#ይድረስ~ለእናቴ~ልጅ
፡
ደምህ እና ደሜ
ከገነቱ ጠበል ከጊዮን ተቀድቶ
ስጋዬ እና ስጋህ
ከበረከት አፈር ከኤደን ተቦክቶ
ያውም በእግዜር ቃል
በተስፋዋ ምድር ሰው ሆኖ እነዳልኖረ
ያ ሁሉ ፍቅራችን
በትንሽ የዘር ክር ስለምን ታሰረ?
:
አንተ'ኮ ክብሬ ነህ
የመጎሴ ሚስጥር ህመሜን ታማሚ
እኔ'ኮ ደስታህ ነኝ
ከባድ ሀዘንህን ቀሎኝ ተሸካሚ፡፡
፡
ያ'ንተ ዘር የኔ ዘር
ትሁፊቴ ትሁፍትህ ባህልህ ባህሌ
ዘመናት ስንኖር
ሳቄ ሳቅህ ነበር በደልህ በደሌ፡፡
፡
ግሸን ስታስቀድስ
ለዱኒያ ዱአ ነጃሽ ካድሜአለሁ
እዛ'ና እዚህ ሆነን
በቁልቢ ስትምል በፂሆን ምያለሁ፡፡
፡
ባ'ክሱም ስመፃደቅ
በ'ላሊበላ አለት ኩራት ተሰምቶሀል
በጀጎል ሳቅራራ
በፋሲለደስ ጌጥ አምረህ ሸልለሀል፡፡
፡
ታዲያ ምነው ዛሬ
ዘመን ባጎደፈው በማይድን ነቀርሳ
በዘር አቅላሚዎች
አንድነትን ጠልተን ተለየን በጎሳ?
:
እባክህ ወንድሜ
ለባለቀን ብለህ ከፍቶህ አታስከፋኝ
አንተ ነህ ደስታዬ
ሲረግጡን ተረግጠህ ሲገፉን አትግፋኝ፡፡
፡
ባይሆን ከረገጠን
ከገፋን ባለቀን ደም እየጨለጠ ከሰከረ ነፍሱ
በአንድነት ጠበል
ተጠምቀን እንዳን
ለለከፈን ሴጣን ፋቅራችን ነው ምሱ፡፡
[ልብ አልባው ገጣሚ]
@GETEM
@GETEM
@GEBRIEL_19
፡
ደምህ እና ደሜ
ከገነቱ ጠበል ከጊዮን ተቀድቶ
ስጋዬ እና ስጋህ
ከበረከት አፈር ከኤደን ተቦክቶ
ያውም በእግዜር ቃል
በተስፋዋ ምድር ሰው ሆኖ እነዳልኖረ
ያ ሁሉ ፍቅራችን
በትንሽ የዘር ክር ስለምን ታሰረ?
:
አንተ'ኮ ክብሬ ነህ
የመጎሴ ሚስጥር ህመሜን ታማሚ
እኔ'ኮ ደስታህ ነኝ
ከባድ ሀዘንህን ቀሎኝ ተሸካሚ፡፡
፡
ያ'ንተ ዘር የኔ ዘር
ትሁፊቴ ትሁፍትህ ባህልህ ባህሌ
ዘመናት ስንኖር
ሳቄ ሳቅህ ነበር በደልህ በደሌ፡፡
፡
ግሸን ስታስቀድስ
ለዱኒያ ዱአ ነጃሽ ካድሜአለሁ
እዛ'ና እዚህ ሆነን
በቁልቢ ስትምል በፂሆን ምያለሁ፡፡
፡
ባ'ክሱም ስመፃደቅ
በ'ላሊበላ አለት ኩራት ተሰምቶሀል
በጀጎል ሳቅራራ
በፋሲለደስ ጌጥ አምረህ ሸልለሀል፡፡
፡
ታዲያ ምነው ዛሬ
ዘመን ባጎደፈው በማይድን ነቀርሳ
በዘር አቅላሚዎች
አንድነትን ጠልተን ተለየን በጎሳ?
