#ጷጉሜ የተባለችው ወር ከየት መጣች?
______ (በአለቃ ዕፁብ ማናዬ)____________
ብዙዎቻችን ስለ ዓመት ስንናገርና ለልጆቻችን ስናስተምር አንድ ዓመት 365 ¼ ቀንት፣ 52 ሳምንታት እና 12 ወራት በማለት እንናገራለል፡፡ እውነትም ልክ ነው፤ ነገር ግን 365 ¼ ማለት ምን ማለት ነው? ¼ የሚባል ቀን አለን? 12 ወራት በሠላሳ በሠላሳ ቀናት የተከፋፈሉ ሆነው ድምራቸው 12X30 = 360 ነው፡፡ ታዲያ 5ቀናት እና ¼ የተባለው ከየት መጣ? ጷጉሜስ የተባለችው ወርስ ከየት መጣች? ለሚባሉትን ጥያቄዎች አስተዋዮች ይጠይቃሉ፡፡ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ግን እንደሚከተለው ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ አስቀምጠውልናል፡፡(ይህ መልስ ብዛት ካላቸው የብራና ጽሑፎች ተውጣቶ ቀለል ባለ ዘዴ የቀረበ ነው፡፡) ይህ ትምህርት የሚገኘው አቡሻኽር በተባለው የቤተክርስቲያን ትምህርት ነው ፡፡ ትምህርቱ ሰፊ ነው፡፡ አብዛኛውም የሒሳብ ስሌት ያለበትም ነው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ወደተነሳንበት ስንመለስ ስንት ወቅቶች አሉን ከተባለ አራት ናቸው፡፡ እነሱም
#1 ክረምት(ከሰኔ26 መስከረም25)፣
#2 መፀው/መከር(ከመስከረም26- ታኅሣሥ25)፣ #3 በጋ/ሐጋይ (ከታኅሣሥ26 - መጋቢት25)፣
#4 ጸደይ/በልግ(ከመጋቢት26 - ሰኔ25) ነው፡፡ እያንዳንዱ ወቅት ደግሞ ሦስት ወራትን ይዟል፡፡ 3X30=90 ነው፡፡ 90 ሲባዛ በ4 ደግሞ 360 ነው፡፡ እንግዲህ የስሌቱ ነገር የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው፡፡
::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
ከላይ አንድ ወቅት 90 ቀን ሳይሆን 91 ቀን 7ሰዓት እና 30 ደቂቃ ነው፡፡ ይህ የሚሆነው የየወሩ ቀን ማጠር እና መርዘምን ተከትሎ በሚመጣ ልዩነት ነው፡፡ #ለምሳሌ
መስከረም ላይ 12 ሰዓት አይመሽም ብርሃን ነው፡፡
ታኅሣሥ ላይ ግን 12 ሰዓት ጭልምልም ይላል፡፡ ሌሊቱም ረዥም ነው፡፡ ለምሳሌ እነዚህ ቀረቡ እንጂ እያንዳንዱ ወር የተለያየ ልዩነት አለው፡፡ ስለዚህ ጠቅላላውን አራቱንም ወቅቶች ስንደምራቸው የምናገኘው ውጤት አንድ ዓመትን ያስገኙልናል፡፡
🚩ክረምት 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
🚩መፀው 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
🚩በጋ/ሐጋይ 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
🚩ጸደይ 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
::::::::::::::::::::::::::
ጠቅለል አድርገን ስንደምረው ዘጠና ዘጠናው ቀን ስንደምረው 90 X 4 = 360 ይሆናል፡፡ ይህ የአሥራሁለት ወሩን ያዘ ማለት ነው፡፡ የየወቅቱን አንዳንድ ቀን ስንደምር 1 X 4 = 4 ይሆናል፡፡ ይህም የጷጉሜ አራቱ ቀናት ናቸው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
የቀሩትን 7 ሰዓት እና 30 ደቂቃዎች ስንደምራቸው 30ሰዓት ይመጣል፡፡ ወደ ዕለት ሲቀየር 1 ቀን እና 6 ሰዓት ይሆናል ማለት ነው፡፡ ከላይ ካገኘነው 4 ጋር ሲደመር 5 ቀናት እና 6 ሰዓት ይሆናል ማለት ነው፡፡
#በጠቅላላ አንድ ዓመት 365 ከ6ሰዓት ወይም ¼የሚባለው ለዚህ ነው ይህ ስድስት ሰዓት በአራት ዓመት አንድቀን ሆኖ ጷጉሜ ስድስት እንድትሆን ያደርገዋል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ጳጉሜ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም “ጭማሪ” ማለት ነው ፡፡ በግእዝ “ወሰከ – ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ተውሳክ (ተጨማሪ) ማለት ነው፡፡ ምዕራባዊያኑ ጳጉሜን የወር ተጨማሪ ቀን አድርገዋታል፡፡ እኛ ግን የዓመት ተጨማሪ ወር አድርገናታል፡፡ ይህቺ ወር በ600 ዓመት 7 ትሆናለች ነገር ግን ሊቃውንት ይቺን የትርፍ ትርፍ ናትና ከስሌት ውጪ የማይኖርባት በማለት ይገልጧታል፡፡
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ጷጉሜ ፫/፳ ፻- ፲፪ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
