የአብስራ ሳሙኤል
ማንበብ ቢሳነን እንጂ
ቅንጣት እውነት መች ይጠፋል?
ህይወት በምድር ገጽ ላይ
ገጸ ሰቡን ማልዶ ይጽፋል.
▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔▔
፩
አሁን አሁን ያለፈችው
ቆንጅዬ ወጣት —
የእንባ ካፍያ፣ ያ'ረጠበው
ጉንጯ መንጣት.
ንስንስ ጸጉሯ ያዘለው
የግንጥል አበባ ገላ፣
ዝም ብላን ያለፈች
እንዲያው እንዲሁ... ዝም ብላ!
ልቡሰ ህሊናው ለመራው
ስውር እውነት እዚህ ይገኛል!
እንዲህ እንዲህ ይለኛል —
❛❛አለመንኩም ብዙ ነገር
አልማለድኩም ምቾት ድሎት፣
መገፋት ላሳሳት ነፍሴ
ለ'ልቧ ልቤን ልሰጣት፣
የልጅነት ትኩስ ህልሜን
ተይ ስላሉኝ መች ቀጨሁት?
ሰው አይደለሁ ተመኘሁት.
እንዲህ እንዲህ በቃል ቢሉት
አይገባውም ያልቀመሰ፣
ለፍቅር ጎኑን ብጠጋው
የፍትወት ፍሙን ለበሰ።
ወንድ እንዲህ ነው አልልህም፣
እሱ ግን እንዲህ ነበረ —
ወድጄ ክብሬን ብሰጠው
የማፍቀር ቅስሜን ሰበረ.
የአበባ ጉንጉን አንጥፎ
በመባው ማሳ ደፈረኝ...
ፈቅጄ ከተኛ'ሁለት;
ከእንግዲህ እውነት ምን ቀረኝ❜❜?
፪
ደሞ ከሷ፣ አሁን አሁን
ካለፈችው ወጣት እግር ስር፣
የነበረች የኔ ቢጤ
ምስኪን ለማኝ፣
ነጠላዋን ለጎዳናው ያነጠፈች፣
እንደ ጤዛ በማለዳው የረገፈች።
ምኞት ህልሟን ምስጥ
የበላው የእግሮቿን ስር፣
ልቡሰ ልቦናህን አንቃው፣
እዚህም እውነት አይጠፋም!
ክብርን በዲናር ከመቸርቸር
መለመን እንዴት አይከፋም?
እንዲህ እንዲህ ትለኛለች
❛❛ይጸድቃሉ በመስጠት፣
ውስጥ ማግኘት አለ!"
ሰው በደለኝ አልልህም፤
የጊዜ እንጂ የሰው ጌታ
ወዴት አለ?
የማውቀው ሰው፦
የሚሰጥም፣ የሚነሳም፣
የሚጥልም፣ የሚያነሳም❜❜።
፫
ደሞ ደሞ
ከሚስኪኗ የኔ ቢጤ ከአይኗ ሳያርቅ
ለጋ እድሜውን በጎዳና የሚቦርቅ፣
አፍ ሲፈታ "የዳቦ አለህ?"
የሚል ቃላት የቀመሰ፣
ለእግሩ ጠጠር ..
ለሌሊቱ ቁር ንፋስ ያንተራሰ።
አዲስ ትውልድ! አዲስ ሀገር!
አዲስ ታሪክ የሚናገር፣
❛❛በዚህ በጎዳና፦
ከሚያልፍ፣ ከሚመጣው፣
ከሚመላለሰው፣
ከመንገደኛው ሰው —
ሁሉም የግሉ ድብቅ እውነት አለው!
የሚያነጣጥለው፣
የሚያመሳሰለው።
ከመልኩ ገጽ ላይ
ተመልከት ሀዘኑን አስተውል ደስታውን፤
ቢተራመስ እንጂ
ማንም አያውቀውም
መድረሻ ቦታውን።
አልፎ፣ ሂያጅ መንገደኛ ነው
የሰው ልጅ በዚች ምድር —
ከልቦናው መቅረዝ በእኩል
ተስፋ ምኞት የሚያሳድር!