:
እባክህ ወንድሜ
ለባለቀን ብለህ ከፍቶህ አታስከፋኝ
አንተ ነህ ደስታዬ
ሲረግጡን ተረግጠህ ሲገፉን አትግፋኝ፡፡
፡
ባይሆን ከረገጠን
ከገፋን ባለቀን ደም እየጨለጠ ከሰከረ ነፍሱ
በአንድነት ጠበል
ተጠምቀን እንዳን
ለለከፈን ሴጣን ፋቅራችን ነው ምሱ፡፡
[ልብ አልባው ገጣሚ]
@GETEM
@GETEM
@GEBRIEL_19
❤1
#ይድረስ #ለሀገሬ
በዚህ ጩኸት መሐል
ችለሽ ባትሰሚኝም ~ አይቀር መናገሬ
እኔ እንዳለው አለሁ ~ እንዴት ነሽ ሀገሬ
እንዴት ነሽ ሃገሬ ~ ንገሪኝ ግዴለም
ስለ ደህንነትሽ ~ የማልሰማው የለም
\
/
\
/
በአድርባይ እጆቹ ~ ደረት እየደቃ
ወድቃለች ይለኛል ~ ገፍትሮሽ ሲያበቃ
አመሉን ላይረሳ ~ ቦርጭ ቢመነኩስ
ታረዘች ይለኛል ~ የገፈፈሽ እርኩስ
በግፍ ተቀብትቶ ~ ቦርጭ ወጥሮት ገላው
ተራበች ይለኛል ~ ቀምቶሽ የበላው
ያላየሁት መስሎት
በትኩሳትሽ ላይ ~ እሳት መለኮሱን
ቅዠት ሲያቃትትሽ
ቀወሰች ይለኛል ~ ያሳብደው እሱን
ሊገነጣጥልሽ ~ ቢላውን አስሎ
ሞታለች ይለኛል ~ አስተዛዛኝ መስሎ
• • •
በቁሙ እያለ ~ የጁን እንዲያገኘው
ካንቺ ቀድሞ አይሙት ~ ሞትሽን የተመኘው
በጎሽን ማይወዱ ~ ሟርተኞች በሙሉ
መኖርሽን ይዩት ~ በህይወት እያሉ
* * *
እኔ ‘ምልሽ
ግን እንዴት ነሽ አንቺ ~ ጤናሽን ደህና ነሽ ?
ወደፊት እንዳትሄጅ
አላራምድ ያለሽ ~ እግርሽን ተሻለሽ ?
#ጎሽ
ማገገም መልካም ነው
ከርሞ ትድኛለሽ ~ ፈጣሪ ከረዳን
ፈፅሞ አይቻልም
ከዘመን በሽታ ~ በአንድ ጀምበር መዳን
ቀላል ነው እያለ ~ ወጌሻሽ ቢዋሽም
የዘመን ወለምታ ~ በጊዜ አይታሽም
• • •
እየጠዘጠዘ ~ በሕመም ቢያስነክስም
የትዉልድ ውልቃት ~ በአንዴ አይመለስም
• • •
ጠባብሶ ለማብላት ~ አራጅ ባይጀግንም
የዘመን ስብራት ~ በበግ አይጠግንም
• • •
ትእግስትሽ ተሟጦ ~ ተስፋሽ ፍፁም ሳይነጥፍ
ቀድሞ የዘረጋሽው ~ እጅሽ ሳይታጠፍ
ወደፊት ተመልከች ~ የኃላሽ ይረሳል
እያረፉ ማዝገም ~ ቢረፍድም ያደርሳል
ካሰብሽበት ቦታ ~ ደርሰሽ እስክታርፊ
እያስነከሰሽም ~ ይሄን ቀን እለፊ
====||====
ከሙሉቀን ሰ•
@getem
@getem
@getem
በዚህ ጩኸት መሐል
ችለሽ ባትሰሚኝም ~ አይቀር መናገሬ
እኔ እንዳለው አለሁ ~ እንዴት ነሽ ሀገሬ
እንዴት ነሽ ሃገሬ ~ ንገሪኝ ግዴለም
ስለ ደህንነትሽ ~ የማልሰማው የለም
\
/
\
/
በአድርባይ እጆቹ ~ ደረት እየደቃ
ወድቃለች ይለኛል ~ ገፍትሮሽ ሲያበቃ
አመሉን ላይረሳ ~ ቦርጭ ቢመነኩስ
ታረዘች ይለኛል ~ የገፈፈሽ እርኩስ
በግፍ ተቀብትቶ ~ ቦርጭ ወጥሮት ገላው
ተራበች ይለኛል ~ ቀምቶሽ የበላው
ያላየሁት መስሎት
በትኩሳትሽ ላይ ~ እሳት መለኮሱን
ቅዠት ሲያቃትትሽ
ቀወሰች ይለኛል ~ ያሳብደው እሱን
ሊገነጣጥልሽ ~ ቢላውን አስሎ
ሞታለች ይለኛል ~ አስተዛዛኝ መስሎ
• • •
በቁሙ እያለ ~ የጁን እንዲያገኘው
ካንቺ ቀድሞ አይሙት ~ ሞትሽን የተመኘው
በጎሽን ማይወዱ ~ ሟርተኞች በሙሉ
መኖርሽን ይዩት ~ በህይወት እያሉ
* * *
እኔ ‘ምልሽ
ግን እንዴት ነሽ አንቺ ~ ጤናሽን ደህና ነሽ ?
