አትሮኖስ
279K subscribers
110 photos
3 videos
41 files
461 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የታካሚው_ማስታወሻ


#ክፍል_ሀያ_አምስት


#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)

#የመጨረሻው_መጨረሻ

ድንገት ስነቃ እራሴን አልጋ ላይ በጀርባዬ ተዘርሬ አገኘሁት፡፡ከፍተኛ ህመም ይሰማኛል፡፡ እራሴ አካባቢ፣ በቀኝ በኩል ሰውነቴን፣ፊቴን ይጠዘጥዘኛል፡፡ ዐይኖቼን ለመክፈት ሞከርኩ፡፡ የቀኝ ዐይኔን
ህመም ተሰማኝ፡፡ አልከፈት አለኝ፡፡ ዐይኔ ምን እንደሆነ ለመዳበስ፣ የቀኝ እጄን ለማንሳት ስሞክር፣ እ...ህ... ከፍተኛ ህመም፡፡ ማንቀሳቀስም፣ ማንሳትም አልቻልኩም፡፡ እጄስ ምን ሆኖ ነው...? ወደ እጄ ዞር ስል፣አንገቴ ከሆነ ነገር ጋር ታስሯል፡፡ ምን ሆኜ ነው..? የት ነው ያለሁት..? ማን ነው እዚህ ያመጣኝ...? በግራ እጄ ላይ የግልኮስ ገመድ
ተንጠልጥሎ አየሁ፡፡ ሆስፒታል ነው ያለሁት። የት ሆስፒታል ነው ያለሁት?፣ ምን ሆኜ ነው...? ለማስታወስ ሞከርኩ፡፡ ብዙ ጥያቄዎች በፍጥነት በጭንቅላቴ ተመላለሱብኝ፡፡ በበር በኩል፣ በርቀት አንድ ነጭ ገዋን የለበሰ ሰው ሲገባ አየሁ፡፡ እንዲስማኝ፣ አ...ብዬ አቃሰትኩ፡፡
እንደገመትኩት ድምፄን ሰምቶ ነው መሰል፣ በቀጥታ ወደ እኔ መጣ፡፡

“ኦ...ነቃህ?፣ በጣም ደስ ይላል፡፡ እንዴት ነህ?፣ ምን ይሰማሃል?” አለኝ፡፡

“ደህና ነኝ፡፡ ትንሽ እራሴ አካባቢ...” በደከመ ድምፅ፡፡

“ቆይ መጣሁ፡፡” ብሎኝ ሄደና፣ ብዙም ሳይቆይ የታካሚ ካርድ ይዞ ተመለሰ፡፡

የግራ እጄን ይዞ የልብ ምቴን ቆጠረ፡፡ በደም መለኪያ የደም ግፊቴን ለካ፡፡ ዐይኖቼን ከፍቶ አያቸው፡፡ ደረቴን በማዳመጫ አዳመጠ፡፡እግሮቼን አንቀሳቅስ እያለኝ፣ እግሮቼን በሹል ነገር እየወጋኝ፣ በሙሉ ስውነቴን መረመረኝ፡፡

“የት እንዳለህ አውቀሃል?” ጠየቀኝ፡፡

“ሆሰፒታል ነኝ መሰለኝ..."

“በጣም ጥሩ። እኔን ታውቀኛለህ?”

“አላውቅህም፡፡ ግን ዶክተር ትመስለኛለህ፡፡”

“እሺ፤ አሁን ስንት ሰዐት ይመስልሃል?”

“ሰዓቱን አላውቅም፡፡”

“በግምት፣ ጥዋት ከሰዓት ወይስ ምሽት ይመስልሃል?”

“መገመት ይከብደኛል።” አጠገቤ ያለ ወንበር ላይ ተቀመጠና መፃፍ ጀመረ፡፡ ለደቂቃዎች ከፃፈ በኋላ፣ “አይዞህ፡፡ ትንሽ አደጋ ደርሶብህ ነው፡፡ አሁን ደህና ነህ፤
ተርፈሃል፡፡ እራስህና እጅህ አካባቢ ትንሽ ጉዳት ደርሶብሃል፡፡ ግን እድለኛ ነህ... ተረፈሃል ለህመምህ ማስታገሻ እንሰጥሃለን አይዞህ ብሎኝ ማስታገሻ መርፌ እንድወጋ አደረገ፡፡ ከብዙ ህመም ቦሃላ መልሶ እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡

ጥዋት ከእንቅልፌ ስነሳ፣ እረጅም እንቅልፍ እንደተኛው ተሰማኝ፡፡ ቀጣዮቹም ቀናት እጅግ በጣም ከባድ ነበሩ። ያለፈውን፣ የተፈጠረውን፣ መቀበልም መቋቋም አልቻልኩም፡፡ እራሴን በቁሜ
ቦርቡሬ፣ ገዝግዤ ጨርሼዋለሁ፡፡ ዳግመኛ እንዳልነሳ እንዳላንሰራራ
አድርጌ ቀብሬዋለሁ፡፡ አሁን ለኔ መኖር ከቀደመው የባሰ ሲኦል ነው፡፡ አሁን መሞት በጣም ያስፈልገኛል፡፡ ተሰምቶኝ ማያውቅ ጭንቀት እየተሰማኝ መጥቷል፡፡ . ትንሽ ድምፅ ይረብሸኛል። እንቅልፍ አይወስደኝም፡፡ ነገርግን፣ እንኳን እራሴን ላጠፋ፣ እራሴን ማንቀሳቀስ
ማልችል እንደሆንኩ ሳስብ እንባዬን መቆጣጠር አቃተኝ፡፡ ጭንቅላቴ
ሊፈነዳ ይደርሳል፡፡ በእንዲህ ባለ ሁኔታ ቀናቶች አለፉ፡፡ ዶክተሮች መጥተው ይከታተሉኛል፤ መድሀኒት ያዙልኛል። ጥዋት ጥዋት፣ የፊቴ ቁስል ይጠረግልኛል፡፡

አንድ ቀን እንደተለመደው ዶክተሮች ከጎበኙኝ ቦሃላ ሌላ እስፔሻሊስት ዶክተር መጥቶ እንደሚያየኝ ነግረውኝ ሄዱ፡፡ ትንሽ ቆይቶ ሚከታተለኝ ወጣት ዶክተር እንደርሱ ነጭ ገዋን ከለበሰ ወጣት ጋር
ተመልሶ መጣ፡፡ አዲሱ ዶክተር ካርዴን ተቀብሎ አገላብጦ አነበበው፡፡

“ማን ነው እዚህ ያመጣው?” አዲሱ ዶክተር ጠየቀ፡፡

“አምስት ቀን ሆነው፡፡ ገዳም አካባቢ የሚኖሩ ሰዎች ናቸው አምጥተውት የሄዱት።”

ዝም አልኩኝ፡፡ በራሴ አፈርኩ፤ ዐይኔን ጨፈንኩ፡፡ አዲሱ ዶክተር፣ እኔን ሳያናግረኝ በእጁ ግራ እጄን እያሻሸ፣ ከስራ ባልደረባው ጋር ያወራል፡፡ በእጁ እንቅስቃሴ፣ ልስላሴና ሙቀት፣ በውስጡ እያዘነልኝ እንደሆነ ተሰማኝ፡፡

“ዶ/ር ሄኖክ እባላለሁ፡፡ ሄኖክ ብለህ ልትጠራኝ ትችላለህ፡፡ የስነ-አዕምሮ ህክምና ክፍል፣ የመጨረሻ አመት የድህረ ምረቃ ሃኪም ነኝ፡፡አንተስ ስምህን ትነግረኛለህ?” ፊቱ፣ ድምፁ፣ ሁሉ ነገሩ ላይ ሃዘኔታና ርህራሄ የሚነበብ መሰለኝ፡፡

“ያቤዝ እባላለሁ፡፡”

“ያቤዝ ማን?”

“ያቤዝ አለማየሁ፡፡”

“እድሜ ?”

“ሠላሳ አራት፡፡”

“እራስህን ልታጠፋ ሞክረህ እንደነበር፣ ምታስታውሰው ነገር አለ?”

ዝም አልኩ፡፡ ጭንቅላቴ ይወቅረኝ ጀመር፡፡

“ደህና ነህ ያቤዝ?”

