ግጥም ብቻ 📘
67.6K subscribers
1.53K photos
31 videos
61 files
174 links
በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።

@getem @serenity13
@wegoch @Words19
@seiloch @shiyach_bicha
@zefenbicha

@leul_mekonnen1
Download Telegram
ኣባ ይፍቱኝ !
(በዕውቀቱ ስዩም)
.
.
ሲኦል አለ ሲሉኝ፤ የለም ብየ ክጀ
የባልቴት ተረት ነው፤ በማለት ቀልጀ
አውቄ በድፍረት፤ በድያለሁና
ያንጹኝ በንስሃ፤ ያንሱኝ በቀኖና
ሲኦል ከነጭፍራው፤ በጉም ተሸፍኖ
እንዴት ሳላየው ኖርኩ፤ ካጠገቤ ሆኖ?
አባ ይፍቱኝ...
ሰይጣን ብሎ ነገር፤ የተጭበረበረ
ዋዛ ነው ቧልት ነው፤ ብየ ኣስብ ነበረ
ይሄው እውነት ሆኖ፤ ዋዛና ተረቱ
ባይኔ በብረቱ...
ዲያብሎስን አየሁት፤ በሸሚዝ ዘንጦ
እልፍ ግዳይ ጥሎ፤ ቸብቸቦ ጨብጦ፡፡
።።።
አባ...
ልክ እንደ ብርሌ፤ አጥንት ሲከሰከስ
አባይን አዋሽን፤ የሚያስንቅ ደም ሲፈስ
ለምለም ፍጥረት ሁላ፤ ወደ አመድ ሲመለስ
ልክ እንደ ሃውልት ጧፍ፤ ምስኪኖች ሲጋዩ
ምድጃው ዳር ሆነው፤ ይሄንን እያዩ
ገሃነም ከላይ ነው፤ ብለው መሳትዎ
እስዎ እንደፈቱኝ ፤ እግዚሃር ይፍታዎ።

@getem
@getem
@gebriel_19
1👍1
#ዝክረ ሙሉ ጌታ ተስፋዬ❤️❤️...!!!

የወፍዬ ግጥም ደራሲ ነው ባለቅኔ ሙሉጌታ ተስፋዬ ...ወፍዬን ከሁለት ልጆቹ ቀጥላ 3ተኛ ልጄ ናት ይላል አያ ሙሌ። ማንም አማርኛ ተናጋሪ ፍጡር በህይወት ዘመኑ ወፍዬን ቢያንስ አንድ ግዜ ሊሰማ ግድ አለበት ይል ነበር አያ ሙሌ። አያ ሙሌ በተለይም የባለቅኔ ምህላ በሚል ስራው በጣም ይታወቃል። ወፍዬ ከሙዚቃም በላይ ነው...ይህ ግጥም በህይወት ተክለሰውነት ላይ ያለን የፍትህ መጓደል በስንኞቹ መነፅር ያሳያል...ስለህይወት ውጣውረድና እንግልት ይተርካል.....ተመስገን ብሎ ስለማደር ሰማያዊ ህይወትን ስለመሻት ያትታል...ስለ ሰው ከንቱነት ይፈላሰፋል....አንዲትን ከመንጋው የተገፋች ሴት እውነት....ፍትህ ስላጣች ሴት ያወጋል በሰውኛና ተምሳሌታዊ ዘይቤም ተቀንብቧል ይህን ሁሉ በውስጡ ያዘለው ይህ ያያ ሙሌ ግጥም ዜማ ታክሎበት በአበበ ተካ ሲንጎራጎር ደግሞ በስንጥቅ ገላችን ላይ ሰርጎ የመቅረት የሆነ አንዳች የህይወትን ስንክሳር በመንገር ጥምን የማርካት ባህሪ አለው እስቲ እናንተስ ምን ትላላችሁ? ይችትላችሁ ሙሉ የሙዚቃዋ ስንኝ።

