#የታካሚው_ማስታወሻ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
......ከተደጋጋሚ ጥዝ የሚል አስፈሪ ድምፅና መንቀጥቀጥ በኋላ ጄሶው ተፈልቅቆ ወጣ፡፡ እጄን እንድዘረጋውና እንዳጥፈው አዘዘችኝ፡፡ የቀደመውን ያህል አይታጠፍም አይዘረጋም፡፡ ዶክተሯ እጄ
ላይ የቀረውን ጥጥና ቆሻሻ በአልኮል እያፀዳችልኝ፡፡
“ጥሩ ነው፡፡ በየቀኑ ለተወሰኑ ደቂቃዎች እንደዚህ እያደረክ ካለማመድከው፣ ወደ ቀድሞው ቦታ ይመለሳል፤” አለችኝ፣ በእጆቿ እጄን እጥፍ ዘርጋ እያደረገች እያሳየችኝ፡፡
“እሱን ሃላፊነት እኔ እወስዳለሁ፡፡ አመሰግናለሁ ዶክ፤” አላት ዶክተር ሄኖክ ፈገግ ብሎ፡፡ ወደኔ ዞር አለና፣
“እንኳን ደስ አለህ ያቤዝ! አሁን ህክምናህን ጨርሰሃል፡፡” አለኝ
እጄን ይዞ እየወጣ፡፡ ምንም
አልመለስኩም፡፡ አሁን ከሆስፒታል ውጣ
ከተባልኩ የት እንደምሄድ፣ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ሃሳብ በአንዴ በድን አደረገኝ፡፡ እጄን እንደያዘኝ የሆስፒታሉን ዋና በር አልፈን ወጣን፡፡ዝምታዬን ሊሰብር፣
“ሆስፒታላችንን እንዴት አየኸው?” አለኝ፡፡
“አሪፍ ነው፡፡” በአጭሩ መለስኩ፡፡ የት እንደምሄድ፣ በምን ገንዘብ እንደምሄድ ጨንቆኛል፡፡ ለዚህም ዶክተርን ማስቸገር እንደሌለብኝ እያሰብኩ ነው፡፡ የሆስፒታሉ በር አካባቢ ወደ ቆሙ ታክሲዎች ሄድን፡፡
ፒያሳ፣ አራዳ እያሉ ይጣራሉ፡፡ ሁሉም ሃገር ፒያሳ አለ ማለት ነው?
ከዚህ በፊት የት ነበር የሰማሁት? አዎ፣ ደሴ፡፡ ስለ ፒያሳ ማሰብ ጀመርኩ። ከሚያስጨንቀኝ ሃሳቤ ፒያሳ ነፃ አወጣችኝ፡፡ ዶክተር አንዱ ታክሲ ውስጥ ይዞኝ ገባ፡፡ ታክሲው የት እንደጠራ አልሰማሁም፡፡ ከቀልቤ አልነበርኩም፡፡ የጎንደርን ፒያሳ ምን እንደምትመስል ለማየት ጓጓው::የተወሰነ እንደሄድን፣ የታክሲው እረዳት፣
“አስራ ስምንት ወራጅ አለ?” ብሎ ጠየቀ፡፡
“አዎ፡፡ ና እዚህ ነን፤” ብሎኝ ዶክተር መውረድ ጀመረ።ተከተልኩት፡፡ ከታክሲው ወርደን ትንሽ እንደተጓዝን፣
“አሁን የምንሄደው ወደኔ ቤት ነው :: ወደ ቤተሰብም ለመሄድ ሆነ ስራ ለመጀመር ተረጋግተህ እስክትወስን እኔ ጋር ትሆናለህ፡፡ ካሁን በኋላ እንደ ሃኪምህ ሳይሆን፣ እንደ ወንድምህ፣ እንደ ጓደኛህ ልታስበኝ ትችላለህ፡፡ ምንም ነገር አታስብ፤ ምትፈልገው ነገር ካለ ምንም
