕይወቷ ካለፈው ሃይማኖት በዳዳ ግድያ ጋር በተያያዘ ደግነት ወርቁ የተባለ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር መዋሉ ይታወሳል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
ከሀጫሉ ግድያ ጋር ተያይዞ በተፈጠረው ብጥብጥ ውስጥ ተሳትፎ አድርገዋል ተብለው በተጠረጠሩ ከ1 ሺህ 200 በላይ የመንግሥት ኃላፊዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል - የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ባለፈው ወር ከአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዞ በተከሰተው ብጥብጥ ላይ ተሳትፎ በማድረግ እና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባለመወጣት የተጠረጠሩ የመንግሥት ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ላይ ሕጋዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ።የአርቲስት ሀጫሉን ግድያ ተከትሎ በተከሰተው ብጥብጥ ውስጥ ተሳትፈዋል እንዲሁም በሕግ የተቀመጠውን ኃላፊነት አልተወጡም በሚል የተጠረጠሩ በቀበሌ፣ በወረዳ እና በዞን ደረጃ ያሉ ከ1 ሺህ 200 በላይ የመንግሥት ኃላፊዎች ላይ ሕጋዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ቢሮው ገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ ከ500 በላይ የሚሆኑ የመንግሥት ሠራተኞች ኃላፊነታቸውን ባለመወጣት እና ብጥብጡ ውስጥ በመሳተፍ ተጠርጥረው ጉዳያቸው እየተጣራ መሆኑን አስታውቋል።የሕግ የበላይነትን የማስከበር ጉዳይ በባለሥልጣናት እና በሠራተኞች የጋራ ጥረት ቀጣይነት እንዲኖረው የሚደረግ መሆኑን በቅርቡ የተካሄደው የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ኮንፈረንስ አቅጣጫ አስቀምጧል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ባለፈው ወር ከአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዞ በተከሰተው ብጥብጥ ላይ ተሳትፎ በማድረግ እና ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባለመወጣት የተጠረጠሩ የመንግሥት ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ላይ ሕጋዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ አስታወቀ።የአርቲስት ሀጫሉን ግድያ ተከትሎ በተከሰተው ብጥብጥ ውስጥ ተሳትፈዋል እንዲሁም በሕግ የተቀመጠውን ኃላፊነት አልተወጡም በሚል የተጠረጠሩ በቀበሌ፣ በወረዳ እና በዞን ደረጃ ያሉ ከ1 ሺህ 200 በላይ የመንግሥት ኃላፊዎች ላይ ሕጋዊ እና ፖለቲካዊ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ቢሮው ገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ ከ500 በላይ የሚሆኑ የመንግሥት ሠራተኞች ኃላፊነታቸውን ባለመወጣት እና ብጥብጡ ውስጥ በመሳተፍ ተጠርጥረው ጉዳያቸው እየተጣራ መሆኑን አስታውቋል።የሕግ የበላይነትን የማስከበር ጉዳይ በባለሥልጣናት እና በሠራተኞች የጋራ ጥረት ቀጣይነት እንዲኖረው የሚደረግ መሆኑን በቅርቡ የተካሄደው የኦሮሚያ ብልጽግና ፓርቲ አመራሮች ኮንፈረንስ አቅጣጫ አስቀምጧል።
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
ከሰሞኑ በወላይታ ዞን የተፈጠረውን አለመረጋጋት ተከትሎ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ርስቱ ይርዳው መገለጫ ሰጥተዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳደሩ በመግለጫቸዉ መንግስት ከክልል አደረጃጀት ጋር በተያያዘ ህግና ስርዓት በሚፈቅደው አግባብ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ቢሆንም በወላይታ አንዳንድ አመራሮች ግን ይህንን ህጋዊ አካሄድ በሚጣረስ መልኩ የሄዱበት ያለው መንገድ በአካባቢው ግጭት እንዲፈጠር ምክንያት ሆነዋል ብለዋል፡፡አመራሮቹ ሀገር የማፍረስ አላማ ካላቸው አካላት ጋር ተቀናጀተው ተልዕኮ በመቀበል እየሰሩ ነበር ብለዋልም፡፡መንግስት በአካባቢው የተፈጠረውን ሁኔታ በህግ አግባብ ብቻ የሚፈታው እንደሆነ የገለፁ ሲሆን የአካባቢው ማህበረሰብም ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ሰላምና ደህንነቱን ሊጠበቅ ይገባል ብለዋል በሰጡት መግለጫ፡፡
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
ርዕሰ መስተዳደሩ በመግለጫቸዉ መንግስት ከክልል አደረጃጀት ጋር በተያያዘ ህግና ስርዓት በሚፈቅደው አግባብ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ቢሆንም በወላይታ አንዳንድ አመራሮች ግን ይህንን ህጋዊ አካሄድ በሚጣረስ መልኩ የሄዱበት ያለው መንገድ በአካባቢው ግጭት እንዲፈጠር ምክንያት ሆነዋል ብለዋል፡፡አመራሮቹ ሀገር የማፍረስ አላማ ካላቸው አካላት ጋር ተቀናጀተው ተልዕኮ በመቀበል እየሰሩ ነበር ብለዋልም፡፡መንግስት በአካባቢው የተፈጠረውን ሁኔታ በህግ አግባብ ብቻ የሚፈታው እንደሆነ የገለፁ ሲሆን የአካባቢው ማህበረሰብም ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ሰላምና ደህንነቱን ሊጠበቅ ይገባል ብለዋል በሰጡት መግለጫ፡፡
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
ችሎቱ በአቶ እስክንድር ነጋ ፣ ስንታየሁ ቸኮልና ቀለብ ስዩም ላይ ዐቃቤ ሕግ የቅድመ ምርመራ ምስክር እንዲያሰማ ፈቀደ!
