አትሮኖስ
283K subscribers
111 photos
3 videos
41 files
500 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#የሴት_ልጅ

የሴት ልጅ ነው በሉኝ ስሜን ተውትና፣ ከፍ ከፍ አድርጉኝ ኩራቴ ናትና። ክብሬ ስለሆነ መጠራት በእናቴ፣ እሷ ስለሆነች ስጋ ደም አጥንቴ፣ ለኔ ልዕልና ነው የሷን ስም ማግኘቴ።

🔘ሀይደር🔘
👍5614🥰1
#የሴት_ልጅ

የሴት ልጅ ይለኛል ያዋረደኝ መስሎት
ስድብ እና ሙገሳ መለየት ተስኖት
አው የሴት ልጅ ነኝ ያውም የጀግናዋ
ጉንበስ ቀና ብላ ለልጅዋ ኗሪዋ
ዘጠኝ ወር ሳልከፍል በሆድዋ ተኝቼ
በጀርባዋ አዝላኝ እሰክሄድ በእግሮቼ
ተደፍታ ስታነድ ምግቡን ለማብሰል
እንጀራ ስትጋግር ፊትዋ መስሎ ከሰል
ሳጠፋ ገስፃ እንዳልኩራ መክራ
በርታ እያለችኝ ሁሌም እንዳልፈራ
አይዞህ አልከፋም ሴት ያሳደገኝ ነኝ
ስድብ ከመሰለህ ደጋግመህ ስደበኝ
አልቀየምህም በስምዋ ስትጠራኝ
እውነቱን ልንገርህ አዎ የሴት ልጅ ነኝ

"መታሰቢያነቱ እናቱን ለሚወድ በሙሉ።"

🔘ሎሬት ፀጋዬ ገ/ መድህን🔘
72👍22🥰2🔥1
#ንግድና_መሐላ

እጅን ለመሀላ

ከፍ አርጎ ዘርግቶ

በድለላ ቋንቋ

አግባብቶና ዋሽቶ

ለመሸጥ ሲታሰብ

የሁለቱን በሃያ፤

የአሥሩን በመቶ

በቀማኞች ጉሊት

በሌቦች ገበያ

ወላሂና እዝጌርን

ወጥ ሆኑ ማባያ ፡፡

#Share #like and #subscribe እያደረጋቹ።

👇Sebscribe

YouTube link👇
https://www.youtube.com/@atronosem
👍266👏2😱1
አሁን በቀደም'ለት..!

መጣች ተቀበልኳት አወጋች አመንኳት ብዙ ብዙ አለችኝ፣ የትም ከርማ መጥታ የሄደችበትን ምክንያት ነገረችኝ፣

ትክክል ነሽ አልኳት ባትሆንም ግድ የለኝ፣ ከመመለሷ እንጂ፣ ከመሄድ ምን አለኝ!?

🔘ሰሎሞን ሽፈራው🔘
👍22
"ቢደርስብህ ሀዘን ቢደርስብህ በደል ተሸሽገህ አልቅስ ወንድ ልጅ ነህ አይደል?

ሚሉህን አትስማ ተረቱን አፍርሰው
አልቅስ አልቅስ ካለህ፤
መሀል አደባባይ ዕንባህን አፍስሰው።

ግድ የለም ተንሰቅሰቅ፤
በልብህ እያነባህ ስቃይ አታስታምም ይህንን አስታውስ ፤

ውስጥህ ሲፈስ ነው የሚገድለው ደም

🔘እዮብ🔘
👍34
#እኔ_ጠላሻለሁ

እንደ ጫማ ሽታ

ልክ እንደ በሽታ

ጌታ በባርያው ላይ እንደ ሚበረታ

#እኔ_ጠላሻለሁ

እንደ ረጅም መንገድ

ለሀብታም እንደ መስገድ

ከጠጡ በኋላ እንደ መንገዳገድ

#እኔ_ጠላሻለሁ

ገንዘብ እንደ ማጣት

ዳገት እንደ መውጣት

ከያዘ እንደ ማይለቅ እንደ ጨካኝ ቅጣት

#እኔ_ጠላሻለሁ

ልክ እንደ መልከስከስ

እምነት እንደ ማርከስ

ማስቲካ እያኘኩ ምላስ እንደ መንከስ

እኔ ጠላሻለሁ . . . (ወዘተ )

አሁን ግን ፈራሁኝ ጀመርኩኝ መብሰልሰል ጠላሁሽ ያበዛሁ #ወድጄሽ ነው መሰል፡፡

🔘እዮብ🔘
30👍27😁10👏4
#አንቺ. . .

እንደዘመኑ ሴት፤
መኪና ላለው ወንድ ጭንሽን ማትከፍቺ ኑሮን ለማሸንፍ፣
የምትታትሪ የምትሟሟቺ
አንቺ. . !

በአቋራጭ ሄደሽ ቁማር ሳትቆምሪ በጉልበት በላብሽ፤
የራስሽን ህይወት ምታስተዳድሪ ቤተክርስቲያን ብለሽ፤
ከቦርጫም ሰውዬ ጋ ክለብ የማታድሪ
አንቺ .. !

የሄዋን ምሳሌ የሴትነት ልኩ
መልካም ፀባይ ያለሽ የጨዋነት መልኩ

ዘመንሽ ይለምለም ...
በበረከትና በፀጋ ተከቦ
መልካሙ ፈጣሪ ፤
መልካሙን በሙሉ ጀባ ይበልሽ አቦ! ! !

🔘እዮብ🔘
🥰41👍172
አልወድክም በይኝ

   ልቤ ተጨነቀ....

መጥላትም ፍቅር ነው

  ቁርጡ ከታወቀ።😔
23👍11
እንገናኝ ስልሽ ደስ ይለኛል'' ያልሽው፣
የት ይሻላል?' ስልሽ ቦታ ያልመረጠጥሽው፣

ፒያሳም ይርቀኛል ቦሌም አልተመቸኝ    ጎተራና ሳሪስ ቄራም ደስ አላለኝ፣

ሜክሲኮ ፍልውሃ ካዛንቺስ አልመጣም፣ አንቺን ለማዝናናት ከተማዋ አትበቃም።

ነፍሴ ተጨነቀች ቦታ አላውቅም ውዴ፣ አልጋዬ ስፊ ነው ይመችሻል እንዴ?
እ.........
😁46🤩7👍6👎4👏3🥰1
#አታጭኝም

የረታኝ ቁመናሽ ወይ መልክሽ አይደለም ተፈጥሮሽ ስቦኝ ነው ከብልጭልጩ ዓለም
ልብሽ ነው የገዛኝ ገራገርነትሽ ተለይቶ ቢታየኝ...

ከአስመሳዮች መሀል እወነተኛነትሽ ውበትሽም ቢጠፋ እርጅና ተጭኖት
እኔ አንቺን ማፍቀሬ አይቆምም እስከሞት ይሄው ቃሌን እንኪ...

ደስታን ልፈጥርልሽ፣ ሰላም ስትፈልጊ ልሆንሽ ማረፊያ

አንቺ እሳት ስትሆኚ እኔ መሬት ልሆን
ንዴት ማራገፊያ
ቃሌ ነው እመኝኝ...

በሀዘን በህመምሽ ደንቀፍም ሲያደርግሽ አታጭኝም እኔን አጠገብሽ ሆኜ
ሁሌም እኔን ስልሽ።

🔘ቴድ ሀበሻ🔘
👍232
''ቱ በል ልምታልህ'' አለችው
ሲያለቅስ አቀፈችው።

''ቱ" አለ
በእጇ መታችለት በጥፊ መሬቱን
ማልቀሱ አበቃ አቆመ ምሬቱን!

አደገ
ትልቅ ሆነ

ህይወትን ቢቀየም
ለብቻው አዘነ በዕንባ ላይወጣለት


ዛሬ ሰው የለውም
ጊዜን ማን ይምታለት ?


🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
👍32🥰7
#የምትመስለው

የኔ ልዕልት ...

