#ከተባበርንእንችላለን!!
#ለጋሽነኝ
እዮብ ሰብስቤ
ሙሉአለም ታከለ ራህዋ ምን ያህል ራሱን ለጥበብ አሳልፎ የሰጠ ድምፃዊ መሆኑን ያወኩት ገና ሎሚ ሽታ የራዲዮ ፕሮግራሜ ላይ እንግድ ሆኖ ሊቀርብ ወደ ስቱዲዮ እየሄድን በነበረን ቆይታ ነበር፡፡ አዲሱ ስራዬን ስማው እስኪ አለኝ ሲበዛ ትሁት ነው ‹‹አምሮብሻል›› የተሰኘውን ዜማ ነበር ያኔ አልተለቀቀም ነበር፡፡ አዳመጥኩት፡፡ በወቅቱ የተሰማኝን ትክክለኛ ስሜት እና አሰተያየቴን ሰጠሁት ሀሳብ ሲቀበል ያስቀናል፡፡ ብዙ ጊዜውን አዲሱ አልበሙ ላይ እያጠፋ እንደሆነ ነገረኝ፡፡ አልበሙን አውጥቶ ህዝቡ ጋር ያለውን ስሜት ለማወቅ እንደጓጓ ፊቱ ላይ ያስታውቃል፡፡ ሙሌ ደስ በሚል ነፃነት ግጥም እና ዜማ የሰጣቸውን ድምፃዊያን እየነገረኝ ከኤፍሬም አማረ ጋርም ተሸንፌያለሁ ቁጥር ሁለትን ሊሰሩ እንዳሰቡ እያጫወተኝ ስቱዲዮ ደረስን፡፡ ፕሮግራሜን የምጀምረው አንተ ቀጥታ ከስቱዲዮ ሆነህ በምታዜመው ዜማ ነው ‹‹ተዘጋጅ›› አልኩት ታዛዥነት ደሙ ውስጥ አለ! በደስታ ‹‹ተሸንፌያለሁን›› ያለ ሙዚቃ መሳሪያ በድምጹ ብቻ አንጎራጎረው ድምፁ የሆነ ምትሀት አለው ሳታውቀው ኤሌክትሪክ የያዘህ እስኪመስልህ ይነዝርሀል፡፡ ሙሌ በቃ ይችላል!! በጣም በሳቅ የታጀበ ቆይታ አድርገን ተለያየን፡፡ ሙሉአለም ስላጋጠመው ህመም ድምጻዊ ደሜ ሉላ ከስቱዲዮ እየወጣን ተደውሎለት ነገረን በጣም ነበር የተረበሽነው፡፡ በቀጣይ ፕሮግራሜ ላይ ከጊልዶ ካሳ (በጣም መመስገን ያለበት ባለሙያ ነው ጊልዶ) ስለሙሌ አጠቃላይ ሁኔታ በስልክ ገብቶ ቆይታ አደረግን በወቅቱ ጊልዶ ካነሳቸው ሃሳቦች መካካል ሙሌን ለማገዝ የተቋቋመው ኮሚቴ ኮንሰርት ሊያዘጋጅ እንደሆነ ነበር በቃላቸውም መሰረት ‹‹ለጋሽ ነኝ›› የተሰኘ የሙዚቃ ኮንሰርት መስከረም 17 በሞዛይክ ሆቴል አሰናድተዋል፡፡ መደበኛ 300 ብር VIP 500 ብር የኮንሰረቱ መግቢያ ዋጋ ነው፡፡ አንድም በተወዳጅ ድምፃዊያን ስራዎች እየተዝናኑ አንድም ተወዳጁን ድምጻዊ ሙሉአለም ታከለ ራህዋን እያገዙ ጥሩ ጊዜ እንዲያሳልፉ ጥሪ ተላልፏል፡፡ ሙሌን ዳግም ሲስቅ እንድናየው እና ጤናው ተመልሶ የጓጓለት አልበሙንም አውጥቶ በጋራ እንድንደሰት አምላክ ይርዳን፡፡
#ከተባበርንእንችላለን!!
#ለጋሽነኝ
እዮብ ሰብስቤ
ሙሉአለም ታከለ ራህዋ ምን ያህል ራሱን ለጥበብ አሳልፎ የሰጠ ድምፃዊ መሆኑን ያወኩት ገና ሎሚ ሽታ የራዲዮ ፕሮግራሜ ላይ እንግድ ሆኖ ሊቀርብ ወደ ስቱዲዮ እየሄድን በነበረን ቆይታ ነበር፡፡ አዲሱ ስራዬን ስማው እስኪ አለኝ ሲበዛ ትሁት ነው ‹‹አምሮብሻል›› የተሰኘውን ዜማ ነበር ያኔ አልተለቀቀም ነበር፡፡ አዳመጥኩት፡፡ በወቅቱ የተሰማኝን ትክክለኛ ስሜት እና አሰተያየቴን ሰጠሁት ሀሳብ ሲቀበል ያስቀናል፡፡ ብዙ ጊዜውን አዲሱ አልበሙ ላይ እያጠፋ እንደሆነ ነገረኝ፡፡ አልበሙን አውጥቶ ህዝቡ ጋር ያለውን ስሜት ለማወቅ እንደጓጓ ፊቱ ላይ ያስታውቃል፡፡ ሙሌ ደስ በሚል ነፃነት ግጥም እና ዜማ የሰጣቸውን ድምፃዊያን እየነገረኝ ከኤፍሬም አማረ ጋርም ተሸንፌያለሁ ቁጥር ሁለትን ሊሰሩ እንዳሰቡ እያጫወተኝ ስቱዲዮ ደረስን፡፡ ፕሮግራሜን የምጀምረው አንተ ቀጥታ ከስቱዲዮ ሆነህ በምታዜመው ዜማ ነው ‹‹ተዘጋጅ›› አልኩት ታዛዥነት ደሙ ውስጥ አለ! በደስታ ‹‹ተሸንፌያለሁን›› ያለ ሙዚቃ መሳሪያ በድምጹ ብቻ አንጎራጎረው ድምፁ የሆነ ምትሀት አለው ሳታውቀው ኤሌክትሪክ የያዘህ እስኪመስልህ ይነዝርሀል፡፡ ሙሌ በቃ ይችላል!! በጣም በሳቅ የታጀበ ቆይታ አድርገን ተለያየን፡፡ ሙሉአለም ስላጋጠመው ህመም ድምጻዊ ደሜ ሉላ ከስቱዲዮ እየወጣን ተደውሎለት ነገረን በጣም ነበር የተረበሽነው፡፡ በቀጣይ ፕሮግራሜ ላይ ከጊልዶ ካሳ (በጣም መመስገን ያለበት ባለሙያ ነው ጊልዶ) ስለሙሌ አጠቃላይ ሁኔታ በስልክ ገብቶ ቆይታ አደረግን በወቅቱ ጊልዶ ካነሳቸው ሃሳቦች መካካል ሙሌን ለማገዝ የተቋቋመው ኮሚቴ ኮንሰርት ሊያዘጋጅ እንደሆነ ነበር በቃላቸውም መሰረት ‹‹ለጋሽ ነኝ›› የተሰኘ የሙዚቃ ኮንሰርት መስከረም 17 በሞዛይክ ሆቴል አሰናድተዋል፡፡ መደበኛ 300 ብር VIP 500 ብር የኮንሰረቱ መግቢያ ዋጋ ነው፡፡ አንድም በተወዳጅ ድምፃዊያን ስራዎች እየተዝናኑ አንድም ተወዳጁን ድምጻዊ ሙሉአለም ታከለ ራህዋን እያገዙ ጥሩ ጊዜ እንዲያሳልፉ ጥሪ ተላልፏል፡፡ ሙሌን ዳግም ሲስቅ እንድናየው እና ጤናው ተመልሶ የጓጓለት አልበሙንም አውጥቶ በጋራ እንድንደሰት አምላክ ይርዳን፡፡
#ከተባበርንእንችላለን!!