#ያንሰራራ_ነፍስ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በእየሩስአሌም_ነጋ
ግን ለምን? ለምን ባሌ...እኔን ማሰብ ተሳነው? አሁን አሁን እስከመኖሬም ማወቁን እጠራጠራለሁ። ለስሙ አብረን ውለን እናድራለን፡፡ ለወገን ለዘመድ የሚተርፍ ፍቅር አለው፡፡ ለኔ ያልሆነበት ምክንያት ምንድነው? ምን አደረኩት? ልጆቼን ለማሳደግ ስል የሰው ደሃ እንደሆንኩ ያውቃል፡፡ የራሱን ፍላጎትና እርካታ በማዳመጥ ፈንታ የኔን ስሜት አንድ ቀን እንኳን አዳምጦልኝ
አያውቅም፡፡ ታዲያ እኔ ፍቅርን ብናፍቅ ማን ይፈርድብኛል? ማን ይከሰኛል?' ከራሷ ጋር እየተሟገተችና ሰው እንዳያያት ወደኋላዋ እየተገላመጠች ከቀጠሮው ቦታ ደረሰች፡፡
በጻፈላት መልዕክት መሰረት የተከራየበትን ሆቴል ለማግኘት ረዘም ያለ ጊዜ ወስዶባታል፡፡ በድካምና በፍርሃት የዛለ ሰውነቷን እየጎተተች የተከራየበት ሆቴል ስትደርስ እግሯ መንቀጥቀጥ ጀመረ።
ጆ ያረፈበትን ክፍል ስታይ ዛሬ የመጀመሪያ ቀኗ ነው፡፡ ስትገባ ጅቡቲያዊው ወጣት ሽርጡን እንዳሸረጠ
ከተቀመጠበት ምንጣፍ ላይ ተነሳ፡፡ “ኦ! ቢ ኦ! ቢ" እያለ ተጠጋት።
እሱ የሷን ፣ እሷ የሱን ስም መያዝ ስላልቻሉ ስማቸውን አሳጥረው በመጀመሪያው ፊደል ይጠራራሉ፡፡
ፍርሃት ያጠላበትን ፊቷን እንደምንም ደብቃ ፈገግ አለች፡፡እጆቹን በወገቧ ዙሪያ ጠምጥሞ አቀፋት። እንደገለባ ቀለላት፡፡
በእቅፏ የማይሞላ ደቃቃ ነገር ነው።
አጥንት እጆቹን ከላይዋ ላይ ሲያነሳ ተራ በተራ ቃኘቻቸው።በአካሉ ላይ ስጋ ያለው አይመስልም፡፡ በበለዘና በጠቆረ ቆዳ የተለበጠ እንጨት መሰላት፡፡ ከወገቡ በላይ እራቁቱን ነው።
ዐይኖቹን ስውነቷ ላይ እያንከባለለ በመጎምጀት አያት። ዛሬ እንደሌላው ሁሉ ቀን አልተሸፋፈነችም። የሰውነቷን ቅርጽ በውል ለይቶ የሚያሳይ ልብስ ለብሳለች። ፀጉሯንም ከተደበቀበት አውጥታ ነስንሳዋለች። ረጅም አንገቷንና ሰልካካ አፍንጫዋን ተራ በተራ ሳመና ጥርት ያለ ጠይም ቆዳዋን እየዳበስ ትላልቅ አይኖቿን በፍቅር ተመለከታቸው። “ኦ ቢ ቢዩቲፉል” አለ፡፡ በወገቧ ዙሪያ እጆቹን አቆላልፎ ቀጭን ወገቧን እየለካ።
ሹራብ፣ ሸሚዝ፣ ሱሪና ሌሎችም ልብሶች ተደበላልቀው በወንበር ላይ ተከምረዋል፡፡ አገልግሎታቸውን የጨረሱ የጁስ
ካርቶኖችና ቁርጥራጭ ቸኮሌቶች በአነስተኛ ጠረጴዛ ላይ ተበታትነዋል፡፡
ቢ እነዚህን ሁሉ ዝርክርኮች በተዝረከረከ መንፈሷ እየቃኘች ልትደብቀው ያልቻለችውን ፍርሐትና ድብርቷን ይዛ ከአልጋው ጫፍ ላይ ተቀመጠች፡፡
ጆ አጠገቧ ተቀመጠና ከንፈሮቿን እየተስገበገበ ጎረሳቸው፡፡
እፉ ውስጥ ያለው የጫት ድቃቂ ወደ አፏ ሲዘልቅ ምራቋን ልትተፋ ሞከረችና ይከፋዋል ብላ ስላሰበች በትግል እየተናነቃት ዋጠችው።
ከንፈሯን በማፈግፈግ ከከንፈሩ አላቃ ገፋ አደረገችው፡፡በአድናቆት ተመለከታት፡፡ “ኦ! ቢ ኦ! ቢ” ተመልሶ ወደ ከንፈሮቿ
ቀረበ።
በድጋሚ ገፋችውና “ኖ...እ... ዛሬ የመጣሁት ከአንተ ጋር ሻይ ለመጠጣት ነው እንጂ ለመቆየት አይደለም፡፡ አየህ መጀመሪያ መግባባት አለብን፡፡”
እጆቿን እያወራጨች ለማስረዳት ሞከረች፡፡ አልገባውም፡፡ትንሽ እንደመደናገር ብሎ፣
“አሌብን አለቢን?” አለና በመጨረሻ የተናገረችውን ቃል ደገመው፡፡ እንዳልገባው አወቀች፡፡ እንዴት እንደምታስረዳው ጨነቃት።
“ቺግር አለ? ቺግር አለ?” ካለ በኋላ ራሱን ነቀነቀና ወደ ኋላው አልጋ ላይ ተንጋለለ፡፡ አሻግራ ከፊት ለፊታቸው ያለውን ፎቅ
