ዝብርቅርቅ ባለዉ በህይወት አዙሪት፤
ፍቺዉም ሳይገባኝ እንደዉ ስንከራተት፤
ሠርክ በጥበቃ በይሆናል ተስፋ፤
ይሞላልኝ መስሎኝ ስዳክር ስለፋ፤
በሰለለ ቅኝት ኑሮዬን ስገፋ፤
የቁሙ ቅዠቴ እጅግ አደከመኝ፤
በህልም መደሰት መኖር አታከተኝ፤
ትርጉም ያጣሁበት ብኩኑ ህይወቴ፤
መኖሬ ከጎዳኝ ይጥቀመኝ መሞቴ፤
ለመሞትም ለካ መመኘት አይበቃም፤
ቀኑ ካልደረሰ ትንፋሽ አይገታም።
ነጠላ አዘቅዝቄ ዘወትር እዬዬ፤
ራሴን ፈርቼ ስሸሽ ከጥላዬ፤
እንደዉ ምን ተሻለኝ?
ምንስ ነው የሚበጀኝ?
.................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
ፍቺዉም ሳይገባኝ እንደዉ ስንከራተት፤
ሠርክ በጥበቃ በይሆናል ተስፋ፤
ይሞላልኝ መስሎኝ ስዳክር ስለፋ፤
በሰለለ ቅኝት ኑሮዬን ስገፋ፤
የቁሙ ቅዠቴ እጅግ አደከመኝ፤
በህልም መደሰት መኖር አታከተኝ፤
ትርጉም ያጣሁበት ብኩኑ ህይወቴ፤
መኖሬ ከጎዳኝ ይጥቀመኝ መሞቴ፤
ለመሞትም ለካ መመኘት አይበቃም፤
ቀኑ ካልደረሰ ትንፋሽ አይገታም።
ነጠላ አዘቅዝቄ ዘወትር እዬዬ፤
ራሴን ፈርቼ ስሸሽ ከጥላዬ፤
እንደዉ ምን ተሻለኝ?
ምንስ ነው የሚበጀኝ?
.................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤25👍4🔥2
እንዴት ነሽ ስላት
ሳቅ ታበዛለች
ትጫወታለች ፤
< አለሁ ! >
ትላለች - እንደሞላላት
ቁስሏን የማላውቅ እዬመሰላት ፤
የዐይኗ መደፍረስ
የገጿ ሽክረት
የአንጀቷ ማረር
የልቧ ቁስለት
ጥልቅ ስቃይዋን እዬነገረኝ ፤
እርሷ ግን ሁሌም አንድ የምትለኝ ፤
- - - - - - - - - አለሁ ደህና ነኝ !
ልዩ ፍጥረት ናት
አይደረሱባትም ፤
ስሟ ሕይወት ነው
ካልተሸከሟት አይረዷትም ፤
በሕመሟ መሳቅ
በቁስሏ ማጌጥ
ታውቅበታለች ፤
ልክ እንደ መሬት
ውኃ'ን ከእሳት ጋር ታቻችላለች ፤
ከራስ ቅራኔ
ከራስ ጋር ሙግት ቢኖርባትም ፤
ከመሳቅ በቀር
በሰው ፊት ማልቀስ አይኾንላትም ፤
ደህና ነኝ ከሚል
ከአንድ ቃል በቀር ——
ሌላ አይወጣትም ፤
እወድዳታለሁ ፤
ደህና ነኝ ስትል
ደህና እንዳልሆነች አውቅባታለሁ።
By Tewodros kassa
@getem
@getem
@paappii
ሳቅ ታበዛለች
ትጫወታለች ፤
< አለሁ ! >
ትላለች - እንደሞላላት
ቁስሏን የማላውቅ እዬመሰላት ፤
የዐይኗ መደፍረስ
የገጿ ሽክረት
የአንጀቷ ማረር
የልቧ ቁስለት
ጥልቅ ስቃይዋን እዬነገረኝ ፤
እርሷ ግን ሁሌም አንድ የምትለኝ ፤
- - - - - - - - - አለሁ ደህና ነኝ !
ልዩ ፍጥረት ናት
አይደረሱባትም ፤
ስሟ ሕይወት ነው
ካልተሸከሟት አይረዷትም ፤
በሕመሟ መሳቅ
በቁስሏ ማጌጥ
ታውቅበታለች ፤
ልክ እንደ መሬት
ውኃ'ን ከእሳት ጋር ታቻችላለች ፤
ከራስ ቅራኔ
ከራስ ጋር ሙግት ቢኖርባትም ፤
ከመሳቅ በቀር
በሰው ፊት ማልቀስ አይኾንላትም ፤
ደህና ነኝ ከሚል
ከአንድ ቃል በቀር ——
ሌላ አይወጣትም ፤
እወድዳታለሁ ፤
ደህና ነኝ ስትል
ደህና እንዳልሆነች አውቅባታለሁ።
By Tewodros kassa
@getem
@getem
@paappii
❤74😢12🔥7👍2🤩1
የአብስራ ሳሙኤል
አባ "ደፋር'ሁን" ብለህ እንዳ'ስተማርከኝ፣
እደፍር ብዬ ጦሬን አነሳሁ፤
ግን ሰው ነኝና ለነፍሴ ሳሳሁ።
እናም አባ፣ ያንተንም ምክር ከንቱ ሳላስቀር፣
ጀግና ነኝ ብዬ እንዲው ባክኜ ከሜዳ እንዳልቀር።
* * *
ከምክርህ ጦሬን፣ ከፍርሀቴ ጋሻን አበጀው፤
እንዲያ ሲሆን ነው ውረድ!
