ቅኔ ናት ሀገሬ !
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።
ጠፍጥፎ የሰራት ፥ ያበጃት ይመስል
ይሄ የቀለም ቀንድ ፥ የህሊና ስንኩል
ትፈርሳለች ይላል ፦
ሟርቱን ከሀገሬ ደጅ ፥ በራፏ ላይ ሊጥል ።
ደግሞም ...
ወዲህ ለቅርሻቱ ፥ ሊጠቅስ ማስረጃ
ምሳሌ አስታኮ ፥ ሊያቆም የቃል ፍርጃ!
መጥሀፉን ሊያብል ፥ ቃልኪዳኗን ሽሮ
ዓይኑ ሩቅ ማትሮ ...
ሶሪያን ይጠራል ፥ ድንበሯን ተሻግሮ ።
# እኔ
የቃል ግንዝ አይጥ ፥ የጠቆረ ዶሮ
የሚከረፋ ደም ፥ የሟርት እንጉርጉሮ
ትፈርሳለች የሚል ፥ የምሁር ደንቆሮ
በሚዘራው ክፋት ፥ በሚያቆየው በደል
ልቤ ሳይሸነገል !
ፈገግ ብዬ አልፋለሁ ፥ ዥልነቱን ላቀል ።
አትፈርስም ሀገሬ !
የቃል ኪዳን ቅጥሬ.. .
ምን ዳሷ ቢያጋድል ፥ መሰረቷ ዘሞ
ምንም ታላቅ ባትሆን ፥ እንዲያ እንደቀድሞ
መቶ ቅጠል በጣሽ ፥ ሚልዩን ደፍተራ
እልፍ ባለ ጋኔን ፥ የእርኩሰት ደመራ
ልበትናት ብሎ.. .
በየ አዳራሹ ... ቢፎክር ቢያቅራራ
ማንነቷን ሊያሽር ...
ንጉስ ብረት ይዞ ፥ በሰይፍ ቢሸልል
ሀገሬ ቢላል ናት ...
በስጋዋ ቁስል ፥ እምነቷን የማጥል ።
አትፈርስም ኢትዮጵያ!
የአዳም መጀመሪያ.. .
ጠኔ ክንዱ ቢያይል ፥ ውሀ ጥም ቢያደብናት
የማጣት ቀንበሩ ፥ ወገቧን ቢያጎብጣት
የወደቀች ብትመስል ፥ ከሁሉ ተናንሳ
በርባን ከስር ወጥቶ ፥ ደንፍቶ ቢያገሳ
ዓለሙ ሊሳለቅ ፥ እንጨቱን አጣምሮ ፥ መስቀሉን ቢያነሳ
ሀገሬ መሲህ ናት ...
የክርስቶስ ሀምሳል ፥ ቀብረናታል ሲሉ ፥ ሞታ ምትነሳ ።
አትፈርስም!
አትፈርስም !
ኢትዮጵያ አትፈርስም...
ቢፈጡሩ ጥያቄ ፥ የሰይጣን ካህናት ፥ ሳንቲም እያነሱ
የዘረጉት ወጥመድ ...
የሚምሱት ጉድጓድ ፥ ሀገሬን ሳይጥላት ፥ ይተርፋል ለነሱ።
#አዎን ማህደር ናት !
ማንም እሳት ቢጭር ፥ ማገዶ ቢከምር ፥ ሊያከስላት አሳሮ
ሀገሬ ሚስጥር ናት !
የፈጣሪ ቅኔ ፥ የስንኞች ግማድ ፥ የፍቅር ቋጠሮ
አፍራሿ ይፈርሳል.. .
በለኮሰው እሳት ፥ በቁሙ እያለቀ ፥ አካሉ ቀንጭሮ ።
@getem
@getem
@getem
(ሚካኤል አስጨናቂ)
።።።።።።።።።።።።።።
ጠፍጥፎ የሰራት ፥ ያበጃት ይመስል
ይሄ የቀለም ቀንድ ፥ የህሊና ስንኩል
ትፈርሳለች ይላል ፦
ሟርቱን ከሀገሬ ደጅ ፥ በራፏ ላይ ሊጥል ።
ደግሞም ...
ወዲህ ለቅርሻቱ ፥ ሊጠቅስ ማስረጃ
ምሳሌ አስታኮ ፥ ሊያቆም የቃል ፍርጃ!
መጥሀፉን ሊያብል ፥ ቃልኪዳኗን ሽሮ
ዓይኑ ሩቅ ማትሮ ...
ሶሪያን ይጠራል ፥ ድንበሯን ተሻግሮ ።
# እኔ
የቃል ግንዝ አይጥ ፥ የጠቆረ ዶሮ
የሚከረፋ ደም ፥ የሟርት እንጉርጉሮ
ትፈርሳለች የሚል ፥ የምሁር ደንቆሮ
በሚዘራው ክፋት ፥ በሚያቆየው በደል
ልቤ ሳይሸነገል !
ፈገግ ብዬ አልፋለሁ ፥ ዥልነቱን ላቀል ።
አትፈርስም ሀገሬ !
የቃል ኪዳን ቅጥሬ.. .
ምን ዳሷ ቢያጋድል ፥ መሰረቷ ዘሞ
ምንም ታላቅ ባትሆን ፥ እንዲያ እንደቀድሞ
መቶ ቅጠል በጣሽ ፥ ሚልዩን ደፍተራ
እልፍ ባለ ጋኔን ፥ የእርኩሰት ደመራ
ልበትናት ብሎ.. .
በየ አዳራሹ ... ቢፎክር ቢያቅራራ
ማንነቷን ሊያሽር ...
ንጉስ ብረት ይዞ ፥ በሰይፍ ቢሸልል
ሀገሬ ቢላል ናት ...
በስጋዋ ቁስል ፥ እምነቷን የማጥል ።
አትፈርስም ኢትዮጵያ!
የአዳም መጀመሪያ.. .
ጠኔ ክንዱ ቢያይል ፥ ውሀ ጥም ቢያደብናት
የማጣት ቀንበሩ ፥ ወገቧን ቢያጎብጣት
የወደቀች ብትመስል ፥ ከሁሉ ተናንሳ
በርባን ከስር ወጥቶ ፥ ደንፍቶ ቢያገሳ
ዓለሙ ሊሳለቅ ፥ እንጨቱን አጣምሮ ፥ መስቀሉን ቢያነሳ
ሀገሬ መሲህ ናት ...
የክርስቶስ ሀምሳል ፥ ቀብረናታል ሲሉ ፥ ሞታ ምትነሳ ።
አትፈርስም!
አትፈርስም !
ኢትዮጵያ አትፈርስም...
ቢፈጡሩ ጥያቄ ፥ የሰይጣን ካህናት ፥ ሳንቲም እያነሱ
የዘረጉት ወጥመድ ...
የሚምሱት ጉድጓድ ፥ ሀገሬን ሳይጥላት ፥ ይተርፋል ለነሱ።
#አዎን ማህደር ናት !
ማንም እሳት ቢጭር ፥ ማገዶ ቢከምር ፥ ሊያከስላት አሳሮ
ሀገሬ ሚስጥር ናት !
የፈጣሪ ቅኔ ፥ የስንኞች ግማድ ፥ የፍቅር ቋጠሮ
አፍራሿ ይፈርሳል.. .
በለኮሰው እሳት ፥ በቁሙ እያለቀ ፥ አካሉ ቀንጭሮ ።
@getem
@getem
@getem
👍1