🍁🍁ዲያሪው 📝
ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
#ክፍል_10
ለመቀንጠስ እጁን ሲያሾል ነበር ያቆምኩት:: ንባቤም ቀጠልኩ። የኔቶ ቀባጣሪም መቀባጠሯን ቀጠለች፣ "ጊዜ በጊዜ እየተተካ በሄደ ቁጥር እኔም ንዴቴ ቀስ በቀስ እየበረደ መጣ። እርግጥ በደሱ ሊረሳ የሚችል አልነበረም። ማንኛውም የሰው ፍጡር የህይወቴ ጎዳና ይህ ይሆናል፣ ሀይወቴንም በዚህ መንገድ፣ እንዲህ አድርጊ! እመራዋለሁ ብሎ የወጠነው ሁሉ ተመሰቃቅሎ ከፊት ለፊቱ የሚያየውና ሊጓዝበት ያሰበው ለስለሳና ደልዳላ መንገድ በእሾህና በጋሬጣ ታጥሮ መውጪያውና መግቢያው ወደማይለይ አባጣና ጎርባጣ መንገድ በቅጽበት ሲለወጥበትና ተስፋ ለተስፋቢስነት ቦታ ሲለቅ ሲያይ መበሳጨት እንዴት ይበዛበታል:: የኔ ሁኔታ ከዚህ የተለየ አልነበረም:: ከአማረ ጋር ሆኜ በደስታና በፍቅር አሳልፈዋለሁ ያልኩት ህይወት የማይጨበጥ ህልም ሆኖ ሲቀር የምመካበትና አንድ አለኝ የምለው ሰው ሲከዳኝና በአንድ ጊዜ ተስፋዬ ተሟጦ የወደፊት ህይወቴ ምን ሊሆን እንደሚችል ልገምት በማልችልበት ሁኔታ ላይ ሆኜ እያለሁ ደስታ ይኖረኛል ብሎ መገመት የዋህነት ነው:: ይሁን እንጂ ዶ/ር አድማሱ በጭንቅት ቀን ከእግዜር የተላከ መልአክ ተመስሎ ባጠገቤ በመገኘቱ ብዙውን ነገር ቀስ በቀስ ባልረሳው እንኳን ለመርሳት እንድሞክር ረድቶኛል:: አብዛኛውን ከትምህርት ውጪ ያለውን ጊዜዬን የማሳልፈው ከእሱ ጋር ነበር፡፡ ብዙውን ጊዜ በትምህርቴ እንድጠነክርና ሁሉንም ነገር እንደ ተራ ነገር እንድረሳው ይመክረኛል፡፡ እኔም አብዛኛውን ጊዜ የግቢውን ወሬ ሳልፈራና ለማንም ቁብ ሳልሰጥ እሱ ቤት እያመሸሁ ጥናቴን ተያያዝኩት፡፡ የሚቸግረኝን እየረዳኝ ከጎኔ ሳይለይ የሚያፅናናኝም እሱ ብቻ ነበር፡፡ ከእሱ ጋር ያለኝ ግንኙነት እየጠነከረ የመሄዱን ያህል የትምህርት ቤት ጎደኞቼ ደግሞ ይበልጥ በጥላቻ ይመለከቱኝ ጀመር። አብዛኛው ተማሪ ከዶ/ር አድማሱ ጋር የነበረኝን ግንኙነት አማረን በጥቅም _ ለውጬ የፈጠርኩት ግንኙነት አድርጎ የተሳሳተ ግንዛቤ ፈጥሮ ስለነበር ቢጠሉኝም በእነሱ አልፈረድኩም:: በተለይ ጓደኞቹ እኔን ጠይቀው በመረዳት ፈንታ እኔን አኩርፈው ወሬውን በመሰላቸው መንገድ ያናፍሱት ስለነበር ተማሪዎቹ የሰሙትን የተሳሳተ ወሬ ሰምተው ቢጠሉኝ አያስገርምም፡፡ ከሃዲዋ እኔ ላልሆን ከሀዲው አማረ መሆኑንና ከዶክተር አድማሱም ጋር ያለኝ ግንኝነት የወንድምና የእህትነት ዓይነት እንደሆነ ለጓደኞቼ ብናገርም የሚያምኑኝ አልነበሩም። ስለዚህም እኔ ይህንኑ ተንትኜ ለማስረዳት እቅሙም ሆነ ችሎታው ስላልነበረኝ እንደመፍትሄ የወሰድኩት ለማንም ሳልጨነቅ ይበልጥ ከተማሪዎች በመራቅ አብዛኛውን ጊዜዬን ከዶክተር አድማሱ ጋር ማሳለፍ ብቻ ነበር።
ጥር 30 ቀን 1978 ዓ.ም
ተሾመ ለእኔ ያለው የፍቅር ስሜት የእብደት እንጂ የጤንነት ነው ማለት ያዳግታል፡፡ አማረ ግቢ ውስጥ በነበረበት ወቅት ምን ያህል እንደምንዋደድና በዚህም የተነሳ ከእሱ ጋር መደባደቡን እያወቀ፣ ከዚህም አልፎ ተርፎ እኔ ለእሱ ፍቅር እንደሌለኝ ደግሜና ደጋግሜ ብነግረውም በፍጹም ሊተወኝ አልቻለም፡፡ እንዲያውም ቀስ በቀስ በሰላማዊ መንገድ እንደማያገኘኝ ስለተረዳ ማስፈራራትና መማታቱን ቀጠለ፡፡ ሌላ የማገባ ከሆነ እኔን፣ የማገባውን ሰውና የራሱን ህይወት ጭምር እንደሚያጠፋ መዛት የዘወትር ተግባሩ ሆነ፡፡ ይሁን እንጂ በወቅቱ ይህንን ለአማረ መናገር ማለት ተጋደሉ ማለት ስለመሰለኝ ለመናገር አልፈለኩም ነበር። አማረ ግቢውን ከለቀቀ በኋላም ተሾመ ይህንኑ ድርጊቱን አጠናክሮ በመቀጠሉ ለመክሰስ እንደወሰንኩ ለኤልሳ ነገርኳት፡፡ ኤልሳ ግን ከከሰስኩት ከዩንቨርስቲ _ ስለሚያባርሩት እሷ እንዲያርፍ እንደምትነግረውና ነገር ግን ምክሯን ሰምቶ ካላረፈ ለወላጆቹ ደውላ እንደምትነግር ቃል ስለገባችልኝ ክሱን ተውኩት፡፡ የነገርኳትን ነግሬዋለሁ ካለች በኋላ ለተወሰነ ጊዜ መተናኮሉን ቢያቆምም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን ዶ/ር አድማሱ ቤት አዘውትሬ መሄዴን በማወቁ ተመልሶ አገረሸበት፡፡ ኤልሳ ይህንኑ ጉዳይ ለወላጆቹ ነግሬአለሁ ትበል እንጂ እሱ ግን በፍፁም ሊታገስ አልቻለም፡፡ በተለይ ሁሌ የሚገርመኝ ነገር ቢኖር ማታ ማታ እየጠበቀ የሚያስፈራራኝና የሚመታኝ ባጋጣሚ ከኤልሳ ተለይቼ በምሄድበት ጊዜ ስለነበር ሆን ብላ ከእሱ ጋር እየተነጋገረች ምክንያት ፈጥራ ከእኔ የምትለይ እየመሰለኝ መጣ፡፡ በወንድምነት ይሁን ወይም በጾታዊ ፍቅር መሆኑ በግልጽ ባይገባኝም፤ ኤልሳ እንደምትወደው ግን አውቃለሁ፡፡ እሱ ግን ለእሷ አንዳችም ፍቅር የለውም.፡፡ እኔ እንዲያውም አንዳንዴ ብገላገል በማለት እስኪ እንደምትወጂው ልንገረው ካልኳት፤ ይህንን ከነገርኩት እንደምንጣላ ከመናገር ውጪ እሱን የእሷ ለማድረግ የምታደርገው ጥረት ግን የለም፡፡ ተሾመ ከእኔ ጋር የሚፈጠረውን አምባጓሮ እያየች ምንም የቅናት ስሜት ስለማላይባት ሆን ብላ እኔና እሱን ለማፋቀር የምታደርገው ምክንያት እንጂ ከእሱ ጋር ፍቅር የላትም ብዬ እንድጠረጥር አደረገኝ፡፡ በመጨረሻም ማስቸገሩ ሲበዛብኝ ሁኔታውን ለዶ/ር አድማሱ ነገርኩት፤ ልከሰው ስላሰብኩም ምን እንደሚመክረኝ ጠየቅሁት፡፡ እሱ ግን መፍትሄ እንድሚፈልግልኝ ቃል ገብቶ እንዳልከሰው ከለከለኝ፡፡ ዛሬ የመጀመሪያውን ሴሚስተር _ ፈተና ጨርስን ውጤት ተለጥፎ በነበረበት ምሽት ወደ ራት ስሄድ ተሾመን እንደተለመደው ከራት ስመለስ ብቻውን አገኘሁት፡፡ ገና እንደደረሰ በጥፊ ካጮለኝ በኋላ፤
"አንቺንም፣ ያን ዶክተርሽንም ካልደፋኂችሁ እኔ ተሾመ አይደለሁም፡ ብሎ ዝቶብኝ ሄደ። አጥፊው በላይ ፊቱ ላይ የነበረውን ንዴቱን ሳይ ክፉኛ ደነገጥኩ፣ ተናደድኩም፡፡ ወዲያው ዶ/ር አድማሱ ጋ ሄድኩና፤ "አንተ ነህ እንዲህ እምትጫወትብኝ፣ ልክሰስ ስልህ እኔ አስታግሰዋለሁ እያልክ ልታስገድለኝ ነው፡፡ ከአሁን ወዲያ የፈለከውን ብትል አላምንህም፣ ቢፈልጉ እንኳን ከዩንቨርስቲ ማባረር _ ቀርቶ እንጦሮጦስም ይክተቱት እንጂ እኔ እንደሆነ ነገ መክሰሴ አይቀርም" እያልኩ ጮህኩበት፡፡ እሱ ግን በተራጋጋ መንፈስ በጥፊ የቀላውን ፊቴን በእጁ እያሻሸ፤ “በቃ ተይ አትናደጂ፣ ከአሁን በኋላ መክሰስ ትችያለሽ፣ እኔ አያገባኝም፡፡ እኔ ይሰማኛል በማለት አንድ ሁለት ጊዜ መካክሬው ነበር፡፡ እሱ ግን ብመክረውም ተመልሶ እዛው ስለሆነ ከአሁን በኋላ አያገባኝም፤ ነገውኑ ክሰሺው" አለኝ፡፡ ጠዋት እሱን ለመክሰስ ወስኜ ከቤት ብወጣም፣ ኤልሳ ቁርስ እየበላን ሳለ ተሾመ በዶ/ር አድማሱ ሁለት ኮርሶች ኤፍ (F) ማግኘቱንና ከዩንቨርስቲ መባረሩን ነገረችኝ፡፡ ይህንን ስሰማ በጣም ደነገጥኩ፡፡ እንደተለያየን በጥድፊያ ወደ ዶ/ር አድማሱ ቢሮ አመራሁ፡፡ እንደገባሁም በሩን ከኋላዬ ዘግቼ! "ዶ/ር፣ ለእኔ ብለህ ነው እንዴ ለተሾመ ኤፍ (F) ሰጥተህ ከትምህርት ቤት እንዲባረር ያደረከው" ብዬ አፈጠጥኩበት?' እሱ ግን ምንም እንደማያውቅ በሚመስል ሁኔታ፤ "ተሾመ ኤፍ አምጥቶ ተባረረ ነው የምትዪኝ? እኔ የሰማሁት አሁን ገና ከአንቺ አፍ ነው፡፡ ለመሆኑ በምን ትምህርት ነው ኤፍ ያመጣው?" ብሎ እኔኑ መልሶ ጠየቀኝ፡ "አንተ በምትሰጣቸው ሁለት ትምህርቶች ነው ወድቆ የተባረረው። ይህንን አታውቅም ማለት ነው?' አልኩት በንዴት፡፡ "ማወቅ አላውቅም፡፡ ነገር ግን ልጁ ሰነፍ መሆኑን አውቃለሁ፡፡ እሱ ትምህርቱን ትቶ አንቺን አፈቀርኩ እያለ ሲሟዘዝ ስለሚውል ቢወድቅ የሚደንቅ አይደለም፡፡ እርግጥ በእኔ ትምህርት ኤፍ ያገኙ ተማሪዎች አሉ፡፡ ይሁን እንጂ እኔ ሁሌ ፈተና ሳርም እንዳላዳላ (Bias እንዳልሆን) በማለት ስም ስለማላይ ኤፍ ያገኘው እሱ ይሁን ሌላ ሰው የማውቀው
ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
#ክፍል_10
ለመቀንጠስ እጁን ሲያሾል ነበር ያቆምኩት:: ንባቤም ቀጠልኩ። የኔቶ ቀባጣሪም መቀባጠሯን ቀጠለች፣ "ጊዜ በጊዜ እየተተካ በሄደ ቁጥር እኔም ንዴቴ ቀስ በቀስ እየበረደ መጣ። እርግጥ በደሱ ሊረሳ የሚችል አልነበረም። ማንኛውም የሰው ፍጡር የህይወቴ ጎዳና ይህ ይሆናል፣ ሀይወቴንም በዚህ መንገድ፣ እንዲህ አድርጊ! እመራዋለሁ ብሎ የወጠነው ሁሉ ተመሰቃቅሎ ከፊት ለፊቱ የሚያየውና ሊጓዝበት ያሰበው ለስለሳና ደልዳላ መንገድ በእሾህና በጋሬጣ ታጥሮ መውጪያውና መግቢያው ወደማይለይ አባጣና ጎርባጣ መንገድ በቅጽበት ሲለወጥበትና ተስፋ ለተስፋቢስነት ቦታ ሲለቅ ሲያይ መበሳጨት እንዴት ይበዛበታል:: የኔ ሁኔታ ከዚህ የተለየ አልነበረም:: ከአማረ ጋር ሆኜ በደስታና በፍቅር አሳልፈዋለሁ ያልኩት ህይወት የማይጨበጥ ህልም ሆኖ ሲቀር የምመካበትና አንድ አለኝ የምለው ሰው ሲከዳኝና በአንድ ጊዜ ተስፋዬ ተሟጦ የወደፊት ህይወቴ ምን ሊሆን እንደሚችል ልገምት በማልችልበት ሁኔታ ላይ ሆኜ እያለሁ ደስታ ይኖረኛል ብሎ መገመት የዋህነት ነው:: ይሁን እንጂ ዶ/ር አድማሱ በጭንቅት ቀን ከእግዜር የተላከ መልአክ ተመስሎ ባጠገቤ በመገኘቱ ብዙውን ነገር ቀስ በቀስ ባልረሳው እንኳን ለመርሳት እንድሞክር ረድቶኛል:: አብዛኛውን ከትምህርት ውጪ ያለውን ጊዜዬን የማሳልፈው ከእሱ ጋር ነበር፡፡ ብዙውን ጊዜ በትምህርቴ እንድጠነክርና ሁሉንም ነገር እንደ ተራ ነገር እንድረሳው ይመክረኛል፡፡ እኔም አብዛኛውን ጊዜ የግቢውን ወሬ ሳልፈራና ለማንም ቁብ ሳልሰጥ እሱ ቤት እያመሸሁ ጥናቴን ተያያዝኩት፡፡ የሚቸግረኝን እየረዳኝ ከጎኔ ሳይለይ የሚያፅናናኝም እሱ ብቻ ነበር፡፡ ከእሱ ጋር ያለኝ ግንኙነት እየጠነከረ የመሄዱን ያህል የትምህርት ቤት ጎደኞቼ ደግሞ ይበልጥ በጥላቻ ይመለከቱኝ ጀመር። አብዛኛው ተማሪ ከዶ/ር አድማሱ ጋር የነበረኝን ግንኙነት አማረን በጥቅም _ ለውጬ የፈጠርኩት ግንኙነት አድርጎ የተሳሳተ ግንዛቤ ፈጥሮ ስለነበር ቢጠሉኝም በእነሱ አልፈረድኩም:: በተለይ ጓደኞቹ እኔን ጠይቀው በመረዳት ፈንታ እኔን አኩርፈው ወሬውን በመሰላቸው መንገድ ያናፍሱት ስለነበር ተማሪዎቹ የሰሙትን የተሳሳተ ወሬ ሰምተው ቢጠሉኝ አያስገርምም፡፡ ከሃዲዋ እኔ ላልሆን ከሀዲው አማረ መሆኑንና ከዶክተር አድማሱም ጋር ያለኝ ግንኝነት የወንድምና የእህትነት ዓይነት እንደሆነ ለጓደኞቼ ብናገርም የሚያምኑኝ አልነበሩም። ስለዚህም እኔ ይህንኑ ተንትኜ ለማስረዳት እቅሙም ሆነ ችሎታው ስላልነበረኝ እንደመፍትሄ የወሰድኩት ለማንም ሳልጨነቅ ይበልጥ ከተማሪዎች በመራቅ አብዛኛውን ጊዜዬን ከዶክተር አድማሱ ጋር ማሳለፍ ብቻ ነበር።
ጥር 30 ቀን 1978 ዓ.ም
ተሾመ ለእኔ ያለው የፍቅር ስሜት የእብደት እንጂ የጤንነት ነው ማለት ያዳግታል፡፡ አማረ ግቢ ውስጥ በነበረበት ወቅት ምን ያህል እንደምንዋደድና በዚህም የተነሳ ከእሱ ጋር መደባደቡን እያወቀ፣ ከዚህም አልፎ ተርፎ እኔ ለእሱ ፍቅር እንደሌለኝ ደግሜና ደጋግሜ ብነግረውም በፍጹም ሊተወኝ አልቻለም፡፡ እንዲያውም ቀስ በቀስ በሰላማዊ መንገድ እንደማያገኘኝ ስለተረዳ ማስፈራራትና መማታቱን ቀጠለ፡፡ ሌላ የማገባ ከሆነ እኔን፣ የማገባውን ሰውና የራሱን ህይወት ጭምር እንደሚያጠፋ መዛት የዘወትር ተግባሩ ሆነ፡፡ ይሁን እንጂ በወቅቱ ይህንን ለአማረ መናገር ማለት ተጋደሉ ማለት ስለመሰለኝ ለመናገር አልፈለኩም ነበር። አማረ ግቢውን ከለቀቀ በኋላም ተሾመ ይህንኑ ድርጊቱን አጠናክሮ በመቀጠሉ ለመክሰስ እንደወሰንኩ ለኤልሳ ነገርኳት፡፡ ኤልሳ ግን ከከሰስኩት ከዩንቨርስቲ _ ስለሚያባርሩት እሷ እንዲያርፍ እንደምትነግረውና ነገር ግን ምክሯን ሰምቶ ካላረፈ ለወላጆቹ ደውላ እንደምትነግር ቃል ስለገባችልኝ ክሱን ተውኩት፡፡ የነገርኳትን ነግሬዋለሁ ካለች በኋላ ለተወሰነ ጊዜ መተናኮሉን ቢያቆምም ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን ዶ/ር አድማሱ ቤት አዘውትሬ መሄዴን በማወቁ ተመልሶ አገረሸበት፡፡ ኤልሳ ይህንኑ ጉዳይ ለወላጆቹ ነግሬአለሁ ትበል እንጂ እሱ ግን በፍፁም ሊታገስ አልቻለም፡፡ በተለይ ሁሌ የሚገርመኝ ነገር ቢኖር ማታ ማታ እየጠበቀ የሚያስፈራራኝና የሚመታኝ ባጋጣሚ ከኤልሳ ተለይቼ በምሄድበት ጊዜ ስለነበር ሆን ብላ ከእሱ ጋር እየተነጋገረች ምክንያት ፈጥራ ከእኔ የምትለይ እየመሰለኝ መጣ፡፡ በወንድምነት ይሁን ወይም በጾታዊ ፍቅር መሆኑ በግልጽ ባይገባኝም፤ ኤልሳ እንደምትወደው ግን አውቃለሁ፡፡ እሱ ግን ለእሷ አንዳችም ፍቅር የለውም.፡፡ እኔ እንዲያውም አንዳንዴ ብገላገል በማለት እስኪ እንደምትወጂው ልንገረው ካልኳት፤ ይህንን ከነገርኩት እንደምንጣላ ከመናገር ውጪ እሱን የእሷ ለማድረግ የምታደርገው ጥረት ግን የለም፡፡ ተሾመ ከእኔ ጋር የሚፈጠረውን አምባጓሮ እያየች ምንም የቅናት ስሜት ስለማላይባት ሆን ብላ እኔና እሱን ለማፋቀር የምታደርገው ምክንያት እንጂ ከእሱ ጋር ፍቅር የላትም ብዬ እንድጠረጥር አደረገኝ፡፡ በመጨረሻም ማስቸገሩ ሲበዛብኝ ሁኔታውን ለዶ/ር አድማሱ ነገርኩት፤ ልከሰው ስላሰብኩም ምን እንደሚመክረኝ ጠየቅሁት፡፡ እሱ ግን መፍትሄ እንድሚፈልግልኝ ቃል ገብቶ እንዳልከሰው ከለከለኝ፡፡ ዛሬ የመጀመሪያውን ሴሚስተር _ ፈተና ጨርስን ውጤት ተለጥፎ በነበረበት ምሽት ወደ ራት ስሄድ ተሾመን እንደተለመደው ከራት ስመለስ ብቻውን አገኘሁት፡፡ ገና እንደደረሰ በጥፊ ካጮለኝ በኋላ፤
"አንቺንም፣ ያን ዶክተርሽንም ካልደፋኂችሁ እኔ ተሾመ አይደለሁም፡ ብሎ ዝቶብኝ ሄደ። አጥፊው በላይ ፊቱ ላይ የነበረውን ንዴቱን ሳይ ክፉኛ ደነገጥኩ፣ ተናደድኩም፡፡ ወዲያው ዶ/ር አድማሱ ጋ ሄድኩና፤ "አንተ ነህ እንዲህ እምትጫወትብኝ፣ ልክሰስ ስልህ እኔ አስታግሰዋለሁ እያልክ ልታስገድለኝ ነው፡፡ ከአሁን ወዲያ የፈለከውን ብትል አላምንህም፣ ቢፈልጉ እንኳን ከዩንቨርስቲ ማባረር _ ቀርቶ እንጦሮጦስም ይክተቱት እንጂ እኔ እንደሆነ ነገ መክሰሴ አይቀርም" እያልኩ ጮህኩበት፡፡ እሱ ግን በተራጋጋ መንፈስ በጥፊ የቀላውን ፊቴን በእጁ እያሻሸ፤ “በቃ ተይ አትናደጂ፣ ከአሁን በኋላ መክሰስ ትችያለሽ፣ እኔ አያገባኝም፡፡ እኔ ይሰማኛል በማለት አንድ ሁለት ጊዜ መካክሬው ነበር፡፡ እሱ ግን ብመክረውም ተመልሶ እዛው ስለሆነ ከአሁን በኋላ አያገባኝም፤ ነገውኑ ክሰሺው" አለኝ፡፡ ጠዋት እሱን ለመክሰስ ወስኜ ከቤት ብወጣም፣ ኤልሳ ቁርስ እየበላን ሳለ ተሾመ በዶ/ር አድማሱ ሁለት ኮርሶች ኤፍ (F) ማግኘቱንና ከዩንቨርስቲ መባረሩን ነገረችኝ፡፡ ይህንን ስሰማ በጣም ደነገጥኩ፡፡ እንደተለያየን በጥድፊያ ወደ ዶ/ር አድማሱ ቢሮ አመራሁ፡፡ እንደገባሁም በሩን ከኋላዬ ዘግቼ! "ዶ/ር፣ ለእኔ ብለህ ነው እንዴ ለተሾመ ኤፍ (F) ሰጥተህ ከትምህርት ቤት እንዲባረር ያደረከው" ብዬ አፈጠጥኩበት?' እሱ ግን ምንም እንደማያውቅ በሚመስል ሁኔታ፤ "ተሾመ ኤፍ አምጥቶ ተባረረ ነው የምትዪኝ? እኔ የሰማሁት አሁን ገና ከአንቺ አፍ ነው፡፡ ለመሆኑ በምን ትምህርት ነው ኤፍ ያመጣው?" ብሎ እኔኑ መልሶ ጠየቀኝ፡ "አንተ በምትሰጣቸው ሁለት ትምህርቶች ነው ወድቆ የተባረረው። ይህንን አታውቅም ማለት ነው?' አልኩት በንዴት፡፡ "ማወቅ አላውቅም፡፡ ነገር ግን ልጁ ሰነፍ መሆኑን አውቃለሁ፡፡ እሱ ትምህርቱን ትቶ አንቺን አፈቀርኩ እያለ ሲሟዘዝ ስለሚውል ቢወድቅ የሚደንቅ አይደለም፡፡ እርግጥ በእኔ ትምህርት ኤፍ ያገኙ ተማሪዎች አሉ፡፡ ይሁን እንጂ እኔ ሁሌ ፈተና ሳርም እንዳላዳላ (Bias እንዳልሆን) በማለት ስም ስለማላይ ኤፍ ያገኘው እሱ ይሁን ሌላ ሰው የማውቀው