ሳትጨነቅ ልትጠይቀኝ ትችላለህ፡፡”
“አመሰግናለሁ ዶክተር፡፡ መቼም የማልከፍለው ውለታህ አለብኝ፡፡ የት እንደምሄድ በጣም ጨንቆኝ ነበር፡፡”
ትልቅ የብረት በር ያለው ግቢ ጋር ስንደርስ፣ ዶክተር በሩን በቁልፍ ከፍቶ ገባን፡፡ ሰፊ ንፁህ ግቢ፣ መሃል ላይ የቆመ ትልቅ ቪላ፣ ዙሪያውን የተደረደሩ ስርቪስ ቤቶች፣ ዶክተር ቪላውን አልፎ ጥግ ላይ
ያለች ሰርቪስ ክፍል ከፍቶ ገባ፡፡
“ግባ፡፡ እንግዲህ የወንደ ላጤ ቤቴ ይቺ ናት፡፡ ብቻዬን ነው ምኖረው፡፡ ካሁን በኋላ እንጋራታለን፡፡ አንድ ቁልፍ እንካ፡፡”
“ደስ ትላለች፡፡” አልኩኝ ወደ ውስጥ ገብቼ ዙሪያውን እየቃኘሁ፡፡መለስተኛ አንድ ክፍል ቤት፣ መሃል ላይ በመጋረጃ ተከፍላለች።ከመጋረጃው ጀርባ አልጋ እንደሆነ ገመትኩ፡፡ ቴሌቪዥን፣ በመፅሃፍት የተሞላ የመፅሃፍት መደርደሪያ፣ ዱካዎች፣ እቤት እንደሚያበስል የሚናገሩ እቃዎች፡፡ ዶክተር አንዲህ እንደሚኖር ገምቼም አላውቅም፡፡እኔ ከዚህ በጣም የተሻለ ንሮ ነበረኝ፡፡
“ቁጭ በል እንጂ፤ ቆመህ ቀረህ እኮ...” አለኝ ዶክተር ወደ ዱካዎች እያመለከተኝ፡፡ አንዱን ስቤ ተቀመጥኩ፡፡ወዲያው ዶክተር
ምግብ ማብሰል ጀመረ፡፡ አንዳንድ ነገር እያቀበልኩት ቆንጆ ሽሮ ወጥ ሰርቶ ምሳ በላን፡፡ በጣም ይጣፍጣል፡፡ የቤት ምግብ ናፍቆኝ ነበር፡፡ እቃ በማጠብ የቤተኝነት ስሜት እንደተሰማኝ ለማሳየት ሞከርኩ። ስንጨርስ ፒያሳ ወስዶ ከተማውን አሳየኝ፡፡ ፑል ተጫወትን፤ ሲመሻሽ ከፒያሳ
ወደቤት ወክ እያደረግን ተመለስን፡፡ ስንመለስ መንገዱ ቁልቁለት ስለሆነ
ነው መሰለኝ፣ ቅርብ እንደሆነ ተሰማኝ፡፡
ህይወት እንዲህ ቀጠለች፡፡ የኪስ ገንዘብ ይሰጠኛል፡፡ እርሱ ወደ ስራ ሲሄድ ከተማ ወጣ ብዬ ሻይ ቡና እላለሁ፡፡ እረፍት ሲሆን ከተማ ወጥተን ሻይ ቡና ብለን ፑል ተጫውተን እንመለሳለን፡፡ ስራ ከዋለ፣
ከስራ ሲመጣ ወክ እያደረግን እንጨዋወታለን፡፡ ዶክተር የሰጠኝ ፍቅር
አሁንም የሚፈልጉኝ ሰዎች እንዳሉ ተሰማኝ፡፡ እንድነቃቃና መኖር እንዳለብኝ እንዳስብ አድርጎኛል፡፡ በጣም ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነው::ስራ መጀመር እንዳለብኝ እያሰብኩ ነው፡፡ እርሱ ስራ ሲሄድ፣ በብዛት
