❤️የገብረ እግዚ ፍቅር❤️
ሎቶማሪዎቹ ጠብቅ ተብዬ
እንዳያምፁ አጥር ተከልዬ
መሳርያውን ይዤ ቦንቦቹን ታጥቄ
እየቶጠባበኩኝ ቦሩን ተጸንቅቄ👮
ዋይ!! ዋይ!! ይቺ ሸር......ጣ
አፈቀርኳት እኮ ነፍሴ ስክትዋጣ💘
አንዲት ቆንጆ ወጣት ስተልፍ አይቻት👩
ቦፍቅር ወ ደኩኝ ልቤን ሰጥቻት
ዋይ!! ዋይ!!ይቺ ሸር...ጣ
ምን አይነት ናት ብሎ ጓዴ ቢጠይቀኝ
ሎሱ ላሳያት ስል ነቅቼ ጠበኩኝ
ድንገት ልጅት መጣች
ተመልከት ያቻት👉👩
"የቱ ጋር ነች አትታይም ባክህ"
ዋይ!! አንተ ሸር......ጣ
ያቻት 👉👩
"የቱ ጋር...
ያቻት😡 👉👩 ዋይ!!ያቺ ቀይ ቀሚስ የለበሰች💃
አታያትም እንዴ ዋይ!! ዋይ!!
የታለች እያለ ይነተርከኛል
አታያትም እንዴ አንተ ሸር...ጣ
አይንክ አይሰራም እንዴ ዋይ!!
ምንአባክ እንደዚ ያደርግሀል😡😡
አነጣጥረክ አታይም እንዴ ዋይ!!
አላያት ስላለኝ እንዲያያት ፈልጌ
አነጣጠርኩና ምልክት አ ድርጌ
ባለኝ ችሎታዬ ጫካ ባካበትኩት
ቃታውን ሳብኩና ግንባሮን ነረትኩት🤦♀
ዋይ!!አያሀት አሁን አላያሀትም እንዴ😠
እሷ ናት መሬት የተኛችው
ከመሬት ላይ ወድቃ ደም የተቀባችው
ብዬ ልነግረው ስል ካጠገቤ ጠፍቶል
ዞር ብዬ ሳየው ጓደኛዬ ይሮጣል🏃
በጥይት መመታት ቁም ነገር መስሎታል
ፍቅርን እረታሁት ፍቅርን እረተሁት
ላለብኝ ብሶት...
ሺ ዘጠኝ ሞቶ....83
ሎቶማሪዎቹ ጠብቅ ተብዬ
እንዳያምፁ አጥር ተከልዬ
መሳርያውን ይዤ ቦንቦቹን ታጥቄ
እየቶጠባበኩኝ ቦሩን ተጸንቅቄ👮
ዋይ!! ዋይ!! ይቺ ሸር......ጣ
አፈቀርኳት እኮ ነፍሴ ስክትዋጣ💘
አንዲት ቆንጆ ወጣት ስተልፍ አይቻት👩
ቦፍቅር ወ ደኩኝ ልቤን ሰጥቻት
ዋይ!! ዋይ!!ይቺ ሸር...ጣ
ምን አይነት ናት ብሎ ጓዴ ቢጠይቀኝ
ሎሱ ላሳያት ስል ነቅቼ ጠበኩኝ
ድንገት ልጅት መጣች
ተመልከት ያቻት👉👩
"የቱ ጋር ነች አትታይም ባክህ"
ዋይ!! አንተ ሸር......ጣ
ያቻት 👉👩
"የቱ ጋር...
ያቻት😡 👉👩 ዋይ!!ያቺ ቀይ ቀሚስ የለበሰች💃
አታያትም እንዴ ዋይ!! ዋይ!!
የታለች እያለ ይነተርከኛል
አታያትም እንዴ አንተ ሸር...ጣ
አይንክ አይሰራም እንዴ ዋይ!!
ምንአባክ እንደዚ ያደርግሀል😡😡
አነጣጥረክ አታይም እንዴ ዋይ!!
አላያት ስላለኝ እንዲያያት ፈልጌ
አነጣጠርኩና ምልክት አ ድርጌ
ባለኝ ችሎታዬ ጫካ ባካበትኩት
ቃታውን ሳብኩና ግንባሮን ነረትኩት🤦♀
ዋይ!!አያሀት አሁን አላያሀትም እንዴ😠
እሷ ናት መሬት የተኛችው
ከመሬት ላይ ወድቃ ደም የተቀባችው
ብዬ ልነግረው ስል ካጠገቤ ጠፍቶል
ዞር ብዬ ሳየው ጓደኛዬ ይሮጣል🏃
በጥይት መመታት ቁም ነገር መስሎታል
ፍቅርን እረታሁት ፍቅርን እረተሁት
ላለብኝ ብሶት...
ሺ ዘጠኝ ሞቶ....83
👍1😁1
#የኔልሰን #ሮህሊላ #ማንዴላ #አጭር #የህይወት #ታሪክ
ሮሊላሂላ ማንዴላ የተወለዱት ፣ ትራንስኪ በተባለው የደቡብ አፍሪካ ከተማ ጁላይ 18 ቀን 1918 ዓም ነው። ኔልሰን የሚለውን ስማቸውን ያገኙት ከጊዜ በኋላ ከአንድ አስተማሪያቸው እንደሆነ የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል። በተወለዱበት አካባቢ ባለው ቲምቡ ጎሳም በአካባቢው ሰው “ማዲባ” በሚል ስም ይጠራሉ።
አባታቸው ፣ ማንደላ የ 9 ዓመት ልጅ ሳሉ ነው የሞቱት። ማንዴላ 23 ዓመት ሲሞላቸው በጎሳው ደንብ መሰረት የሚመጣላቸውን ሚስት ላለማግባት ሲሉ ያደጉበትን ከተማ ትተው ወደ ጆሃንስበርግ ሄዱ።
በ 25 ዓመታቸው ዩኒቨርሲቲ በመግባት ማንዴላ በፎርት ሃሬ ዩኒቨርሲቲ እና በዊትዋተርስራንድ ዩኒቨርሲቲ ተምረው በ1942 በህግ ተመርቀዋል። በተመረቁ በሁለተኛው ዓመት የመጀመሪያ ሚስታቸው የሆኑትን ኤቪሊን ማሴ በማግባት አራት ልጆችን አፈሩ። በ1958 እስከተለያዩበት ቀን ድረስ አብረው ቆይተዋል። ከዚያ ፊታቸውን ወደ ትግሉ በማዞር የአፍሪካ ናሽናል ኮንግረስ በተባለው ፓርቲ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ መሆን ጀመሩ። በ1952 ማንዴላ የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳት በመሆን የአፓርታይድ ሥርዓትን በጽኑ መታገል ጀመሩ። በ1956 ማንዴላ በአገር ክህደት ወንጀል በጊዜው በነበረው የነጮች መንግስት ተከሰሱ- ክሱ አምስት ዓመት ያህል በክርክር ከቆየ በኋላ ማንዴላ በክርክሩ አሸነፉ።
በማርች ወር 1960 ዓም፣ ሻርፕቪል በተሰኘችው ከተማ ፣ ጸረ አፓርታይድ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ላይ ከነበሩት ጥቁር ሰልፈኞች መካከል 69 ያህሉን ፖሊሶች ተኩሰው በመግደላቸው ብጥብጡ ከፍ ያለ ደረጃ ደረስ። የወቅቱ መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ እንቅስቃሴ ሲከለክል እንደማንዴላ በበኩላቸው ሰላማዊ ትግል እንደማያዋጣ በማመን ልዩ የጦር ሃይል አደራጁ። ማንዴላም የጦሩ የበላይ አዛዥ በመሆኑ እርዳታ ፍለጋ ወደሌሎች አገራት ጉዞ ማድረግ ጀመሩ።
ከውጭ አገር ሲመለሱ እዚያ ደቡብ አፍሪካ ላይ ተያዙና አምስት ዓመት እስር ተፈረደባቸው። በ1963 እንደገና ማንዴላና ሌሎች የ ኤ ኤን ሲ መሪዎች መንግስትን በሃይል ለመገልበጥ የሚል ክስ ተከፈተባቸውና ፍርድ ቤት ቀረቡ። ከዚያም ማንዴላ ዕድሜ ይፍታህ ተፈረደባቸውና ሮቢን ደሴት ያለ እስር ቤት ተላኩ። ማንዴላ ከሮቢን ደሴት ሌላ በተዘዋወሩባቸው ተጨማሪ እስር ቤቶች በጠቅላላ 27 ዓመት በ እስር ሲቆዩ ፣ በመላው ዓለም የነጻነት ምሳሌ ተደረገው ተወሰዱ - ዝናቸውም እየሰፋ መጣ።
