የቀበሮ ፀሎት
(ታገል ሰይፉ)
------
እባክህ አምላኬ- ብትሬን ቀባና
እኔም ልወዝወዘው-የሙሴን ጎዳና
ያላንዳች ፍርሃት-ያለምንም ችግር
ባህሩን ከፍዬ- ህዝቤን እንዳሻግር፡፡
*
አቤት የኔ ጌታ ይህም አያረካም
በቃልህ ታምኜ -ከሆንኩልህ መልካም
ለእኔም ፍቀድልኝ-ያብራምን ምልክት
ከምድር አሸዋ-ዘሬ እንዲበረክት፡፡
*
አቤቱ ምን ልሁን-ይህም አልጠቀመኝ
እስቲ እንደ ዮናስ-ህዝብ ፊት አቁመኝ
*
ትንቢቴን ሰምቶልኝ-ሀገር ይተራመስ
ሰው እህል ይጡም-ከብቱም ሳር አይቅመስ፡፡
ይህም አያረካም-ይልቅ እንደዳዊት
አንተን በሚፈራ-ብዙ ሺህ ሠራዊት
ዙፋኔ ተከቦ-በደስታ እንዳመልክህ
የዚህን ሰው ኮከብ -አውጣልኝ እባክህ
*
አደራህን ታዲያ- ጭንቅ አትወድም ነፍሴ
ልመናዬን ሰምተህ-ካደረግከኝ ሙሴ
መከራውን ማረኝ-ያርባ ዓመት ስደቱን
በሲና በረሃ-መራብ መጠማቱን፡፡
*
ነቢዩ ዮናስን -አርገህም ስትፈጥረኝ
የባህሩን ፍዳ- ያሳውን ሆድ ማረኝ፡፡
*
አብረሃምን ሆኜም-በደስታ ሳመልክህ
ልጅህን እረደው-አትበለኝ እባክህ፡፡
***
የዲዊትም ኮከብ-በኔ ላይ ሲወጣ
እባክህ አምላኬ -ጎልያድ አይምጣ፡፡
@getem
@getem
@gebriel_19
(ታገል ሰይፉ)
------
እባክህ አምላኬ- ብትሬን ቀባና
እኔም ልወዝወዘው-የሙሴን ጎዳና
ያላንዳች ፍርሃት-ያለምንም ችግር
ባህሩን ከፍዬ- ህዝቤን እንዳሻግር፡፡
*
አቤት የኔ ጌታ ይህም አያረካም
በቃልህ ታምኜ -ከሆንኩልህ መልካም
ለእኔም ፍቀድልኝ-ያብራምን ምልክት
ከምድር አሸዋ-ዘሬ እንዲበረክት፡፡
*
አቤቱ ምን ልሁን-ይህም አልጠቀመኝ
እስቲ እንደ ዮናስ-ህዝብ ፊት አቁመኝ
*
ትንቢቴን ሰምቶልኝ-ሀገር ይተራመስ
ሰው እህል ይጡም-ከብቱም ሳር አይቅመስ፡፡
ይህም አያረካም-ይልቅ እንደዳዊት
አንተን በሚፈራ-ብዙ ሺህ ሠራዊት
ዙፋኔ ተከቦ-በደስታ እንዳመልክህ
የዚህን ሰው ኮከብ -አውጣልኝ እባክህ
*
አደራህን ታዲያ- ጭንቅ አትወድም ነፍሴ
ልመናዬን ሰምተህ-ካደረግከኝ ሙሴ
መከራውን ማረኝ-ያርባ ዓመት ስደቱን
በሲና በረሃ-መራብ መጠማቱን፡፡
*
ነቢዩ ዮናስን -አርገህም ስትፈጥረኝ
የባህሩን ፍዳ- ያሳውን ሆድ ማረኝ፡፡
*
አብረሃምን ሆኜም-በደስታ ሳመልክህ
ልጅህን እረደው-አትበለኝ እባክህ፡፡
***
የዲዊትም ኮከብ-በኔ ላይ ሲወጣ
እባክህ አምላኬ -ጎልያድ አይምጣ፡፡
@getem
@getem
@gebriel_19
❤3
ቅድሚያ!
~~~~~~
ባልተኛው ልባችን ~ ቀልደኛው ልባችን ~ ከእውነት ቢታረቅም
ተጓዥ ያናንቃል ~ ጉዞ ካልጀመሩ ~ ለሀሳብ አይርቅም
ፊት እየቀደመ ~ ምኞት ከእርምጃ ~ ንግግር ከስራው
የዘመኔ ዳዊት
ጎልያድን ሳይሆን ~ ጠጠር መልቀሙን ነው ~ በብርቱ ሚፈራው
(በረከት ታደሰ)
@getem
@getem
@lula_al_greeko
~~~~~~
ባልተኛው ልባችን ~ ቀልደኛው ልባችን ~ ከእውነት ቢታረቅም
ተጓዥ ያናንቃል ~ ጉዞ ካልጀመሩ ~ ለሀሳብ አይርቅም
ፊት እየቀደመ ~ ምኞት ከእርምጃ ~ ንግግር ከስራው
የዘመኔ ዳዊት
ጎልያድን ሳይሆን ~ ጠጠር መልቀሙን ነው ~ በብርቱ ሚፈራው
(በረከት ታደሰ)
@getem
@getem
@lula_al_greeko
ሲገባህ ውደደኝ
✍(ገነት ሽብሩ)
.
.
ወርቁ ሞኝነት ነው ፣ ሰም ያጣ ቅኔ
በስም አልባ ስሜቶች
ከህሊናህ ጓዳ....
መውደድ ይሁን ፣ መጥላት
መላቅ ይሁን ፣ መዝቀጥ
መኖር ይሁን ፣ መጥፋት፡
ድሎት አይሉት ፍዳ
ሀሴት አይሉት ፣ ዋይታ
ልብህን እያመሠ ፣ መንፈስህን ሲረታ
አከላትህ ዝሎ ፣ ፍቅር ትርጉም ሲያጣ
ካንድ ወገን ላልሆነ ፣ ለስሜት ዲቃላ
በግድድር ልሳን ፣ መኖርን ላነጋ
ቃላቴ ሳሱብኝ ፣ ምን ብዬ ላውጋህ?
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እስቲ ጌታን ሹፈው....
በሰራቸው እጆች ፣ በጥፊ ሲመታ
የጠፋን ሊያገኝ ፣ ማንነቱን ሲያጣ
ተንቆ ጌታ ፣ ተገፍቶ መምህሬ
ፍቅሩን አስረዳ ፣ በደሙ ጠመኔ፡፡
ግን ለምን ስትል...
አጀብ ነው ብለው ፣ ጊንየስ ላይ መዝግበው
ሊፈምስ አይደለም
ያው...ፍቅር....ነው
ያው....መውደድ...ነው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ለጊዜ ስትል ፣ ባልገባህ ስሜት
ባላየህ ባልኖርክበት ፣ ወድሻለው አትበለኝ
ይልቅ ሌላውን ትተህ ፣ ሲገባህ ውደደኝ፡፡
★★★
✍(ገነት ሽብሩ)
@getem
@getem
@gebriel_19
✍(ገነት ሽብሩ)
.
