የጎፋ ዞን መንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ
41 subscribers
89 photos
1 video
Download Telegram
የጎፋ ዞን ነዋሪዎች አሸባሪዎቹን ሕወሓትና ሸኔን የሚያወግዝ እንዲሁም ጀግናውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሚደግፍ ሰልፍ አካሄዱ
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

ሣውላ፣ ጥቅምት 29 ቀን 2014 ዓ.ም የጎፋ ዞን ነዋሪዎች የሽብር ቡድኖቹን ሕወሓትና ሸኔን የሚያወግዝ እንዲሁም ጀግናውን የሀገር መከላከያ ሠራዊትን የሚደግፍ ሰልፍ በሣውላ ከተማ አካሂደዋል።

የጎፋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዶ/ር ጌትነት በጋሻው ለሰልፉ ታዳሚዎች ባስተላለፉት መልዕክት ሀገራችን ኢትዮጵያ ጥንታዊት ታሪክ ያላትና የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ተምሳሌትና ኩራት መሆኑዋን ተናግረዋል።

ዶ/ር ጌትነት አክለውም እኛ ኢትዮጵያውያን የአባቶቻችን ፈለግ በመከተልና አንድነታችንን በማጠናከር የአሸባሪዎቹን የሕወሓትና ሸኔን ሀገር ሴራ በማክሸፍና የሚያጋጥሙንን ጊዜያዊ ፈተናዎችን በመቋቋም የኢትዮጵያን ሉአላዊነት በማስከበር ሀገራዊ ኃላፊነት መወጣት ይኖርብናል ብለዋል።

የሰልፉ ታዳሚዎች በበኩላቸው አሸባሪዎቹ ሕወሓትና ሸኔ ኢትዮጵያን የማፍረስ ሴራ ለማክሸፍ ከጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት የትም፣ መቼም እና በምንም ሁኔታ ለሀገራችን እንዘምታለን ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

የቀድሞ የመከላከያ ሠራዊት አባላትና 17 የዞኑ አመራሮች በበኩላቸው የመንግሥትን ጥሪ በመቀበል የሽብር ቡድኖቹን ሕወሓትና ሸኔን እስከ ግንባር በመሄድ ለመፋለምና ለመደምሰስ መዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።

ሰልፈኞቹ " በፕሮፓጋንዳው ጦርነት አንበገርም፣ ታላቁ የለውጥ ጉዟችን በውስጥና በውጭ ጠላቶቻችን አይደናቀፍም፣ ክብር ለጀግናው መከላከያችንና ለመላው የፀጥታ ኃይላችን፣ ለቀረበልን የክተት ጥሪ በሕዝባዊ ቁጭትና ጽናት ተሰልፈናል የሚሉና ሌሎችም የሽብር ቡድኖቹን ሕወሓትና ሸኔንና የውጭ ሚዲያዎች የሀሰት ፕሮፖጋንዳ የሚያወግዙ እንዲሁም ጀግናውን የሀገር መከላከያ ሠራዊትን የሚደግፉ የተለያዩ መፈክሮችን አሰምተዋል።

አከባቢያችሁን ጠብቁ!

ወደ ግንባር ዝመቱ!

መከላከያን ደግፉ!

ኢትዮጵያ ታሸንፋለች!!

የጎፋ ዞን መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ


#ጥቅምት 29 ቀን 2014 ዓ.ም
#ሣውላ
#በጎፋ #ዞን #በአራተኛው #ዙር #የሀገር #መከላከያ #ሰራዊት #ድጋፍ #በዓይነት #እና #በገንዘብ #ከ16.5 #ሚሊዮን #ብር #በላይ #ለማሰባሰብ #በዕቅድ #ተይዞ #እየተሰራ #እንደሚገኝ #የዞኑ #ዋና #አስተዳዳሪ #ዶ/ር #ጌትነት #በጋሻው #ገለፁ
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

በጎፋ ዞን ሀገርን ለማደን በህልውና ዘመቻ ለተሠማራው ለጀግናው የመከላከያ ሠራዊት እየተደረገ ባለው የተቀናጀ ጥረት አራተኛ ዙር የሀብት አሰባሰብ ሥራ በህዝቡ የተባበረ ክንድ ተጠናክሮ መቀጠሉን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ገለፁ።
የዞኑ ህዝብ ለጀግናው የመከላከያ ሠራዊት የተለያዩ ድጋፎችን በአይነት፣ በጉልበት እና በገንዘብ የማሰባሰቡ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በዞኑ ሀገርን የማደን የህልውና ዘመቻን ለማሳካት እየተደረገ ባለው የተቀናጀ ጥረት በየደረጃው የሚገኘው ማህበረሰብ በተለይም ወጣቱ ኃይል በሁሉ አቀፍ ድጋፎች በሁሉም ዙሮች የነቀ ተሳትፎ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

በዚህም የእናት ጡት ነካሹ የሆነው አሸባሪው ቡድን ህወሃት ሀገራችንን የመበተን ተልዕኮን አንግቦ የሀገር መከታና ጋሻ የሆነውን የሰሜን ዕዝ መከላከያ ሠራዊት ላይ ጥቃት በመሰንዘር ከተነሳበት ጊዜ ጀምሮ መንግስት ተግበራዊ ያደረገውን ህግ የማስከበር ዘመቻ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የዞኑ ህዝብ ሀገራዊ ጥሪውን ተቀብሎ ጁንታውን የመደምሰስ ህልውና ዘመቻ ላይ እየተዋደቀ ላለው ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ደጀንነቱን አስመስክሯል።

በተለይም የዞናችን ህዝቦች የእናት ሀገራቸውን ክብርና ሉዓላዊነት ለማስከበር ግንባር ለዘመተው የመከላከያ ሠራዊታችን በአስፈላጊው ሁሉ በመደገፍ ያላቸውን ደጀንነት በውል ለማረጋገጥ አራተኛ ዙር የሀብት አሰባሰብ ሥራ በአሁኑ ሰዓትም ተጠናክሮ ቀጥሏል ።

በአሁኑ ወቅትም በዞኑ በየመዋቅሩ በጠንካራ የህዝብ ተሳትፎ በዓይነት የተለያዩ ግብዓቶች እየተሰበሰበ እንደሚገኝ ከሁሉም መዋቅሮች ባገኛነው መረጃ ለማወቅ ተችሏል።

በተጨማሪም ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ ምልምል መደበኛ የመከላከያ ሰራዊት፣ የቀድሞ የደርግ ሰራዊት፣ የተቀናሽ ሰራዊት፣ ብሔራዊ ተጠባባቂ ኃይል እና ሚሊሺያዎች የሀገርን ጥሪ ተቀብለው ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ጎን ለመሰለፍ ቁርጠኝነታቸውን አሳይተዋል።

ዘገባው:- #የጎፋ #ዞን #መንግስት #ኮሚኒኬሽን
#ጉዳዮች #መምሪያ #ነው

#ህዳር /02/2014 ዓ.ም
#ሣውላ