በ1990 ዓ.ም የደቡብ አፍሪካ የነጮች መንግስት በተደረገበት ዓለም አቀፍ ጫና ማንዴላን ከ እስር ፈታቸው። ኤ ኤን ሲ የተባለው ድርጅታቸውም እንዲንቀሳቀስ ተፈቀደለት - ማንዴላም ተመልሰው ሊቀመንበር ሆኑ።
ማንዴላና የዚያን ጊዜው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ኤፍ ደብሊው ደ ክላርክ በጋራ የዓለም የሰላም የኖቤል ሽልማት ተሸለሙ። ይህም የሆነው ጥቁሩ ማንዴላና ነጩ ደ ክላርክ የአፓርታይድ ሥር ዓትን ለማጥፋት ቁርጠኛ ስምምነት በማድረጋቸው ነበር።
በ1994 ደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያውን ነጻ ምርጫ አደረገችና ማንዴላ የአገሪቷ የመጀመሪያ ጥቁር ፕሬዚዳንት ሆኑ። በ1998 ማንዴላ ለሶስተኛ ጊዜ ትዳር በመያዝ ከግራሻ ሚሼል ጋር ተጣመሩ። በ1997 ከ ኤ ኤን ሲ ሊቀመንበርነት ለቀቁ። በ1999 ደግሞ ፕሬዚዳንትነት በቃኝ አሉ። በ2004 ዓ.ም ማንዴላ ከፖሊቲካው ራሳቸውን አራቁና ጡረታ መውጣታቸውን አስታወቁ። እንዲያውም ያን ጊዜ “ለማውቃችሁ ሁሉ እኔ እደውልላችኋለሁ እንጂ እናንተ እንዳትደውልሉኝ” ማለታቸው ይነገርላቸዋል። ጡረታ በወጡ በዓመቱ ትልቁ ወንድ ልጃቸው ማካቶ ማንዴላ መሞቱ ልባቸውን በሃዘን ሰበረው። በተለይ አሟሟቱ በ ኤች አይ ቪ ስለነበር፣ ማንዴላ ያንን ምክንያት አድርገው ደቡብ አፍሪካውያን ከ ኤድስ ቫይረስ እንዲጠበቁና እንደማንኛውም በሽታ ቶሎ እንዲታከሙ ጥሩ አቀረቡ። ከዚያ ወዲህ ግን በበጎ አድራጎት ሥራ ሲሳተፉ ቆይተዋል። በ2010 ደቡብ አፍሪካ የዓለም ዋንጫን እንድታዘጋጅ ትልቅ ጥረት ያደረጉትን ማንዴላ ነበሩ። በመዝጊያው በዓል ላይም በመገኘት ለውድድሩ ድምቀት ሰጥተዋል። ዕድሜያቸው እየገፋም በመሄዱ 91 ዓመት ከሞላቸው ጊዜ በኋላ፣ በተለይም ከጃንዋሪ 2011 ጀምሮ ግን ባደረባቸው የስንባ ምች እየተስቃዩ በተደጋጋሚ ሆስፒታል ሲገቡና ሲወጡ ቆይተዋል።
ኔልሰን ማንዴል በግል ህይወታቸው ሳቂታና ተጫዋች መሆናቸው ይነገርላቸዋል። ፈግግታቸው ከማንም ልብ ሰርስሮ የሚገባ ነው። በሚገርም ሁኔታ 27 ዓመት በ እስር በመቆየታቸው ምንም የሚሰማቸው ምሬት እንደሌለ ሁልጊዜ ይናገሩ ነበር። ደቡብ አፍሪካም ለክብራቸው በገንዘቧ ላይ ፎቷቸውን ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ማተም ጀምራለች። ኔልሰን ሮህሊላ ማንዴላ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው ፣ ኅዳር 26 ቀን 2006 (ዲሴምበር 5 ቀን 2013) በወዳጅ ዘመድና ቤተሰብ ተከበው አረፉ። ማንዴላ ዛሬ በህይወት የሉም፣ በሁሉም ሰው ህሊና ውስጥ ግን ታላቅ ስብዕናቸው ለዘላለም ይኖራል።
ውድ የቻናላችን ተከታታዬች በተብራራ መልኩ በኔል ሰን ማንዴላ የህይወት ታርክ ዙርያ የተፃፈውን
LONG WALK TO FREEDOM በ PDF
ቀርቦላችኋል መልካም ንባብ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ሮሊላሂላ ማንዴላ የተወለዱት ፣ ትራንስኪ በተባለው የደቡብ አፍሪካ ከተማ ጁላይ 18 ቀን 1918 ዓም ነው። ኔልሰን የሚለውን ስማቸውን ያገኙት ከጊዜ በኋላ ከአንድ አስተማሪያቸው እንደሆነ የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል። በተወለዱበት አካባቢ ባለው ቲምቡ ጎሳም በአካባቢው ሰው “ማዲባ” በሚል ስም ይጠራሉ።
አባታቸው ፣ ማንደላ የ 9 ዓመት ልጅ ሳሉ ነው የሞቱት። ማንዴላ 23 ዓመት ሲሞላቸው በጎሳው ደንብ መሰረት የሚመጣላቸውን ሚስት ላለማግባት ሲሉ ያደጉበትን ከተማ ትተው ወደ ጆሃንስበርግ ሄዱ።
በ 25 ዓመታቸው ዩኒቨርሲቲ በመግባት ማንዴላ በፎርት ሃሬ ዩኒቨርሲቲ እና በዊትዋተርስራንድ ዩኒቨርሲቲ ተምረው በ1942 በህግ ተመርቀዋል። በተመረቁ በሁለተኛው ዓመት የመጀመሪያ ሚስታቸው የሆኑትን ኤቪሊን ማሴ በማግባት አራት ልጆችን አፈሩ። በ1958 እስከተለያዩበት ቀን ድረስ አብረው ቆይተዋል። ከዚያ ፊታቸውን ወደ ትግሉ በማዞር የአፍሪካ ናሽናል ኮንግረስ በተባለው ፓርቲ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ መሆን ጀመሩ። በ1952 ማንዴላ የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳት በመሆን የአፓርታይድ ሥርዓትን በጽኑ መታገል ጀመሩ። በ1956 ማንዴላ በአገር ክህደት ወንጀል በጊዜው በነበረው የነጮች መንግስት ተከሰሱ- ክሱ አምስት ዓመት ያህል በክርክር ከቆየ በኋላ ማንዴላ በክርክሩ አሸነፉ።
በማርች ወር 1960 ዓም፣ ሻርፕቪል በተሰኘችው ከተማ ፣ ጸረ አፓርታይድ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ላይ ከነበሩት ጥቁር ሰልፈኞች መካከል 69 ያህሉን ፖሊሶች ተኩሰው በመግደላቸው ብጥብጡ ከፍ ያለ ደረጃ ደረስ። የወቅቱ መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ እንቅስቃሴ ሲከለክል እንደማንዴላ በበኩላቸው ሰላማዊ ትግል እንደማያዋጣ በማመን ልዩ የጦር ሃይል አደራጁ። ማንዴላም የጦሩ የበላይ አዛዥ በመሆኑ እርዳታ ፍለጋ ወደሌሎች አገራት ጉዞ ማድረግ ጀመሩ።