.
ወርቁ ሞኝነት ነው ፣ ሰም ያጣ ቅኔ
በስም አልባ ስሜቶች
ከህሊናህ ጓዳ....
መውደድ ይሁን ፣ መጥላት
መላቅ ይሁን ፣ መዝቀጥ
መኖር ይሁን ፣ መጥፋት፡
ድሎት አይሉት ፍዳ
ሀሴት አይሉት ፣ ዋይታ
ልብህን እያመሠ ፣ መንፈስህን ሲረታ
አከላትህ ዝሎ ፣ ፍቅር ትርጉም ሲያጣ
ካንድ ወገን ላልሆነ ፣ ለስሜት ዲቃላ
በግድድር ልሳን ፣ መኖርን ላነጋ
ቃላቴ ሳሱብኝ ፣ ምን ብዬ ላውጋህ?
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እስቲ ጌታን ሹፈው....
በሰራቸው እጆች ፣ በጥፊ ሲመታ
የጠፋን ሊያገኝ ፣ ማንነቱን ሲያጣ
ተንቆ ጌታ ፣ ተገፍቶ መምህሬ
ፍቅሩን አስረዳ ፣ በደሙ ጠመኔ፡፡
ግን ለምን ስትል...
አጀብ ነው ብለው ፣ ጊንየስ ላይ መዝግበው
ሊፈምስ አይደለም
ያው...ፍቅር....ነው
ያው....መውደድ...ነው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ለጊዜ ስትል ፣ ባልገባህ ስሜት
ባላየህ ባልኖርክበት ፣ ወድሻለው አትበለኝ
ይልቅ ሌላውን ትተህ ፣ ሲገባህ ውደደኝ፡፡
★★★
✍(ገነት ሽብሩ)
@getem
@getem
@gebriel_19
*እጦት*
አንዳች ስሜት ነገር ነፍስያዬን ከባት ናፍቆት ሲናፍቀኝ
ካቀረቀርኩበት ቀና ብዬ ባየው ሠማዮ ቀረበኝ
............................
በጠራው ሠማይ ላይ በአምላክ እጅ ያጌጠ ምስልህ እየታየኝ
ነፍስህ በሀሴት ረቃ ፈገግታ ስትጭር ውብ ሣቅህ ናፈቀኝ
............................
የሣቅህ ውብ ዜማ የጥርሶችህ ድርድር
ዕንባዬን አብሶት ከደስታ ማማ ላይ ነፍሴን ሲያንደረድር
...........................
ደመናው ከለለኝ ጉም ጋረደው ዓይኔን ሠማዮ 'ራቀኝ
የማግኘት ጣረ ሞት ንጋቴን አፅልሞት ካንተ ሊያራርቀኝ
...........................
ለካስ...
በዕምነት የተኳለ ያፍቃሪ ልብ እውነት ስቃይ ነው ማለፊያው
ጎጆ ያልቀለሠ ማደሪያ ያጣ ወፍ ክንፉ ነው ማረፊያው
............................
አንተ ትቀርብ እንደው ላምላክ ንገርልኝ የማይቻል ያስችለኝ
የናፈኸኝ ለታ ሠማይ ዝቅ ብላ ካንተ ታገናኘኝ
............................
ግና ...
አልሠመረም መሠል
የቃየል እርግማን በኔ ላይ ደረሠ ምድር ፍሬ ነሣኝ
አይኖቼ ተራቡህ ነፍሴ ተጨነቀ ተቅበዝብዥ አረነኝ
.............................
ምነው ባትናፍቀኝ ነፍሴን ባታርደው
ምናለ ብረሣህ ብጠላህ አንተ ሠው
............................
እንዴውም ጠላሁህ አትውደደኝ ይቅር
ሠማይ በጥፍ ይራቅ እዛው ይበል ጥንቅር
............................
ፍቅር ማለት ምነው በጥላቻ አለም
የምን እንባ ማፍሰስ ዘላለም መታመም
...........................
ክህደት እያለ ምን ያረጋል ዕምነት
በሐሠት እያወጉ ምን ይረባል እውነት
..........................
ደግሞም ጠልተኸኛል ይህንን አውቃለሁ
በአንተ ትርጓሜ እምነት ክህደት ነው
...........................
ታምነኝ ይሆን ብዬ እጄን ብዘረጋ
አንተ ጠርጣሪ ሠው ልብህ የማይረጋ
...........................
አትውደደኝ ይቅር ...
እንድትወደኝ ብዬ ህልሜን ከምገፋ
ጠልተኸኝ ልታመም ዘመኔን ልገፋ
............................
እንደውም ጠላሁህ አልውደድህ ይቅር
ሠማይ በጥፍ ይራቅ እዛው ይበል ጥንቅር
............................
ግና...
በአፍቃሪ ልክ ዕምነት
ጥላቻ ፍቅር ነው ያልመተረው ልኬት
...................//...................
ተፃፈ በሔለን ፋንታሁን
@getem
@getem
አንዳች ስሜት ነገር ነፍስያዬን ከባት ናፍቆት ሲናፍቀኝ
ካቀረቀርኩበት ቀና ብዬ ባየው ሠማዮ ቀረበኝ
............................
በጠራው ሠማይ ላይ በአምላክ እጅ ያጌጠ ምስልህ እየታየኝ
ነፍስህ በሀሴት ረቃ ፈገግታ ስትጭር ውብ ሣቅህ ናፈቀኝ
............................
የሣቅህ ውብ ዜማ የጥርሶችህ ድርድር
ዕንባዬን አብሶት ከደስታ ማማ ላይ ነፍሴን ሲያንደረድር
...........................
ደመናው ከለለኝ ጉም ጋረደው ዓይኔን ሠማዮ 'ራቀኝ
የማግኘት ጣረ ሞት ንጋቴን አፅልሞት ካንተ ሊያራርቀኝ
...........................
ለካስ...
በዕምነት የተኳለ ያፍቃሪ ልብ እውነት ስቃይ ነው ማለፊያው
ጎጆ ያልቀለሠ ማደሪያ ያጣ ወፍ ክንፉ ነው ማረፊያው
............................
አንተ ትቀርብ እንደው ላምላክ ንገርልኝ የማይቻል ያስችለኝ
የናፈኸኝ ለታ ሠማይ ዝቅ ብላ ካንተ ታገናኘኝ
............................
ግና ...
አልሠመረም መሠል
የቃየል እርግማን በኔ ላይ ደረሠ ምድር ፍሬ ነሣኝ
አይኖቼ ተራቡህ ነፍሴ ተጨነቀ ተቅበዝብዥ አረነኝ
.............................