እናም እኔ፦
የማውቀው ሰው፦
**የሚሰጥም፣ የሚነሳም፣
የሚጥልም፣ የሚያነሳም❜❜።
@getem
@getem
@getem
❤35👍5
ይህ ቀዥቃዣ ዝናብ - ገላሽን ይንካና
ወዮለት ሰማዩ - ወዮለት ደመና !
ወፍ አይዘምርልሽ - ዛፍ አያስጠልልሽ
በቃ እኔ አለሁልሽ !
ደግሞ ይሄን እወቂ !
ሆዴ እንደሚበላኝ ፥ ካለኔ ስትስቂ
እንቅልፍ እንደማጣ ፥ በፀሐይ ስትፈኪ
ምራቄ እንደሚመር ፥ በእግዜር ስትመኪ !
እኔ ነኝ ጠባቂሽ !
እኔ ደስታሽ !
እኔ ፈገግታሽ !
ሁሉንም የምሆን ... !
እግዜር ፥ አላህ ፥ ሰማይ
ንፋስ ፥ ውሃ ፥ ድንጋይ
ያንቺ ብቻ አገልጋይ !
ያንቺ ብቻ ታጋይ !
"ክነፍ !" በዪኝ - ልክነፍ
"እረፍ !" በዪኝ - ልረፍ
ብቻ ደስታሽ ሁሉ ፥ በእኔ በኩል ይለፍ !!!
by Habtamu hadera
@getem
@getem
@paappii
ወዮለት ሰማዩ - ወዮለት ደመና !
ወፍ አይዘምርልሽ - ዛፍ አያስጠልልሽ
በቃ እኔ አለሁልሽ !
ደግሞ ይሄን እወቂ !
ሆዴ እንደሚበላኝ ፥ ካለኔ ስትስቂ
እንቅልፍ እንደማጣ ፥ በፀሐይ ስትፈኪ
ምራቄ እንደሚመር ፥ በእግዜር ስትመኪ !
እኔ ነኝ ጠባቂሽ !
እኔ ደስታሽ !
እኔ ፈገግታሽ !
ሁሉንም የምሆን ... !
እግዜር ፥ አላህ ፥ ሰማይ
ንፋስ ፥ ውሃ ፥ ድንጋይ
ያንቺ ብቻ አገልጋይ !
ያንቺ ብቻ ታጋይ !
"ክነፍ !" በዪኝ - ልክነፍ
"እረፍ !" በዪኝ - ልረፍ
ብቻ ደስታሽ ሁሉ ፥ በእኔ በኩል ይለፍ !!!
by Habtamu hadera
@getem
@getem
@paappii
❤58👎12🤩9👍7😁5😱5🔥4🎉2
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
ኖሮ ማለፍ ብቻ አይደለም የህይወቴ ጥግጋቱ
በሀብት በዕቁባት አይለካም የዐላማዬ ጽናቱ
ቁና ባይሞላ ከቁብ፣ ከእፍኝ ባይቆጠር
የድርሻዬን ልጣል ጠጠር...
የድርሻዬን ላዋጣላት
ሀገሬኮ ማንም የላት!
***
እንዲህ እንዲህ፣ በዚህ በዚህ
በየጎዳናው ላይ
ደም እንደ ወራጅ ውሀ በሚገበርበት
ሀዘን እሮሮ'ችን
እንባችን በዝናብ በሚታበስበት
ሰቂቃና ሰቆቃ ባደቀቃት ሀገር
መኖር ብቻ አይበቃም
***
በዘመን ድልድይ ላይ ኦናነት ማሻገር
የድርሻዬን መንገድ ልያዝ
የድርሻዬን ፋና ልቅደድ
ቀጣይ ትውልድ ተተክቶኝ
ወደሚሻው እንዲራመድ ...
***
ስብከት መሰል አይደል?
ድሮም እውነት ይሰለቻል
ያልገነቡት ሀገር ማውረስ
ለቀብር መች ይመቻል?
ብቻ ብቻ፣ እንዲሁ ማለፍ እፈራለሁ!