ጸዳል ክብሯ ከሴት መሐል አቻ የሌለው
በማለዳ ደምቃ የፈካች
ውብ ጸሐይ ነው የምትመስለው

ብዬሸ ነበር ያኔ ድሮ ልጅ እያለው

ግና ዛሬ አደግሁና
ሁሉን በጥልቅ ሳስተውለው
ይቅር በይኝ ማሪኝ ውዴ አጥፍቻለው

ለካ ጸሐይ ራሷ ናት
ቁር'ጥ አንቺን የምትመስለው !
👍16🥰7👏2
🍁🍁ዲያሪው 📝

ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
#ክፍል_10

ለመቀንጠስ እጁን ሲያሾል ነበር ያቆምኩት:: ንባቤም ቀጠልኩ። የኔቶ ቀባጣሪም መቀባጠሯን ቀጠለች፣ "ጊዜ በጊዜ እየተተካ በሄደ ቁጥር እኔም ንዴቴ ቀስ በቀስ እየበረደ መጣ። እርግጥ በደሱ ሊረሳ የሚችል አልነበረም። ማንኛውም የሰው ፍጡር የህይወቴ ጎዳና ይህ ይሆናል፣ ሀይወቴንም በዚህ መንገድ፣ እንዲህ አድርጊ! እመራዋለሁ ብሎ የወጠነው ሁሉ ተመሰቃቅሎ ከፊት ለፊቱ የሚያየውና ሊጓዝበት ያሰበው ለስለሳና ደልዳላ መንገድ በእሾህና በጋሬጣ ታጥሮ መውጪያውና መግቢያው ወደማይለይ አባጣና ጎርባጣ መንገድ በቅጽበት ሲለወጥበትና ተስፋ ለተስፋቢስነት ቦታ ሲለቅ ሲያይ መበሳጨት እንዴት ይበዛበታል:: የኔ ሁኔታ ከዚህ የተለየ አልነበረም:: ከአማረ ጋር ሆኜ በደስታና በፍቅር አሳልፈዋለሁ ያልኩት ህይወት የማይጨበጥ ህልም ሆኖ ሲቀር የምመካበትና አንድ አለኝ የምለው ሰው ሲከዳኝና በአንድ ጊዜ ተስፋዬ ተሟጦ የወደፊት ህይወቴ ምን ሊሆን እንደሚችል ልገምት በማልችልበት ሁኔታ ላይ ሆኜ እያለሁ ደስታ ይኖረኛል ብሎ መገመት የዋህነት ነው:: ይሁን እንጂ ዶ/ር አድማሱ በጭንቅት ቀን ከእግዜር የተላከ መልአክ ተመስሎ ባጠገቤ በመገኘቱ ብዙውን ነገር ቀስ በቀስ ባልረሳው እንኳን ለመርሳት እንድሞክር ረድቶኛል:: አብዛኛውን ከትምህርት ውጪ ያለውን ጊዜዬን የማሳልፈው ከእሱ ጋር ነበር፡፡ ብዙውን ጊዜ በትምህርቴ እንድጠነክርና ሁሉንም ነገር እንደ ተራ ነገር እንድረሳው ይመክረኛል፡፡ እኔም አብዛኛውን ጊዜ የግቢውን ወሬ ሳልፈራና ለማንም ቁብ ሳልሰጥ እሱ ቤት እያመሸሁ ጥናቴን ተያያዝኩት፡፡ የሚቸግረኝን እየረዳኝ ከጎኔ ሳይለይ የሚያፅናናኝም እሱ ብቻ ነበር፡፡ ከእሱ ጋር ያለኝ ግንኙነት እየጠነከረ የመሄዱን ያህል የትምህርት ቤት ጎደኞቼ ደግሞ ይበልጥ በጥላቻ ይመለከቱኝ ጀመር። አብዛኛው ተማሪ ከዶ/ር አድማሱ ጋር የነበረኝን ግንኙነት አማረን በጥቅም _ ለውጬ የፈጠርኩት ግንኙነት አድርጎ የተሳሳተ ግንዛቤ ፈጥሮ ስለነበር ቢጠሉኝም በእነሱ አልፈረድኩም:: በተለይ ጓደኞቹ እኔን ጠይቀው በመረዳት ፈንታ እኔን አኩርፈው ወሬውን በመሰላቸው መንገድ ያናፍሱት ስለነበር ተማሪዎቹ የሰሙትን የተሳሳተ ወሬ ሰምተው ቢጠሉኝ አያስገርምም፡፡ ከሃዲዋ እኔ ላልሆን ከሀዲው አማረ መሆኑንና ከዶክተር አድማሱም ጋር ያለኝ ግንኝነት የወንድምና የእህትነት ዓይነት እንደሆነ ለጓደኞቼ ብናገርም የሚያምኑኝ አልነበሩም። ስለዚህም እኔ ይህንኑ ተንትኜ ለማስረዳት እቅሙም ሆነ ችሎታው ስላልነበረኝ እንደመፍትሄ የወሰድኩት ለማንም ሳልጨነቅ ይበልጥ ከተማሪዎች በመራቅ አብዛኛውን ጊዜዬን ከዶክተር አድማሱ ጋር ማሳለፍ ብቻ ነበር።

ጥር 30 ቀን 1978 ዓ.ም

ተሾመ ለእኔ ያለው የፍቅር ስሜት የእብደት እንጂ የጤንነት ነው ማለት ያዳግታል፡፡ አማረ ግቢ ውስጥ በነበረበት ወቅት ምን ያህል እንደምንዋደድና በዚህም የተነሳ ከእሱ ጋር መደባደቡን እያወቀ፣ ከዚህም አልፎ ተርፎ እኔ ለእሱ ፍቅር እንደሌለኝ ደግሜና ደጋግሜ ብነግረውም በፍጹም ሊተወኝ አልቻለም፡፡ እንዲያውም ቀስ በቀስ በሰላማዊ መንገድ እንደማያገኘኝ ስለተረዳ ማስፈራራትና መማታቱን ቀጠለ፡፡ ሌላ የማገባ ከሆነ እኔን፣ የማገባውን ሰውና የራሱን ህይወት ጭምር እንደሚያጠፋ መዛት የዘወትር ተግባሩ ሆነ፡፡ ይሁን እንጂ በወቅቱ ይህንን ለአማረ መናገር ማለት ተጋደሉ ማለት ስለመሰለኝ ለመናገር አልፈለኩም ነበር። አማረ ግቢውን ከለቀቀ በኋላም ተሾመ ይህንኑ ድርጊቱን አጠናክሮ በመቀጠሉ ለመክሰስ እንደወሰንኩ ለኤልሳ ነገርኳት፡፡ ኤልሳ ግን ከከሰስኩት ከዩንቨርስቲ _ ስለሚያባርሩት እሷ እንዲያርፍ እንደምትነግረውና ነገር ግን ምክሯን ሰምቶ ካላረፈ ለወላጆቹ ደውላ እንደምትነግር ቃል ስለገባችልኝ ክሱን ተውኩት፡፡ የነገርኳትን ነግሬዋለሁ ካለች በኋላ ለተወሰነ ጊዜ መተናኮሉን ቢያቆምም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን ዶ/ር አድማሱ ቤት አዘውትሬ መሄዴን በማወቁ ተመልሶ አገረሸበት፡፡ ኤልሳ ይህንኑ ጉዳይ ለወላጆቹ ነግሬአለሁ ትበል እንጂ እሱ ግን በፍፁም ሊታገስ አልቻለም፡፡ በተለይ ሁሌ የሚገርመኝ ነገር ቢኖር ማታ ማታ እየጠበቀ የሚያስፈራራኝና የሚመታኝ ባጋጣሚ ከኤልሳ ተለይቼ በምሄድበት ጊዜ ስለነበር ሆን ብላ ከእሱ ጋር እየተነጋገረች ምክንያት ፈጥራ ከእኔ የምትለይ እየመሰለኝ መጣ፡፡ በወንድምነት ይሁን ወይም በጾታዊ ፍቅር መሆኑ በግልጽ ባይገባኝም፤ ኤልሳ እንደምትወደው ግን አውቃለሁ፡፡ እሱ ግን ለእሷ አንዳችም ፍቅር የለውም.፡፡ እኔ እንዲያውም አንዳንዴ ብገላገል በማለት እስኪ እንደምትወጂው ልንገረው ካልኳት፤ ይህንን ከነገርኩት እንደምንጣላ ከመናገር ውጪ እሱን የእሷ ለማድረግ የምታደርገው ጥረት ግን የለም፡፡ ተሾመ ከእኔ ጋር የሚፈጠረውን አምባጓሮ እያየች ምንም የቅናት ስሜት ስለማላይባት ሆን ብላ እኔና እሱን ለማፋቀር የምታደርገው ምክንያት እንጂ ከእሱ ጋር ፍቅር የላትም ብዬ እንድጠረጥር አደረገኝ፡፡ በመጨረሻም ማስቸገሩ ሲበዛብኝ ሁኔታውን ለዶ/ር አድማሱ ነገርኩት፤ ልከሰው ስላሰብኩም ምን እንደሚመክረኝ ጠየቅሁት፡፡ እሱ ግን መፍትሄ እንድሚፈልግልኝ ቃል ገብቶ እንዳልከሰው ከለከለኝ፡፡ ዛሬ የመጀመሪያውን ሴሚስተር _ ፈተና ጨርስን ውጤት ተለጥፎ በነበረበት ምሽት ወደ ራት ስሄድ ተሾመን እንደተለመደው ከራት ስመለስ ብቻውን አገኘሁት፡፡ ገና እንደደረሰ በጥፊ ካጮለኝ በኋላ፤