እንውረድ!
ሲሉ የሚበጀው።
ዝናቡ እስኪ'ጠል ሸሸት ማለት፣
ጠለል ማለት መፍራት አይከፋም፣
ውድቀት ነው ብለን ከሳቅንበት ስር፣
መማሪያ የሚሆን ጥበብ አይጠፋም!
by Yabisra Samuel
@getem
@getem
@paappii
Telegram
Yabu
........
❤43👍4🔥2
እኔ ጭምቱ ሰው
ፍቅር ተለክፌ
ከእድገት ሀገሬ
ለሷ ስል ከንፌ
ሮቤ አለች ሲሉኝ
ሮቤ በርሬ
ሳስስ ስፈልጋት
ስጠይቅ አድሬ
ሸገር ሄደች ሲሉኝ
ባቀና አዲሳባ
እንኳንስ አካሏ
ዳናዋም አልገባ
ባክኜ ባክኜ
ከደከምኩ በኋላ
ምፈልጋት ፍቅሬ
ታየች ከ አሰላ
ገላንን ዱከምን ቢሾፍቱን አልፌ
ከሞጆና ናዝሬት ወንጂ ተገኝቼ
በሶደሬ በኩል ልሂድ ወደ ዴራ
ኢትያን አልፌ እንድገኝ አሰላ።
መነ ጂረኛ ኮ አቲ ቤክተ ላታ
ዮካን ፉዴን ጎንደር ኮ ሊጣ
(ዋ ነን ጀዲ አኒስ አብዲን ሙራ
አፉራ ኬ ዴቤን በርባቸ ኬን ጆራ)
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
ፍቅር ተለክፌ
ከእድገት ሀገሬ
ለሷ ስል ከንፌ
ሮቤ አለች ሲሉኝ
ሮቤ በርሬ
ሳስስ ስፈልጋት
ስጠይቅ አድሬ
ሸገር ሄደች ሲሉኝ
ባቀና አዲሳባ
እንኳንስ አካሏ
ዳናዋም አልገባ
ባክኜ ባክኜ
ከደከምኩ በኋላ
ምፈልጋት ፍቅሬ
ታየች ከ አሰላ
ገላንን ዱከምን ቢሾፍቱን አልፌ
ከሞጆና ናዝሬት ወንጂ ተገኝቼ
በሶደሬ በኩል ልሂድ ወደ ዴራ
ኢትያን አልፌ እንድገኝ አሰላ።
መነ ጂረኛ ኮ አቲ ቤክተ ላታ
ዮካን ፉዴን ጎንደር ኮ ሊጣ
(ዋ ነን ጀዲ አኒስ አብዲን ሙራ
አፉራ ኬ ዴቤን በርባቸ ኬን ጆራ)
ዮኒ
ኣታን @yonatoz
@getem
@getem
@getem
❤24👍8🔥8🤩3
ኪሴ፣ እኔ ፣ እግዜር
(ሳሙኤል አለሙ)
ዝር---ዝር
አምስት ብር
ዝር---ዝር
አስር ብር
ከኪሴ ቁና ፥ ሞልቶ ሲሰፈር
አላውቀውምና ፥ የነገን ነገር
ከንፈሬን እመጣለው።
ስምህን አዋጣለው።
(እግዜር ይስጥልኝ!)
እያለኝ፥ አለ-ማፈሬ
እያለኝ፥ የታጠፈው ብሬ
ባለ-መቀደዱ...
እያለኝ፥ የኪሴ ጨርቁ
ባለ-መተልተሉ...
ግን እንዴት ፥ ያጣ ስንመስል፤
እኔና ኪሴ ፥ አንዲት አንቆስል።
ስለማርያም ሲሉኝ...
ኖሮኝ እጄን እንዳልሰበስበው፤
ስለወላዲቷ ሲሉኝ...
እንዳጣ ሰው
ኪሴን እንዳልደባብሰው፤
ወይ በፀሐዩ
ወይ በዝናቡ
ወይ በንፋሱ
ብቻ ምልክት ስጠኝ ፥ የሚያስታውሱ
@getem
@getem
@getem
(ሳሙኤል አለሙ)
ዝር---ዝር
አምስት ብር
ዝር---ዝር
አስር ብር
ከኪሴ ቁና ፥ ሞልቶ ሲሰፈር
አላውቀውምና ፥ የነገን ነገር
ከንፈሬን እመጣለው።
ስምህን አዋጣለው።
(እግዜር ይስጥልኝ!)