አየችና ሰዎች የሚመለከቷት ስለመሰላት ተነስታ መጋረጃውን ጋረደች፡፡
እዚያው መስኮቱ ጋር እንዳለች በእንግሊዝኛ በቀጣዩ ቀን እንደምትመጣ ነገረችው፡ በአዎንታ ራሱን ሲነቀንቅ ሀሳቧ የገባው መሰላት።
እተቀመጠችበት ትቷት ወደ መጸደጃ ቤት ገባ፡፡ የገላ መታጠቢያ ውሃ ሲለቀቅ አደመጠች፡፡ '
ተመስገን ሀሳቡን ቀይሯል፡፡ አለችና በፍርሐት የተሸማቀቀ ሰውነቷን ፈታ አደረገች፡፡
እየቆየች ስታስበው ለምን እንደመጣች ገረማት። ትናንት ጠዋት ገንዘብና ፍቅርን እለግስሻለሁ ነይ ብሎ በእንግሊዝኛ
በሞባይል መልእክት የጻፈላት ትዝ አላት፡፡ መልእክቱን የጻፈለት ሰው እንዳለ ተገንዝባለች፡፡ ምክንያቱም ከአረብኛና ከፈረንሳይኛ በስተቀር ለመግባቢያ የሚሆን ቋንቋ የለውም፡፡
ገንዘብና ፍቅር ባንድ ላይ የሚቸሩ ቁሶች ናቸው እንዴ?”እራሷን ጠየቀች፡፡ ግን ሁለቱንም ነገሮች ብትፈልጋቸውም
እንደፍቅር ግን የራባት ነገር የለም፡፡
የጆ ክፍል ምቾት የሚስጥ አይደለም፡፡ ሁለት ሻንጣዎች እዚህና እዚያ ወድቀዋል፡፡ የአልጋ ልብሱ መሬት ላይ ተዘርግቷል።እላዩ ላይ በአንድ ሳህን ላይ የተለነቀጠ ጎመን የሚመስል ነገር
ተቀምጧል። ምናልባት የታኘከ ጫት ይሆናል ብላ አሰበች፡፡
የክፍሉ ሽታ ከራሷ ሽቶ ጋር ተዳምሮ ውስጥን የሚያውክ ሽታ ፈጥሯል። “ጆ ትክክለኛ ፍቅር ይሰጠኛል?” ለሚለው ሀሳቧ እርግጠኛ አይደለችም፡፡
ግን በባሏ ተስፋ በቆረጠች አግኝታዋለች፡በተዋወቁበት ጥቂት ጊዜ ውስጥ እሷን ከማድነቅ የተቆጠበበት ደቂቃ አልነበረም፡፡
ከጆ የምትወድለት ነገር ቢኖር አድናቆቱን መግለጹና ለደቂቃ ከላይዋ ላይ የማይነሱ ዐይኖቹን ነው፡፡ ግን ፍቅር እንዳልያዛት
እርግጠኛ ነች፡፡የባሏን ቁመና አሰበች፡፡ ቆንጆ ነው! ቆንጆ! ታዲያ ምን ዋጋ
አለው? ግን ለምን ይሆን ስሜቴ የማይገባው? የምለብሰው፣
የምበላውና የምጠጣው፣ የማይገደው?”
“ቢ ካም! ቢ ካም!” አላት፡፡
በፍርሃት የመታጠቢያ ክፍሉን ከፍታ ጭንቅላቷን ወደ ውስጥ አስገብታ ተመለከተች፡፡ የተገመሱና የጠቆሩ ጥርሶቹን አሳያት፡፡ ደስ የሚልና ብሩህ ፈገግታ ከፊቱ ላይ አነበበች፡፡ እንደዚህ
አይነት አስደሳች ፈገግታ ከአስቀያሚ ጥርሶች መሐል ይፈጠራል ብላ አስባ አታውቅም፡፡
ካም! ካም!” አለና እጆቹን በገላው ላይ አሻሻቸው፡፡ ነይና እንታጠብ እንዳላት ገባትና ወደኋላ አፈግፍጋ ወደ ቀደመው ቦታ ተመልሳ ቁጭ አለች፡፡
ወጥታ ልትሄድ አሰኝቷት ወደ በሩ ተመለከተች፡፡ ምን ማድረግ እንዳለባት እርግጠኛ አልሆነችም፡፡
“ምን ፈልጌ መጣሁ?...f ለምን? ... ግን አይፈረድብኝም፡፡ በፍቅር ዐይኑ እያየ የሚንከባከበኝ እፈልጋለሁ፡፡ አምላኬ መጥፊያዬ ደረሰ ማለት ነው? እኔ አልቻልኩም፡፡ አንተ ከቻልክ ግን ከዚህ ብልግና አውጣኝ?” ፈጣሪዋን ተማጸነችዉ።
“እውነት ይሄ ሰው እውነተኛ ፍቅር ይለግሰኛል? እስቲ ለማንኛውም ልሞክረው፡፡ እኔ የምፈልገው ፍቅር ምን አይነት ነው? ግዚያዊ ፍላጎቱን የሚያረካብኝን ወንድ ወይስ...?”
ራሷ ለራሷ ጥያቄ ሆነች፡፡ ወደ ራሷ ድምዳሜ የደረሰች ሲመስላት ደግሞ፣ አሁን የኔን ነፍስ የሚያስጨንቃት ፍቅር
የማጣት ጉዳይ ነው ብላ ለሚጮኸው ውስጧ መለሰችለት።
እሰራልሀለሁ! እንዳስጠላሁህ እጠላሀለሁ!፡፡ አለቅህም! አሁን
በእርግጥ የምትለኝን ሆኛለሁ። እንኳን
ደስ ያለህ! ምንም የማላውቀዋን ጨዋ “አመንዝራ! ብለህ ትሰድበኝ ነበር፡፡
እግዚአብሔር ይይልህ፣ አመነዘርኩልህ... እንዴት አይነት ደካማ ሰው ነኝ!”
ግድግዳውን ቃኘች፤ ቀለሙ በያለበት ተፋፍቋል፡፡ በተፋቀው ቀለም ውስጥ ዝብርቅርቅ ስእሎች ታዩዋት፡፡ በስእሎቹ ውስጥ እርሷ አለች፡፡ ከባሏ ሊነጥላት የእርሷን ቀሚስ የሚጎትት ኮስማና ሰው
ታያት። አሁን በስስት እያየ የሚያደንቃት ትፈልጋለች። “እኔ አድናቆት ፈላጊ ሴት ሆኜ ነው? አይ ማንኛዋም ሴት ከማንም ወንድ ከፍተኛ ግምት የሚሰጠውን የተቃራኒ ጾታ እንክብካቤ ትወዳለች።
እኔ ብቻ አይደለሁም፡፡ ጆ ሲያየኝ ውሎ ሲያየኝ ሲያድር አይጠግብም፡፡ በርከት ላለ ግዜ ያደንቀኛል። ጥሩ ፍቅር ሊለግሰኝ ፍቃደኛ እንደሆነ ነግሮኛል። ምን ዋጋ አለው? በየትኛው ቋንቋችን
እንግባባ? የጭንቀት ትንፋሽ በረጅሙ
፡
፡
#ክፍል_አንድ
፡
፡
#በእየሩስአሌም_ነጋ
ግን ለምን? ለምን ባሌ...እኔን ማሰብ ተሳነው? አሁን አሁን እስከመኖሬም ማወቁን እጠራጠራለሁ። ለስሙ አብረን ውለን እናድራለን፡፡ ለወገን ለዘመድ የሚተርፍ ፍቅር አለው፡፡ ለኔ ያልሆነበት ምክንያት ምንድነው? ምን አደረኩት? ልጆቼን ለማሳደግ ስል የሰው ደሃ እንደሆንኩ ያውቃል፡፡ የራሱን ፍላጎትና እርካታ በማዳመጥ ፈንታ የኔን ስሜት አንድ ቀን እንኳን አዳምጦልኝ
አያውቅም፡፡ ታዲያ እኔ ፍቅርን ብናፍቅ ማን ይፈርድብኛል? ማን ይከሰኛል?' ከራሷ ጋር እየተሟገተችና ሰው እንዳያያት ወደኋላዋ እየተገላመጠች ከቀጠሮው ቦታ ደረሰች፡፡
በጻፈላት መልዕክት መሰረት የተከራየበትን ሆቴል ለማግኘት ረዘም ያለ ጊዜ ወስዶባታል፡፡ በድካምና በፍርሃት የዛለ ሰውነቷን እየጎተተች የተከራየበት ሆቴል ስትደርስ እግሯ መንቀጥቀጥ ጀመረ።
ጆ ያረፈበትን ክፍል ስታይ ዛሬ የመጀመሪያ ቀኗ ነው፡፡ ስትገባ ጅቡቲያዊው ወጣት ሽርጡን እንዳሸረጠ
ከተቀመጠበት ምንጣፍ ላይ ተነሳ፡፡ “ኦ! ቢ ኦ! ቢ" እያለ ተጠጋት።
እሱ የሷን ፣ እሷ የሱን ስም መያዝ ስላልቻሉ ስማቸውን አሳጥረው በመጀመሪያው ፊደል ይጠራራሉ፡፡
ፍርሃት ያጠላበትን ፊቷን እንደምንም ደብቃ ፈገግ አለች፡፡እጆቹን በወገቧ ዙሪያ ጠምጥሞ አቀፋት። እንደገለባ ቀለላት፡፡
በእቅፏ የማይሞላ ደቃቃ ነገር ነው።
አጥንት እጆቹን ከላይዋ ላይ ሲያነሳ ተራ በተራ ቃኘቻቸው።በአካሉ ላይ ስጋ ያለው አይመስልም፡፡ በበለዘና በጠቆረ ቆዳ የተለበጠ እንጨት መሰላት፡፡ ከወገቡ በላይ እራቁቱን ነው።
ዐይኖቹን ስውነቷ ላይ እያንከባለለ በመጎምጀት አያት። ዛሬ እንደሌላው ሁሉ ቀን አልተሸፋፈነችም። የሰውነቷን ቅርጽ በውል ለይቶ የሚያሳይ ልብስ ለብሳለች። ፀጉሯንም ከተደበቀበት አውጥታ ነስንሳዋለች። ረጅም አንገቷንና ሰልካካ አፍንጫዋን ተራ በተራ ሳመና ጥርት ያለ ጠይም ቆዳዋን እየዳበስ ትላልቅ አይኖቿን በፍቅር ተመለከታቸው። “ኦ ቢ ቢዩቲፉል” አለ፡፡ በወገቧ ዙሪያ እጆቹን አቆላልፎ ቀጭን ወገቧን እየለካ።
ሹራብ፣ ሸሚዝ፣ ሱሪና ሌሎችም ልብሶች ተደበላልቀው በወንበር ላይ ተከምረዋል፡፡ አገልግሎታቸውን የጨረሱ የጁስ
ካርቶኖችና ቁርጥራጭ ቸኮሌቶች በአነስተኛ ጠረጴዛ ላይ ተበታትነዋል፡፡
ቢ እነዚህን ሁሉ ዝርክርኮች በተዝረከረከ መንፈሷ እየቃኘች ልትደብቀው ያልቻለችውን ፍርሐትና ድብርቷን ይዛ ከአልጋው ጫፍ ላይ ተቀመጠች፡፡
ጆ አጠገቧ ተቀመጠና ከንፈሮቿን እየተስገበገበ ጎረሳቸው፡፡
እፉ ውስጥ ያለው የጫት ድቃቂ ወደ አፏ ሲዘልቅ ምራቋን ልትተፋ ሞከረችና ይከፋዋል ብላ ስላሰበች በትግል እየተናነቃት ዋጠችው።
ከንፈሯን በማፈግፈግ ከከንፈሩ አላቃ ገፋ አደረገችው፡፡በአድናቆት ተመለከታት፡፡ “ኦ! ቢ ኦ! ቢ” ተመልሶ ወደ ከንፈሮቿ
ቀረበ።
በድጋሚ ገፋችውና “ኖ...እ... ዛሬ የመጣሁት ከአንተ ጋር ሻይ ለመጠጣት ነው እንጂ ለመቆየት አይደለም፡፡ አየህ መጀመሪያ መግባባት አለብን፡፡”
እጆቿን እያወራጨች ለማስረዳት ሞከረች፡፡ አልገባውም፡፡ትንሽ እንደመደናገር ብሎ፣