🍁🍁ዲያሪው 📝
ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
#ክፍል_10
የዶክተር አድማሱ ሁኔታ ዛሬ ለየት ያለ ቢሆንም እነን ግን አላስፈራኝም:: ብዙ ጊዜ ወደ ቤቱ ስመጣ በራስ የመተማመን ስሜት ይሰማኛል:: የማልፈልገውን ነገር ከፍቃዴ ውጪ እንደማያደርግ እርግጠኛ ነኝ:: ይህ ጠባዩ ነው እሱን አእማረ የተሻለ የሚያደርገው:: ከውስኪው እየተጎነጨሁ በሄድኩ ቁጥር የደስታ ስሜት እየተሰማኝ መጣ:: ለምደንሰው ዳንስም መጠንቀቅ ትቼአለሁ:: ሰውነቱ ላይ ተለጥፌ ስደንስ፣ እሱም አንገቴን ሲስመኝ ሰውነቴ ልክ ኮረንቲ እንደያዘው ነዘረኝ፡ “አልሚና እውነት እኔና አንቺ አሁን ልንለያይ ነው?" ይለኛል በየጨዋታው መሀል፡፡ ዝም ስለው ትንሽ ቆየት ይልና እርግጠኛ በሚመስል አኳኋን፤ “በፍፁም አንለያይም" ይላል:: እኔ ግን ዳግም እንደማንገናኝና ዛረ የመጨረሻችን እንደሚሆን እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ “አልሚ ዛሬ መቼም መሸ እንደማትይኝ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ለመሆኑ እናትሽን የት አስተኛሻቸው?" አለኝ በዳንሳችን መሃል። እኔ አልጋ ላይ ተኝታለች፡፡ እኔ ግን አንተን ሳልሰናበት መሄድ ስለሌለብኝና ላደረክልኝ ውለታ ተመጣጣኝ የሆነ ነገር ማድረግ ባልችልም ቢያንስ ያለችኝን ትንሽ ስጦታ ልሰጥህ ነው የመጣሁት” አልኩት፡፡ “የስጦታ ትንሽ የለውም፡፡ ደግሞስ ምን ውለታ ውዬልሽ ነው? እኔ ያደረኩት ነገር ቢኖር በተሳሳተ መንገድ ተጉዘሽ ተስጥኦሽን አላግባብ እንዳታጠፊው መንገዱን ማሳየት ብቻ ነው'' አለኝ፡፡ እኔም የእሱ ውለታ እንዲህ እንደቀላል ነገር የሚታይ እንዳልሆነና የሰውን ልጅ የሕይወት ጎዳና ከማስተካከል የበለጠ ክቡር ውለታ እንደሌለ ነገርኩት። ጭምቅ አድርጎ አቅፎ ዓይን ዓይኔን ወደ ታች እያየና ግንባሬን እየሳመ ምን እንደሚያደርግ ግራ እንደተጋባ ሰው ተመለከተኝ:: በመሀሉ እንደባነነ ሰው፤ “አልሚ ግን ስጦታው ምንድነው?''አለኝ፡፡ “ልሰጥህ የምችለው ትንሽ ነገር፤ ግን ክቡር የሆነውን ራሴን ነው ብዬ ልብሴን ማወላለቅ ጀመርኩ፡፡ ዶክተር አድማሱ የሀፍርት ሸማውን ስቀድለት ፊቱ በሙሉ በፈገግታ ብርሀን ተሞላ፡፡ እቅፍ አድርጎ እየሳመ ወደ መኝታ ቤት ተሸክሞ ወሰደኝ:: የተዘጋጀሁበት ጉዳይ ስለነበር በመደሰቱ ደስ አለኝ፡፡ ቢያንስ ዛሬ በእኔ ይደሰት:: የባከነ ገላን ለአንድ ቀን ብዙ ውለታ
ለዋለና አለኝታ ለነበረ ጓደኛ አሳልፎ መስጠት ትልቅ ስጦታ ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል አይደለም፣ ያውም ደስታው ለጋራ ለሆነ ነገር! ዶ/ር አድማሱ አልጋ ላይ አስተኝቶኝ ልብሱን አወላልቆ ራቁትን ላየው አፍረት ተሰማኝ፡፡ ለምን እንደሆን ባይገባኝም ፍቅረኛዬ ሳይሆን አስተማሪዬ መሆኑ ጎልቶ ስለታየኝ በእፍረት መልክ አንሶላውን ገልጩ ውስጥ ገባሁ፡፡ መብራቱንም ለማጥፋት እጄን ስዘረጋ፣ እጀን ወደ ቦታው እየመለስና አንሶላውን እየገፈፈ፤ "አልሚና ዛሬማ ይህንን የናፈቅሁትን ገላ እንዳላይ ሊሸፈንብኝና መብራት ሊጠፋብኝ አይገባም፡፡ ሲሆን ሲሆን ጠግቤ በደንብ እንዳየው ተራ መብራት ብቻ ሳይሆን ፓውዛ ሊበራበት በተገባ ነበር" እያለ ከላይ ጀምሮ ገላዬን እየሳመ ቀስ በቀስ ወደ ሆዴ መውረድ ጀመረ፡፡ እንደፈራሁት ሳይሆን ሰውነቴ ሰውነቱን ለመቀበል ተዘጋጀ፡፡ ዶክተር አድማሱ ግን እዚህ ላይም እንደሌላው ጊዜ ረጋ ያለ ስለነበርና ሳይቻኮል መሳምና መደባበሱን ብቻ ስለተያያዘው እዚሁ ላይ እንዳይቆም መፍራቴ አልቀረም፡፡ እኔ ሁሉም ነገር በቶሎ እንዲሆን ከመጠን በላይ የቸኮልኩ ቢሆንም እሱ ግን ስሞና ዳሶ ሊጠግበኝ አልቻለም፡፡ በስስት መልክ የማይስመው የሰውነቴ ክፍል አልነበረም፡፡ ይህ ደግሞ እኔን ይበልጥ አጣደፈኝ፡፡ እንደፈራሁት አልሆነም ስሞኝ እንደጠገበ ስጦታዬን ተቀበለኝ፡፡ ግን ነገሩ ሁሉ እንደቸኮልኩለት አልሆነም፡፡ ደስታው የእሱ እንጂ የጋራችን ሊሆን አልቻለም፡፡ ለእኔ እዳ የመክፈል ያህል ሲሆንብኝ ለእሱ ግን ሴት ገላ ውስጥ ሳይሆን ገነት የገባ ያህል ተሰምቶት ነበር:: በጣም የገረመኝ ነገር ቢኖር በየመሀሉ የማስበው ከፍቃዴ ውጪ ከአማረ ጋር ያሳለፍኩትን ያን በእጅጉ የተሻለውን ሌሊት ነበር፡፡ እሱ እንደዚያ እየጮኸ ደስታውን ሲገልፅ ሳይና ደስታውን ልጋራው አለመቻሌን ስገነዘብ፤ ያውቅብኛል ብዬ ስለፈራሁ የውሸት ድምፅ እያወጣሁና ውስጤ አድማሱን ሳይሆን አማረን እንዳቀፍኩ ያህል እንዲሰማው ዓይኔን ጨፍኜ ለማሳመን ሞከርኩ። ባይሳካልኝም በተወሰነ መልኩ ደስታውን የጋራ ለማድረግ ጣርኩ፡፡ ሁሉም ነገር ካለቀ በኋላ ግን ለምን እንዲህ ሊሆን ቻለ? ስል ራሴን ጠየቅሁ :: ለምን ገላዬን ብቻ ሰጠሁት? ለምን ሁለመናዬን ልሰጠው አልቻልኩም? ምነው ደስታን እየሰጠሁት ደስታን መቀበል ተሳነኝ? እሱም አድማሱም እንደአማረ ለወንድ ልጅ የተሰጠውን ጾታዊ ፀጋ የተላበስ ሆኖ ሳለ ለእኔ ግን ለምን ከእሱ አንሶ ታየኝ? የሚሉት ጥያቄዎች ተመላለሱብኝ እንጂ ትዝታው ከእኔ ጋር ሊቀር አልቻለም፡፡"
ሠራተኛዬ ጋሼ ብላ ስትጠራኝ ከገባሁበት የሐሳብ ባህር ተስፈንጥሬ ወጣሁ። የሚገርመው ነገር መንቃቴን እንጂ ሠራተኛዬ እንደቀሰቀሰችኝ አላወቅሁም ነበር፡፡ ከፊት ለፊቴ ቀጥ ብላ ቆማ በመገረም ዓይን ትኩር ብላ ትመለከተኛለች፡፡ “ምነው?'' አልኳት በንዴት፡፡ “ምነው ደህና አይደሉም እንዴ? እረባክዎትን ሀኪም ቤት ይሂዱ:: ደግሞም ከሥራ ከቀሩ ይኸው ዛሬ ሁለተኛ ቀኖት ነው፡፡ የሆኑ ሰውዬ ከመሥሪያ ቤትም ደውለው ደህንነቶን ጠይቀውኝ ነበር፡፡ እኔም የምመልሰው ሳጣ ዘመድ ጥየቃ ወደ ገጠር ሄደዋል አልኳቸው፡፡ እሳቸው ግን! "የምን ገጠር ነው የምታወሪው? የሱ ዘመዶች በሙሉ አዲስ አበባ አይደሉ እንዴ ያሉት?'' ብለው ጮሁብኝ፣ "አይ እንግዲያው በደንብ ሳልሰማ ቀርቼ ይሆናል፣ ምናልባት ጓደኛዪ ጋ ብለውኝ ይሆናል" ብዬ እየፈራሁ መለስኩላቸው፣ "ከደወሉ ወንድወሰን ደውልልኝ ብሎሃል ብዬ እንድነግሮትም ነግረውኛል" እያለች የባጥ የቆጡን መቀባጠሩን ተያያዘችው:: መቼም እሷና ሬዲዮ አንዴ ወሬ ከጀመሩ ካልዘጓቸው በስተቀር አያቆሙም፡፡ ነገር ግን ምን ታድርግ ሁኔታዬ እንኳን ለእሷ ለእኔም ግራ የሚያጋባ ሆኗል፡፡ ግራ መጋባቷን ሳይ አዘንኩላት:: አልፎ አልፎ አብረን በምናሳልፋቸው ሌሊቶች የምትፍለቀለቅባቸውና የምትደሰትባቸው ወቅቶች ነበሩ:: አሁን ግን ፍቅረኛዋ እሷን ዘንግቶ ሌሊቱን በፍቅር ሳይሆን በማያቋርጥ ንባብና ትካዜ ሲያሳልፈው ስታይ እንዴት ግራ አትጋባ፣ እንዴትስ ጤነኛ ነው ብላ ታስብ፡፡ እርግጥ ነው ጤነኛ አልነበርኩም፡፡ ራሴን የሚያዞር ማለቂያ የሌለው ታሪክ ከእንቅልፍ ማጣት ጋር ተደምሮ ጩህ ጩህ ሊያሰኘኝ እየቃጣው ነው:: በዚህ ላይ ደግሞ የማነበው የሚያጓጓና የሚያስደስት ታሪክ ሳይሆን የሀዘንና የመርዶ ዜና ነበር፡፡ እርግጥ ከዚህ በላይ ምን መርዶ ይኖራል? “እጅግ ለምትወደው" ፍቅረኛዋ ለአንድ ቀን ሳትወድ በግድ በሰጠችው ገላ የምትፀፀት ሴት፣ ዛሬ ደግሞ በፍላጎቷ ለማትወደው ሰው የምወደውንና የማፈቅረውን ገላ በስጦታ ገፀ በረከት ካቀረበች በኋላ "ደስታ አጣሁበት" እያለች ስትደሰኩርና እኔን ብቻ ገላዋ እንደናፈቀ አድርጋ ስታወራ ከመስማት የበለጠ ምን የሚያናድድ መርዶ አለ:: ግን ዜናው የመርዶ መሆኑን ባውቅም ልተወው