ወደፊት እንዳትሄጅ
አላራምድ ያለሽ ~ እግርሽን ተሻለሽ ?
#ጎሽ
ማገገም መልካም ነው
ከርሞ ትድኛለሽ ~ ፈጣሪ ከረዳን
ፈፅሞ አይቻልም
ከዘመን በሽታ ~ በአንድ ጀምበር መዳን
ቀላል ነው እያለ ~ ወጌሻሽ ቢዋሽም
የዘመን ወለምታ ~ በጊዜ አይታሽም
• • •
እየጠዘጠዘ ~ በሕመም ቢያስነክስም
የትዉልድ ውልቃት ~ በአንዴ አይመለስም
• • •
ጠባብሶ ለማብላት ~ አራጅ ባይጀግንም
የዘመን ስብራት ~ በበግ አይጠግንም
• • •
ትእግስትሽ ተሟጦ ~ ተስፋሽ ፍፁም ሳይነጥፍ
ቀድሞ የዘረጋሽው ~ እጅሽ ሳይታጠፍ
ወደፊት ተመልከች ~ የኃላሽ ይረሳል
እያረፉ ማዝገም ~ ቢረፍድም ያደርሳል
ካሰብሽበት ቦታ ~ ደርሰሽ እስክታርፊ
እያስነከሰሽም ~ ይሄን ቀን እለፊ
====||====
ከሙሉቀን ሰ•
@getem
@getem
@getem
👍3
#ይድረስ_ለናፍቆቴ
.
.
"እቴ....''
ከመንጋው ነጥሎ ለክህነት ሚያበቃኝ፣
ሞቼ ብገኝ እንኳን ከሞት የሚያነቃኝ።
የሳቅሽን ፀዳል ዜማው እያስታወስኩ፣
የደስ ደስ ገላሽን በልቤ እየሳልኩ።
እስክትመጪ ድረስ፤
እስካገኝሽ ድረስ፤
የባተለ ውሎ የሚያባዝት ምሽት፣
በትዝታ ፈረስ ትዝታዬን ሽሽት።
መኳተን መበተን መሳሳት አባባኝ፣
አልጋ ላይ አውሎ ብቻዬን አስነባኝ።"
ብዬ ባስነገርኩሽ ባስላኩሽ ማግስት፣
መተከዜ አሞሽ አሳጥቶሽ ትግስት።
በረሽ መጥተሽልኝ፤
በስስት አቅፈሽኝ ፤
ስመሽ አክመሽኝ ፤
ነቅለሽ ስታደርቂው የማጣትን አረም፣
"ኮነነ ፍስሀ" እነሆ መስከረም።
.
.
ብቻ.........
የማደርገው ሳጣ ብቸኝነት አስሮኝ፣
አንጀቴ ሲላወስ ብርዱ አስመርሮኝ።
ካለሽበት ቦታ እስካለሁበት ድረስ፣
በትሬንታ ኳትሮ በበቅሎ በፈረስ።
"ባክሽ ድረሽልኝ ነይ" ስልሽ ከመጣሽ፣
ዘመን ተለወጠ "እነሆ እንቁጣጣሽ"።
.
.
እቴ......
