ወንድ እና ጡት
--------------------
"ኦ!አዳም!" "ኦ!አዳም!"
ጥሪ መጣ ከአርያም!
"አቤት ባይ ግን የለም!
በጡቶቿ መሀል አንገቱን ወሽቆ፣
በለሱን ይገምጣል አዳም ተደብቆ።
ከዚያኔ ጀምሮ . . .
በጡት መሀል ልክፍት፣
አዳም ይባክናል ከህይወት እስከ ሞት።
ልጅ ሆኖ እየጠባ፣
ይደበቅበታል ጎርምሶ ሲያገባ።
==============
በላ ልበልሀ!
-----------------
በላ ልበልሀ፣
በሀገርህ ዠማ ስር
ሙግት ልግጠምሀ!
ከቢራው ግሳት ነጥሎ፣
ቁንጣኑ ይቅርብኝ ብሎ።
ኢትዮጵያን ብሎ የዋለ፣
ሀገሬን ብሎ የማለ፣
እስቲ ይቆጠር ስንት አለ?
============
የድሌ ቀን
-------------
ባልነዘረ ክራር
ባልተነፋ እምቢልታ፣
ባልተመታ ታምቡር
ባልጮኸ ጡሩንባ፣
አካሌ ሲደንስ
እስክስታ ሲመታ።
በሌለ ሙዚቃ
ብለው ለሚስቁ፣
የድል ቀን ሲመጣ፣
"ሹ.ክ.ሹ.ክ.ታ" እንኳ
ቅኝት መሆኑን ባወቁ።
===========
የ"10" ሣንቲም እውነት
በወንድወሠን ካሣ
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
@getem
@getem
@SABT48
--------------------
"ኦ!አዳም!" "ኦ!አዳም!"
ጥሪ መጣ ከአርያም!
"አቤት ባይ ግን የለም!
በጡቶቿ መሀል አንገቱን ወሽቆ፣
በለሱን ይገምጣል አዳም ተደብቆ።
ከዚያኔ ጀምሮ . . .
በጡት መሀል ልክፍት፣
አዳም ይባክናል ከህይወት እስከ ሞት።
ልጅ ሆኖ እየጠባ፣
ይደበቅበታል ጎርምሶ ሲያገባ።
==============
በላ ልበልሀ!
-----------------
በላ ልበልሀ፣
በሀገርህ ዠማ ስር
ሙግት ልግጠምሀ!
ከቢራው ግሳት ነጥሎ፣
ቁንጣኑ ይቅርብኝ ብሎ።
ኢትዮጵያን ብሎ የዋለ፣
ሀገሬን ብሎ የማለ፣
እስቲ ይቆጠር ስንት አለ?
============
የድሌ ቀን
-------------
ባልነዘረ ክራር
ባልተነፋ እምቢልታ፣
ባልተመታ ታምቡር
ባልጮኸ ጡሩንባ፣
አካሌ ሲደንስ
እስክስታ ሲመታ።
በሌለ ሙዚቃ
ብለው ለሚስቁ፣
የድል ቀን ሲመጣ፣
"ሹ.ክ.ሹ.ክ.ታ" እንኳ
ቅኝት መሆኑን ባወቁ።
===========
የ"10" ሣንቲም እውነት
በወንድወሠን ካሣ
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
@getem
@getem
@SABT48
#ትዝታ,,,,
ደሞ መጣ ክረምት በጋውን አባሮ፤
ያለፈ ህይወቴን ትዝታን ከምሮ፡፡
በሚወርደው የዝናብ ዶፍ መሀል፤
የበፊት ወዳጄ ፍቅሬ ይታየኛል ፤
ብርድ ባወረዛው መስኮቴ ፊት ቆሜ አሻግሬ አያለው፤
ከዝናቡ መሀል እኔና እሱን አየው፡
ወገቤን በ'ጆቹ ጠበቅ አርጎ አቅፎኝ፡
ደሞ ፈገግ አልኩኝ ሁኔታው አስገርሞኝ፡
ብዬም ተመኘሁኝ የጥንቷን ባረገኝ፡፡
አሁንም ናልኝ ፍቅሬ ፤
ና'ማ ተከተለኝ በዝናብ እንበስብስ፤
ለዘመን የሚተርፍ ትዝታን እንቀልስ፤
ህይወትን እናድስ፤
ልብሳችን ይበስብስ፤
ፀጉራችን ይበስብስ፤
ጫማችን ይበስብስ፤
በተፈጥሮ ፀጋ አካላችን ይራስ፡፡
ና'ማ ተከተለኝ በ ዶፉ እንሩጥ፤
በቃ ያስወድቀን ያ ልስልስ ያፈር ድጥ፡፡
እጆቼን ያዛቸው አጥብቀህ በጆችህ፤
በ አንደድ ትቆራኝ ህይወቴ ከ'ይወትህ፡፡
ና'ማ ተከተለኝ እንደ ልጅ እንሁን፡
ጎርፍ ውስጥም እንግባ ጭቃውም ያዳልጠን፤
ሁሉንም እረስተን በፍቅር እንስከር፤
የኔና አንተን ብቻ ሌ,,ላ አለም እንፍጠር፡፡
//ማህሌት መሰረት //
@getem
@getem
ደሞ መጣ ክረምት በጋውን አባሮ፤
ያለፈ ህይወቴን ትዝታን ከምሮ፡፡
በሚወርደው የዝናብ ዶፍ መሀል፤
የበፊት ወዳጄ ፍቅሬ ይታየኛል ፤
ብርድ ባወረዛው መስኮቴ ፊት ቆሜ አሻግሬ አያለው፤
