ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
" #ቀርታ_ያስቀረችን_ምርጥ_ዘር "

ጊዜው ክረምት ወቅቱም የዘር የመከር ወቅት በመሆኑ ዘርና ፍሬ ዝናብና ጠል ገበሬና በሬ ያለ መነጣጠል ይነሱበታል ። የክረምት ወቅት ምሳሌያዊ ትርጉም ዘርፈ ብዙ ነው ። አንዱ ና ዋናው ግን የ5500 ዘመን ወይም የብሉይ ኪዳን ዘመን ፣ የመከራ ፣ የስቃይ ፣ የጨለማ ጊዜ ምሳሌ መሆኑ ነው :: ይኸውም ክረምት የ5ሺህ 500 ዘመን ወይም የብሉይ ኪዳን ምሳሌ ነው መባሉ በክረምት ጭጋግ ፣ ጉም ፣ደመና ይበረታሉ ነጎድጓዳት ይሰማሉ መባርቅት በርቀው ያስደነግጣሉ ይልቁኑ ደግሞ ውኃ ይሰለጥናል :: የክረምት ወቅት ሰቆቃ ይበዛዋል ይልቁኑ በስደት በደጅ ላሉ ሰውች ይብስባቸዋል “ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፤”
የሚለው የጌታችን ምክርም የዚህን የክረምት ወቅት ጠንካራነት ያሳያል። ማቴ24፥20

የ5500ዘመንም ዘመነ ፍዳ ዘመነ መከራ ዘመነ ጨለማ ነውና በእግረ አጋንንት ተገዝተን በሲዖል እሳት ውስጥ ተግዘን ኖረናል ። በክረምት ውኃ እንዲሰለጥን በብሉይ ኪዳንም ውኃ ሰልጥኖ ፍጥረትን አጥፍቷል ገኃነመ እሳት በርትቷል በክረምት ምድር በውኃ እረክታ ትረሰርሳለች መሬት ትጨቀያለች በብሉይም ሰዎች በኃጢያት ዝናብ በስብሰው በሰዶም ግብር ጨቅይተው ነበር በዚህ ሰበብም ፈጣሪና ፍጡር ሰማይና ምድር ሰውና መላእክት ነፍስና ሥጋ ተጣልተው ከርመዋል በመሆኑም ዘመነ ብሉይ (5500 ዘመን) ከአሰቃቂው የክረምት ወቅት ጋር በእጅጉ ይመሳሰላል ። በመካከላቸውም የጠብ ግድግዳ ተገንብቶ ቆይቷል ቤተ ክርስቲያን በዚህ ወቅት ዘሪ ሊዘራ ወጣ እያለች የመንገድ ዳር፣ የጭንጫ ፣የሾህ ልቡና ያላቸውን ምዕመኖቿን ልብ በስብከተ መልካም መሬት አድርጋ በወንጌሏ ታቀናዋለች ቃል ዘርታ ሕይወት ታጭዳለች ።

ዛሬ ዛሬ ዓለማችን ነጭ ጥቁር ሀገራችን ደግሞ ኦሮሞ ትግሬ አማራ ጉራጌ በመባባል ተከፋፈለዋል። ሁሉም ዘሩ ምርጥ ዘር እንደሆነ ያስባል ሌላው ዘር ሁሉ እንክርዳድ የሚመስለው ነቀዝ ብዙ ነው ። ከሰዶምና ከጎሞራ ቅጣት የተረፍንባት ምርጥ ዘራችን ድንግል ማርያም ነች። ሶሪያዊው ቅዱስ ኤፍሬም የመመኪያችን ዘውድ የድኅነታችም መጀመራያ ብሎ እንደጠራት ትምክተ ዘመድነ የምትባል እመቤታችን ነች ። ከእርሷ በቀር ምርጥ ዘር የሚባል የለንም ።
ይህች ንጽሕት ዘር ወርቅ ነች ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም በኃጢያት ጭቃ ከወደቁት ከአዳም እና ከሔዋን ዘሮች የተገች ዳግማዊት ሔዋን ብትሆንም የበደል ጥንት አልነካታም የመተላለፍ እድፍ አላጎደፋትም ስለዚህ በአዳም ገላ ውስጥ ታበራ የነበረች ነጭ እንቁ ነች።