ምነው ባትናፍቀኝ ነፍሴን ባታርደው
ምናለ ብረሣህ ብጠላህ አንተ ሠው
............................
እንዴውም ጠላሁህ አትውደደኝ ይቅር
ሠማይ በጥፍ ይራቅ እዛው ይበል ጥንቅር
............................
ፍቅር ማለት ምነው በጥላቻ አለም
የምን እንባ ማፍሰስ ዘላለም መታመም
...........................
ክህደት እያለ ምን ያረጋል ዕምነት
በሐሠት እያወጉ ምን ይረባል እውነት
..........................
ደግሞም ጠልተኸኛል ይህንን አውቃለሁ
በአንተ ትርጓሜ እምነት ክህደት ነው
...........................
ታምነኝ ይሆን ብዬ እጄን ብዘረጋ
አንተ ጠርጣሪ ሠው ልብህ የማይረጋ
...........................
አትውደደኝ ይቅር ...
እንድትወደኝ ብዬ ህልሜን ከምገፋ
ጠልተኸኝ ልታመም ዘመኔን ልገፋ
............................
እንደውም ጠላሁህ አልውደድህ ይቅር
ሠማይ በጥፍ ይራቅ እዛው ይበል ጥንቅር
............................
ግና...
በአፍቃሪ ልክ ዕምነት
ጥላቻ ፍቅር ነው ያልመተረው ልኬት
...................//...................
ተፃፈ በሔለን ፋንታሁን
@getem
@getem
#ኡስታዙ_እና_ቄሱ
ከውሰር[ጋዜጠኛው ዶክተር]
.
በዚህች ጠባብ ሀገር፣በዚህች በአንድ ምድር፤
ቄሱ እና ኡስታዙ አይተናኮስም፣በወል ነው የሚያድር።
.
ይሄ ጀግና ኡስታዝ አማማውን ታጥቆ፣ሙደወሩን ለብሶ፤
ፂሙን አስረዝሞ ሱሪውን አሳጥሮ፤ከቁርአን አጣቅሶ፤
ከመስጂዱ ቅጥር፣ሲያሰግድ ይውላል ኻምሴ ተመላልሶ።
ከሰላት ቡሀላም ዲስኩር ይጀምራል፣ወደ ኡማው ዞሮ፤
የአንድዬን እዝነት፣የአምላክን ቀጪነት፣ይነግራል ዘርዝሮ።
፡
ይሄም ጀግና ፓፓስ፣መስቀሉን ጨብጦ፣ካባውን ደርቦ፤
ውቡን አክሊል ለብሶ፣ይገባል ቤተስቲያን፣ከምእመናን ቀርቦ።
መርጌታው ሲያስተምር፣የያሬድን ዜማ፤
ዲያቆኑ ይቀድሳል፣የእግዜርን ቃላት፣ለህዝቡ ሊያሰማ።
መምህሩም ለህዝቡ፣ሠላም ይሰብካሉ፤
ቄሱም ፀበል ረጭተው፣በስም አብ ይላሉ።
፡
እንዲህ ናት ሀገሬ፣ይህች ጠባብ ምድር፤
ቄሱ እና ኡስታዙ፣አይተናኮልም፣በወል ነው የሚያድር።
፡
አሀዱ አምላክ ብለው፣ቤተስቲያን ገብተው፣ሲቀድሱ ቄሱ፤
ከመስጂዱ ቅጥር፣አላሁ አክበር አሉ፣ጌታን ሲያወድሱ፤
በስም አብ ብለው፣ስብከት ሲጀምሩ፣ቄሱ ለምእመናን፤
ቢስሚላህ ብለው ነው፣ኡስታዝ የሚያሰሙት፣ሚጀምሩት ዳእዋን።
፡
እንዲህ ናት ሀገሬ፣ይህች ጠባብ ምድር፤
ሙስሊም ክርስቲያኑ አይተናኮስም፣በወል ነው የሚያድር።
፡
#Kewser
@getem
@getem
@getem
ከውሰር[ጋዜጠኛው ዶክተር]
.
በዚህች ጠባብ ሀገር፣በዚህች በአንድ ምድር፤
ቄሱ እና ኡስታዙ አይተናኮስም፣በወል ነው የሚያድር።
.
ይሄ ጀግና ኡስታዝ አማማውን ታጥቆ፣ሙደወሩን ለብሶ፤
ፂሙን አስረዝሞ ሱሪውን አሳጥሮ፤ከቁርአን አጣቅሶ፤
ከመስጂዱ ቅጥር፣ሲያሰግድ ይውላል ኻምሴ ተመላልሶ።
ከሰላት ቡሀላም ዲስኩር ይጀምራል፣ወደ ኡማው ዞሮ፤
የአንድዬን እዝነት፣የአምላክን ቀጪነት፣ይነግራል ዘርዝሮ።
፡
ይሄም ጀግና ፓፓስ፣መስቀሉን ጨብጦ፣ካባውን ደርቦ፤
ውቡን አክሊል ለብሶ፣ይገባል ቤተስቲያን፣ከምእመናን ቀርቦ።
መርጌታው ሲያስተምር፣የያሬድን ዜማ፤
ዲያቆኑ ይቀድሳል፣የእግዜርን ቃላት፣ለህዝቡ ሊያሰማ።
መምህሩም ለህዝቡ፣ሠላም ይሰብካሉ፤
ቄሱም ፀበል ረጭተው፣በስም አብ ይላሉ።
፡
እንዲህ ናት ሀገሬ፣ይህች ጠባብ ምድር፤
ቄሱ እና ኡስታዙ፣አይተናኮልም፣በወል ነው የሚያድር።
፡
አሀዱ አምላክ ብለው፣ቤተስቲያን ገብተው፣ሲቀድሱ ቄሱ፤
ከመስጂዱ ቅጥር፣አላሁ አክበር አሉ፣ጌታን ሲያወድሱ፤
በስም አብ ብለው፣ስብከት ሲጀምሩ፣ቄሱ ለምእመናን፤
ቢስሚላህ ብለው ነው፣ኡስታዝ የሚያሰሙት፣ሚጀምሩት ዳእዋን።
፡
እንዲህ ናት ሀገሬ፣ይህች ጠባብ ምድር፤
ሙስሊም ክርስቲያኑ አይተናኮስም፣በወል ነው የሚያድር።
፡
#Kewser
@getem
@getem
@getem
-------አበሱዳ----------
==================
