#አካብዳለሁ_!!
ባገርሽ...ባገሬ
ከታካሚው በላይ...ብዙ ሺህ #ዶክተሮች
የሰው ኮታ እስኪገኝ ፥ እፅ እየቀመሙ
እንደፈላ ችግኝ ፥ እዚም እዛም ሄደው
ባለ #ሀብቶቻችን ፥ የጤና ማእከል ፥ ሰርክ እያቋቋሙ
#መንግስት እየጦረን ፥ እነሱ እያከሙ
ምን አላት #ሁለት_ወር ?
መች ጠፍቶ ቀለቡ...?
ሲሻን ካመት አመት
እግር አሰቅለው
የምንበላው መኖ ፥ #አርሶ አደሮቻችን እያቀራረቡ
#ነጋዴዎቻችን ፥ አንድ ለሚገዛ ፥ አስር ሲመርቁ
#አከራዮቻችን ፥ ቤት ክራይ ሲለቁ
ባህል ቀማሚያን ፥ ማርከሻ ሲፈጥሩ
እልፎች በምህላ ፥ ምህረት ሲጠሩ...
ይህን ሁሉ ድሎት...
ያየና የሰማ ፥ #ቫይረሱ በራሱ..አይመጣም ወደኛ
ተሽከርክረን ውለን .... #ጧ ብለን እንተኛ ።
ደግሞም #ተናፋቂ ...
ከራሳችን አልፈን ፥ አለምን ጠባቂ
ከሰው የተለየን ፥ ሰዎች እንደሆንን ፥ ቀድሞኑ ስታውቂ
ምቾት ላንገላታው ...እንደኔና እንዳቺ ...ለተፍታታ ዜጋ
#ኮሮራ እንዳይዘን ፥ ስለምነው እሱ ፥ ቅንጣት የምንሰጋ ?
ብዬ መደለያ ...ቅንጣ የተስፋ ቃል...ከምኞት ስላጣሁ
ክብደቱ እንዲከብድሽ ... #ለማካበድ_ወጣሁ!!
አይግረምሽ እንግዲ.... #አካበድሁ!!
✍ #አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
✍ @Abr_sh
@getem
@getem
@getem
ባገርሽ...ባገሬ
ከታካሚው በላይ...ብዙ ሺህ #ዶክተሮች
የሰው ኮታ እስኪገኝ ፥ እፅ እየቀመሙ
እንደፈላ ችግኝ ፥ እዚም እዛም ሄደው
ባለ #ሀብቶቻችን ፥ የጤና ማእከል ፥ ሰርክ እያቋቋሙ
#መንግስት እየጦረን ፥ እነሱ እያከሙ
ምን አላት #ሁለት_ወር ?
መች ጠፍቶ ቀለቡ...?
ሲሻን ካመት አመት
እግር አሰቅለው
የምንበላው መኖ ፥ #አርሶ አደሮቻችን እያቀራረቡ
#ነጋዴዎቻችን ፥ አንድ ለሚገዛ ፥ አስር ሲመርቁ
#አከራዮቻችን ፥ ቤት ክራይ ሲለቁ
ባህል ቀማሚያን ፥ ማርከሻ ሲፈጥሩ
እልፎች በምህላ ፥ ምህረት ሲጠሩ...
ይህን ሁሉ ድሎት...
ያየና የሰማ ፥ #ቫይረሱ በራሱ..አይመጣም ወደኛ
ተሽከርክረን ውለን .... #ጧ ብለን እንተኛ ።
ደግሞም #ተናፋቂ ...
ከራሳችን አልፈን ፥ አለምን ጠባቂ
ከሰው የተለየን ፥ ሰዎች እንደሆንን ፥ ቀድሞኑ ስታውቂ
ምቾት ላንገላታው ...እንደኔና እንዳቺ ...ለተፍታታ ዜጋ
#ኮሮራ እንዳይዘን ፥ ስለምነው እሱ ፥ ቅንጣት የምንሰጋ ?