ከዝናቡ መሀል እኔና እሱን አየው፡
ወገቤን በ'ጆቹ ጠበቅ አርጎ አቅፎኝ፡
ደሞ ፈገግ አልኩኝ ሁኔታው አስገርሞኝ፡
ብዬም ተመኘሁኝ የጥንቷን ባረገኝ፡፡
አሁንም ናልኝ ፍቅሬ ፤
ና'ማ ተከተለኝ በዝናብ እንበስብስ፤
ለዘመን የሚተርፍ ትዝታን እንቀልስ፤
ህይወትን እናድስ፤
ልብሳችን ይበስብስ፤
ፀጉራችን ይበስብስ፤
ጫማችን ይበስብስ፤
በተፈጥሮ ፀጋ አካላችን ይራስ፡፡
ና'ማ ተከተለኝ በ ዶፉ እንሩጥ፤
በቃ ያስወድቀን ያ ልስልስ ያፈር ድጥ፡፡
እጆቼን ያዛቸው አጥብቀህ በጆችህ፤
በ አንደድ ትቆራኝ ህይወቴ ከ'ይወትህ፡፡
ና'ማ ተከተለኝ እንደ ልጅ እንሁን፡
ጎርፍ ውስጥም እንግባ ጭቃውም ያዳልጠን፤
ሁሉንም እረስተን በፍቅር እንስከር፤
የኔና አንተን ብቻ ሌ,,ላ አለም እንፍጠር፡፡
//ማህሌት መሰረት //
@getem
@getem
በዛ በበጋ በዛ በክረምት
በዛበበጋ በዛበክረምት
ወዳጄ ጠፍቶብኝ ፍለጋ
እውነት ሸሽታኝ ሆናብኝ አንተጋ
ካደግንበት ቀዬ፣ካደግንበት መንደር
ከሀደ ደኑ አድባር፣ከ አባቢያ ሀገር
ከዚያ ወብ ስፍራችን
አባጊዲ እግር ስር
አ፣ባ፣ጫ፣ዳ ስንቆጥር
ተኮ፣ ለማ እያልን ስንቀንስ ስንደምር
ካደግንበት ቀዬ፣ ካሳደገን መንደር
ከአዴ ኪሮስ አድባር፣ከ አያ ፈጠነ ሀገር
እስክስ ያልንበቱ ለአንባሻ ሽልማት
አዴ ከመይ ብለን እንጎቻ ለመብላት
ጨፍቅን አጅበን እልፍ ከብት መንዳት
እሳትዳር ቁጭብለን የስንዝሮን ተረት
መስማት
ትዝ ይልሀል? ትዝይልሀል አይደል ወንድምዬ
የዘመን ጓዴ እኩያዬ
ትዝ ይልሀል አይደል በዛ በበጋ በዛ በክረምት
በልጅነት ስንጫወት
ትዝ ይልሀል ወይ በብይ ስንደባደብ
በሴት ስንተራረብ
በ አሮጊት ፈስ
ስንቧቀስ
ትዝ ይልሀል አይደል ዘይቱን ስንለቅም
ካባ ወርደን ድፋርስ ውሀ ስንዋኝም
ደግሞ ለልደታ አድባር እንዳያኮርፋ
ከሰው ማሳ ፌስታል ብና በህብረት ስንዘርፍ
የእማማ እጅጋየሁን ቦርዴ ስንመጥ
የእትዬ ፀሀይን አነባበሮ ስንገምጥ
ጸግሞ ለጉዞአችን የጅሬንን አቀበት ለመውጣት
የንጉሱን ቤተመንግስት ተሳልሞ ለመምጣት
ተራራ ላይሆነን የጀሚላን ሀገር አጋሮን ለማየት
ቁም አገዳ የዘረፍነው
እልፍ ቃሪያ የነቀልነው
በዛ በበጋ በክረምት
በልጅነት በህብረት ስንጫወት
ከዚያ ካደግንበት ቀዬ፣ካደግንበት መንደር
ከአያ ጨፍቅ ግዛት፣ከሼህ ጀበል ሀገር
ትዝይልህ እንደሆን
ሴት ተናጥቀናል
ከ ጌኑ ጎመን ሰርቀናል
ከሼኪ ፓስቲ ቤት መልስ አጭበርብረናል
ጉርምስና ደርሶብን
አፍላ እድሜ ወጥሮን
ከየም ሰፈር፣ዳውሮ በር
ከአጂፕ፣ሰቃበር
ጫት ፍለጋ ስንዞር
አትረሳውም አይደል ወንድምዬ
አውቃለው መቼም አትረሳውም
ኦሾን ራምፓን አንብበን
ኪቶ ወንዝ ላይ ዮጋ መስራት ሲያምረን
ደግሞ ሙግት ስለ ጃንሆይ ተከራክረን
ስለ ቴድሮስ አብረን አዠነን
ስለ ጂብራን ደም እንባ አልቅሰን
ፐ-በዓሉ ግርማ ኦሮማይ የመፅሀፍ ቁንጮ እያልን
የአቤ አልወለድም እጅጉን ደስ ሲለን
ስለ ጉዱ ካሳ በጣሙን ሲገርመን
ምን አለፍህ
ምን አለፍህ ወንድም አለም የኔ ያንተ
የልጅነት፣የአፍላ ታሪክ እኮ ተወስቶ አያልቅም
መጨረሻው ባያምርልን
ካደግንበት ከኖርንበት ቀዬ
መጥቶ አዲስ ፈሊጥ አዲስ ዘዬ
፦እትብታችን
፦ መንፈሳችን
፦ የልጅነት ትዝታችን ካለበት መንደር
ሰፋሪ ናቹ ተብለን ስንባረር
አውቃለው! አውቃለው ወንድም አለም
ከፍቶሀል፥ከፍቶኛል
የሀደ ጃፈር ፍትፋት ናፍቆሀል ናፍቆኛል
የፋጤ ወፍራም ብና አምሮሀል አምሮኛል
የእቴትዬ ቁጣ ናፋቆሀል አውቃለው
የአዴ ኪሮስ ሽሮም ታይቶሀል አውቃለው
አቤት!አቤት ግን ጊዜ እንዴት ክፉ ነው
ወንድማማችን በዘር የበተነው
ጊዜ እንዴት ክፉ ነው?
