ዐውደ ምሕረት
3.69K subscribers
929 photos
24 videos
271 files
192 links
"ቤተ ክርስቲያን ባሕረ ጥበባት
አትመረመርም እጅግ ጥልቅ ናት"
Download Telegram
" #የጻድቅ_መታሰቢያ_ለበረከት_ነው ፤ የኀጥኣን ስም ግን ይጠፋል።"

#ምሳሌ_10÷7
#አቡነ_ጴጥሮስ_ጳጳሰ_ዘምሥራቅ_ኢትዮጵያ_ተላዌ_አሰሩ_ለአቡነ_ኢየሱስ_ሞዓ

በ1885 ዓ/ም ፍቼ ከተማ ተወለዱ፤ የዓለም ስማቸውም፤ ኃይለ ማርያም ተባለ። በ1909 ዓ/ም መንኩሰው፤ “በ1910 ዓ/ም በወላሞ ወረዳ የደብረ መንክራት ገዳም መምህር ተብለው ተሾሙ። በ1916 ዓ/ም በዝዋይ ደሴት የገዳሙ መምህር ሆኑ። በ1921 ዓ/ም በእስክንድርያ ቅዱስ ማርቆስ ከአራት ጳጳሳት ጋር ጳጳስ ሲሆኑ ስማቸውም ጴጥሮስ ተባለ።” (ጳዎሎስ ኞኞ፤ “የኢትዮጵያና የኢጣልያ ጦርነት”፤ ገጽ 156)።

የጣልያንን ወረራ ለመከላከል በ1928 አዋጅ በታወጀ ጊዜ በወቅቱ የምስራቅ ኢትዮጵያ ጳጳስ የነበሩት አቡነ ጴጥሮስ ንጉሠነገሥቱንተከትለው ወደማይጨው ዘመቱ።
#በ1928 ሐምሌ21 ቀን የተባበሩት የአርበኞች ግምባርአዲስ አበባ ላይ የሠፈረውን የጠላት ጦርለመዋጋት በአደረገው ቀጠሮ መሠረት አቡነጴጥሮሥ በነደጃዝማች አበራ ካሣ ይመራከነበረው የሰላሌ ጦር አብረው ወደ አዲስአበባ ገቡ። ይህ ጦር ግን የሚፈለገው ውጤጥ አለመምጣቱን በመገንዘብ ወደመጣበት ሢያፈገፍግ አቡነ ጴጥሮሥ የአዲስአበባን ህዝብ ሰብከው በጠላት ላይ ለማስነሳት እና ሀገሩንና ሃይማኖቱን እንዳያጣ ለማንቃት በማሰብ ከጦሩ ተለይተው አዲስ አበባ ቀሩ። ብዙም ሳይቆዩ አንድ ቀን ብቻ እንደቆዩ ተይዘው የጦር አለቆች ፊት ቀረቡ።

ብፁእነታቸው ከተያዙበት ጊዜ ጀምሮ በጠላት የጥይት እሩምታ እስከተገደሉበት ጊዜ ድረስየነበረውን ሂደት 'ኮርየር ዴላሴራ' (corrieredella sera) የተባለው ጋዜጣ ወኪል እና የምስራቅ አፍሪካ ዜና መዋዕል አዘጋጅ የነበረው 'ፖጃሌ' የተባለ ጋዜጠኛ እ.ኤ.አ. ሰኔ 15ቀን 1936 ዓም አዲስ አበባ በነበረ ጊዜሂደቱን ባየውና በተመለከተው መንገድ እንደሚከተለው ፅፎ ነበር
"ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ቁመታቸው ረዘም ፊታቸውም ዘለግ ያለና መልካቸው ጠየም ያለ ዐዋቂነታቸውና ትሕትናቸው ከገጻቸው የሚነበብ ሲሆን በዚህ ጊዜ ለብሰውት የነበረው ልብሰ ጵጵስና ጥቁር ካባ ያውም በጭቃ የተበከለ ነበር፡፡ በዚህ ሁኔታ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ወደ ችሎት ቀረቡ፡፡ ለፍርድም የተሠየሙት ዳኞች ሦስት ሲሆኑ እነዚህም ጣሊያኖችና የጦር ሹማምንት ናቸው፡፡ የመካከለኛው ዳኛ ኮሎኔል ነበር፡፡ የቀረበባቸውም ወንጀል 'ሕዝብ ቀስቅሰዋል፣ ራስዎም ዐ ምፀዋል፣ ሌሎችንም አንዲያምፁ አድርገዋል' የሚል ነበር፡፡ ዳኛውም 'ካህናቱም ሆኑ የቤተ ከህነት ባለሥልጣኖች ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ቂርሎስም የኢጣሊያንን መንግሥት ገዢነት አምነው አሜን ብለው ሲቀበሉ አርስዎ ለምን ዐመፁ፣ ለምን ብቻዎን አፈንጋጭ ሆኑ?' ሲል ጠየቃቸው ፡፡ #አቡነ_ጴጥሮስም የሚከተለውን #መለሱ''፡፡
#አቡነ_ቄርሎስ_ግብፃዊ ናቸው፣ #ስለ_ ኢትዮጵያና_ኢትዮጵያውያን_የሚገዳቸው_ነገር የለም፡፡#አኔ_ግን_ኢትዮጵያዊ_ነኝ፡፡ #አላፊነትም_ያለብኝ_የቤተ_ክርስቲያን_አባት_ነኝ፡፡ ስለዚህ #ስለ_ሀገሬና_ስለ_ቤተ_ክርስቲያኔ _አቆረቆራለሁ፡፡ ከዚህ በቀር ለእናንተ ችሎት የማቀርበው ነገር የለኝም፡፡ #ለፈጣረዬ_ብቻ _የምናገረውን አናገራለሁ፡፡ #እኔን ለመግደል እንደወሰናችሁ አውቃለሁ፡፡ #ስለዚህ_በእኔ_ላይ_ _የፈለጋችሁትን_አድርጉ፡፡ #ግን_ተከታዮቼን_አትንኩ' አሉ፡፡
ይህንንም ብለው በጥይት ተደብድበው ሲገደሉ እንዲያይ ተጋብዞ ለተሰበሰበው ሕዝብ የሚከተለውን ሕያው መልእከት አስተላለፉ፡፡
'#'አረማዊ የሆነው የፋሺስት መንግሥት #ቤተክርስቲያንን_ለማቃጠል፣ ሕዝበ ክርስቲያንን ለመግደል፣ ሃይማኖትን ለማጥፋት፣ ታሪካችንን ለማበላሸት የመጣ ነው፡ #እንጂ በጎ ለመሥራት፣ እውነተኛ ፍርድ ለመስጠት ስላልመጣ #ለዚህ_ለግፈኛ_አትገዙ !!!፡፡ ስለ ውድ #ሀገራችሁ፣ ስለ ቀናች #ሃይማኖታችሁ_ተከላከለ
#ነጻነታችሁ_ከሚረክስ_ሙታቹህ_ስማችሁ_ሲቀደስ_ታላቅ_ዋጋ_ያለው_ክብር_ታገኛላችሁ#የኢትዮጵያ_ሕዝብ ለዚህ ለጠላት #እንዳይገዛ_አውግዣለሁ_የኢትዮጵ_መሬት ጠላትን ብትቀበል የተረገመች ትሁን። #በፈጣሪየ_በኢየሱስ_ክርስቶስ_ስም_የተገዘተች ትሁን።''