ከውጭ አገር ሲመለሱ እዚያ ደቡብ አፍሪካ ላይ ተያዙና አምስት ዓመት እስር ተፈረደባቸው። በ1963 እንደገና ማንዴላና ሌሎች የ ኤ ኤን ሲ መሪዎች መንግስትን በሃይል ለመገልበጥ የሚል ክስ ተከፈተባቸውና ፍርድ ቤት ቀረቡ። ከዚያም ማንዴላ ዕድሜ ይፍታህ ተፈረደባቸውና ሮቢን ደሴት ያለ እስር ቤት ተላኩ። ማንዴላ ከሮቢን ደሴት ሌላ በተዘዋወሩባቸው ተጨማሪ እስር ቤቶች በጠቅላላ 27 ዓመት በ እስር ሲቆዩ ፣ በመላው ዓለም የነጻነት ምሳሌ ተደረገው ተወሰዱ - ዝናቸውም እየሰፋ መጣ።
በ1990 ዓ.ም የደቡብ አፍሪካ የነጮች መንግስት በተደረገበት ዓለም አቀፍ ጫና ማንዴላን ከ እስር ፈታቸው። ኤ ኤን ሲ የተባለው ድርጅታቸውም እንዲንቀሳቀስ ተፈቀደለት - ማንዴላም ተመልሰው ሊቀመንበር ሆኑ።
ማንዴላና የዚያን ጊዜው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ኤፍ ደብሊው ደ ክላርክ በጋራ የዓለም የሰላም የኖቤል ሽልማት ተሸለሙ። ይህም የሆነው ጥቁሩ ማንዴላና ነጩ ደ ክላርክ የአፓርታይድ ሥር ዓትን ለማጥፋት ቁርጠኛ ስምምነት በማድረጋቸው ነበር።
በ1994 ደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያውን ነጻ ምርጫ አደረገችና ማንዴላ የአገሪቷ የመጀመሪያ ጥቁር ፕሬዚዳንት ሆኑ። በ1998 ማንዴላ ለሶስተኛ ጊዜ ትዳር በመያዝ ከግራሻ ሚሼል ጋር ተጣመሩ። በ1997 ከ ኤ ኤን ሲ ሊቀመንበርነት ለቀቁ። በ1999 ደግሞ ፕሬዚዳንትነት በቃኝ አሉ። በ2004 ዓ.ም ማንዴላ ከፖሊቲካው ራሳቸውን አራቁና ጡረታ መውጣታቸውን አስታወቁ። እንዲያውም ያን ጊዜ “ለማውቃችሁ ሁሉ እኔ እደውልላችኋለሁ እንጂ እናንተ እንዳትደውልሉኝ” ማለታቸው ይነገርላቸዋል። ጡረታ በወጡ በዓመቱ ትልቁ ወንድ ልጃቸው ማካቶ ማንዴላ መሞቱ ልባቸውን በሃዘን ሰበረው። በተለይ አሟሟቱ በ ኤች አይ ቪ ስለነበር፣ ማንዴላ ያንን ምክንያት አድርገው ደቡብ አፍሪካውያን ከ ኤድስ ቫይረስ እንዲጠበቁና እንደማንኛውም በሽታ ቶሎ እንዲታከሙ ጥሩ አቀረቡ። ከዚያ ወዲህ ግን በበጎ አድራጎት ሥራ ሲሳተፉ ቆይተዋል። በ2010 ደቡብ አፍሪካ የዓለም ዋንጫን እንድታዘጋጅ ትልቅ ጥረት ያደረጉትን ማንዴላ ነበሩ። በመዝጊያው በዓል ላይም በመገኘት ለውድድሩ ድምቀት ሰጥተዋል። ዕድሜያቸው እየገፋም በመሄዱ 91 ዓመት ከሞላቸው ጊዜ በኋላ፣ በተለይም ከጃንዋሪ 2011 ጀምሮ ግን ባደረባቸው የስንባ ምች እየተስቃዩ በተደጋጋሚ ሆስፒታል ሲገቡና ሲወጡ ቆይተዋል።
ኔልሰን ማንዴል በግል ህይወታቸው ሳቂታና ተጫዋች መሆናቸው ይነገርላቸዋል። ፈግግታቸው ከማንም ልብ ሰርስሮ የሚገባ ነው። በሚገርም ሁኔታ 27 ዓመት በ እስር በመቆየታቸው ምንም የሚሰማቸው ምሬት እንደሌለ ሁልጊዜ ይናገሩ ነበር። ደቡብ አፍሪካም ለክብራቸው በገንዘቧ ላይ ፎቷቸውን ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ማተም ጀምራለች። ኔልሰን ሮህሊላ ማንዴላ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው ፣ ኅዳር 26 ቀን 2006 (ዲሴምበር 5 ቀን 2013) በወዳጅ ዘመድና ቤተሰብ ተከበው አረፉ። ማንዴላ ዛሬ በህይወት የሉም፣ በሁሉም ሰው ህሊና ውስጥ ግን ታላቅ ስብዕናቸው ለዘላለም ይኖራል።
ውድ የቻናላችን ተከታታዬች በተብራራ መልኩ በኔል ሰን ማንዴላ የህይወት ታርክ ዙርያ የተፃፈውን
LONG WALK TO FREEDOM በ PDF
ቀርቦላችኋል መልካም ንባብ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
❤2👍1
Forwarded from MarkdownBot
💉💉💉💉💉💉💉💉💉💉💉💉
ስለጤና ምን ማወቅ ይፈልጋሉ? ሁላችንም ማውቅ የሚገባን
💊..ስለ ደም ግፊት
💊..ስለ ደም ማነስ
💊..ስለ ስኳር በሽታ
💊 ..ስለ አስም...........እና ሌሎችንም የጤና የተብራራ መረጃ ከፈለጉ⤵️
OPEN የሚለውን መጫን በቂ ነው.....መልካም ጤና..
➷➷➷➷➷
➻ open & join
➻ open & join
➻ open & join
➹➹➹➹➹➹
ስለጤና ምን ማወቅ ይፈልጋሉ? ሁላችንም ማውቅ የሚገባን
💊..ስለ ደም ግፊት
💊..ስለ ደም ማነስ
💊..ስለ ስኳር በሽታ
💊 ..ስለ አስም...........እና ሌሎችንም የጤና የተብራራ መረጃ ከፈለጉ⤵️
OPEN የሚለውን መጫን በቂ ነው.....መልካም ጤና..
➷➷➷➷➷
➻ open & join
➻ open & join
➻ open & join
➹➹➹➹➹➹
👍2
ከድር ሚስት ማግኘት አቃተው፡፡ ሞከረ... ሞከረ..... ሊሳካልት
አልቻለም፡፡ ወደ ፈጣሪው እያለቀሰ ለመነ፡፡ አሁንም ሊሳካለት
አልቻለም፡፡ ተስፋ ቆረጠ፡፡ እራሱን ለማጥፋት ወሰነ፡፡ ከእለታት
በአንዱ ምሽት የመታነቂያ ገመድ ለመግዛት ሰፈር ውስጥ ወዳለች
ትንሽዬ ሱቅ በዝግታ አዘገመ፡፡ ሱቅ ሲደርስ ሱቅ ውስጥ ማንም
የለም፡፡
:
"ባለሱቅ" ብሎ ተጣራ አንገቱን ወደ ታች ደፍቶ መሬት መሬቱን
እያየ፡፡ ቆንጅዬዋ ባለሱቅ በብርሀን ፍጥነት መጣች፡፡ "ምን
ልስጥህ ከድርዬ" አለችው
የሰማውን ቃል ማመን አቃተው.... ቀና ብሎ ልጅቷን አያት.....