እያለኝ፥ አለ-ማፈሬ
እያለኝ፥ የታጠፈው ብሬ
ባለ-መቀደዱ...
እያለኝ፥ የኪሴ ጨርቁ
ባለ-መተልተሉ...
ግን እንዴት ፥ ያጣ ስንመስል፤
እኔና ኪሴ ፥ አንዲት አንቆስል።
ስለማርያም ሲሉኝ...
ኖሮኝ እጄን እንዳልሰበስበው፤
ስለወላዲቷ ሲሉኝ...
እንዳጣ ሰው
ኪሴን እንዳልደባብሰው፤
ወይ በፀሐዩ
ወይ በዝናቡ
ወይ በንፋሱ
ብቻ ምልክት ስጠኝ ፥ የሚያስታውሱ
@getem
@getem
@getem
👍17❤10🤩1
" አይ ወጣትነቴ"
( ግዮናይ ነኝ)!፧
በባህል ታጥሬ በ'ምነቴ እየኮራሁ:
ወጣትነቴ አልቆ እንዳላረጅ ፈራሁ።
በመጠጥ ሰክሬ ፖሊስ ሳላስቸግር:
ከመንገዱ ቆሜ ሴቶችን ሳልፎግር።
ለነገ 'ሚበጀኝ እውቀቱን ሳልቀስም:
ወይ እንደኩዮቼ ሸጋ ከንፈር ሳልስም።
አወይ ወጣትነት...
በቅኔ ሳልዘምር ሳልዘፍን ባ'ራራይ:
ወይ አንዷን አቅፌ አልጋ ሳልከራይ።
ብላክ ሌብል ውስኪን ሳላንቆረቁረው:
የ'ግር አጣጣሌን ምንም ሳልቀይረው።
ከሜዳ ሳልቦርቅ ፈረስ እየገራሁ፣
ወጣትነቴ አልቆ እንዳላረጅ ፈራሁ።
@getem
@getem
@getem
( ግዮናይ ነኝ)!፧
በባህል ታጥሬ በ'ምነቴ እየኮራሁ:
ወጣትነቴ አልቆ እንዳላረጅ ፈራሁ።
በመጠጥ ሰክሬ ፖሊስ ሳላስቸግር:
ከመንገዱ ቆሜ ሴቶችን ሳልፎግር።
ለነገ 'ሚበጀኝ እውቀቱን ሳልቀስም:
ወይ እንደኩዮቼ ሸጋ ከንፈር ሳልስም።
አወይ ወጣትነት...
በቅኔ ሳልዘምር ሳልዘፍን ባ'ራራይ:
ወይ አንዷን አቅፌ አልጋ ሳልከራይ።
ብላክ ሌብል ውስኪን ሳላንቆረቁረው:
የ'ግር አጣጣሌን ምንም ሳልቀይረው።
ከሜዳ ሳልቦርቅ ፈረስ እየገራሁ፣
ወጣትነቴ አልቆ እንዳላረጅ ፈራሁ።
@getem
@getem
@getem
❤54😢13👎5👍3🤩1
ተስፋ?
.
.
እንደ እምዬ እቅፍ የምንናፍቀዉ፤
ዘወትር ሳንታክት የምንጠብቀዉ፤
ብርሃን እንዲሆን በምናብ የሳልነዉ
በልባችን ያለ ተስፋ ግን ምንድነው?
......................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
እንደ እምዬ እቅፍ የምንናፍቀዉ፤
ዘወትር ሳንታክት የምንጠብቀዉ፤
ብርሃን እንዲሆን በምናብ የሳልነዉ
በልባችን ያለ ተስፋ ግን ምንድነው?
......................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤40
ፍቅር በዝምታ
ደስ የሚለው ህመም ሰውን የ መውደድ
አዎ ያማል እኮ ለማይገባው ሰው ጨርቅ ጥሎ ማበድ
ባንተ ደስታ መሳቅ የራስን ሀዘን ረስቶ
ደሞ ማዘን መጨነቅ ሀዘንክን አይቶ
ሁሉም ስላንተ ብቻ አንዳች ሳልል ለኔ
ያንተን ህይወት ኖራለው ባክኖ ስለ የኔ
እራሴን ገደልኩት የኔ ምለው አጣው
የኔን ደስታ የኔን ስሜት ከቶ ምን ዋጠው ?