“አሌብን አለቢን?” አለና በመጨረሻ የተናገረችውን ቃል ደገመው፡፡ እንዳልገባው አወቀች፡፡ እንዴት እንደምታስረዳው ጨነቃት።
“ቺግር አለ? ቺግር አለ?” ካለ በኋላ ራሱን ነቀነቀና ወደ ኋላው አልጋ ላይ ተንጋለለ፡፡ አሻግራ ከፊት ለፊታቸው ያለውን ፎቅ
አየችና ሰዎች የሚመለከቷት ስለመሰላት ተነስታ መጋረጃውን ጋረደች፡፡
እዚያው መስኮቱ ጋር እንዳለች በእንግሊዝኛ በቀጣዩ ቀን እንደምትመጣ ነገረችው፡ በአዎንታ ራሱን ሲነቀንቅ ሀሳቧ የገባው መሰላት።
እተቀመጠችበት ትቷት ወደ መጸደጃ ቤት ገባ፡፡ የገላ መታጠቢያ ውሃ ሲለቀቅ አደመጠች፡፡ '
ተመስገን ሀሳቡን ቀይሯል፡፡ አለችና በፍርሐት የተሸማቀቀ ሰውነቷን ፈታ አደረገች፡፡
እየቆየች ስታስበው ለምን እንደመጣች ገረማት። ትናንት ጠዋት ገንዘብና ፍቅርን እለግስሻለሁ ነይ ብሎ በእንግሊዝኛ
በሞባይል መልእክት የጻፈላት ትዝ አላት፡፡ መልእክቱን የጻፈለት ሰው እንዳለ ተገንዝባለች፡፡ ምክንያቱም ከአረብኛና ከፈረንሳይኛ በስተቀር ለመግባቢያ የሚሆን ቋንቋ የለውም፡፡
ገንዘብና ፍቅር ባንድ ላይ የሚቸሩ ቁሶች ናቸው እንዴ?”እራሷን ጠየቀች፡፡ ግን ሁለቱንም ነገሮች ብትፈልጋቸውም
እንደፍቅር ግን የራባት ነገር የለም፡፡
የጆ ክፍል ምቾት የሚስጥ አይደለም፡፡ ሁለት ሻንጣዎች እዚህና እዚያ ወድቀዋል፡፡ የአልጋ ልብሱ መሬት ላይ ተዘርግቷል።እላዩ ላይ በአንድ ሳህን ላይ የተለነቀጠ ጎመን የሚመስል ነገር
ተቀምጧል። ምናልባት የታኘከ ጫት ይሆናል ብላ አሰበች፡፡
የክፍሉ ሽታ ከራሷ ሽቶ ጋር ተዳምሮ ውስጥን የሚያውክ ሽታ ፈጥሯል። “ጆ ትክክለኛ ፍቅር ይሰጠኛል?” ለሚለው ሀሳቧ እርግጠኛ አይደለችም፡፡
ግን በባሏ ተስፋ በቆረጠች አግኝታዋለች፡በተዋወቁበት ጥቂት ጊዜ ውስጥ እሷን ከማድነቅ የተቆጠበበት ደቂቃ አልነበረም፡፡
ከጆ የምትወድለት ነገር ቢኖር አድናቆቱን መግለጹና ለደቂቃ ከላይዋ ላይ የማይነሱ ዐይኖቹን ነው፡፡ ግን ፍቅር እንዳልያዛት
እርግጠኛ ነች፡፡የባሏን ቁመና አሰበች፡፡ ቆንጆ ነው! ቆንጆ! ታዲያ ምን ዋጋ
አለው? ግን ለምን ይሆን ስሜቴ የማይገባው? የምለብሰው፣
የምበላውና የምጠጣው፣ የማይገደው?”
“ቢ ካም! ቢ ካም!” አላት፡፡
በፍርሃት የመታጠቢያ ክፍሉን ከፍታ ጭንቅላቷን ወደ ውስጥ አስገብታ ተመለከተች፡፡ የተገመሱና የጠቆሩ ጥርሶቹን አሳያት፡፡ ደስ የሚልና ብሩህ ፈገግታ ከፊቱ ላይ አነበበች፡፡ እንደዚህ
አይነት አስደሳች ፈገግታ ከአስቀያሚ ጥርሶች መሐል ይፈጠራል ብላ አስባ አታውቅም፡፡
ካም! ካም!” አለና እጆቹን በገላው ላይ አሻሻቸው፡፡ ነይና እንታጠብ እንዳላት ገባትና ወደኋላ አፈግፍጋ ወደ ቀደመው ቦታ ተመልሳ ቁጭ አለች፡፡
ወጥታ ልትሄድ አሰኝቷት ወደ በሩ ተመለከተች፡፡ ምን ማድረግ እንዳለባት እርግጠኛ አልሆነችም፡፡
“ምን ፈልጌ መጣሁ?...f ለምን? ... ግን አይፈረድብኝም፡፡ በፍቅር ዐይኑ እያየ የሚንከባከበኝ እፈልጋለሁ፡፡ አምላኬ መጥፊያዬ ደረሰ ማለት ነው? እኔ አልቻልኩም፡፡ አንተ ከቻልክ ግን ከዚህ ብልግና አውጣኝ?” ፈጣሪዋን ተማጸነችዉ።
“እውነት ይሄ ሰው እውነተኛ ፍቅር ይለግሰኛል? እስቲ ለማንኛውም ልሞክረው፡፡ እኔ የምፈልገው ፍቅር ምን አይነት ነው? ግዚያዊ ፍላጎቱን የሚያረካብኝን ወንድ ወይስ...?”
ራሷ ለራሷ ጥያቄ ሆነች፡፡ ወደ ራሷ ድምዳሜ የደረሰች ሲመስላት ደግሞ፣ አሁን የኔን ነፍስ የሚያስጨንቃት ፍቅር
የማጣት ጉዳይ ነው ብላ ለሚጮኸው ውስጧ መለሰችለት።
እሰራልሀለሁ! እንዳስጠላሁህ እጠላሀለሁ!፡፡ አለቅህም! አሁን
በእርግጥ የምትለኝን ሆኛለሁ። እንኳን
ደስ ያለህ! ምንም የማላውቀዋን ጨዋ “አመንዝራ! ብለህ ትሰድበኝ ነበር፡፡
እግዚአብሔር ይይልህ፣ አመነዘርኩልህ... እንዴት አይነት ደካማ ሰው ነኝ!”
