#መላእከ ውቃቢ
.......ካለፈው የለጠቀ.........
ሰኔ 12የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ምክንያት በማድረግ በዚሁ ርዕስ ሥር መላከ ውቃቢ ማለት ምን ማለት እንደሆነ እና ነገደ መላእክትን ከነ አለቆቻቸው መዳሰስ ጀምረን ነበር ዛሬም ቀጣዮንና የመጨረሻውን ክፍል ሰኔ 19 የቅዱስ ገብርኤልን በዓል ምክንያት አድርገን ይዘንላችሁ ቀርበናል። ዛሬ
.........................
#ውቃቢ የሚለው ገላጭ ግሥ ለምን በብዛት ከጥንቁልና ጋር ተያይዞ ይነሳል? መላእክትስ እራሳቸው ስለዚህ (ስለ ጥንቁልና) ምን ይላሉ? የሚለውን እንቃኛለን አብራቹን ቆዮ ::
..........................
ውቃቢ የሚለው ቃል አቃቢ ጠባቂ የሚል ትርጉም ያለው በመሆኑ ሰዎች ያድነናል ከክፉሁ ነገር ይጠብቀናል ብለው ስለሚያምኑ የሚያመልኩትን አካል ውቃቢዬ (ጠባቂዬ )ብለው ሲጠሩ ይስተዋላል ጠንቆይ ከሰዎች በግ ፍየል በሬ ገንዘብ ወዘተ ነገሮች የሚጠብቅ(የሚሻ)እንጂ ሰዎችን የሚጠብቅ አይደለም ስለዚህ ውቃቢ የሚለው ስም አይገባውም ከዛይልቅ አውዳሚ የሚለው ስመ ስያሜ ይስማማዋል ::ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጠንቋይ የሚለውስ መጠሪያ ስትተረጉመው እራሱ ጠንቋይ ማለት #ጠ_ን_ቀ_ነ_ዋ_ይ (የገንዘብ ጠንቅ ) ማለት ነው ብላ አርቃ ትተረጉማለት:: እውነት ነው የተባረከ ሥራ እንድሰጥህ ውድ ሽቶ አምጣ የተባረከ ትዳር እንድሰጥህ መካደሚያ የሚሆን ቪላ ቤት ሰርተህ ስጠኝ የተባረከ ልጅ እንድሰጥህ ሰንጋ በሬ ጣልልኝ የሚሉ ጠንቀ ነዋዮች (ጠንቋዮች) ብዙ ናቸው:: ለሰዎች ሁሉ ሁለት ሁለት ጠባቂ አቃቢ መላክ አላቸው አንዱ በቀን ሌላኛው በሌሊት የቀኑ ከጠዋቱ 12ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ይጠብቅና ለሌላኛው መላክ ይሰጠዋል ያም መላክ ይህ ሰው ደገኛ ነውን ይለዋል ደገኛ ከሆነ አዎን እጁ ከምጽዋት እግሩ ከቤተ እግዚአብሔር ጆሮው ከቃለ እግዚአብሔር ሰውነቱ ከጦም አይተለየኝ ይለዋል ተረኛው መላክም ደስ እያለው ከምሽቱ 12ሰዓት እስከ ንጋቱ 12ሰዓት ይጠብቀዋል ሰውየው ደገኛ ካልሆነ ግን ማለትም እጁ ከምጽዋት እግሩ ከቤተ እግዚአብሔር ሰውነቱ ከጦም ከራቀ ግን ተረካቢው መላክ ያዝናል ምነው አምላኬ ይህን ከምታስጠብቀኝ እንሰሳ ብታስጠብቀኝ ይሻላል ይላል ይጠየፈዋል ::ጠንቋዮች ጠንቀኞች ናቸው :: በማሳያ ጠቀስን እንጂ ጠንቀኝነታቸውም በገንዘብ ብቻ የሚቆም አይደለም የእግሬን እጣቢ ጠጣ የሚሉ ጠንቀ ጤና ፣ ያገባአት ሴት ዕጣ ክፍልህ አይደለችም የሚሉ ጠንቀ ፍቅር ፣ ግደል