"ምን ሰራህ?" ይለኛል ነፍሴ
ከጥገትሽ ጠብቶ ባይጸናም
"አለሁሽ!" ይላል መንፈሴ
"አልደላሺኝም ለኔም !
ሳር ቅጠልሽ መቼ ጣመኝ?
እንዴት ትቼ ልተውሽ?
ህመምሽ ሰርክ እያመመኝ!"
***
እማ እማ እናት አለም...
ኖሮ ማለፍ ጀብድ አይደለም!
ጀንበርን በስካር እየተደበቁ
ከየጎዳናው ላይ ቢነሱ፣ ቢወድቁ...
***
ታሪክ አያድስም፣ ዘመን አያቀናም
ወዝ ያልፈሰሰበት በምኞት አይጸናም
ጥቂት ጠጠር እናዋጣ እፍኝ መባ እንገብራት
ከእኛ ሌላ፣..ሀገሬኮ ማንም የላት!
@getem
@getem
@getem
❤21🔥3
ጥያቄ??
አሁን በእኛ ዘመን ፍቅር የምንለዉ፤
በቅዱስ መፅሐፍ ሠርክ የምናነበዉ፤
ካፋችን ማይጠፋ ቀን በቀን ምንጠራዉ፤
ፍቺዉ የጠፋብን ፍቅር ግን ምንድነዉ??
..................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
አሁን በእኛ ዘመን ፍቅር የምንለዉ፤
በቅዱስ መፅሐፍ ሠርክ የምናነበዉ፤
ካፋችን ማይጠፋ ቀን በቀን ምንጠራዉ፤
ፍቺዉ የጠፋብን ፍቅር ግን ምንድነዉ??
..................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤35👍7🔥4
መንገደኛው ልቤ ቅጽበት'ዓት ከአንቺ ያደረ
መሄድ አመል ሆኖበት ደሞ ሌላ አፈቀረ
ደሞ ከሌላ አደረ አዲስ ምዕራፍ ተጀመረ
‧˚‧༘
ቀን ያሻገረኝ ዛጎሌን ጥዬ
ሁሉም እንዳንቺ አይደለም ብዬ
ነፍሴን ላጽናናት ወይ ልደልላት
ናፍቆት ትዝታው ይበቃል ስላት
༄
ተቀበለቺኝ
❛❛ይሁና አለቺኝ❜❜
በል ሂድ እንግዲ...
⸻
#ከአዲስ መስክ ላይ
ልዬ የሆነ ብስራት አይጠፋም
ከንፎ መሰበር ሮጦ መውደቅ
ህልምን ከመስበር ፍጹም አይከፋም
✨
ደሞ ወደ አዲስ ጠረን
ደሞ ወደ አዲስ ገላ
ይሁን ብላ ህይወት ስታባብለኝ
⸻•⸻
ይኀው ደሞ ትዝ አለኝ
ተሳሰረብኝ እግሬ
በአንቺም ጊዜ አኮብኩቧል
ክንፎቹን ልክ እንደ ዛሬ
💧
ትዝ አለሽ ያኔ?
በሀዘን በእንባ የተማጸንኩሽ
የበደሌ ስር ቅሉ ሳይገባኝ
ይቅርታ ያልኩሽ
🕯
ገፍተሽ መሄድሽ
ብቻዬን ስሆን ዛሬም ያመኛል
አንዴ የቆሰለ ማደሪያስ
ቢያገኝ መች አምኖ ይተኛል?
✨
ግና ፍቅሬ...
ቢሆንም ባይሆንም
ክንፋም ህልሞች እንጂ
ጨለማ አልለምንም
ትሏ ህይወቴ
በጀንበር ብስራት ክንፍ ያበቀለ
☾
ሁሉም እንዳንቺ አይደለም ያለ
ደሞ ሌላ አፈቀረ
አዲስ ምዕራፍ ተጀመረ
𓇢
አንድ አይኑን ለመንገድ ገልጦ
ከሌላ ልቡ ውስጥ አደረ...