ግድግዳውን ቃኘች፤ ቀለሙ በያለበት ተፋፍቋል፡፡ በተፋቀው ቀለም ውስጥ ዝብርቅርቅ ስእሎች ታዩዋት፡፡ በስእሎቹ ውስጥ እርሷ አለች፡፡ ከባሏ ሊነጥላት የእርሷን ቀሚስ የሚጎትት ኮስማና ሰው
ታያት። አሁን በስስት እያየ የሚያደንቃት ትፈልጋለች። “እኔ አድናቆት ፈላጊ ሴት ሆኜ ነው? አይ ማንኛዋም ሴት ከማንም ወንድ ከፍተኛ ግምት የሚሰጠውን የተቃራኒ ጾታ እንክብካቤ ትወዳለች።
እኔ ብቻ አይደለሁም፡፡ ጆ ሲያየኝ ውሎ ሲያየኝ ሲያድር አይጠግብም፡፡ በርከት ላለ ግዜ ያደንቀኛል። ጥሩ ፍቅር ሊለግሰኝ ፍቃደኛ እንደሆነ ነግሮኛል። ምን ዋጋ አለው? በየትኛው ቋንቋችን
እንግባባ? የጭንቀት ትንፋሽ በረጅሙ
👍4
#ያንሰራራ_ነፍስ
፡
፡
#ክፍል_ሁለት(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በእየሩስአሌም_ነጋ
ጆ በሐሳብ እርቃ የሄደችውን ቢ በዐይኗ የሞላውን እንባ አይቶ በርከክ አለና አገጯን ይዞ እየተመለከታት፡፡ “ቺግር አለ?” አለ።
“ችግር አለ” የሚለውን ቋንቋ ብቻ እንዴት እንደለመደው ደንቋታል። “ምናለ አማርኛ ቢስማና የልቤን በነገርኩት፡፡ ይሄኔ
አውቄ የምባልግ፣ በኃጢአት የወደኩ፣ አዳፋ አድርጎ ያየኝ ይሆናል፡፡
ምክንያቱም ባልና ልጆች እንዳሉኝ ነግሬዋለሁ። እሱንም ባስተርጓሚ።
ምን እንደምትፈልግ ግራ የገባው ይመስላል። ገፋ አድርጎ ወደ አልጋው አንጋለላት፤ እንደተኛች መላ አካሉን አየችው፡፡
ሀፍረተ ስጋው ከመላው አካሉ የሚበልጥ መሰላት። ደግሞ ከወደ ጫፉ ለምጽ የያዘዘው ይመስል ነጽቷል። ቀፈፋት፡፡ ዳበሳት፡፡ ዝም አለችው፡፡ እጇን ይዞ አካሉን እንድትዳብስለት በእጁ አስነካት።
እሷ ግን በተቃውሞ ወደ ነበረበት ቦት መለሰችው፡፡
ቀስ እያለ እላይዋ ላይ የተጋደመው ጆ አንዳች ኃይል የተመላ ይመስል ከብዶ ነፍስና ስጋዋን የሚለያይባት መሰላት፡፡
ያንን ሩህሩህና ኩሩ ባሏን በዐይነ ህሊናዋ አየችው። ሰፊና ግዙፍ ትከሻ ቢኖረውም ይህን ያክል አይከብዳትም፡ታከብረዋለች፣
ትወደዋለች ከሱ ሌላ ምንም አትፈልግም ነበር፡፡ እሱ ግን አንደ አንድ ግኡዝ ነገር መገልገያ አድርጓታል። እሱ ለብዙ ሰዎች ጉርስና ልብስ ነው፡፡ እሷ ግን በእርዛትና በጥማት ብትንገላታ ግድ የለውም፡፡
እኔ ገንዘብ ከሰው መጠበቅ የለብኝም፡፡ ምክንያቱም የመስራት አቅምና ችሎታ አለኝ፡፡ ስራ መስራት አለብኝ፡፡ ግፋ ቢል
ባሌን ላጣው እችላለሁ፡፡ ለገንዘብና ለፍቅር አሳልፌ ጨዋነቴን ልለውጠው አልፈልግም።ከነፍስና ስጋዋ ጋር ተሟገተች። ወዲያው ደግሞ ግን ደግሞ አይዞሽ እያለ የጎደለኝን እየፈለገ ሲከፋኝ እያባበለ ስሜቴን የሚያዳምጥ ወንድ እፈልጋለሁ፡፡ እኔ ለባሌ የማደርገውን
እሱም ለኔ ሊያደርግ ግድ ነው፡፡ አለበለዚያ ግን... አለች በትግሉ
መካከል እየተወራጨች።
ጆ ከንፈሯን የማላመጥ ያህል በአፉ ውስጥ ከቶ እያልመጠመጠ ነው። “ለምንድነው ከንፈሬን እንዲህ አድርጎ
የሚበላኝ?” አፏን ደም ደም አላት።
ከደረቱ ቀና ብሎ የለተቱና ከማስያዢያቸው ያመለጡ
ጡቶቿን ሊይዝ እጁን ሲስድ የጡት ማስያዢያ ስፖንጆች ውስጥ እጁ እያዋለለ የከሰሉ ደቃቃ ከንፈሮቹን አሞጥሙጦ ሊስማቸው ገሰገሰ፡፡
እጁን ከጡቷ ላይ መንጭቃ አወጣችው። መልሶ አስገባ፡፡ ይሄኔ እኮ ያጎጠጎጠ መስሎት ይሆናል፡፡ እንደ ለተተ ማን
በነገረው፡፡ ኮስተር ብላ እንደቀድሞ አፈጠጠች፡፡
“ቺግር አለ?” አለና በሚያሳዝንና በሚያባብል ዐይኑ አያት፡፡
“ችግር የለም!” አለች፡፡ እያቃተተች፡፡
“ኦ! ቢ ኦ! ቢ አይ ላቭ ዩ ሶ ማች፡፡” አለና ከላይዋ ላይ ተስፈንጥሮ ተነሳቶ አጠገቡ የተቀመጠች አነስተኛ እቃ ማስቀመጫ
ስር አጎነበሰ፡፡ ሰውነቱን ድጋሚ ተመለከተችው፡፡ ትንሽ፣ ደቃቃ
እራቁቱን ቁጢጥ ብሎ ብይ የሚጫወት መሰላት፡፡ እጆቹን ወደ ውስጥ ልኮ አንድ ነገር መዞ አወጣና ወደርሷ አመለከታት፡፡