እንዴት ነው የቻልኩት ሁሌ አንተን ማሰቡን
በሁሉም ቦታ ላይ ምስልክን መሳሉን
ለማን ይግባኝ ላቅርብ ላሰማ ስሞታ
ላንተ ብቻ ልቤ ሁሌም እየመታ
ማን ይገባው ይሆን ባወራ የሆዴን
ያልተፈቀደልኝን በጥልቅ መውደዴን
እኔማ መረጥኩኝ ችሎ መቆየቱን
ደና መስሎ መሳቅ መሰንበቱን
ልክ እንደ አምላኬ ልክ እንደ አንዱ ጌታ
ልቤ በ ሰው ፍቅር እየተንገላታ
ለካስ ፍቅር ማለት እግዚአብሔር ማለት ነው
እራሱ ክርስቶስ የተሰቀለው ነው
ታድያ እኔ ማነኝ ወደድኩኝ የምለው
በፍቅር ምክንያት እንዲ የማነባው
ፍቅር ማለት ህመም መሆኑን ባወኩኝ
አንተን በ ማጣቴ እንዲህ ባላዘንኩኝ
መጥቼ እንዳልነግርክ ቤትኛው ድፍረቴ
በህይወቴ ሞልቶ የ ገዛ ጭንቀቴ
እንኳን ግድ ሳይሰጥክ ለኔ ምንም ሳትወደኝ
አድርጎት ፈጣሪ ድንገት እንኳን አንተ እኔን ብትወደኝ
የለኝም አቅሙ ልነግርክ የልቤን ትርታ
ስወድክ ኖራለው ሁሌም በ ዝምታ
ነሀሴ 12
By mhret
@getem
@getem
@paappii
ደስ የሚለው ህመም ሰውን የ መውደድ
አዎ ያማል እኮ ለማይገባው ሰው ጨርቅ ጥሎ ማበድ
ባንተ ደስታ መሳቅ የራስን ሀዘን ረስቶ
ደሞ ማዘን መጨነቅ ሀዘንክን አይቶ
ሁሉም ስላንተ ብቻ አንዳች ሳልል ለኔ
ያንተን ህይወት ኖራለው ባክኖ ስለ የኔ
እራሴን ገደልኩት የኔ ምለው አጣው
የኔን ደስታ የኔን ስሜት ከቶ ምን ዋጠው ?
እንዴት ነው የቻልኩት ሁሌ አንተን ማሰቡን
በሁሉም ቦታ ላይ ምስልክን መሳሉን
ለማን ይግባኝ ላቅርብ ላሰማ ስሞታ
ላንተ ብቻ ልቤ ሁሌም እየመታ
ማን ይገባው ይሆን ባወራ የሆዴን
ያልተፈቀደልኝን በጥልቅ መውደዴን
እኔማ መረጥኩኝ ችሎ መቆየቱን
ደና መስሎ መሳቅ መሰንበቱን
ልክ እንደ አምላኬ ልክ እንደ አንዱ ጌታ
ልቤ በ ሰው ፍቅር እየተንገላታ
ለካስ ፍቅር ማለት እግዚአብሔር ማለት ነው
እራሱ ክርስቶስ የተሰቀለው ነው
ታድያ እኔ ማነኝ ወደድኩኝ የምለው
በፍቅር ምክንያት እንዲ የማነባው
ፍቅር ማለት ህመም መሆኑን ባወኩኝ
አንተን በ ማጣቴ እንዲህ ባላዘንኩኝ
መጥቼ እንዳልነግርክ ቤትኛው ድፍረቴ
በህይወቴ ሞልቶ የ ገዛ ጭንቀቴ
እንኳን ግድ ሳይሰጥክ ለኔ ምንም ሳትወደኝ
አድርጎት ፈጣሪ ድንገት እንኳን አንተ እኔን ብትወደኝ
የለኝም አቅሙ ልነግርክ የልቤን ትርታ
ስወድክ ኖራለው ሁሌም በ ዝምታ
ነሀሴ 12
By mhret
@getem
@getem
@paappii
❤44🔥5👍2
ቢራቢሮ ቢራቢሮ ቢራቢሮ ሆና ነፍሴ፣
መታገሉን አልችልበት ቀን እስኪያልፍ፤
ዝም ነው መልሴ።
እንደ ዛሬ ሆኖ አይቀርም
ነገም ቀኑ ይለወጣል፤
አሁን ትል ነው ያልኩት ገላ፣
ቀን ሲያሽረው ክንፍ ያወጣል።
እቀስማለሁ የአበባን ማር፤
እበራለሁ ከፍ ብዬ።
ጊዜ ደርሶ ያሻረኝን በረከቱን ተቀብዬ፤
ትልነቴን መሬት ጥዬ!
አንተም አንቺም ወገኖቼ፣
ቢራቢሮ ናት ነፍሳችሁ!
ትል እንዳለች አትግደሏት፤
ቀን የማያልፍ ቢመስላችሁ።
ከታገሱት እሺ፣ ካሉት፣
እንደ የ'አቅሙ ሁሉ ይገፋል።
መከራ የህይወት ድልድይ ነው —
የተጽናና ተሻግሮ ያልፋል፤
እምቢ ያለው ይቀጠፋል።
By @YabisraSamuel
@getem
@getem
@getem
❤29
"ነበር "ይሆናሉ
.
.