#አባታችን_ብጹዕ_አቡነ_ጴጥሮስ _ሐቀ _ነበሩ። ነገር ግን ለኢጣሊያ ለጋስዮን ታዝዞ የመጣው አስተርጓሚ ዳኞች የሚሉትን ብቻ ከማስተርገ፡ም በቀር አባታችን የሚናገሩትን ሐቀኛ ንግግር አላስተረጎመም፡፡ አኔ እንኳን የሰማሁት በአዲስ አበበ ለሠላሳ ዓመት የኖረው የእቴጌ ሆቴል ሐላፊ የነበረው የግሪክ ዜጋ ማንድራኮስ አጠገቢ ተቀምጦ ስለ ነበር የተናገሩትን ሁሉ ስለ ገለጠልኝ ነው፡፡ እኔ እንደ ሰማሁት ፍርዱን ለመስማት በብዛት የተስበስቡት ጣሊያኖችና ታዝዞ የወጣው የአዲስ አበበ ሕዝብ ሐቀኛ የሆነውን ንግግራቸውን ቢሰማ ኖሮ ልባቸው ይነካ ነበር"።
ሆኖም አስተርጓሚው በጳጳሱ ላይ ተጽዕኖ ስላሳደረበቸው እውነተኛ ንግግራቸው ሳይገለጥ ቀረ። ቀጥሎም ብፁእነታቸው በፍርድ ችሎት ላይ እንዳሉ ሕዝቡ ሁሉ ስለ ርሳቸው እያዘነ ሳለ መስቀላቸውን አውጥተው እየጸለዩ ሕዝቡን ባረኩ። ወዲያው የሞታቸው ፍርድ ሲሰማ ሕዝቡ በኢጣልያ የእጅ ሰላምታ ዓይነት እጁን እንዲያነሣ ታዘዘ። በዚያን ጊዜ አቡነ ጴጥሮስ የሞታቸው ሰዓት መድረሱን ዐውቀው ስዓታቸውን ከኪሳቸው አውጥተው ተመለከቱ። በዚህ ጊዜ ሁሉ ምንም ፍርሃት አይታይባቸውም ነበር። የሞታቸውን ፍርድ ያነብ የነበረው ኢጣሊያዊ ዳኛ ግን ይንቀጠቀጥ ነበር፡፡ ታላቅ ፍርሃትም በፈቱ ላይ ይታይ ነበር።
ይሙት በቃ የተፈረደባቸው ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ በችሎት ፊት ለብዙ ሰዓታት ቆመው ስለዋሉኖ ደከሞአቸው ስለ ነበር ለመቀመጥ ፈልገው ዳኛውን በትሕትናና በፈገግታ ጠየቁት። እንዲ ቀመጡም ፈቀደላቸው፡፡ በመጨረሻም የሞታቸው ፍርድ ከተነበበ በኋላ የፈረዱባቸውን ዳኞች ጸልየው በመስቀላቸው ባረኩዋቸው። ብፁዕነታቸው እስከ መቃብር አፋፍ ድረስ የፍርሃትና የድንጋጤ ምልክት ያይደለ ከልብ የሆነ ፍጹም ቆራጥነት ይታይባቸው ነበር፡፡
የሀገራቸው በጠላት መወረር የሕዝበቸው መገደልና መታስር የቤተ ከርስቲያናቸው መደፈር እስከ ሞት ያደረሳቸው እኒህ እውነተኛ ጳጳስ ለመገደል ሊወስዱ ጥይት አልፎ ሌላ ስው እንዳይጎዳ ግንብ ይፈለግ ጀመር፡፡ ሩቅ ባለመሔድ ከመካነ ፍትሑ 10 ሜትር ርቆ ግንብ ያለው መግደያ ቦታ ተገኘና ወደዚያ ተወስዱ። ከገዳዮቹም አንዱ 'ፊትዎን ለመሸፈን ይፈልጋሉገ?' ሲል ጠየቃቸው፡፡ 'ይህ የአንተ ሥራ ነው' ሲሉ ብፁዕነታቸው መለሱ'፡፡ ከመግደያውም ቦታ እንደ ደረሱ ወንበር ቀረበላቸውና ፊታቸውን ወደ ግንቡ ጀርባቸውን ወደ ሕዝቡ እድርገው እንዲቀመጡ ሆኑ።
ከዚያ በኋላ ስምንት ወታደሮች በስተጀርባቸው ሃያ ርምጃ ርቀው ተንበርክከው በተጠንቀቅ ቆሙ። ወዲያው አዛዡ 'ተኩስ' በማለት ትእዛዝ ሲስጥ ስምንቱም ተኩስው መቱዋቸው። ግን በስምንት ጥይት ሳይሞቱ ቀሩ። መሞታቸውንና አላመሞታቸውን ለማረጋገጥ ዶክተር ተጠራ። ዶክተሩም እንዳልሞቱ አረጋገጠ። ከዚያም ሌላ ወታደር በሦስት የሽጉጥ ጥይት ራስ ቅላቸውን መትቶ ገደላቸው፡፡
የብፁዕነታቸው አሰክሬን ማንም እንዳይወስደው በአስቸኳይ ከአዲስ አበባ ውጭ ማንም በማያውቀው ቦታ በምሥጢር አንዲቀበር ተደሪገ። በዚያች ሌሊት በአዲስ አበባ ውስጥ በየቤቱ ልቅሶና ዋይታ ሆነ" በተጨማሪም ደራሲና ጋዜጠኛ ጳውሎስ ኞኞ "አቡነ ጴጥሮስ እንዴት ሞቱ" ሲል ሙሴ ፓይላክን ጠይቆአቸው እርስቸውም