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
መሄድ አመል ሆኖበት ደሞ ሌላ አፈቀረ
ደሞ ከሌላ አደረ አዲስ ምዕራፍ ተጀመረ
‧˚‧༘
ቀን ያሻገረኝ ዛጎሌን ጥዬ
ሁሉም እንዳንቺ አይደለም ብዬ
ነፍሴን ላጽናናት ወይ ልደልላት
ናፍቆት ትዝታው ይበቃል ስላት
༄
ተቀበለቺኝ
❛❛ይሁና አለቺኝ❜❜
በል ሂድ እንግዲ...
⸻
#ከአዲስ መስክ ላይ
ልዬ የሆነ ብስራት አይጠፋም
ከንፎ መሰበር ሮጦ መውደቅ
ህልምን ከመስበር ፍጹም አይከፋም
✨
ደሞ ወደ አዲስ ጠረን
ደሞ ወደ አዲስ ገላ
ይሁን ብላ ህይወት ስታባብለኝ
⸻•⸻
ይኀው ደሞ ትዝ አለኝ
ተሳሰረብኝ እግሬ
በአንቺም ጊዜ አኮብኩቧል
ክንፎቹን ልክ እንደ ዛሬ
💧
ትዝ አለሽ ያኔ?
በሀዘን በእንባ የተማጸንኩሽ
የበደሌ ስር ቅሉ ሳይገባኝ
ይቅርታ ያልኩሽ
🕯
ገፍተሽ መሄድሽ
ብቻዬን ስሆን ዛሬም ያመኛል
አንዴ የቆሰለ ማደሪያስ
ቢያገኝ መች አምኖ ይተኛል?
✨
ግና ፍቅሬ...
ቢሆንም ባይሆንም
ክንፋም ህልሞች እንጂ
ጨለማ አልለምንም
ትሏ ህይወቴ
በጀንበር ብስራት ክንፍ ያበቀለ
☾
ሁሉም እንዳንቺ አይደለም ያለ
ደሞ ሌላ አፈቀረ
አዲስ ምዕራፍ ተጀመረ
𓇢
አንድ አይኑን ለመንገድ ገልጦ
ከሌላ ልቡ ውስጥ አደረ...
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
❤18👍14😱2
(በዕምዓዕላፍ)
ወደ ውስጥ ፈሶ
ወደ ውስጥ አልቅሶ
መሬት ሳትረሰርስ
እምባውን ጨርሶ
ይሆናል እያልኩኝ በመላምት ተስፋ
ምኞት ላያፀናኝ ነፍሴ ተቀስፋ
የልቤ መናወዝ
የኔ መንጠራወዝ
ስለ አንቺ ነበረ
ፍቅርሽ መስቀል ሆኖ የተቸነከረ
በጠባብ ማነቆ ቀንበር ተሸክሜ
የፍቅርን መቀነት በተስፋ አገልድሜ
ከእድሜ
ቀድሜ
እንሆ አሰስኩሽ.......
ለዘመናት ባጀሁ
አመታትን ፈጀሁ
አንጋጥጬ እያዬሁ የማይወርድ መና
ሰማዩን ከልሎት የማይዘንብ ደመና
እያዬሁ ሳላምን
እግዜርን ስለምን
እኔ ወበከንቱ
የትም ቀረሁ እቱ
@getem
@getem
@getem
ወደ ውስጥ ፈሶ
ወደ ውስጥ አልቅሶ
መሬት ሳትረሰርስ
እምባውን ጨርሶ
ይሆናል እያልኩኝ በመላምት ተስፋ
ምኞት ላያፀናኝ ነፍሴ ተቀስፋ
የልቤ መናወዝ
የኔ መንጠራወዝ
ስለ አንቺ ነበረ
ፍቅርሽ መስቀል ሆኖ የተቸነከረ
በጠባብ ማነቆ ቀንበር ተሸክሜ
የፍቅርን መቀነት በተስፋ አገልድሜ
ከእድሜ
ቀድሜ
እንሆ አሰስኩሽ.......