“ደህና ነኝ ዶክተር።”

“እሺ ያቤዝ፣ ለህክምናህ ስለሚረዳኝ የሆነውን ነገር ልትነግረኝ ትችላለህ?፡፡ ልትነግረኝ ምትፈልገውን፣ ግን ትክክለኛውን ብቻ ንገረኝ፡፡ እያንዳንዱ የምትነግረኝ መረጃ ካንተ ፍቃድ ውጪ፣ ለማንኛም ሶስተኛ ወገን በፍፁም አይደርስም፡፡ ለቤተሰብህም ቢሆን እንኳን፡፡ መናገር የማትፈልጋቸው ነገሮች ካሉ እለፋቸው፣ እንዳትዋሸኝ፡፡››
“እሺ!” አልኩት በደከመ ድምፅ፡፡ ውስጤ በጣም እየተረበሸ ነው፡፡ምን ብዬ ነው የምነግረው? ከየት ነው የምጀምረው? የተፈጠረውን ወደ ኋላ ሳስበው፣ እንባ እየተናነቀኝ መጣ፡፡

“ያቤዝ እየጠበኩህ ነው፡፡ የሆነውን፣ የተፈጠረውን ንገረኝ፡፡እራስህን ልታጠፋ ለምን ሞከርክ?”

ማልቀስ ጀመርኩኝ፡፡ ዶክተር ሊያባብለኝ ሞከረ፡፡ ውስጤ ጭራሽ ገነፈለ፡፡ “እኔ ከሞትኩ ቆይቻለሁ፡፡ በቁሜ የአርባና ሰማንያ ተዝካሬን አውጥቻለሁ፡፡ ሀብትና ንብረቴን ነፍስ ይማር ብዬ በትኜዋለሁ፡፡ለወራት ስንከራተት የከረምኩት፣ አስክሬኔን የምቀብርበት ምቹ ቦታ ፍለጋ ነበር እንጂ፣ ላለመሞት አልነበረም፡፡ እንዴት ተረፍኩኝ...? ለምን..? እኔ
መኖር አልፈልግም...!” እየጮኸኩ ተንሰቀሰኩ፡፡ ቢያባብሉኝም፣ ማቆም
አልቻልኩም፡፡ እንባዬ የፊቴን ቁስል እየለበለበኝ ይወርዳል፡፡ ዶክተሮቹ
ከወንበራቸው ሲነሱ፣ ኮቴ ሲበዛ፣ ግርግር ሲፈጠር፣ እጄ ላይ በተቀጠለው ግሉኮስ፣ መድሃኒት ሲስጠኝ ይሰማኛል፡፡ የማለቅስበት ሃይል እየከዳኝ፣ ሳላስበው እንቅልፍ ወሰደኝ፡፡

ከዛች ቀን ጀምሮ የዶክተር ሄኖክ ክትትል በጣም የተለየ ነበረ፡፡እንደቤተሰብ ብዙ ሰዓታት ከኔ ጋር ያሳልፋል። ጥሩ ተቀራርበናል፤የሚሰማኝን የህመም ስሜት እነግረዋለሁ፡፡ መድሃኒት ያዝልኛል፡፡
ያዘዘልኝ መድሃኒቶች፣ ጥሩ እንቅልፍ እንድተኛ እያገዙኝ ነው፡፡እኔ ሳልፈልጋቸው ወደ ጭንቅላቴ እንደፈለጉ ሚፈነጩብኝ፣ እነዛ ተላምጠው ማያልቁ አስጨናቂና ተስፋቢስ ሃሳቦች እንደ ሀምሌ ዝናብ
እኝኝ ማለታቸውን አየቀነሱልኝ ነው፡፡ ዶ/ር ሄኖክ በተለየ አቅርቦት ይንከባከበኛል፡፡ እንደታካሚው ሳይሆን፣ እንደታላቅ ወንድም፣ እንደቤተሰብ፣ በሁሉም ነገር እያገዘኝ ነው፡፡ ከሁሉም ታካሚዎች ቀድሞ እኔን ይጎበኘኛል የሚያስታምመኝ ቤተሰብ ስለሌለ ይሁን አዛኝ ተፈጥሮ
ኖሮት ባላውቅም፣ ካወቀኝ ጀምሮ ከኔ አልተለየም፡፡ የህክምና ወጪዬንም
እየሸፈነ እንደሆነ አውቂያለሁ፡፡ አልፎ አልፎ ምግብ ከውጪ ያስመጣልኛል፤ አብዛኛውን ግዜ ስራውን ሲጨርስ፣ በተለየ ርህራሄና ፍቅር ያጫውተኛል፤ ያበረታታኛል፡፡ ተስፋንና ጥንካሬን በውስጤ ይረጨል፡፡ ቀናቶች ሲያልፉ፣ እየተሻለኝ መጥቷል፡፡ የፊቴና የእጄ
ቁስሎች ለውጥ አላቸው፡፡ ህመሞቼ እየቀነሱ፣ ለውጥ እያመጣሁ፣ የሞተው፣ የተቀበረው ተስፋዬ ዳግም ያቆጠቁጥ ጀመር፡፡