ቋንቋ አለመቻል ልጅነት እንጂ
እውነት ግን ወንድምዬ ንቀት ነው
ዝም አትበል ንገረኝ እውነት እንደዛ ነው
የኔስ ነገር እውነት እንዳሉህ ነው
አንቺ ሸዋበር ሆይ የጅማ መርካቶ
አንቺ አራዳ ሆይ ካስፈለገም ቦሳ ኪቶ
ሁሉም ይጠየቁ
እውነት እኛን ካላወቁ
እስቲ ይጠየቁ መፈናቀላችንን ከናፈቁ
ይጨየቁ፣ ጠይቁ
ከናሆም አየለ
ለአብሮ አደጎቼ በሙሉ
@getem
@getem
@gebriel_19
በዛበበጋ በዛበክረምት
ወዳጄ ጠፍቶብኝ ፍለጋ
እውነት ሸሽታኝ ሆናብኝ አንተጋ
ካደግንበት ቀዬ፣ካደግንበት መንደር
ከሀደ ደኑ አድባር፣ከ አባቢያ ሀገር
ከዚያ ወብ ስፍራችን
አባጊዲ እግር ስር
አ፣ባ፣ጫ፣ዳ ስንቆጥር
ተኮ፣ ለማ እያልን ስንቀንስ ስንደምር
ካደግንበት ቀዬ፣ ካሳደገን መንደር
ከአዴ ኪሮስ አድባር፣ከ አያ ፈጠነ ሀገር
እስክስ ያልንበቱ ለአንባሻ ሽልማት
አዴ ከመይ ብለን እንጎቻ ለመብላት
ጨፍቅን አጅበን እልፍ ከብት መንዳት
እሳትዳር ቁጭብለን የስንዝሮን ተረት
መስማት
ትዝ ይልሀል? ትዝይልሀል አይደል ወንድምዬ
የዘመን ጓዴ እኩያዬ
ትዝ ይልሀል አይደል በዛ በበጋ በዛ በክረምት
በልጅነት ስንጫወት
ትዝ ይልሀል ወይ በብይ ስንደባደብ
በሴት ስንተራረብ
በ አሮጊት ፈስ
ስንቧቀስ
ትዝ ይልሀል አይደል ዘይቱን ስንለቅም
ካባ ወርደን ድፋርስ ውሀ ስንዋኝም
ደግሞ ለልደታ አድባር እንዳያኮርፋ
ከሰው ማሳ ፌስታል ብና በህብረት ስንዘርፍ
የእማማ እጅጋየሁን ቦርዴ ስንመጥ
የእትዬ ፀሀይን አነባበሮ ስንገምጥ
ጸግሞ ለጉዞአችን የጅሬንን አቀበት ለመውጣት
የንጉሱን ቤተመንግስት ተሳልሞ ለመምጣት
ተራራ ላይሆነን የጀሚላን ሀገር አጋሮን ለማየት
ቁም አገዳ የዘረፍነው
እልፍ ቃሪያ የነቀልነው
በዛ በበጋ በክረምት
በልጅነት በህብረት ስንጫወት
ከዚያ ካደግንበት ቀዬ፣ካደግንበት መንደር
ከአያ ጨፍቅ ግዛት፣ከሼህ ጀበል ሀገር
ትዝይልህ እንደሆን
ሴት ተናጥቀናል
ከ ጌኑ ጎመን ሰርቀናል
ከሼኪ ፓስቲ ቤት መልስ አጭበርብረናል
ጉርምስና ደርሶብን
አፍላ እድሜ ወጥሮን
ከየም ሰፈር፣ዳውሮ በር
ከአጂፕ፣ሰቃበር
ጫት ፍለጋ ስንዞር
አትረሳውም አይደል ወንድምዬ
አውቃለው መቼም አትረሳውም
ኦሾን ራምፓን አንብበን
ኪቶ ወንዝ ላይ ዮጋ መስራት ሲያምረን
ደግሞ ሙግት ስለ ጃንሆይ ተከራክረን
ስለ ቴድሮስ አብረን አዠነን
ስለ ጂብራን ደም እንባ አልቅሰን
ፐ-በዓሉ ግርማ ኦሮማይ የመፅሀፍ ቁንጮ እያልን
የአቤ አልወለድም እጅጉን ደስ ሲለን
ስለ ጉዱ ካሳ በጣሙን ሲገርመን
ምን አለፍህ
ምን አለፍህ ወንድም አለም የኔ ያንተ
የልጅነት፣የአፍላ ታሪክ እኮ ተወስቶ አያልቅም
መጨረሻው ባያምርልን
ካደግንበት ከኖርንበት ቀዬ
መጥቶ አዲስ ፈሊጥ አዲስ ዘዬ
፦እትብታችን
፦ መንፈሳችን
፦ የልጅነት ትዝታችን ካለበት መንደር
ሰፋሪ ናቹ ተብለን ስንባረር
አውቃለው! አውቃለው ወንድም አለም
ከፍቶሀል፥ከፍቶኛል
የሀደ ጃፈር ፍትፋት ናፍቆሀል ናፍቆኛል
የፋጤ ወፍራም ብና አምሮሀል አምሮኛል
የእቴትዬ ቁጣ ናፋቆሀል አውቃለው
የአዴ ኪሮስ ሽሮም ታይቶሀል አውቃለው
አቤት!አቤት ግን ጊዜ እንዴት ክፉ ነው
ወንድማማችን በዘር የበተነው
ጊዜ እንዴት ክፉ ነው?
ቋንቋ አለመቻል ልጅነት እንጂ
እውነት ግን ወንድምዬ ንቀት ነው
ዝም አትበል ንገረኝ እውነት እንደዛ ነው
የኔስ ነገር እውነት እንዳሉህ ነው
አንቺ ሸዋበር ሆይ የጅማ መርካቶ
አንቺ አራዳ ሆይ ካስፈለገም ቦሳ ኪቶ
ሁሉም ይጠየቁ
እውነት እኛን ካላወቁ
እስቲ ይጠየቁ መፈናቀላችንን ከናፈቁ
ይጨየቁ፣ ጠይቁ
ከናሆም አየለ
ለአብሮ አደጎቼ በሙሉ
@getem
@getem
@gebriel_19
🚪ልዩ የኪነ ጥበብ ምሽት
ያልታመመ አይምሮን እንዴት ማከም ይቻላል?
በ አትዮጵያ ብሄራዊ ቲያትር
ሰኞ ግንቦት 5 / 2011
11:00 ጀምሮ
አዘጋጅ ሰምና ወርቅ ሚዲያ
@tebeb_mereja @getem
@tebeb_mereja @wegoch
ያልታመመ አይምሮን እንዴት ማከም ይቻላል?
በ አትዮጵያ ብሄራዊ ቲያትር
ሰኞ ግንቦት 5 / 2011
11:00 ጀምሮ
አዘጋጅ ሰምና ወርቅ ሚዲያ
@tebeb_mereja @getem
@tebeb_mereja @wegoch
የሰካራሙ ሴራ*
(ቡሩክ ካሳሁን)
ዛሬ
‹‹እድል ከኔ ጋር ነች ኢላማዬ መታ
ለዚ ድንቅ ስኬት እጠጣለሁ ማታ››
ነገ
‹‹አለም ከፈችብኝ ፊቷ በኔ ዞረ
ከማጧ ይወጣል በደንብ የሰከረ
አልኮልኮ ውሀ ነው ጨጓራው ላረረ››
ብሎ እንዳልነበረ
ከንግዲ ምጠጣው በሁለት አጋጣሚ በማለት በየነ
ብለን ሳንጨርስ ‹ይሄ ሰው ሰከነ›
አጋጣሚው ለካ ልደቱ ከሆነ ልደቱ ካልሆነ!