ልቤ አረገደ -ላንዲት ወሸባ ፣
ለመልከ ልዩ- ለወር ቀዘባ ፣
-------------—-------------------
----------
ወሸኔ ናት እሷ-የወርቅ ፍልቃቂ፣
አይን የምትሞላ ሴት - የሰው ቀልብ ሰራቂ።
----------------------------
የአትክል ስፍራ - እንደሚያምረው ሁላ፣
አይንን እንደሚስበው-እንደ ወይን ዘለላ፣
----------------
እንዴው ባንድ ቦታ - ድንገት ካገደመች፣
የሰው አይን ማረፊያ -ጉዳይ ትሆናለች።
------------------
መዳኒት ነች እሷ -እንደ ወርቅ በሜዳ፣
እንደ ጥቁሩ ፍሬ -ልክ እንዳበሱዳ፣
-----------------------
ከሷ ፈውስ ፈላጊ-ታማሚው በዛና፣
እልፍ ሆነ ከቤቷ-ደጇን የሚጠና።
-----------------
ከተለየ ጭቃ ውብ አድርጎ ፈጥሯት፣
ያያት ፈዞ ቀረ -እንኳን ያፈቀራት።
----------------------
ፈላጊዋ አሸን -ብዙ ነው ሚመኛት ፣
ጠበበኝ መንገዱ - ከሷ ምደርስበት።
------------------
ድምቀት ሆናቸው- ብርሃን ለሰፈር፣
ቆሌያቸው ሆና - ለነሱ አድባር፣
እንዳይናቸው ብሌን -ያዩዋታል በፍቅር ።
-------------
አንዋር እሁድ 13/08/11
@getem
@getem
@getem
==================
ልቤ አረገደ -ላንዲት ወሸባ ፣
ለመልከ ልዩ- ለወር ቀዘባ ፣
-------------—-------------------
----------
ወሸኔ ናት እሷ-የወርቅ ፍልቃቂ፣
አይን የምትሞላ ሴት - የሰው ቀልብ ሰራቂ።
----------------------------
የአትክል ስፍራ - እንደሚያምረው ሁላ፣
አይንን እንደሚስበው-እንደ ወይን ዘለላ፣
----------------
እንዴው ባንድ ቦታ - ድንገት ካገደመች፣
የሰው አይን ማረፊያ -ጉዳይ ትሆናለች።
------------------
መዳኒት ነች እሷ -እንደ ወርቅ በሜዳ፣
እንደ ጥቁሩ ፍሬ -ልክ እንዳበሱዳ፣
-----------------------
ከሷ ፈውስ ፈላጊ-ታማሚው በዛና፣
እልፍ ሆነ ከቤቷ-ደጇን የሚጠና።
-----------------
ከተለየ ጭቃ ውብ አድርጎ ፈጥሯት፣
ያያት ፈዞ ቀረ -እንኳን ያፈቀራት።
----------------------
ፈላጊዋ አሸን -ብዙ ነው ሚመኛት ፣
ጠበበኝ መንገዱ - ከሷ ምደርስበት።
------------------
ድምቀት ሆናቸው- ብርሃን ለሰፈር፣
ቆሌያቸው ሆና - ለነሱ አድባር፣
እንዳይናቸው ብሌን -ያዩዋታል በፍቅር ።
-------------
አንዋር እሁድ 13/08/11
@getem
@getem
@getem
#እንድቅትዮን ፬
ዕንቁላል ፋብሪካ በሚገኘው በገነት መናፈሻ
#ማክሰኞ ሚያዚያ 29 2011ዓ.ም.
አመሻሹ 11:30
መግቢያ ዋጋ 50 ብር
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
ዕንቁላል ፋብሪካ በሚገኘው በገነት መናፈሻ
#ማክሰኞ ሚያዚያ 29 2011ዓ.ም.
አመሻሹ 11:30
መግቢያ ዋጋ 50 ብር
@tebeb_mereja
@tebeb_mereja
ኖርኩ አልልም እኔ
(ቡሩክ ካሳሁን)
የባንክ አካውንቴ ሞልቶ ካልፈሰሰ
መንግስት ሊቀፍለኝ ድግስ ካልደገሰ
የግቢዬ ቅጥር ከኤርትራ ካነሰ
ሲራጩ የኖሩት ይስጡ ትንታኔ
በየትኛው አፌ ኖርኩ ልበል እኔ?
ቁርሴን አዲሳባ ምሳ ፓሪስ ለንደን
ለመዛናናት ቬጋስ አማዞን ለአደን
ካልፈነጨሁባት አለምን በውኔ
ኖርኩ አልልም እኔ
እኔና ሃሳቤን ተሳልቆ የናቀ
እንደ እንቧይ ፈርጦ ፊቴ ካልደቀቀ
ምን ጥሩ ብሰራ ላልተርፍ ከኩነኔ
ይህንን ካላየሁ ኖርኩ አልልም እኔ
በአለም ኑሮዬ ካልተቀማጠልኩኝ
ነብርን በጡጫ ነርቼ ካልጣልኩኝ
በመሞቴ ማግስት በመቃብሬ ላይ
በወርቃማ ቀለም ለሁሉም እንዲታይ
‹ኖርኩ አልልም እኔ› ብላቹ ፃፉበት
የውሸት ኖሪያለሁ የእውነት ልሙትበት፡፡
@getem
@getem
@getem
(ቡሩክ ካሳሁን)
የባንክ አካውንቴ ሞልቶ ካልፈሰሰ
መንግስት ሊቀፍለኝ ድግስ ካልደገሰ
የግቢዬ ቅጥር ከኤርትራ ካነሰ
ሲራጩ የኖሩት ይስጡ ትንታኔ
በየትኛው አፌ ኖርኩ ልበል እኔ?
ቁርሴን አዲሳባ ምሳ ፓሪስ ለንደን
ለመዛናናት ቬጋስ አማዞን ለአደን
ካልፈነጨሁባት አለምን በውኔ
ኖርኩ አልልም እኔ
እኔና ሃሳቤን ተሳልቆ የናቀ
እንደ እንቧይ ፈርጦ ፊቴ ካልደቀቀ
ምን ጥሩ ብሰራ ላልተርፍ ከኩነኔ
ይህንን ካላየሁ ኖርኩ አልልም እኔ
በአለም ኑሮዬ ካልተቀማጠልኩኝ
ነብርን በጡጫ ነርቼ ካልጣልኩኝ
በመሞቴ ማግስት በመቃብሬ ላይ
በወርቃማ ቀለም ለሁሉም እንዲታይ
‹ኖርኩ አልልም እኔ› ብላቹ ፃፉበት
የውሸት ኖሪያለሁ የእውነት ልሙትበት፡፡
@getem
@getem
@getem
+ጎበዝ ባንድእንጩህ+
ሳቅና ዳንሳችን ልብስና ቋንቋችን
ከጋራ ሜዳችን ለጉድ ቢለቀቅም
ከማንነት በቀር አግባብቶን አያውቅም
ይልቁንስ ወገን
ቀን ይወጣል ሲባል ቀን እየጨለመ
ያትጠገብ ጌታ መብት ለጠየቀው ሞት እየሸለመ
ቤተሰብ አርጎብን ስርቆና ዘረፋ
እንደ ስኳር ሁሉ አቁሞ ሲያድለን ሞትን በወረፋ
ዝምብለን እያየን
አለን መስሎን እንጅ ሁላችን አልቀናል
ጎበዝ ባንድ እንጬህ ቋንቋ ቢለያየን ለቅሶ ያግባባናል፡፡
///ሀብታሙ ያለው///
@getem
@getem
@gebriel_19
ሳቅና ዳንሳችን ልብስና ቋንቋችን
ከጋራ ሜዳችን ለጉድ ቢለቀቅም
ከማንነት በቀር አግባብቶን አያውቅም
ይልቁንስ ወገን
ቀን ይወጣል ሲባል ቀን እየጨለመ
ያትጠገብ ጌታ መብት ለጠየቀው ሞት እየሸለመ
ቤተሰብ አርጎብን ስርቆና ዘረፋ
እንደ ስኳር ሁሉ አቁሞ ሲያድለን ሞትን በወረፋ
ዝምብለን እያየን
አለን መስሎን እንጅ ሁላችን አልቀናል
ጎበዝ ባንድ እንጬህ ቋንቋ ቢለያየን ለቅሶ ያግባባናል፡፡
///ሀብታሙ ያለው///
@getem
@getem
@gebriel_19
♡ ስሞት አትቅበረኝ ♡♡♡
በሂወት እያለሁ እንባዬን ካልጠረግህ ፣
በእኔ እንባ ማንባት ካላዘነ ልብህ ፣
ሰታመም ዝም ካልህ ፣
እራቤ ካልገባህ ፣
ጭንቀቴም ብሶቴም ከመሰለህ ተራ ፣
ድፍርሱ ሂወቴ በፍቅርህ ካልጠራ ፣
ደብዛዛዉ ሂወቴ በፍቅርህ ካልበራ ፣
ተልካሻዉ ኑሮዬን
ካላሰናዳከዉ ፣
የተደላደለ ቦታ ካላሲያዝከዉ ፣
ማየት የተሳነዉ
ፍቅሬን ካልመራሀዉ ፣
እዉነት እልሃለሁ ዉዴ...
ስሞት አትቅበረኝ ፣
እንባም አታንባልኝ ፣
ፀፀትም አትግባ
ይልቁንስ ፍቅሬ...
እንደ ሻማ ቀልጦ ፍቅሬ ሳያልቅብህ ፣
እጂጉን አምሮ ልቤ ሳይቆርጥብህ ፣
ስታመም አስታመኝ ፣
ሰከፋ አፅናናኝ ፣
ስወድቅ ደግፈኝ ፣
የጭንቀቴን ብሶት
የዉስጤን ተረዳኝ ፣
ድፍርሱን ሂወቴን
በፍቅርህ አጥራልኝ ፣
ደብዛዛዉ ሂወቴን
በፍቅርህ አብራልኝ ፣
ተልካሻዉ ኑሮዬ
ፈጥነህ አሰናዳዉ ፣
የተደላደለ ቦታዉን አሲዘዉ ፣
ማየት የተሳነዉ
ልቤን ይዘሀ ምራዉ ፣
ደስታና ፍቅርን ከልብ አስተምረኝ ፣
ሁል ጊዜ ሳቅልኝ ፣
ይሄ ካልሆነ ግን
ስሞት አትቅበረኝ ::
ምንጭ፦ ወንጌላዊት እሙ
=======================
ለ "ስሞት አትቅበረኝ" ግጥም ምላሽ
ከአያልቅበት ሰለሞን
እሙ በህይወት እስካለሽ እንባሽን አብሼ
ስታለቅሺ ሳይሽ ተንሰቅስቄ አልቅሼ
ስትዝኚ ዕያየሁ እጥፍ ካላዘንኩኝ
ምኑን ሰው ተባልኩኝ
ሢያምሽ ካላመመኝ
እራብሽ ካልራበኝ
ምኑን አፈቀርኩሽ ምኑን ወዳጅ ሆንኩኝ
ጭንቀትሽ ብሶትሽ ከመሰለኝ ተራ
ድፍርሱ ህይወትሽ በፍቅሬ ካልጠራ
ተልካሻው ኑሮሽን ካላሰናዳሁት
የተደላደለ ቦታ ካላሲያዝኩት
ምናል ባልተዋወቅን እላለሁኝ ዕኔ
ለፍቅርሽ መከታ ስላለመሆኔ
ይልቅስ አታስቢ ፍቅሬ
ቃል ልግባልሽ ዛሬ
ስታለቅሺ አልቅሼ ስታዝኝም አዝናለው
ባስለቀሰሽ ጉዳይ ዳኛም እሆናለው
እፋረደዋለው።
ፍቅርሽን ቀንበቀን በፍቅሬ አድሳለው
ምስቅልቅል ህይወትሽን ዘውትር አድሳለው
እታመንሻለው
አይንሽ አያለቅስም
ልብሽ አይቆዝምም
ፈገግታሽ አይፈዝም
የፊትሽም ፀዳል ከቶ አይደብዝዝም
ይኸውልሽ ፍቅሬ ቃል ልግባ ደግሜ
ፍቅርሽ ተሰራጭቷል ባካልና ደሜ
ሲያምሽ ያምመኛል ሥታዝኚም አዝናለው
ስታለቅሺ አልቅሼ ስትስቂም ስቃለው
በፊትሽ ብርሐን እኔም እደምቃለው
ነገርግን ፍቅሬ ሆይ ስሚኝ በጽሞና
ምናልባት ሚሆነውን አላውቀውምና
አድምጭ እንደገና
ምናልባት ይህ ቃሌን መጠበቅ ቢያቅተኝ
ለፍቅርሽ መከታ መሖን ቢያታክተኝ
ህይወትሽን ማቃናት ባልችል በስንፍና
ይሄ ወዳጅነት ከቶ አይሆንምና
አድምጭ እንደገና
በፍቅሬ ፍቅርሽን መፈውስ ቢሳነኝ
ሀዘንሽን ማዘን ከቶ ባይቻለኝ
ዕንባሽን አብሼ
ባንቺ ፈንታ አልቅሼ
ሀዘንሽን አዝኜ
ሥታባክኝ ባክኜ
ካልተገኝኁ እኔ
ስትሞች አላለቅስም
ለቅሶ አልቀመጥም
በሞትሽ አላዝንም
ይልቅስ አድምጭ ነግርሻለው
ስትሞቺ ሞታለው
እከተልሻለው
እዚሕ በበደልኩሽ ላይ ቤት እክስሻለው
እመኝኝ ቃሌ ነው።
ምንጭ፦ አያልቅበት ሰለሞን
@getem
@getem
@getem
በሂወት እያለሁ እንባዬን ካልጠረግህ ፣
በእኔ እንባ ማንባት ካላዘነ ልብህ ፣
ሰታመም ዝም ካልህ ፣
እራቤ ካልገባህ ፣
ጭንቀቴም ብሶቴም ከመሰለህ ተራ ፣
ድፍርሱ ሂወቴ በፍቅርህ ካልጠራ ፣
ደብዛዛዉ ሂወቴ በፍቅርህ ካልበራ ፣
ተልካሻዉ ኑሮዬን
ካላሰናዳከዉ ፣
የተደላደለ ቦታ ካላሲያዝከዉ ፣
ማየት የተሳነዉ
ፍቅሬን ካልመራሀዉ ፣
እዉነት እልሃለሁ ዉዴ...