ከጨረቃ የፈካ ውብ ፈገግታ በልጅቷ ገፅ ላይ ተመለከተ፡፡
"ከድርዬ" ብላ ስለጠራችው ተደነቀ፡፡ :
የመኖር ተስፍ በልቡ ውስጥ ሲቀጣጠል ተሰማው፡፡ እናም ገመድ
ሊገዛበት ባመጣው ብር ለእራት የሚሆነውን እንጀራ ገዝቶ
ተመለሰ፡፡ ወደ ቤቱ ገባ፡፡ እራቱን በልቶ አልጋው ላይ ወደቀ፡፡ "ምን
ልስጥህ ከድርዬ" የሚለው የልጅቷ ድምፅ አይምሮ ውስጥ
አቃጨለበት፡፡ የዛን ቀን ማታ ከወትሮው በተለየ መልኩ በተስፍ
ተሞልቶ ስለነገ እያሰበ ሳለ..... ድንገት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ
ወሰደው፡፡
:
ይህ ሰው ባለሱቋ ስሙን አቆላምጣ ስለጠራችው ብቻ የመሞት
ውሳኔውን አስቀየረችው፡፡ ሁላችንም ከአፋችን ለምናወጣው ቃል
እንጠንቀቅ፡፡ አንድ ጥሩ ቃል በተናገርን ቁጥር ምናልባትም
የአንድን ሰው በህይወት የመኖር ተስፋ እናለመልም ይሆናል፡፡
አልቻለም፡፡ ወደ ፈጣሪው እያለቀሰ ለመነ፡፡ አሁንም ሊሳካለት
አልቻለም፡፡ ተስፋ ቆረጠ፡፡ እራሱን ለማጥፋት ወሰነ፡፡ ከእለታት
በአንዱ ምሽት የመታነቂያ ገመድ ለመግዛት ሰፈር ውስጥ ወዳለች
ትንሽዬ ሱቅ በዝግታ አዘገመ፡፡ ሱቅ ሲደርስ ሱቅ ውስጥ ማንም
የለም፡፡
:
"ባለሱቅ" ብሎ ተጣራ አንገቱን ወደ ታች ደፍቶ መሬት መሬቱን
እያየ፡፡ ቆንጅዬዋ ባለሱቅ በብርሀን ፍጥነት መጣች፡፡ "ምን
ልስጥህ ከድርዬ" አለችው
የሰማውን ቃል ማመን አቃተው.... ቀና ብሎ ልጅቷን አያት.....
ከጨረቃ የፈካ ውብ ፈገግታ በልጅቷ ገፅ ላይ ተመለከተ፡፡
"ከድርዬ" ብላ ስለጠራችው ተደነቀ፡፡ :
የመኖር ተስፍ በልቡ ውስጥ ሲቀጣጠል ተሰማው፡፡ እናም ገመድ
ሊገዛበት ባመጣው ብር ለእራት የሚሆነውን እንጀራ ገዝቶ
ተመለሰ፡፡ ወደ ቤቱ ገባ፡፡ እራቱን በልቶ አልጋው ላይ ወደቀ፡፡ "ምን
ልስጥህ ከድርዬ" የሚለው የልጅቷ ድምፅ አይምሮ ውስጥ
አቃጨለበት፡፡ የዛን ቀን ማታ ከወትሮው በተለየ መልኩ በተስፍ
ተሞልቶ ስለነገ እያሰበ ሳለ..... ድንገት ጭልጥ ያለ እንቅልፍ
ወሰደው፡፡
:
ይህ ሰው ባለሱቋ ስሙን አቆላምጣ ስለጠራችው ብቻ የመሞት
ውሳኔውን አስቀየረችው፡፡ ሁላችንም ከአፋችን ለምናወጣው ቃል
እንጠንቀቅ፡፡ አንድ ጥሩ ቃል በተናገርን ቁጥር ምናልባትም
የአንድን ሰው በህይወት የመኖር ተስፋ እናለመልም ይሆናል፡፡
👍8
#እመኚኝ !
ነይ ግቢ በሞቴ
እቤት ማንም የለም
የለችም እናቴ
እመኚኝ ግዴለም
ምንም አናደርግም
ወደ ውስጥ ገብተሽ
በሩን ብዘጋውም
አንድ ላይ ተቀምጠን
አብረን ብናወጋም
ከንፈርሽን ልስም
ወዳንቺ ብጠጋም
ብስምሽም እንኳን
ስጋት እንዳገባሽ ምንም አናደርግም... በፀጉሮችሽ መሃል
ጣቴን ባንሸራሽር
ጠረንሽን ቢሸተኝ
ገብቼ አንገትሽ ስር
እጄ ሚይዘው አጥቶ
ጡትሽን ቢነካካ እየጨባበጠ
መጠኑን ቢለካ
እንዳትጠረጥሪኝ ለሌላ
እንዳይመስልሽ ውዴ
ሙች እመኚኝ...
.
.
.
በዚህ ሁሉ መሃል በስሜት
ገንፍዬ ልብስሽን ባወልቅም
ልብሴን ወዲያ ጥዬ
እርቃንሽን ሆነሽ እርቃኔንም ሆኜ
አልጋው ላይ ብጥልሽ
በክንዴ ዘግኜ በሚገርም ሁኔታ
ፍቅር ብንሰራም እመኚኝ አለሜ
እኔ ልሙትልሽ
ምንም አናደርግም
ነይ ግቢ በሞቴ
እቤት ማንም የለም
የለችም እናቴ
እመኚኝ ግዴለም
ምንም አናደርግም
ወደ ውስጥ ገብተሽ
በሩን ብዘጋውም
አንድ ላይ ተቀምጠን
አብረን ብናወጋም
ከንፈርሽን ልስም
ወዳንቺ ብጠጋም
ብስምሽም እንኳን
ስጋት እንዳገባሽ ምንም አናደርግም... በፀጉሮችሽ መሃል
ጣቴን ባንሸራሽር
ጠረንሽን ቢሸተኝ
ገብቼ አንገትሽ ስር
እጄ ሚይዘው አጥቶ
ጡትሽን ቢነካካ እየጨባበጠ
መጠኑን ቢለካ
እንዳትጠረጥሪኝ ለሌላ
እንዳይመስልሽ ውዴ
ሙች እመኚኝ...
.
.
.
በዚህ ሁሉ መሃል በስሜት
ገንፍዬ ልብስሽን ባወልቅም
ልብሴን ወዲያ ጥዬ
እርቃንሽን ሆነሽ እርቃኔንም ሆኜ
አልጋው ላይ ብጥልሽ
በክንዴ ዘግኜ በሚገርም ሁኔታ
ፍቅር ብንሰራም እመኚኝ አለሜ
እኔ ልሙትልሽ
ምንም አናደርግም
👍3😁3
የ'አዲስ ዘመን ዜማ!!
.
በ'አይኔ በራፍ ላይ ..
የ'ሆነ አይነት ደስታ .. ሲያልፍ ይታየኛል
በ'ጆሮዬ ሽንቁር
የ'ነፃነት ድምፀት ... ጥሪው ይሰማኛል
ተራራ እና መስኩን
የ'ሞላው አበባ .. ቀልቤን ቀልብ ነስቶ
አያለሁ ሲጣራ
ተፈጥሮ በኩራት .. ጭጋ'ጉን አፅድቶ
.
እዚያ'ጋ ..
እረኛው በዋሽንት
ፍቅሩን እያሰበ .. .. በ'ዜማው ሲጣራ
ስንኞች ሰድሮ
ዜማ እየቀመረ .. .. ሙዚቃ ሲሰራ
በሙዚቃው ቅኝት
ዘመን ይሉት ብርኃን ... ይታያል ሲበራ
.
እዚህ'ጋ ..
ልጃ'ገረድ ሴቶች
በ'ወግ የሀገር ልብስ .. ደምቀው እና አማምረው
የልጅነትን ጌጥ
ባ'ንዲት ከበሮ ምት .. .. .. .. ...ፈገግታ ኣጭረው
"አበባ አየህ .. " ሊሉ
ከ'ዘመን በረከት .. .. አደይዋ'ን ሲቀጥፉ
ይታያል!