''አንቺን ልጥራሽ እንጂ እጣዬ እድሌ፣
ከሌላ አልገጥም ሽርክት ነው አመሌ።
ጠረንሽ ከራቀኝ ያነጫንጨኛል፣
አብረሽኝ እያለሽ መኖርሽ ያምረኛል።
.
.
በቃ ልይሽ አሁን ልታገስ ህመሜን፣
ከእቅፍሽ ልዝለቅ ተካፈዪኝ ህልሜን።''
ብዬ እንደተናገርኩ ካፌ እንደወጣ፣
ፍቅሬ መጥተሽልኝ ናፍቆት ከተቀጣ።
ማጣት ጓዙን ጭኖ ፍቅርሽን ከተካ፣
የቆዘመው ቤቴ በሳቅሽ ከፈካ፣
አውራ ዶሮ ጮኸ "እነሆ ፋሲካ"።
.
.
መቼም ሰው አይደለን፤
ተፈጥሮ በህጉ መልካም ሳያድለን፤
ምናልባት ባይፃፍ ማከምሽ መዳኔ፣
ቢፈተን እምነትሽ ቢፈተን ኪዳኔ።
መክሳትሽ መክሳቴ፤
ማጣት መገርጣቴ።
አይድረስ ከጆሮው ጠላት አይገምተው፣
እስካገኝሽ ድረስ፤
ሁሉንም ሁሉንም ለ'ግዜሩ ነው መተው።
.
.
.
እናም የኔ ናፍቆት......
መስከረም ሲጠባ ሰማዩ ሲፈካ፣
በበዓል 'ባውዳመት በገና ፋሲካ።
እምነቴን ሳላጎድፍ ቃሌም ሳይጓደል፣
በ "ትመጫለሽ" ስም ልጠብቅሽ አይደል ????።
✍ ዓቢይ ( @abiye12 )
@getem
@getem
@getem
.
.
"እቴ....''
ከመንጋው ነጥሎ ለክህነት ሚያበቃኝ፣
ሞቼ ብገኝ እንኳን ከሞት የሚያነቃኝ።
የሳቅሽን ፀዳል ዜማው እያስታወስኩ፣
የደስ ደስ ገላሽን በልቤ እየሳልኩ።
እስክትመጪ ድረስ፤
እስካገኝሽ ድረስ፤
የባተለ ውሎ የሚያባዝት ምሽት፣
በትዝታ ፈረስ ትዝታዬን ሽሽት።
መኳተን መበተን መሳሳት አባባኝ፣
አልጋ ላይ አውሎ ብቻዬን አስነባኝ።"
ብዬ ባስነገርኩሽ ባስላኩሽ ማግስት፣
መተከዜ አሞሽ አሳጥቶሽ ትግስት።
በረሽ መጥተሽልኝ፤
በስስት አቅፈሽኝ ፤
ስመሽ አክመሽኝ ፤
ነቅለሽ ስታደርቂው የማጣትን አረም፣
"ኮነነ ፍስሀ" እነሆ መስከረም።
.
.
ብቻ.........
የማደርገው ሳጣ ብቸኝነት አስሮኝ፣
አንጀቴ ሲላወስ ብርዱ አስመርሮኝ።
ካለሽበት ቦታ እስካለሁበት ድረስ፣
በትሬንታ ኳትሮ በበቅሎ በፈረስ።
"ባክሽ ድረሽልኝ ነይ" ስልሽ ከመጣሽ፣
ዘመን ተለወጠ "እነሆ እንቁጣጣሽ"።
.
.
እቴ......
''አንቺን ልጥራሽ እንጂ እጣዬ እድሌ፣
ከሌላ አልገጥም ሽርክት ነው አመሌ።
ጠረንሽ ከራቀኝ ያነጫንጨኛል፣
አብረሽኝ እያለሽ መኖርሽ ያምረኛል።
.
.
በቃ ልይሽ አሁን ልታገስ ህመሜን፣
ከእቅፍሽ ልዝለቅ ተካፈዪኝ ህልሜን።''
ብዬ እንደተናገርኩ ካፌ እንደወጣ፣
ፍቅሬ መጥተሽልኝ ናፍቆት ከተቀጣ።
ማጣት ጓዙን ጭኖ ፍቅርሽን ከተካ፣
የቆዘመው ቤቴ በሳቅሽ ከፈካ፣
አውራ ዶሮ ጮኸ "እነሆ ፋሲካ"።
.
