#የኔልሰን #ሮህሊላ #ማንዴላ #አጭር #የህይወት #ታሪክ
ሮሊላሂላ ማንዴላ የተወለዱት ፣ ትራንስኪ በተባለው የደቡብ አፍሪካ ከተማ ጁላይ 18 ቀን 1918 ዓም ነው። ኔልሰን የሚለውን ስማቸውን ያገኙት ከጊዜ በኋላ ከአንድ አስተማሪያቸው እንደሆነ የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል። በተወለዱበት አካባቢ ባለው ቲምቡ ጎሳም በአካባቢው ሰው “ማዲባ” በሚል ስም ይጠራሉ።
አባታቸው ፣ ማንደላ የ 9 ዓመት ልጅ ሳሉ ነው የሞቱት። ማንዴላ 23 ዓመት ሲሞላቸው በጎሳው ደንብ መሰረት የሚመጣላቸውን ሚስት ላለማግባት ሲሉ ያደጉበትን ከተማ ትተው ወደ ጆሃንስበርግ ሄዱ።
በ 25 ዓመታቸው ዩኒቨርሲቲ በመግባት ማንዴላ በፎርት ሃሬ ዩኒቨርሲቲ እና በዊትዋተርስራንድ ዩኒቨርሲቲ ተምረው በ1942 በህግ ተመርቀዋል። በተመረቁ በሁለተኛው ዓመት የመጀመሪያ ሚስታቸው የሆኑትን ኤቪሊን ማሴ በማግባት አራት ልጆችን አፈሩ። በ1958 እስከተለያዩበት ቀን ድረስ አብረው ቆይተዋል። ከዚያ ፊታቸውን ወደ ትግሉ በማዞር የአፍሪካ ናሽናል ኮንግረስ በተባለው ፓርቲ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ መሆን ጀመሩ። በ1952 ማንዴላ የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳት በመሆን የአፓርታይድ ሥርዓትን በጽኑ መታገል ጀመሩ። በ1956 ማንዴላ በአገር ክህደት ወንጀል በጊዜው በነበረው የነጮች መንግስት ተከሰሱ- ክሱ አምስት ዓመት ያህል በክርክር ከቆየ በኋላ ማንዴላ በክርክሩ አሸነፉ።
በማርች ወር 1960 ዓም፣ ሻርፕቪል በተሰኘችው ከተማ ፣ ጸረ አፓርታይድ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ላይ ከነበሩት ጥቁር ሰልፈኞች መካከል 69 ያህሉን ፖሊሶች ተኩሰው በመግደላቸው ብጥብጡ ከፍ ያለ ደረጃ ደረስ። የወቅቱ መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ እንቅስቃሴ ሲከለክል እንደማንዴላ በበኩላቸው ሰላማዊ ትግል እንደማያዋጣ በማመን ልዩ የጦር ሃይል አደራጁ። ማንዴላም የጦሩ የበላይ አዛዥ በመሆኑ እርዳታ ፍለጋ ወደሌሎች አገራት ጉዞ ማድረግ ጀመሩ።
ከውጭ አገር ሲመለሱ እዚያ ደቡብ አፍሪካ ላይ ተያዙና አምስት ዓመት እስር ተፈረደባቸው። በ1963 እንደገና ማንዴላና ሌሎች የ ኤ ኤን ሲ መሪዎች መንግስትን በሃይል ለመገልበጥ የሚል ክስ ተከፈተባቸውና ፍርድ ቤት ቀረቡ። ከዚያም ማንዴላ ዕድሜ ይፍታህ ተፈረደባቸውና ሮቢን ደሴት ያለ እስር ቤት ተላኩ። ማንዴላ ከሮቢን ደሴት ሌላ በተዘዋወሩባቸው ተጨማሪ እስር ቤቶች በጠቅላላ 27 ዓመት በ እስር ሲቆዩ ፣ በመላው ዓለም የነጻነት ምሳሌ ተደረገው ተወሰዱ - ዝናቸውም እየሰፋ መጣ።