ስሞት አትቅበረኝ ፣
እንባም አታንባልኝ ፣
ፀፀትም አትግባ
ይልቁንስ ፍቅሬ...
እንደ ሻማ ቀልጦ ፍቅሬ ሳያልቅብህ ፣
እጂጉን አምሮ ልቤ ሳይቆርጥብህ ፣
ስታመም አስታመኝ ፣
ሰከፋ አፅናናኝ ፣
ስወድቅ ደግፈኝ ፣
የጭንቀቴን ብሶት
የዉስጤን ተረዳኝ ፣
ድፍርሱን ሂወቴን
በፍቅርህ አጥራልኝ ፣
ደብዛዛዉ ሂወቴን
በፍቅርህ አብራልኝ ፣
ተልካሻዉ ኑሮዬ
ፈጥነህ አሰናዳዉ ፣
የተደላደለ ቦታዉን አሲዘዉ ፣
ማየት የተሳነዉ
ልቤን ይዘሀ ምራዉ ፣
ደስታና ፍቅርን ከልብ አስተምረኝ ፣
ሁል ጊዜ ሳቅልኝ ፣
ይሄ ካልሆነ ግን
ስሞት አትቅበረኝ ::
ምንጭ፦ ወንጌላዊት እሙ
=======================
ለ "ስሞት አትቅበረኝ" ግጥም ምላሽ
ከአያልቅበት ሰለሞን
እሙ በህይወት እስካለሽ እንባሽን አብሼ
ስታለቅሺ ሳይሽ ተንሰቅስቄ አልቅሼ
ስትዝኚ ዕያየሁ እጥፍ ካላዘንኩኝ
ምኑን ሰው ተባልኩኝ
ሢያምሽ ካላመመኝ
እራብሽ ካልራበኝ
ምኑን አፈቀርኩሽ ምኑን ወዳጅ ሆንኩኝ
ጭንቀትሽ ብሶትሽ ከመሰለኝ ተራ
ድፍርሱ ህይወትሽ በፍቅሬ ካልጠራ
ተልካሻው ኑሮሽን ካላሰናዳሁት
የተደላደለ ቦታ ካላሲያዝኩት
ምናል ባልተዋወቅን እላለሁኝ ዕኔ
ለፍቅርሽ መከታ ስላለመሆኔ
ይልቅስ አታስቢ ፍቅሬ
ቃል ልግባልሽ ዛሬ
ስታለቅሺ አልቅሼ ስታዝኝም አዝናለው
ባስለቀሰሽ ጉዳይ ዳኛም እሆናለው
እፋረደዋለው።
ፍቅርሽን ቀንበቀን በፍቅሬ አድሳለው
ምስቅልቅል ህይወትሽን ዘውትር አድሳለው
እታመንሻለው
አይንሽ አያለቅስም
ልብሽ አይቆዝምም
ፈገግታሽ አይፈዝም
የፊትሽም ፀዳል ከቶ አይደብዝዝም
ይኸውልሽ ፍቅሬ ቃል ልግባ ደግሜ
ፍቅርሽ ተሰራጭቷል ባካልና ደሜ
ሲያምሽ ያምመኛል ሥታዝኚም አዝናለው
ስታለቅሺ አልቅሼ ስትስቂም ስቃለው
በፊትሽ ብርሐን እኔም እደምቃለው
ነገርግን ፍቅሬ ሆይ ስሚኝ በጽሞና
ምናልባት ሚሆነውን አላውቀውምና
አድምጭ እንደገና
ምናልባት ይህ ቃሌን መጠበቅ ቢያቅተኝ
ለፍቅርሽ መከታ መሖን ቢያታክተኝ
ህይወትሽን ማቃናት ባልችል በስንፍና
ይሄ ወዳጅነት ከቶ አይሆንምና
አድምጭ እንደገና
በፍቅሬ ፍቅርሽን መፈውስ ቢሳነኝ
ሀዘንሽን ማዘን ከቶ ባይቻለኝ
ዕንባሽን አብሼ
ባንቺ ፈንታ አልቅሼ
ሀዘንሽን አዝኜ
ሥታባክኝ ባክኜ
ካልተገኝኁ እኔ
ስትሞች አላለቅስም
ለቅሶ አልቀመጥም
በሞትሽ አላዝንም
ይልቅስ አድምጭ ነግርሻለው
ስትሞቺ ሞታለው
እከተልሻለው
እዚሕ በበደልኩሽ ላይ ቤት እክስሻለው
እመኝኝ ቃሌ ነው።
ምንጭ፦ አያልቅበት ሰለሞን
@getem
@getem
@getem
ትርጉምና ንፃሬ ፩
፨፨፨
በዝናብ በዶፉ መጓዝ እወዳለሁ
እንባዬ አይታይም እሄንን እውቃለሁ
ብሎ ነበር ቻርሊ ቀልደኛው ተዋናይ
ዛሬ ላይ ግን በዝቶ አልታየሁኝም ባይ
በጭጋግ እለታት ጭስ በደበቃቸው
ሲያጨሱ እሚውሉ አሸን ሰብእ ናቸው
ትርጉም ሳይገባቸው ሳያውቁት በውሉ
መደበቅ መስሏቸው ቃሉ ማስተዋሉ
መዋኛ ገንዳ ውስጥ የሚሸኑ አሉ
ህመምን መሸፈን እንባን መሰወሩ
ፈገግ ብሎ ማለፍ መልካም እያወሩ
ውስጠት ቢቃጠልም ፊትን ማቀዝቀዙ
ለመሸከም ነበር ህመምን በወዙ
ወትሮም ያልተረዳ መች አርፎ ቁጭ ይላል
መልካምን በክፋት ተግብሮት ይኮራል
፨፨፨
ኪነ ዳን ( @Nirvana134 )
@getem
@getem
@getem
፨፨፨
በዝናብ በዶፉ መጓዝ እወዳለሁ
እንባዬ አይታይም እሄንን እውቃለሁ
ብሎ ነበር ቻርሊ ቀልደኛው ተዋናይ
ዛሬ ላይ ግን በዝቶ አልታየሁኝም ባይ
በጭጋግ እለታት ጭስ በደበቃቸው
ሲያጨሱ እሚውሉ አሸን ሰብእ ናቸው
ትርጉም ሳይገባቸው ሳያውቁት በውሉ
መደበቅ መስሏቸው ቃሉ ማስተዋሉ
መዋኛ ገንዳ ውስጥ የሚሸኑ አሉ
ህመምን መሸፈን እንባን መሰወሩ
ፈገግ ብሎ ማለፍ መልካም እያወሩ
ውስጠት ቢቃጠልም ፊትን ማቀዝቀዙ
ለመሸከም ነበር ህመምን በወዙ
ወትሮም ያልተረዳ መች አርፎ ቁጭ ይላል
መልካምን በክፋት ተግብሮት ይኮራል
፨፨፨
ኪነ ዳን ( @Nirvana134 )
@getem
@getem
@getem
♥♥#የኔ_ሴት♥♥
#ከውሰር[ጋዜጠኛው ዶክተር]
.