ከተደረደሩት የስነ አዕምሮ መፅሃፍት እያነሳሁ፣ ስለ ባይፖላር ለመረዳት በብዛት በቤቱ ከደረደራቸው የስነ አዕምሮ መፅሃፍት እየመረጥኩ ሳነብብ እውላለሁ፡፡
#ህመም_አልባው_በሽታ
ዶክተር የባይ ፖላር በሽታ አለበህ ካለኝ ቀን ጀምሮ፣ ስለ ባይፖላር የማወቅ ፍላጎቴ ጨምሯል፡፡ መድሃኒት ከጀመርኩኝ በኋላ እያየሁ ያለሁት ለውጥ ጥሩ ስሜት ፈጥሮልኛል፣ ከቀደመው ስሜቴ
ጋር ሳነፃፅረው፣ አሁን የተለየ የተረጋጋሁ ይመስለኛል። አለምን የማይበትን መነፅር የቀየርኩ ያህል ልዩነት ይሰማኛል፡፡ ባይ ፖላር ግን ምን ማለት ነው...? እብድ ማለት ነው...? ወፈፌ...? ቀውስ ማለት
ይሆን...? ሆ...ሆ... ኧረ በጭራሽ...! እኔማ ቀውስ አይደለሁም፡፡
እንትና ቀውሱ፣ እንትና እብዱ፣ ያ ሾጡ፣ ቅብርጥሱ፣ ምናምን ሲሉ እሰማለሁ፡፡ ህመሞች ይሁኑ ስድቦች አይገቡኝም፡፡ እኔን ማንም እንዲህ ሲለኝ አልሰማሁም፡፡ ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ሆኖ ይሆን እንዴ?
ኖ.ኖ. እብድማ ብዙ ግዜ ተብዬ አውቃለሁ፡፡ እና ባይፖላር እብድ
ማለት ነው? ስለበሽታዬ ለማወቅ በየቀኑ አሰላስላለሁ። ዶክተር እንዳለው፣ ታምሜ ከነበር ይኼ በሽታ ህመም አልባ በሽታ ነው፡፡ ዶክተር ስራ ሲሄድ፣ እቤት ያለውን ስራ ጨርስና፣ ከተደረደሩት የስነ አዕምሮ
መፅሃፍት፣ እየቀያየርኩ አነበብኩኝ፡፡ አብዛኞቹ በሽታዎች ተመሳሳይ ሆኑብኝ፡፡ አንዱን ከአንዱ መለየት ቸገረኝ፡፡ ዶክተርን ማብራሪያ እንዲሰጠኝ ሚመቸውን ቀን መጠበቅ ጀመርኩ፡፡
አንድ ቀን ዶክተር አዳር ስርቶ ጥዋት መጣ፡፡ ከሰዐት ምሳ በልተን ፀሃዩ በረድ ሲል እንደተለመደው ወክ ልናደርግ ከቤት ወጣን፡፡በአባ ሳሙኤል አድርገን ቁልቁል ወደ እየሱስ መውረድ ጀመርን፡፡ ዛሬ
ለቀናት ያጠራቀምኳቸውን ጥያቄዎች ላዘንብበት ተዘጋጀሁ፡፡ ከግቢ
ወጥተን ትንሽ እንደተጓዝን፤
“ዶክ ጥያቄ ልጠይቅህ ፈልጌ ነበር”
“ጣድያ ምን ችግር አለው፣ ጠይቀኛ፡፡”
“ዶክ ባይፖላር አለብህ ካልከኝ ጀምሮ ስለበሽታው ለማወቅ ብዙ ሞክሬያለሁ፡፡ ብዙ አነበብኩ፤ ግን አልገባኝም፡፡ አስረዳኝ?”