______ (በአለቃ ዕፁብ ማናዬ)____________
ብዙዎቻችን ስለ ዓመት ስንናገርና ለልጆቻችን ስናስተምር አንድ ዓመት 365 ¼ ቀንት፣ 52 ሳምንታት እና 12 ወራት በማለት እንናገራለል፡፡ እውነትም ልክ ነው፤ ነገር ግን 365 ¼ ማለት ምን ማለት ነው? ¼ የሚባል ቀን አለን? 12 ወራት በሠላሳ በሠላሳ ቀናት የተከፋፈሉ ሆነው ድምራቸው 12X30 = 360 ነው፡፡ ታዲያ 5ቀናት እና ¼ የተባለው ከየት መጣ? ጷጉሜስ የተባለችው ወርስ ከየት መጣች? ለሚባሉትን ጥያቄዎች አስተዋዮች ይጠይቃሉ፡፡ ቀደምት ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ግን እንደሚከተለው ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ አስቀምጠውልናል፡፡(ይህ መልስ ብዛት ካላቸው የብራና ጽሑፎች ተውጣቶ ቀለል ባለ ዘዴ የቀረበ ነው፡፡) ይህ ትምህርት የሚገኘው አቡሻኽር በተባለው የቤተክርስቲያን ትምህርት ነው ፡፡ ትምህርቱ ሰፊ ነው፡፡ አብዛኛውም የሒሳብ ስሌት ያለበትም ነው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ወደተነሳንበት ስንመለስ ስንት ወቅቶች አሉን ከተባለ አራት ናቸው፡፡ እነሱም
#1 ክረምት(ከሰኔ26 መስከረም25)፣
#2 መፀው/መከር(ከመስከረም26- ታኅሣሥ25)፣ #3 በጋ/ሐጋይ (ከታኅሣሥ26 - መጋቢት25)፣
#4 ጸደይ/በልግ(ከመጋቢት26 - ሰኔ25) ነው፡፡ እያንዳንዱ ወቅት ደግሞ ሦስት ወራትን ይዟል፡፡ 3X30=90 ነው፡፡ 90 ሲባዛ በ4 ደግሞ 360 ነው፡፡ እንግዲህ የስሌቱ ነገር የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው፡፡
::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::::
ከላይ አንድ ወቅት 90 ቀን ሳይሆን 91 ቀን 7ሰዓት እና 30 ደቂቃ ነው፡፡ ይህ የሚሆነው የየወሩ ቀን ማጠር እና መርዘምን ተከትሎ በሚመጣ ልዩነት ነው፡፡ #ለምሳሌ
መስከረም ላይ 12 ሰዓት አይመሽም ብርሃን ነው፡፡
ታኅሣሥ ላይ ግን 12 ሰዓት ጭልምልም ይላል፡፡ ሌሊቱም ረዥም ነው፡፡ ለምሳሌ እነዚህ ቀረቡ እንጂ እያንዳንዱ ወር የተለያየ ልዩነት አለው፡፡ ስለዚህ ጠቅላላውን አራቱንም ወቅቶች ስንደምራቸው የምናገኘው ውጤት አንድ ዓመትን ያስገኙልናል፡፡
🚩ክረምት 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
🚩መፀው 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
🚩በጋ/ሐጋይ 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
🚩ጸደይ 91 ቀን 7 ሰዓት ከ30 ደቂቃ
::::::::::::::::::::::::::
ጠቅለል አድርገን ስንደምረው ዘጠና ዘጠናው ቀን ስንደምረው 90 X 4 = 360 ይሆናል፡፡ ይህ የአሥራሁለት ወሩን ያዘ ማለት ነው፡፡ የየወቅቱን አንዳንድ ቀን ስንደምር 1 X 4 = 4 ይሆናል፡፡ ይህም የጷጉሜ አራቱ ቀናት ናቸው፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
የቀሩትን 7 ሰዓት እና 30 ደቂቃዎች ስንደምራቸው 30ሰዓት ይመጣል፡፡ ወደ ዕለት ሲቀየር 1 ቀን እና 6 ሰዓት ይሆናል ማለት ነው፡፡ ከላይ ካገኘነው 4 ጋር ሲደመር 5 ቀናት እና 6 ሰዓት ይሆናል ማለት ነው፡፡
#በጠቅላላ አንድ ዓመት 365 ከ6ሰዓት ወይም ¼የሚባለው ለዚህ ነው ይህ ስድስት ሰዓት በአራት ዓመት አንድቀን ሆኖ ጷጉሜ ስድስት እንድትሆን ያደርገዋል፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
ጳጉሜ የሚለው ስያሜ “ኤፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም “ጭማሪ” ማለት ነው ፡፡ በግእዝ “ወሰከ – ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ተውሳክ (ተጨማሪ) ማለት ነው፡፡ ምዕራባዊያኑ ጳጉሜን የወር ተጨማሪ ቀን አድርገዋታል፡፡ እኛ ግን የዓመት ተጨማሪ ወር አድርገናታል፡፡ ይህቺ ወር በ600 ዓመት 7 ትሆናለች ነገር ግን ሊቃውንት ይቺን የትርፍ ትርፍ ናትና ከስሌት ውጪ የማይኖርባት በማለት ይገልጧታል፡፡
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
ጷጉሜ ፫/፳ ፻- ፲፪ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