የሚያመለክታትን ነገር አየችው። አውጥቶ አሳያትና አቀበላት፡፡ ተቀብላ አየችው፡፡ ኮንደም ነው፡፡
“እኔ ለዛሬ ዝግጁ አይደለሁም፡፡ በኮንደም እንጠቀም ማለትህ ጥሩ ነው” አለችው፡፡
“ቺግር አለ?” አላት፡፡
ችግር ያምጣብህ! ችግር አለ ከማለት በስተቀር የሚያቀው ንግግር የለም፡፡ አመዳም! አለች በውስጧ፡
ተነስቶ መሄድ እንደሚያዋጣት ገባትና ከመቀመጫዋ ስትነሳ በማባበል እያየ አስቀመጣትና ስልክ ደወለ፡፡
ሁለቱም በራሳቸው ሐሳብ ሲባዝኑ ከቆዩ በኋላ በር ተንኳኳ፡፡ ጆ ሽርጡን አገልድሞ ከፈተና በፈረንሳይኛ ድምጹን ከፍ
አድርጎ አንድ መልእክት አስተላለፈ።
አዲሱ ሰውዬ ወደ እርሷ እየተመለከተ፣
“ሀሳብሽ ምን እንደሆነ ማወቅ ይፈልጋል። ምክንያቱም እርሱ በጣም ይወድሻል። ልትረጂው ይገባል እኔ አብሬው የምሰራ
ጓደኛው ነኝ፡፡ ላንቺ ሲል እንግሊዘኛና አማርኛ ሊማር ዝግጅት ላይ ነው፡፡ ለብልግና ወይም ለጊዜያዊ ስሜት የሚፈልግሽ እንዳልሆነ ልትረጂ ይገባል።” አላት፡፡
ተመልሳ ተቀመጠች። ጆ አሁንም ፈገግ ለማለት ሞክሮ አስቀያሚ ጥርሶቹን አሳያት። አንዳች ነገር እንድትናገር በጥያቄ አስተያየት እያዩዋት ነው።
የመጣው ሰው ንግግሩን ቀጠለ፡፡
“በእርግጥ ምንም ባለመነጋገራችሁ ብዙ ነገሮች ላያግባቧችሁ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ለጊዜው ፍቅር ሊያግባባችሁ ይችላል፡፡ ወደፊት ግን በሚያደርገው ብርቱ ጥረት ቋንቋዉን ሊያዳብርና ልትግባቡ
ትችላላችሁ” አላት፡፡
ዛሬ እንደምትቸኩልና ለሌላ ጊዜ በረጅም ሰዓት በሰፊው እንደምታጫውተው ነገረችው። ጆ አስተርጓሚ ጓደኛውን
ቀና ብሎ አይቶ አመስግኖ ሸኘውና አጠገቧ ቁጭ ብሎ ጀርባዋን
እየደባበሰ በፍቅር ተመለከታት።
ቢ አሁን ከቅድሙ ፍርሃቷ እየለቀቃት ሲሄድ ተሰማት፡፡ ፈገግታውን አሳያትና ሽርጡን ከላዩ ላይ ወደ መሬት ጣለው::
ቅድም ካየችው የተለየ ነገር የለም፡፡
ጭንቀቷን ለመርሳት ስትሞክር የፍትወት ፍላጎት በመላ ሰውነቷ የናኘ መሰላት። እጆቿን እሱ እንደፈለገው በገላው
ልታዟዙር ሞከረች።
ጆ አንዴ ከንፈሯን ስሞ ከፊት ለፊቷ ቁጭ አለ፡፡ ልትዳራ ፈልጋ የውጭው ጨለማ እየጠነከረ ሲመጣ ቤቷን አሰበች። ይህኔ
ባሏ ከንፈሩን ጥሎና አገጩን አስረዝሞ ይጠብቃታል፡፡ ልጆቿ በተቀመጡበት ያንጎላጃሉ። በፍጥነት ተነሳች፡፡ ጆ ዘሎ እጁን ሲይዛት የሚያስገድዳት መሰላት፡፡ አንስታ በመስኮት ልትወረውረው እንደምትችል፣ ጠንካራ እንደሆነች፣ እንኳን ይህን ኮስማና ቀርቶ በትግል
እንደማያሸንፋት ታውቃለች።
ጆ ከተዝረከረኩ እቃዎቹ መኸከል ሱሪውን ስቦ ከኪሱ በርከት ያሉ አረንጓዴ ብሮች አውጥቶ ሰጣት። ቢ በፈገግታ ያለ
አንዳች መግደርደር ተቀበለችውና ከእጁ አፈትልካ ወደበሩ አመራች፡፡
ቺግር አለ?” አላት።
ችግር ያጣድፍህ!' አለች በውስጧ፡፡ ወደ ውጭ ወጥታ በሩን በላዩ ላይ ዘጋችው:: የሰጣትን ብር ጨምድዳ ቦርሳዋ ውስጥ
ከተተች፡፡
“ደግሜ እመጣ ይሆን ጌታ ሆይ? እኔ ለመምጣት እፈልጋለሁ። አንተ ግን ኃጢአት እንዳልሰራ እርዳኝ፡፡
ዞራ ተመለከተች፡፡ ከፊል እርቃኑን ከክፍሉ ውስጥ አውጥቶ ይመለከታታል። ቅን የሚያስመስሉትን ዐይኖቹን አይታ እጇን
አርገበገበችለት፡፡ ሙሉ በሙሉ ወጥቶ ተመለከታት።
ፈገግታ ከፊቱ አልጠፋም፡፡ “ምስኪን!” አለችና አካባቢዋን ሳትቃኝ እንዳቀረቀረች አጎንብሳ ወጣች፡፡
አምላኬ ሌብነት እንዴት ያሳቅቃል? ምንድን ነው የማደርገው? ኦ ጌታ ሆይ! አንተ ምን እንደማደርግ ታውቃለህ? ምን
እንደሆንኩም ጭምር፡፡ አሁን ኃጢአት እያደረግሁ ነው ማለት ነው? ግን ማንን ነው የምጎዳው? ማንንስ ነው የምጠቅመው? ይሄ በእጄ
ጨምቄ የያዝኩት ብር የኃጢአት ገንዘብ ነው?”