በ1990 ዓ.ም የደቡብ አፍሪካ የነጮች መንግስት በተደረገበት ዓለም አቀፍ ጫና ማንዴላን ከ እስር ፈታቸው። ኤ ኤን ሲ የተባለው ድርጅታቸውም እንዲንቀሳቀስ ተፈቀደለት - ማንዴላም ተመልሰው ሊቀመንበር ሆኑ።
ማንዴላና የዚያን ጊዜው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ኤፍ ደብሊው ደ ክላርክ በጋራ የዓለም የሰላም የኖቤል ሽልማት ተሸለሙ። ይህም የሆነው ጥቁሩ ማንዴላና ነጩ ደ ክላርክ የአፓርታይድ ሥር ዓትን ለማጥፋት ቁርጠኛ ስምምነት በማድረጋቸው ነበር።
በ1994 ደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያውን ነጻ ምርጫ አደረገችና ማንዴላ የአገሪቷ የመጀመሪያ ጥቁር ፕሬዚዳንት ሆኑ። በ1998 ማንዴላ ለሶስተኛ ጊዜ ትዳር በመያዝ ከግራሻ ሚሼል ጋር ተጣመሩ። በ1997 ከ ኤ ኤን ሲ ሊቀመንበርነት ለቀቁ። በ1999 ደግሞ ፕሬዚዳንትነት በቃኝ አሉ። በ2004 ዓ.ም ማንዴላ ከፖሊቲካው ራሳቸውን አራቁና ጡረታ መውጣታቸውን አስታወቁ። እንዲያውም ያን ጊዜ “ለማውቃችሁ ሁሉ እኔ እደውልላችኋለሁ እንጂ እናንተ እንዳትደውልሉኝ” ማለታቸው ይነገርላቸዋል። ጡረታ በወጡ በዓመቱ ትልቁ ወንድ ልጃቸው ማካቶ ማንዴላ መሞቱ ልባቸውን በሃዘን ሰበረው። በተለይ አሟሟቱ በ ኤች አይ ቪ ስለነበር፣ ማንዴላ ያንን ምክንያት አድርገው ደቡብ አፍሪካውያን ከ ኤድስ ቫይረስ እንዲጠበቁና እንደማንኛውም በሽታ ቶሎ እንዲታከሙ ጥሩ አቀረቡ። ከዚያ ወዲህ ግን በበጎ አድራጎት ሥራ ሲሳተፉ ቆይተዋል። በ2010 ደቡብ አፍሪካ የዓለም ዋንጫን እንድታዘጋጅ ትልቅ ጥረት ያደረጉትን ማንዴላ ነበሩ። በመዝጊያው በዓል ላይም በመገኘት ለውድድሩ ድምቀት ሰጥተዋል። ዕድሜያቸው እየገፋም በመሄዱ 91 ዓመት ከሞላቸው ጊዜ በኋላ፣ በተለይም ከጃንዋሪ 2011 ጀምሮ ግን ባደረባቸው የስንባ ምች እየተስቃዩ በተደጋጋሚ ሆስፒታል ሲገቡና ሲወጡ ቆይተዋል።
ኔልሰን ማንዴል በግል ህይወታቸው ሳቂታና ተጫዋች መሆናቸው ይነገርላቸዋል። ፈግግታቸው ከማንም ልብ ሰርስሮ የሚገባ ነው። በሚገርም ሁኔታ 27 ዓመት በ እስር በመቆየታቸው ምንም የሚሰማቸው ምሬት እንደሌለ ሁልጊዜ ይናገሩ ነበር። ደቡብ አፍሪካም ለክብራቸው በገንዘቧ ላይ ፎቷቸውን ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ማተም ጀምራለች። ኔልሰን ሮህሊላ ማንዴላ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው ፣ ኅዳር 26 ቀን 2006 (ዲሴምበር 5 ቀን 2013) በወዳጅ ዘመድና ቤተሰብ ተከበው አረፉ። ማንዴላ ዛሬ በህይወት የሉም፣ በሁሉም ሰው ህሊና ውስጥ ግን ታላቅ ስብዕናቸው ለዘላለም ይኖራል።