ለዘመናት ባጀሁ
አመታትን ፈጀሁ
አንጋጥጬ እያዬሁ የማይወርድ መና
ሰማዩን ከልሎት የማይዘንብ ደመና
እያዬሁ ሳላምን
እግዜርን ስለምን
እኔ ወበከንቱ
የትም ቀረሁ እቱ
@getem
@getem
@getem
👍38❤29🔥2😢2🎉1
የማርያም መንገድ
.
.
መንፈሴ ሲዝል ሰላሜ ጠፍቶ፤
ልቤ ሲታወክ ዉስጤ ተረትቶ፤
ቢጨንቀኝ ጊዜ........
አጥብቄ ለመንኩ የማርያም መንገድ፤
ካለሁበት ማጥ ያሻግረኝ ዘንድ።
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
መንፈሴ ሲዝል ሰላሜ ጠፍቶ፤
ልቤ ሲታወክ ዉስጤ ተረትቶ፤
ቢጨንቀኝ ጊዜ........
አጥብቄ ለመንኩ የማርያም መንገድ፤
ካለሁበት ማጥ ያሻግረኝ ዘንድ።
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤49🔥6👍4
ኤሊና ጥንቸል ተቀጣጠሩ
ማራቶን ሩጫ ሊወዳደሩ።
የውድድሩ ሲያበቃ ሩጫ
እስቲ ገምቱ የማነው ዋንጫ?
— አዝማሪው —
በብላቴና ዕድሜዬ ስለ ህይወት ሲቀኙልኝ
ኤሊም ሆኜ እንድ'ቀድም
ጥንቸሎቼን አስተኙልኝ
መኖር መልካም ቀና ጥበብ የምትሻ
አሁን ባይገባንም
ትርጉም አይታጣም በስተ'መጨረሻ
፩
አየሽ በዚህ ተረት መኖር እንዲህ ይቀኛል
ሸክም ያልከው ዛጎል ጌጥህ ነው ይለኛል
አልችልም ካልክበት
አበቃ ካልክበት
ደሞ በአዲስ ፈና መንገድህን ቀጥል
የናቁት ጠጠር ነው ግዙፉን የሚጥል
ያቅተኛል ብለህ
ይከብደኛል ብለህ
በፍጹም አትፍራ።
ነበልባል ህልምህን
በእንቅልፋም ልቧች ላይ
ጎጆ አድርገህ ስራ።
ልቦናው የበራለት ከትልም ይማራል
ባሪያ ብለው የናቁት በጊዜው ይከብራል
አትፍራ! ግድየለም!
ሰጋር እግሩን አይተህ
❛❛አልቀድመውም አትበል❜❜
የኑሮን ውርርድ ሳትታክት ተቀበል
#ህይወት ጥበበኛው
መልካም ቅኔ አያጣም
ላሸነፈው ዋንጫ
ለደከመው ደሞ እንቅልፍ አይታጣም።
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
ማራቶን ሩጫ ሊወዳደሩ።
የውድድሩ ሲያበቃ ሩጫ
እስቲ ገምቱ የማነው ዋንጫ?
— አዝማሪው —
በብላቴና ዕድሜዬ ስለ ህይወት ሲቀኙልኝ
ኤሊም ሆኜ እንድ'ቀድም
ጥንቸሎቼን አስተኙልኝ
መኖር መልካም ቀና ጥበብ የምትሻ
አሁን ባይገባንም
ትርጉም አይታጣም በስተ'መጨረሻ
፩
አየሽ በዚህ ተረት መኖር እንዲህ ይቀኛል
ሸክም ያልከው ዛጎል ጌጥህ ነው ይለኛል
አልችልም ካልክበት
አበቃ ካልክበት
ደሞ በአዲስ ፈና መንገድህን ቀጥል
የናቁት ጠጠር ነው ግዙፉን የሚጥል
ያቅተኛል ብለህ
ይከብደኛል ብለህ
በፍጹም አትፍራ።
ነበልባል ህልምህን
በእንቅልፋም ልቧች ላይ
ጎጆ አድርገህ ስራ።
ልቦናው የበራለት ከትልም ይማራል
ባሪያ ብለው የናቁት በጊዜው ይከብራል
አትፍራ! ግድየለም!