"አንቺንም፣ ያን ዶክተርሽንም ካልደፋኂችሁ እኔ ተሾመ አይደለሁም፡ ብሎ ዝቶብኝ ሄደ። አጥፊው በላይ ፊቱ ላይ የነበረውን ንዴቱን ሳይ ክፉኛ ደነገጥኩ፣ ተናደድኩም፡፡ ወዲያው ዶ/ር አድማሱ ጋ ሄድኩና፤ "አንተ ነህ እንዲህ እምትጫወትብኝ፣ ልክሰስ ስልህ እኔ አስታግሰዋለሁ እያልክ ልታስገድለኝ ነው፡፡ ከአሁን ወዲያ የፈለከውን ብትል አላምንህም፣ ቢፈልጉ እንኳን ከዩንቨርስቲ ማባረር _ ቀርቶ እንጦሮጦስም ይክተቱት እንጂ እኔ እንደሆነ ነገ መክሰሴ አይቀርም" እያልኩ ጮህኩበት፡፡ እሱ ግን በተራጋጋ መንፈስ በጥፊ የቀላውን ፊቴን በእጁ እያሻሸ፤ “በቃ ተይ አትናደጂ፣ ከአሁን በኋላ መክሰስ ትችያለሽ፣ እኔ አያገባኝም፡፡ እኔ ይሰማኛል በማለት አንድ ሁለት ጊዜ መካክሬው ነበር፡፡ እሱ ግን ብመክረውም ተመልሶ እዛው ስለሆነ ከአሁን በኋላ አያገባኝም፤ ነገውኑ ክሰሺው" አለኝ፡፡ ጠዋት እሱን ለመክሰስ ወስኜ ከቤት ብወጣም፣ ኤልሳ ቁርስ እየበላን ሳለ ተሾመ በዶ/ር አድማሱ ሁለት ኮርሶች ኤፍ (F) ማግኘቱንና ከዩንቨርስቲ መባረሩን ነገረችኝ፡፡ ይህንን ስሰማ በጣም ደነገጥኩ፡፡ እንደተለያየን በጥድፊያ ወደ ዶ/ር አድማሱ ቢሮ አመራሁ፡፡ እንደገባሁም በሩን ከኋላዬ ዘግቼ! "ዶ/ር፣ ለእኔ ብለህ ነው እንዴ ለተሾመ ኤፍ (F) ሰጥተህ ከትምህርት ቤት እንዲባረር ያደረከው" ብዬ አፈጠጥኩበት?' እሱ ግን ምንም እንደማያውቅ በሚመስል ሁኔታ፤ "ተሾመ ኤፍ አምጥቶ ተባረረ ነው የምትዪኝ? እኔ የሰማሁት አሁን ገና ከአንቺ አፍ ነው፡፡ ለመሆኑ በምን ትምህርት ነው ኤፍ ያመጣው?" ብሎ እኔኑ መልሶ ጠየቀኝ፡ "አንተ በምትሰጣቸው ሁለት ትምህርቶች ነው ወድቆ የተባረረው። ይህንን አታውቅም ማለት ነው?' አልኩት በንዴት፡፡ "ማወቅ አላውቅም፡፡ ነገር ግን ልጁ ሰነፍ መሆኑን አውቃለሁ፡፡ እሱ ትምህርቱን ትቶ አንቺን አፈቀርኩ እያለ ሲሟዘዝ ስለሚውል ቢወድቅ የሚደንቅ አይደለም፡፡ እርግጥ በእኔ ትምህርት ኤፍ ያገኙ ተማሪዎች አሉ፡፡ ይሁን እንጂ እኔ ሁሌ ፈተና ሳርም እንዳላዳላ (Bias እንዳልሆን) በማለት ስም ስለማላይ ኤፍ ያገኘው እሱ ይሁን ሌላ ሰው የማውቀው
👍404
ነገር የለም፡፡ ያም ሆነ ይህ አንቺ ምን አስጨነቀሽ? እንዲያውም አንቺ ከስሰሺው ለእሱ መባረር ምክንያት ከመሆን ድነሻል" ብሎ በተረጋጋ መንፈስ አባብሎ ሸኘኝ።

ከተሾመ መባረር በኋላ የግቢው ሰው በእኔ ላይ ያለው ጥላቻ እየተባባሰ መጣ። እርግጥ ተሸመ ከእኔ ጋር ባለው ጠብ የተነሳ ሆን ተብሎ በዶ/ር አድማሱ እንደተባረረ ለአካዳሚክ ኮሚሽን ከሶ በተደረገው ምርመራ ይህንን የሚደግፍ ወይም የሚያረጋግጥ ምንም ማስረጃ ስላልተገኘ ክሱ ውድቅ ተደርጎበታል፡፡ ይሁን እንጂ እኔን ራሴን ጨምሮ አብዛኛው ተማሪ ዶ/ር አድማሱ ሆን ብሎ ያደረገው ነው በማለት በመጠርጠራቸው በዚህ የተነሳ ቢጠሉኝ አያስደንቅም፡፡ ያም ሆነ ይህ እያዘንኩም ቢሆን ተሾመ ግቢውን ለቆ በመሄዱ ሰላም አገኘሁ፡፡ ነገር ግን ኤልሳ በዚሁ የተነሳ ውስጥ ውስጡን ተቀይማኝ ስለነበር ጓደኝነታችን ቢቀጥልም እንደድሮው ግን ሊሆን አልቻለም፡፡ ሰኔ 4 ቀን 1978 ዓ.ም "እግዚአብሄር ሳይደግስ አይጣላም እንደሚባለው ሁሉ፣ በዚህ ግቢ ውስጥ የተለያየ ችግርና መከራ ቢፈራረቅብኝም በዶ/ር አድማሱ እርዳታ የመመረቂያ ፕሮጀክቴን በተሳካ ሁኔታ አጠናቅቲ ለማቅረብ ዝግጅቲን ጨረስኩ:: የምመረቀው በእርሻ ምህንድስና ሲሆን የመመረቂያ ፕሮጄክቴ ጥቃቅን የመስኖ ቴክኖሎጂ (Micro-Irrigation) በሚባለው ላይ ነበር። እነዚህ በቀላሉ በሰው ጉልበት ወይም በእንስሳት ኃይል ሊንቀሳቀሱ የሚችሉ የህ ፓምፖች ሲሆኑ ወንዞችን፣ በጉድጓድ ወይም በኩሬዎች የተከማቸ ውሀን በመጠቀም ለአትክልትና ፍራፍሬ ልማት የሚጠቅም የመስኖ ቴክኖሎጂ ነው፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ እንደ ዛምቢያና ናይጄሪያ በመሳሰሉ አገሮች በስፋት የሚጠቀሙበት ሲሆን “አርፈሽ ተኚ” እያሉ ይጠሩታል:: ይህ ስያሜ የተሰጠው ወንዱ ቀን ቀን በዚህ ፓምፕ ውሀ ለማውጣት በእግሩ ወይም በእጁ ፓምፑን ሲያሽከረክር ውሎ ደክሞት ወደ ቤት ስለሚገባና ለወሲብ የሚሆን አቅም ስለሌለው ሚስቱ እንዳትረብሸው የሚሰጠው ማስጠንቀቂያ ምን ሊሆን እንደሚችል ለማሳየት የሚጠቀሙበት ብሂል ነው:: ለፕሮጄክት የተጠቀምኩበት ቴክኖሎጂ በአገራችን እምብዛም የተለመደ ስላልነበር ተግባር ላይ ቢውል ጠቀሚታው የጎላ ነው በሚል የመረጥኩት ሲሆን፤ በአነስተኛ ወጪ ከአካባቢ ቁሳቁስ ሊሰራ የሚችልና ማንኛውም ሰው በቀላሉ ተረድቶ ሊተገብረው የሚችል ተስማሚ ቴክኖሎጂ ነው:: ፕሮጄክቱን በዓለማያ አካባቢ ካሉ አርሶ አደሮች ጋር በጋራ ያከናወንነው ሲሆን ገበሬዎቹ ይህንን ፓምፕ በአካባቢያቸው ከሚገኝ ቁሳቁስ _ ሰርተው ውሀ ለማውጣትና ሰብላቸውን ለማጠጣት ተጠቅመውበታል፡፡ በዚህም ከፍተኛ ምርት ሊያገኙ ችለዋል፡፡ የመመረቂያዬ ቀን ተቃርቦ ፕሮጄክቴን የማቀርብበት ቀን ሲደርስ የተደባለቀ ስሜት ፈጠረብኝ፡፡ በአንድ በኩል ይኸን ለእኔ ገነትም ገሀነምም የነበረውን ዩንቨርስቲ ለቅቄ የምወጣበት ቀን በመድረሱ ሁሉንም ነገር በቶሎ