.
ስኬቱ ቢለይም ውድቀቱ ቢለይም
ውጤቱ አንድ ነው የሞላ መለኪያ እያነሱ እልም!
እሱኮ ፅኑ ነው ከጊዜ ለውጥጋ አይቀያየርም፡፡
.
ደግሞ ለሰካራም ሰበብ መቼ ያጣል
ይሄ ግጥም ራሱ ያስጠጣል ያስጠጣል!!
*ሴራ በዚህ አገባብ ተንኮል የሚለውን አቻ ፍቺ ይዞ የሚገኝ ሳይሆን ይልቁንም በልብ-ወለድ፣ በፊልም ድርሰትና በመሳሰሉት አላባ ሆኖ ምናገኘውን ‹ሴራ› ማለትም ምክንያትንና ውጤትን በአንድ ላይ በመያዝ የታሪኩን ቅጥጥል የሚፈጥርልን እንደ ማለት ነው፡፡
@getem
@getem
@burukassahunC
(ቡሩክ ካሳሁን)
ዛሬ
‹‹እድል ከኔ ጋር ነች ኢላማዬ መታ
ለዚ ድንቅ ስኬት እጠጣለሁ ማታ››
ነገ
‹‹አለም ከፈችብኝ ፊቷ በኔ ዞረ
ከማጧ ይወጣል በደንብ የሰከረ
አልኮልኮ ውሀ ነው ጨጓራው ላረረ››
ብሎ እንዳልነበረ
ከንግዲ ምጠጣው በሁለት አጋጣሚ በማለት በየነ
ብለን ሳንጨርስ ‹ይሄ ሰው ሰከነ›
አጋጣሚው ለካ ልደቱ ከሆነ ልደቱ ካልሆነ!
.
ስኬቱ ቢለይም ውድቀቱ ቢለይም
ውጤቱ አንድ ነው የሞላ መለኪያ እያነሱ እልም!
እሱኮ ፅኑ ነው ከጊዜ ለውጥጋ አይቀያየርም፡፡
.
ደግሞ ለሰካራም ሰበብ መቼ ያጣል
ይሄ ግጥም ራሱ ያስጠጣል ያስጠጣል!!
*ሴራ በዚህ አገባብ ተንኮል የሚለውን አቻ ፍቺ ይዞ የሚገኝ ሳይሆን ይልቁንም በልብ-ወለድ፣ በፊልም ድርሰትና በመሳሰሉት አላባ ሆኖ ምናገኘውን ‹ሴራ› ማለትም ምክንያትንና ውጤትን በአንድ ላይ በመያዝ የታሪኩን ቅጥጥል የሚፈጥርልን እንደ ማለት ነው፡፡
@getem
@getem
@burukassahunC
👍1
*ምን አለ ? *
እንካ ሠላምቲያ በምንቲያ ሳትለኝ ቃልህን ሣልወርሰው
መልሴን ተቀምቼ በለምን ጥያቄ እንዴት ልመልሰው
.........................
እንኪ ያለኝ ሁሉ የልብ አውቃ መስሎኝ በምንቲያ የምለው ፣
ለካስ ከኔ ነጥቆ ጥሙ እንዲቆርጥለት መጥለቂያው አርጎኝ ነው
።
....................
አለማወቅ ደጉ መሬት እያስላሰ ነግሰሻል ይለኛል
አላዋቂ እኔ ሺ የማስከትለው መንጋ ያሰኘኛል
....................
ያለማወቅ ህመም ስቃዮን ማን አይቶት
ፈራጅ በበዛበት ቀጪው ባልተለየ በታረዘ ችሎት
......................
ፈራጅ በበዛበት ...
ልክነት ልክ አቷል
ጓራዴው ተቀምጦ ሠገባው ይቆርጣል
እውነት ነው ልክ አቷል
እንዴት ከድህነት ስቃይ ይመረጣል ?
................
ዘወርዋራ አለም እያገላበጠው
መዛኝ ልክ ቢያጣ
እንዴት ፍቅር እያለ ይመለካል ቁጣ ?
..................
እንኩ ሠላምቲያ በምንቲያ አትበሉኝ
አላውቅም ያመኛል
መዳኛዬን ጥሩት ድህነቴን ፈልጉት እሱ ይሻለኛል
............... .....
መዳኛዬን ጥሩት ፈልጉት ያድነኝ
ከራሴ ልታረቅ ሠው መሆን ያክብረኝ
....................
በምን ላለኝ ሁሉ ...
እንኪ ላለኝ ሁሉ በምንታዬን ልቸር
ምን አለ እያልኩኝ የልቤን ልናገር
.............//..............
በሔለን ፋንታሁን
@getem
@getem
@lula_al_greeko
እንካ ሠላምቲያ በምንቲያ ሳትለኝ ቃልህን ሣልወርሰው
መልሴን ተቀምቼ በለምን ጥያቄ እንዴት ልመልሰው
.........................
እንኪ ያለኝ ሁሉ የልብ አውቃ መስሎኝ በምንቲያ የምለው ፣
ለካስ ከኔ ነጥቆ ጥሙ እንዲቆርጥለት መጥለቂያው አርጎኝ ነው
።
....................
አለማወቅ ደጉ መሬት እያስላሰ ነግሰሻል ይለኛል
አላዋቂ እኔ ሺ የማስከትለው መንጋ ያሰኘኛል
....................
ያለማወቅ ህመም ስቃዮን ማን አይቶት
ፈራጅ በበዛበት ቀጪው ባልተለየ በታረዘ ችሎት
......................
ፈራጅ በበዛበት ...
ልክነት ልክ አቷል
ጓራዴው ተቀምጦ ሠገባው ይቆርጣል
እውነት ነው ልክ አቷል
እንዴት ከድህነት ስቃይ ይመረጣል ?
................
ዘወርዋራ አለም እያገላበጠው
መዛኝ ልክ ቢያጣ
እንዴት ፍቅር እያለ ይመለካል ቁጣ ?