በተስፋ ባህር ጉዞ፣ወደ ፊት ነጎድኩኝ፤
የኔን ሴት ፍለጋ፣መልህቄን ያዝኩና፣ወደፊት ቀዘፍኩኝ፤
ግጣሜን ስስላት፣ሀዋዬን አፈቀርኩ፣ነገን ዛሬ አስቤ፤
ያላወኳት ሚስቴን ሳላዉቃት ወደድኳት፣ማፍቀሯን ተርቤ።
ስለሷ እያሰብኩኝ፤
በተስፋው ባህር ላይ፣ፍቅሬ ተንሳፈፈ፤
ጨለማው ነግቶልኝ፣ደስታዬም ገዘፈ፤
ብእሬም አድምቆ፦
የኔ ሴት እያለ፣ብዙ ግጥም ፃፈ።
.
ሌሎች ከሴታቸው፣አሉታውን ገልጠው፤
የሚስትነት ጣእም፣የላትም ይላሉ፣ጥፍጥናዋን ሽጠው።
የታል ሚስትነቷ?የታል ሴትነቷ?ይላሉ በትዝብት፤
ሚስትነቷን አጥተው፣ሴትነቷን ሸሽተው፣ዘውትረው በግርምት።
.
የብሶት ዜማቸው፣ጎልቶ ውስጤ ቢገባ፤
መልህቄን ቀዝፌ፣የኔን ሴት አየዋት፣ሠመመን ስገባ፤
በተስፋው አለም ውስጥ ጎጆዬን ስቀልስ፣የኔ ሴት ውስጥ አለች፤
እራሷን አፅድታ፣በስራ ተጠምዳ፣ሽር ጉድ እያለች፤
ሠላምታዬን ሳቀርብ፣ምላሹን መልሳ ግንባሬን ሳመችኝ፤
እንኳን ደህና መጣህ፣አረፍ በል ፍቅሬ፣ፍቅሯን ለገሠችኝ፤
የሚስትነት ለዛን፣የሴትነት ጣእሙን፣ግቱን አሳየችኝ፤
.
ጠባብ ቤቴ ያኔ አማረ፤
ሳቋ ጎልቶ ጭንቀት ቀረ፤
መዉደቅ መክሰር ተሰበረ፤
ፍቅር ነግሶ ጎልቶ ኖረ፤
መንገሳችን ተበሰረ፤
ልቦናችን በፍቅራችን፣አካላችን ተሳሠረ።
በሷ ብርታት ጠነከርኩኝ፣ፀባይ ገዛው በፍቅር ላቅኩኝ፤
በስግደቴ በረታሁኝ፣በንግስቴ ንጉስ ሆንኩኝ።
እሷ ማለት እኮ፦
የሷ መኖር የሚያኖረኝ፤
እሷ ማለት በቃ እኔ ነኝ፤
ብለው እንዳዜሙት፣ግነትን ቀላቅለው፤
በሷነት መንፈስ ውስጥ፣የኔ መንፈስ አለው፤
ገላዋ የኔው ነው፣ለሌላው ሽፍን ነው፤
የኔ ደስታ ማለት፣ስለሷ መኖር ነው።
የኔ ሴት ለእኔ፦
አይኗ እያነባ ልቧ እያዘነ፤
ቃሏ ከእውነት ውጭ፣ለሀሠት የቦዘነ፤
"ህይወቴ ባዶ ናት አንድ ቀን ያለርሡ፤"
ብላ ምትፀልይ ናት፣ቆማ ከመጅሊሡ፤
.
ፍቅሯ ያስነባኛል፣ምክሯ ይሠራኛል፤
የእሷነት ተግሳፅ፣እኔን ያኖረኛል፤
ያኔ ኮራሁ በማግባቴ፤
ውሀ አጣጬን በማግኘቴ፤
ደመቀልኝ እኔነቴ፤
አስከበረኝ ባልነቴ፤
በሀሳቤ አለች ለኔ ሚስቴ።
[KEWSER]
@getem
@getem
@Alkewsism
#ከውሰር[ጋዜጠኛው ዶክተር]
.
በተስፋ ባህር ጉዞ፣ወደ ፊት ነጎድኩኝ፤
የኔን ሴት ፍለጋ፣መልህቄን ያዝኩና፣ወደፊት ቀዘፍኩኝ፤
ግጣሜን ስስላት፣ሀዋዬን አፈቀርኩ፣ነገን ዛሬ አስቤ፤
ያላወኳት ሚስቴን ሳላዉቃት ወደድኳት፣ማፍቀሯን ተርቤ።
ስለሷ እያሰብኩኝ፤
በተስፋው ባህር ላይ፣ፍቅሬ ተንሳፈፈ፤
ጨለማው ነግቶልኝ፣ደስታዬም ገዘፈ፤
ብእሬም አድምቆ፦
የኔ ሴት እያለ፣ብዙ ግጥም ፃፈ።
.
ሌሎች ከሴታቸው፣አሉታውን ገልጠው፤
የሚስትነት ጣእም፣የላትም ይላሉ፣ጥፍጥናዋን ሽጠው።
የታል ሚስትነቷ?የታል ሴትነቷ?ይላሉ በትዝብት፤
ሚስትነቷን አጥተው፣ሴትነቷን ሸሽተው፣ዘውትረው በግርምት።
.
የብሶት ዜማቸው፣ጎልቶ ውስጤ ቢገባ፤
መልህቄን ቀዝፌ፣የኔን ሴት አየዋት፣ሠመመን ስገባ፤
በተስፋው አለም ውስጥ ጎጆዬን ስቀልስ፣የኔ ሴት ውስጥ አለች፤
እራሷን አፅድታ፣በስራ ተጠምዳ፣ሽር ጉድ እያለች፤
ሠላምታዬን ሳቀርብ፣ምላሹን መልሳ ግንባሬን ሳመችኝ፤
እንኳን ደህና መጣህ፣አረፍ በል ፍቅሬ፣ፍቅሯን ለገሠችኝ፤
የሚስትነት ለዛን፣የሴትነት ጣእሙን፣ግቱን አሳየችኝ፤
.