ግደል የሚሉጨጠንቀ ሠላም ፣ አሁን ምን ቀረህ እራስህን አጥፋ አጥፋ የሚያሰኙ ጠንቀ ተስፋ ፣ አምጣ አምጣ የሚሉ በዝባዦች ጠንቀ ብልጥግና፣ የሚያጠራጥሩ ከእምነት ጎዳና የሚያወጡ ጠንቀ እምነትቶች ጭምር ናቸው:: እግዚአብሔር ግን እነዚህ መሠል ሰዎች ጋር እንዳንገኝ አስጠንቅቆናል “አስማተኛም፥ መተተኛም፥ በድግምት የሚጠነቍልም፥ መናፍስትንም የሚጠራ፥ ጠንቋይም፥ ሙታን ሳቢም በአንተ ዘንድ አይገኝ።” ዘዳግም 18፥11 ባንተ ዘንድ አይገኝ ማለት አንተ እራስህ ጠንቁል ጠንቁል የሚል ሰሜት አይሰማህ እንደዚህም የሚያደርጉ ቤተሰቦች ወንድሞች ወይም እህቶች ጓደኞች የሥራ ባልደረቦች አይኑሩህ ማለቱ ጭምር ነው ጠንቋዮች እግዚአብሔር እና የእግዚአብሔር ሰዎችን የሚገዳደሩ ደፋሮችም ናቸው:: ለምሳሌ ላይ የእግዚአብሔር ነቢይ የሆነ ነቢዮ ሙሴን የተገዳደሩትን ሁለቱን ጠንቋዮች መመልከት እንችላለን መገዳደራቸው ግን በተአምራት ሳይሆን በምትዐት በቅድስና ብቃት ሳይሆን በእርኩሰት ብቃት በማድረግ ሳይሆን ያደረጉ በማስመሰል በቅዱሱ በእግዚአብሔር መንፈስ ሳይሆን በእርኩሱ በሰይጣን መንፈስ በመሰራት ነው :: “ሙሴና አሮንም ወደ ፈርዖን ገቡ፥ እግዚአብሔርም እንዳዘዛቸው እንዲሁ አደረጉ፤ አሮንም በትሩን በፈርዖንና በባሮቹ ፊት ጣለ፥ እባብም ሆነች።” ዘጸአት 7፥10 ፈርዖንም ጠቢባንንና መተተኞችን ጠራ፤ የግብፅም ጠንቋዮች በአስማታቸው እንዲሁ ደግሞ አደረጉ እያንዳንዳቸውም በትራቸውን ጣሉ፥ እባቦችም ሆኑ፤ የአሮን በትር ግን በትራቸውን ዋጠች።” ዘጸአት 7፥12 እነዚህ ሙሴና አሮንን የተገዳደሩ ሁለቱ ጠንቋዮች ምንም እንኳን በምተአት በትሮቻቸውን ወደ እባብነት ቢለውጡም ከጠንቋዮች ምትዐት ይልቅ የእግዚአብሔር ሰዎች ተአምራት እንደሚበልጥ ሲያስገነዝበን የጠንቋዮቹ እባቦች በነ ሙሴ እባቦች ተመዋጡ ብሎናል:: ዛሬም ይመላቸው እንጂ የኃላ የኃላ ሥር ማሽ፣ ቅጠል በጣሽ ፣ ሙት ሳቢ፣ ጋኔን ጠሪ፣ ሞራ ገላጭ ውቃቢ አምላኪ ሙአርተኛ እና መተተኛ በገሃነም እሳት መዋጣቸው አይቀርም :: “የዚህች ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና። እርሱ ጥበበኞችን በተንኰላቸው የሚይዝ፤ ደግሞም፦ ጌታ የጥበበኞችን አሳብ ከንቱ እንደ ሆነ ያውቃል ተብሎ ተጽፎአልና።”1ኛ ቆሮንቶስ 3፥19-20 በመጽሐፍ ዲቢሎስ እባብ ተብሎ ተጠርቷል“የቀደመውንም እባብ ዘንዶውን እርሱም ዲያብሎስና ሰይጣን የተባለውን ያዘው፥” ራእይ 20፥2 ታዲያ የእባቡን የዲያቢሎስን ጥበብ (መርዝ) በጥበቡ ለመሻር ሲል መድኃኒተ ዓለም ሥግው ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ተገለጠ ለመርዘኛው መድኃኒት መርዙ ነውና ዲያቢሎስ በመድኃኒት የሞተ የተሸነፈ የመጀመሪያ ፍጡር ሆነ “ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። 1ኛ ዮሐንስ 3፥9 :: ጥንቆላ ጠንቀኝነት ነውና በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የተጠየፈ ነው ኢት አምልክ (ሌሎች አማልክትን አታምልክ የሚል ትዕዛዝም አስቀድሞ መስጠቱ ለዚሁ ነው:: ዘጸ20፥1- ፍቅረ ጣዖት ያደረባቸው እሥራኤል ዘሥጋም ሙሴ በሥጋ በተለያቸው ጊዜ እግዚአብሔር አምላክ ከእሥራኤል ፊት ቅዱሱን የሙሴን ሥጋ ሰውሮባቸው ነበር ::ለምን ያልን እንደሆነ ሙሴን አብዝተው ይወዱት ስለነበረ ሥጋውን ሳይቀብሩ እናምልከው ይሉ ነበርና ነው:: ሰው ለሚወደው ነገር ባሪያ ነው :: ክፋት የክፋት ልጅ ዲያቢሎስ ታዲያ የተሠወረውን የውሴን ሥጋ ካለበት አድርሶ ለእስራኤል ገልጦላቸው ሊያሰመልካቸው ወደደ በዚህ ጊዜ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ስለ ሙሴ ሥጋ ከሰይጣን ጋር ተከራከረ:: ዛሬ ብዙዎች በቅዱሳን አማላጅነትና ተራዳይነት መማጠናችንን እያነሱ ይኮኑኑናል ቅድስ ኦርቶዶክስ ግን ሙሴን ሳይሆን የሙሴ አምላክ ክርስቶስን ታመልካለች ለሙሴ የጸጋ ለክርስቶስ የባህሪ የአምልኮ ስግደት ታቀርባለች ሙሴን አማላጅ ክርስቶስን ደግሞ ፈራጅ ብላ ታከብራቸዋለች:: ሰይጣን ዲያቢሎስ ግን እስራኤል የሙሴን ሥጋ አግኝተው እንዲያመልኩት እንዲጠነቁሉበት ለማድረግ ካልገለጥኩ ሲል ተጋ ቅዱስ ሚካኤል ግን ገሰጸው ሲገስጸውም አልተሳደበም፣ አልተራገመምም :: “የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር፦ ጌታ ይገሥጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም።” ይሁዳ 1፥9 ዛሬም በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በፍርሃትም ይሁን በድፍረት የሚጠነቁሉና የሚያስጠነቁሉ ሰዎችን መሳደብ ሳይሆን መገሰጽ ማንቋሸሽ ሳይሆን ማስተማር እና ከዚህ ሕይወት በቸርነቱ ነጻ ያወጣቸው ዘንድ መለመን እንደሚገባን አስተምሮናል::
..........ይቆየን..........ተፈጸመ...... ዝንቱ ጡሁማር::
ከአቃቢያነ መላክ ከቅዱስ ሚካኤል ወገብርኤል እረድኤትን ይክፈለይ::
አዘጋጅ:- #ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
@YEAWEDIMERITE
ሰኔ 19/2012ዓ.ም
👇👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ዓውደ ምህረት የእናንተ
.......ካለፈው የለጠቀ.........