..................
እንኩ ሠላምቲያ በምንቲያ አትበሉኝ
አላውቅም ያመኛል
መዳኛዬን ጥሩት ድህነቴን ፈልጉት እሱ ይሻለኛል
............... .....
መዳኛዬን ጥሩት ፈልጉት ያድነኝ
ከራሴ ልታረቅ ሠው መሆን ያክብረኝ
....................
በምን ላለኝ ሁሉ ...
እንኪ ላለኝ ሁሉ በምንታዬን ልቸር
ምን አለ እያልኩኝ የልቤን ልናገር
.............//..............
በሔለን ፋንታሁን
@getem
@getem
@lula_al_greeko
👍1
ተረት ተረት
ድሮ ድሮ
ገዢና ተገዢ
አውራጅ እና ወራጅ
ፈራጅ እና አድማጭ
ሽቅብ እና ቁል ቁል
የሚተያዪባት
ጣሪያ ካስማ የሌላት
ዓለም እንዳበደች
ሌጣዋን ነበረች።
እሺ......
(እሺ ማለት ጥሩ)
ከዚያማ ሲኖሩ
ሲኖሩ..... ሲኖሩ ...
ከለታት ባንድ ዕለት
አላዛር ከበላይ
ባለጠጋው ከታች
እንደተቀመጡ
ባንዲት ጠብታ ውሀ
ተው ስጠኝ አልሰጥም
ክርክር ገጠሙ
(ይሄኔ ፈጣሪ እጅጉን አዘነ
ተከፍቶም አልቀረ
መፍትሄ ወጠነ።
እሺ......
(እሺ ማለት ጥሩ
ከዚያማ
የበላይ የሆነው
በታችኛው ኑሮ
አይቶ እንዳይሳለቅ
የበታች የሆነው
በላይኛው ድሎት
ቀንቶ እንዳይሳቀቅ
እግዜር እጁን ጠልቆ
ከውቅያኖስ ትቢያ
ምድርን ጋረዳት
በሰማይ ወስከምቢያ።
እሺ......
(እሺ ማለት ጥሩ)
ከዚያማ ሲኖሩ
ሲኖሩ..... ሲኖሩ ....
የላዩን ባናቅም
ከታች ግን ባሉ
ትንንሽ እግዜሮች
እንደ አሸን ፈሉ ፈልተውም አልቀሩ
ትንንሽ ሰማያት
ለራሳቸው ሰሩ
እሺ......
(እሺ ማለት ጥሩ
ከዚያማ ሲኖሩ
ሲኖሩ..... ሲኖሩ .....
ገዢና ተገዢ
አውራጅ እና ወራጅ
ፈራጅ እና አድማጭ እንዳይተያዩ
መብራት ያጠፋሉ
አንዳይገናኙ
ስብሰባ ይገባሉ
እንዳይሰማሙ
ቢሮ ይቆልፋሉ።
ዳኒ.B
@getem
@getem
@gebriel_19
ድሮ ድሮ
ገዢና ተገዢ
አውራጅ እና ወራጅ
ፈራጅ እና አድማጭ
ሽቅብ እና ቁል ቁል
የሚተያዪባት
ጣሪያ ካስማ የሌላት
ዓለም እንዳበደች
ሌጣዋን ነበረች።
እሺ......
(እሺ ማለት ጥሩ)
ከዚያማ ሲኖሩ
ሲኖሩ..... ሲኖሩ ...
ከለታት ባንድ ዕለት
አላዛር ከበላይ
ባለጠጋው ከታች
እንደተቀመጡ
ባንዲት ጠብታ ውሀ
ተው ስጠኝ አልሰጥም
ክርክር ገጠሙ
(ይሄኔ ፈጣሪ እጅጉን አዘነ
ተከፍቶም አልቀረ
መፍትሄ ወጠነ።
እሺ......
(እሺ ማለት ጥሩ
ከዚያማ
የበላይ የሆነው
በታችኛው ኑሮ
አይቶ እንዳይሳለቅ
የበታች የሆነው
በላይኛው ድሎት
ቀንቶ እንዳይሳቀቅ
እግዜር እጁን ጠልቆ
ከውቅያኖስ ትቢያ
ምድርን ጋረዳት
በሰማይ ወስከምቢያ።
እሺ......
(እሺ ማለት ጥሩ)
ከዚያማ ሲኖሩ
ሲኖሩ..... ሲኖሩ ....
የላዩን ባናቅም
ከታች ግን ባሉ
ትንንሽ እግዜሮች
እንደ አሸን ፈሉ ፈልተውም አልቀሩ
ትንንሽ ሰማያት
ለራሳቸው ሰሩ
እሺ......
(እሺ ማለት ጥሩ
ከዚያማ ሲኖሩ
ሲኖሩ..... ሲኖሩ .....
ገዢና ተገዢ
አውራጅ እና ወራጅ
ፈራጅ እና አድማጭ እንዳይተያዩ
መብራት ያጠፋሉ
አንዳይገናኙ
ስብሰባ ይገባሉ
እንዳይሰማሙ
ቢሮ ይቆልፋሉ።
ዳኒ.B
@getem
@getem
@gebriel_19
///ማስመሰል///
ያ ሁሉ መታከክ መሸጎጥ ከእቅፋ
የእጆቹ መዘርጋት ፣ሮጦ ማቀፉ
የልቡን ንክሻ ሰውሮ በሸሩ
ስሞ ሲሰናበት ባስመሳይ ከንፈሩ
መግባቢያ ነበረ ይሄ ሁሉ ሴራ
ከ 30 ዲናር ወዳጆቹ ጋራ
የጌታ መከራ የስቃይ መንገዱ
ጥርጊያውን ካገኘ በይሁዳ ጓዱ
በማስመሰል ጅራፍ ጌታውን ለጎዳ
ይነስበት እንዴ ከሰቀሉት መሀል መመደብ ይሁዳ??