አጠናቆ መውጣት ደስታን ሲፈጥርብኝ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ፍቅርን ከነፈጉኝ ተማሪዎች ፊት ቆሜ ፕሮጄክቴን ማቅረብ ፍርሀት ነዛብኝ: ዶ/ር አድማሱ ቀደም ሲል ፕሮጀክቴ አድናቆት ማግኘቱን፣ አብሬ ከምሰራው መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት የአምስት ሺ ብር ሽልማት ያስገኘልኝና በዩንቨርስቲውም ተደናቂነትን ያተረፈ መሆኑን ያውቅ ስለነበር፤ ያለፈውን ነገር ሁሉ ትቼ ዛሬ ፕሮጄክቴን በተዋጣለት መልኩ በማቅረብ ላይ እንዳተኩር ደጋግሞ መክሮኛል:: ለእኔም ከሐሳብ የመውጪያ ብቸኛው መንገድ ይኸው በመሆኑና ብዙ ደክሜበት ስለነበር የተዋጣለት እንደሚሆን እርግጠኛ ነበርኩ:: ቀኑ ደርሶ ፕሮጄክቴን ለማቅረብ ስወጣ ጉልበቴ አካላቴን መሸከም አቅቶት ተብረከረከ፡፡ እንደምንም ወጥቼ የመጀመሪያውን ቃል ለመናገር አፌን ከከፈትኩ በኋላ ግን ፍርሀቴ ጠፍቶ ሁለመናዬ ፕሮጄክቴ ውስጥ ገባ:: የፈራሁት የተማሪዎች ዓይን ብዙም ተፅዕኖ ሳያሳድርብኝ ሁሉም ነገር በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ፡፡ ጥሩና ስኬታማ ነገር በማቅረቤ ተማሪው እጅግ ከመደነቁ የተነሳ ባልጠበቁት ሁኔታ ወደ መቀመጪያ ቦታዬ እስከምደርስ ድረስ ቆመው አጨበጨቡልኝ፡፡ የጠበቅሁትን ሳይሆን ያልጠበቅሁትን በማየቴ እጅግ ተደሰትኩ፡፡ እነዚያ ይጠሉኛል ብዬ የምገምታቸው ተማሪዎች ሁሉ ቆሞው ሲያጨበጭቡልኝ ሥራዬ በእርግጠኝነት የተዋጣለት መሆኑ ተሰምቶኛል፡፡ ከእኔ በፊትም ሆነ በኋላ እንደ እኔ የተጨበጨበለት ተማሪም አልነበረም:: ወደ ወንበሬ እንደተመለስኩ መጀመሪያ መመልከት የፈለኩት ዶክተር አድማሱን ነበር፡፡ እንደእኔ የደከመበት ፕሮጄክት ስለነበር ምን እንደተሰማው ለማወቅ መጓጓቴ አግባብነት ነበረው:: መድረኩ ላይ ቁጭ ብሉ ተማሪዎቹ ሁሉ የእኔንና የእሱን ሁኔታ እንደሚከታተሉ ቢያውቅም፣ ለዚህ ምንም ቁብ ሳይሰጠው ከሌሎች አስተማሪዎች በተለየ ሁኔታ እያጨበጨበ ፊቱ በፈገግታ ተሞልቶ በአድናቆት ራሱን ሲነቀንቅ በማየቴ ዓይኔ በእምባ ተሞላ፡፡ ስሜቴን መቆጣጠር ተስኖኝ የደስታ እምባ በጉንጮቼ ላይ ወረደ:: እርግጥ ደስታና ሐዘን የተፈራረቀበት የዩንቨርስቲ ህይወቴ ባልጠበቁት አኳኋን እንዲህ በተሳካ ሁኔታ በመጠናቀቁ በደስታ ብዛት ባነባ የሚገርም አልነበረም። እነሆ እኔና ዶ/ር አድማሱ የለፋንበትና የደከምንበት ፕሮጄክት በውጤታማነት ተጠናቀቀ፡፡ ሁሉም ነገር በዚህ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ የረዳኝን አምላኬንም እዚያው እተቀመጥኩበት ዓይኔን ጨፍኜ ምስጋና አቀረብኩለት፡፡ ለእኔ የዚህ ፕሮጄክት መሳካት ለትልቅ ግምት የሚሰጠው ነበር፡፡ ምክንያቱም በሁሉም ውጤቶቼ ከተማሪው በሙሉ የተሻለ ከፍተኛ ውጤት ያመጣሁ በመሆኔና ፕሮጄክቴም በጠበቅሁት ሁኔታ ከተጠናቀቀ የሽልማቱ ወርቅ የእኔው እንደሚሆን የማረጋግጥበት ወቅት በመሆኑ ነው:: ይህንንም ዛሬ ማረጋገጥ ስለቻልኩ በደስታ ባለቅስ የሚበዛብኝ አልነበረም:: ተማሪው ይህንኑ

ስለሚያውቁ፣ እኔን ቢጠሉኝም ሥራዬን ግን በመውደዳቸው አልባቸው አጨብጭበውልኛል:: ተማሪዎቹ ሁሉ ይጠሉኛል ብዬ የማስብ ቢሆንም ለመጀመሪያ ጊዜ ግን "ማን ያውቃል ብዙ የሚወዱኝ ሊኖሩ ይችላሉ ብዬም ማሰብ ጀመርኩ:: ሰኔ 25 ቀን 1978 ዓ.ም ዛሬ የመመረቂያችን ቀን በመሆኑ ግቢው ጥቁር ገዋን በለበሱ ተማሪዎች፣ የአበሻ ቀሚስና ሱፍ ልብስ በለበሱና ልጆቻችውን ለማስመረቅ ተጋጊጠው በመጡ ወላጆች አሸብርቋል። ይህ ቀን ለእኔ እንደአለፈው ሕይውቴ ሁሉ ሁለት ገፅታ አለው፡፡ በአንድ በኩል የተማሪዎች ቁንጮ መሆኔ የሚበሰርበት የብስራት ቀን ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ ውጣ ውረድ የበዛበት የታሪኬ ምዕራፍ የሚዘጋበት ዕለት ነበር:: አባቴ በወቅቱ በመታመሙ ምክንያት ባይመጣም እናቴ ግን መጥታ ነበር፡፡ የምፀልየው ግን እናቴ የሳንቲሙን አንድ ገፅታ ብቻ ሰምታና አይታ እንድትመለስ ነበር፡፡ ይህም ደክማና ለፍታ ያሳደገቻት ልጅ የተማሪዎች ቁንጮ ሆና ስትመረቅ ማየት ነው:: ይህንንም ሳስብ ልቤ በደስታ ይሞላል:: እንደጠበቅሁትም ሆነ፡፡ የሽልማቱን ወርቅ አጥልቄ እንዳየች እናቴ ማልቀስ ብቻ ሳይሆን በእምባ ታጥባ ነበር፡፡ ተቃቅፈን ተላቀስን፡፡ ዶ/ር አድማሱም ዛሬ ደስታውን መቆጣጠር _ አልቻለም:: _ ከአዳራሹ ስንወጣ የተማሪዎቹ ዓይን ሳይፈራ አቅፎ ሳመኝና፤ “አንቺ ገና ብዙ ትላልቅ ነገር ሊሰራ የሚችል ጭንቀላት ያለሽ ነሽ፡፡ አደራ በማይረባ ነገር እንዳታበላሺው" አለኝ፡፡ ለራሴም ከአሁን በኋላ ይህንን ጭንቅላት ላላበላሸውና ትላልቅ ረቂቅ ነገሮችን የሚያብሰለስል እንጂ ግለሰቦችንና የእነሱን ዝባዝንኬ ታሪክ በማውጣትና በማውረድ እንዲላሽቅ እንደማላደርገው ቃል ገባሁ፡፡ ከምረቃው አዳራሽ እንደወጣን ፎቶግራፍ ለመንሳት ወደ አትክልቱ ቦታ አመራን፡፡ አማረን ለማስታወስ
👍252
በማለት በእነዚያ በአጭሩ በተከመከሙና በመንገዱ ግራና ቀኝ በተተከሉ ፅዶች በተዋበው "የፍቅር ጎዳና" ላይ እስከሚበቃኝ ድረስ ከእናቴ፣ ከዶ/ር አድማሱና ከብዙ አድናቂ ተማሪዎች ጋር ፎቶ ተነሳሁ፡፡ እያንዳንዷ ከሰዎች ጋር ተቃቅፌ የምነሳት ፎቶ፣ ከአማረ ጋር ከላይብረሪ ወጥተን በዚህ መንገድ ላይ ተቃቅፈን የሄድንበት ጊዜ የሚያስታውሰኝ በመሆኑ ከደስታዬ ባሻግር አንዳች ነገር እንደቀረብኝ ዓይነት ስሜት ተሰማኝ፡፡ አፍ አውጥቼ ባልናገርም፤