ቁርጥራጭ ሃሳቤን፣
ዉስጣዊ ንዳዴን፣
ማንም የማያዉቀዉ ጥልቅ ሰቀቀኔን፣
በነጭ ወረቀት ላይ ሰብስቤ ላሰፍረዉ፣
በቃላቴ ድርድር ጭንቀቴን ላበርደዉ፣
የልቤን ተንፍሼ መዳኔን እያመንኩ፣
ብዕሬን አንስቼ ለመፃፍ ተጣደፍኩ።
ትርጉም አልባ ፊደላትን ቀጣጥዬ፣
በሀዘን ብሶት በመከራ ተከልዬ፣
ወረቀቴ ራሰ በትኩስ እንባዬ።
ለካ..........
የዉስጥን ለመግለጽ ቃላቶች ያጥራሉ፣
ካይን ተሰዉረዉ በነዉ ይጠፋሉ፣
ፍቺ ታጥቶላቸዉ ኢምንት ይሆናሉ።
.............................
ይህ ሁሉ ቢሆንም፣
ይህ ሁሉ ቢሆንም፣
ዘላለም አለሜን ሙሾ አላወርድም፣
ዛሬዬን ለነገ አሳልፌ አልሰጥም።
ፅልመት የዋጣቸዉ አያሌ ቀናቶች፣
እንቅልፍ የራቃቸው ረጃጅም ሌቶች፣
በጊዜ መሪነት ተጥለው ያልፋሉ፣
በአዲስ ተተክተዉ ነበር ይባላሉ፣
ለልጅ ልጅ ሚነገር ታሪክ ይሆናሉ።
......................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
ቁርጥራጭ ሃሳቤን፣
ዉስጣዊ ንዳዴን፣
ማንም የማያዉቀዉ ጥልቅ ሰቀቀኔን፣
በነጭ ወረቀት ላይ ሰብስቤ ላሰፍረዉ፣
በቃላቴ ድርድር ጭንቀቴን ላበርደዉ፣
የልቤን ተንፍሼ መዳኔን እያመንኩ፣
ብዕሬን አንስቼ ለመፃፍ ተጣደፍኩ።
ትርጉም አልባ ፊደላትን ቀጣጥዬ፣
በሀዘን ብሶት በመከራ ተከልዬ፣
ወረቀቴ ራሰ በትኩስ እንባዬ።
ለካ..........
የዉስጥን ለመግለጽ ቃላቶች ያጥራሉ፣
ካይን ተሰዉረዉ በነዉ ይጠፋሉ፣
ፍቺ ታጥቶላቸዉ ኢምንት ይሆናሉ።
.............................
ይህ ሁሉ ቢሆንም፣
ይህ ሁሉ ቢሆንም፣
ዘላለም አለሜን ሙሾ አላወርድም፣
ዛሬዬን ለነገ አሳልፌ አልሰጥም።
ፅልመት የዋጣቸዉ አያሌ ቀናቶች፣
እንቅልፍ የራቃቸው ረጃጅም ሌቶች፣
በጊዜ መሪነት ተጥለው ያልፋሉ፣
በአዲስ ተተክተዉ ነበር ይባላሉ፣
ለልጅ ልጅ ሚነገር ታሪክ ይሆናሉ።
......................................................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤30👍9
( ተረት ተረት )
============
ያኔ በጥንት ወራት ...
በጣም ሚዋደዱ ጎረቤት ነበሩ
ወይን ይመስል ግተውት በፍቅር የሰከሩ
ቤታቸው አጥር አልባ ሆኖ የሚኖሩ
በድህነት በእርቃን ማይተፉፈሩ
ለሚያያቸው ሁሉ ተስፋን የሚዘሩ
ሁለት ' አንድ ' የሆኑ .. ጎረቤት ነበሩ
ግና ከሰው ስህተት አይጠፋም እንዲሉ
ከዕለታት ባንዱ ቀን
ከአንተ ርቄ ህይወት ከአንተ ርቄ ኑሮ
ለኔ አይከብድ እያሉ
ከቤታቸው መሐል ግድግዳ ተከሉ
ከደጃቸው የእሾህ አጥር አስከለሉ
በለጋ ፍቅራቸው አጉል ቀበጡበት
ተሸነጋገሉ !!
ታዲያ ቀን ሲገፋ ናፍቆት ሲያነዳቸው
የአንዱ ህይወት ያላንዱ አልሞላ ሲላቸው
ዳግም ፍቅር ሲሹ ...
በሞኝነት ተክለው ያቆሙት ግድግዳ
መሠረቱ ጸንቶ አልፈርስም አላቸው
ብቻ በትዝታ ብቻ በወዮታ
በናፍቆት አውራጃ አለፈ ህይወታቸው !
ፍቅሬ ...
እኔና አንቺም ያኔ
እንደኒህ ምስኪናን ጎረቤቶች ነበርን
ብዙ ተጎንጭተን በፍቅር የሰከርን
ከአይን ያውጣቹ እያለ ያየ ሚመርቀን
ግና እንደማይጠፋ ከብረትም ዝገት
ከአንተ ርቄ ኑሮ ካንቺ ርቄ ህይወት
ያላንተ ሳቅ ፌሽታ ያላንቺ መደሰት
አይከብድም እያልን በትኩስ ፍቅራችን
አጉል ቀብጠንበት ..