(ወፍዬ)
ከአበበ ተካ ዘፈን
......
ጭራ ጭራ የምታድረው (2)
ጭራ ለቅማ የምታድረው (2)
እንዴት አስናቀችኝ
ቀድማኝ ጎጆ ወጥታ ጎጆ አስተማረችኝ
ጎጇቤት ጎጆ እኔን ወፍዬ አስቀናችኝ
……..
ምነው ባደረገኝ
የሷ ጋሻ ጃግሬ
እንደምንም ብዬ እኔም ጥሬ ግሬ
ያገዳ ጎጆዬን ባቆምኳት ማግሬ
አጉል በቃኝ ላይል
አይን አይቶ ገምቶ
ወይ ሞልቶ ላይሞላ
ጆሮ አይችሉ ሰምቶ
እንዴት ጎጆ ይቅር
አርሶና ሸምቶ
……..
ገመና ከታቹን የሳር ቤት ያማረሽ
ሚስጥረ መለኮት ማነው ያስተማረሽ (2)
ካፈር ክዳን ጎጆ መሬቱን ፈልፍሎ
ከሰማይ ቤት እጣሽ ማን በሰጠኝ ከፍሎ (2)
………..
እኔን እኔን እኔን ይብላኝ (2)
እኔን አይኔን እኔን ይብላኝ (2)
የቀን ሰው ሌት አፈር
ልቤ እሩቅ አሳቢው
ቅርብ አድሮ ሲደፈር
ምን ነበር ቢቆጨው ጎጆ አጥቶ ከማፈር
………
ፈጣሪዋን አምና ያፏን ጥሬ ሰጥታ
ለጭሮ አዳር ውሎ በዝማሬ ወጥታ
አዳኝ እንዴት ያጥቃት ፍርድና ዳኛ አጥታ
አጣው ነጣው ብላ እንደሰው ባይከፋት
ምፅዋት ባትለምን ትርፉን ባንደግፋት
ጎጆዋ ለቻላት ምን ነበር ባንገፋት
………
ታማ ትንፋሽ አጥሯት ደክማ ስታጣጥር
ማን ያቃናት ይሆን ውለታ ሳይቆጥር (2)
ወልዶ ማሳደጉን ብዙ ሰው ቢያውቅበት
ያፉን ማን ይሰጣል የጁ ሲርቅበት (2)
እህህ ወፊቱ እሁሁ ወፊቱ እህህ ወፍዬ እህህ ወፊቱ እህህ ወፍቱ (8)

#ምንጭ:-ስንታየሁ እንደከተበው

እሱ ወፊቱን❤️የአያ ሙሌን ስራ አስታውሶ ሲዘክርልን ሲከትብልን ነፍሳችን ደስ ደስ አላትና...በሚጎመዝዘው ድምፃችን ተጫወትናት👇👇👇

@balmbaras
ተረኛ ነህ ተነስ !

(ሚካኤል አስጨናቂ)

።።።።።።።።።።።።።።።

#እግዜርን ቀስቅሱት!

ከተኛበት አንቁት.. .

ዝም ብለህ ነበር ፥ አሸልበህ ነበር

ሲተራመስ ሀገር ፥ ቅጡን ሲስት መንደር

ብላችሁ ንገሩት! 

#አርምሞህ አይሎ ፥ እሳት ሆኖ ፈጀን

እንዳበደ ውሻ ...

አቅሉን እንደሳተ ፥ እኛን አናከሰን 

እንባችን ፈሰሰ 

ባለም ተዳረሰ 

ክብራችን ተጣለ 

ኩራትም ጎደለ 

አቀርቅረን ቀረን 

ጀርባ ሰጠን ዘመን

#በእረፍታችን ማግስት ፥ በሞታችን ሳልስት

"ኩራትን አክብሩ" ፥ ብሎ የሚቧልት

ተነሳብን መንግስት !

አሁን ምን ይሉት ነው ?

እንዲህ ያለ ፈሊጥ ፥ የነገር ጨዋታ

የኩራት ቀን ማክበር ...

ከራት በሞተበት ፥ የመቃብር ቦታ?

ብላችሁ ጠይቁት !

ጎደልን !