"ምናለ ዛሬ አጠገቤ በነበርና ደስታዬ እጥፍ ድርብ በሆነ˚ አልኩ፡፡ ምረቃው ካበቃ በኋላ ግቢውን ለቅቄ የምሄድበት ቀን ቁርጥ እየሆነ ሲመጣ ደግሞ ፍርሀት ወረረኝ:: ግን ለምን? ከዚህ በኋላ እዚህ ምን ቀረኝ? ለምንስ ፈራሁ? ራሴን ጠየቅሁ:: አዎ! እርግጥ ነው የእኔ ለእዚህ መብቃት ምሥጋናው መድረስ ያለበት ለዶ/ር አድማሱ ነው:: ይህንን ሁሉ መከራ አልፌ ለዚህ እንድደርስ ያበቃኝ እሱ ነው:: የቀረኝ አንድ ጓደኛም እሱ ብቻ ነበር:: ዛሬ ደግሞ በተራው እሱንም ላጣው ነው። ከእሱ መለየቴን ሳስብ ልቤ በፍርሀት ራደ:: ለዚህ ሁሉ ውለታው ምን ሊከፈለው ይቻላል? ይህን ምንም ስጦታ ሊተካው የማይችለውን ውለታውን እኔ ከፍዬ ልወጣው ስለማልችል አምላኬ ሁሉንም ጥሩ ጥሩ ነገር እንዲያደርግለት ተመኘሁ:: እናቴን ግቢውን እያዞርኩ ሳስጎበኛት በመዋሌ በጣም ደክሟት ስለነበር በጊዜ መተኛት በመፈለጓ አልጋዬን ለቅቄላት እኔ ግን ከጎደኞቼ ጋር እንደማድር ነግሬያት ተሰናብቼያት ወጣሁ፡፡ ይህንን ሁሉ ጊዜ አጠገቤ ሆኖ ሲያፅናናኝና ሲረዳኝ የነበረውን ዶክተር አድማሱን ቀኑን ሙሉ ስላላገኘሁትና የዋለልኝን ውለታ ሁሉ ልመልሰው የማልችል ቢሆን እንኳ ቢያንስ አቅሜ የቻለውን ስጦታ መስጠት አለብኝ ብዬ በመወሰኔ ስጦታዬን ይዤ ወደ ቤቲ አመራሁ:: ወደ ቤቱ እንደምመጣ ያወቀ ይመስል ቤቱን አሰማምሮ ጠበቀኝ:: ጠረጴዛው በምግብና በተለያዩ መጠጦች በመሞላቱ ሌላ እንግዳ ይኖራል ብዬ ገመትኩ፡፡ እንደገባሁ እቅፎና ጉንጬን ስሞ ወንበር ስቦ አስቀመጠኝ:: ብቻችንን እንድንሆን ፈልጌ ብሄድም የዶክተር አድማሱ ዝግጅት ሲታይ ግን እንግዳ እንዳለበት ያመላክታል፡፡ ከዚህ ቀደም ሰው ሲጋብዝ አይቼው ስለማላውቅ፤ “እንግዶች ጋብዘሃል እንዴ?'' አልኩት፡፡ “አዎን ትልቅ እንግዳ፣ ከእንግዶች ሁሉ የላቀና የማከብረው'' አለኝ:: "ማንን?" አልኩት ግራ ተጋብቼ፡፡ "አንቺን” አለኝ ጉንጬን እየሳመ፡፡ ፍላጎቴ ይህ ስለነበር ደስ አለኝ፡፡ ጠረጴዛው ላይ _ ለስላሳና አልኮል መጠጦች እንዲሁም የተለያዩ የምግብ ዓይነቶች ተደርድረዋል:: በሕይወቴ ከአማረ ጋር ከጠጣሁት ቢራ ውጪ ሌላ አልኮል መጠጥ ጠጥቼ አላውቅም፡፡ ዶ/ር አድማሱ አልፎ አልፎ ወደ ቤቱ ስሄድ ቢጋብዘኝም፤ ያቺ የመጀመሪያዋ መጠጥ ያስከተለችውን መዘዝ ስለማውቅ፣ መልሴ ሁሌ "አልወድም ነበር፡፡ ታዲያ ዛሬ የተለያዩ የአልኮል መጠጦችንም ደርድሮ ሲጠብቀኝ ገረመኝ፡፡ ይሁን እንጂ ዛሬ ደስ

ስላለኝና ቀኑንም ለየት ላደርገው ስለፈለግሁ እንካንስ መጠጥ የሚያስደስት ከሆነና ካልገደለኝ መርዝም ቢቀርብልኝ እንደምጠጣው እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ የማላውቀውን የመጠጥ ዓይነት ሲያስመርጠኝም አልጠጣም የሚል ቃል ትንፍሽ አላልኩም:: “የቱ ይሻልሻል? ውስኪ፣ ቢራ ወይስ ወይን?” አስመረጠኝ፡፡ “አንተ የምትጠጣውን፣ ደስ ያለህን ቅዳልኝ' አልኩት፡፡ "እንግዲያውስ ውስኪ ይሻልሻል፡፡ ዛሬ የደስታ ቀን ስለሆነ በመጠኑ ብትጠጪ አይጎዳሽም ብሎ ቀዳልኝ፡፡ በሆዴም ቢጎዳስ፣ ለአንድ የደስታ ቀን ያልሆነ ጨጎራ ወይም ጉበት ይበጣጠስ አልኩ፡፡ (የሚጎዳውን ባላውቅም መቼም ከእነዚህ አንዱን ይሆናል ብዬ ጠርጥሬ)። ራት ከበላን በኋላ በስጦታ ወረቀት የተጠቀለለ ትንሽ ፓኮ አምጥቶ ስጠኝ፡፡ ክፈቺው ብሎ ስከፍተው ውስጡ የወርቅ ሀብልና ፖስት ካርድ ነበረበት:: ሀብሉን አንስቶ አንገቴ ላይ አጠለቀልኝና ፖስት ካርዱን "አንብቢው" አለኝ። “የእኔ በመሆንሽ ኮራሁብሽ፣ እንኳን ደስ አለን፡፡ ለእኔ የመጀመሪያዬና የመጨረሻዬ እንደምትሆኚ ቃል እገባለሁ" ይላል፡፡ ደነገጥኩ፡፡ የደነገጥኩት ስጦታ ልሰጠው መጥቼ ስለቀደመኝ ሳይሆን እኔ እሱ ለሚመኘው ጉዳይ መብቃቴ ላይ እርግጠኛ ስላልነበርኩ ነው፡፡ ከስጦታው በኋላ መጠጡን እየቀማመስን መዝናናቱን ተያያዝነው:: በመሳሪያ ብቻ የተቀነባበረ ሙዚቃ ተከፍቷል። ከቴፑ የሚወጣው ድምፅ እንኳንስ ህያው ሰብዓዊ ፍጥረትን ቀርቶ ዛፍንም ቢሆን ማንቀሳቀሱ አይቀርም ያሰኛል:: ዶክተር አድማሱ መለያየታችን ተሰምቶታል፡፡ ከወትሮው ለየት ባለና በሚያሳዝን ሁኔታ ስለመለያየታችን አስከፊነት እየደጋገመ ያወራኛል:: በመሀሉ ፈራ ተባ እያለ “እንደንስ አለኝ" “አልችልም" አልኩት “ምን መቻል ያስፈልጋል፣ ነይ እኔ አሳይሻለሁ" ብሎ እንድንደንስ እጁን ሰጠኝ፡፡ በቀዝቃዛ ሙዚቃ ታጅበን ቯልስ መደነስ ጀመርን:: ከአንገቱ ስር ውሽቅ ብዬና ደረቱ ላይ ተለጥፌ ስደንስ ሰውነታችን ብቻ ሳይሆን ልባችንም ሲደንስ ምቱ ይሰማ ጀመር:: የሰውነታችን ሙቀት ከእኔ ወደ እሱ ከእሱ ወደእኔ ሲመጣ በግልፅ ታወቀኝ::

ይቀጥላል...

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️
👍30
''ምነው?'' አላት ዝም አለች
ለቅሶ ከየት ይምጣ ዕንባ ጨርሳለች

    ''ንገሪኝ'' ብሎ ዓይኗን ሲያየው
        ቆይቷል ሰው ካወያየው።

          አቀፋት ዝም እንዳለች
          ለዘላለም ቀዝቅዛለች

             "ደና ነሽ" አላት
          እንደምንም እየጣረ

      አንድ ቃል አወጣች
                ''ደና ምን ነበረ?''