ሰጋር እግሩን አይተህ
❛❛አልቀድመውም አትበል❜❜
የኑሮን ውርርድ ሳትታክት ተቀበል
#ህይወት ጥበበኛው
መልካም ቅኔ አያጣም
ላሸነፈው ዋንጫ
ለደከመው ደሞ እንቅልፍ አይታጣም።
የአብስራ ሳሙኤል
@getem
@getem
@getem
❤44👍9🔥3
አብሮ መጥፋት
በፍቅር ሰንሰለት እኔን ላንቺ ድሮ፣
ያለፈ ታሪክሽን
የኀጢአቴን ግርሻት ሊያጠፋ ቀን ቀጥሮ፤
"ወደ ኋላ መዞር ላ'ፍታ ሳትመኙ፣
ወደ ፊት ተጓዙ ነጋችሁን ቃኙ!
ለፍቅር ታመኑ ለፍቅር ተቀኙ!"
የሚል ትእዛዝ ሰጥቶን
ትናንትናችን ላይ እቶን እሳት ቢለቅ፣
ወላዋይ መንፈስሽ
ልክ እንደ ሎጥ ሚስት ታየ ሲፍረከረክ፡፡
የቀድሞ ፍቅረኛሽ…
ያ ሁሉ ትዝታ
መጥፋት አብከንክኖሽ በድንገት ስትዞሪ፣
የጨው ሐውልት ግግር
አድርጎ ቢያስቀርሽ የፍጥረት ፈጣሪ፤
ሎጥን ልምሰል ብዬ…
የፍቅርሽ እርምጃ
ከኋላዬ ሲቀር ወደ ፊት አልሄድም፣
አይቼሽ ለማልቀስ
አይቼሽ ለመድረቅ
ያ'ምላኬን ቃል ሽሬ መዞሬ አይቀርም፡፡
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@getem
በፍቅር ሰንሰለት እኔን ላንቺ ድሮ፣
ያለፈ ታሪክሽን
የኀጢአቴን ግርሻት ሊያጠፋ ቀን ቀጥሮ፤
"ወደ ኋላ መዞር ላ'ፍታ ሳትመኙ፣
ወደ ፊት ተጓዙ ነጋችሁን ቃኙ!
ለፍቅር ታመኑ ለፍቅር ተቀኙ!"
የሚል ትእዛዝ ሰጥቶን
ትናንትናችን ላይ እቶን እሳት ቢለቅ፣
ወላዋይ መንፈስሽ
ልክ እንደ ሎጥ ሚስት ታየ ሲፍረከረክ፡፡
የቀድሞ ፍቅረኛሽ…
ያ ሁሉ ትዝታ
መጥፋት አብከንክኖሽ በድንገት ስትዞሪ፣
የጨው ሐውልት ግግር
አድርጎ ቢያስቀርሽ የፍጥረት ፈጣሪ፤
ሎጥን ልምሰል ብዬ…
የፍቅርሽ እርምጃ
ከኋላዬ ሲቀር ወደ ፊት አልሄድም፣
አይቼሽ ለማልቀስ
አይቼሽ ለመድረቅ
ያ'ምላኬን ቃል ሽሬ መዞሬ አይቀርም፡፡
#ኤልዳን
@eldan29
@getem
@getem
@getem
❤35🔥5🤩2👍1
(የሞገሴ ልጅ)
ከእኔ ካልመጣ
ሂጂልኝ ማለትን - አፌ ካልተማረ፣
ካልሄድኩ ካለ ልብሽ፣
ብከለክለውስ - መቼ ትቶት ቀረ?
ኁሌ አትሂጂ ባይ
ኁሌ ልሂድ በሚል ረባሽ ከተገፋ፣
ሰይጣንን ያስቀናል፣
እንኳንስ በሌላው በራሱ ሲከፋ!
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
ከእኔ ካልመጣ
ሂጂልኝ ማለትን - አፌ ካልተማረ፣
ካልሄድኩ ካለ ልብሽ፣
ብከለክለውስ - መቼ ትቶት ቀረ?