ነቢየ ልዑል ቅዱስ ኢሳይያስ “የሠራዊት ጌታ #እግዚአብሔር_ዘርን_ባያስቀርልን_ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር።” ብሎ የተናገረላት ከኃጢያት መተዳደፍ በመንጻት ከከፋት ሥራ ሁሉ ቀርታ ከጥፈት ያስቀረችን ምርጥ ዘራችን እመቤታችን ነች። ኢሳ 1፥9 ይህችሁም ንጽሕይት ዘር በወርኃ ክረምቱ ማዕከላዊ ጊዜ በሆነው በነሐሴ 7 (ሰባት)በዛሬዋ ቀን ከሐናና ከኢያቄም ተጸንሳልናለች ይህ ቀን የእመቤታችን ብቻ ሳይሆን እያገዳደለን ካለው የዘረኝነት ግዳይ ዓለማችንንና የሀገራችንን ትንሳኤ የምታደርግበት የድኅነታችን ጽንስ መጀመሪያም ቀን ነው።

በክረምት ወቅት የሰማይ መስኮቶች ተከፍተው ዝናብ ለዘር ጠል ለመከር ይሰጣሉ ታዲያ ይህ ጊዜ ለትጉህ ገበሬ ምቹ ነው በሬውን ይጠምዳል መሬቱን ያርሳል ዘሩን ይዘራል ዝናቡን በጉድጓድ ያጠራቅማል መባርቅቱን ፣ ነፋሳቱን ይታገሳል። በመጨረሻውም የድካሙን ፍሬ አዝመራውን ያጭዳል በመከራ እንዳልዘራ በደስታ ይሰበስባል " በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ይለቅማሉ ። በሄዱ ጊዜ፥ ዘራቸውን ተሸክመው እያለቀሱ ተሰማሩ፤ በተመለሱ ጊዜ ግን ነዶአቸውን ተሸክመው ደስ እያላቸው ይመጣሉ ። መዝ (125) 126 ÷5 ሰነፍ ገበሬ በአንጻሩ ብርዱን ቸነፈሩን ተሰቆ ቤቱ ይተኛል እገሌ ከኔ ወገን ነው ደግ ነው እገሊት ከወንዝ ማዶ ናት አትመስለንም ባለፈችበት እንዳታልፉ በዞረችበት አትዙሩ የሚል ነው የአጥንት እንጂ የእህል ዘር የማያውቅ :: ዘረኝነት ኃጢያት ነው ኃጢያት ደግሞ ማጣት ማለት ነው ባለ ብዙ ዘሮች ነን የሚሉ ዘረኞች ሃይማኖቱን፣ ምግባሩን ፣ ፖለቲካውን ፣ ሥልጣኑን ፣ ዕውቀቱን፣ ውበቱን ፣ ሙቀቱን ፣ድምቀቱን፣ ዝናውን ፣ተሰሚነቱን የያዙ ይመስላቸው ይሆናል ነገር ግን አንዱም እንኳ የላቸውም አጥተውታል። ሰው ኃጢያትን (ዘረኝነት) ዘርቶ እንዴት አንድነትን ሊያጭድ ይችላል ??? በእኩልነት ሰበብ በኩይ ከከፋፈሉን በኃላ በእንድነት ደግሞ እንምራቹ አሉን በአንድ ገመድ ሁሉንም ከብቶች አስሬ ልምራቸው የሚል እረኛ የለም ቢኖር ግን ይህ ምንደኛ እንጂ እረኛ አይደለም ምክንያቱም ከብቶቹን በአንድ ታስረው ወደ ሚፈልጉት የልማት ጉዳና የሥልጣኔ ማማ መድረስ አይቻላቸውምና። አንዱ ወድቆ ሊላውን የሚጠልፍበት የውድቀት ትርምስ ነው የሚሆንባቸው ። ከዛም አልፎ ከለመለመው መስክ ሳይሰማሩ በረፍትም ውኃ ዘንድ ሳይቀርቡ ከናፈቁት በረታቸውም ሳይገቡ የነጣቂ ተኩላ ሲሳይ የጅብ እራት ሆነው ይቀራሉ ። “ኃጢአትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፥ ”ምሳሌ 22፥8 " ማሰር መፍትኤ የሚሆነው ጠባቂ ከሌለ ብቻ ነው! " ። እረኛ ካለ ገመድ ለምኔ ?


........ ይቆየን.............