ውድ የቻናላችን ተከታታዬች በተብራራ መልኩ በኔል ሰን ማንዴላ የህይወት ታርክ ዙርያ የተፃፈውን
LONG WALK TO FREEDOM በ PDF
ቀርቦላችኋል መልካም ንባብ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ሮሊላሂላ ማንዴላ የተወለዱት ፣ ትራንስኪ በተባለው የደቡብ አፍሪካ ከተማ ጁላይ 18 ቀን 1918 ዓም ነው። ኔልሰን የሚለውን ስማቸውን ያገኙት ከጊዜ በኋላ ከአንድ አስተማሪያቸው እንደሆነ የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል። በተወለዱበት አካባቢ ባለው ቲምቡ ጎሳም በአካባቢው ሰው “ማዲባ” በሚል ስም ይጠራሉ።
አባታቸው ፣ ማንደላ የ 9 ዓመት ልጅ ሳሉ ነው የሞቱት። ማንዴላ 23 ዓመት ሲሞላቸው በጎሳው ደንብ መሰረት የሚመጣላቸውን ሚስት ላለማግባት ሲሉ ያደጉበትን ከተማ ትተው ወደ ጆሃንስበርግ ሄዱ።
በ 25 ዓመታቸው ዩኒቨርሲቲ በመግባት ማንዴላ በፎርት ሃሬ ዩኒቨርሲቲ እና በዊትዋተርስራንድ ዩኒቨርሲቲ ተምረው በ1942 በህግ ተመርቀዋል። በተመረቁ በሁለተኛው ዓመት የመጀመሪያ ሚስታቸው የሆኑትን ኤቪሊን ማሴ በማግባት አራት ልጆችን አፈሩ። በ1958 እስከተለያዩበት ቀን ድረስ አብረው ቆይተዋል። ከዚያ ፊታቸውን ወደ ትግሉ በማዞር የአፍሪካ ናሽናል ኮንግረስ በተባለው ፓርቲ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ መሆን ጀመሩ። በ1952 ማንዴላ የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳት በመሆን የአፓርታይድ ሥርዓትን በጽኑ መታገል ጀመሩ። በ1956 ማንዴላ በአገር ክህደት ወንጀል በጊዜው በነበረው የነጮች መንግስት ተከሰሱ- ክሱ አምስት ዓመት ያህል በክርክር ከቆየ በኋላ ማንዴላ በክርክሩ አሸነፉ።
በማርች ወር 1960 ዓም፣ ሻርፕቪል በተሰኘችው ከተማ ፣ ጸረ አፓርታይድ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ላይ ከነበሩት ጥቁር ሰልፈኞች መካከል 69 ያህሉን ፖሊሶች ተኩሰው በመግደላቸው ብጥብጡ ከፍ ያለ ደረጃ ደረስ። የወቅቱ መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ እንቅስቃሴ ሲከለክል እንደማንዴላ በበኩላቸው ሰላማዊ ትግል እንደማያዋጣ በማመን ልዩ የጦር ሃይል አደራጁ። ማንዴላም የጦሩ የበላይ አዛዥ በመሆኑ እርዳታ ፍለጋ ወደሌሎች አገራት ጉዞ ማድረግ ጀመሩ።