ደራሲ ፍስሐ ተክሌ
#ክፍል_10
የዶክተር አድማሱ ሁኔታ ዛሬ ለየት ያለ ቢሆንም እነን ግን አላስፈራኝም:: ብዙ ጊዜ ወደ ቤቱ ስመጣ በራስ የመተማመን ስሜት ይሰማኛል:: የማልፈልገውን ነገር ከፍቃዴ ውጪ እንደማያደርግ እርግጠኛ ነኝ:: ይህ ጠባዩ ነው እሱን አእማረ የተሻለ የሚያደርገው:: ከውስኪው እየተጎነጨሁ በሄድኩ ቁጥር የደስታ ስሜት እየተሰማኝ መጣ:: ለምደንሰው ዳንስም መጠንቀቅ ትቼአለሁ:: ሰውነቱ ላይ ተለጥፌ ስደንስ፣ እሱም አንገቴን ሲስመኝ ሰውነቴ ልክ ኮረንቲ እንደያዘው ነዘረኝ፡ “አልሚና እውነት እኔና አንቺ አሁን ልንለያይ ነው?" ይለኛል በየጨዋታው መሀል፡፡ ዝም ስለው ትንሽ ቆየት ይልና እርግጠኛ በሚመስል አኳኋን፤ “በፍፁም አንለያይም" ይላል:: እኔ ግን ዳግም እንደማንገናኝና ዛረ የመጨረሻችን እንደሚሆን እርግጠኛ ነበርኩ፡፡ “አልሚ ዛሬ መቼም መሸ እንደማትይኝ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ለመሆኑ እናትሽን የት አስተኛሻቸው?" አለኝ በዳንሳችን መሃል። እኔ አልጋ ላይ ተኝታለች፡፡ እኔ ግን አንተን ሳልሰናበት መሄድ ስለሌለብኝና ላደረክልኝ ውለታ ተመጣጣኝ የሆነ ነገር ማድረግ ባልችልም ቢያንስ ያለችኝን ትንሽ ስጦታ ልሰጥህ ነው የመጣሁት” አልኩት፡፡ “የስጦታ ትንሽ የለውም፡፡ ደግሞስ ምን ውለታ ውዬልሽ ነው? እኔ ያደረኩት ነገር ቢኖር በተሳሳተ መንገድ ተጉዘሽ ተስጥኦሽን አላግባብ እንዳታጠፊው መንገዱን ማሳየት ብቻ ነው'' አለኝ፡፡ እኔም የእሱ ውለታ እንዲህ እንደቀላል ነገር የሚታይ እንዳልሆነና የሰውን ልጅ የሕይወት ጎዳና ከማስተካከል የበለጠ ክቡር ውለታ እንደሌለ ነገርኩት። ጭምቅ አድርጎ አቅፎ ዓይን ዓይኔን ወደ ታች እያየና ግንባሬን እየሳመ ምን እንደሚያደርግ ግራ እንደተጋባ ሰው ተመለከተኝ:: በመሀሉ እንደባነነ ሰው፤ “አልሚ ግን ስጦታው ምንድነው?''አለኝ፡፡ “ልሰጥህ የምችለው ትንሽ ነገር፤ ግን ክቡር የሆነውን ራሴን ነው ብዬ ልብሴን ማወላለቅ ጀመርኩ፡፡ ዶክተር አድማሱ የሀፍርት ሸማውን ስቀድለት ፊቱ በሙሉ በፈገግታ ብርሀን ተሞላ፡፡ እቅፍ አድርጎ እየሳመ ወደ መኝታ ቤት ተሸክሞ ወሰደኝ:: የተዘጋጀሁበት ጉዳይ ስለነበር በመደሰቱ ደስ አለኝ፡፡ ቢያንስ ዛሬ በእኔ ይደሰት:: የባከነ ገላን ለአንድ ቀን ብዙ ውለታ
ለዋለና አለኝታ ለነበረ ጓደኛ አሳልፎ መስጠት ትልቅ ስጦታ ተደርጎ ሊወሰድ የሚችል አይደለም፣ ያውም ደስታው ለጋራ ለሆነ ነገር! ዶ/ር አድማሱ አልጋ ላይ አስተኝቶኝ ልብሱን አወላልቆ ራቁትን ላየው አፍረት ተሰማኝ፡፡ ለምን እንደሆን ባይገባኝም ፍቅረኛዬ ሳይሆን አስተማሪዬ መሆኑ ጎልቶ ስለታየኝ በእፍረት መልክ አንሶላውን ገልጩ ውስጥ ገባሁ፡፡ መብራቱንም ለማጥፋት እጄን ስዘረጋ፣ እጀን ወደ ቦታው እየመለስና አንሶላውን እየገፈፈ፤ "አልሚና ዛሬማ ይህንን የናፈቅሁትን ገላ እንዳላይ ሊሸፈንብኝና መብራት ሊጠፋብኝ አይገባም፡፡ ሲሆን ሲሆን ጠግቤ በደንብ እንዳየው ተራ መብራት ብቻ ሳይሆን ፓውዛ ሊበራበት በተገባ ነበር" እያለ ከላይ ጀምሮ ገላዬን እየሳመ ቀስ በቀስ ወደ ሆዴ መውረድ ጀመረ፡፡ እንደፈራሁት ሳይሆን ሰውነቴ ሰውነቱን ለመቀበል ተዘጋጀ፡፡ ዶክተር አድማሱ ግን እዚህ ላይም እንደሌላው ጊዜ ረጋ ያለ ስለነበርና ሳይቻኮል መሳምና መደባበሱን ብቻ ስለተያያዘው እዚሁ ላይ እንዳይቆም መፍራቴ አልቀረም፡፡ እኔ ሁሉም ነገር በቶሎ እንዲሆን ከመጠን በላይ የቸኮልኩ ቢሆንም እሱ ግን ስሞና ዳሶ ሊጠግበኝ አልቻለም፡፡ በስስት መልክ የማይስመው የሰውነቴ ክፍል አልነበረም፡፡ ይህ ደግሞ እኔን ይበልጥ አጣደፈኝ፡፡ እንደፈራሁት አልሆነም ስሞኝ እንደጠገበ ስጦታዬን ተቀበለኝ፡፡ ግን ነገሩ ሁሉ እንደቸኮልኩለት አልሆነም፡፡ ደስታው የእሱ እንጂ የጋራችን ሊሆን አልቻለም፡፡ ለእኔ እዳ የመክፈል ያህል ሲሆንብኝ ለእሱ ግን ሴት ገላ ውስጥ ሳይሆን ገነት የገባ ያህል ተሰምቶት ነበር:: በጣም የገረመኝ ነገር ቢኖር በየመሀሉ የማስበው ከፍቃዴ ውጪ ከአማረ ጋር ያሳለፍኩትን ያን በእጅጉ የተሻለውን ሌሊት ነበር፡፡ እሱ እንደዚያ እየጮኸ ደስታውን ሲገልፅ ሳይና ደስታውን ልጋራው አለመቻሌን ስገነዘብ፤ ያውቅብኛል ብዬ ስለፈራሁ የውሸት ድምፅ እያወጣሁና ውስጤ አድማሱን ሳይሆን አማረን እንዳቀፍኩ ያህል እንዲሰማው ዓይኔን ጨፍኜ ለማሳመን ሞከርኩ። ባይሳካልኝም በተወሰነ መልኩ ደስታውን የጋራ ለማድረግ ጣርኩ፡፡ ሁሉም ነገር ካለቀ በኋላ ግን ለምን እንዲህ ሊሆን ቻለ? ስል ራሴን ጠየቅሁ :: ለምን ገላዬን ብቻ ሰጠሁት? ለምን ሁለመናዬን ልሰጠው አልቻልኩም? ምነው ደስታን እየሰጠሁት ደስታን መቀበል ተሳነኝ? እሱም አድማሱም እንደአማረ ለወንድ ልጅ የተሰጠውን ጾታዊ ፀጋ የተላበስ ሆኖ ሳለ ለእኔ ግን ለምን ከእሱ አንሶ ታየኝ? የሚሉት ጥያቄዎች ተመላለሱብኝ እንጂ ትዝታው ከእኔ ጋር ሊቀር አልቻለም፡፡"
ሠራተኛዬ ጋሼ ብላ ስትጠራኝ ከገባሁበት የሐሳብ ባህር ተስፈንጥሬ ወጣሁ። የሚገርመው ነገር መንቃቴን እንጂ ሠራተኛዬ እንደቀሰቀሰችኝ አላወቅሁም ነበር፡፡ ከፊት ለፊቴ ቀጥ ብላ ቆማ በመገረም ዓይን ትኩር ብላ ትመለከተኛለች፡፡ “ምነው?'' አልኳት በንዴት፡፡ “ምነው ደህና አይደሉም እንዴ? እረባክዎትን ሀኪም ቤት ይሂዱ:: ደግሞም ከሥራ ከቀሩ ይኸው ዛሬ ሁለተኛ ቀኖት ነው፡፡ የሆኑ ሰውዬ ከመሥሪያ ቤትም ደውለው ደህንነቶን ጠይቀውኝ ነበር፡፡ እኔም የምመልሰው ሳጣ ዘመድ ጥየቃ ወደ ገጠር ሄደዋል አልኳቸው፡፡ እሳቸው ግን! "የምን ገጠር ነው የምታወሪው? የሱ ዘመዶች በሙሉ አዲስ አበባ አይደሉ እንዴ ያሉት?'' ብለው ጮሁብኝ፣ "አይ እንግዲያው በደንብ ሳልሰማ ቀርቼ ይሆናል፣ ምናልባት ጓደኛዪ ጋ ብለውኝ ይሆናል" ብዬ እየፈራሁ መለስኩላቸው፣ "ከደወሉ ወንድወሰን ደውልልኝ ብሎሃል ብዬ እንድነግሮትም ነግረውኛል" እያለች የባጥ የቆጡን መቀባጠሩን ተያያዘችው:: መቼም እሷና ሬዲዮ አንዴ ወሬ ከጀመሩ ካልዘጓቸው በስተቀር አያቆሙም፡፡ ነገር ግን ምን ታድርግ ሁኔታዬ እንኳን ለእሷ ለእኔም ግራ የሚያጋባ ሆኗል፡፡ ግራ መጋባቷን ሳይ አዘንኩላት:: አልፎ አልፎ አብረን በምናሳልፋቸው ሌሊቶች የምትፍለቀለቅባቸውና የምትደሰትባቸው ወቅቶች ነበሩ:: አሁን ግን ፍቅረኛዋ እሷን ዘንግቶ ሌሊቱን በፍቅር ሳይሆን በማያቋርጥ ንባብና ትካዜ ሲያሳልፈው ስታይ እንዴት ግራ አትጋባ፣ እንዴትስ ጤነኛ ነው ብላ ታስብ፡፡ እርግጥ ነው ጤነኛ አልነበርኩም፡፡ ራሴን የሚያዞር ማለቂያ የሌለው ታሪክ ከእንቅልፍ ማጣት ጋር ተደምሮ ጩህ ጩህ ሊያሰኘኝ እየቃጣው ነው:: በዚህ ላይ ደግሞ የማነበው የሚያጓጓና የሚያስደስት ታሪክ ሳይሆን የሀዘንና የመርዶ ዜና ነበር፡፡ እርግጥ ከዚህ በላይ ምን መርዶ ይኖራል? “እጅግ ለምትወደው" ፍቅረኛዋ ለአንድ ቀን ሳትወድ በግድ በሰጠችው ገላ የምትፀፀት ሴት፣ ዛሬ ደግሞ በፍላጎቷ ለማትወደው ሰው የምወደውንና የማፈቅረውን ገላ በስጦታ ገፀ በረከት ካቀረበች በኋላ "ደስታ አጣሁበት" እያለች ስትደሰኩርና እኔን ብቻ ገላዋ እንደናፈቀ አድርጋ ስታወራ ከመስማት የበለጠ ምን የሚያናድድ መርዶ አለ:: ግን ዜናው የመርዶ መሆኑን ባውቅም ልተወው