ጎደልን!

ከክብር ተጣልን ...

መውደድ ፅፈት ሆኖ ፥ ቀረ በወረቀት 

ፍቅር በቃል ወርዶ ፥ ሰማን እንደተረት

ህዝብህ ሽንቁር ሆነ ፥ ጠፋ አንዳች ውታፍ

ገላውን ገረፈ...

እርሱ ባበጃጀው ፥ በገመደው ጅራፍ ።

ብላችሁ ንገሩት!

#አሁን ምን ይሉት ነው ?

ፍቅር በሞተበት ፥ በሰነፎች ሀገር 

"የፍቅር ቀን" ብሎ ፥ የቃል ፍቅር ማክበር?

ብላችሁ ጠይቁት ! 

ዝም ያለም እንደሆን.. .

እንዳምናው ካቻምናው ፥ እንደዛኛው ዘመን 

ዛሬ ቀን ከፋብህ 

የስላቅ ጨዋታው ባንተም ደረሰብህ ።

የእኛ ቤት ፈርሶ ...

ቅጥራችን ተድሶ ...

ዝም ብለህ ስታፌዝ ፥ ስትስቅ በሰው ለቅሶ

ያንተም ቤት ነደደ ፥ መቅደስህ ፈራርሶ ።

አሁንስ ምን ቀረህ?

እናትህ ስትነድ ፥ እሳት ሲለቁባት 

በል ሰይፍህን ምዘዝ ፥ ዝምታህን ሻራት ።

ብላችሁ ንገሩት.. .

እግዜሩን ቀስቅሱት !!

@getem
@getem
@getem
#ዝክረ ሙሉ ጌታ ተስፋዬ

ለሰዓት እላፊ !
❤️❤️❤️

በመጨረሻም ሁለት ግጥም በድምፅም በፅሁፍም ጀባ ብለን እንሰናበት🙏


ሙሌ አባ መንገዴ


አስያ አስያ፣
ንኡድ ቃል አምሳያ፣
እንኪ ስላንትያ፣
እሸትሽ ቅኔ ነዉ፣ ገላሽ ቦለቅያ፣
አቦ በየጁ ሞት፣ አቦ በወልዲያ፣
አቀብይኝ ዛሬ፣
ቅኔ እምኩልበት ፤ ቅኔ መሞሸሪያ፤
ትመጫለሽ አሉ፣
በ “ሙልየ..” ሲሉሽ ፣
የጁ ኪቢ ቃሉ፤ ማክሰኞ ገበያ፡፡
አስያ ጨብራሪት፣
የሃራ ወበሎ ፤ የታች ቆላይቱ፣
ጨብረር ጨብረር በይ፣
ተንጎማለይበት ፤ ነይማ ሸጊቱ፣
ወፈፍ ወፈፍ በይ፣
በጎጆየ ታዛ፣ አልፈሽ በምርጊቱ፡፡
ሀድራዉ ከሞቀበት፣
ቱፍታው ከሞላበት ፤ ከእነ ኩሌ ማጀት፣
ሀቂቃ አይደለም ወይ?
ካ'ስያ ጋር ኑሮ ፤ ካ'ስያ ጋር ማርጀት።
አውገረድ አስያ ፤
በበልጅግሽ ባሩድ፣ ባልቤንሽ ማንገቻ፣
እንደ ንጉስ አሽከር ፤
አሻቅቦ ያያል ፤ ቀልቤ አንችኑ ብቻ፤
ምን ያድርግ ብለሽ ነው፤
ወትሮም ከላይ ቤት ነዉ፣ ቅኔና ኮርቻ፡፡
ተገማሸሪበት ፤
ቀብረር ቀብረር በይ፣ አስያ በሞቴ፣
አህሪቡ ስትይኝ ፤
ጅስሜ ይበረታል ፤ ይጠናል ጉልበቴ ።
ከሙሉጌታ ጋር፣
ከሙሉ ሸጋ ጋር፣
ጉባርጃ ማርያም ላይ ፤ ያሰርሽዉ ቃል ኪዳን፣
እኔንም ዘንድሮ ፤
ጠራኝ ግጠም አለኝ፣ አወደኝ እንደእጣን፡፡
እኔም እንደ ሙሌ፣ እንደሙሉጌታ፣
ቀየዉ እንዳስከፋዉ፣ እንደቆላ ሽፍታ፣
ግጠም ግጠም አለኝ፣ የያዘኝ በሽታ፡፡
እገጥማለሁ እንጅ፣
በየበራበሩ ቅኔ ዛር አለብኝ፣
ላዩን በውድመን ፤
ታቹን በሶደማ ፤
አስያ ጨብራሪት፣ ወስዳ ሸሽጋብኝ፡፡
ልለማመን እስቲ፣
በእነነየ ጉፍታ ፤ በየጁ ቀለበት፣
ልመጀነዉ እስቲ፣
በአውገረድ ሹምባሽ ቤት ፤የላስቴን አቀበት፣
እንደግሽር ገላ፣ እንደወዳጅ እብለት፣
ምርኩዝ የሚሆነዉ፣ ለታፈረ ጉልበት፣
ጠብቆ ሲሰፋ ነው ፤ ቅኔና ዘለበት፡፡
ሀየ በል ገለሌ፣ እምቢ በል ጃዉሳ፣
ልቤ “..ቸ..” በል አለኝ “..ቸ..” በል ደንገላሳ፣
ብረር ብረር አለኝ፣ ቅኔ ቀለም አንሳ፣
ወትሮም ወደ ላይ ነዉ፣ ቅኔና ግሪሳ፣
ግጠም ግጠም አለኝ ፣ በልጅግህን አንሳ፣
አውቃለሁ አምናለሁ፤
የሞት ባልንጀር ነዉ፣ ቅኔና ወሳንሳ፡፡
አስያ ከገባች፣ ከማጀቷ ወጥታ፣
ጎዝጉዙልኝ ካለች፣ ወዳጃ ተጠርታ፣
ጀማዉ ከደመቀ፣ ቅጥሩ ከተፈታ፣
ግጠም ግጠም አለኝ፣ እንደሙሉጌታ፡፡
አያ ሙሌ ሆዴ፣
ቅኔ እሳት አመዴ፣
ከርታታዉ ዘመዴ፣
እኔ አለሁህ ልበል? አንተ አለሀኝ እንዴ?
ሰገነት ባትወጣ፣ ግብርህ ባይታወቅ፣
በሺህ ጋዜጠኛ፣ ስምህ ባይዳመቅ፣
በቲፎዞ ባሩድ፣ ባይሞቅ ያንተ ሽታ፣
በጭብጨባ ባይድን፣ ያንተ ሆድ በሽታ፣
ቃል አልተሸነፈም፣ ቅኔህ አልተረታ፣
“ታላቁ ሰዉ መጣ”፣
“ባለቅኔዉ መጣ”፣
“ያ ደራሲዉ መጣ”፣
ብለዉ ባይሰግዱልህ፣
ብለዉ ባይጮሁልህ፣ ምን ግድህ ምን ግዴ፣
አትንሰፈሰፍም ፣ለሹመት ለጓንዴ
ስሙልኝ አያምርህ፣ እንደቆላ ገዴ፣
አቦ ሆድ ይመርቅ፣ ሙሌ አባ መንገዴ፡፡

((( ጃ ኖ )))💚💛❤️

(( ማስታወሻነቱ ለባለቅኔው
ሙሉጌታ ተስፋዬ ❤️❤️❤️) )



@balmbaras
@getem
@getem
👍1
#ዝክረ ሙሉጌታ ተስፋዬ ( አያ ሙሌ )❤️


ሙሉ-- ጌታ!!!!!!!