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ችሎት በአቶ እስክንድር ነጋ ፣ ስንታየሁ ቸኮልና ቀለብ ስዩም ላይ ዐቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክር እንዲያሰማ ብይን ሰጥቷል፡፡እነ አቶ እስክንድር ነጋ የአርቲስት ሀጫሉን ሞት ተከትሎ ግጭት እንዲቀሰቀስ ማድረጋቸውና በውጤቱም የሰው ህይወት መጥፋቱንና ንብረት መውደሙ ብሎም ሌሎች ወንጀሎችን ጠቅሶ ዐቃቤ ሕግ ለችሎቱ አቤቱታ አቅርቧል፡፡በወንጀሎቹ ላይ የሚያስረዱ 7 ምስክሮችን ስም ዝርዝርንም ዐቃቤ ህግ አካቷል፡፡በምስክሮችና ጠቋሚዎች ጥበቃ አዋጅ 699/2003 መሰረት አራት ምስክሮች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ ጥቃት እንዳይደርስባቸው ማንነታቸው ሳይታወቅ እንዲመሰክሩና ቀሪዎቹ ደግሞ በዝግ ችሎት የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጥ ነው ዐቃቤ ሕግ ያመለከተው፡፡
የተጠርጣሪ ጠበቆች በበኩላቸው ተገቢውን መቃወሚያ ለማቅረብ የዐቃቤ ሕግ አቤቱታ ግልባጭ ቅጅ እንዲደርሳቸው ጠይቀዋል፡፡ስለምስክሮች ሁኔታም አቤቱታ ለማቅረብ ጊዜ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ዐቃቤ ሕግም በጉዳዩ ላይ ምላሽ ሰጥቷል፡፡የግራቀኙን ክርክር የሰማው ችሎቱ የቀዳሚ ችሎት ዓላማ ማስረጃ ማቆየትና ምስክሮችንም በመስቀለኛ ጥያቄ በሚፈተኑበት ስርዓት ስለሚመራ እንዲሁም ይህ ችሎት ውሳኔ የሚሰጥ ባለመሆኑ በተጠርጣሪዎች ላይ የሚፈጠር ጫና የለም ብሏል፡፡በዚህ የቀዳሚ ምርመራ ችሎት የአቤቱታ ቅጂ ለጠበቆች ይሰጥ የሚል ህግ ባለመሆኑ ይህንን ክርክር አልተቀበልኩም ብሏል፡፡በመሆኑም የዐቃቤ ሕግ ምስክሮችን ለመስማትና ከምስክሮች ጋር በተያያዘ ከጠበቆች የሚነሳውን መቃወሚያ ለመስማት ችሎቱ ለነገ ነሐሴ 6፣2012 ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል፡፡
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ተረኛ ችሎት በአቶ እስክንድር ነጋ ፣ ስንታየሁ ቸኮልና ቀለብ ስዩም ላይ ዐቃቤ ህግ የቅድመ ምርመራ ምስክር እንዲያሰማ ብይን ሰጥቷል፡፡እነ አቶ እስክንድር ነጋ የአርቲስት ሀጫሉን ሞት ተከትሎ ግጭት እንዲቀሰቀስ ማድረጋቸውና በውጤቱም የሰው ህይወት መጥፋቱንና ንብረት መውደሙ ብሎም ሌሎች ወንጀሎችን ጠቅሶ ዐቃቤ ሕግ ለችሎቱ አቤቱታ አቅርቧል፡፡በወንጀሎቹ ላይ የሚያስረዱ 7 ምስክሮችን ስም ዝርዝርንም ዐቃቤ ህግ አካቷል፡፡በምስክሮችና ጠቋሚዎች ጥበቃ አዋጅ 699/2003 መሰረት አራት ምስክሮች በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ ጥቃት እንዳይደርስባቸው ማንነታቸው ሳይታወቅ እንዲመሰክሩና ቀሪዎቹ ደግሞ በዝግ ችሎት የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጥ ነው ዐቃቤ ሕግ ያመለከተው፡፡
የተጠርጣሪ ጠበቆች በበኩላቸው ተገቢውን መቃወሚያ ለማቅረብ የዐቃቤ ሕግ አቤቱታ ግልባጭ ቅጅ እንዲደርሳቸው ጠይቀዋል፡፡ስለምስክሮች ሁኔታም አቤቱታ ለማቅረብ ጊዜ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ዐቃቤ ሕግም በጉዳዩ ላይ ምላሽ ሰጥቷል፡፡የግራቀኙን ክርክር የሰማው ችሎቱ የቀዳሚ ችሎት ዓላማ ማስረጃ ማቆየትና ምስክሮችንም በመስቀለኛ ጥያቄ በሚፈተኑበት ስርዓት ስለሚመራ እንዲሁም ይህ ችሎት ውሳኔ የሚሰጥ ባለመሆኑ በተጠርጣሪዎች ላይ የሚፈጠር ጫና የለም ብሏል፡፡በዚህ የቀዳሚ ምርመራ ችሎት የአቤቱታ ቅጂ ለጠበቆች ይሰጥ የሚል ህግ ባለመሆኑ ይህንን ክርክር አልተቀበልኩም ብሏል፡፡በመሆኑም የዐቃቤ ሕግ ምስክሮችን ለመስማትና ከምስክሮች ጋር በተያያዘ ከጠበቆች የሚነሳውን መቃወሚያ ለመስማት ችሎቱ ለነገ ነሐሴ 6፣2012 ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል፡፡
#ETV
@YeneTube @FikerAssefa1