ኁሌ አትሂጂ ባይ
ኁሌ ልሂድ በሚል ረባሽ ከተገፋ፣
ሰይጣንን ያስቀናል፣
እንኳንስ በሌላው በራሱ ሲከፋ!
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
❤22🔥5👍1🤩1
እጠራጠራለሁ
ተቃርበሽ ተቃርበሽ ስጠፊ ስላየሁ
ደግሞም እቀናለሁ
እንደኔ ምትወጂው ይኖር ወይ እላለሁ
አልመስል አለኝ እውነት-የምትስሚኝ የምታቅፊኝ
ተቃርበሽ ልጠፊኝ?
ፍቅር ጣዕም አስለምደሽ ከአይን ልደበዝሽ
ለምንድነው የምትስሚኝ?
ለምንድነው የምስምሽ?
እጠራጠራለሁ
ስትርቂኝ ስላየሁ
ስትስሚኝ ስላየሁ
ካንቺ ፍቅር ውጥን ብርቅም ብሸሽም
እወድሻለሁኝ ግን ልቤ አያምንሽም
አፈቅርሻለሁኝ ግን ልቤ አያምንሽም።
ብቻ
አለሁ እንዳለነው
ስትቀርቢኝ እያየው
ስትርቂኝ እያየው
አለሁኝ እንዳለሁ
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ተቃርበሽ ተቃርበሽ ስጠፊ ስላየሁ
ደግሞም እቀናለሁ
እንደኔ ምትወጂው ይኖር ወይ እላለሁ
አልመስል አለኝ እውነት-የምትስሚኝ የምታቅፊኝ
ተቃርበሽ ልጠፊኝ?
ፍቅር ጣዕም አስለምደሽ ከአይን ልደበዝሽ
ለምንድነው የምትስሚኝ?
ለምንድነው የምስምሽ?
እጠራጠራለሁ
ስትርቂኝ ስላየሁ
ስትስሚኝ ስላየሁ
ካንቺ ፍቅር ውጥን ብርቅም ብሸሽም
እወድሻለሁኝ ግን ልቤ አያምንሽም
አፈቅርሻለሁኝ ግን ልቤ አያምንሽም።
ብቻ
አለሁ እንዳለነው
ስትቀርቢኝ እያየው
ስትርቂኝ እያየው
አለሁኝ እንዳለሁ
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
👍15❤11😢2
ወንድ አይደለሁ?
ታውቂም አይደል?
ወንድነቱ የሰጠኝን - ክብር ኩራት እንዴት ልጣል?
ላንድ ላንቺ ተንበርክኬ፣
ላንድ ላንቺ በመሸነፍ፣
ጠመንጃዬን ዝቅ አድርጌ ባንቺ ፍቅር - ራሴን ስፅፍ፤
ወንድነቴ ጠፍቶ አይደለም - ላንቺ ሲሆን ዝም ያለው፣
ከናት እቅፍ ሙቀት በላይ - ያንቺ መሳም ቢደላው ነው።
ግን ፀባይሽ ተለዋውጦ - እሹሩሩ እስካልዳኘው፣
ትንሽ ግዜ ቢቆይ እንጂ - ወንድነቴን እንዳሞኘው፤
ጠብ እርግፍ እያልኩልሽ ከቆጠርሽው እንደምንም፣
ረስተሽ እንጂ የማረክሽው - ሓይል ያጣ ልብ አልነበረም።
ግን ያው ተውኩት!
ዳግም ራራሁ!
አንከባክበኝ ስትይ እማ - መቼ ድሮስ አመነታሁ!
ነይ ተጠጊ ወደጎኔ - ፍርጥም ክንዴን ተንተራሽው፣
አትተወኝ ባልተለየው ሄዳለሁ ቃል - እንደልብሽ ግፊው እሺው፤
ብስጭቴን - አባሪልኝ - በከንፈርሽ ውድ መና፣
ከእጆችሽ መድሓኒቴን - አቀብይኝ ዳብሽኝ እና፤
እስትንፋስሽ እንፋሎቱ - ብርዴን ይዞት ገደል ይግባ፣
ቀለበቴን አጥልቄልሽ ዛሬም ዳግም እንጋባ!