ከውጭ አገር ሲመለሱ እዚያ ደቡብ አፍሪካ ላይ ተያዙና አምስት ዓመት እስር ተፈረደባቸው። በ1963 እንደገና ማንዴላና ሌሎች የ ኤ ኤን ሲ መሪዎች መንግስትን በሃይል ለመገልበጥ የሚል ክስ ተከፈተባቸውና ፍርድ ቤት ቀረቡ። ከዚያም ማንዴላ ዕድሜ ይፍታህ ተፈረደባቸውና ሮቢን ደሴት ያለ እስር ቤት ተላኩ። ማንዴላ ከሮቢን ደሴት ሌላ በተዘዋወሩባቸው ተጨማሪ እስር ቤቶች በጠቅላላ 27 ዓመት በ እስር ሲቆዩ ፣ በመላው ዓለም የነጻነት ምሳሌ ተደረገው ተወሰዱ - ዝናቸውም እየሰፋ መጣ።
በ1990 ዓ.ም የደቡብ አፍሪካ የነጮች መንግስት በተደረገበት ዓለም አቀፍ ጫና ማንዴላን ከ እስር ፈታቸው። ኤ ኤን ሲ የተባለው ድርጅታቸውም እንዲንቀሳቀስ ተፈቀደለት - ማንዴላም ተመልሰው ሊቀመንበር ሆኑ።
ማንዴላና የዚያን ጊዜው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ኤፍ ደብሊው ደ ክላርክ በጋራ የዓለም የሰላም የኖቤል ሽልማት ተሸለሙ። ይህም የሆነው ጥቁሩ ማንዴላና ነጩ ደ ክላርክ የአፓርታይድ ሥር ዓትን ለማጥፋት ቁርጠኛ ስምምነት በማድረጋቸው ነበር።
በ1994 ደቡብ አፍሪካ የመጀመሪያውን ነጻ ምርጫ አደረገችና ማንዴላ የአገሪቷ የመጀመሪያ ጥቁር ፕሬዚዳንት ሆኑ። በ1998 ማንዴላ ለሶስተኛ ጊዜ ትዳር በመያዝ ከግራሻ ሚሼል ጋር ተጣመሩ። በ1997 ከ ኤ ኤን ሲ ሊቀመንበርነት ለቀቁ። በ1999 ደግሞ ፕሬዚዳንትነት በቃኝ አሉ። በ2004 ዓ.ም ማንዴላ ከፖሊቲካው ራሳቸውን አራቁና ጡረታ መውጣታቸውን አስታወቁ። እንዲያውም ያን ጊዜ “ለማውቃችሁ ሁሉ እኔ እደውልላችኋለሁ እንጂ እናንተ እንዳትደውልሉኝ” ማለታቸው ይነገርላቸዋል። ጡረታ በወጡ በዓመቱ ትልቁ ወንድ ልጃቸው ማካቶ ማንዴላ መሞቱ ልባቸውን በሃዘን ሰበረው። በተለይ አሟሟቱ በ ኤች አይ ቪ ስለነበር፣ ማንዴላ ያንን ምክንያት አድርገው ደቡብ አፍሪካውያን ከ ኤድስ ቫይረስ እንዲጠበቁና እንደማንኛውም በሽታ ቶሎ እንዲታከሙ ጥሩ አቀረቡ። ከዚያ ወዲህ ግን በበጎ አድራጎት ሥራ ሲሳተፉ ቆይተዋል። በ2010 ደቡብ አፍሪካ የዓለም ዋንጫን እንድታዘጋጅ ትልቅ ጥረት ያደረጉትን ማንዴላ ነበሩ። በመዝጊያው በዓል ላይም በመገኘት ለውድድሩ ድምቀት ሰጥተዋል። ዕድሜያቸው እየገፋም በመሄዱ 91 ዓመት ከሞላቸው ጊዜ በኋላ፣ በተለይም ከጃንዋሪ 2011 ጀምሮ ግን ባደረባቸው የስንባ ምች እየተስቃዩ በተደጋጋሚ ሆስፒታል ሲገቡና ሲወጡ ቆይተዋል።