ቅኔን ያህል ክህነት፤
አረሆን ያህል ሹመት፤
ካማልክቶቹ ዘንድ፤ ተሰጥቶት በደቦ፤
የብእሩ ልሳን፤
ሰው በሚባል ቅኔ፤
ሰው በሚባል ታምር፤ ዙሪያውን ተከቦ፤
በሰው ሳቅ ረብቶ፤ በሰው እንባ ባክኖ፤
ያም ለኔ ያም ለኔ፤
ለኔ ሁን እያለ፤
ግብር ቢደረደር፤ በጎጥ ልቡ ባዝኖ፤
እሱማ አጃኢብ ነው፤
ሰም ቅኔውን ፈታው፤ ለሁሉም ዘብ ሆኖ።


ዘብ እንጅ ዘብ አደር፤
ቋሚ እንጅ፤ ወጥቶ አደር፤
ያዳም ጎጆ ሲፈርስ፤
ሰብቅታኒ ብሎ፤ በእምባው የሚገደር፤
ዘማች የቀናው ቀን፤
ዳቦውን አግምጦ፤
ስለ ስሟ ማርያም፤
ቀን የሚሸኝበት፤ ቆሎ የሚበደር።


ሰውን ያህል ሰማይ፤ ሰብን ያህል ፀጋ፤
ኑሮን ያህል እንቅልፍ፤ ሞትን ያህል አልጋ፤
ተሸክሞ ሚዞር፤ በነጋ በጠባ፤
በጥውልግ ነፍስያ፤ በንጣት ሲላጋ፤
መዳኒት በራቀው፤ በማይቆም ፍለጋ፤
ህመሙ ሚሽረው፤
ወይ በቅንጣት ቅኔ፤ ወይ በድፍርስ እንባ።


ሰማያት ተቀደው፤ እንባ ካላዋሱ፤
አእዋፍ በማለዳ፤
አፍ መሻሪያ ቅኔ፤
እጅ መንሻ አምሃ፤ ዜማ ካልደረሱ፤
ይኸ ባለቅኔ፤
ቅኔ ማር ካልነካው፤ ካልደረሰ ምሱ፤
ዝናብ ቢጥል እንኳ፤
መልካው አይወረዛ፤ ወንዞችም አይፈሱ።


ምን ጎተራ ቢጎድል፤ አውድማው ቢሳሳ፤
ምን መሬት ብትከዳ፤ ሰማይ ጠል ቢነሳ፤
አፍ ሳይሽር ማለዳ፤
ከማእዱ በፊት፤
የህጣናት እምባ፤ ሲቃ እየቀደመ፤
አባት በልጁ ፊት፤
አባትነት ጎድሎት፤ከፈን እያለመ፤
ይህን ባዬ ጊዜ፤
ምስኪን ባለቅኔ፤
ጎደለ ወይ ብሎ ፤
ፈረሰ ወይ ብሎ፤ ልቡ ይጨነቃል፤
ስማኝ ኧረ ስማኝ፤
እያለ አዶናይን፤ ሰርክ ይጨቀጭቃል፤
ከጭቅጨቃው ወርዶ፤
ከመንበረህ የለህ፤
የለህም እያለ፤
ዘመን ሚያሻግር፤ ውብ ቅኔ ያፈልቃል።


ስለ ፍቅር መፃፍ፤
ስለ እንባ መቀኘት፤
ስለ ርሃብ መደስኮር፤ ምን ያቅታል ወጉ፤
ምን ያቅታል ደግሞ፤
ስለ እርሻው መንደቅደቅ፤
ስለ በሬው ማውራት፤ ከተማ መሃል ላይ እያረገረጉ።
ውነቴን ውነቴን፤
ሽርፍራፊ ቃላት፤
ማዳወር አይከብድም፤
የቃል ጮማ መቁረጥ፤ በየጥጋጥጉ፤
አዳ ምን ዋጋ አለው፤
ስለ ውጋት መፃፍ፤
ውጋት አያክምም፤ አብረው ካልተወጉ።


ግን ፤
ደግሞ ግን፤
ፍቅር መሆን እንጅ፤
እንባ መሆን እንጅ፤
ሩህሩህ እንስፍስፍ፤በብእርም በእውንም፤
በብእር ደግ ሆኖ፤
በሩን የሚዘጋ፤
እሱም አይፈልገን፤ እኛም አንከጅልም።