🔘ኤልያስ ሽታኹን🔘
🥰14👍112
ከቃላት ስብስብ ከመፃፍት ማህደር
ከሊቅ ፀሐፍቶች ከአዋቂዎች መንደር
የቅን ልብ መግለጫ አንቺን የሚመስልሽ ፈልጌ አስፈልጌ ቃል አጣሁ ሚገልፅሽ!።

አለኝ ብዙ መውደድ አለኝ እልፍ ፍቅር መግለፅ ስላልቻልኩኝ ፍፁም እንዳይልሽ ቅር
ብቻ እንድታውቂው እኔ ደስ እንዲለኝ
አንድ ነገር ልበል በልብሽ ፃፊልኝ፣

እ-ወ-ድ-ሻ-ለ-ው!!
9👍7
#ወፍ_በሆንኩኝ

ምንአለ ለዛሬ በሆንኩኝ እና ወፋ፤
በክንፌ በርሬ ግቢአችሁ ለማረፍ፤ ስትገቢ-ስትወጭ አንችን እያየሁኝ፤ ለሰከንድኦች እንኳን ምነዉ ወፍ በሆንኩኝ፤

ፍቅርሽን ሰርቄ ይዠው በበረርኩኝ፤
👍7
🍁🍁ዲያሪው 📝

ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
#ክፍል_10


የዶክተር አድማሱ ሁኔታ ዛሬ ለየት ያለ ቢሆንም እነን ግን አላስፈራኝም:: ብዙ ጊዜ ወደ ቤቱ ስመጣ በራስ የመተማመን ስሜት ይሰማኛል:: የማልፈልገውን ነገር ከፍቃዴ ውጪ እንደማያደርግ እርግጠኛ ነኝ:: ይህ ጠባዩ ነው እሱን አእማረ የተሻለ የሚያደርገው:: ከውስኪው እየተጎነጨሁ በሄድኩ ቁጥር የደስታ ስሜት እየተሰማኝ መጣ:: ለምደንሰው ዳንስም መጠንቀቅ ትቼአለሁ:: ሰውነቱ ላይ ተለጥፌ ስደንስ፣ እሱም አንገቴን ሲስመኝ ሰውነቴ ልክ ኮረንቲ እንደያዘው ነዘረኝ፡ “አልሚና እውነት እኔና አንቺ አሁን ልንለያይ ነው?" ይለኛል በየጨዋታው መሀል፡፡ ዝም ስለው ትንሽ ቆየት ይልና እርግጠኛ በሚመስል አኳኋን፤ “በፍፁም አንለያይም" ይላል:: እኔ ግን ዳግም እንደማንገናኝና ዛረ የመጨረሻችን እንደሚሆን እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ “አልሚ ዛሬ መቼም መሸ እንደማትይኝ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ለመሆኑ እናትሽን የት አስተኛሻቸው?" አለኝ በዳንሳችን መሃል። እኔ አልጋ ላይ ተኝታለች፡፡ እኔ ግን አንተን ሳልሰናበት መሄድ ስለሌለብኝና ላደረክልኝ ውለታ ተመጣጣኝ የሆነ ነገር ማድረግ ባልችልም ቢያንስ ያለችኝን ትንሽ ስጦታ ልሰጥህ ነው የመጣሁት” አልኩት፡፡ “የስጦታ ትንሽ የለውም፡፡ ደግሞስ ምን ውለታ ውዬልሽ ነው? እኔ ያደረኩት ነገር ቢኖር በተሳሳተ መንገድ ተጉዘሽ ተስጥኦሽን አላግባብ እንዳታጠፊው መንገዱን ማሳየት ብቻ ነው'' አለኝ፡፡ እኔም የእሱ ውለታ እንዲህ እንደቀላል ነገር የሚታይ እንዳልሆነና የሰውን ልጅ የሕይወት ጎዳና ከማስተካከል የበለጠ ክቡር ውለታ እንደሌለ ነገርኩት። ጭምቅ አድርጎ አቅፎ ዓይን ዓይኔን ወደ ታች እያየና ግንባሬን እየሳመ ምን እንደሚያደርግ ግራ እንደተጋባ ሰው ተመለከተኝ:: በመሀሉ እንደባነነ ሰው፤ “አልሚ ግን ስጦታው ምንድነው?''አለኝ፡፡ “ልሰጥህ የምችለው ትንሽ ነገር፤ ግን ክቡር የሆነውን ራሴን ነው ብዬ ልብሴን ማወላለቅ ጀመርኩ፡፡ ዶክተር አድማሱ የሀፍርት ሸማውን ስቀድለት ፊቱ በሙሉ በፈገግታ ብርሀን ተሞላ፡፡ እቅፍ አድርጎ እየሳመ ወደ መኝታ ቤት ተሸክሞ ወሰደኝ:: የተዘጋጀሁበት ጉዳይ ስለነበር በመደሰቱ ደስ አለኝ፡፡ ቢያንስ ዛሬ በእኔ ይደሰት:: የባከነ ገላን ለአንድ ቀን ብዙ ውለታ

ለዋለና አለኝታ ለነበረ ጓደኛ አሳልፎ መስጠት ትልቅ ስጦታ ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል አይደለም፣ ያውም ደስታው ለጋራ ለሆነ ነገር! ዶ/ር አድማሱ አልጋ ላይ አስተኝቶኝ ልብሱን አወላልቆ ራቁትን ላየው አፍረት ተሰማኝ፡፡ ለምን እንደሆን ባይገባኝም ፍቅረኛዬ ሳይሆን አስተማሪዬ መሆኑ ጎልቶ ስለታየኝ በእፍረት መልክ አንሶላውን ገልጩ ውስጥ ገባሁ፡፡ መብራቱንም ለማጥፋት እጄን ስዘረጋ፣ እጀን ወደ ቦታው እየመለስና አንሶላውን እየገፈፈ፤ "አልሚና ዛሬማ ይህንን የናፈቅሁትን ገላ እንዳላይ ሊሸፈንብኝና መብራት ሊጠፋብኝ አይገባም፡፡ ሲሆን ሲሆን ጠግቤ በደንብ እንዳየው ተራ መብራት ብቻ ሳይሆን ፓውዛ ሊበራበት በተገባ ነበር" እያለ ከላይ ጀምሮ ገላዬን እየሳመ ቀስ በቀስ ወደ ሆዴ መውረድ ጀመረ፡፡ እንደፈራሁት ሳይሆን ሰውነቴ ሰውነቱን ለመቀበል ተዘጋጀ፡፡ ዶክተር አድማሱ ግን እዚህ ላይም እንደሌላው ጊዜ ረጋ ያለ ስለነበርና ሳይቻኮል መሳምና መደባበሱን ብቻ ስለተያያዘው እዚሁ ላይ እንዳይቆም መፍራቴ አልቀረም፡፡ እኔ ሁሉም ነገር በቶሎ እንዲሆን ከመጠን በላይ የቸኮልኩ ቢሆንም እሱ ግን ስሞና ዳሶ ሊጠግበኝ አልቻለም፡፡ በስስት መልክ የማይስመው የሰውነቴ ክፍል አልነበረም፡፡ ይህ ደግሞ እኔን ይበልጥ አጣደፈኝ፡፡ እንደፈራሁት አልሆነም ስሞኝ እንደጠገበ ስጦታዬን ተቀበለኝ፡፡ ግን ነገሩ ሁሉ እንደቸኮልኩለት አልሆነም፡፡ ደስታው የእሱ እንጂ የጋራችን ሊሆን አልቻለም፡፡ ለእኔ እዳ የመክፈል ያህል ሲሆንብኝ ለእሱ ግን ሴት ገላ ውስጥ ሳይሆን ገነት የገባ ያህል ተሰምቶት ነበር:: በጣም የገረመኝ ነገር ቢኖር በየመሀሉ የማስበው ከፍቃዴ ውጪ ከአማረ ጋር ያሳለፍኩትን ያን በእጅጉ የተሻለውን ሌሊት ነበር፡፡ እሱ እንደዚያ እየጮኸ ደስታውን ሲገልፅ ሳይና ደስታውን ልጋራው አለመቻሌን ስገነዘብ፤ ያውቅብኛል ብዬ ስለፈራሁ የውሸት ድምፅ እያወጣሁና ውስጤ አድማሱን ሳይሆን አማረን እንዳቀፍኩ ያህል እንዲሰማው ዓይኔን ጨፍኜ ለማሳመን ሞከርኩ። ባይሳካልኝም በተወሰነ መልኩ ደስታውን የጋራ ለማድረግ ጣርኩ፡፡ ሁሉም ነገር ካለቀ በኋላ ግን ለምን እንዲህ ሊሆን ቻለ? ስል ራሴን ጠየቅሁ :: ለምን ገላዬን ብቻ ሰጠሁት? ለምን ሁለመናዬን ልሰጠው አልቻልኩም? ምነው ደስታን እየሰጠሁት ደስታን መቀበል ተሳነኝ? እሱም አድማሱም እንደአማረ ለወንድ ልጅ የተሰጠውን ጾታዊ ፀጋ የተላበስ ሆኖ ሳለ ለእኔ ግን ለምን ከእሱ አንሶ ታየኝ? የሚሉት ጥያቄዎች ተመላለሱብኝ እንጂ ትዝታው ከእኔ ጋር ሊቀር አልቻለም፡፡"