ዘንድሮ ዘንድሮ የይሁዳ አንጡር
ተንሰራፍቶ ከትሟል በሁላችን ሰፈር
ሙልጭልታ አንደበት አዳልጤ ሽለላ የፈገግታ ጉጠት የክፍት አተላ
በውስጡ የሞላ ስንቱ አለ ሞልጫፍ
የሳመን ሲመስለን ልክ እንደ ይሁዳ አቅፎ የሚደፍ
በዝህኛው ዘመን ቢመጣ ለሳንሱር
ይሁዳ እራሱ
ከኛ የሚማረው ብዙ ተንኮል ነበር
ግጥም።ምህረት ሻውል(Mሬ)
@getem
@getem
@getem
ያ ሁሉ መታከክ መሸጎጥ ከእቅፋ
የእጆቹ መዘርጋት ፣ሮጦ ማቀፉ
የልቡን ንክሻ ሰውሮ በሸሩ
ስሞ ሲሰናበት ባስመሳይ ከንፈሩ
መግባቢያ ነበረ ይሄ ሁሉ ሴራ
ከ 30 ዲናር ወዳጆቹ ጋራ
የጌታ መከራ የስቃይ መንገዱ
ጥርጊያውን ካገኘ በይሁዳ ጓዱ
በማስመሰል ጅራፍ ጌታውን ለጎዳ
ይነስበት እንዴ ከሰቀሉት መሀል መመደብ ይሁዳ??
ዘንድሮ ዘንድሮ የይሁዳ አንጡር
ተንሰራፍቶ ከትሟል በሁላችን ሰፈር
ሙልጭልታ አንደበት አዳልጤ ሽለላ የፈገግታ ጉጠት የክፍት አተላ
በውስጡ የሞላ ስንቱ አለ ሞልጫፍ
የሳመን ሲመስለን ልክ እንደ ይሁዳ አቅፎ የሚደፍ
በዝህኛው ዘመን ቢመጣ ለሳንሱር
ይሁዳ እራሱ
ከኛ የሚማረው ብዙ ተንኮል ነበር
ግጥም።ምህረት ሻውል(Mሬ)
@getem
@getem
@getem
" ንገሪኝ "
( በአምባዬ ጌታነህ )
ሀገሬ እናቴ እምዬ የምልሽ፣
ስምሽን አስር ጊዜ ጠርቼ ማልጠግብሽ፣
እንደው ለሰላምሽ
ከቶ እንደምን አለሽ!
እኔ እንዳለሁ አለሁ
ስግነት ገምዶኝ
ከገዳይሽ ጋራ ምግብ እየበላሁ።
ደግሞ ከሟች ድንኳን ለእዝን ተቀምጬ፣
በገዳይ ስግነት በሞተው ወንድሜ ቀብር ተረግጬ፣
በዘር ነህ እሳቤ በከፋፍለህ ሴራ፣
ግማሼ ሟች ሆኖ ግማሽ ገዳይ ጋራ
ሳልሞት ተከፍየ እንደ አባት ሰባራ በሄድኩት አፍሬ፣
ከገዳይ ጋ ስስቅ በሟቹ ሳለቅስ እኖራለሁ ሳልኖር በቁም ተቀብሬ።
እንደዛች ሴት ህይወት
"የገደለው ባልሽ፣
የሞተው ወንድምሽ፣
ሀዘንሽ ቅጥ አጣ፣
ከቤትሽ አልወጣ"
እንደተባለላት
እኔም ጉዴ ሁሉ ጓድየ ጋ ሆኖ
መኖር እያስጠላኝ፣
ሞት እየናፈቀኝ፣
እንዳለሁ አለሁኝ።
፡
:
እታተይ ሀገሬ፣
አንቺስ እንደምን ነሽ
ኑሮ እንዴት ይዞሻል፣
ትንሳኤሽ ርቆ ህዝቤን አፋጅቶታል።
ተስፋሽን ሚለኩስ የድል ችቦ ይዞ፣ አንድ ሰው ታጥቷል፣
የጎጥ ነፃ አውጭ እንጅ የአገር ነፃ አውጭ ጠፍቷል።
ንገሪኝ እማየ መቼ ነው 'ሚነጋው፣
ከጥላቻ ወተን በፍቅር ምንኖረው
ንገሪኝ እማየ
እየተራመደ በጥበብ መንገድሽ
ይሄንን የሚያደርግ ፦
ሞተው ከኖሩት ውጪ ሌላ ማን ልጅ አለሽ፣
ንግሪኝ እስኪ ቆይ
መቼ ነው አንድቀን?፣
ምንድን ነው ይነጋል?
በጎጥ ተጨራርሰን፣
ቀየሽ ባዶ ሲሆን?
ን.....ገ.....ሪ.....ኝ!
@getem
@getem
@amba8
( በአምባዬ ጌታነህ )
ሀገሬ እናቴ እምዬ የምልሽ፣
ስምሽን አስር ጊዜ ጠርቼ ማልጠግብሽ፣
እንደው ለሰላምሽ
ከቶ እንደምን አለሽ!
እኔ እንዳለሁ አለሁ
ስግነት ገምዶኝ
ከገዳይሽ ጋራ ምግብ እየበላሁ።
ደግሞ ከሟች ድንኳን ለእዝን ተቀምጬ፣
በገዳይ ስግነት በሞተው ወንድሜ ቀብር ተረግጬ፣
በዘር ነህ እሳቤ በከፋፍለህ ሴራ፣
ግማሼ ሟች ሆኖ ግማሽ ገዳይ ጋራ
ሳልሞት ተከፍየ እንደ አባት ሰባራ በሄድኩት አፍሬ፣
ከገዳይ ጋ ስስቅ በሟቹ ሳለቅስ እኖራለሁ ሳልኖር በቁም ተቀብሬ።
እንደዛች ሴት ህይወት
"የገደለው ባልሽ፣
የሞተው ወንድምሽ፣
ሀዘንሽ ቅጥ አጣ፣
ከቤትሽ አልወጣ"
እንደተባለላት
እኔም ጉዴ ሁሉ ጓድየ ጋ ሆኖ
መኖር እያስጠላኝ፣
ሞት እየናፈቀኝ፣
እንዳለሁ አለሁኝ።
፡
:
እታተይ ሀገሬ፣
አንቺስ እንደምን ነሽ
ኑሮ እንዴት ይዞሻል፣
ትንሳኤሽ ርቆ ህዝቤን አፋጅቶታል።
ተስፋሽን ሚለኩስ የድል ችቦ ይዞ፣ አንድ ሰው ታጥቷል፣
የጎጥ ነፃ አውጭ እንጅ የአገር ነፃ አውጭ ጠፍቷል።
ንገሪኝ እማየ መቼ ነው 'ሚነጋው፣
ከጥላቻ ወተን በፍቅር ምንኖረው
ንገሪኝ እማየ
እየተራመደ በጥበብ መንገድሽ
ይሄንን የሚያደርግ ፦
ሞተው ከኖሩት ውጪ ሌላ ማን ልጅ አለሽ፣
ንግሪኝ እስኪ ቆይ
መቼ ነው አንድቀን?፣
ምንድን ነው ይነጋል?