ብእር ቀለም ቢያጥረው፤ በላቡ እየፃፈ፤
ላቡ ሲደርቅበት፤ ደም እየቀፈፈ፤
ህላዌና ተስፋ፤
ቅኔና ሰውነት፤ እየተጠራሩ፤
ከደም የተቀዳ፤
ከመቅኖ ያደረ፤ ህያው ቅኔ ሰሩ፤
በቃ፤
ይኸው ነው ማጀቱ፤ ይኸው ነው ትዳሩ።


ርስቱን፤
ጠፍ ድስቱን፤
ልጅ ሚስቱን፤
በፊደል ተክቶ፤
ያባትነት እጁን፤
በቅኔ እያሰላ፤ ምስኪን ልቡን ሰጥቶ፤
የዘረ ሰብ ቀልቡን፤ ዳር ከዳር ዘርግቶ፤
በነፍስያ ሀቂቅ፤
የቀልብያን ስስት፤ በቸር ቅኔ ዘግቶ፤
በክፋት ምንዳ ላይ፤
የተንኮልን ጫካ፤ በሳቅ ጦር ረቶ፤
ከጉድለት ባርነት፤
በምህላ በአርምሞ፤ ራሱን አንፅቶ፤
ሙሉ-ጌታ ሆነ፤
በእንባና በቅኔ፤ ጎዶሎውን ሞልቶ።


(((( ጃ ኖ )))💚💛❤️

(((ለባለቅኔው ሙሉጌታ ተስፋዬ))

@balmbaras
@getem
@getem

አያ ሙሌ በሀይል ነፍፍፍፍፍ ብዙዙዙዙ እልፍ አእላፍ ወድሀለው❤️❤️❤️ ነፍስህን በገነት ያኑራት ! !!!!!!
ያያሙሌ ስንብት


“ኸረ ይሄ ሰው ነብይ ሳይሆን አይቀርም፡፡እንዲችው ሌሊቱን ሙሉ ለጆሮ የሚከብዱ
ነገሮችን ሲናገር ነው ያነጋው”
አያ ሙሌ ድንገት አምርሮ የሚያለቅስባቸው ጊዜያትም ነበሩ፡፡ በግንቦት ወር 1996 አሁን
ማረፍ ነው የምፈልግው ብሎ ቤት ተከራየ፡፡ ወይዘሮ ከበቡሽን ሲሰናበትም…” ነገርኩሽ
አልሰማሽም፣ ልሄድ ነው አልረሳሽም” ብሏቸው ነበር፡፡
የፒያሳን አቀበት እየወጣ ቴድሮስ አደባባይ ሲደርስ ድንገት ሐሳቡን ቀይሮ ወደ ጎላ ሚካኤል
ዞሮ አማትቦ ዘለግ ላለ ሰዓት ፀለየ፡፡ ሦስት ቁጥር አውቶብስ ይዞ ዓለምገና ሄደ፡፡ አንድ
ሆቴል ዉስጥ 13 ቁጥር መኝታ ይዞ አደረ፡፡ ጓደኞቹ ግማሽ በድን ኾኖ ከሆቴሌ ሲያወጡት
የሆቴሉ ዘበኛ እንዲህ ተናገሩ፡፡
“ኸረ ይሄ ሰው ነብይ ሳይሆን አይቀርም፡፡እንዲችው ሌሊቱን ሙሉ ለጆሮ የሚከብዱ
ነገሮችን ሲናገር ነው ያነጋው”
በነገታው ነሐሴ 28፣ ቀን 1996 ዓ.ም አረፈ፡፡

