ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
ስለ ታቦቲቱ የባዕዳኑ መልከታ
...... #ካለፈው የቀጠለ.....
#ጀምስ_ብሩስ /james bruce/
____________________________
#የዓባይን ምንጭ ወይስ #ታቦቲቱን ፍለጋ ???
_________________________________


ባለፈው ጽሑፋችን ግራሃም ሐንኰክ የጠፋው ታቦት ዘራፊዎች/#Raiders_of_the_Lost_Ark/ በሚል ርእስ የተሠራውን የሆሊውድ ፊልም በ 1983 ናይሮቢ ውስጥ ካየ በኋላ ታቦቲቱን ለማግኘት እንደተነሳሳ ዓይተን ነበር። አሁን ደግሞ ጀምስ ብሩስን በሽፋን ስም ታቦቲቱንና መገኛዋን ለማግኘት ያደረገውን ምሥጢራዊ ጥረት እንመለከታለን።
#ከክርስቶፈር ደጋማ ሞት በኋላ "የክርስቶስ ሠራዊት" ስለ ኢትዮጵያ ለማወቅ የነበረው ጉጉት እየቀዘቀዘ ሲመጣ የስኮትላንዱ "ምሥጢራዊ የወንድማማቶች ማህበርም " ስለ ሰሎሞን ቤተ መቅደስና የቃል ኪዳኑ ታቦት የወረሳቸው አንዳንድ ምሥጢራዊ የሃይማኖት ሥርዓቶች ሲኖሩ በነዚህም ውስጥ ታቦቱ ጉልህ ሚና አለው።
በመሆኑም በዚህ ረገድ በድፍረቱና በቆራጥነቱ ስለሚታወቀውና ቴምፕላሮችን ካዳነው ከንጉስ ብሩስ ጋር የዘር ግንዱን ስለሚቆጠረውና ኢትዮጵያ በስፋት ስለጎበኘው የእስኮትላንዱ ተወላጅ ጀምስ ብሩስ መለመለ።
#ረጅሙና ግዙፉ ጀምስ ብሩስ ስኮትላንድ ውስጥ 1730 ተወለዶ ከፍተኛ ትምህርቱን በኤደን ብራ ዩኒቨርሲቲ ያጠናቀቀ ምሁር ነው። በትምህርቱ በኋላ ኢስት ኢንድያ በተባለ ድርጅት ተቀጥሮ ሠርቷል። ይሁንና በ1754 ባለ ቤቱ ስለሞተች በደረሰበት ብስጭት የተነሣ ከሀገር ወደ ሀገር መዘዋወር የጀመረ ሰው ነው።
የነበረው የቋንቋ ችሎታው በማጤንም በሰሜን አፍሪካ አልጀርስ ውስጥ የብሪቲሽ ቆንጽላ በመሆን እንዲሰራ ከመደረጉም ባሻገር ወደ ቅድስቲቱ ሀገር ወደ ኢየሩሳሌምም ተጉዟል። በቋንቋ ረገድ አረብኛ፣ፖርቱጋልኛ እንዲሁም ጥንታዊ የሆነውን የኢትዮጵያ ቋንቋ (ግእዝን) ያውቅ ነበር።
#ጀምስ_ብሩስ በ1759 የግእዝ ቋንቋ ያጠናበት ዋነኛ ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ ለመዝለቅ ላሰበው ጉዞ ዝግጅት ለማድረግ ሲሆን ከእርሱ በፊት ወደ ኢትዮጵያ ተጉዘው የነበሩ ሰዎችን የጻፏቸውንም በማንበብ በማጥናት ስለ ሀገሪቱ በቂ ዕውቀት ጨብጦ ነበር ዘዚያም 1768ወደ ካይሮ በመሄድ ታሪካዊ ጉዞዎን ለመጀመር ዝግጅቱን አጠናቀቀ።
ብሩስ ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ ምን አነሳሳው? እርሱ እንደሚለው የዓባይን ወንዝ ምንጭ ለማግኘትከ1768-1773በተከታታይ የተደረጉ ጉዞዎች( Travels to Discover The Source of Nile in The Years 1768-1773 የሚል ባለ 3ሺህ ገጽ መጻሕፍ በ5 ተከታታይ ጥራዝ ጽፎል። ቢሆንም ግን ቅሉ የዓባይን ወንዝ ምንጭ በትክክል እንኳ አላወቀውም፤አልደረሰበትም የዓባይ ወንዝ ጣና እንደሆነ አስፎሯልና
#ኢትዮጵያዊያን ሊቃውንት ግን የዓባይ ምንጭ ግሽ ዓባይ ሰከላ እንደሆነ እና ዋነኛ ምንጩም ገነት እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስን ዋቢ አድርገው ይገልጻሉ ፤ያምናሉ #ዘፍ 2÷10 -13 የሱ ዓላማ ታቦቲቱን ማግኘት እንጂ የዓባይን ምንጭ ማግኘት ስላልነበረ ነው ያን የሚያክል ባለ ብዙ ገጽ መጽሐፍ ጽፎ ከስተት የደረሰው ። በኢትዮጵያም ሁለት ዓመት ከቆየ በኋላ ሦስት የመጽሐፈ ሄኖክ ቅጂዎችን ሰርቆ ኮብልሏል።

ኢትዮጵያ አ.አ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ነሐሴ ፯ / ፳ ፻ ፲ ፫