የሚክተለውን ተናግረዋል። "አቡነ ጴጥሮስ የተገደሉ ዕለት እዚያው ነበርኩ። መጀመሪያ በእጃቸው ይዘውት የነበረውን መጽሐፍ ቅዱሳ ቸውን ተሳለሙት። ቀጥለውም በያዙት
መስቀል አማትበው ሕዝ ቡን ባረኩ፡፡ የኪሳቸውንም ሰዓት አውጥተው ካዩ በኋላ መልሰው ከ ኪሳቸው ክተቱት። ወዲያው ወታደሮች በሩምታ ተኩስው ገደሉ ዋቸው። ይህ እንደሆነ አስገድዶ ኮሎኔል ተመልካቹን ሕዝብ አጨብጭቡ ብሎ አዘዘና ተጨበጨበ።
ማታ ከአስገዳዩ ኮለኔል ጋር ተገኖኝተን ስንጫወት 'በዚህ ቄስ መገደል አኮ ሕዝቡ ተደሰቷለ' እለኝ 'እንዴት?' ብለው 'አላየህም ሲያጨበጭብ' አለኝ። እኔም #ባታውቀው_ነው_እንጂ_የሕዝቡ_ባህል_ሲናደድም_ያጨበጭባል' አልኩት። 'እንዴት?' ቢለኝ እጄን እያጨበጨብኩ አሳየሁት። ከዚህ በኋላ " የሆነው ቢሆን እኔ ትልቅ ማስታወሻ አግኝቼአለሁ " ብሎ አቡነ ጴጥሮስ ሲገደሉ ይዘውት የነበረውን መስቀልና መጽሐፍ ቅዱስ የኪስ ስዓታቸውን ጭምር አሳየኝ። #መጽሐፍ_ቅዱሱ መሐል ለመሐል በጥይት ተስንጥቋል። መስቀሉም ልክ በመሐከሉ ላይ ጥይት በስቶት ወጥቷል። የኪስ ስዓታቸውንም እንዳየሁት፡ እንደዚሁ ጥይት በስቶ ታል"
ጠላት ድል ተደርጎ ኢትዮጵያ ነፃነቷን ከተቀዳጀች በኋላ የብፁዕነታቸውን አኩሪ ታሪክ ትውልድ ሲዘክርላቸው እንዲኖር መታሰቢያ ይሆናቸው ዘንድ በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት አሳሳቢነት #ሐምሌ 16 ቀን 1938 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ እምብርት ሐውልት ቆሞላቸዋል ::

...........ይቆየን...... #አባታችን_ከአቡነ_ጴጥሮስ_ረድኤትና_በረከት እርሱ #በቸርነቱ_ይክፈለን_አሜን🙏


#ምንጭ
1) ዜና ጳጳሳት ኢትዮጵያውያን (ዲ/ን መርሻ አለሀኝ)
2) ታሪካዊ መዝገበ ሰብ (ፋንታሁን እንግዳ

#ዓውደ_ምህረት_የእናንተ
@AwediMeherit
@AwediMeherit
#ሐዲስ_ሱራፊ_ተክለ_ሃይማኖት

#ሱራፊ ማለት መልአክ፣ ከካህናተ ሰማይ አንዱ ማለት ነው፡፡ ሱራፌን፣ ሱራፌል፣ ሱራፌም (በፅርዕ ሴራፊም፣ በዕብራይስጥ ስራፊም) ማለት የነገድ ስም፣ ልዑላን መላእክት፣ ሊቃናት፣ የሚያጥኑ፣ ካህናት፣ ቀሳውስት፣ ቀዳሾች ማለት ነው /ኪዳነ ወልድ ክፍሌ/ ከዚህ ላይ ሱራፊ ነጠላ ቍጥርን ሲያመለክት፤ ሱራፌል ደግሞ ብዙ ቍጥርን ያመለክታል፡፡ ሱራፌል ለቅዱሳን በሰው አምሳል በመገለጣቸው ሽማግሌዎች ተብለው ተጠርተዋል /ኢሳ.24፥23፤ መሳ.13፥2-25፤ /፡፡ በግእዝ ቋንቋ ደግሞ ካህናተ ሰማይ ይባላሉ፡፡ ካህናተ ሰማይ ሱራፌል ቁጥራቸው 24 እንደሆነ ባለ እራዮ ዮሐን ጽፎልናል ይህ ግን 24ሰዓት ያለ እረፍት የሚያመሰግኑ መሆናቸውን ለማመልከት የተጠቀመበት አገላለጽ ነው እንጂ ቁጥራቸውስ 24ብቻ ሆኖ አይደለም ።


ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ ላይ ስማቸውን ጭምር በመጥቀስ ለኻያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ሰላምታ አቅሮቦላቸዋል። በአብ መንበር ዙሪያ ላሉ ለ24ቱ ሰማያውያን ካህናት ሰላምታ ይገባል፤ በእጆቻቸው ውስጥ ላለ ማዕጠንትም ሰላምታ ይገባል፤ በራሶቻቸው ላይ ላሉ አክሊላትም ሰላምታ ይገባል፤ አካኤል፣ ፋኑኤል፣ ጋኑኤል፣ ታድኤል፣ እፍድኤል፣ ዘራኤል፣ ኤልኤል፣ ተዳኤል፣ ዮካኤል፣ ገርድኤል፣ ልፍድኤል፣ መርዋኤል፣ ኑራኤል፣ ክስልቱኤል፣ ኡራኤል፣ ባቱኤል፣ ሩአኤል፣ ሰላትኤል፣ ጣውርኤል፣ እምኑኤል፣ ፔላልኤል፣ታልዲኤል፣ ፐስልዱኤል፣ አሌቲኤል ለተባሉ ስሞቻቸውም ሰላምታ ይገባል) በማለት አወድሷቸዋል (አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ተአምኆ ቅዱሳን ንባቡና ትርጓሜው / መጋቢ ሐዲስ ሮዳስ እንደተረጎመው)

ዛሬ በዚህች መጠነኛ ጽሁፍ ኅዳር 24ቀን ከነዚህ ካህናተ ሰማይ ሱራፌል ጋር ተደምሮ የሥላሴን መንበር ያጠነ አዲሱን ምድራዊ ሱራፊን ተክለ ሃይማኖት /ተክለ ኤልን /እናስተዋውቃችዋለን። ካህናተ ሰማይ ሱራፌል ከዘር የተገኙ ምድራዊያን አይደለም ተክለ ኤል ተክለ ሃይማኖት ግን ከሕግ ዘር የተገኘ ምድራዊ ሰው የሆነ ሐዲስ ሱራፊ ነው።
‹ተክል› ማለት ፍሬያማ ዕንጨት፣ ዛፍ፣ ቅመም፣ ቅጠላ ቅጠል፣፣ የሚሸተት፣ቢበሉት ጥጋብ ፣ቢያርፉበት ጥላ የሚሆን ገነታዊ ዕፅ፣ እንዲሁም ሕግ ሥርዓት ማለት ነው /ማቴ.15፥13/፡፡

"ኤል" ማለት ደግሞ እግዚአብሔር ማለት ነው :: ስመ መላእክት ስመ እግዚአብሔርን ያዘሉ በመሆናቸው የሁሉም ቅዱሳን መላእክ ስም "ኤል" የሚል መቀጽል አለው ለምሳሌ ከላይ የጠቀስናቸው የሃያራቱን ካህናተ ሰማይ የሱራፌልን ስም መመልከት ይቻላል :- አካኤል፣ ፋኑኤል፣ ጋኑኤል ወ.ዘ.ተ ስለዚህ "ተክለ ኤል " ማለታችንም ይህ ሐዲስ ሱራፊ ስሙ ከስማቸው ጭምር የሚገጥም መሆኑን ለመግለጥ ነው። የእግዚአብሔር ተክል ተክለ እግዚአብሔር ማለታችን ነው :: ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ባስልዮስ ዘ ቄሳሪያ እኔስ እግዚአብሔር ባልኩ ጊዜ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ማለቴ ነው ብሎ እንደተናገረ " ተክለ ኤል" ተክለ እግዚአብሔር ሲባልም የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተክል የሚል ትርጉም ይሰጣል ።


#አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የተወለዱት በሸዋ ክፍለ ሀገር ዛሬ ኢቲሳ በመባል በሚታወቀው ከከሰም ጅረት አካባቢ ባለ ቦታ በጥንቱ ፈጠጋር ቡልጋ በደብረ ጽላልሽ አውራጃ ዞረሬ በተባለው ሥፍራ በቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ዘርዐ ዮሐንስ ወይም ጸጋ ዘአብ (የአብ ሥጦታ) ከሚባል ካህን እና ሣራ ወይም እግዚእ ኅረያ(እግዚአብሔር የመረጣት)በመባል ከምትታወቅ ደጋግ ከሆኑ ባልና ሚስቶች በመላእክ አብሳሪነት መጋቢት 24 ቀን ተፀንሰው ታኅሣሥ 24 ቀን 1197 ዓ.ም ገደማ ነው።
ወላጆቻቸውም ፍስሐ ጺዮን ።(የፂዮን ደስታዋ)ብለው ሰየሟቸው፡፡ ጻድቁ በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው ዕቅፍ ወርደው ‹‹ አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ›› በማለት የፈጠራቸውን አምላክ አመስግነዋል። ይህን ጊዜ እናታቸው እግዚ ኀረያም በመገረም ሆና " ይህ ሥራ የአባት ነው ላንተ የሚገባህ ጡት መጥባት ነው" ብላ ለህጻኑ ጡቷን አጎረሰችሁ ፡፡ ይህም የህጻኑ ሁኔታ መላእካዊ ግብሩን ገና በህጻንነት የገለጠ ነበር ቀን ከለሊት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ ማመስገን የመላእክት መገለጫ ነውና ኢሳ 6÷6 ። ካህኑ ፀጋ ዘአብ የወቅቱን የቤተ ክርሰቲያን አገልግሎታቸውን ጨርሰው ወደ ቤታቸው ሲገቡ ሚስታቸው እግዚእ ኀረያ በመገረም ሆና የሦስት ቀን ልጃቸው ፍስሐ ፂዮን እንዴት ባለ ምስጋና ፈጣሪያቸውን እንዳመሰገነ ነገረቻቸው ጸጋ ዘአብም ህጻኑን ተቀብለው ታቅፈው እየሳሙ ልጄ ሺህ ዘመን ኑርልኝ እንዲ እያልክ በቤተ መቅደስ ስትቀድስ ዐይህ ዘንድ እመኛለው አሉ።

የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ከአብሮ አደግ ጓደኞቹ ጋር በዱር ፈረስ ሲጋልብ ጦር ሲሰብቅ ተገናኝቶት ፍስሐ ጺዮን የሚለውን ስሙን በፈጣሪው ትዛዝ መሠረት ለውጦ ከእንግዲህ ወዲህ "ተክለሃይማኖት" እየተባልክ ተጠራ እንጂ ስም ፍስሐ ጺዮን አይሁን አላቸው አበው ስምን መላእክ ያወጣዋል እንዲሉ ፡፡ አያይዞም ፈረስ መጋለብ ጦር መስበቅ ቀስት መወርወር እንሰሳት ማደንን ተው ከእንግዲህ ወዲህ መስቀል ጨብጥ በወንጌል ስበክ ከአፍህ በሚወረወር በቃለ እግዚአብሔር መረብነት ሰው አድን አለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በመላእኩ ክንፍ ላይ ተገልጦ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጌሃለሁ ብሎ በሐዋርያት ሾመት ሐዋርያ አድርጎ ሾመው። ጓደኞቹም ከያሉበት ተሰብስበው ወደ ተክለ ሃይማኖት ቀረቡ ከፊቱ የሚወጣው ብርሃን ግን አላስተያይ አላቸው ስለዚህ ፊትህን ማየት አቃተን ተሸፋፈንልን ሲሉ ተማጠኑት። ሙሴ ከሲና ተራራ ከእግዚአብሔር ጋር ተነጋግሮ በወረደ ጊዜ አሮንና የእስራኤል ልጆች ሁሉ ሙሴ ሆይ ከፊትህ የሚወጣው ብርሃን አላስተያይ ብሎናልና እባክህ ፊትህን ሸፍንልኝ እንዳሉት ዘጽ 34÷29_35

#ጻድቁ በተወለዱ በ15 ዓመታቸው ዲቊናን፤ በ22 ዓመታቸው ደግሞ ቅስናን ከግብፃዊው ጳጳስ ከአባ ጌርሎስ ወይም (ከአባ ቄርሎስ) ዘንድ ተቀብለዋል፡፡ ሐዋርያዊ ተግባርንም በከተታ እና በፈጠጋር (በጽላልሽና በአካባቢዋ፣በዳሞት በምድረ ወላይታ፣በአምሓራና በሸዋ በሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ፣ በኣድያማተ ትግራይ፣በገዳመ ዋሊ (ዋልድባ) ፣በገነተ ማርያም ላስታ በደብረ ዘመዶ ማርያም ገዳም፣ በኤርትራ ገዳማት ፣በደብረ ዳሞ አቡነ አረጋዊ ገዳም ወዘተ በአገሪቱ ወንጌል ባልተዳረሰበት ቦታ ሁሉ እየተዘዋወሩ በመላዋ ኢትዮጵያ ወንጌልን አስፍተዋል።
ጻድቁ አባታችን ሕይወታቸዉን ሙሉ ለእግዚአብሔር በመስጠት፣ እንደ በሬ ተጠምደው፣ እንደ ገበሬ ታጥቀው፣ ይህንን ዓለም ንቀው፣ በጾም በጸሎት ተወስነው በብሕትውና በመኖራቸው፤ እርሳቸው በአሚነ ሥላሴ ጸንተው ሌሎችንም እንዲጸኑና እንዲያምኑ በማድረጋቸው፤ እንደዚሁም እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት ወንጌልን በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ በመስበክ በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ድውያነ ሥጋን በተአምራት፣ ድውያነ ነፍስን በትምህርት የፈወሱ ዛሬም በአጸደ ነፍስ ሆነው የሚፈውሱ ሐዲስ ሐዋርያ ሐዲስ ሱራፊ ናቸው።


በየ ደረሱበት ሥፍራ ሁሉ ከሥራቸው ጽናት ከተአምራታቸው ብዛት የተነሳ አንተ ሰውነህን ወይስ መላእክ ነህን ንገረን ይሏቸው ነበር። እርሳቸውም ከንቱ ውዳሴን ነፍሳቸው አጥብቃ ትጸየፈው ነበርና አባቶቼ እንደ

#ቀጣዮይ ይመልከቱ
👇👇👇👇
“ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን ለራስህ አዘጋጀህ"
#መዝ ፯ {፰} ፥፪
#ማቴ፳ ፩ ፥ ፲ ፮
ይህች ቀን #አባታችን_ቅዱስ_ተክለ_ሃይማኖት በተወለዱ በሦስተኛ ቀናቸው ከእናታቸው
ከእግዚኅረያ ዕቅፍ ወርደው ሥላሴን በአንድነት፤ በሦስትነት ያመሰገኑበት ቀን ነው። ቀኑ "
#ከሰተ_አፍሁ "በመባልም በኢቲሳ ተክለ ሃይማኖት በድምቀት ይከበራል። ቅዱሱ የገድል
መጻሕፋቸውም እንዲህ ተርኮልን እናነባለን።
#ይህውም_እግዚአብሔር የመረጠው ልጅ በተወለደ በሦስተኛው ቀን ይህችም
የመዳኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትንሣኤው መታሰቢያ በምትሆን በታወቀች ቀን በዕለተ
ሰንበት (እሁድ) ከመዓልቱ (ከቀኑ) በ፫ ሰዓት ይህ ብላቴና እጁን አንስቶ ወደ ሰማይ
ተመልክቶ ጮሆ ተናገረ።
#እግዚአብሔርንም እንዲህ ብሎ አመሰገነ።
#ከወልድ_ከመንፈስ_ቅዱስ_ጋር_በባህሪ_በሕልውና_አንድ_የሚሆን_አብ_በአካል_በስም_ልዮ_ነው
#ከአብ_ከመንፈስ_ቅዱስ_ጋር_በባህሪ_በሕልውና_አንድ_የሚሆን_ወልድ_በአካል_በስም_ልዮ_ነው
#ከአብ_ከወልድ_ጋር_በባህሪ_በሕልውና_አንድ_የሚሆ_መንፈስ_ቅዱስ_በአካል_በስም_ልዮ_ነው
በሦስት ሰዓት በቅዳሴ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ ወደ ወደደው ይወርዳልና ሕጻኑም መንፈስ
ቅዱስ ሲወርድ አይቶ ይህን ሦስት ምስጋና አቀረበ።
#እናቱም ከተመረጠ ልጇ ይህን ጽኑ ነገር ሰምታ በልቦናዋ አደነቀች "ልጄ ፍስሐ ጽዮን ምን
ትላለህ ?" አለችው። "........ ይህ ቃል የአባትህ ነው ላንተ ግን የሚገባህ ጡት መጥባት
ነው" ብላ ጡቷን አጎረሰችው።
ባሏ ጸጋ ዘአብ ቤተ መቅደስ የሚያጥንበትን ጊዜ ጨርሶ ሲመጣ ልጇ የተናገረውን ሁሉ
ነገረችሁ ጸጋ ዘአብም ነገሩን ሰምቶ አደነቀ ልጁንም ታቅፎ አንስቶ እየሳመ ልጄ
#እግዚአብሔር ያሳድግህ ብዙ ዘመን ያኑርህ እንዲህ እያልክ በቤተ እግዚአብሔር
ስትቀድስ ዓይህ ዘንድ እመኛለሁና"
#ገድለ ተክለ ሃይማኖት
ምዕራፍ ፲ ፭ ፥ ከቁጥር ፱ እስከ ፳፬
የ፲ ፱ ፻ ፹፱ ዓ.ም ፬ ተኛው ዕትም
ኃ/ማርያም አ.አ ኢትዮጵያ
ታኅሣሥ ፳ ፮ /፪ሺ፻-፲ ፫ዓ.ም
" #ዕለት_ሳበችው_ምሕረትም_ጠቀሰችው"
_______________________________
#አባታችን_ሁልጊዜ እንዲህ ይሉ ነበር። ‹‹የሚጣፍጥ ምግብን መውደድ ኃጢአትን
ያመጣል፣ሞትን ያስከትላል፡፡ ክንፍ ያላቸው የሰማይ ወፎች እንኳን በመብል ምክንያት
ይጠመዳሉ፣ ምግብ በመሻት ከምድር ላይ ይወድቃሉ በወጥመድም ይያዛሉ፡፡የሰው ልጅም
ምግብን በመውደድ በኃጢአት ይወድቃልና እኔስ ለሰውነቴ ምግብ መጠጥን
አልፈልግም፤ልብስም አልሻም ዕራቁቴን ከእናቴ ማኅፀን እንደወጣሁ እንዲሁ ዕረቁቴን ወደ
መቃብር እመለሳለሁ እንጂ፡፡ከዚህ ከኃላፊው ዓለም በሞት በተለየሁ ጊዜ መብል
መጠጥንና ልብስን ማን ያስከትልልኛል?›› አሉ። ዳግመኛም‹‹ሰው:ሊደርስበ
ማይችልበት:በረሃ:እኖራለሁ፣ ነጣቂ ተኩላዎችና አራዊቶች ባሉበት እነርሱ እንዲበሉኝ
ሥጋዬን እጥላለሁ፤ ዳዊት በመዝሙር ‹የጻድቃን ሥጋቸው ለዱር አራዊት ነው› እንዳለ እኔ
ክፉ አውሬዎች፣ ተናዳፊ እባቦችና ዘንዶዎች ወዳሉበት እገባለሁ ምግብም እሆናቸው ዘንድ
እወዳለሁ››በማለት አባታችን ራሳቸውን ለሞት አሳልፈው ይሰጡ ነበር ነገር ግን አራዊቱ
ሁሉ እየሰገዱላቸው ይገዙላቸው ከእግራቸውም በታች ይተኙ ነበር፡፡ እንደሚታዘዝ ደቀ
መዝሙርም ይታዙላቸው ነበር፤ለጸሎትም በሚቆሙበት ጊዜ አብረዋቸው ይቆማሉ፡፡
በፊታቸውም ይጫወታሉ፡፡
#በመጨረሻም ዕለት ሳበችሁ ምሕረትም ጠቀሰችሁ ለሞትም የሚያበቃ ጽኑ ሕማም
ታመመ የሚጠጋበት የዛፍ ጥላ በሌለበት እንደ አንበሳ በበርሃ ወደቀ ለጸሎት ከቆመበት
ጊዜ አንስቶ እስከ ሞተበት ቀን ድረስ እጆቹን በትምህርተ መስቀል እንዳማተበ ነበር ። ብዙ
ግሁሳንም ወደ እርሱ መጡ #እግዚአብሔር አምላክም ብዙ የብዙ ብዙ መላእክትን
አስከትሎ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምን አስቀድሞ ዳዊትንም በገና አስይዞ ተገለጠና
ነብሱን አክብሮ ተቀበላት፣ሳማት፣ ደስታውንም መላት መላእክትም ከዳዊት ጋር "ክቡር ሞቱ
ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር " የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው" እያሉ
በአንድነት ዘመሩለት #መዝ ፻ ፲ ፭ {፻ ፲ ፮ }÷፲ ፭
#እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ
እናውቃለን።”
#ሮሜ ፰ ፥፳ ፰
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፭ ቀን ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
Forwarded from ዐውደ ምሕረት (😷ተርቢኖስ ሰብስቤ😷)
" #ዕለት_ሳበችው_ምሕረትም_ጠቀሰችው"
_______________________________
#አባታችን_ሁልጊዜ እንዲህ ይሉ ነበር። ‹‹የሚጣፍጥ ምግብን መውደድ ኃጢአትን
ያመጣል፣ሞትን ያስከትላል፡፡ ክንፍ ያላቸው የሰማይ ወፎች እንኳን በመብል ምክንያት
ይጠመዳሉ፣ ምግብ በመሻት ከምድር ላይ ይወድቃሉ በወጥመድም ይያዛሉ፡፡የሰው ልጅም
ምግብን በመውደድ በኃጢአት ይወድቃልና እኔስ ለሰውነቴ ምግብ መጠጥን
አልፈልግም፤ልብስም አልሻም ዕራቁቴን ከእናቴ ማኅፀን እንደወጣሁ እንዲሁ ዕረቁቴን ወደ
መቃብር እመለሳለሁ እንጂ፡፡ከዚህ ከኃላፊው ዓለም በሞት በተለየሁ ጊዜ መብል
መጠጥንና ልብስን ማን ያስከትልልኛል?›› አሉ። ዳግመኛም‹‹ሰው:ሊደርስበ
ማይችልበት:በረሃ:እኖራለሁ፣ ነጣቂ ተኩላዎችና አራዊቶች ባሉበት እነርሱ እንዲበሉኝ
ሥጋዬን እጥላለሁ፤ ዳዊት በመዝሙር ‹የጻድቃን ሥጋቸው ለዱር አራዊት ነው› እንዳለ እኔ
ክፉ አውሬዎች፣ ተናዳፊ እባቦችና ዘንዶዎች ወዳሉበት እገባለሁ ምግብም እሆናቸው ዘንድ
እወዳለሁ››በማለት አባታችን ራሳቸውን ለሞት አሳልፈው ይሰጡ ነበር ነገር ግን አራዊቱ
ሁሉ እየሰገዱላቸው ይገዙላቸው ከእግራቸውም በታች ይተኙ ነበር፡፡ እንደሚታዘዝ ደቀ
መዝሙርም ይታዙላቸው ነበር፤ለጸሎትም በሚቆሙበት ጊዜ አብረዋቸው ይቆማሉ፡፡
በፊታቸውም ይጫወታሉ፡፡
#በመጨረሻም ዕለት ሳበችሁ ምሕረትም ጠቀሰችሁ ለሞትም የሚያበቃ ጽኑ ሕማም
ታመመ የሚጠጋበት የዛፍ ጥላ በሌለበት እንደ አንበሳ በበርሃ ወደቀ ለጸሎት ከቆመበት
ጊዜ አንስቶ እስከ ሞተበት ቀን ድረስ እጆቹን በትምህርተ መስቀል እንዳማተበ ነበር ። ብዙ
ግሁሳንም ወደ እርሱ መጡ #እግዚአብሔር አምላክም ብዙ የብዙ ብዙ መላእክትን
አስከትሎ እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያምን አስቀድሞ ዳዊትንም በገና አስይዞ ተገለጠና
ነብሱን አክብሮ ተቀበላት፣ሳማት፣ ደስታውንም መላት መላእክትም ከዳዊት ጋር "ክቡር ሞቱ
ለጻድቅ በቅድመ እግዚአብሔር " የቅዱሳኑ ሞት በእግዚአብሔር ፊት የከበረ ነው" እያሉ
በአንድነት ዘመሩለት #መዝ ፻ ፲ ፭ {፻ ፲ ፮ }÷፲ ፭
#እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ
እናውቃለን።”
#ሮሜ ፰ ፥፳ ፰
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
መጋቢት ፭ ቀን ፳ ፻ ፲ ፫ ዓ.ም
#24ቱ_ካህናተ_ሰማይ_25 ሆኑ !
_______

አስቀድመው ቅዱሳን ሐዋርያት 12 ብቻ ነበሩ ከመካከላቸውም ይሁዳ ገንዘብ ወዶ ዘመድ ለምዶ አገልግሎቱን ትቶ ሄደ ሐዋርያትም ወንጌል በዓለም ሳይሰበክ ቢቀር አገልግሎታችን ተስተጎግሎ መቅረቱ አይደለ ብለው እግዚአብሔር ባወቀ ይሁዳ በተዋት አገልግሎት ፈንታ ሌላ ሰው እንዲሿምላቸው በርናባስንና ማትያስን አቀረቡ መንፈስ ቅዱስም ማቲያስን መርጦ ሰጣቸው:: የሚገርመው ነገር የእግዚአብሔር ድንቅ ስጦታ ነው በአንዱ ይሁዳ ፈንታ ሁለት ምትኮችን ሰጣቸው አንዱ ማቲያስ ሲሆን ሌላው እራሱ በቃሉ ሐዲስ ሐዋርያ ብሎ የሾመው ተክለ ሃይማኖት ነው ቅዱስ ጳውሎስን ከአሳዳጅነት ቅዱስ ጴጥሮስን ከዓሳ አጥማጅነት እደጠራቸው ሐዋርያትን በጠራበት አጠራሩ አባታችን ተክለ ሃይማኖትን እንሰሳ ከሚያድኑበት ("ድ")ጠብቆ ይነበብ) ጫካ ጠርቶ በወንጌል መረብነት ሰው የሚድኑ ("ድ")ላልቶ ይነበብ አዳኝ ሐዲስ ሐዋርያ አድርጉ ሾማቸው የሐዋርያት ቁጥረም 12 ቢሆንም በሐዲሱ ኢትዮጵያዊ ሐዋርያ አማካኝነት ያለ ወትሮ 13 ሆነ ምነው መጻሕፍት 12ቱ ሐዋርያት አይደል የሚለው ቢሉ መጻሕፍት በቀረበው የመጥራትም ፀባይ አላቸው 12ቱን ሐዋርያት አስሩም አያለ እንደጠራቸው ማለት ነው ስለዚህ 12ሐዋርያት ስላለ 13ተኛ አይጨመርም አያሰኝም

#አባታችን ተክለ ሃይማኖት ቁጥራቸው ከሐዋርያት ወገን ብቻ ሳይሁን ከስማዕታትም ጋር ጭምር ነው ምነው ሰማዕታት ስለ ክርስቶስ ሲሉ ሥጋቸውን የቆረሱ ደማቸውን ለምስክርነት ያፈሰሱ እንደነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያሉ ሰዎች አይደሉም እንዴ ቢሉ አባታችን ተክለ ሃይማኖት መከራን አብዝቶ በመቀሎል ከሰማዕቱ በምን ተለዮ?በዳሞቱ ንጉስ እጃቸው በሰይፍ ተቆረጠች እግዚአብሔር እንደ ቀድሞ ጤነኛ አደረገላቸውጉልያድን በሚያካክሉ በሞተሎሚ በወታደሮች በሽምግልና አቅማቸው ደም በአፍና በአፍንጫቸው እስኪተፉ ተደብድበዋል በንብ ቀፎ ተደርገው ወደ ገደል ተጥለዋል ከዚህ ሁሉ ስቃይና ደም መፍሰስ በኃላ እራሱ አልበቃ ብሏቸው ወደ አደባባይ ወጥቼ ስለ ስምህ መስክሬ እንደሰማዕታት ደሜን አፍስሼ ልሞት እፈልጋለው አሉ:: እግዚአብሔር ግን ከዚህ በላይ ሰማዕትነት አንደሌለ ሲነግረን እኔ ከአንተ ሰውነት በእመምህ ምክንያት የሚወጣውን ፈሳሽ እኔ እንደ ሰማዕታት ደም አቆጥርልሃለው ብሎ ዕረፍታቸውን በሰማዕታት ዕረፍት ቆጠረው ::
#አንዳንድ ሞኝ ሰዎች ይህን በማንበብ እንዴት የተክለ ሃይማኖት በእመም ከሰውነታቸው የወጣ ፈሳሽ(ተቅማጥ)እንዴት ከሰማዕታት ደም ጋር እኩል ይሆናል? ሲሉ ይሰማሉ ጌታችን መዳኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌሉ" ከሁሉ ከሚያንሱ ከእነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ እንኳ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል"ሲል ተደምጧል #ማቴ 25 ÷40 ታዲያ ለሰው ማድረግ ለእርሱ እንደማድረግ ተደርጎ ከተቆጠረ ወይም የአባታችን የሰውነት ( ፈሳሽ ተቅማጥ) እንዴት አንደ ሰማዕታት ደም መቆጠሩ ስህተት አይደለም እንደውም ይህ ነገር ስህተት ነው ከማለት ይልቅ የጌታችን ምሳሌ ስህተት ይመስላል ሰው ሲራብ ማብላት ሰው ሲጠማ ማጠጣት ሰው ሲታሰር ሄዶ መጠነቅ የማይራበው እግዚአብሔር ተርቦ እንደ ማብላት የማይጠማውን እግዚአብሔርን ተጠምቶ እንደ ማጠጣት የመይታሰረው እግዚአብሔርን ታስሮ እንደተጠየቀ አድርጉ መቁጠር አንዴት ይቻላል? ሌላውና ወሳኙ ነጥብ በህመም ከሰውነት የሚወጣ ፈሳሽ(ተቅማጥ) እና ደም ከሚያስከትሉት ችግር አንጻር ምንም ልዮነት የላቸውም በሳይንሱም ዓለም አገልግሎቱን ያልጨረሰ ፈሳሽ ከሰውነት ከወጣ በቶላ በሌላ ፈሳሽ ምግቦች እንዲተካ ይደረጋል ለምሳሌ" ሀተት "የተሰኘውን የጠቅማጥ በሽታ ብንወስድ ለሁለት ሳምንት እና ከዛ በላይ ለሆኑ ቀኞች ተተኪ ፈሳሽ ምግብ ሳንወስድ ዝም ብንለው ወደ ሞት ያደርሰናል ይህ ማለት ደም ሥር ተቆርጦ ብዙ ደም ከፈሰሰ በኃላ ምንም ተተኪ ፈሳሽ ሳይወስዱ እንደመቀመጥ እና እነደሚያስከትለው ችግር ሊቆጠር ይችላል:: ስለዚህ ሰማዕታት ደማቸውን አፈሰሱ ሲባል ለመኖር የሚያስችላቸውን ወሳኝ ነገር(ደም)ከሰውነታቸው ወጣ ማለት ነው አባታችን ተክለ ሃይማኖትም ልክ እንደ ደም ጥቅምነቱን ሳይሰጥ ከሰውነታቸው በመውጣቱ ደሙ ሳይፈስ ቀርቶ ቢሆን ኖሮ ሰማዕታት የክብርን አክሊል ወደ ሚቀዳጅባት ሞት እንደማይቀርቡ ሁሉ አባታችንም ለሞት ባልቀረቡ ነበር::

አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ቁጥራቸው ከሐዋርያት ወይም ከሰማዕታት ወገን ናቸው ተብሎ ብቻ አይታለፍም ከካህናተ ሰማይ ከሡራፌል ጋርም ይመደባሉ ለወትሮ ካህናተ ሰማይ ሡራፌል ቁጥራቸው 24ብቻ ነበሩ ኢትዮጵያዊው አባት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት የኢትዮጵያ ሲሳይ ሐዲስ ሐዋርያ ሰማእት ወነብይ ወካህን በተወለዱ እና ባደጉ ጊዜ ግን 25ለመሆን ተገደዋል ::ኃዳር 24ቀን 24ቱ ካህናተ ሰማይ ሡራፌል እንደለመዱት ሥሉስ ቅዱስ ብለው መንበሩን አያጠኑ ሳለ ድንገት ቅዱስ ሚካኤል ከሰዎች ወገን የሆነ ሰው ሲሆን እንደ መላእክት ስድስት የፀጋ ክንፎች የተሰጡት ብርሃን ዘኢትዮጵያ የሆነውን አባታችን ተክለ ሃይማኖትን ይዞ አመጣው የወርቅ ማዕጥንትም ተሰጠው ከዙፋኑም ወዳጄ ተክለ ሃይማኖት ቁጥርህ ከንግዲህ ወዲህ ከ24ቱ ሰማያተ ካህናት ጋር ይሁን አለው:: 25ተኛ ካህንም ሆኖ የሥላሴን መንበር ሥሉስ ቅዱስ እያለ በወርቅ ማዕጥንት አጠነ: : ራዕ ዮሐ 4÷4 ገድለተክለ ሃይማኖት
*ይቆየን*****
#የአባታችን እረድኤትና ምልጃው አይለየን ለዘላለሙ አሜን!!!
#በድጋሚ የተለጠፈ
አ.አ ኢትዮጵያ
ተክለ ኤል ኃ/ማርያም
ኅዳር 23ቀን 2012 ዓ,ም