ሠራተኛዬ ጋሼ ብላ ስትጠራኝ ከገባሁበት የሐሳብ ባህር ተስፈንጥሬ ወጣሁ። የሚገርመው ነገር መንቃቴን እንጂ ሠራተኛዬ እንደቀሰቀሰችኝ አላወቅሁም ነበር፡፡ ከፊት ለፊቴ ቀጥ ብላ ቆማ በመገረም ዓይን ትኩር ብላ ትመለከተኛለች፡፡ “ምነው?'' አልኳት በንዴት፡፡ “ምነው ደህና አይደሉም እንዴ? እረባክዎትን ሀኪም ቤት ይሂዱ:: ደግሞም ከሥራ ከቀሩ ይኸው ዛሬ ሁለተኛ ቀኖት ነው፡፡ የሆኑ ሰውዬ ከመሥሪያ ቤትም ደውለው ደህንነቶን ጠይቀውኝ ነበር፡፡ እኔም የምመልሰው ሳጣ ዘመድ ጥየቃ ወደ ገጠር ሄደዋል አልኳቸው፡፡ እሳቸው ግን! "የምን ገጠር ነው የምታወሪው? የሱ ዘመዶች በሙሉ አዲስ አበባ አይደሉ እንዴ ያሉት?'' ብለው ጮሁብኝ፣ "አይ እንግዲያው በደንብ ሳልሰማ ቀርቼ ይሆናል፣ ምናልባት ጓደኛዪ ጋ ብለውኝ ይሆናል" ብዬ እየፈራሁ መለስኩላቸው፣ "ከደወሉ ወንድወሰን ደውልልኝ ብሎሃል ብዬ እንድነግሮትም ነግረውኛል" እያለች የባጥ የቆጡን መቀባጠሩን ተያያዘችው:: መቼም እሷና ሬዲዮ አንዴ ወሬ ከጀመሩ ካልዘጓቸው በስተቀር አያቆሙም፡፡ ነገር ግን ምን ታድርግ ሁኔታዬ እንኳን ለእሷ ለእኔም ግራ የሚያጋባ ሆኗል፡፡ ግራ መጋባቷን ሳይ አዘንኩላት:: አልፎ አልፎ አብረን በምናሳልፋቸው ሌሊቶች የምትፍለቀለቅባቸውና የምትደሰትባቸው ወቅቶች ነበሩ:: አሁን ግን ፍቅረኛዋ እሷን ዘንግቶ ሌሊቱን በፍቅር ሳይሆን በማያቋርጥ ንባብና ትካዜ ሲያሳልፈው ስታይ እንዴት ግራ አትጋባ፣ እንዴትስ ጤነኛ ነው ብላ ታስብ፡፡ እርግጥ ነው ጤነኛ አልነበርኩም፡፡ ራሴን የሚያዞር ማለቂያ የሌለው ታሪክ ከእንቅልፍ ማጣት ጋር ተደምሮ ጩህ ጩህ ሊያሰኘኝ እየቃጣው ነው:: በዚህ ላይ ደግሞ የማነበው የሚያጓጓና የሚያስደስት ታሪክ ሳይሆን የሀዘንና የመርዶ ዜና ነበር፡፡ እርግጥ ከዚህ በላይ ምን መርዶ ይኖራል? “እጅግ ለምትወደው" ፍቅረኛዋ ለአንድ ቀን ሳትወድ በግድ በሰጠችው ገላ የምትፀፀት ሴት፣ ዛሬ ደግሞ በፍላጎቷ ለማትወደው ሰው የምወደውንና የማፈቅረውን ገላ በስጦታ ገፀ በረከት ካቀረበች በኋላ "ደስታ አጣሁበት" እያለች ስትደሰኩርና እኔን ብቻ ገላዋ እንደናፈቀ አድርጋ ስታወራ ከመስማት የበለጠ ምን የሚያናድድ መርዶ አለ:: ግን ዜናው የመርዶ መሆኑን ባውቅም ልተወው
👍313👏2
አቅም አልነበረኝምና ሳልወድ በግድ ንባቤን ለመቀጠል ወሰንኩ:: መጨረሻውን ማወቅ ስለነበረብኝ ዲያሪውን መሬት ላይ ወድቆ አገኘሁት:: የተኛሁት ልብሴንም ሆነ ጫማዬን ሳላወልቅ ነበር። ያነበብኩትን የመጨረሻ ታሪክል ላስታውሰው ባልፈልግም ራስ ምታት ጥሎብኝ እንደሄደ ግን አልረሳሁትም:: የከሀዲዋ ፍቅረኛዬ የክህደት ታሪክ አሁን የተፈፀመ ያህል ሊያሳብደኝ ደርሷል:: ንባቤን ትቼ ወደ ሥራ መሄድ እንዳለብኝ ቢሰማኝም ጨክኜ መሄድ ግን አልቻልኩም :: ሥራ ልግባ ብልም ቀኑን በሙሉ ይህንኑ ሳብሰለስል እንጂ ሥራ ስርቼ እንደማልመጣ እርግጠኛ ነበርኩ።

ሰኔ 26 ቀን 1978 ዓ.ም

የትምህርት ቤቱን ግቢ ለቅቂ የምወጣበት ቀን በመድረሱ የተደበላለቀ ስሜት ወረረኝ። በአንድ በኩል በደስታ ያልተጠናቀቀው ታሪኬ የሚጠናቀቅበት ቀን በመሆኑና እነዚያን ባየኋቸው ቁጥር አማረን የሚያስታውሱኝን የፍቅር መንገዶችና ለምለም ሳሮች ዳግም ላላያቸው የምሰናበትበት ቀን በመሆኑ ደስተኛ ነበርኩ፡፡ ነገር ግን ምንም እንኳን እያፈቀረኝ ላፈቅረው ባልችልም የምወደውን ዶ/ር አድማሱን ጥዬው ስለምሄድና ወደ ብቸኝነት ባህር ተመልሼ እንደምገባ ሳስታውስ ደግሞ ሀዘን ይሰፍንብኛል፡፡ ግን ምን ላድርግ? ልወደው ሞከርኩ፣ ያለኝንም ልሰጠው ፈቀድኩ፣ ግን አልሆነም :: እኔ ለእሱ፣ እሱ ለእኔ የተፈጠርን አልነበርንም:: ስለዚህ ዳግም ዓይኑን ሳላይ ግቢውን ለቅቄ ለመውጣት ተጣደፍኩ፡፡ ይሁን እንጂ ነገሮች ሁሉ እንዳሰብኳቸው በቶሎ የሚቋጩ አልነበሩም:: ዩንቨርስቲው ያመጣሁትን ውጤት መሰረት በማድረግ እዚያው ቀርቼ ለድህረ ምረቃ (ማስትሬት) እንድማርና በትርፍ ጊዜዬ በረዳት ሌክቸረርነት እንድሰራ ጠየቀኝ:: እኔ ግን ይህንን ለመቀበል ዝግጁ ባልሆንም ዶ/ር አድማሱ ግን በዚህ ዕድል መጠቀም እንዳለብኝ ይገፋፋኝ ጀመር:: እየደጋገመም ሁሌ የሚለውን፣ችግሮችን በመጋፈጥ እንጂ በመሸሽ ማምለጥ እንደማይቻል ይነግረኛል:: የሚሸሽን ማባረር ይቀላል፤ ነገር ግን ደፍሮና ዓይኑን አፍጦ የመጣን ችግር ወይም ተመሳሳይ መሰናክል ጀግና ካልሆኑ በስተቀር መጋፈጥ ያስፈራል:: ችግርም ፈሪን ይደፍራል፤ የሚጋፈጠውን ግን ይሸሻል፡፡ ስለዚህ ገና ለገና ያለፈውን አስቸጋሪ ጊዜ እያስታወስኩ ከፊቴ የመጣውን ብሩህ ዕድል እንዳላበላሽው እየደጋገመ ይመክረኛል፡፡ ለሚመጣው ችግር ከጎኔ እንደማይለይ እየገለፀ እዚሁ እንድቀር ይጎተጉተኝ ጀመር፡፡ ምንም እንኳን እዚህ መቆየት እንደማልፈልግ ብነግረውም ሁለት ዓመታትን ታግሼ የማስትሬት ዲግሪዬን ከያዝኩ በኋላ ግቢውን ለቅቄ ልሄድ እንደምችል እየነገረ ሊያግባባኝ ሞከረ።