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሀያ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በመለሰ_ታዬ (MD)
......ከተደጋጋሚ ጥዝ የሚል አስፈሪ ድምፅና መንቀጥቀጥ በኋላ ጄሶው ተፈልቅቆ ወጣ፡፡ እጄን እንድዘረጋውና እንዳጥፈው አዘዘችኝ፡፡ የቀደመውን ያህል አይታጠፍም አይዘረጋም፡፡ ዶክተሯ እጄ
ላይ የቀረውን ጥጥና ቆሻሻ በአልኮል እያፀዳችልኝ፡፡
“ጥሩ ነው፡፡ በየቀኑ ለተወሰኑ ደቂቃዎች እንደዚህ እያደረክ ካለማመድከው፣ ወደ ቀድሞው ቦታ ይመለሳል፤” አለችኝ፣ በእጆቿ እጄን እጥፍ ዘርጋ እያደረገች እያሳየችኝ፡፡
“እሱን ሃላፊነት እኔ እወስዳለሁ፡፡ አመሰግናለሁ ዶክ፤” አላት ዶክተር ሄኖክ ፈገግ ብሎ፡፡ ወደኔ ዞር አለና፣
“እንኳን ደስ አለህ ያቤዝ! አሁን ህክምናህን ጨርሰሃል፡፡” አለኝ
እጄን ይዞ እየወጣ፡፡ ምንም
አልመለስኩም፡፡ አሁን ከሆስፒታል ውጣ
ከተባልኩ የት እንደምሄድ፣ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ሃሳብ በአንዴ በድን አደረገኝ፡፡ እጄን እንደያዘኝ የሆስፒታሉን ዋና በር አልፈን ወጣን፡፡ዝምታዬን ሊሰብር፣
“ሆስፒታላችንን እንዴት አየኸው?” አለኝ፡፡
“አሪፍ ነው፡፡” በአጭሩ መለስኩ፡፡ የት እንደምሄድ፣ በምን ገንዘብ እንደምሄድ ጨንቆኛል፡፡ ለዚህም ዶክተርን ማስቸገር እንደሌለብኝ እያሰብኩ ነው፡፡ የሆስፒታሉ በር አካባቢ ወደ ቆሙ ታክሲዎች ሄድን፡፡
ፒያሳ፣ አራዳ እያሉ ይጣራሉ፡፡ ሁሉም ሃገር ፒያሳ አለ ማለት ነው?
ከዚህ በፊት የት ነበር የሰማሁት? አዎ፣ ደሴ፡፡ ስለ ፒያሳ ማሰብ ጀመርኩ። ከሚያስጨንቀኝ ሃሳቤ ፒያሳ ነፃ አወጣችኝ፡፡ ዶክተር አንዱ ታክሲ ውስጥ ይዞኝ ገባ፡፡ ታክሲው የት እንደጠራ አልሰማሁም፡፡ ከቀልቤ አልነበርኩም፡፡ የጎንደርን ፒያሳ ምን እንደምትመስል ለማየት ጓጓው::የተወሰነ እንደሄድን፣ የታክሲው እረዳት፣
“አስራ ስምንት ወራጅ አለ?” ብሎ ጠየቀ፡፡
“አዎ፡፡ ና እዚህ ነን፤” ብሎኝ ዶክተር መውረድ ጀመረ።ተከተልኩት፡፡ ከታክሲው ወርደን ትንሽ እንደተጓዝን፣
“አሁን የምንሄደው ወደኔ ቤት ነው :: ወደ ቤተሰብም ለመሄድ ሆነ ስራ ለመጀመር ተረጋግተህ እስክትወስን እኔ ጋር ትሆናለህ፡፡ ካሁን በኋላ እንደ ሃኪምህ ሳይሆን፣ እንደ ወንድምህ፣ እንደ ጓደኛህ ልታስበኝ ትችላለህ፡፡ ምንም ነገር አታስብ፤ ምትፈልገው ነገር ካለ ምንም