@YEAWEDIMERITE
አዘጋጅ :- ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
ነሐሴ 7 ቀን 2012ዓ,ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (ተርቢኖስ ሰብስቤ)
" #ቀርታ_ያስቀረችን_ምርጥ_ዘር "

ጊዜው ክረምት ወቅቱም የዘር የመከር ወቅት በመሆኑ ዘርና ፍሬ ዝናብና ጠል ገበሬና በሬ ያለ መነጣጠል ይነሱበታል ። የክረምት ወቅት ምሳሌያዊ ትርጉም ዘርፈ ብዙ ነው ። አንዱ ና ዋናው ግን የ5500 ዘመን ወይም የብሉይ ኪዳን ዘመን ፣ የመከራ ፣ የስቃይ ፣ የጨለማ ጊዜ ምሳሌ መሆኑ ነው :: ይኸውም ክረምት የ5ሺህ 500 ዘመን ወይም የብሉይ ኪዳን ምሳሌ ነው መባሉ በክረምት ጭጋግ ፣ ጉም ፣ደመና ይበረታሉ ነጎድጓዳት ይሰማሉ መባርቅት በርቀው ያስደነግጣሉ ይልቁኑ ደግሞ ውኃ ይሰለጥናል :: የክረምት ወቅት ሰቆቃ ይበዛዋል ይልቁኑ በስደት በደጅ ላሉ ሰውች ይብስባቸዋል “ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ፤”
የሚለው የጌታችን ምክርም የዚህን የክረምት ወቅት ጠንካራነት ያሳያል። ማቴ24፥20

የ5500ዘመንም ዘመነ ፍዳ ዘመነ መከራ ዘመነ ጨለማ ነውና በእግረ አጋንንት ተገዝተን በሲዖል እሳት ውስጥ ተግዘን ኖረናል ። በክረምት ውኃ እንዲሰለጥን በብሉይ ኪዳንም ውኃ ሰልጥኖ ፍጥረትን አጥፍቷል ገኃነመ እሳት በርትቷል በክረምት ምድር በውኃ እረክታ ትረሰርሳለች መሬት ትጨቀያለች በብሉይም ሰዎች በኃጢያት ዝናብ በስብሰው በሰዶም ግብር ጨቅይተው ነበር በዚህ ሰበብም ፈጣሪና ፍጡር ሰማይና ምድር ሰውና መላእክት ነፍስና ሥጋ ተጣልተው ከርመዋል በመሆኑም ዘመነ ብሉይ (5500 ዘመን) ከአሰቃቂው የክረምት ወቅት ጋር በእጅጉ ይመሳሰላል ። በመካከላቸውም የጠብ ግድግዳ ተገንብቶ ቆይቷል ቤተ ክርስቲያን በዚህ ወቅት ዘሪ ሊዘራ ወጣ እያለች የመንገድ ዳር፣ የጭንጫ ፣የሾህ ልቡና ያላቸውን ምዕመኖቿን ልብ በስብከተ መልካም መሬት አድርጋ በወንጌሏ ታቀናዋለች ቃል ዘርታ ሕይወት ታጭዳለች ።

ዛሬ ዛሬ ዓለማችን ነጭ ጥቁር ሀገራችን ደግሞ ኦሮሞ ትግሬ አማራ ጉራጌ በመባባል ተከፋፈለዋል። ሁሉም ዘሩ ምርጥ ዘር እንደሆነ ያስባል ሌላው ዘር ሁሉ እንክርዳድ የሚመስለው ነቀዝ ብዙ ነው ። ከሰዶምና ከጎሞራ ቅጣት የተረፍንባት ምርጥ ዘራችን ድንግል ማርያም ነች። ሶሪያዊው ቅዱስ ኤፍሬም የመመኪያችን ዘውድ የድኅነታችም መጀመራያ ብሎ እንደጠራት ትምክተ ዘመድነ የምትባል እመቤታችን ነች ። ከእርሷ በቀር ምርጥ ዘር የሚባል የለንም ።
ይህች ንጽሕት ዘር ወርቅ ነች ወርቅ ከጭቃ ይገኛል ግን ጭቃ አይደለም እመቤታችንም በኃጢያት ጭቃ ከወደቁት ከአዳም እና ከሔዋን ዘሮች የተገች ዳግማዊት ሔዋን ብትሆንም የበደል ጥንት አልነካታም የመተላለፍ እድፍ አላጎደፋትም ስለዚህ በአዳም ገላ ውስጥ ታበራ የነበረች ነጭ እንቁ ነች።

