ቀናሁ
=== ===
ለመንኩት አምላክን
አበባ እንዲያደርግሽ
ንብ ሆኜ መጥቼ
እየዞርኩ ልቀስምሽ
ማለዳ ማለዳ
በበራፋችሁ ሳልፍ
ብመለከት ጊዜ
ፀሀይ ስትሞቂ
ፈጣሪን ለመንኩት
"ፀሀይ አርገኝ "ብዬ
ውብ #ሠውነትሽ ላይ
እንዳርፍ ዘና ብዬ፡፡
ያንገትሽ #ማተብ
ያለ ማንም ከልካይ
ገብቶ ሲንከላወስ
በጡቶችሽ ክፋይ
ብመለከት ጊዜ...
ቀናሁ በማተብሽ
ቀናው በመስቀሉ
ጡትሽን ተንተርሶ
በመዋል በማደሩ፡፡
#ቅዳሜ እረፋድ ላይ
ስትመጭ ከገበያ....
ትኩስ ለጋ ጎመን
በክንድሽ ታቅፈሽ
በሌላኛው እጅሽ
ዘንቢል አንጠልጥለሽ..
ብመለከት ጊዜ...
እንደ ጎመን መሆን
ተመኘው ለቅፅበት
በአካሌ እንዲሠራጭ
የአክናድሽ ሙቀት
ተመኘው ለቅፅበት
መሆን እንደ ዘንቢል
ውብ ለሥላሳ ጣትሽ
በገላዬ እንዲውል፡፡
ትናንትና ደግሞ..
ከኛ ቤት ፊት ለፊት
ውሐ ስትቀጂ
ከየት እንደ መጣ
ያልታወቀ ንፋስ
ቀሚስሽን ገልቦ
ጀምበር የመሠለ
ያ ውቡ ጭንሽን
ቢያሳየኝ በስሱ
እምልልሻለው
ቀናሁ በንፋሱ፡፡
doju.
@getem
@getem
@getem
=== ===
ለመንኩት አምላክን
አበባ እንዲያደርግሽ
ንብ ሆኜ መጥቼ
እየዞርኩ ልቀስምሽ
ማለዳ ማለዳ
በበራፋችሁ ሳልፍ
ብመለከት ጊዜ
ፀሀይ ስትሞቂ
ፈጣሪን ለመንኩት
"ፀሀይ አርገኝ "ብዬ
ውብ #ሠውነትሽ ላይ
እንዳርፍ ዘና ብዬ፡፡
ያንገትሽ #ማተብ
ያለ ማንም ከልካይ
ገብቶ ሲንከላወስ
በጡቶችሽ ክፋይ
ብመለከት ጊዜ...
ቀናሁ በማተብሽ
ቀናው በመስቀሉ
ጡትሽን ተንተርሶ
በመዋል በማደሩ፡፡
#ቅዳሜ እረፋድ ላይ
ስትመጭ ከገበያ....
ትኩስ ለጋ ጎመን
በክንድሽ ታቅፈሽ
በሌላኛው እጅሽ
ዘንቢል አንጠልጥለሽ..
ብመለከት ጊዜ...
እንደ ጎመን መሆን
ተመኘው ለቅፅበት
በአካሌ እንዲሠራጭ
የአክናድሽ ሙቀት
ተመኘው ለቅፅበት
መሆን እንደ ዘንቢል
ውብ ለሥላሳ ጣትሽ
በገላዬ እንዲውል፡፡
ትናንትና ደግሞ..
ከኛ ቤት ፊት ለፊት
ውሐ ስትቀጂ
ከየት እንደ መጣ
ያልታወቀ ንፋስ
ቀሚስሽን ገልቦ
ጀምበር የመሠለ
ያ ውቡ ጭንሽን
ቢያሳየኝ በስሱ
እምልልሻለው
ቀናሁ በንፋሱ፡፡
doju.
@getem
@getem
@getem
😁1
#ቅዳሜ!
።።።።።
#ፀሀይ አድልታለች
ከሰርክ ብርሀኗ.. .ሀይሏን አለዝባ
በስሱ ወታለች ።
እኔ.. .
ስለምን ነው? እያልሁ እያየኋት ቆሜ
ትዝ ቢለኝ ድንገት ቀኑ ነው ቅዳሜ ።
#ቅዳሜ!