ሳትጨነቅ ልትጠይቀኝ ትችላለህ፡፡”
“አመሰግናለሁ ዶክተር፡፡ መቼም የማልከፍለው ውለታህ አለብኝ፡፡ የት እንደምሄድ በጣም ጨንቆኝ ነበር፡፡”
ትልቅ የብረት በር ያለው ግቢ ጋር ስንደርስ፣ ዶክተር በሩን በቁልፍ ከፍቶ ገባን፡፡ ሰፊ ንፁህ ግቢ፣ መሃል ላይ የቆመ ትልቅ ቪላ፣ ዙሪያውን የተደረደሩ ስርቪስ ቤቶች፣ ዶክተር ቪላውን አልፎ ጥግ ላይ
ያለች ሰርቪስ ክፍል ከፍቶ ገባ፡፡
“ግባ፡፡ እንግዲህ የወንደ ላጤ ቤቴ ይቺ ናት፡፡ ብቻዬን ነው ምኖረው፡፡ ካሁን በኋላ እንጋራታለን፡፡ አንድ ቁልፍ እንካ፡፡”
“ደስ ትላለች፡፡” አልኩኝ ወደ ውስጥ ገብቼ ዙሪያውን እየቃኘሁ፡፡መለስተኛ አንድ ክፍል ቤት፣ መሃል ላይ በመጋረጃ ተከፍላለች።ከመጋረጃው ጀርባ አልጋ እንደሆነ ገመትኩ፡፡ ቴሌቪዥን፣ በመፅሃፍት የተሞላ የመፅሃፍት መደርደሪያ፣ ዱካዎች፣ እቤት እንደሚያበስል የሚናገሩ እቃዎች፡፡ ዶክተር አንዲህ እንደሚኖር ገምቼም አላውቅም፡፡እኔ ከዚህ በጣም የተሻለ ንሮ ነበረኝ፡፡
“ቁጭ በል እንጂ፤ ቆመህ ቀረህ እኮ...” አለኝ ዶክተር ወደ ዱካዎች እያመለከተኝ፡፡ አንዱን ስቤ ተቀመጥኩ፡፡ወዲያው ዶክተር
ምግብ ማብሰል ጀመረ፡፡ አንዳንድ ነገር እያቀበልኩት ቆንጆ ሽሮ ወጥ ሰርቶ ምሳ በላን፡፡ በጣም ይጣፍጣል፡፡ የቤት ምግብ ናፍቆኝ ነበር፡፡ እቃ በማጠብ የቤተኝነት ስሜት እንደተሰማኝ ለማሳየት ሞከርኩ። ስንጨርስ ፒያሳ ወስዶ ከተማውን አሳየኝ፡፡ ፑል ተጫወትን፤ ሲመሻሽ ከፒያሳ
ወደቤት ወክ እያደረግን ተመለስን፡፡ ስንመለስ መንገዱ ቁልቁለት ስለሆነ
ነው መሰለኝ፣ ቅርብ እንደሆነ ተሰማኝ፡፡
ህይወት እንዲህ ቀጠለች፡፡ የኪስ ገንዘብ ይሰጠኛል፡፡ እርሱ ወደ ስራ ሲሄድ ከተማ ወጣ ብዬ ሻይ ቡና እላለሁ፡፡ እረፍት ሲሆን ከተማ ወጥተን ሻይ ቡና ብለን ፑል ተጫውተን እንመለሳለን፡፡ ስራ ከዋለ፣
ከስራ ሲመጣ ወክ እያደረግን እንጨዋወታለን፡፡ ዶክተር የሰጠኝ ፍቅር
አሁንም የሚፈልጉኝ ሰዎች እንዳሉ ተሰማኝ፡፡ እንድነቃቃና መኖር እንዳለብኝ እንዳስብ አድርጎኛል፡፡ በጣም ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነው::ስራ መጀመር እንዳለብኝ እያሰብኩ ነው፡፡ እርሱ ስራ ሲሄድ፣ በብዛት