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
ታውቂም አይደል?
ወንድነቱ የሰጠኝን - ክብር ኩራት እንዴት ልጣል?
ላንድ ላንቺ ተንበርክኬ፣
ላንድ ላንቺ በመሸነፍ፣
ጠመንጃዬን ዝቅ አድርጌ ባንቺ ፍቅር - ራሴን ስፅፍ፤
ወንድነቴ ጠፍቶ አይደለም - ላንቺ ሲሆን ዝም ያለው፣
ከናት እቅፍ ሙቀት በላይ - ያንቺ መሳም ቢደላው ነው።
ግን ፀባይሽ ተለዋውጦ - እሹሩሩ እስካልዳኘው፣
ትንሽ ግዜ ቢቆይ እንጂ - ወንድነቴን እንዳሞኘው፤
ጠብ እርግፍ እያልኩልሽ ከቆጠርሽው እንደምንም፣
ረስተሽ እንጂ የማረክሽው - ሓይል ያጣ ልብ አልነበረም።
ግን ያው ተውኩት!
ዳግም ራራሁ!
አንከባክበኝ ስትይ እማ - መቼ ድሮስ አመነታሁ!
ነይ ተጠጊ ወደጎኔ - ፍርጥም ክንዴን ተንተራሽው፣
አትተወኝ ባልተለየው ሄዳለሁ ቃል - እንደልብሽ ግፊው እሺው፤
ብስጭቴን - አባሪልኝ - በከንፈርሽ ውድ መና፣
ከእጆችሽ መድሓኒቴን - አቀብይኝ ዳብሽኝ እና፤
እስትንፋስሽ እንፋሎቱ - ብርዴን ይዞት ገደል ይግባ፣
ቀለበቴን አጥልቄልሽ ዛሬም ዳግም እንጋባ!
By @eyadermoges
@getem
@getem
@getem
❤37👎3🔥3🤩2
ፍትህ ለቃላት
ቤት ለመድፋት በሚል ሰበብ አሳብቤ
እንቅልፌን ሰውቼ ቃላትን ሰብስቤ
ከቶ አልማግጥም ቃል በቃል ደርቤ፡፡
ማንስ ሆኜና ነው ቃላትን ምመርጠው
አንደኛው ከሌላው የማበላልጠው?
ላንዲት ተራ ግጥም
ወይ ሊጥም ወይ ላይጥም
የአንዱን ክብር ጥዬ ሌላ ቃል አልመርጥም!
ቃል ሁሉ እኩል ነው መነሻው ከፊደል፤
አይከብድም ወይ ታዳ ሺህ ቃላት መበደል፡፡
ያኛው አይመጥንም ቤት ያፈርሳል ደርሶ
እንዴት ሰው ፊት ይቀርባል የግጥም ህግ ጥሶ
በሚል አጉል ልማድ ብዬ ቤት ለመድፋት
በቃላት ዘር ላይ አልፈፅምም ጥፋት፡፡
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
ቤት ለመድፋት በሚል ሰበብ አሳብቤ
እንቅልፌን ሰውቼ ቃላትን ሰብስቤ
ከቶ አልማግጥም ቃል በቃል ደርቤ፡፡
ማንስ ሆኜና ነው ቃላትን ምመርጠው
አንደኛው ከሌላው የማበላልጠው?
ላንዲት ተራ ግጥም
ወይ ሊጥም ወይ ላይጥም
የአንዱን ክብር ጥዬ ሌላ ቃል አልመርጥም!
ቃል ሁሉ እኩል ነው መነሻው ከፊደል፤
አይከብድም ወይ ታዳ ሺህ ቃላት መበደል፡፡
ያኛው አይመጥንም ቤት ያፈርሳል ደርሶ
እንዴት ሰው ፊት ይቀርባል የግጥም ህግ ጥሶ
በሚል አጉል ልማድ ብዬ ቤት ለመድፋት
በቃላት ዘር ላይ አልፈፅምም ጥፋት፡፡
By @Abuugida
@getem
@getem
@getem
❤41👍11🔥7😁7🤩3👎2🎉2