ብዬ መደለያ ...ቅንጣ የተስፋ ቃል...ከምኞት ስላጣሁ
ክብደቱ እንዲከብድሽ ... #ለማካበድ_ወጣሁ!!
አይግረምሽ እንግዲ.... #አካበድሁ!!
✍ #አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ)
✍ @Abr_sh
@getem
@getem
@getem
#ሁለት_ገፅታ
።
አይዳንድ ጊዜ : ሰዉ ከራስ ሲስማማ፣
ሲሄድ ሲራመድ : በሀሳብ ማማ፤
አይጣል ነዉ ነገሩ፣
አይፈታ ሚስጢሩ።
፧
ሰዉ . . . .
ከራስ ተስማምቶ : ሲመቸዉ ጊዜያቱ፣
ረጥቦ ሲለመልም : ዉስጠት አንጀቱ፤
ፈጣሪን አይሰማ : ከራሱ ሲጣላ፣
ራሱን ተመክቶ : አያገኝ ከለላ።
፧
ሀሴት ሲጎናፀፍ፣
በቀሽም ሀሳብ : ከጎን ሲደጋገፍ፤
ያገኘ ሲመስለዉ : ኪሱ ሲሞላ፣
ጠግቦ ስለዋለ : ሲሞላ(ሞ) በተድላ፤
ሚስጢር ነዉ ነገሩ፣
አይጣል ነዉ ሚስጢሩ።
፧
ደግሞም . . . . .
ሲከፋዉ . . .ተድላ ሲከዳዉ፣
ሆድ ሲብሰዉ : ባዶነት ሲሰማዉ(ሰ)፤
ከራሱ አይስማማ፣
ከቶ አይራመድ : በሀሳብ ማማ።
፧
. . . . .
ደግሞም ደግሞም፣
ሰዉ ከራስ ተጣልቶና ከርሞም፤
ሲናከስ ከሀሳቡ፣
ሲኮፈስ ከልቡ፤
ሲራቆት ሲናቆር፣
ሲፋጅ ሲሸናቆር፤
ሲከፋዉ በሆዱ ሲከዳ፣
የልቅሶ እንባ ከልቡ ሲቀዳ፤
ማልቀስ፣
ከሁሉ መናከስ፣
ከህይወት መፋለስ፤
ስራዉ ሆኖ በየጊዜው፣
ፈጣሪን ያማራል: ሆዱ ሲጎለዉ።
፧
ደግሞም . . . . .
ከራስ ተስማምቶ : ሲመቸዉ ጊዜያቱ፣
ረጥቦ ሲለመልም : ዉስጠት አንጀቱ፤
ይኖራል ፈጣሪን ረስቶ፣
ነፍስ እያለዉ ሞቶ።
ይኖራል ረስቶ አስራቱን፣
ደሀዉን መቀለቡን፣
እጅ መዘርጋቱን።
ይኖራል ረስቶ : የእዉነትን አምላክ፣
ያቺን የፈጣሪ እናት : ያቺን ወላዲተ አምላክ።
፧
፧
እንግዲህ . . . .
የዚህ አለም ኑሮ : እንዲህ ነዉ በየአይነት፣
ሲያጡ ፈጣሪን መፈለግ : ሳይነጋ ለማግኘት።
ሲያገኙም አምላክን መሸሽ : ሲመሽ ላለመገኘት።
በቃ ይህ አለም : እንዲህ ነዉ ሀቁ : የሞላዉ ልዩነት፣
ማግኘት ማጣት ሰፍቶ : ጠፍቶ አንድነት፣
ያገኙትን ማጣት : ያጡትን መግኘት።
።
18 / 10 / 2010
@getem
@getem
@getem
።
አይዳንድ ጊዜ : ሰዉ ከራስ ሲስማማ፣
ሲሄድ ሲራመድ : በሀሳብ ማማ፤
አይጣል ነዉ ነገሩ፣
አይፈታ ሚስጢሩ።
፧
ሰዉ . . . .