.
መቼም ሰው አይደለን፤
ተፈጥሮ በህጉ መልካም ሳያድለን፤
ምናልባት ባይፃፍ ማከምሽ መዳኔ፣
ቢፈተን እምነትሽ ቢፈተን ኪዳኔ።
መክሳትሽ መክሳቴ፤
ማጣት መገርጣቴ።
አይድረስ ከጆሮው ጠላት አይገምተው፣
እስካገኝሽ ድረስ፤
ሁሉንም ሁሉንም ለ'ግዜሩ ነው መተው።
.
.
.
እናም የኔ ናፍቆት......
መስከረም ሲጠባ ሰማዩ ሲፈካ፣
በበዓል 'ባውዳመት በገና ፋሲካ።
እምነቴን ሳላጎድፍ ቃሌም ሳይጓደል፣
በ "ትመጫለሽ" ስም ልጠብቅሽ አይደል ????።
✍ ዓቢይ ( @abiye12 )
@getem
@getem
@getem
❤35👍30🔥9😱2
#ይድረስ_ለተከፋች_ሴት
.
.
ይኸውልሽ የኔ አይናማ፤
አንዴ ብቻ እኔን ስሚኝ አታለቃቅሺ እርሺው እንባሽን፤
ሰው ከመሆንሽ ሳትሸራርፊ እጥፍ ውደጂው ያስለቀሰሽን።
ልብሽን በእምነት አፅኚው የዛሬ ቀንሽም ያልፋል፣
ችግርሽ ምን ቢደራረብ በእግዜር እጆች ይገፋል።
የምታምኚው አምላክሽ እኮ፤
ከሞት መንጋጋም ነፍስ ያስተርፋል።
"ተሳሳትኩ " ??
አልተሳሳትኩም !!!!!
የተስፋ መሃረብ ይዘሽ ትኩስ እንባሽን በይ አደራርቂው፣
መደነቃቀፍ ብርታት ከሆነ ገፊሽን ሁሉ ወደሽ መርቂው።
ወርቅን እራሱ፤
"ወርቅ ሆነ" እንዲባል የተጋጋመ እሳት በልቶታል፣
ታድያ አምላክሽ ይመካብሽ ዘንድ ሺ ቢፈትንሽ ክፋቱ የታል ????
"እኔ አልታየኝም"።
.
.
እናምልሽ ውድ ዓለሜ መፈተንሽን እንዳትጠዪው፣
ይልቅናሽስ ፈገግ ብለሽ "ፈጣሪዬ ሆይ ተመስገን" በይው።
✍ ዓቢይ ( @abiye12 )
@getem
@getem
@getem
.
.
ይኸውልሽ የኔ አይናማ፤
አንዴ ብቻ እኔን ስሚኝ አታለቃቅሺ እርሺው እንባሽን፤
ሰው ከመሆንሽ ሳትሸራርፊ እጥፍ ውደጂው ያስለቀሰሽን።
ልብሽን በእምነት አፅኚው የዛሬ ቀንሽም ያልፋል፣
ችግርሽ ምን ቢደራረብ በእግዜር እጆች ይገፋል።
የምታምኚው አምላክሽ እኮ፤
ከሞት መንጋጋም ነፍስ ያስተርፋል።
"ተሳሳትኩ " ??
አልተሳሳትኩም !!!!!
የተስፋ መሃረብ ይዘሽ ትኩስ እንባሽን በይ አደራርቂው፣
መደነቃቀፍ ብርታት ከሆነ ገፊሽን ሁሉ ወደሽ መርቂው።
ወርቅን እራሱ፤
"ወርቅ ሆነ" እንዲባል የተጋጋመ እሳት በልቶታል፣
ታድያ አምላክሽ ይመካብሽ ዘንድ ሺ ቢፈትንሽ ክፋቱ የታል ????
"እኔ አልታየኝም"።
.
.
እናምልሽ ውድ ዓለሜ መፈተንሽን እንዳትጠዪው፣
ይልቅናሽስ ፈገግ ብለሽ "ፈጣሪዬ ሆይ ተመስገን" በይው።
✍ ዓቢይ ( @abiye12 )
@getem
@getem
@getem
👍54❤42🔥2😱2🎉2