ሰኔ 12የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ምክንያት በማድረግ በዚሁ ርዕስ ሥር መላከ ውቃቢ ማለት ምን ማለት እንደሆነ እና ነገደ መላእክትን ከነ አለቆቻቸው መዳሰስ ጀምረን ነበር ዛሬም ቀጣዮንና የመጨረሻውን ክፍል ሰኔ 19 የቅዱስ ገብርኤልን በዓል ምክንያት አድርገን ይዘንላችሁ ቀርበናል። ዛሬ
.........................
#ውቃቢ የሚለው ገላጭ ግሥ ለምን በብዛት ከጥንቁልና ጋር ተያይዞ ይነሳል? መላእክትስ እራሳቸው ስለዚህ (ስለ ጥንቁልና) ምን ይላሉ? የሚለውን እንቃኛለን አብራቹን ቆዮ ::
..........................
ውቃቢ የሚለው ቃል አቃቢ ጠባቂ የሚል ትርጉም ያለው በመሆኑ ሰዎች ያድነናል ከክፉሁ ነገር ይጠብቀናል ብለው ስለሚያምኑ የሚያመልኩትን አካል ውቃቢዬ (ጠባቂዬ )ብለው ሲጠሩ ይስተዋላል ጠንቆይ ከሰዎች በግ ፍየል በሬ ገንዘብ ወዘተ ነገሮች የሚጠብቅ(የሚሻ)እንጂ ሰዎችን የሚጠብቅ አይደለም ስለዚህ ውቃቢ የሚለው ስም አይገባውም ከዛይልቅ አውዳሚ የሚለው ስመ ስያሜ ይስማማዋል ::ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጠንቋይ የሚለውስ መጠሪያ ስትተረጉመው እራሱ ጠንቋይ ማለት #ጠ_ን_ቀ_ነ_ዋ_ይ (የገንዘብ ጠንቅ ) ማለት ነው ብላ አርቃ ትተረጉማለት:: እውነት ነው የተባረከ ሥራ እንድሰጥህ ውድ ሽቶ አምጣ የተባረከ ትዳር እንድሰጥህ መካደሚያ የሚሆን ቪላ ቤት ሰርተህ ስጠኝ የተባረከ ልጅ እንድሰጥህ ሰንጋ በሬ ጣልልኝ የሚሉ ጠንቀ ነዋዮች (ጠንቋዮች) ብዙ ናቸው:: ለሰዎች ሁሉ ሁለት ሁለት ጠባቂ አቃቢ መላክ አላቸው አንዱ በቀን ሌላኛው በሌሊት የቀኑ ከጠዋቱ 12ሰዓት እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት ይጠብቅና ለሌላኛው መላክ ይሰጠዋል ያም መላክ ይህ ሰው ደገኛ ነውን ይለዋል ደገኛ ከሆነ አዎን እጁ ከምጽዋት እግሩ ከቤተ እግዚአብሔር ጆሮው ከቃለ እግዚአብሔር ሰውነቱ ከጦም አይተለየኝ ይለዋል ተረኛው መላክም ደስ እያለው ከምሽቱ 12ሰዓት እስከ ንጋቱ 12ሰዓት ይጠብቀዋል ሰውየው ደገኛ ካልሆነ ግን ማለትም እጁ ከምጽዋት እግሩ ከቤተ እግዚአብሔር ሰውነቱ ከጦም ከራቀ ግን ተረካቢው መላክ ያዝናል ምነው አምላኬ ይህን ከምታስጠብቀኝ እንሰሳ ብታስጠብቀኝ ይሻላል ይላል ይጠየፈዋል ::ጠንቋዮች ጠንቀኞች ናቸው :: በማሳያ ጠቀስን እንጂ ጠንቀኝነታቸውም በገንዘብ ብቻ የሚቆም አይደለም የእግሬን እጣቢ ጠጣ የሚሉ ጠንቀ ጤና ፣ ያገባአት ሴት ዕጣ ክፍልህ አይደለችም የሚሉ ጠንቀ ፍቅር ፣ ግደል ግደል የሚሉጨጠንቀ ሠላም ፣ አሁን ምን ቀረህ እራስህን አጥፋ አጥፋ የሚያሰኙ ጠንቀ ተስፋ ፣ አምጣ አምጣ የሚሉ በዝባዦች ጠንቀ ብልጥግና፣ የሚያጠራጥሩ ከእምነት ጎዳና የሚያወጡ ጠንቀ እምነትቶች ጭምር ናቸው:: እግዚአብሔር ግን እነዚህ መሠል ሰዎች ጋር እንዳንገኝ አስጠንቅቆናል “አስማተኛም፥ መተተኛም፥ በድግምት የሚጠነቍልም፥ መናፍስትንም የሚጠራ፥ ጠንቋይም፥ ሙታን ሳቢም በአንተ ዘንድ አይገኝ።” ዘዳግም 18፥11 ባንተ ዘንድ አይገኝ ማለት አንተ እራስህ ጠንቁል ጠንቁል የሚል ሰሜት አይሰማህ እንደዚህም የሚያደርጉ ቤተሰቦች ወንድሞች ወይም እህቶች ጓደኞች የሥራ ባልደረቦች አይኑሩህ ማለቱ ጭምር ነው ጠንቋዮች እግዚአብሔር እና የእግዚአብሔር ሰዎችን የሚገዳደሩ ደፋሮችም ናቸው:: ለምሳሌ ላይ የእግዚአብሔር ነቢይ የሆነ ነቢዮ ሙሴን የተገዳደሩትን ሁለቱን ጠንቋዮች መመልከት እንችላለን መገዳደራቸው ግን በተአምራት ሳይሆን በምትዐት በቅድስና ብቃት ሳይሆን በእርኩሰት ብቃት በማድረግ ሳይሆን ያደረጉ በማስመሰል በቅዱሱ በእግዚአብሔር መንፈስ ሳይሆን በእርኩሱ በሰይጣን መንፈስ በመሰራት ነው :: “ሙሴና አሮንም ወደ ፈርዖን ገቡ፥ እግዚአብሔርም እንዳዘዛቸው እንዲሁ አደረጉ፤ አሮንም በትሩን በፈርዖንና በባሮቹ ፊት ጣለ፥ እባብም ሆነች።” ዘጸአት 7፥10 ፈርዖንም ጠቢባንንና መተተኞችን ጠራ፤ የግብፅም ጠንቋዮች በአስማታቸው እንዲሁ ደግሞ አደረጉ እያንዳንዳቸውም በትራቸውን ጣሉ፥ እባቦችም ሆኑ፤ የአሮን በትር ግን በትራቸውን ዋጠች።” ዘጸአት 7፥12 እነዚህ ሙሴና አሮንን የተገዳደሩ ሁለቱ ጠንቋዮች ምንም እንኳን በምተአት በትሮቻቸውን ወደ እባብነት ቢለውጡም ከጠንቋዮች ምትዐት ይልቅ የእግዚአብሔር ሰዎች ተአምራት እንደሚበልጥ ሲያስገነዝበን የጠንቋዮቹ እባቦች በነ ሙሴ እባቦች ተመዋጡ ብሎናል:: ዛሬም ይመላቸው እንጂ የኃላ የኃላ ሥር ማሽ፣ ቅጠል በጣሽ ፣ ሙት ሳቢ፣ ጋኔን ጠሪ፣ ሞራ ገላጭ ውቃቢ አምላኪ ሙአርተኛ እና መተተኛ በገሃነም እሳት መዋጣቸው አይቀርም :: “የዚህች ዓለም ጥበብ በእግዚአብሔር ፊት ሞኝነት ነውና። እርሱ ጥበበኞችን በተንኰላቸው የሚይዝ፤ ደግሞም፦ ጌታ የጥበበኞችን አሳብ ከንቱ እንደ ሆነ ያውቃል ተብሎ ተጽፎአልና።”1ኛ ቆሮንቶስ 3፥19-20 በመጽሐፍ ዲቢሎስ እባብ ተብሎ ተጠርቷል“የቀደመውንም እባብ ዘንዶውን እርሱም ዲያብሎስና ሰይጣን የተባለውን ያዘው፥” ራእይ 20፥2 ታዲያ የእባቡን የዲያቢሎስን ጥበብ (መርዝ) በጥበቡ ለመሻር ሲል መድኃኒተ ዓለም ሥግው ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ተገለጠ ለመርዘኛው መድኃኒት መርዙ ነውና ዲያቢሎስ በመድኃኒት የሞተ የተሸነፈ የመጀመሪያ ፍጡር ሆነ “ስለዚህ የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ። 1ኛ ዮሐንስ 3፥9 :: ጥንቆላ ጠንቀኝነት ነውና በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የተጠየፈ ነው ኢት አምልክ (ሌሎች አማልክትን አታምልክ የሚል ትዕዛዝም አስቀድሞ መስጠቱ ለዚሁ ነው:: ዘጸ20፥1- ፍቅረ ጣዖት ያደረባቸው እሥራኤል ዘሥጋም ሙሴ በሥጋ በተለያቸው ጊዜ እግዚአብሔር አምላክ ከእሥራኤል ፊት ቅዱሱን የሙሴን ሥጋ ሰውሮባቸው ነበር ::ለምን ያልን እንደሆነ ሙሴን አብዝተው ይወዱት ስለነበረ ሥጋውን ሳይቀብሩ እናምልከው ይሉ ነበርና ነው:: ሰው ለሚወደው ነገር ባሪያ ነው :: ክፋት የክፋት ልጅ ዲያቢሎስ ታዲያ የተሠወረውን የውሴን ሥጋ ካለበት አድርሶ ለእስራኤል ገልጦላቸው ሊያሰመልካቸው ወደደ በዚህ ጊዜ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ስለ ሙሴ ሥጋ ከሰይጣን ጋር ተከራከረ:: ዛሬ ብዙዎች በቅዱሳን አማላጅነትና ተራዳይነት መማጠናችንን እያነሱ ይኮኑኑናል ቅድስ ኦርቶዶክስ ግን ሙሴን ሳይሆን የሙሴ አምላክ ክርስቶስን ታመልካለች ለሙሴ የጸጋ ለክርስቶስ የባህሪ የአምልኮ ስግደት ታቀርባለች ሙሴን አማላጅ ክርስቶስን ደግሞ ፈራጅ ብላ ታከብራቸዋለች:: ሰይጣን ዲያቢሎስ ግን እስራኤል የሙሴን ሥጋ አግኝተው እንዲያመልኩት እንዲጠነቁሉበት ለማድረግ ካልገለጥኩ ሲል ተጋ ቅዱስ ሚካኤል ግን ገሰጸው ሲገስጸውም አልተሳደበም፣ አልተራገመምም :: “የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር፦ ጌታ ይገሥጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም።” ይሁዳ 1፥9 ዛሬም በማወቅም ሆነ ባለማወቅ በፍርሃትም ይሁን በድፍረት የሚጠነቁሉና የሚያስጠነቁሉ ሰዎችን መሳደብ ሳይሆን መገሰጽ ማንቋሸሽ ሳይሆን ማስተማር እና ከዚህ ሕይወት በቸርነቱ ነጻ ያወጣቸው ዘንድ መለመን እንደሚገባን አስተምሮናል::
..........ይቆየን..........ተፈጸመ...... ዝንቱ ጡሁማር::
ከአቃቢያነ መላክ ከቅዱስ ሚካኤል ወገብርኤል እረድኤትን ይክፈለይ::
አዘጋጅ:- #ተርቢኖስ ሰብስቤ ኃ/ማርያም
@YEAWEDIMERITE
ሰኔ 19/2012ዓ.ም
👇👇👇👇👇👇👇👇
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ዓውደ ምህረት የእናንተ