ቀስ በቀስ ወደ ራሷ ተመለሰች። “አይሆንም እኔ ጨዋ ነኝ፡፡ አሁን ያደረግሁትን ሁሉ አላደረግሁም፡፡ በፍጹም! ይሄም ገንዘብ የኔ አይደለም! ጆም ቢሆን ከንፈሬን አልሳመም! ጆንን አላውቀውም፡፡ የማንንም እርቃነ ስጋ ተመልክቼ አላውቅም፤ ከባሌ በስተቀር፡፡”
ከደቂቃዎች በፊት የሰራችውን እውነት ሽምጥጥ አድርጋ ክዳ፣ በሩጫ ወደ ጆ ክፍል ደርሳ በሩን ስትገፋው ተከፈተ፡፡
ጆ አልጋው ላይ ተኝቶ ያቃስታል። ይህን የሚያቃስት ሰው አታውቀውም። ከሔደች በኋላም እንደሚያስቃስተው
አልገባትም፡፡ ግን የእርሱ ገንዘብ በእጇ አለ። ብሮቹን አልጋው ላይ በተነቻቸው፡፡
ጆ በድንጋጤ ከተንጋለለበት ተነስቶ ብሮቹን አያቸው ሐሳቧን እንደቀየረች ገባው፡፡ የተበተነውን ብር ከላዩ ላይ አራግፎ ወደ በሩ እሮጠ፡ የለችም፡፡
ተመልሶ በመስኮቱ በኩል ወደ ውጭ ሲመለከት
፡
፡
#ክፍል_ሁለት(የመጨረሻ ክፍል)
፡
፡
#በእየሩስአሌም_ነጋ
ጆ በሐሳብ እርቃ የሄደችውን ቢ በዐይኗ የሞላውን እንባ አይቶ በርከክ አለና አገጯን ይዞ እየተመለከታት፡፡ “ቺግር አለ?” አለ።
“ችግር አለ” የሚለውን ቋንቋ ብቻ እንዴት እንደለመደው ደንቋታል። “ምናለ አማርኛ ቢስማና የልቤን በነገርኩት፡፡ ይሄኔ
አውቄ የምባልግ፣ በኃጢአት የወደኩ፣ አዳፋ አድርጎ ያየኝ ይሆናል፡፡
ምክንያቱም ባልና ልጆች እንዳሉኝ ነግሬዋለሁ። እሱንም ባስተርጓሚ።
ምን እንደምትፈልግ ግራ የገባው ይመስላል። ገፋ አድርጎ ወደ አልጋው አንጋለላት፤ እንደተኛች መላ አካሉን አየችው፡፡
ሀፍረተ ስጋው ከመላው አካሉ የሚበልጥ መሰላት። ደግሞ ከወደ ጫፉ ለምጽ የያዘዘው ይመስል ነጽቷል። ቀፈፋት፡፡ ዳበሳት፡፡ ዝም አለችው፡፡ እጇን ይዞ አካሉን እንድትዳብስለት በእጁ አስነካት።
እሷ ግን በተቃውሞ ወደ ነበረበት ቦት መለሰችው፡፡
ቀስ እያለ እላይዋ ላይ የተጋደመው ጆ አንዳች ኃይል የተመላ ይመስል ከብዶ ነፍስና ስጋዋን የሚለያይባት መሰላት፡፡
ያንን ሩህሩህና ኩሩ ባሏን በዐይነ ህሊናዋ አየችው። ሰፊና ግዙፍ ትከሻ ቢኖረውም ይህን ያክል አይከብዳትም፡ታከብረዋለች፣
ትወደዋለች ከሱ ሌላ ምንም አትፈልግም ነበር፡፡ እሱ ግን አንደ አንድ ግኡዝ ነገር መገልገያ አድርጓታል። እሱ ለብዙ ሰዎች ጉርስና ልብስ ነው፡፡ እሷ ግን በእርዛትና በጥማት ብትንገላታ ግድ የለውም፡፡
እኔ ገንዘብ ከሰው መጠበቅ የለብኝም፡፡ ምክንያቱም የመስራት አቅምና ችሎታ አለኝ፡፡ ስራ መስራት አለብኝ፡፡ ግፋ ቢል
ባሌን ላጣው እችላለሁ፡፡ ለገንዘብና ለፍቅር አሳልፌ ጨዋነቴን ልለውጠው አልፈልግም።ከነፍስና ስጋዋ ጋር ተሟገተች። ወዲያው ደግሞ ግን ደግሞ አይዞሽ እያለ የጎደለኝን እየፈለገ ሲከፋኝ እያባበለ ስሜቴን የሚያዳምጥ ወንድ እፈልጋለሁ፡፡ እኔ ለባሌ የማደርገውን
እሱም ለኔ ሊያደርግ ግድ ነው፡፡ አለበለዚያ ግን... አለች በትግሉ
መካከል እየተወራጨች።
ጆ ከንፈሯን የማላመጥ ያህል በአፉ ውስጥ ከቶ እያልመጠመጠ ነው። “ለምንድነው ከንፈሬን እንዲህ አድርጎ
የሚበላኝ?” አፏን ደም ደም አላት።
ከደረቱ ቀና ብሎ የለተቱና ከማስያዢያቸው ያመለጡ
ጡቶቿን ሊይዝ እጁን ሲስድ የጡት ማስያዢያ ስፖንጆች ውስጥ እጁ እያዋለለ የከሰሉ ደቃቃ ከንፈሮቹን አሞጥሙጦ ሊስማቸው ገሰገሰ፡፡
እጁን ከጡቷ ላይ መንጭቃ አወጣችው። መልሶ አስገባ፡፡ ይሄኔ እኮ ያጎጠጎጠ መስሎት ይሆናል፡፡ እንደ ለተተ ማን
በነገረው፡፡ ኮስተር ብላ እንደቀድሞ አፈጠጠች፡፡
“ቺግር አለ?” አለና በሚያሳዝንና በሚያባብል ዐይኑ አያት፡፡
“ችግር የለም!” አለች፡፡ እያቃተተች፡፡
“ኦ! ቢ ኦ! ቢ አይ ላቭ ዩ ሶ ማች፡፡” አለና ከላይዋ ላይ ተስፈንጥሮ ተነሳቶ አጠገቡ የተቀመጠች አነስተኛ እቃ ማስቀመጫ
ስር አጎነበሰ፡፡ ሰውነቱን ድጋሚ ተመለከተችው፡፡ ትንሽ፣ ደቃቃ
እራቁቱን ቁጢጥ ብሎ ብይ የሚጫወት መሰላት፡፡ እጆቹን ወደ ውስጥ ልኮ አንድ ነገር መዞ አወጣና ወደርሷ አመለከታት፡፡
የሚያመለክታትን ነገር አየችው። አውጥቶ አሳያትና አቀበላት፡፡ ተቀብላ አየችው፡፡ ኮንደም ነው፡፡
“እኔ ለዛሬ ዝግጁ አይደለሁም፡፡ በኮንደም እንጠቀም ማለትህ ጥሩ ነው” አለችው፡፡
“ቺግር አለ?” አላት፡፡
ችግር ያምጣብህ! ችግር አለ ከማለት በስተቀር የሚያቀው ንግግር የለም፡፡ አመዳም! አለች በውስጧ፡
ተነስቶ መሄድ እንደሚያዋጣት ገባትና ከመቀመጫዋ ስትነሳ በማባበል እያየ አስቀመጣትና ስልክ ደወለ፡፡
ሁለቱም በራሳቸው ሐሳብ ሲባዝኑ ከቆዩ በኋላ በር ተንኳኳ፡፡ ጆ ሽርጡን አገልድሞ ከፈተና በፈረንሳይኛ ድምጹን ከፍ
አድርጎ አንድ መልእክት አስተላለፈ።
አዲሱ ሰውዬ ወደ እርሷ እየተመለከተ፣
“ሀሳብሽ ምን እንደሆነ ማወቅ ይፈልጋል። ምክንያቱም እርሱ በጣም ይወድሻል። ልትረጂው ይገባል እኔ አብሬው የምሰራ
ጓደኛው ነኝ፡፡ ላንቺ ሲል እንግሊዘኛና አማርኛ ሊማር ዝግጅት ላይ ነው፡፡ ለብልግና ወይም ለጊዜያዊ ስሜት የሚፈልግሽ እንዳልሆነ ልትረጂ ይገባል።” አላት፡፡
ተመልሳ ተቀመጠች። ጆ አሁንም ፈገግ ለማለት ሞክሮ አስቀያሚ ጥርሶቹን አሳያት። አንዳች ነገር እንድትናገር በጥያቄ አስተያየት እያዩዋት ነው።
የመጣው ሰው ንግግሩን ቀጠለ፡፡
“በእርግጥ ምንም ባለመነጋገራችሁ ብዙ ነገሮች ላያግባቧችሁ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ለጊዜው ፍቅር ሊያግባባችሁ ይችላል፡፡ ወደፊት ግን በሚያደርገው ብርቱ ጥረት ቋንቋዉን ሊያዳብርና ልትግባቡ
ትችላላችሁ” አላት፡፡
ዛሬ እንደምትቸኩልና ለሌላ ጊዜ በረጅም ሰዓት በሰፊው እንደምታጫውተው ነገረችው። ጆ አስተርጓሚ ጓደኛውን
ቀና ብሎ አይቶ አመስግኖ ሸኘውና አጠገቧ ቁጭ ብሎ ጀርባዋን
እየደባበሰ በፍቅር ተመለከታት።
ቢ አሁን ከቅድሙ ፍርሃቷ እየለቀቃት ሲሄድ ተሰማት፡፡ ፈገግታውን አሳያትና ሽርጡን ከላዩ ላይ ወደ መሬት ጣለው::
ቅድም ካየችው የተለየ ነገር የለም፡፡
ጭንቀቷን ለመርሳት ስትሞክር የፍትወት ፍላጎት በመላ ሰውነቷ የናኘ መሰላት። እጆቿን እሱ እንደፈለገው በገላው
ልታዟዙር ሞከረች።
ጆ አንዴ ከንፈሯን ስሞ ከፊት ለፊቷ ቁጭ አለ፡፡ ልትዳራ ፈልጋ የውጭው ጨለማ እየጠነከረ ሲመጣ ቤቷን አሰበች። ይህኔ
ባሏ ከንፈሩን ጥሎና አገጩን አስረዝሞ ይጠብቃታል፡፡ ልጆቿ በተቀመጡበት ያንጎላጃሉ። በፍጥነት ተነሳች፡፡ ጆ ዘሎ እጁን ሲይዛት የሚያስገድዳት መሰላት፡፡ አንስታ በመስኮት ልትወረውረው እንደምትችል፣ ጠንካራ እንደሆነች፣ እንኳን ይህን ኮስማና ቀርቶ በትግል
እንደማያሸንፋት ታውቃለች።
ጆ ከተዝረከረኩ እቃዎቹ መኸከል ሱሪውን ስቦ ከኪሱ በርከት ያሉ አረንጓዴ ብሮች አውጥቶ ሰጣት። ቢ በፈገግታ ያለ
አንዳች መግደርደር ተቀበለችውና ከእጁ አፈትልካ ወደበሩ አመራች፡፡
ቺግር አለ?” አላት።
ችግር ያጣድፍህ!' አለች በውስጧ፡፡ ወደ ውጭ ወጥታ በሩን በላዩ ላይ ዘጋችው:: የሰጣትን ብር ጨምድዳ ቦርሳዋ ውስጥ
ከተተች፡፡
“ደግሜ እመጣ ይሆን ጌታ ሆይ? እኔ ለመምጣት እፈልጋለሁ። አንተ ግን ኃጢአት እንዳልሰራ እርዳኝ፡፡
ዞራ ተመለከተች፡፡ ከፊል እርቃኑን ከክፍሉ ውስጥ አውጥቶ ይመለከታታል። ቅን የሚያስመስሉትን ዐይኖቹን አይታ እጇን
አርገበገበችለት፡፡ ሙሉ በሙሉ ወጥቶ ተመለከታት።
ፈገግታ ከፊቱ አልጠፋም፡፡ “ምስኪን!” አለችና አካባቢዋን ሳትቃኝ እንዳቀረቀረች አጎንብሳ ወጣች፡፡
አምላኬ ሌብነት እንዴት ያሳቅቃል? ምንድን ነው የማደርገው? ኦ ጌታ ሆይ! አንተ ምን እንደማደርግ ታውቃለህ? ምን
እንደሆንኩም ጭምር፡፡ አሁን ኃጢአት እያደረግሁ ነው ማለት ነው? ግን ማንን ነው የምጎዳው? ማንንስ ነው የምጠቅመው? ይሄ በእጄ
ጨምቄ የያዝኩት ብር የኃጢአት ገንዘብ ነው?”
ቀስ በቀስ ወደ ራሷ ተመለሰች። “አይሆንም እኔ ጨዋ ነኝ፡፡ አሁን ያደረግሁትን ሁሉ አላደረግሁም፡፡ በፍጹም! ይሄም ገንዘብ የኔ አይደለም! ጆም ቢሆን ከንፈሬን አልሳመም! ጆንን አላውቀውም፡፡ የማንንም እርቃነ ስጋ ተመልክቼ አላውቅም፤ ከባሌ በስተቀር፡፡”
ከደቂቃዎች በፊት የሰራችውን እውነት ሽምጥጥ አድርጋ ክዳ፣ በሩጫ ወደ ጆ ክፍል ደርሳ በሩን ስትገፋው ተከፈተ፡፡
ጆ አልጋው ላይ ተኝቶ ያቃስታል። ይህን የሚያቃስት ሰው አታውቀውም። ከሔደች በኋላም እንደሚያስቃስተው
አልገባትም፡፡ ግን የእርሱ ገንዘብ በእጇ አለ። ብሮቹን አልጋው ላይ በተነቻቸው፡፡
ጆ በድንጋጤ ከተንጋለለበት ተነስቶ ብሮቹን አያቸው ሐሳቧን እንደቀየረች ገባው፡፡ የተበተነውን ብር ከላዩ ላይ አራግፎ ወደ በሩ እሮጠ፡ የለችም፡፡
ተመልሶ በመስኮቱ በኩል ወደ ውጭ ሲመለከት
👍4❤1🔥1