በጎጥ ተጨራርሰን፣
ቀየሽ ባዶ ሲሆን?
ን.....ገ.....ሪ.....ኝ!
@getem
@getem
@amba8
Jeremiah:
ዉድ ቤተሰቦች እንደምን ቆያችሁ?
የፈጠረን አምላክ ከሰጠን እጅግ ብዙ መልካም ነገሮች መካከል የምንተነፍሰዉ አየር እጅግ የላቀ ዋጋ ያለው ይመስለኛል፣
ይሄን አየር በነፃነት እየተነፈሱ መኖር ደሞ እንዴት መታደል ነው!
የዚህን ጥቅም ለመረዳት ለ20 ሰከንድ መተንፈስ በማንችልበት ሁኔታ ውስጥ መሆን ብቻ በቂ ነው፡፡ እኛ ለሰከንዶች የሚከብደንን ነገር ሰዎች እየኖሩት ቢሆንስ??
ለዚህም ነው እህታችን ስመኝሽን መተዋወቅ ያስፈለገን፣ ስመኝሽ ለሰዓታት እንኳን ተፈጥሮ የቸረንን አየር በነፃነት እንድትተነፍስ
ሣንባዋ አልፈቀደላትም
ሁለቱም ሣንባዋቻ ከጥቅም ውጪ
በመሆናቸው ምክንያት በየጊዜዉ በሚሞላ የታመቀ ኦክስጅን
(oxygen bottle) እየተነፈሰች ዘወትር ከ አልጋዋ
ሣትርቅ ለመኖር ተገድዳለች፡፡
በዚህ ሁኔታ ውስጥ በመሆኗ መስራት አትችልም ፣መማር አትችልም ፣ የ 8 አመት ሴት ልጇን እንደ ማንኛውም እናት ምግብ
ልትቋጥርላት ቀርቶ ወደ ት/ቤት እንኳን
መሸኘት ተስኗታል፡፡
"እንደው ምን እንረዳሽ ዘንድ ትፈልጊያለሽ? "ብለን ስንጠይቃት
"የምትችሉትን ብቻ አድርጉልኝ በተለይ በተለይ ግን የራበኝ ሰው ነው ሰው ያስፈልገኛልና እባካችሁ ከጎንሽ ነኝ በሉኝ
ከልጄም አትራቁብኝ" ነበር ያለችው
እናም በመጪው እሁድ ስመኝሽ ቤቷ ቡና እንደምታፈላ እና ሰዉ ሁሉ እነዲጋበዝላት ትፈልጋለች እናም ለ ስመኝሽን እኔም ከጎንሽ ነኝ ማለት የፈለገ ሁሉ እሁድ ትጠብቀናለችና ሄደን የምንችለውን ሁሉ እነደርግ ዘንድ የመልካም በጎ ፈቃደኛ ቤተሰብ ጥሪ ነው፡፡
ዋጋ ያላት ነፍስ ለሌሎች የኖረችዋ ነች፡፡
የምንገናኘው፡ መገናኛ ሸዋ ሱፐር ማርኬት
ሰዓት፡ 2፡30
ለበለጠ መረጃ -0938753747
0912888649
Telegram a- @heny10 or @Ermiasgech
@getem
@wegoch
ዉድ ቤተሰቦች እንደምን ቆያችሁ?
የፈጠረን አምላክ ከሰጠን እጅግ ብዙ መልካም ነገሮች መካከል የምንተነፍሰዉ አየር እጅግ የላቀ ዋጋ ያለው ይመስለኛል፣
ይሄን አየር በነፃነት እየተነፈሱ መኖር ደሞ እንዴት መታደል ነው!
የዚህን ጥቅም ለመረዳት ለ20 ሰከንድ መተንፈስ በማንችልበት ሁኔታ ውስጥ መሆን ብቻ በቂ ነው፡፡ እኛ ለሰከንዶች የሚከብደንን ነገር ሰዎች እየኖሩት ቢሆንስ??
ለዚህም ነው እህታችን ስመኝሽን መተዋወቅ ያስፈለገን፣ ስመኝሽ ለሰዓታት እንኳን ተፈጥሮ የቸረንን አየር በነፃነት እንድትተነፍስ
ሣንባዋ አልፈቀደላትም
ሁለቱም ሣንባዋቻ ከጥቅም ውጪ
በመሆናቸው ምክንያት በየጊዜዉ በሚሞላ የታመቀ ኦክስጅን
(oxygen bottle) እየተነፈሰች ዘወትር ከ አልጋዋ
ሣትርቅ ለመኖር ተገድዳለች፡፡
በዚህ ሁኔታ ውስጥ በመሆኗ መስራት አትችልም ፣መማር አትችልም ፣ የ 8 አመት ሴት ልጇን እንደ ማንኛውም እናት ምግብ
ልትቋጥርላት ቀርቶ ወደ ት/ቤት እንኳን
መሸኘት ተስኗታል፡፡
"እንደው ምን እንረዳሽ ዘንድ ትፈልጊያለሽ? "ብለን ስንጠይቃት
"የምትችሉትን ብቻ አድርጉልኝ በተለይ በተለይ ግን የራበኝ ሰው ነው ሰው ያስፈልገኛልና እባካችሁ ከጎንሽ ነኝ በሉኝ
ከልጄም አትራቁብኝ" ነበር ያለችው
እናም በመጪው እሁድ ስመኝሽ ቤቷ ቡና እንደምታፈላ እና ሰዉ ሁሉ እነዲጋበዝላት ትፈልጋለች እናም ለ ስመኝሽን እኔም ከጎንሽ ነኝ ማለት የፈለገ ሁሉ እሁድ ትጠብቀናለችና ሄደን የምንችለውን ሁሉ እነደርግ ዘንድ የመልካም በጎ ፈቃደኛ ቤተሰብ ጥሪ ነው፡፡
ዋጋ ያላት ነፍስ ለሌሎች የኖረችዋ ነች፡፡
የምንገናኘው፡ መገናኛ ሸዋ ሱፐር ማርኬት
ሰዓት፡ 2፡30
ለበለጠ መረጃ -0938753747
0912888649
Telegram a- @heny10 or @Ermiasgech
@getem
@wegoch