እጄን ሁለት ጊዜ ራጅ ተነሳሁ፡፡የተሰበረው አጥንቴ ጥሩ ሆኖ ጠግኗል፡፡ የታሰረልኝ ጄሶ ሊፈታልኝ ቀጠሮ ተሰጠኝ፡፡ የፊቴ ቁስል ህመሙ ጠፍቷል፡፡ በእጆቼ ዳበስኩት፤ ይሻክራል፡፡ ፊቴ ላይ ትልቅ
የማይሽር
👍4
#የተወጋ_ልብ


#ክፍል_ሃምሳ_ስምንት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

..ባሌ... በሬሳ!
( ከአራት ዓመታት በፊት)

ከቀኑ አስር ሰዓት ተኩል አናቱ ላይ! በፀጥታዋ የምትታወቀው በሬሳ
በኡኡታ ተደበላለቀች። ሰማዩ በነጎድጓድ ድምፅ ታረሰ... በሬሳ ወልዳ አሳድጋ ለከፍተኛ ቁም ነገር ያበቃችው ተወዳጅና ብርቅዬ ልጇን እንደ ክፉ ድመት መልሳ ወደ ማህፀንዋ ልታስገባ አፏን በሰፊው ከፍታ አዛጋች፡፡ መልአከ ሞት አስገምጋሚውን የነጕድጓድ ድምፅ አሰምቶ በመቅስፍት በትሩ የአስካለን ልብ ያለርህራሄ በረቃቀሰው... ልጅዋ ናፍቋት፣
በህልሟ እየተመላለስ ሲያቃዣት ከረመና፣ ናፍቆቱ ዐይኗን ሊያወጣው ደረሰና ዳቦ ቆሎ ቆርጣ አዘጋጅታ ወደ አዲስ አበባ ሄዳ ልጇን እቅፍ
አድርጋ ለመሳም ቸኩላ ዝግጅቷን በማፋጠን ላይ ነበረች። ያ እንደነ
ፍሷ የምትወደው የምትሳሳለት ልጇ ግን መንገዱን ሊያስቀርላት፣ አዲስ አበባ ድረስ ሄዳ እንዳትንከራተት ድካሙን ሊቀንስላት በእንጨት ሳጥን
ተሞሽሮ ወደሷ እየገሰገሰላት ነበር።