ከተደረደሩት የስነ አዕምሮ መፅሃፍት እያነሳሁ፣ ስለ ባይፖላር ለመረዳት በብዛት በቤቱ ከደረደራቸው የስነ አዕምሮ መፅሃፍት እየመረጥኩ ሳነብብ እውላለሁ፡፡
#ህመም_አልባው_በሽታ
ዶክተር የባይ ፖላር በሽታ አለበህ ካለኝ ቀን ጀምሮ፣ ስለ ባይፖላር የማወቅ ፍላጎቴ ጨምሯል፡፡ መድሃኒት ከጀመርኩኝ በኋላ እያየሁ ያለሁት ለውጥ ጥሩ ስሜት ፈጥሮልኛል፣ ከቀደመው ስሜቴ
ጋር ሳነፃፅረው፣ አሁን የተለየ የተረጋጋሁ ይመስለኛል። አለምን የማይበትን መነፅር የቀየርኩ ያህል ልዩነት ይሰማኛል፡፡ ባይ ፖላር ግን ምን ማለት ነው...? እብድ ማለት ነው...? ወፈፌ...? ቀውስ ማለት
ይሆን...? ሆ...ሆ... ኧረ በጭራሽ...! እኔማ ቀውስ አይደለሁም፡፡
እንትና ቀውሱ፣ እንትና እብዱ፣ ያ ሾጡ፣ ቅብርጥሱ፣ ምናምን ሲሉ እሰማለሁ፡፡ ህመሞች ይሁኑ ስድቦች አይገቡኝም፡፡ እኔን ማንም እንዲህ ሲለኝ አልሰማሁም፡፡ ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ሆኖ ይሆን እንዴ?
ኖ.ኖ. እብድማ ብዙ ግዜ ተብዬ አውቃለሁ፡፡ እና ባይፖላር እብድ
ማለት ነው? ስለበሽታዬ ለማወቅ በየቀኑ አሰላስላለሁ። ዶክተር እንዳለው፣ ታምሜ ከነበር ይኼ በሽታ ህመም አልባ በሽታ ነው፡፡ ዶክተር ስራ ሲሄድ፣ እቤት ያለውን ስራ ጨርስና፣ ከተደረደሩት የስነ አዕምሮ
መፅሃፍት፣ እየቀያየርኩ አነበብኩኝ፡፡ አብዛኞቹ በሽታዎች ተመሳሳይ ሆኑብኝ፡፡ አንዱን ከአንዱ መለየት ቸገረኝ፡፡ ዶክተርን ማብራሪያ እንዲሰጠኝ ሚመቸውን ቀን መጠበቅ ጀመርኩ፡፡
አንድ ቀን ዶክተር አዳር ስርቶ ጥዋት መጣ፡፡ ከሰዐት ምሳ በልተን ፀሃዩ በረድ ሲል እንደተለመደው ወክ ልናደርግ ከቤት ወጣን፡፡በአባ ሳሙኤል አድርገን ቁልቁል ወደ እየሱስ መውረድ ጀመርን፡፡ ዛሬ
ለቀናት ያጠራቀምኳቸውን ጥያቄዎች ላዘንብበት ተዘጋጀሁ፡፡ ከግቢ
ወጥተን ትንሽ እንደተጓዝን፤
“ዶክ ጥያቄ ልጠይቅህ ፈልጌ ነበር”
“ጣድያ ምን ችግር አለው፣ ጠይቀኛ፡፡”
“ዶክ ባይፖላር አለብህ ካልከኝ ጀምሮ ስለበሽታው ለማወቅ ብዙ ሞክሬያለሁ፡፡ ብዙ አነበብኩ፤ ግን አልገባኝም፡፡ አስረዳኝ?”
✨ይቀጥላል✨
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2