ኣይናቸው ሰማይ ላይ .. ዘመን'ን ሲያነጥፉ
.
.
አለ አይደል!
.
ከንፈሯ ላይ ታመህ
እ'ጭኗ ስር ሞተህ
ዳግም ልትኖረው
በ'ትንሳኤ ፍቅሯ .. የምትዘራው ህይወት?
ኣለ ኣይድል!
በዝምታዋ ውስጥ
ቃሏን እያደመጥህ
ከ'እስትፋንሷ ሃቂቃ
በ'ሚወጡ ቃላት ..የ'ምትቀብረው ስሜት?
.
.
(አውውውውውውው !!!
ይሄም እንደዚያው ነው!)
.
ጎርፍ ያመሰው መንደር
እርጋታ ተሞልቶ .. .. .. .. ከ'ክብሩ ሲመለስ
ሰማይ ቁጣው በርዶ
የ'ሰላሙ ነፋስ .. .. .. ምድሪቱ ላይ ሲነፍስ
ያኔ .. ይታወቃኛል!
ያ'ዲስ ዘመን ዜማ
በ'ውብ የ'ተስፋ ቃል ይቀሰቅሰኛል!
.
.
.
መልካም ቅዳሜ ይሁንላቹ የኔ ምርጦች !
(ከሰማይ ወገብ ስር .. )
.
በ'አይኔ በራፍ ላይ ..
የ'ሆነ አይነት ደስታ .. ሲያልፍ ይታየኛል
በ'ጆሮዬ ሽንቁር
የ'ነፃነት ድምፀት ... ጥሪው ይሰማኛል
ተራራ እና መስኩን
የ'ሞላው አበባ .. ቀልቤን ቀልብ ነስቶ
አያለሁ ሲጣራ
ተፈጥሮ በኩራት .. ጭጋ'ጉን አፅድቶ
.
እዚያ'ጋ ..
እረኛው በዋሽንት
ፍቅሩን እያሰበ .. .. በ'ዜማው ሲጣራ
ስንኞች ሰድሮ
ዜማ እየቀመረ .. .. ሙዚቃ ሲሰራ
በሙዚቃው ቅኝት
ዘመን ይሉት ብርኃን ... ይታያል ሲበራ
.
እዚህ'ጋ ..
ልጃ'ገረድ ሴቶች
በ'ወግ የሀገር ልብስ .. ደምቀው እና አማምረው
የልጅነትን ጌጥ
ባ'ንዲት ከበሮ ምት .. .. .. .. ...ፈገግታ ኣጭረው
"አበባ አየህ .. " ሊሉ
ከ'ዘመን በረከት .. .. አደይዋ'ን ሲቀጥፉ
ይታያል!
ኣይናቸው ሰማይ ላይ .. ዘመን'ን ሲያነጥፉ
.
.
አለ አይደል!
.
ከንፈሯ ላይ ታመህ
እ'ጭኗ ስር ሞተህ
ዳግም ልትኖረው
በ'ትንሳኤ ፍቅሯ .. የምትዘራው ህይወት?
ኣለ ኣይድል!
በዝምታዋ ውስጥ
ቃሏን እያደመጥህ
ከ'እስትፋንሷ ሃቂቃ
በ'ሚወጡ ቃላት ..የ'ምትቀብረው ስሜት?
.
.
(አውውውውውውው !!!
ይሄም እንደዚያው ነው!)
.
ጎርፍ ያመሰው መንደር
እርጋታ ተሞልቶ .. .. .. .. ከ'ክብሩ ሲመለስ
ሰማይ ቁጣው በርዶ
የ'ሰላሙ ነፋስ .. .. .. ምድሪቱ ላይ ሲነፍስ
ያኔ .. ይታወቃኛል!
ያ'ዲስ ዘመን ዜማ
በ'ውብ የ'ተስፋ ቃል ይቀሰቅሰኛል!
.
.
.
መልካም ቅዳሜ ይሁንላቹ የኔ ምርጦች !
(ከሰማይ ወገብ ስር .. )
...ትንሽ ቦት...
በዚህ አመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ትንሽ በታ መጠለያ
ትንሽ ቦታ መሰደጃ
ምናለበት፣
ለምን አልባት ብንተውለት
ፍፁም መሆን ስለማንችል
ትንሽ ባዶ እንዋዋል፣በልባችን ደግ በኩል
በአንጎላችን መላወሻ
ትንሽ ቦታ እንተውለት
"ምን አልባት" የምንልበት
ልክ እንደ አምና ለዚህ አመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሰር ይቅር ማያ
ይቅር ብንል መታሰሪያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ
ጥግ ድረስ ባለን ስፍራ ጥግ ድረስ የለም ፋታ
በልባችን ደግ በኩል እንፈልግ ባዶ ቦታ
የጳጉሜ አይነት ትንሽ ቦታ
ለዘመን መለወጫ።
በነብይ መኮነን
በዚህ አመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ትንሽ በታ መጠለያ
ትንሽ ቦታ መሰደጃ
ምናለበት፣
ለምን አልባት ብንተውለት
ፍፁም መሆን ስለማንችል
ትንሽ ባዶ እንዋዋል፣በልባችን ደግ በኩል
በአንጎላችን መላወሻ
ትንሽ ቦታ እንተውለት
"ምን አልባት" የምንልበት
ልክ እንደ አምና ለዚህ አመት
ብንጣላ መታረቂያ
ብንታረቅ ለመጣያ
ብንታሰር ይቅር ማያ
ይቅር ብንል መታሰሪያ
ትንሽ እንተው ባዶ ቦታ
ጥግ ድረስ ባለን ስፍራ ጥግ ድረስ የለም ፋታ
በልባችን ደግ በኩል እንፈልግ ባዶ ቦታ
የጳጉሜ አይነት ትንሽ ቦታ
ለዘመን መለወጫ።
በነብይ መኮነን
👍1
የባከነ ሌሊት!!!!
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ::
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ::
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው::
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ::
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ::
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::
በውቀቱ ስዩም
ወይ ሮንድ አላደርኩ
ወይ ኮኮብ አልቆጠርኩ
ወይ ደልቶኝ አልጨፈርሁ
ወይ ውስኪ አልተዳፈርሁ
የባለጌ ወንበር :ኮርቻ አልተሳፈርሁ
ወይ ሰአታት ቁሜ
ቤተክስያን ስሜ
ሰይጣን አላሳፈርሁ::
ሌቦች ደብድበውት
አንዱን ምስኪን ላሥር
ባምቢስ ድልድዩ ሥር
ቆስሎ የወደቀ
ገላው በላዩ ላይ :እንደጨርቅ ያለቀ
ፊቱ ተሸፍኖ : በደምና አቧራ
"በኡራኤል ርዱኝ " ብሎ የሚጣራ
ምስኪን አባወራ
ብብት ሥር ገብቼ
አፋፍሼ አንስቼ
ተሸክሜ አድኜ
ስፈልግ አምቡላንስ :ሲሻኝ ዶክተር ሁኜ
ወይ ምግባር አልሠራሁ
ወይ ጀብድ አልፍፀምኩኝ : ወይ ፅድቅ አላፈራሁ::
አንድ በትረ-ሙሴ
ሁለት ስስ አሎሎ
ከጭኔ መሀከል ሲያመሽ ተንጠልጥሎ
ሲባክን ዝምብሎ
" እሸኝ የኔ ጀግና እንደሰነፍ ቆሎ"
የምትል መለሎ
ልቤን ሳትሰውረው
አልጋየን ሳትሰብረው::
ወግ ቢጤ ሞንጭሬ: ፌስቡክ ላይ ሳለጥፍ
" እናትዋን ጨረቃ" የሚል ግጥም ሳልጥፍ::
አንዲት ሴት- አዳሪ :ቺቺንያ ምንገድ ላይ
እድሉዋ ሰባራ :ሰውነቱዋ አማላይ
ካፍያውና እንባዋ : ተጋግዞ ሚያረጥባት
ደምበኛ ስትጠበቅ :ደመኛ ጥሎባት
አምስት ደፋሪዎች : ከበው ሲያዋክቧት
ሲገፉ ሲስቧት
" እረ በናታችሁ በወላድ ማህፀን
እህት የላችሁም?" ብላ ስትማፀን
ልመናዋ ስቦኝ
እንዳበጀ በለው : በደሏ አንገብግቦኝ
ከሁዋላ ደርሼ
ነበልባል ለብሼ: ነበልባል ጎርሼ
እንደብሩስሊ: እንዳየሩ ጋኔን
እግሬን ወንጨፍ ወንጨፍ
ወዝወዝ ወዝወዝ ጎኔን
በማረግ ቃኝቼ
ከሁዋላ ነው ሲሉኝ ከፊት ተገኝቼ
ካምስቱ መከከል አራቱን ነጥየ
ከቻልኩ በካራቲ ካልቻልኩ በሳቅ ጥየ::
ድል ሳላስመዘግብ
ውጥረት ሳለረግብ
ወይ ታሪክ ሳልሰራ -ወይ ታሪክ ሳልዘግብ
ያለምንም ጣጣ : ያለምንም ፀጋ
አለሰበብ መሽቶ አለሰበብ ነጋ::
በውቀቱ ስዩም
👍1👏1
#አንቺ #ሰትስሚኝ😘
የምትዞርው አለም ባንዴ ትቆማለች
እሩቁዋ ጨርቃ ያኔ ትቀርባለች
ምድርም የዛኔ በእኛ ትደምቃለች ........................ ታሸበርቃለች
ልጆችዋ ነን እና እኛን ትድራለች አንቺ ሰትስሚኝ!!!!! ከተራራ እንደ መውደቅ ሰልጣን እንደ መልቀቅ ተሰቅሎ እንደ መታነቅ ሱሪ እንደ መውለቅ
ነብሴ ትጨነቃለች ልቤ ትመታለች አንቺን አንቺን ፍቅርን ትፈራለች አንቺ ሰትስሚኝ!!!!! ሞቶ እንደ መነሳት የወደቀ እንደ ማንሳት በጥይት እንደ መሳት ችግር እንደ መርሳት
ህይወቴ ታድሳ ብሩህ ትሆናለች
ጎዶሎዋ አለም ያኔ ትሞላለች አንቺ ሰትስሚኝ!!!!
ወፎች ያዜማሉ ኮዋክብት ይርግፍሉ
አማልክት ይወርዳሉ አራዊት ይታደማሉ
መንግሰታት መግደል ያቆማሉ ................ታክሲዋች ይጭናሉ ...............አዋቂዋች ይታዘላሉ
.................ነጋዴዋች ያተርፋሉ አንቺ ሰትስሚኝ!!!! ጽልመት ይባርራል ሰልጣንም ያርጃል
ህፃን ልጅም ያድጋል ግጥምም ያልቃል
የምትዞርው አለም ባንዴ ትቆማለች
እሩቁዋ ጨርቃ ያኔ ትቀርባለች
ምድርም የዛኔ በእኛ ትደምቃለች ........................ ታሸበርቃለች
ልጆችዋ ነን እና እኛን ትድራለች አንቺ ሰትስሚኝ!!!!! ከተራራ እንደ መውደቅ ሰልጣን እንደ መልቀቅ ተሰቅሎ እንደ መታነቅ ሱሪ እንደ መውለቅ
ነብሴ ትጨነቃለች ልቤ ትመታለች አንቺን አንቺን ፍቅርን ትፈራለች አንቺ ሰትስሚኝ!!!!! ሞቶ እንደ መነሳት የወደቀ እንደ ማንሳት በጥይት እንደ መሳት ችግር እንደ መርሳት
ህይወቴ ታድሳ ብሩህ ትሆናለች
ጎዶሎዋ አለም ያኔ ትሞላለች አንቺ ሰትስሚኝ!!!!
ወፎች ያዜማሉ ኮዋክብት ይርግፍሉ
አማልክት ይወርዳሉ አራዊት ይታደማሉ
መንግሰታት መግደል ያቆማሉ ................ታክሲዋች ይጭናሉ ...............አዋቂዋች ይታዘላሉ
.................ነጋዴዋች ያተርፋሉ አንቺ ሰትስሚኝ!!!! ጽልመት ይባርራል ሰልጣንም ያርጃል
ህፃን ልጅም ያድጋል ግጥምም ያልቃል
ውድ የቻናላችን ተከታዮች በዳንኤል ሰቲል ተፅፎ በአብይ ደምሴ የተተረጎመውን ብርቅርቅታ የተሰኘውን ቆየት ያለ መፅሐፍ ያላነበበው ካለ ሙሉውን በPdf ቀርቦላችኋል መልካም ንባብ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
አዝዤ ልጎርሰው፥
ያጠቀስኩት ሽሮ፥ አፌን ገፍቶ ይርቃል
ማባያ የሰነግኩት፥
አረንጓዴ ቃርያ፥ በቅፅበት ይደርቃል
እንደ በረኅ ምድር፥
እንጀራዬ ከስሎ፥ ይሰነጣጠቃል።
ጆሮዬ ከፒያሳ፥
ቦሌ እሚንቆረቆር፥ ይሰማዋል ድራፍት
አይኔ ካራት ኪሎ፥
ቄራ የሚፈረሽ፥ ይታየዋል ፍትፍት።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
ያበዳሪን ሰፈር፥
በጀግና አረማመድ፥ ሄዳለሁ ሰንጥቄ
የቡቲኩን ጌታ፥
የጃኬቱን ዋጋ፥ አልፋለሁ ጠይቄ
ስቸስት የከዳኝ፥
ወዳጄን ፈልጌ፥ አልሳለሁ ጥፊ
እንዳያዩኝ ብዬ፥
ከተደበቅኋቸው፥
ካ'ከራዬ ጋራ፥ እነሳለሁ ሰልፊ።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
ኤድናሞል ደጃፍ፥ ላይ እንጎራደዳለሁ...
ቮድካ እንኳ ባይገኝ፥
የሜንት ያ'ፕሬቲቭ፥ ቦትል አወርዳለሁ
ባለረዥም ፀጉር፥
ባለ ለስላሳ ድምፅ፥ ባለ አይን ባለ አንገት
እያልኩ የተውኳቸው፥
የቸከሶቼ ስልክ፥ ትዝ ይለኛል ድንገት።
ፀሃይ ሲያዘቀዝቅ፥
እያንገሸገሸኝ፥
እያንቀጠቀጠኝ፥ ፀጥ ያለው ሰፈሬ
ወደ ሃያሁለት፥
ቦሌ መድሃኒያለም፥
ወደ አትላስ ጀርባ፥ይመራኛል እግሬ።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
አዝዤ ልጎርሰው፥
ያጠቀስኩት ሽሮ፥ አፌን ገፍቶ ይርቃል
ማባያ የሰነግኩት፥
አረንጓዴ ቃርያ፥ በቅፅበት ይደርቃል
እንደ በረኅ ምድር፥
እንጀራዬ ከስሎ፥ ይሰነጣጠቃል።
ጆሮዬ ከፒያሳ፥
ቦሌ እሚንቆረቆር፥ ይሰማዋል ድራፍት
አይኔ ካራት ኪሎ፥
ቄራ የሚፈረሽ፥ ይታየዋል ፍትፍት።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
ያበዳሪን ሰፈር፥
በጀግና አረማመድ፥ ሄዳለሁ ሰንጥቄ
የቡቲኩን ጌታ፥
የጃኬቱን ዋጋ፥ አልፋለሁ ጠይቄ
ስቸስት የከዳኝ፥
ወዳጄን ፈልጌ፥ አልሳለሁ ጥፊ
እንዳያዩኝ ብዬ፥
ከተደበቅኋቸው፥
ካ'ከራዬ ጋራ፥ እነሳለሁ ሰልፊ።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
.
.