ከራስ ተስማምቶ : ሲመቸዉ ጊዜያቱ፣
ረጥቦ ሲለመልም : ዉስጠት አንጀቱ፤
ፈጣሪን አይሰማ : ከራሱ ሲጣላ፣
ራሱን ተመክቶ : አያገኝ ከለላ።
፧
ሀሴት ሲጎናፀፍ፣
በቀሽም ሀሳብ : ከጎን ሲደጋገፍ፤
ያገኘ ሲመስለዉ : ኪሱ ሲሞላ፣
ጠግቦ ስለዋለ : ሲሞላ(ሞ) በተድላ፤
ሚስጢር ነዉ ነገሩ፣
አይጣል ነዉ ሚስጢሩ።
፧
ደግሞም . . . . .
ሲከፋዉ . . .ተድላ ሲከዳዉ፣
ሆድ ሲብሰዉ : ባዶነት ሲሰማዉ(ሰ)፤
ከራሱ አይስማማ፣
ከቶ አይራመድ : በሀሳብ ማማ።
፧
. . . . .
ደግሞም ደግሞም፣
ሰዉ ከራስ ተጣልቶና ከርሞም፤
ሲናከስ ከሀሳቡ፣
ሲኮፈስ ከልቡ፤
ሲራቆት ሲናቆር፣
ሲፋጅ ሲሸናቆር፤
ሲከፋዉ በሆዱ ሲከዳ፣
የልቅሶ እንባ ከልቡ ሲቀዳ፤
ማልቀስ፣
ከሁሉ መናከስ፣
ከህይወት መፋለስ፤
ስራዉ ሆኖ በየጊዜው፣
ፈጣሪን ያማራል: ሆዱ ሲጎለዉ።
፧
ደግሞም . . . . .
ከራስ ተስማምቶ : ሲመቸዉ ጊዜያቱ፣
ረጥቦ ሲለመልም : ዉስጠት አንጀቱ፤
ይኖራል ፈጣሪን ረስቶ፣
ነፍስ እያለዉ ሞቶ።
ይኖራል ረስቶ አስራቱን፣
ደሀዉን መቀለቡን፣
እጅ መዘርጋቱን።
ይኖራል ረስቶ : የእዉነትን አምላክ፣
ያቺን የፈጣሪ እናት : ያቺን ወላዲተ አምላክ።
፧
፧
እንግዲህ . . . .
የዚህ አለም ኑሮ : እንዲህ ነዉ በየአይነት፣
ሲያጡ ፈጣሪን መፈለግ : ሳይነጋ ለማግኘት።
ሲያገኙም አምላክን መሸሽ : ሲመሽ ላለመገኘት።
በቃ ይህ አለም : እንዲህ ነዉ ሀቁ : የሞላዉ ልዩነት፣
ማግኘት ማጣት ሰፍቶ : ጠፍቶ አንድነት፣
ያገኙትን ማጣት : ያጡትን መግኘት።
።
18 / 10 / 2010
@getem
@getem
@getem
👍1
#ቀሽም_ብይን
ምሩቅ ጥበብ ሰሪ
የሸራ ቀበኛ ፥ የቀለም ቀማሪ
ጠቢባን ጠበብቶች
የቀለም አባቶች
የብሩሽ አርበኛ ፥ የኪነት ገማቾች
በዘመን የቆሙት
ከትውልዱ ወጥተው ፥ የሚተዛዘቡት
አልያ ....ዘመን አልፈው
በነጠረ ስራ....
ከኛ ጀምበር ጥላ ፥ በሞገስ የቆሙት
መናኛም.....ሆኑ ...ዝነኛ
ትሁትም ....ሆኑ ....ጉረኛ
እርቃን አፍቃሪዎች!
ምስል ደጋሚዎች!
ምጡቅ አሳቢዎች!
ብቻ.....ሰአሊ የሆኑ
ሸራ የወጠሩ ፥ ብሩሽ የዘገኑ
ሁለት ግዜ ነው.... የሚስሉ
ሁለት ግዜ ነው ....የሚያጤኑ
#አንድ...
በረጅም ግዜ ተመስጦ ...በጥቂት ግዜ መቃኘት
የሚፈለገውን ውበት ፥ ተኩሮ በማየት
በህሊና ችንካር ሸራ
ያኔ ነው ፥ የጥበብ ሽል ፥ ፅንሱ የሚዘራ
#ሁለት...
እንግዲህ በሀሳብ ፥ ምስሉ እንደታያቸው
በውን አለም ሸራ ...ይጫራል ንድፋቸው
አይን እና እጆቻቸው ፥ እኩል እስከቻሉ
የግል አይናቸውን ፥ ለሰው ይቸራሉ
ያዩትን ...ለማውረድ
ፅንፉን ለማዋደደ
ጣጥረው..
ጫጭረው...
ሞንጭረው...
የለቀለቁትን.... አቅመ ጥበብ ቅይጥ
ጋለሪ እያገባ ...ወዳጅ እንዲያቋምጥ
ሁለቴ ተረግዞ...ሁለቴ ይማጣል
አፍቃሪው በርትቶ....
ወላድ ለመጠየቅ ...አውደርይ ይወጣል
በዚህ ኩናቴ ውስጥ...
አንዳቹም ሰአሊ
ልጁን የሰቀለ ፥ በቤት በጋለሪ
እስኪያረጅ ...እስኪሸጥ
ማንጠልጠል ይወዳል ፥ ጭንቁን እንደ ትሪ
የብሩሹ አጣጣል ፥ ቀለም ስብጥሩ
የመልእክቱ ምጥቀት ፥ ብራና ሚስጥሩ
ገለፃው......ውብቱ
ጨረሩ ....ሙቀቱ
ሺህ ግዜ ፥ እልፍ አመት
እኛን ቢገርመንም...
ቢያጅበንም ...ደርሶ
የሁለቴ ምጥ ነው
ዘመን የሚሻገር ፥ በቀለማት ርሶ
አየሽልኝ ውዴ....
እንዲህ ያለውን ሰው
ወሮታው ሲዘከር ስላንጠለጠለ
በምናቤ ጓዳ...
የማይከስም ምስልን...ራሴ ላስጠለለ
አፍቃሪነት ዳሩ...
ከጠቢብም በላይ ...ጥበብ እንዳዘለ
ምስክሬ ነፍሴ
ባገኘው ወረቀ....አንቺን እንደሳለ
ምን ይሆን መስፈርቱ
ማነው የሚረዳ...
አይኔ በከደነ ፥ ገፅታሽ ሲቀዳ
ምስልሽ ሲንቀራወዝ ...በህልሜ ሰሌዳ
በውኔም በወረቀት ፥ ሲብስ በግድግዳ
የብዙ ብዙን ምጥ....አዕላፈ ውልጃ
ከሁለት ግልግል...ካንድ ተኩል ውርጃ
ለማመዛዘኛ....ቢጠፋ ብልሀቱ
ተደብቄ ኖርኩኝ ፥ የመልክሽ ሎሬቱ ።
✍ አብርሀም_ተክሉ ( መርዕድ)
@Abrham_teklu
@getem
@getem
ምሩቅ ጥበብ ሰሪ
የሸራ ቀበኛ ፥ የቀለም ቀማሪ
ጠቢባን ጠበብቶች
የቀለም አባቶች
የብሩሽ አርበኛ ፥ የኪነት ገማቾች
በዘመን የቆሙት
ከትውልዱ ወጥተው ፥ የሚተዛዘቡት
አልያ ....ዘመን አልፈው
በነጠረ ስራ....
ከኛ ጀምበር ጥላ ፥ በሞገስ የቆሙት
መናኛም.....ሆኑ ...ዝነኛ
ትሁትም ....ሆኑ ....ጉረኛ
እርቃን አፍቃሪዎች!
ምስል ደጋሚዎች!
ምጡቅ አሳቢዎች!
ብቻ.....ሰአሊ የሆኑ
ሸራ የወጠሩ ፥ ብሩሽ የዘገኑ
ሁለት ግዜ ነው.... የሚስሉ
ሁለት ግዜ ነው ....የሚያጤኑ
#አንድ...
በረጅም ግዜ ተመስጦ ...በጥቂት ግዜ መቃኘት
የሚፈለገውን ውበት ፥ ተኩሮ በማየት
በህሊና ችንካር ሸራ
ያኔ ነው ፥ የጥበብ ሽል ፥ ፅንሱ የሚዘራ
#ሁለት...
እንግዲህ በሀሳብ ፥ ምስሉ እንደታያቸው
በውን አለም ሸራ ...ይጫራል ንድፋቸው
አይን እና እጆቻቸው ፥ እኩል እስከቻሉ
የግል አይናቸውን ፥ ለሰው ይቸራሉ
ያዩትን ...ለማውረድ
ፅንፉን ለማዋደደ
ጣጥረው..
ጫጭረው...
ሞንጭረው...
የለቀለቁትን.... አቅመ ጥበብ ቅይጥ
ጋለሪ እያገባ ...ወዳጅ እንዲያቋምጥ
ሁለቴ ተረግዞ...ሁለቴ ይማጣል
አፍቃሪው በርትቶ....
ወላድ ለመጠየቅ ...አውደርይ ይወጣል
በዚህ ኩናቴ ውስጥ...
አንዳቹም ሰአሊ
ልጁን የሰቀለ ፥ በቤት በጋለሪ
እስኪያረጅ ...እስኪሸጥ
ማንጠልጠል ይወዳል ፥ ጭንቁን እንደ ትሪ
የብሩሹ አጣጣል ፥ ቀለም ስብጥሩ
የመልእክቱ ምጥቀት ፥ ብራና ሚስጥሩ
ገለፃው......ውብቱ
ጨረሩ ....ሙቀቱ
ሺህ ግዜ ፥ እልፍ አመት
እኛን ቢገርመንም...
ቢያጅበንም ...ደርሶ
የሁለቴ ምጥ ነው
ዘመን የሚሻገር ፥ በቀለማት ርሶ
አየሽልኝ ውዴ....
እንዲህ ያለውን ሰው
ወሮታው ሲዘከር ስላንጠለጠለ
በምናቤ ጓዳ...
የማይከስም ምስልን...ራሴ ላስጠለለ
አፍቃሪነት ዳሩ...
ከጠቢብም በላይ ...ጥበብ እንዳዘለ
ምስክሬ ነፍሴ
ባገኘው ወረቀ....አንቺን እንደሳለ
ምን ይሆን መስፈርቱ
ማነው የሚረዳ...