ዘይኑን፣ አማረችንና ባልንጀሮቹን የጫነው አውቶቡስ ከቀኑ አስር
ሰዓት ተኩል ላይ በሬሳ ሲደርስ መንደሪቱ በጩኸት ታመሰች። እማዬ! እማምዬ! ጉድ ሆን! ወንድም ጋሼ...ወንድም ጋሼ! ጌትዬ!ጌትሽ!…. የኔ ፍቅር! እናቱ አስካለ አስቀድሞ ምንም ፍንጭ እንዲደርሳት ሳይደረግ ተዘጋጂ! ተጠንቀቂ! ሳትባል ሳይነገራት መአት ወረደባት። ምፅአተ
ቁጣውን ያረገዘው የሰቆቃ ጭጋግ ጥቁር ደመናውን በደሳሳ ጎጆዋ ላይ በድንገት አጥልቶ እንደ ንስር አሞራ ሲያንዣብብ ቆየና በከፍተኛ ጭካኔ መአተ እርግማኑን እንደ በረዶ ያዘንብባት ጀመር።
የመኩሪያ አደራ! ስትል የኖረች እናት ከሷ በፊት ትንሹ ልጇ እሷን ቀድሞ አባቱን ጠያቂ ይሆናል ብላ ለደቂቃ እንኳ አስባ አታውቅም ነበር። እንኳን ሞቱ ረጅም
እንቅልፉ የሚያስጨንቃት ልጅ ጉንፋን ስለመታመሙ ወሬ ሳትሰማ አስከሬኑን እንድትሸከም ሲፈረድባት ምን ይባላል? ያልፍልኛል ብሉ ደፋ ቀና ሲል ከርሞ በማእረግ የተመረቀላት ልጇን ደስታ አጣጥማ ሳትጨርስ ከጎኗ በድንገት ስታጣው የሚስማትን ስሜት ምን ቃላት ሊገልጡት ይችላሉ? ምናልባት በአስካለ ላይ የደረሰባትን ሰቆቃ ምሳ ቋጥሮ እቅፎ ስሞ ትምህርት ቤት የሸኘውን ህፃን ልጁን በመኪና አደጋ የተነጠቀ ወላጅ፣ ለወሊድ ሆስፒታል ይዟት የገባ ጤነኛ ሚስቱን አስከሬን በድንገት የታቀፈ አባወራ፣ በሠርጓ ዋዜማ እጮኛዋ በተኛበት አልጋ ላይ እስትንፋሱ ተቋርጣ ያገኘች ሙሽራ የበለጠ ሊረዷት ይችሉ ይሆናል። በዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል የተደረገለት ጥረት ሳይሳካ በመቅረቱ በሶስተኛ ቀኑ በዚያው በሆስፒታሉ ውስጥ እንዳለ ህይወቱ ያለፈው ልጇ አስከሬኑ
ተጭኖ መምጣቱና ከሷ ቀድሞ ከአባቱ መቃብር አጠገብ የቀብር ስርአቱ በህዝብ ፊት በአደባባይ ተፈፅሞ አፈር መልበሱ በገሃድ እየታየ ለደቂቃ እንኳ ሞቱን አምና መቀበል ተስኗት በድን ሆና ቀረች፡፡
በቀብሩ ዕለት የአማረችን አሳዛኝ የለቅሶ ዜማ፣ የእናቱን ሁኔታ፣ የእህቱን እሪታ ሰምቶ አንጀቱ ያልተርገፈገፈ፣በእንባ ያልተራጨ፣ በእዬዬ ጉሮሮው ያልተዘጋ አልነበረም፡፡ ለዚያ ምግባረ ሰናይ ልጅ፣ ላዚያ አመለ ሽጋ ልጅ፣ለዚያ ትህትናው ለተመሰከረለት ልጅ፣ ለዚያ ገና በለጋነቱ የአባቱን አደራ ሊወጣ የቤተሰብ ሃላፊነት ቀንበርን በጫንቃው ተሸክሞ
ሲጎትት ለኖረ ልጅ የማያለቅስ ማን አለ? ከእያንዳንዱ ሰው እንባ እንደ
ውሃ ተቀዳለት፡፡ የሰማይ አእዋፍ ጭምር ተንጫጩለት። አጅሬ ሞት አይረታ የበላውን አይመልስ ሆነ እንጂ....
በዚያን እለት በማህፀኗ የተሸከመችው የአራት ወር ፅንስ ትንሹ ጌትነት ከሆዷ ውስጥ ሆኖ እየረገጣት አማረች የሚከተለውን የሃዘን እንጉርጉሮዋን አሰማች...

ስንዴ ዘርቻለሁ ቡቃያው ያማረ፣
ዛላው ተንዠርጎ ተስፋን ያሳደረ።
ዘሮች ተበትነው በእፍኝ አፈር ላይ፣
ጎልቶ እንዲወጣ ምርጡ እንዲለይ፣
ተመራማሪዎች ተወራረዱና፣
ውጤቱን ለማወቅ አወጡ ፈተና።
እኩል እየበሉ እኩል እየጠጡ፣
አንደኛው ከሌላው ከተበላለጡ፣
ሊመርጡ ፈጣኑን ለልማት ሊያወጡ፣
ተስማሙ ባንድ ድምፅ ሽልማት ሊሰጡ፡፡
አያጠራጥርም ቡቃያዬ አደገ፣
ቀድሞ ለመበላት ለመድረስ ፈለገ፡፡
በከባድ ልዩነት ሁሉንም በለጠ፣
ተፈላጊነቱን በኩራት ገለጠ።
ታዲያ ምን ያደርጋል ሳይታይ ውጤቱ፣
ታጭዶና ተወቅቶ ሳይመዘን ምርቱ፣
አብቦ እንዳሽተ ፍሬ እንዳጋተ፣
ስሩ ተበጠስ ሞተ ተከተተ።
ቡቃያዬ እንጭጩ ቡቃያዬ ሆዴ፣
እጦማለሁ ብዬ ነይ ነይ ከሁዳዴ፣
ተስፋ ያደረግሁት ባንተ አይደለም እንዴ?
ጌትሽ ቡቃያዬ ጌትሽ ቀለበቴ፣
አጊጬ ሳልጠግብህ አድርጌህ ከጣቴ፣
ምነው ሾልከህ ጠፋህ ሆድዬ አንጀቴ?
ቃልህን አታጥፍም ብዬ ስኮራብህ፣
ሚስጥር ጠባቂ ነህ ብዬ ስመካብህ፣
አሳፈርከኝ ዛሬ አመኔታም የለህ፡፡
አይታችሁ ያጣችሁ እናንተ ፍረዱ፣
እምነትን ዘርታችሁ ክህደትን ስታጭዱ።
አበቃ ተስፋዬ ሞተ መነመነ፣
የመኖሬ ትርጉም ባዶ ቀፎ ሆነ፡፡
አልችለውምና ጧት ማታ እዬዬ፣
ክብርና ኩራቴ ጥላ ከለላዬ፣
አልቀርም ጠብቀኝ ጌትሽ እጮኛዬ።