ኤድናሞል ደጃፍ፥ ላይ እንጎራደዳለሁ...
ቮድካ እንኳ ባይገኝ፥
የሜንት ያ'ፕሬቲቭ፥ ቦትል አወርዳለሁ
ባለረዥም ፀጉር፥
ባለ ለስላሳ ድምፅ፥ ባለ አይን ባለ አንገት
እያልኩ የተውኳቸው፥
የቸከሶቼ ስልክ፥ ትዝ ይለኛል ድንገት።
ፀሃይ ሲያዘቀዝቅ፥
እያንገሸገሸኝ፥
እያንቀጠቀጠኝ፥ ፀጥ ያለው ሰፈሬ
ወደ ሃያሁለት፥
ቦሌ መድሃኒያለም፥
ወደ አትላስ ጀርባ፥ይመራኛል እግሬ።
.
.
<<ደሞዝ ወጥቷል>> የሚል፥
ሜሴጅ የገባ ቀን፥ እንዲህ ያደርገኛል
👍4
፨ዘመም ይላል እንጂ፨
እንደ ጊዜው መክፋት
እንደ ግፉ መስፋት
እንዳገሩ ክስመት
እንዳገሬው ጥመት
እንደሰው ጭካኔ፤ እንደ ልቡ ፍሬ
ታምር ነው መትረፍሽ ፤ ታምር ነው መኖሬ::
የበጎ ሰው ሀሳብ ፤ ሲካድ እለት በለት
ጉድጏድ ተምሶለት
ሰብእና ሲቀበር፤
በዚህ ምድር መኖር ፤ አያስመኝም ነበር::
ምድሩ ሳር ቅጠሉ፤ በስጋት ተሞልቶ
የማለዳው ሰማይ፤ እንዳንቀልባ ቀልቶ
ታረደ
ነደደ
ከዘብጥያ ወጥቶ
ዘብጥያ ወረደ
የሚል ዜና ብቻ አየሩን ሲሞላው
ሰው በገዛ ጥላው
በርግጎ ሲሸበር
በዚህ ምድር መኖር ፤አያስመኝም ነበር::
አዎ
ለጊዜውም ቢሆን፤ ግፍ ያደነዝዛል
በደል ያስተክዛል
ጊዜም ጠብን ሽሮ፤ ወደ ፊት ይጏዛል
በልብ ሰሌዳ ላይ ፤ቂም ይደበዝዛል
በነገ ያመነ
ልጁን ቀብሮ መጥቶ፤ ሚስቱን ያስረግዛል::
ይቅርታና ምህረት
ፍቅርና ህብረት
ከግፍ ጋር ፍልሚያቸው ፤ ቢሆን የሞት ሽረት
ዳገት ይወጣሉ ፤ በንጥፍጣፊ አቅም
የመኖር ፍላጎት
ዘመም ይላል እንጂ ፤ ተገርስሶ አይወድቅም::
((በውቀቱ ስዩም))
እንደ ጊዜው መክፋት
እንደ ግፉ መስፋት
እንዳገሩ ክስመት
እንዳገሬው ጥመት
እንደሰው ጭካኔ፤ እንደ ልቡ ፍሬ
ታምር ነው መትረፍሽ ፤ ታምር ነው መኖሬ::
የበጎ ሰው ሀሳብ ፤ ሲካድ እለት በለት
ጉድጏድ ተምሶለት
ሰብእና ሲቀበር፤
በዚህ ምድር መኖር ፤ አያስመኝም ነበር::
ምድሩ ሳር ቅጠሉ፤ በስጋት ተሞልቶ
የማለዳው ሰማይ፤ እንዳንቀልባ ቀልቶ
ታረደ
ነደደ
ከዘብጥያ ወጥቶ
ዘብጥያ ወረደ
የሚል ዜና ብቻ አየሩን ሲሞላው
ሰው በገዛ ጥላው
በርግጎ ሲሸበር
በዚህ ምድር መኖር ፤አያስመኝም ነበር::
አዎ
ለጊዜውም ቢሆን፤ ግፍ ያደነዝዛል
በደል ያስተክዛል
ጊዜም ጠብን ሽሮ፤ ወደ ፊት ይጏዛል
በልብ ሰሌዳ ላይ ፤ቂም ይደበዝዛል
በነገ ያመነ
ልጁን ቀብሮ መጥቶ፤ ሚስቱን ያስረግዛል::
ይቅርታና ምህረት
ፍቅርና ህብረት
ከግፍ ጋር ፍልሚያቸው ፤ ቢሆን የሞት ሽረት
ዳገት ይወጣሉ ፤ በንጥፍጣፊ አቅም
የመኖር ፍላጎት
ዘመም ይላል እንጂ ፤ ተገርስሶ አይወድቅም::
((በውቀቱ ስዩም))
#የማሪያም #ንግስ #ዕለት
.
.
.
የማርያም ንግስለት
አዳፋ ነጠላ
በቀጠነ ገላ ÷ነፋስ የሚጥለው
የነተበ ጫማ
ጥቁር ያዘን ቀሚስ ÷ኑሮ ያጨቀየው
ለብሳ የተገኘች ,,,,,,
ከቤተስኪያን አጸድ —ቆማ ከዋርካውስር
አንዲት ምስኪን ባልቴት —,,,,,ትለማመንነበር
አደራሽ ን ማርያም
አደራሽን ማርያም
እበላው የለኝ መሶ ቤ ተራቁቷል
እለብሰው የለኝም ጀረረባዬ በርዶታል ።
ወድቃ የተነሳች
እንባ ያፈሰሰች
ተስፋዋ ማርያምን ትለምናት ነበር
ከቤተስኪያን ጓሮ ቆማ ከዋርካው ስር ።
*
የደብሩ አለቃ
ካ ባ ላንቃ ለብሶ ሞጣህቱን ደርቦ
ልክ የሌለው ቦርጬ ወደፊት ተስቦ
ጮክ ብሎ ያወራል
ጮክብሎ ያስተምራል ።
1
የመቅደሱ ቀለም ሊታደስ ይገባል
2
የካህናት ደሞዝ ሊጨመር ይገባል
3
ደጀ ሰላም ወንበር እጅጉን ያንሰናል ,,,,
እናም ,,,
በዚህ ታላቅ ደብር ይህ ችግር ስላለ
ለማርያም የሚሆን እ ጃችሁ የታለ ?
እያለ ።,,,,
ህዝቡን ያስተምራል
ህዝቡን ይደልላል ።
ለንግሱ የመጡ
ባለ ብዙ ብሮች
ብዙ ባለጠጎች
ጥለት የለበሱ በሽቶ የራሱ
ቆመው የነበሩ እፊት ተመቅደሱ
ቀለም እንዲቀባ እንዲታደስ ደብሩ
ለደጀ ሰላሙ ደግሞም ለወንበሩ
በ ሺ ሚቆጠሩ
ብሮች ወረወሩ
የደብሩ አለቃ ግንባር በጣም ወዛ
የሚወረው ብሩም በጣም በዛ
*
የዛች የየምስኪን ነብስ
ያቺ ታላቅ መቅደስ
ቆማ ከዋርካስር
ተስፋዋ ማርያምን ትለማመን ነበር
አደራሽን ማርያም
አደራሽን ማርያም
እበላው የለኝም መሶቤ ተራቁቷል
እጠጣው የለኘኝም ማድጋዬ ጓድሏል
እለብሰው የለኝም ጀርባዬን በርዶታል
አንቺው ነሽ ተስፋዬ የኔ ተስፋ ሞቷል
ወድቃ የተነሳች
እንባ ያፈሰሰች ።
ግና —ግን ለዛሬ —ለክብርሽ እንዲሆን
ተቀበይ ስጦታ ውሰጅ አማሀዬን
የሟች ባሌን ማስታወሻ የአንገት ሃብሌን፡፡
በኤፍሬም ስዩም
.
.
.
የማርያም ንግስለት
አዳፋ ነጠላ
በቀጠነ ገላ ÷ነፋስ የሚጥለው
የነተበ ጫማ
ጥቁር ያዘን ቀሚስ ÷ኑሮ ያጨቀየው
ለብሳ የተገኘች ,,,,,,
ከቤተስኪያን አጸድ —ቆማ ከዋርካውስር
አንዲት ምስኪን ባልቴት —,,,,,ትለማመንነበር
አደራሽ ን ማርያም
አደራሽን ማርያም
እበላው የለኝ መሶ ቤ ተራቁቷል
እለብሰው የለኝም ጀረረባዬ በርዶታል ።
ወድቃ የተነሳች
እንባ ያፈሰሰች
ተስፋዋ ማርያምን ትለምናት ነበር
ከቤተስኪያን ጓሮ ቆማ ከዋርካው ስር ።
*
የደብሩ አለቃ
ካ ባ ላንቃ ለብሶ ሞጣህቱን ደርቦ
ልክ የሌለው ቦርጬ ወደፊት ተስቦ
ጮክ ብሎ ያወራል
ጮክብሎ ያስተምራል ።
1
የመቅደሱ ቀለም ሊታደስ ይገባል
2
የካህናት ደሞዝ ሊጨመር ይገባል
3
ደጀ ሰላም ወንበር እጅጉን ያንሰናል ,,,,
እናም ,,,
በዚህ ታላቅ ደብር ይህ ችግር ስላለ
ለማርያም የሚሆን እ ጃችሁ የታለ ?
እያለ ።,,,,
ህዝቡን ያስተምራል
ህዝቡን ይደልላል ።
ለንግሱ የመጡ
ባለ ብዙ ብሮች
ብዙ ባለጠጎች
ጥለት የለበሱ በሽቶ የራሱ
ቆመው የነበሩ እፊት ተመቅደሱ
ቀለም እንዲቀባ እንዲታደስ ደብሩ
ለደጀ ሰላሙ ደግሞም ለወንበሩ
በ ሺ ሚቆጠሩ
ብሮች ወረወሩ
የደብሩ አለቃ ግንባር በጣም ወዛ
የሚወረው ብሩም በጣም በዛ
*
የዛች የየምስኪን ነብስ
ያቺ ታላቅ መቅደስ
ቆማ ከዋርካስር
ተስፋዋ ማርያምን ትለማመን ነበር
አደራሽን ማርያም
አደራሽን ማርያም
እበላው የለኝም መሶቤ ተራቁቷል
እጠጣው የለኘኝም ማድጋዬ ጓድሏል
እለብሰው የለኝም ጀርባዬን በርዶታል
አንቺው ነሽ ተስፋዬ የኔ ተስፋ ሞቷል
ወድቃ የተነሳች
እንባ ያፈሰሰች ።
ግና —ግን ለዛሬ —ለክብርሽ እንዲሆን
ተቀበይ ስጦታ ውሰጅ አማሀዬን
የሟች ባሌን ማስታወሻ የአንገት ሃብሌን፡፡
በኤፍሬም ስዩም
👍3
😁ደስታን ፍለጋ😁
በግምት ወደ 50 ሰው የሚይዝ ህብረት በአንድ አዳራሽ ለጥብቅ ጉዳይ ይሰባሰባሉ::ፕሮግራሙ ከመጀመሩ በፊት መድረክ መሪው ታዳሚዎችን አንድ ጫወታ ሊያጫውት ይወስናል::በአዳራሹ ለተሰበሰቡ ሰዎች አንዳንድ ፊኛ ሰጥቷቸው ስማቸውን በእስክሪብቶ ፊኛው ላይ እንዲፅፉበት ያዛቸዋል::
ሁሉም ፅፈው ከጨረሱ በሁዋላ ፊኛው ተሰብስቦ በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ ተበታትኖ እንዲቀመጥ ያደርጋል::በመቀጠል ጫወታው በ5 ደቂቃ ጠባቧ ክፍል ውስጥ ተበታትኖ ከተቀመጠው ፊኛ እያንዳንዳቸው ስማቸው የተፃፈበትን ፊኛ አግኝቶ መመለስ ነው ተባለ::በቅፅበት ያቺ ክፍል ስማቸውን በሚፈልጉ ታዳሚዎች ትርምስምስዋ ወጣ::ነገር ግን በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ትዕዛዙን ተግብሮ ስሙን ያገኘ አንድ እንኳን አልነበረም::የጫወታው አስተባባሪም ከመድረክ ወጥቶ 1 ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ለሀምሳዎቹም ፊኛቸው ስማቸውን እየጠራ መለሰ:: ደስታም እንዲህ ናት::በዚህች ጠባብ እና በማይሞላላት አለም ትውልድ ከሌላው ይልቅ የራሱን ደስታ ፍለጋ ይተራመሳል!!
ነገር የደስታን መገኛ በቅጡ አላወቀም::
አትጠራጠሩ በክፍሉ ውስጥ መጀመርያ ያገኙትን ፊኛ ለስሙ ባለቤት እየጠሩ ቢሰጣጡ ልክ እንደመድረኩ 1 ደቂቃ አይፈጅባቸውም ነበር::
ስለዚህ የእርሶን ደስታ ማግኘት ይሻሉ ??
የሌላ ሰው ደስታ በእጅዎ ነውና ይመልሱ ያን ጊዜ የእርሶ የሆነ ነገር ወደ እጅዎ ለመግባ ጊዜ አይፈጅም!!! ደስተኛ ቀን ተመኘሁ
በግምት ወደ 50 ሰው የሚይዝ ህብረት በአንድ አዳራሽ ለጥብቅ ጉዳይ ይሰባሰባሉ::ፕሮግራሙ ከመጀመሩ በፊት መድረክ መሪው ታዳሚዎችን አንድ ጫወታ ሊያጫውት ይወስናል::በአዳራሹ ለተሰበሰቡ ሰዎች አንዳንድ ፊኛ ሰጥቷቸው ስማቸውን በእስክሪብቶ ፊኛው ላይ እንዲፅፉበት ያዛቸዋል::
ሁሉም ፅፈው ከጨረሱ በሁዋላ ፊኛው ተሰብስቦ በአንድ ጠባብ ክፍል ውስጥ ተበታትኖ እንዲቀመጥ ያደርጋል::በመቀጠል ጫወታው በ5 ደቂቃ ጠባቧ ክፍል ውስጥ ተበታትኖ ከተቀመጠው ፊኛ እያንዳንዳቸው ስማቸው የተፃፈበትን ፊኛ አግኝቶ መመለስ ነው ተባለ::በቅፅበት ያቺ ክፍል ስማቸውን በሚፈልጉ ታዳሚዎች ትርምስምስዋ ወጣ::ነገር ግን በተሰጣቸው የጊዜ ገደብ ትዕዛዙን ተግብሮ ስሙን ያገኘ አንድ እንኳን አልነበረም::የጫወታው አስተባባሪም ከመድረክ ወጥቶ 1 ደቂቃ ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ለሀምሳዎቹም ፊኛቸው ስማቸውን እየጠራ መለሰ:: ደስታም እንዲህ ናት::በዚህች ጠባብ እና በማይሞላላት አለም ትውልድ ከሌላው ይልቅ የራሱን ደስታ ፍለጋ ይተራመሳል!!
ነገር የደስታን መገኛ በቅጡ አላወቀም::
አትጠራጠሩ በክፍሉ ውስጥ መጀመርያ ያገኙትን ፊኛ ለስሙ ባለቤት እየጠሩ ቢሰጣጡ ልክ እንደመድረኩ 1 ደቂቃ አይፈጅባቸውም ነበር::
ስለዚህ የእርሶን ደስታ ማግኘት ይሻሉ ??
የሌላ ሰው ደስታ በእጅዎ ነውና ይመልሱ ያን ጊዜ የእርሶ የሆነ ነገር ወደ እጅዎ ለመግባ ጊዜ አይፈጅም!!! ደስተኛ ቀን ተመኘሁ
👍2