ክፍተታችን ሰፋ ጉድለታችን በዛ
በእልህ በሞኝነት !!
ታዲያ ጊዜ ደጉ ቀጥቶ ሲያስተምረን
የኔን ጉዞ ያላንቺ .. ያንቺን ጉዞ ያለኔ
ኦናነት ሲነግረን
ምን መልሶ ማፍቀር አንድ መሆን ቢያምረን
ቀብጠን የሄድነውን የየግል ጎዳን
እስክንመለሰው .. አያ ሞት ቀደመን
ትላንት ላይ ብቻ በነበሩ ቀረን !!
By @Kiyorna
@getem
@getem
@paappii
============
ያኔ በጥንት ወራት ...
በጣም ሚዋደዱ ጎረቤት ነበሩ
ወይን ይመስል ግተውት በፍቅር የሰከሩ
ቤታቸው አጥር አልባ ሆኖ የሚኖሩ
በድህነት በእርቃን ማይተፉፈሩ
ለሚያያቸው ሁሉ ተስፋን የሚዘሩ
ሁለት ' አንድ ' የሆኑ .. ጎረቤት ነበሩ
ግና ከሰው ስህተት አይጠፋም እንዲሉ
ከዕለታት ባንዱ ቀን
ከአንተ ርቄ ህይወት ከአንተ ርቄ ኑሮ
ለኔ አይከብድ እያሉ
ከቤታቸው መሐል ግድግዳ ተከሉ
ከደጃቸው የእሾህ አጥር አስከለሉ
በለጋ ፍቅራቸው አጉል ቀበጡበት
ተሸነጋገሉ !!
ታዲያ ቀን ሲገፋ ናፍቆት ሲያነዳቸው
የአንዱ ህይወት ያላንዱ አልሞላ ሲላቸው
ዳግም ፍቅር ሲሹ ...
በሞኝነት ተክለው ያቆሙት ግድግዳ
መሠረቱ ጸንቶ አልፈርስም አላቸው
ብቻ በትዝታ ብቻ በወዮታ
በናፍቆት አውራጃ አለፈ ህይወታቸው !
ፍቅሬ ...
እኔና አንቺም ያኔ
እንደኒህ ምስኪናን ጎረቤቶች ነበርን
ብዙ ተጎንጭተን በፍቅር የሰከርን
ከአይን ያውጣቹ እያለ ያየ ሚመርቀን
ግና እንደማይጠፋ ከብረትም ዝገት
ከአንተ ርቄ ኑሮ ካንቺ ርቄ ህይወት
ያላንተ ሳቅ ፌሽታ ያላንቺ መደሰት
አይከብድም እያልን በትኩስ ፍቅራችን
አጉል ቀብጠንበት ..
ክፍተታችን ሰፋ ጉድለታችን በዛ
በእልህ በሞኝነት !!
ታዲያ ጊዜ ደጉ ቀጥቶ ሲያስተምረን
የኔን ጉዞ ያላንቺ .. ያንቺን ጉዞ ያለኔ
ኦናነት ሲነግረን
ምን መልሶ ማፍቀር አንድ መሆን ቢያምረን
ቀብጠን የሄድነውን የየግል ጎዳን
እስክንመለሰው .. አያ ሞት ቀደመን
ትላንት ላይ ብቻ በነበሩ ቀረን !!
By @Kiyorna
@getem
@getem
@paappii
❤55👍7🔥3😱3
ሚዛኑ ቢያደላ፤ ጊዜ ሆኖ ዳኛ
ቋንቋ ቀለም ሆነ፤ የሰው መመዘኛ።
ትገል እደው ግደል፤ ታድን እንደው አድን
ጠባሳ አይዝም፤ መርቅዞ የሚድን።
ብዬ ባዜምበት ....
ይፈትለው ጀመረ ቃል አጠቃቀሜን
ምንሽር አንስቼ ላላሳየው አቅሜን
ማንስ ገሎ ዳነ ማን ሞቶ ተረሳ ?
ፍጻሜው ሰይፍ ነው፤ ሰይፍ ለሚያነሳ።
***
ስለዚህ፤ ትርጉሙን
"ሀገር" ማለት ብባል?
"ሀገር" ማለት "ሰው ነው" አልልም ደፍሬ።
ሀገር የሚሆን ሰው፤ አታለች ሀገሬ።
By @YabisraSamuel
@getem
@getem
@paappii
❤62🔥16👍7
እኔ እና ገጣሚው
(Desu Fikriel)
ዛሬም ባይገባኝም - እንዴት እንዳመንኩሽ - እንዴት እንዳሳትሽኝ
"ፍቅር ይኑር እንጅ ገንዘብ ምን ያደርጋል" ብለሽ አሳመንሽኝ።
ካመንኩሽ በኋላ...
በቅጡ ሳንኖር ሳምንት ሳይሞላ
"ዋናው ገንዘቡ ነው ፍቅር አይበላ"
ብለሽ ክደሽኛል
ፍቅር ባያውረኝ - እንኳን ለኔ ቀርቶ - ለልጅ አይሳትም
የዘመን ሀቅ ነው - ፍቅር 'በድሀ ደንብ' - አይመሰረትም
ከካድሽኝ በኋላ
ሱራፌል መልአኩን - ከ'ሳት ሰይፉ ጋራ - ልቤ ዳር አቁሜ
ሴት ውስጤ ላትገባ - ዳግም ላላፈቅር - ማልኩኝ ደጋግሜ
የምልሽ ገብቶሻል?
ለነገሩ ተይው
ቢገባሽም እንኳን - ገብቶኛል አትይም - መካድ ለምዶብሻል
በርግጥ አታነቢም (ምናልባት ከሰማሽ)
አንድ ባለቅኔ
ፍቅረኛውን ቀጥሮ - ትንሽ በማርፈዷ - ብዙ የበሸቀ
ምድሩ አልበቃ ብሎት ከጨረቃዋ ጋር በእልህ ተናነቀ
ፍቅረኛውን መክራ ያስቀረች ይመስል ዓለምን ጠልቷታል
የሚቀኝላትን
የሚሳሳላትን ጨረቃዋን እንኳ 'እናቷን' ብሏታል
የምልሽ ገብቶሻል?
ለነገሩ ተይው
ቢገባሽም እንኳን - ገብቶኛል አትይም - መካድ ለምዶብሻል
ይሄን ባለቅኔ
ያረፈደችው ሴት (አንቺ እንዳደረግሽው) ከድታው ቢሆን ኖሮ
ከፈጣሪው ጋራ መሟገቱ አይቀርም ፍጡሩን ተሻግሮ
እያልኩ አስባለሁ
ህመም በወለደው አስታማሚ ቅኔ ቁስሌን አሻሻለሁ
የሚገርምሽ ነገር
ግጥም ልፅፍ ነበር
'ያማል' የሚል ርዕስ ከዚህ ሰው አንስቼ
ግን አስቢው እስኪ የእሱ ሴት አርፍዳ እኔ ተከድቼ
አንድ አይነት ስንቀኝ
ሳስበው ራሱ ብቻየን ቁጭ ብዬ እንደ ጅል አሳቀኝ
የምልሽ ገብቶሻል?
ለነገሩ ተይው
ቢገባሽም እንኳን - ገብቶኛል አትይም - መካድ ለምዶብሻል
@getem
@getem
@paappii
(Desu Fikriel)
ዛሬም ባይገባኝም - እንዴት እንዳመንኩሽ - እንዴት እንዳሳትሽኝ
"ፍቅር ይኑር እንጅ ገንዘብ ምን ያደርጋል" ብለሽ አሳመንሽኝ።
ካመንኩሽ በኋላ...
በቅጡ ሳንኖር ሳምንት ሳይሞላ
"ዋናው ገንዘቡ ነው ፍቅር አይበላ"
ብለሽ ክደሽኛል
ፍቅር ባያውረኝ - እንኳን ለኔ ቀርቶ - ለልጅ አይሳትም
የዘመን ሀቅ ነው - ፍቅር 'በድሀ ደንብ' - አይመሰረትም
ከካድሽኝ በኋላ
ሱራፌል መልአኩን - ከ'ሳት ሰይፉ ጋራ - ልቤ ዳር አቁሜ
ሴት ውስጤ ላትገባ - ዳግም ላላፈቅር - ማልኩኝ ደጋግሜ
የምልሽ ገብቶሻል?
ለነገሩ ተይው
ቢገባሽም እንኳን - ገብቶኛል አትይም - መካድ ለምዶብሻል
በርግጥ አታነቢም (ምናልባት ከሰማሽ)
አንድ ባለቅኔ
ፍቅረኛውን ቀጥሮ - ትንሽ በማርፈዷ - ብዙ የበሸቀ
ምድሩ አልበቃ ብሎት ከጨረቃዋ ጋር በእልህ ተናነቀ
ፍቅረኛውን መክራ ያስቀረች ይመስል ዓለምን ጠልቷታል
የሚቀኝላትን
የሚሳሳላትን ጨረቃዋን እንኳ 'እናቷን' ብሏታል
የምልሽ ገብቶሻል?
ለነገሩ ተይው
ቢገባሽም እንኳን - ገብቶኛል አትይም - መካድ ለምዶብሻል
ይሄን ባለቅኔ
ያረፈደችው ሴት (አንቺ እንዳደረግሽው) ከድታው ቢሆን ኖሮ
ከፈጣሪው ጋራ መሟገቱ አይቀርም ፍጡሩን ተሻግሮ
እያልኩ አስባለሁ
ህመም በወለደው አስታማሚ ቅኔ ቁስሌን አሻሻለሁ
የሚገርምሽ ነገር
ግጥም ልፅፍ ነበር
'ያማል' የሚል ርዕስ ከዚህ ሰው አንስቼ
ግን አስቢው እስኪ የእሱ ሴት አርፍዳ እኔ ተከድቼ
አንድ አይነት ስንቀኝ
ሳስበው ራሱ ብቻየን ቁጭ ብዬ እንደ ጅል አሳቀኝ
የምልሽ ገብቶሻል?
ለነገሩ ተይው
ቢገባሽም እንኳን - ገብቶኛል አትይም - መካድ ለምዶብሻል
@getem
@getem
@paappii
❤69🔥17👍7😱4
የምርቃና_ግፉ
(በረከት በላይነህ)
የሙዚቃ ሊቁ፣
ሙዚቃ ቀማሚው ዜማ እየቀመረ
ጠባቧ "ስቲዲዮ" ጫት ሞልቷት ነበረ።
ሳተናው ነጋዴ ትርፉን እያሰላ
ሊቅም ቁርሱን በላ።
ሹማምንቶቻችን ፣
ገንቢ አፍራሾቻችን ፣
ዕቅዱን ሲጽፉ ፣
በትዕዛዝ ያደገ አወደይ ቀጠፉ።
ጎረምሳው አፍቃሪሽ ጫት በዱቤ ቅሞ፣
ደብዳቤ ፃፈልሽ ከገረባ መሃል
ምርቅን ቃላት ለቅሞ።
እናስ!
መሪ ከተከታይ፣
ፍትህ ከተበዳይ፣
ጥበብ ከአድናቂው፣
መላሽ ከጠያቂው፣
የነቃ ከእውኑ
የተኛ ከሕመሙ
ውበት ከቀለሙ
እኮ በምን ስሌት? እንደምን ይስማማ?
ሰጪና ተቀባይ ፣ እኩል አልቃሙማ።
@getem
@getem
@paappii
(በረከት በላይነህ)
የሙዚቃ ሊቁ፣
ሙዚቃ ቀማሚው ዜማ እየቀመረ
ጠባቧ "ስቲዲዮ" ጫት ሞልቷት ነበረ።
ሳተናው ነጋዴ ትርፉን እያሰላ
ሊቅም ቁርሱን በላ።
ሹማምንቶቻችን ፣
ገንቢ አፍራሾቻችን ፣
ዕቅዱን ሲጽፉ ፣
በትዕዛዝ ያደገ አወደይ ቀጠፉ።
ጎረምሳው አፍቃሪሽ ጫት በዱቤ ቅሞ፣
ደብዳቤ ፃፈልሽ ከገረባ መሃል
ምርቅን ቃላት ለቅሞ።
እናስ!
መሪ ከተከታይ፣
ፍትህ ከተበዳይ፣
ጥበብ ከአድናቂው፣
መላሽ ከጠያቂው፣
የነቃ ከእውኑ
የተኛ ከሕመሙ
ውበት ከቀለሙ
እኮ በምን ስሌት? እንደምን ይስማማ?
ሰጪና ተቀባይ ፣ እኩል አልቃሙማ።
@getem
@getem
@paappii
❤38😁25🔥4👍3🤩2
አንተ ማለት እኮ......
.
.
የአይኖችህ ማማር፤
ዉስጥ የሚሰረስር፤
የጥርሶችህ ፀዳል ልብ የሚሰነጥቅ፤
ፈገግታህ ሚወደድ መንፈስን የሚሰርቅ፤
አንተ ማለት እኮ......
የሹማምንት አብራክ የመኳንንት ዘር፤
ነቅዕ ያልተገኘብህ የዉቦች ሀሉ ዳር፤
ልቡ 'ሚደነግጥ ያየ የሚመኝህ፤
በነጋ በጠባ ሁሉ የሚያልምህ፤
አንተ ማለት እኮ........
በፈራሽ ዉበትህ ሠርክ የምትመካ፤
በለበስከዉ አልባስ ሰዉን የምትለካ፤
ከራስህ ተጣልተህ ሰላምህን ያጣህ፤
መደሰት የራቀህ አንተ ማለት ይህ ነህ።
...............................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
.
.
የአይኖችህ ማማር፤
ዉስጥ የሚሰረስር፤
የጥርሶችህ ፀዳል ልብ የሚሰነጥቅ፤
ፈገግታህ ሚወደድ መንፈስን የሚሰርቅ፤
አንተ ማለት እኮ......
የሹማምንት አብራክ የመኳንንት ዘር፤
ነቅዕ ያልተገኘብህ የዉቦች ሀሉ ዳር፤
ልቡ 'ሚደነግጥ ያየ የሚመኝህ፤
በነጋ በጠባ ሁሉ የሚያልምህ፤
አንተ ማለት እኮ........
በፈራሽ ዉበትህ ሠርክ የምትመካ፤
በለበስከዉ አልባስ ሰዉን የምትለካ፤
ከራስህ ተጣልተህ ሰላምህን ያጣህ፤
መደሰት የራቀህ አንተ ማለት ይህ ነህ።
...............................
በዔደን ታደሰ
@topazionnn
@getem
@getem
❤34🔥5👍4