ሰላም እደሩልኝ!💚

@balmbaras
@getem
ቆንጆ ነኝ
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
ስላንቺ ቁንጅና
ስላንቺ ቁመና
ከንፈር እና ዳሌ
ጥርስና ተረከዝ ፣ ፀጉር ገለመሌ
ለጡት ለወገብሽ ፣ ለፀባይሽ ጭምር
በግጥም በዝርው ፣ ባድናቆት ስዘምር
እስከዛሬ ድረስ...
ውበትሽን አግንኜ ፣ ሰርክ መለፈፌ
እኔ ስለራሴ ...
አንዳች ቀን እንኳን ፣ ግጥም አለመፃፌ
ሲትጠዪኝ ቆጨኝ
ቢሆንም ቆንጆ ነኝ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እርግጥ ነው ብዙዎች...
ስለኔ ሳወራ ፣ ድንገት ያኮርፉኛል
ያንተን ሌሎች ያውሩ ፣ ብለው ይነግሩኛል
እኔን ከኔ በላይ...
እርግጠኛ ሆኖ ፣ ሌላ እንዴት ያውቀኛል?!
።።።።፣፣
እናም እኔ ማለት...
ቁመቴ ከአክሱም ፣ በእጥፍ ይረዝማል
ጣፋጭ አንደበቴ...
መስማት ለተሳነው ፣ ለስልሶ ይሰማል
ውብ አረማመዴ...
እንኳን መንገደኛን ፣ መንገድን ያቆማል፡፡
፡፡፡፡፡፡
የከንፈሬ ወዙ ፣ ጥፍጥናው አያልቅም
ጥርሴ ሺ ገዳይ ነው!
ሺ ሟች ላለማየት ፣ ኗሪ ፊት አልስቅም፡፡
ከአይኔ ብሌን ውስጥ ፣ ብርሐን ይፈልቃል
አይኔን ያየ ሁሉ
ልቡን አሳውሮ ፣ በፍቅር ይወድቃል፡፡
፡፡፡፡፡
የገላዬ ጠረን ፣ ከሽቱ እጥፍ ነው
መልካም ጠረን ሁሉ...
አለ ባሉት ስፍራ ፣ እኔ አለሁ ማለት ነው፡፡
ፀባየ ትሁት ነኝ ፣ ምጡቅ ነው እውቀቴ
ግርማ ሞገሳም ነው ፣ ተክለ ሰውነቴ
ያየኝ ይወደኛል
የወደየኝ ሁሉ ፣ መቼም አይጠላኝም
ከዚ በላይ እንኳን...
ብዙም ስለራሴ ፣ የማውቀው የለኝም፡፡
እንደውም እንደውም...
አልጎርርም እንጂ ፣
ያፈር ሰውነቴን ፣ በቁንጅና አብየው
ቆንጆ ማየት ሲያምረኝ ፣ራሴን ነው ማየው፡፡
ብቻ ግን ቆንጆ ነኝ!!!

@getem
@getem
@gebriel_19
የተከበራችሁ የ ግጥም ብቻ ቤተሰቦች

ሥዕል ብቻ ሚለው ቻናላችን ላይ የ ሥዕል ውድድር እየተካሄደ ይገኛል ገብታችሁ ይመጥናል ለምትሉት ሥዕል ድምዕ እንድትሰጡልን በ አክብሮት እንጠይቃለን 🙏

@seiloch
@seiloch
@seiloch



ግጥም ብቻ
ሥዕል ብቻ
@gebriel_19
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
///// "አልሰጥም!" ትያለሽ?/////