አ- በ- ው
-------------------------
(ከናሆም አየለ)
ተረትን ከምሳሌ እየደባለቁት
እያንዳንዷን ቅፅበት እያንዳንዷን ሁነት
በአንዲት ሀረግ አስረው
ትንሿን ገጠመኝ ትልቁን መከራ
በቃል አቅለውት ሲያደርጉት ተራ
ደግሞ አክብደውት ሲካብ እንደጋራ
ይሉሀል አበው
ስር ስርህ እያሉ ተረብ ነው ዘዬ'ቸው
------------------
ትላንት
ስትሰጪኝ- ስገፋ
ስትፈልጊኝ-ስሸሽ
ስትለሚብኝ-ስከፋብሽ
አንድያ ልብሽን ወንድ ያላወቃትን
ብቸኛ ፋቅርን ላንተ ብቻ ያልሻትን
ስንቅ ሳጣጥላት
ስገፋ ሳርቃት
አበው አይተው ድንገት
በእጅ የያዙት ወርቅ ብለው ያሉኝ እለት
የምን ወርቅ አመጡ
ይልቅስ ያድምጡ
ዘመድ ከዘመዱ
አህያም ካመዱ
እንዲኖር ግድ ነው
ለኔ አትገባኝም ብጤዋን ትፈልግ
እኔ ከሷ ልሆን? እኮ እንዴት ሲደረግ
ይህ ነበር መልሴ
ኩራት ያሳበጣት ተላላዋን ነብሴን አደብ አስገዝቼ
ቦታሽን እኔ ውስጥ ስፈልግ ቆይቼ
ብመለስ አንቺ ጋር
ሆነሽ ከእከሌ ጋር
ያገኘውሽ እለት
አበው እደለመዱት
ተረት ከምሳሌን እየደባለቁት
ላለፈ ክረምት ብለውኝ አረፉት፡፡
@getem
@getem
@gebriel_19
-------------------------
(ከናሆም አየለ)
ተረትን ከምሳሌ እየደባለቁት
እያንዳንዷን ቅፅበት እያንዳንዷን ሁነት
በአንዲት ሀረግ አስረው
ትንሿን ገጠመኝ ትልቁን መከራ
በቃል አቅለውት ሲያደርጉት ተራ
ደግሞ አክብደውት ሲካብ እንደጋራ
ይሉሀል አበው
ስር ስርህ እያሉ ተረብ ነው ዘዬ'ቸው
------------------
ትላንት
ስትሰጪኝ- ስገፋ
ስትፈልጊኝ-ስሸሽ
ስትለሚብኝ-ስከፋብሽ
አንድያ ልብሽን ወንድ ያላወቃትን
ብቸኛ ፋቅርን ላንተ ብቻ ያልሻትን
ስንቅ ሳጣጥላት
ስገፋ ሳርቃት
አበው አይተው ድንገት
በእጅ የያዙት ወርቅ ብለው ያሉኝ እለት
የምን ወርቅ አመጡ
ይልቅስ ያድምጡ
ዘመድ ከዘመዱ
አህያም ካመዱ
እንዲኖር ግድ ነው
ለኔ አትገባኝም ብጤዋን ትፈልግ
እኔ ከሷ ልሆን? እኮ እንዴት ሲደረግ
ይህ ነበር መልሴ
ኩራት ያሳበጣት ተላላዋን ነብሴን አደብ አስገዝቼ
ቦታሽን እኔ ውስጥ ስፈልግ ቆይቼ
ብመለስ አንቺ ጋር
ሆነሽ ከእከሌ ጋር
ያገኘውሽ እለት
አበው እደለመዱት
ተረት ከምሳሌን እየደባለቁት
ላለፈ ክረምት ብለውኝ አረፉት፡፡
@getem
@getem
@gebriel_19
እምነት?
(ቡሩክ ካሳሁን)
አሀዱ አሀዱ
ከህጎቹ ቀደምት ከወግ ከልማዱ
ላልገደፈ ፃድቅ ላላለፈ ወጣት
ምንድነው ትርጉሙ ሲኦል ቅጣት ሀጥያት?
ሲዘልል ለኖረስ ሲጠጣ ሲዘሙት
ህጎቹን ለጣሰ በርትቶ እስኪሞት
ምን ግድ ይሰጠዋል ገነት ብትኖር ብትቀር
አለች ብሎ ማመን ምን ጠብ ሊያረግለት ከመጎምጀት በቀር?
ከዚህ በመነሳት አንዳንዶች ዋለሉ
‹እምነት እውነት ሳይሆን
ከራስ መታረቂያ ድልድይ ነው› እያሉ፡፡
@getem
@getem
@burukassahunC
(ቡሩክ ካሳሁን)
አሀዱ አሀዱ
ከህጎቹ ቀደምት ከወግ ከልማዱ
ላልገደፈ ፃድቅ ላላለፈ ወጣት
ምንድነው ትርጉሙ ሲኦል ቅጣት ሀጥያት?
ሲዘልል ለኖረስ ሲጠጣ ሲዘሙት
ህጎቹን ለጣሰ በርትቶ እስኪሞት
ምን ግድ ይሰጠዋል ገነት ብትኖር ብትቀር
አለች ብሎ ማመን ምን ጠብ ሊያረግለት ከመጎምጀት በቀር?
ከዚህ በመነሳት አንዳንዶች ዋለሉ
‹እምነት እውነት ሳይሆን
ከራስ መታረቂያ ድልድይ ነው› እያሉ፡፡
@getem
@getem
@burukassahunC
ሀያል ፍቅር
(ቡሩክ ካሳሁን)
ጥንቸሉ በኤሊው ኤሊው በጥንቸሉ
ከገደል በሰፋው ፍቅር ወድቀው ሳሉ
አንዱ ለአንደኛው እራሱን ለወጠ
ጥንቸሉ ሲያዘግም ኤሊው እየሮጠ!
@getem
@getem
@burukassahunC
(ቡሩክ ካሳሁን)
ጥንቸሉ በኤሊው ኤሊው በጥንቸሉ
ከገደል በሰፋው ፍቅር ወድቀው ሳሉ
አንዱ ለአንደኛው እራሱን ለወጠ
ጥንቸሉ ሲያዘግም ኤሊው እየሮጠ!
@getem
@getem
@burukassahunC