ጠባብ ቤቴ ያኔ አማረ፤
ሳቋ ጎልቶ ጭንቀት ቀረ፤
መዉደቅ መክሰር ተሰበረ፤
ፍቅር ነግሶ ጎልቶ ኖረ፤
መንገሳችን ተበሰረ፤
ልቦናችን በፍቅራችን፣አካላችን ተሳሠረ።
በሷ ብርታት ጠነከርኩኝ፣ፀባይ ገዛው በፍቅር ላቅኩኝ፤
በስግደቴ በረታሁኝ፣በንግስቴ ንጉስ ሆንኩኝ።
እሷ ማለት እኮ፦
የሷ መኖር የሚያኖረኝ፤
እሷ ማለት በቃ እኔ ነኝ፤
ብለው እንዳዜሙት፣ግነትን ቀላቅለው፤
በሷነት መንፈስ ውስጥ፣የኔ መንፈስ አለው፤
ገላዋ የኔው ነው፣ለሌላው ሽፍን ነው፤
የኔ ደስታ ማለት፣ስለሷ መኖር ነው።
የኔ ሴት ለእኔ፦
አይኗ እያነባ ልቧ እያዘነ፤
ቃሏ ከእውነት ውጭ፣ለሀሠት የቦዘነ፤
"ህይወቴ ባዶ ናት አንድ ቀን ያለርሡ፤"
ብላ ምትፀልይ ናት፣ቆማ ከመጅሊሡ፤
.
ፍቅሯ ያስነባኛል፣ምክሯ ይሠራኛል፤
የእሷነት ተግሳፅ፣እኔን ያኖረኛል፤
ያኔ ኮራሁ በማግባቴ፤
ውሀ አጣጬን በማግኘቴ፤
ደመቀልኝ እኔነቴ፤
አስከበረኝ ባልነቴ፤
በሀሳቤ አለች ለኔ ሚስቴ።
[KEWSER]
@getem
@getem
@Alkewsism
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ትንቢት
(ቡሩክ ካሳሁን)
ነገ
ፀሀይ በምስራቅ ትወጣለች ነፋሳትም ይነፍሳሉ
ትንቢቱ አማናዊ ነውና ምዕመናን አሜን በሉ
አሜን እንደማለት ቁጭ ብላቹ ምታፈጡ
ከአሜን ይቀራልና ዣንጥላ ይዛቹ ውጡ
ከአሜን ሚቀር ትንቢት ነው ወይ? ወይ ምርቃት? የምትሉ
አተካራውን ትታቹ እደግመዋለው አሜን በሉ!
ከነገወዲያ ነገ ትላንተ ይሆናል
ትንቢት መናገር ባላቆምም ትንቢቴ ግን ይፈፀማል
ብዙዎች ትንቢቴን አጣጥለው ይስታሉ
ነገር ግን
ከነገ ወዲያ ላይ ቆመው ነገን ትላንት ይላሉ
ለትንቢቴም ይታመናሉ
ደግም በምዕራብ ፀሀይ ትጠልቃለች
ከእርሷ መሄድ ለጥቆ ይከተላል ጨለማም
ነገ የደረሰ ምስክሬ ነውቆጥረው በትንቢት አልታማም
በጠቆረውም ሰማይ 1001 ከዋክብት ይታያሉ
ቁጥሩን ለሚጠራጠሩ ቆጥረው ማረጋገጥ ይችላሉ
በረከት በበረከት ትሆናላቹ እንደታየኝ ሌሊት ሳልም
አትጠራጠሩ እንኳን ህልሜ የምቃዠው ጠብ አትልም
በረከቱ እንዲሞላቹ በአዲስ ፀጋ እንድትሰምጡ
በኪሳቹ ያለውን ያለስስት ለኔ ስጡ፡፡
@getem
@getem
@burukassahunC
(ቡሩክ ካሳሁን)
ነገ
ፀሀይ በምስራቅ ትወጣለች ነፋሳትም ይነፍሳሉ
ትንቢቱ አማናዊ ነውና ምዕመናን አሜን በሉ
አሜን እንደማለት ቁጭ ብላቹ ምታፈጡ
ከአሜን ይቀራልና ዣንጥላ ይዛቹ ውጡ
ከአሜን ሚቀር ትንቢት ነው ወይ? ወይ ምርቃት? የምትሉ
አተካራውን ትታቹ እደግመዋለው አሜን በሉ!
ከነገወዲያ ነገ ትላንተ ይሆናል
ትንቢት መናገር ባላቆምም ትንቢቴ ግን ይፈፀማል
ብዙዎች ትንቢቴን አጣጥለው ይስታሉ
ነገር ግን
ከነገ ወዲያ ላይ ቆመው ነገን ትላንት ይላሉ
ለትንቢቴም ይታመናሉ
ደግም በምዕራብ ፀሀይ ትጠልቃለች
ከእርሷ መሄድ ለጥቆ ይከተላል ጨለማም
ነገ የደረሰ ምስክሬ ነውቆጥረው በትንቢት አልታማም
በጠቆረውም ሰማይ 1001 ከዋክብት ይታያሉ
ቁጥሩን ለሚጠራጠሩ ቆጥረው ማረጋገጥ ይችላሉ
በረከት በበረከት ትሆናላቹ እንደታየኝ ሌሊት ሳልም
አትጠራጠሩ እንኳን ህልሜ የምቃዠው ጠብ አትልም
በረከቱ እንዲሞላቹ በአዲስ ፀጋ እንድትሰምጡ
በኪሳቹ ያለውን ያለስስት ለኔ ስጡ፡፡
@getem
@getem
@burukassahunC
ክፍት የስራ ቦታ
(ቡሩክ ካሳሁን)
ድርጅታችን
ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ የተመረቀ
ስለሚሰራው ስራ ከ ሀ እስከ ፐ ያወቀ
ከጠቅላይ ሚኒስተሩ ሜዳልያ
ከከንቲባው ጠቦት ዋልያ
ያገኘ
የኮብል ስቶን ንጣፍ ለሰፊው ህዝብ ያበረከተ
20 አመቱ ሆኖ የ22 አመት ልምድ ያካበተ
ከተቻለ ስለ ደም-ወዝ ማያነሳ
ካልሆነ ግን ያለንን ሰጥተነው እጅ የሚነሳ
ከተገኘ ውድ አመልካች
እነዚህን አሟልተህ ከኛ ብትቀርብም
ቆንጆ ሴት ከመጣች ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡
@getem
@getem
@burukassahunC
(ቡሩክ ካሳሁን)
ድርጅታችን
ከታወቀ ዩኒቨርሲቲ የተመረቀ
ስለሚሰራው ስራ ከ ሀ እስከ ፐ ያወቀ
ከጠቅላይ ሚኒስተሩ ሜዳልያ
ከከንቲባው ጠቦት ዋልያ
ያገኘ
የኮብል ስቶን ንጣፍ ለሰፊው ህዝብ ያበረከተ
20 አመቱ ሆኖ የ22 አመት ልምድ ያካበተ
ከተቻለ ስለ ደም-ወዝ ማያነሳ
ካልሆነ ግን ያለንን ሰጥተነው እጅ የሚነሳ
ከተገኘ ውድ አመልካች
እነዚህን አሟልተህ ከኛ ብትቀርብም
ቆንጆ ሴት ከመጣች ምንም ማድረግ አይቻልም፡፡
@getem
@getem
@burukassahunC