ይህን ሁሉ ግዜ
ይህን ሁሉ ወራት
መልሶ መላልሶ
ዘውትር ቢለምንሽ
"አልሰጥም!" ትያለሽ?
እንዲህ ተመችቶሽ
እንዲህ ተወልውለሽ
ሊፈርጥ የደረሰ
ዳሌ ተሸክመሽ
ትርንጎ ጉንጭሽን
በዲምፕል አስጊጠሽ
ውብ ከናፍርሽን
እንዲህ አሞጥሙጠሽ
በአሎሎ አይኖችሽ
ተድላን እያስነበብሽ
ይህ ምስኪን "እባክሽ?"
ብሎ ሲማፀንሽ
ድምፅሽን ከፍ አርገሽ
"አልሰጥም!" ትያለሽ?
በችግርሽ ዘመን
ነበረ ከጎንሽ
ሰው በሚያሻሽ ግዜም
ከቶም አልተለየሽ
የስኬትን እርካብ-
"ሀ" ብለሽ ስትርግጪ
ነበር ድጋፍሽ
የዝና ፈረስሽን ስትፈናጠጪ።
እኮ አሁን ያ አልፎ
ታሪክ ተቀይሮ
ሃሴት አስፈንድቆሽ
እሮሮሽ ተቀብሮ
ካንቺ ተመኝቶ
ካንቺ እግር ተደፍቶ
በ'ንባ ሲማፀንሽ
"አልሰጥም!" ትያለሽ?
ዛሬ ቀን ሞልቶልሽ
ተመልካች አግኝተሽ
በአንድናቂ ተከበሽ
በዝና ተውጠሽ
ረጅም ሽንጥሽን
ያለልክ መዘሽ
በወርቅ አልማዝ ዕንቁ
እንዲህ ተንቆጥቁጥሽ
በሃብት በልፅገሽ
ሁሉ ተርፎ ሞልቶሽ
ቁንጅና አረስርሶሽ
ውበት ተደፍቶብሽ
አንዳችም ሳታጪ
አንዳች ሳይጎልሽ
በረከት የሚያፈስ
ያን ገነት አንደበት
ያን ውብ አፍሽን
በ እምቢታ ሞልተሽ
"እባክሽን እቱ አንድ ሺህ ብር
ብድር"
ስጪኝ ብሎ ቢልሽ
እንዲህ ሲማፀንሽ
"አልሰጥም!" ትያለሽ???
እቱ ሙች! ክፉ ነሽ!!!

Hahahaha....
I Gotch you guys!
(መንግስቱ መ)

@getem
@getem
@getem
የቁንጅና ወራት
(በላይ በቀለ ወያ)
.
.
የወጣትነትሽን
የውብ ቁንጅናሽን
የሴት ተፈጥሮሽ..
ከሴትነትሽ ላይ - አውልቆ ለመጣል
‹‹ወጣት እድሜሽ ያልፋል
ውበትሽ ይረግፋል››
ቢሉሽ
የከጀሉሽ
ሊበሉሽ።
………….
እናም..
በሴት ተፈጥሮሽ ላይ፣
ወጣት እድሜሽ ቢያልፍም፣
ውበትሽ አይረግፍም፡፡
።።።።።።።።
ምክንያቱም…….
ከሴት ተፈጥሮ ላይ፣
ወጣት እድሜ ሲሸሽ - እርጅና አስከትሎ
ውበት ግን አይረግፍም!
እናት ከመሆን ጋር - ይመጣል ተኩሎ !!!

( በላይ በቀለ ወያ )

💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️

@getem
@getem
#ልቀቀን!
-
አንት ራስ-አምላኪ ፥ ለራስ ምስል ሰጋጅ
ያዙኝ ልቀቁኝ ባይ -
ቃልህ እንደ ንጉሥ ፥ ንግግርህ አዋጅ፣
ጉልበትህ የድመት ፥ ግሳትህ ያንበሳ
ዕንባህ ቅርር የሚል -
መሽቶ ማይነጋልህ ፥ ሥምህ ካልተነሳ፣...
ዋ! ብቻ ሙዚቃህ ፥ ሰርክ ማስፈራራት
ትን ይለን ይመስል -
አንተ ሳትባርከው ፥ የበላነው እራት፣...
.
ባክህ ተለመነን
ዛሬን እሺ በለን፣ ...
በፈጠረህ አምላክ ፥ ባበጀህ ከጭቃ
ባልቀጠርንህ ችሎት ፥ አትቁም ጠበቃ!!
.
ጣቶችህን ሰብስብ ፥ ደጃችን አትድረስ፣
እርግፍ አርገህ ተወን ፥ እንሙት ... እንጨረስ!
ግዴለም እንፈንዳ ፥ እንፍረጥ እንደ እንቧይ
ብቻ አንተ ልቀቀን ፥ ከቅዠትህ ሰማይ ፨፨
------------------------//------------------------
(በርናባስ ከበደ )

@getem
@getem
@getem