አይኔ በከደነ ፥ ገፅታሽ ሲቀዳ
ምስልሽ ሲንቀራወዝ ...በህልሜ ሰሌዳ
በውኔም በወረቀት ፥ ሲብስ በግድግዳ
የብዙ ብዙን ምጥ....አዕላፈ ውልጃ
ከሁለት ግልግል...ካንድ ተኩል ውርጃ
ለማመዛዘኛ....ቢጠፋ ብልሀቱ
ተደብቄ ኖርኩኝ ፥ የመልክሽ ሎሬቱ ።
✍ አብርሀም_ተክሉ ( መርዕድ)
@Abrham_teklu
@getem
@getem
❤1👍1
የነበረሽን የፊትሽን ገፅታ
ናፍቃለሁ
የነበረሽን የአለባበስ ባህል
ናፍቃለሁ
የነበረሽን ሰላም
የነበረሽን ፍቅር
ናፍቃለሁ
ዛሬ ላይ የለሽም
ናፈኩሽ
ፈለኩሽ....አላገኘሁሽም
እግርሽና እግርሽ ተጠላልፈው ቀሩ
የገዛ አካላትሽ
በገዛ አካላትሽ ሆን ብለው ታጠሩ
በማይሆን ተመሩ
የማይሆን ከመሩ
መጥፊያሽን አፈሩ
በአንቺነትሽ ውስጥ
ሌላ አንቺዎች ወጡ
እኔ ብቻ ሚሉ አንቺን የሚቀጡ
የለሽም
.
.
የለሽም
.
.
አላገኘሁሽም
ጠፍታለች ከሚሉ
ለሃሜት ለወሬ ስሟን ከሚያውሉ
አይን አይኔን እያዩ
በነገር በአሽሙር ጎኔን ከሚወጉኝ
ምናል ከኔው ጋራ ወተው ቢያፋልጉኝ
.
.
.
#ሁለት_ሀገር
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ናፍቃለሁ
የነበረሽን የአለባበስ ባህል
ናፍቃለሁ
የነበረሽን ሰላም
የነበረሽን ፍቅር
ናፍቃለሁ
ዛሬ ላይ የለሽም
ናፈኩሽ
ፈለኩሽ....አላገኘሁሽም
እግርሽና እግርሽ ተጠላልፈው ቀሩ
የገዛ አካላትሽ
በገዛ አካላትሽ ሆን ብለው ታጠሩ
በማይሆን ተመሩ
የማይሆን ከመሩ
መጥፊያሽን አፈሩ
በአንቺነትሽ ውስጥ
ሌላ አንቺዎች ወጡ
እኔ ብቻ ሚሉ አንቺን የሚቀጡ
የለሽም
.
.
የለሽም
.
.
አላገኘሁሽም
ጠፍታለች ከሚሉ
ለሃሜት ለወሬ ስሟን ከሚያውሉ
አይን አይኔን እያዩ
በነገር በአሽሙር ጎኔን ከሚወጉኝ
ምናል ከኔው ጋራ ወተው ቢያፋልጉኝ
.
.
.
#ሁለት_ሀገር
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
👍40😢12❤6🤩1
#ሁለት_ማዶ
:
:
:
ማዶ ቆማ ታየኛለች
ማዶ ቆሜ አያታለሁ፤
እንዳየችኝ ትስቃለች
እኔም ሳያት እስቃለሁ።
ወዳኛለች ያሳብቃል
እርግጥ እኔም ወዳታለሁ።
:
:
ረግረጉን ልቤ ችሎ ቀስ እያለ አዘገመ፤
እፎይ ልል ስል ክምር ቋጥኝ
በተጠንቀቅ ፊቴ ቆመ።
:
:
ልቤ ሳይዝል አጠረኝ እጅ፤
ወዲያ ማዶ ያለችው ልጅ፤
አሁንም አለች፤
ተራራውን ታውቀዋለች፤
አያታለው ታየኛለች፤
እስቃለሁ ትስቃለች።
:
:
ልንያያዝ ተንጠራራን፤
በእምነቷ በእምነቴ
እንዲረዳን ፍቅርን ጠራን።
:
:
ሁለት ማዶ ሁለት እምነት
ድልድይ አልባ ማያስቀጥል፤
ብቻ ...
ብቻ ...
ብቻ ...