ከብዙ ማሰብ፣ ማውጣትና ማውረድ በኋላ ግን ከዚህ ወጥቼ የማሳልፈውን ባዶ ህይወት በማሰብ፣ እንዲሁም በዶ/ር አድማሱና በጓደኞች ውትወታና ግፊት የተነሳ ሐሳቤን ለውጬ ትምህርቴን ለመቀጠል ወሰንኩ:: እርግጥ ነው ራሴን በትምህርት መጥመዱ ከጭንቀት ለመውጣት የተሻለ መንገድ መሆኑን ባውቅም መራቅ የፈለኩት ግን ግቢውን ነበር። በመጨረሻ ግን ዶ/ር አድማሱ ካለ ብቸኛ እንደማልሆን ገባኝ፡፡ ከትምህርትና ከሥራR ጋር ተያይዞም አንዳንድ የማሟላቸው ቅድመ ሁኔታዎች በመኖራቸው ከእናተ ጋር ወደ ቤቴ መመለስ አልቻልኩም። ያለኝ አማራጭ እናቴን ከእኛ አካባቢ ከመጣች ልጅ ጋር አያይዞ መላክ ስለነበር ከዶ/ር አድማሱ ገንዘብ ወሰድኩና እንደምመጣ ነግሬ ተሰናበትኳት፡፡ ሳልወድ በግድ በዚያ በማልወደው ግቢ ውስጥ ዳግመኛ መኖርና መማር ጀመርኩ፡፡ ከትምህርቴም ጎን ለጎን የረዳት ሌክቸረርነት ሥራዬንም ተያያዝኩት:: ሁለቱን ግራና ቀኝ ማካሄድ ከባድ ቢሆንም እንደፈለኩት ሙሉ ጊዜዬንና ትኩረቴን የሚወስድ ስለነበር ለጭንቀት የማጠፋውን ጊዜ አስወግዶልኛል፣ በዚህም ደስተኛ ሆንኩ:: በረዳት ሌክቸረርነት የምሰራው ተማሪዎችን በሙከራ ሥራዎች ላይ ማገዝ ስለነበር የሚከብድ ሥራም አልነበረም። ከዚህ በላይ ደግሞ ብቸኝነቴን ለማባረር ስል ከዶ/ር አድማሱ ጋር የነበረኝን ግንኙነት ይበልጥ አጠናከርኩት፡፡ ከትምህርትና ከሥራ መልስ በኋላ አዳሬ በተሰጠኝ ቤት ውስጥ ሳይሆን ከዶ/ር አድማሱ ጋር ሆነ:: ሊያገባኝ እንደሚፈልግ እየደጋገመ ቢነግረኝም መጀመሪያ ትምህርቴን መጨረስ እንዳለብኝ ስለነገርኩትና እሱም ስለአመነበት ሊያስገድደኝ አልፈለገም፡፡ ለስሙ ነው እንጂ አዳሬ ከእሱው ቤት በመሆኑ አኳኋናችን ሁሉ ትዳር እንደመያዝ ያህል ነው:: እወቁልኝ ባይባልም የትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ የሚያየን ልክ እንደባልና ሚስት ነበር: በምረቃው ዕለት የተጀመረው የፍቅር ጨዋታም የዘወትር ተግባር እየሆነ መጥቷል፡፡ አንዳንዴ ይህንን ሁኔታ ሳስብ ሳትወድ በግድ ወደአላሰበችው ወጥመድ ውስጥ የገባች ፍጡር የሆንኩ ያህል ይሰማኛል:: በዚህ ሁኔታ ውስጥ እያለሁ ይበልጥ የሚገርመኝ ነገር ቢኖር ራሴን አሳልፌ ልሰጠው ዝግጁ ብሆንም የሚወደኝን ዶ/ር አድማሱን ግን መውደድ አለመቻሌ ነው:: አንዳንዴም ፍቅር የሚይዘው አንዴ ብቻ ሊሆን ይችላል ብዬ ስለማስብ ከእንግዲህ ወዲህ ወንድ አልወድ ይሆን? እያልኩ እሰጋለሁ፡፡ መሥጋቴ ግን ተገቢ ይመስለኛል፣ በፍቅርና ከፍቅር ውጪ ያለውን ሕይወቴን ሳወዳደር ፍቅር የሕይወት ቅመም ነው የሚባለው እውነት

መሆኑን አረጋግጫለሁና:: ታዲያ ወጥ ያለ ቅመም እንደማይጣፍጥ ሁሉ ሕይወት ያለ ፍቅር ባዶ ናትና መፍራቴ የሚደንቅ አልነበረም:: ዶ/ር አድማሱ ለእኔ ያለው ፍቅር ወደር የለውም። ከሥራ እንደወጣ የሚመጣው በቀጥታ ወደ ቤት ነው:: ጥናት እያስጠናኝ እንኳን በየመሀሉ ጉንጩን እየሳመ እየደጋገመ እወድሻለሁ ይለኛል:: ደግነቱ ፍቅሩ የእኔን ጥናት የሚረብሽ አልነበረም:: ዘወትር እንደሚወደኝና ትምህርቴን ስጨርስ ተጋብተን ልጅ ወልደን በደስታ እንደምንኖር! እኔም ትምህርቴን ሳጠናቅቅ እሱ ሥራ ለውጦ አዲስ አበባ እንደሚገባ፣ እዚያም እኔና እሱ የተሻለ ኑሮ እንደምንኖርና ከዚህ ከማልወደው ግቢም በዚህ መልኩ እንደምገላገል ይነግረኛል፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ የራሱን ቤት የሠራ በመሆኑ እዚያ እንደገባም መኪና እንደሚገዛና አንደላቆ እንደሚያኖረኝ እየደጋገመ ይነግረኛል፡፡ እኔ ግን ለዚህ ሁሉ መልስ አልነበረኝም:: ለእኔ ደስታ ማለት መኪና፣ ቤት፣ ወይም ሌላ ሊሆን አይችልም፣ የእኔ ደስታ ከአማረ ጋር አክትሟል።" ዲያሪውን እያነበብኩ አንዳንዴ ሳቄ ይመጣል፡፡ ሌላ ግዜ ደግሞ በውኔ ሳይሆን በህልሜ ያማየው ይመስለኛል:: አልማዝ በዲያሪዋ ላይ መዋሸትዋን ቀጥላለች፣ እኔን የጨነቀኝ ግን ሌላ ሳይሆን ይህቺ ሰው በህይወት ትኖር ይሆን? ወይስ እንደዋሸች ሞታ ይሆን? የሚለው ነው:: ብዙ ውሸቶችን ባነበብኩ ቁጥር በዲያሪው ውስጥ መሞቷን ባነብ እንኳ ሌላ ውሸት ነው ብዬ አስብ እንደሆን እንጂ፣ በእውነትም ሞታለች ብዬ ለመቀበል ሳያስቸግረኝ አይቀርም። አባቴ የሚዋሽ ሰው አይወድም ነበር፡፡ ምንም ያህል መጥፎ ሥራ ብሰራ ያን ድርጊት መፈፀሜን ካመንኩ ንክች አያደርገኝም፡፡ አንዴ ትዝ ይለኛል አንድ አዲስ ቤት እየሰራ ስለነበር እኔም ከአናጢውና ከግንበኛው ጋር አብሬ ስሰራ እውል ነበር፡፡ የሚያወሩት ወሬ ከሴት ጋር ስላሳለፉት የፍቅር ጨዋወታ ስለነበር ወሬያቸውን መስማት ያስደስተኝ ነበር፡፡ አንድ ቀን ታዲያ እዚሁ አዲስ ቤት ውስጥ ከጓደኞቼ ጋር ሆኜ በሳንቲም "ዘውድ “ጎፈር" እያልን ድብድብ ስንጫወት አባቴ ይመጣል:: ወደ ቤት ስንገባ አይቶን ስለነበር ቢጣራና በሩን ለመክፈት ቢሞክርም መልስ ስላጣ በመስኮት ብቅ ብሎ፤ “እናንተ! ብላችሁ ብላችሁ ቁማር ትጫወቱ ጀመር?" ብሎ ሲጮህብን፣ ያታለልኩት መስሎኝ፤ “አይ አባዬ ቁማር እየተጫወትን አይደለም፣
👍213