የሚፈካ ሰማይ ... ያረበበ አየር
ላብራ ሳልሞቅ ብላ የምትወጣ ጀንበር።
የአዳም ዘር እረፍት.. .
የደስታ ሰገነት ...
የጀበና ቡና.. . ጥቂት ማኪያቶ
ዱለት ምላስ ሰንበር በአዋዜ ታሽቶ
ካፌ በረንዳ ላይ ጨዋታ ተጋርቶ
መፅሄት ጋዜጣ መፅሀፍ ሸምቶ
ከጥበብ ጋር መዋል ... !
ወርቅን ማመሳጠር በቅኔ መሰላል።
#ቅዳሜ!
በጠጉሮቿ መሀል አበባ ሰክታ
ሲኒማ ኢምፓየር ስሩን ተጠግታ
አስር ጊዜ የጇን ፥ ሰዓት የምትቆጥር
ከመንገዱ ቁልቁል ፍቅሯን የምትማትር
አይመጣም ወይ ብላ ከንፈሯን የጣለች
ይመጣልም ብላ
ፈገግ ወደማለት ...ዳርዳርታ ላይ ያለች
እርሷን የምትመስል የቀናት ምስጢር ነች።
#ቅዳሜ!
ነጠላ ባጣፉ ፣ ቄጠማ በያዙ
ሽቶ ተነስንሰው
ከባንኮኒው ግድም ፣ አልኮልን በሚያዙ
በመዝሙር ውዳሴ ከመላዕክት ጋራ
በማለዳው ጮራ.. .
ደግሞ ወዲህ ምሽት
በሳልሳ በቡጊ.. .. በሬጌ ጭፈራ
በኒህ ሁለት ፅንፎች መሀል ተወስና
"አፍቃሪሽ አይቋረጥ" ብለው የመረቋት
ዘማሪም ደናሹም እኩል የሚወዷት
የቀኖች ንግስት ናት !
....
(ሚካኤል አስጨናቂ)
@getem
@getem
@paappii
።።።።።
#ፀሀይ አድልታለች
ከሰርክ ብርሀኗ.. .ሀይሏን አለዝባ
በስሱ ወታለች ።
እኔ.. .
ስለምን ነው? እያልሁ እያየኋት ቆሜ
ትዝ ቢለኝ ድንገት ቀኑ ነው ቅዳሜ ።
#ቅዳሜ!
የሚፈካ ሰማይ ... ያረበበ አየር
ላብራ ሳልሞቅ ብላ የምትወጣ ጀንበር።
የአዳም ዘር እረፍት.. .
የደስታ ሰገነት ...
የጀበና ቡና.. . ጥቂት ማኪያቶ
ዱለት ምላስ ሰንበር በአዋዜ ታሽቶ
ካፌ በረንዳ ላይ ጨዋታ ተጋርቶ
መፅሄት ጋዜጣ መፅሀፍ ሸምቶ
ከጥበብ ጋር መዋል ... !
ወርቅን ማመሳጠር በቅኔ መሰላል።
#ቅዳሜ!
በጠጉሮቿ መሀል አበባ ሰክታ
ሲኒማ ኢምፓየር ስሩን ተጠግታ
አስር ጊዜ የጇን ፥ ሰዓት የምትቆጥር
ከመንገዱ ቁልቁል ፍቅሯን የምትማትር
አይመጣም ወይ ብላ ከንፈሯን የጣለች
ይመጣልም ብላ
ፈገግ ወደማለት ...ዳርዳርታ ላይ ያለች
እርሷን የምትመስል የቀናት ምስጢር ነች።
#ቅዳሜ!
ነጠላ ባጣፉ ፣ ቄጠማ በያዙ
ሽቶ ተነስንሰው
ከባንኮኒው ግድም ፣ አልኮልን በሚያዙ
በመዝሙር ውዳሴ ከመላዕክት ጋራ
በማለዳው ጮራ.. .
ደግሞ ወዲህ ምሽት
በሳልሳ በቡጊ.. .. በሬጌ ጭፈራ
በኒህ ሁለት ፅንፎች መሀል ተወስና
"አፍቃሪሽ አይቋረጥ" ብለው የመረቋት
ዘማሪም ደናሹም እኩል የሚወዷት
የቀኖች ንግስት ናት !
....
(ሚካኤል አስጨናቂ)
@getem
@getem
@paappii
👍2❤1