ስቃ ድብን ስቄ ቅጥል።
#ሄኖክ_ብርሃኑ (@yeneeyita)
@getem
@getem
@getem
:
:
:
ማዶ ቆማ ታየኛለች
ማዶ ቆሜ አያታለሁ፤
እንዳየችኝ ትስቃለች
እኔም ሳያት እስቃለሁ።
ወዳኛለች ያሳብቃል
እርግጥ እኔም ወዳታለሁ።
:
:
ረግረጉን ልቤ ችሎ ቀስ እያለ አዘገመ፤
እፎይ ልል ስል ክምር ቋጥኝ
በተጠንቀቅ ፊቴ ቆመ።
:
:
ልቤ ሳይዝል አጠረኝ እጅ፤
ወዲያ ማዶ ያለችው ልጅ፤
አሁንም አለች፤
ተራራውን ታውቀዋለች፤
አያታለው ታየኛለች፤
እስቃለሁ ትስቃለች።
:
:
ልንያያዝ ተንጠራራን፤
በእምነቷ በእምነቴ
እንዲረዳን ፍቅርን ጠራን።
:
:
ሁለት ማዶ ሁለት እምነት
ድልድይ አልባ ማያስቀጥል፤
ብቻ ...
ብቻ ...
ብቻ ...
ስቃ ድብን ስቄ ቅጥል።
#ሄኖክ_ብርሃኑ (@yeneeyita)
@getem
@getem
@getem
❤38👍13😱7😁3🔥2
#ሁለት_ማዶ
:
:
:
ማዶ ቆማ ታየኛለች
ማዶ ቆሜ አያታለሁ፤
እንዳየችኝ ትስቃለች
እኔም ሳያት እስቃለሁ።
ወዳኛለች ያሳብቃል
እርግጥ እኔም ወዳታለሁ።
:
:
ረግረጉን ልቤ ችሎ ቀስ እያለ አዘገመ፤
እፎይ ልል ስል ክምር ቋጥኝ
በተጠንቀቅ ፊቴ ቆመ።
:
:
ልቤ ሳይዝል አጠረኝ እጅ፤
ወዲያ ማዶ ያለችው ልጅ፤
አሁንም አለች፤
ተራራውን ታውቀዋለች፤
አያታለው ታየኛለች፤
እስቃለሁ ትስቃለች።
:
:
ልንያያዝ ተንጠራራን፤
በእምነቷ በእምነቴ
እንዲረዳን ፍቅርን ጠራን።
:
:
ሁለት ማዶ ሁለት እምነት
ድልድይ አልባ ማያስቀጥል፤
ብቻ ...
ብቻ ...
ብቻ ...
ስቃ ድብን ስቄ ቅጥል።
#ሄኖክ_ብርሃኑ (@yeneeyita)
@yeneeyita
@getem
@getem
@getem
:
:
:
ማዶ ቆማ ታየኛለች
ማዶ ቆሜ አያታለሁ፤
እንዳየችኝ ትስቃለች
እኔም ሳያት እስቃለሁ።
ወዳኛለች ያሳብቃል
እርግጥ እኔም ወዳታለሁ።
:
:
ረግረጉን ልቤ ችሎ ቀስ እያለ አዘገመ፤
እፎይ ልል ስል ክምር ቋጥኝ
በተጠንቀቅ ፊቴ ቆመ።
:
:
ልቤ ሳይዝል አጠረኝ እጅ፤
ወዲያ ማዶ ያለችው ልጅ፤
አሁንም አለች፤
ተራራውን ታውቀዋለች፤
አያታለው ታየኛለች፤
እስቃለሁ ትስቃለች።
:
:
ልንያያዝ ተንጠራራን፤
በእምነቷ በእምነቴ
እንዲረዳን ፍቅርን ጠራን።
:
:
ሁለት ማዶ ሁለት እምነት
ድልድይ አልባ ማያስቀጥል፤
ብቻ ...
ብቻ ...
ብቻ ...
ስቃ ድብን ስቄ ቅጥል።
#ሄኖክ_ብርሃኑ (@yeneeyita)
@yeneeyita
@getem
@getem
@getem
❤31👍24🎉3😱2🤩1