የእናቱ የአስካለ ሁኔታ እንዲህ ነበር ተብሎ በቀላሉ የሚገለፅ አል
ሆነም፡፡ የሚያዩ ዐይኖቿ ታወሩ...
የሚሰሙ ጆሮዎቿ ደነቆሩ... የሚናገረው አንደበቷ ተዘጋ፡፡በዚያ በደካማ ሰውነቷ ላይ የወደቀባትን ክምር የስቃይ ሸክም መቋቋም ተስኗት አቅም አጣችና ራሷን ሳተች። ቀወሰች።
ሁለት ቀን ሙሉ ነፍሷ ሳትወጣ የሞተ በድኗ እየተጠበቀ ሳለ በሶስተኛው ቀን ላይ ማንም ሰው ሳያያት በእኩለ ለሊቱ ሹልክ ብላ ሮጣ ወጣችና በባሏና በልጇ መቃብር መካከል ወዲያና ወዲህ ስትንከላወስ ከቆየች በኋላ
የምትወደው ልጇን ተከትላ ባሏ አዘጋጅቶ ወደሚጠብቃቸው አዲስ ዓለም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አብራ ተቀላቀለች። አይ የሰው ነገር?!

ከደሙ ንፁህ መሆኑን ሳያውቅለት ለዘለዓለም አንደበቱ በመዘጋቱ የሸዋዬ ባል ቶሎሳ እንኳ“ሞት ሲያንሰው ነው” ሲል ነበር የፈረደበት።

#የመጨረሻው_መጨረሻ
#ሳኦልና_ጳውሎስ

ታደሰ በእውነቱ ከሆስፒታል እንዲወጣ ተደርጐ በመኖሪያ ቤቱ
ውስጥ አልጋ ላይ ከዋለ ልክ ሳምንቱ.. ለሰው ጥሩ መስራት ለራስ ነው። ታደሰን ለመጠየቅና ለማፅናናት በየጊዜው የሚመጣው ሰው ቁጥሩ
በርካታ ነው፡፡ በጠያቂ ብዛት መዳን ቢቻል ኖሮ ታደሰ የዚህ ዕድል ተጠቃሚ መሆን በቻለ ነበር። ዛሬ ግን እያቃሰተ ህመሙን የሚያዳምጥበት ቀን አልነበረም፡፡ የምራቅ ዕጢዎቹ ማመንጨት አቁመዋል። ከንፈሮቹ ኩበት መስለው ደርቀዋል። ጥቁር መልኩ የጣፊያ ዓይነት መልክ
እየያዘ ሄደ...ወይዘሮ ወደሬ ማዕድ ቤት ውስጥ ጉድ ጉድ እያሉ ነበር።
ለጊዜው ሁለቱ ብቻ ነበሩ። ሰላማዊት የታደሰን ሁኔታ አጤነች፡፡ በየጊዜው እየሰለለች የመጣች ተስፋዋ ልትበጠስ መቃረቧን ተረዳች፡፡ ውድ ባሏ ሊለያት እንደሆነ ጠርጥራ ፍርሃት አደረባት።

“ታዴ! እየበረታህ ነው?” አልጋው ጠርዝ ላይ ቁጭ ብላ በግራ
መዳፏ ትኩሳቱን እየለካች ጠየቀችው፡፡
“እህ!.. እህ!.. እህ.! ሰላሜ..” ዐይኖቹን በዐይኖቿ ላይ አንከራተ
ታቸው።ከሆስፒታል የወጣው የመዳን ተስፋው እየመነመነ በመምጣቱ ምክንያት መሆኑን አውቆታል፡፡ሚስቱን እያፈቀረና እየወደዳት ብቸኛ አድርጓት ሊሄድ በአስገዳጁ የሞት ጠንካራ ክንድ ተጨምድዶ መያዙን ተገንዝቦታልና ሙሉ ለሙሉ እጁን ከመስጠቱ በፊት አደራ ሊላትና የልቡን ሊነግራት ወሰነ።
👍10