ኔልሰን ማንዴል በግል ህይወታቸው ሳቂታና ተጫዋች መሆናቸው ይነገርላቸዋል። ፈግግታቸው ከማንም ልብ ሰርስሮ የሚገባ ነው። በሚገርም ሁኔታ 27 ዓመት በ እስር በመቆየታቸው ምንም የሚሰማቸው ምሬት እንደሌለ ሁልጊዜ ይናገሩ ነበር። ደቡብ አፍሪካም ለክብራቸው በገንዘቧ ላይ ፎቷቸውን ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ ማተም ጀምራለች። ኔልሰን ሮህሊላ ማንዴላ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው ፣ ኅዳር 26 ቀን 2006 (ዲሴምበር 5 ቀን 2013) በወዳጅ ዘመድና ቤተሰብ ተከበው አረፉ። ማንዴላ ዛሬ በህይወት የሉም፣ በሁሉም ሰው ህሊና ውስጥ ግን ታላቅ ስብዕናቸው ለዘላለም ይኖራል።
ውድ የቻናላችን ተከታታዬች በተብራራ መልኩ በኔል ሰን ማንዴላ የህይወት ታርክ ዙርያ የተፃፈውን
LONG WALK TO FREEDOM በ PDF
ቀርቦላችኋል መልካም ንባብ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
❤2👍1
#አጭር_ልብወለድ
#የልጅነት_ዕይታ
ይህ ታሪክ የተከሰተው የሁለተኛ ክፍል ተማሪና የዘጠኝ ዓመት ልጅ እያለው ነው በወቅቱ ዱርዬው አባቴ እና ጭምቶ እናቴ በእኔ ላይ የፈጸሙትን አሻጥር ነው የምተርክላችሁ እለቱ ቅዳሜ 10 ሰዓት አካባቢ ነው አባቴ ና ዘመድ ጠይቀን እንምጣ ብሎኝ እናቴን በማስፈቀድ ይዞኝ ወጣ የምንሄደው ወንድሙ ጋር ነው እኛ ከምንኖርበት በመኪና የአንድ ሰዓት መንገድ ነው ፤ አድረን ነገ በማግስቱ እንድንመጣ ማለት ነው፡፡በጥም ነበር የፈነጠዝኩት አንደኛ ሁሌ ከአበቴ ጋር ሆኜ ወደ ሆነ ቦታ ስጓዝ በራስ መተማመኔ ይጨምራል.ሁለተኛ አጐቴ የእኔ እኩያ የሆነ ልጅ አለው ከእሱ ጋር በመጫወት የማሳልፈው ጊዜ ለእኔ ጣፋጭ ነው፡፡
ሄድን…አጐቴ ቤት ደረስን የአጐቴ ሚስት በጣም በጥሩ መስተንግዶ ነበር የተቀበለችን መክሰስ ቀረበልን.ቡና ተፈላ…12 ሰዓት አካባቢ ሲሆን አባቴ መጣው ተጫወት ብሎኝ ከቤት ሲወጣ እምቢ ብዬ ተከተልኩት.ግንባሩን ቢቆጥርብኝም…ሊያስፈራራኝ ቢሞክርም ምን እንደነካኝ አላውቅም ያለወትሮዬ እምቢኝ አልኩት..እንደ ፍላጐቱም ልታዘዝለት አልቻልኩም..በመጨረሻም ብቻ ሳይመስለው..ሁለተኛ ይዞኝ እንደማይመጣ እየዛተብኝ ይዞኝ ሄደ፡፡‹‹ የት ይዞህ ሄደ አትሉኝ…?››ሆነች ቀይ ወፈር ያለች…አዲስ የሚያምር ቀሚስ የለበሰች ሴትዬ ቤት እሱን ስታየው በደስታ ተፍነከነከች ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳሙና ወደ እኔ ጐንበስ ብላ አገላብጣ ሳመችኝ..ልትስመኝ ጐንበስ ባለችበት ወቅት ከሁለት የተቀሰሩ ቀይ ጡቶቾ ስንጥቅ መሀከል የሚመነጭ የሚመስል ደስ ሚል ሽታ ተበትኖ በአፍና በአፍንጫዬ ተመሰገብኝ…
‹‹የቀረህ መስሎኝ እኮ ተበሳጭቼብህ ነበር››አለችው ‹‹እመጣለው ብዬሽ ጨክኜ እንዴት እቀራለው?››አላት..ወደእኔ ገልመጥ እለ
‹‹ልጅህ ደግሞ አንተን ይመስላል ››አለችው እኔን እኔን እያች
‹‹ታዲያ እኔ ወልጄው ማንን እንዲመስልልሽ ትፈልጊያለሽ?››አላት..
ለምን እንደሆነ አላውቅም ሁሌ አባትህን ነው የምትመስለው ሲሉኝ እግዚያብሄርነው ነው ምትመስለው እንዳሉኝ ነገር ትንሾ ልቤ በድስታ ትንፈራፈራለች ሴትዬዋ እኛን አስቀምጣ ወደ ጐዲያ ገባችና ሲኒዋን ይዛ በመምጣት አቀራረበች ….ከሰል አቀጣጠለች..እጃችንን አስታጠበችን ና ሚያስጐመዥ የዶሮ ወጥ አቀረበችልን፡፡
‹‹ብሉ… ብሉ…..››ስትል
‹‹ነይ አንቺም ቁጭ በይ አላት››አባቴ ቀብረር ብሎ
‹‹ቡናውን ብቆላ አይሻልም ብለህ ነው?›› አለችው.. ግን ሁኔታዋን ሲያዬት ከእኛ ጋር ቁጭ ብላ ለመብላት የቋመጠች ትመስላለች
‹‹ተይ ባክሽ ይደርሳል››ሲላት ብዙም ሳታቅማማ ኩርሲዋን ይዛ በመምጣት በእሱ እና በእኔ መሀከል ተሰክታ ቁጭ አለች በፈገግታዋ እና ባቀረበችልን ሚያስጐመዥ ዶሮ ወጥ ያስደሰተችኝ ቢሆንም በመሀከላችን በመሰካቶ ግን ቅር አሰኝታኛለች..እንኳን ሌላ ሴት ይቅርና እናቴ እንኳን ከአባቴ ስታርቀኝ ደስ አይለኝም ነበር..እውነቱን ንገረን ካላችሁኝ ግን ብዙውን ጊዜ ቅር ይለኝ የነበረው በእኔና በእናቴ መሀከል አባቴ ሲሰነቀር ነው .አባቴ ከእናቴ ሲያርቀኝ ያበሽቀኛል…ልክ አሁን ይህቺ ሴትዬ እንዳበሸቀችኝ፡፡
አባቴ ምግቡን ደህና አድርጐ ጠቀለለና ይጐርሳል ብዬ ስጠብቅ ለእሷ አጐረሳት…. እሷም የመጀመሪያውን ጉርሻ አጐረሰችው ፈጥጬ የሁለቱን ጉርሻ ቅብብል በማየት ስቁለጨለጭ ‹‹ብላ እንጂ ምን ያደፈዝሀል?›› በሚል የቁጣ ይሁን የትዕዛዝ ባለየለት ንግግር አስበረገገኝ ታምረኛው አባቴ ፡፡
‹‹ወይ አፈር ስሆን እረሳንህ አይደል›› በብጣቂ እንጀራ ወጥ ነካ ነካ አድርጋ እኔንም አጐረሰችኝ ፡፡የአባቴ ሁኔታ ግን በጣም ገርሞኛል እናቴን ብቻ ይመስለኝ ነበር እንደዛ የሚያጐርሰው..ለካ ሌሎችንም ሴቶች በተመሳሳይ ሁኔታ ያጐርሳል…ድግሞ እኮ ‹‹…እኔ ከአንቺ ውጭ እኮ ማጉረስም መጉረስም አልወድም›› እያለ ለእናቴ ጉራውን ሲነፋ ስንት ቀን ሰምቼዋለው መሰላችