#ደስ ይበልሽ#
-ቀዳሚት ሔዋንን ሰይጣንን ሸንግሎ ሞት ወደ ዓለም ገባ ፤ ዳግሚት ሔዋን ድንግል #ማርያምን ግን ቅዱስ #ገብርኤል አብሥሯት ሕይወት ተወለደልን።
-ሔዋንን ሰይጣን ሲያታልላት ብዙ መጠየቅ
እየቻለች አመነችው ፤ #እመቤታችንን ግን ቅዱስ #ገብርኤል ሲያበሥራት መረመረችው።
- ሔዋን መልአከ ጽልመትን አምና ነፍሰ ገዳዩ ቃየንን ወለደች ፤ ድንግል #ማርያም ግን ብርሃናዊውን መልአክ አምና ነፍሳችንን የሚያድነውን ወለደች።
- በሔዋን ከጸጋ መጉደልን ዐወቅን ፤ #በእመቤታችን በድንግል #ማርያም ግን በጸጋ መሞላትን ተረዳን።
"ደስ የተሰኘህ ሆነህ ምሥራችን የተናገርህ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው።ወደ እኛ የመጣ (ሰው የሆነን) የጌታን ልደት ነገርኸን ለድንግል #ማርያምም ጸጋን የተመላሽ ሆይ #እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ ብለህ አበሠርካት" (ውዳሴ #ማርያም ዘረቡዕ)
- ከሔዋን የተረፈውን ኃዘን ልጆቿ ሁሉ ለ5500 ዘመናት ተካፈሉ ፤ #ከእመቤታችን የተረፈውን ደስታ ግን ዓለም ሁሉ ተካፈለ።
-እኛም ከቅዱስ #ገብርኤል ጋር "ጸጋን የተመላሽ ደስተኛዪቱ ሆይ ደስ ይበልሽ"
-ከቅዱስ #ኤፍሬም ጋር "በሚገባ የአምላክ እናት ተብለሻልና ደስ ይበልሽ ፤ የሔዋን መድኃኒት ሆይ ደስ ይበልሽ" እንልሻለን።
#እመቤታችን #ማርያም ሆይ መልአከ ብሥራት አንቺን ደስ እንዳሰኘሽ ፤ በዛሬዪቱ ቀን ያዘንን እኛን ደስ አሰኚን!!!
-አማናዊ በዓለ ሱታፌ ያድርግልን አሜን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ታኅሣሥ 22/2017 ዓ.ም
-ቀዳሚት ሔዋንን ሰይጣንን ሸንግሎ ሞት ወደ ዓለም ገባ ፤ ዳግሚት ሔዋን ድንግል #ማርያምን ግን ቅዱስ #ገብርኤል አብሥሯት ሕይወት ተወለደልን።
-ሔዋንን ሰይጣን ሲያታልላት ብዙ መጠየቅ
እየቻለች አመነችው ፤ #እመቤታችንን ግን ቅዱስ #ገብርኤል ሲያበሥራት መረመረችው።
- ሔዋን መልአከ ጽልመትን አምና ነፍሰ ገዳዩ ቃየንን ወለደች ፤ ድንግል #ማርያም ግን ብርሃናዊውን መልአክ አምና ነፍሳችንን የሚያድነውን ወለደች።
- በሔዋን ከጸጋ መጉደልን ዐወቅን ፤ #በእመቤታችን በድንግል #ማርያም ግን በጸጋ መሞላትን ተረዳን።
"ደስ የተሰኘህ ሆነህ ምሥራችን የተናገርህ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ሆይ የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው።ወደ እኛ የመጣ (ሰው የሆነን) የጌታን ልደት ነገርኸን ለድንግል #ማርያምም ጸጋን የተመላሽ ሆይ #እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ ብለህ አበሠርካት" (ውዳሴ #ማርያም ዘረቡዕ)
- ከሔዋን የተረፈውን ኃዘን ልጆቿ ሁሉ ለ5500 ዘመናት ተካፈሉ ፤ #ከእመቤታችን የተረፈውን ደስታ ግን ዓለም ሁሉ ተካፈለ።
-እኛም ከቅዱስ #ገብርኤል ጋር "ጸጋን የተመላሽ ደስተኛዪቱ ሆይ ደስ ይበልሽ"
-ከቅዱስ #ኤፍሬም ጋር "በሚገባ የአምላክ እናት ተብለሻልና ደስ ይበልሽ ፤ የሔዋን መድኃኒት ሆይ ደስ ይበልሽ" እንልሻለን።
#እመቤታችን #ማርያም ሆይ መልአከ ብሥራት አንቺን ደስ እንዳሰኘሽ ፤ በዛሬዪቱ ቀን ያዘንን እኛን ደስ አሰኚን!!!
-አማናዊ በዓለ ሱታፌ ያድርግልን አሜን!!!
#ኢዮብ ክንፈ
#ታኅሣሥ 22/2017 ዓ.ም
❤ከዕለቱ #መዝሙር❤
#መዝሙረ ዳዊት 69
አቤቱ፥ እኔን ለማዳን ተመልከት፤ አቤቱ፥ እኔን ለመርዳት ፍጠን።
ነፍሴን የሚሹአት ይፈሩ ይጐስቍሉም፥ ክፉንም የሚመክሩብኝ ወደ ኋላቸው ይመለሱ ይፈሩም።
እንኳ እንኳ የሚሉኝ አፍረው ወዲያው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።
የሚሹህ ሁሉ በአንተ ሐሤት ያድርጉ ደስ ይበላቸው፤ ማዳንህን የሚወድዱ ሁልጊዜ፦ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ይበሉ።
እኔ ችግረኛና ምስኪን ነኝ፤ አቤቱ፥ እርዳኝ፤ ረዳቴ ታዳጊዬም አንተ ነህ፤ አቤቱ፥ አትዘግይ።
እንኳን ለጻድቁ፣ለየዋሁ፣ለደጉ፣ለብእሴ #እግዚአብሔር ለቅዱስ #ዳዊት በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ!!!የቅዱስ #ዳዊት በረከቱ ይደርብን!!!
#ታኅሣሥ 23/2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#መዝሙረ ዳዊት 69
አቤቱ፥ እኔን ለማዳን ተመልከት፤ አቤቱ፥ እኔን ለመርዳት ፍጠን።
ነፍሴን የሚሹአት ይፈሩ ይጐስቍሉም፥ ክፉንም የሚመክሩብኝ ወደ ኋላቸው ይመለሱ ይፈሩም።
እንኳ እንኳ የሚሉኝ አፍረው ወዲያው ወደ ኋላቸው ይመለሱ።
የሚሹህ ሁሉ በአንተ ሐሤት ያድርጉ ደስ ይበላቸው፤ ማዳንህን የሚወድዱ ሁልጊዜ፦ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ይበሉ።
እኔ ችግረኛና ምስኪን ነኝ፤ አቤቱ፥ እርዳኝ፤ ረዳቴ ታዳጊዬም አንተ ነህ፤ አቤቱ፥ አትዘግይ።
እንኳን ለጻድቁ፣ለየዋሁ፣ለደጉ፣ለብእሴ #እግዚአብሔር ለቅዱስ #ዳዊት በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ!!!የቅዱስ #ዳዊት በረከቱ ይደርብን!!!
#ታኅሣሥ 23/2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
“#ከሕፃናትና ከሚጠቡ ልጆች አፍ ምስጋናን አዘጋጀህ ስለ ጠላትህ፥ ጠላትንና ቂመኛን ለማጥፋት።”(መዝ 8፥2)
#ፍስሐ #ጽዮን የተባለ #ተክለሃይማኖት በተወለደ በሦስተኛው ቀን "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ እግዚአብሔርን አመሰገነ።
#ነቢየ #እግዚአብሔር #ኤርምያስ “በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ።” (ኤር 1፥5)እንደተባለ ቅዱስ #ተክለሃይማኖት ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ነቢይ ሆኖ ለእግዚአብሔር ተለየ።
#መልአከ #ብርሃን ቅዱስ #ገብርኤል ስለ ቅዱስ #ዮሐንስ መጥምቅ“በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤”( ሉቃስ 1፥15) እንዳለ #ተክለሃይማኖት ጻድቅ ከዓለምና ከምኞቷ ሁሉ የተለየ ፤ በጌታም ፊት ታላቅ የተባለ ፤ መንፈስ ቅዱስም የሞላበት ነው።ዳግመኛም መልአክ “ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።”(ሉቃ 1፥14) እንዳለ በፍስሐ ጽዮን (በጽዮን ደስታ) በ #ተክለሃይማኖት መወለድ ለጊዜው አባቱ ቅዱስ #ጸጋ ዘአብና እናቱ ቅድስት #እግዚእ ኃረያ ተደስተዋል ፤ ለፍጻሜው ግን ጽዮን የተባለች ቅድስት #ቤተክርስቲያን ተደስታለች።
#ቅዱስ #ጳውሎስም ስለ ራሱ “ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም”(ገላ1፥15-16) እንዳለ አባታችን #ተክለሃይማኖት በጸጋ #መንፈስ #ቅዱስ ለስብከተ ወንጌል ገና በማኅፀን ተጠራ።
#ጌታም በወንጌል ስለ እነ #ተክለሃይማኖት እንዲህ አለ “በእናት ማኅፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አሉ”(ማቴ 19፥12)
#እንኳን አደረሳችሁ!!!
#ታኅሣሥ 26 /2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ
#ፍስሐ #ጽዮን የተባለ #ተክለሃይማኖት በተወለደ በሦስተኛው ቀን "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብሎ እግዚአብሔርን አመሰገነ።
#ነቢየ #እግዚአብሔር #ኤርምያስ “በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማኅፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ፥ ለአሕዛብም ነቢይ አድርጌሃለሁ።” (ኤር 1፥5)እንደተባለ ቅዱስ #ተክለሃይማኖት ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ነቢይ ሆኖ ለእግዚአብሔር ተለየ።
#መልአከ #ብርሃን ቅዱስ #ገብርኤል ስለ ቅዱስ #ዮሐንስ መጥምቅ“በጌታ ፊት ታላቅ ይሆናልና፥ የወይን ጠጅና የሚያሰክር መጠጥ አይጠጣም፤ ገናም በእናቱ ማኅፀን ሳለ መንፈስ ቅዱስ ይሞላበታል፤”( ሉቃስ 1፥15) እንዳለ #ተክለሃይማኖት ጻድቅ ከዓለምና ከምኞቷ ሁሉ የተለየ ፤ በጌታም ፊት ታላቅ የተባለ ፤ መንፈስ ቅዱስም የሞላበት ነው።ዳግመኛም መልአክ “ደስታና ተድላም ይሆንልሃል፥ በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።”(ሉቃ 1፥14) እንዳለ በፍስሐ ጽዮን (በጽዮን ደስታ) በ #ተክለሃይማኖት መወለድ ለጊዜው አባቱ ቅዱስ #ጸጋ ዘአብና እናቱ ቅድስት #እግዚእ ኃረያ ተደስተዋል ፤ ለፍጻሜው ግን ጽዮን የተባለች ቅድስት #ቤተክርስቲያን ተደስታለች።
#ቅዱስ #ጳውሎስም ስለ ራሱ “ነገር ግን በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ የለየኝ በጸጋውም የጠራኝ እግዚአብሔር በአሕዛብ መካከል ስለ እርሱ ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ልጁን በእኔ ሁኔታ ሊገልጥ በወደደ ጊዜ፥ ወዲያው ከሥጋና ከደም ጋር አልተማከርሁም”(ገላ1፥15-16) እንዳለ አባታችን #ተክለሃይማኖት በጸጋ #መንፈስ #ቅዱስ ለስብከተ ወንጌል ገና በማኅፀን ተጠራ።
#ጌታም በወንጌል ስለ እነ #ተክለሃይማኖት እንዲህ አለ “በእናት ማኅፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አሉ”(ማቴ 19፥12)
#እንኳን አደረሳችሁ!!!
#ታኅሣሥ 26 /2017 ዓ.ም
#ኢዮብ ክንፈ