ነቢየ ልዑል ቅዱስ ኢሳይያስ “የሠራዊት ጌታ #እግዚአብሔር_ዘርን_ባያስቀርልን_ኖሮ፥ እንደ ሰዶም በሆንን እንደ ገሞራም በመሰልን ነበር።” ብሎ የተናገረላት ከኃጢያት መተዳደፍ በመንጻት ከከፋት ሥራ ሁሉ ቀርታ ከጥፈት ያስቀረችን ምርጥ ዘራችን እመቤታችን ነች። ኢሳ 1፥9 ይህችሁም ንጽሕይት ዘር በወርኃ ክረምቱ ማዕከላዊ ጊዜ በሆነው በነሐሴ 7 (ሰባት)በዛሬዋ ቀን ከሐናና ከኢያቄም ተጸንሳልናለች ይህ ቀን የእመቤታችን ብቻ ሳይሆን እያገዳደለን ካለው የዘረኝነት ግዳይ ዓለማችንንና የሀገራችንን ትንሳኤ የምታደርግበት የድኅነታችን ጽንስ መጀመሪያም ቀን ነው።

በክረምት ወቅት የሰማይ መስኮቶች ተከፍተው ዝናብ ለዘር ጠል ለመከር ይሰጣሉ ታዲያ ይህ ጊዜ ለትጉህ ገበሬ ምቹ ነው በሬውን ይጠምዳል መሬቱን ያርሳል ዘሩን ይዘራል ዝናቡን በጉድጓድ ያጠራቅማል መባርቅቱን ፣ ነፋሳቱን ይታገሳል። በመጨረሻውም የድካሙን ፍሬ አዝመራውን ያጭዳል በመከራ እንዳልዘራ በደስታ ይሰበስባል " በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ይለቅማሉ ። በሄዱ ጊዜ፥ ዘራቸውን ተሸክመው እያለቀሱ ተሰማሩ፤ በተመለሱ ጊዜ ግን ነዶአቸውን ተሸክመው ደስ እያላቸው ይመጣሉ ። መዝ (125) 126 ÷5 ሰነፍ ገበሬ በአንጻሩ ብርዱን ቸነፈሩን ተሰቆ ቤቱ ይተኛል እገሌ ከኔ ወገን ነው ደግ ነው እገሊት ከወንዝ ማዶ ናት አትመስለንም ባለፈችበት እንዳታልፉ በዞረችበት አትዙሩ የሚል ነው የአጥንት እንጂ የእህል ዘር የማያውቅ :: ዘረኝነት ኃጢያት ነው ኃጢያት ደግሞ ማጣት ማለት ነው ባለ ብዙ ዘሮች ነን የሚሉ ዘረኞች ሃይማኖቱን፣ ምግባሩን ፣ ፖለቲካውን ፣ ሥልጣኑን ፣ ዕውቀቱን፣ ውበቱን ፣ ሙቀቱን ፣ድምቀቱን፣ ዝናውን ፣ተሰሚነቱን የያዙ ይመስላቸው ይሆናል ነገር ግን አንዱም እንኳ የላቸውም አጥተውታል። ሰው ኃጢያትን (ዘረኝነት) ዘርቶ እንዴት አንድነትን ሊያጭድ ይችላል ??? በእኩልነት ሰበብ በኩይ ከከፋፈሉን በኃላ በእንድነት ደግሞ እንምራቹ አሉን በአንድ ገመድ ሁሉንም ከብቶች አስሬ ልምራቸው የሚል እረኛ የለም ቢኖር ግን ይህ ምንደኛ እንጂ እረኛ አይደለም ምክንያቱም ከብቶቹን በአንድ ታስረው ወደ ሚፈልጉት የልማት ጉዳና የሥልጣኔ ማማ መድረስ አይቻላቸውምና። አንዱ ወድቆ ሊላውን የሚጠልፍበት የውድቀት ትርምስ ነው የሚሆንባቸው ። ከዛም አልፎ ከለመለመው መስክ ሳይሰማሩ በረፍትም ውኃ ዘንድ ሳይቀርቡ ከናፈቁት በረታቸውም ሳይገቡ የነጣቂ ተኩላ ሲሳይ የጅብ እራት ሆነው ይቀራሉ ። “ኃጢአትን የሚዘራ መከራን ያጭዳል፥ ”ምሳሌ 22፥8 " ማሰር መፍትኤ የሚሆነው ጠባቂ ከሌለ ብቻ ነው! " ። እረኛ ካለ ገመድ ለምኔ ?


........ ይቆየን.............

@YEAWEDIMERITE
አዘጋጅ :- ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
ነሐሴ 7 ቀን 2012ዓ,ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit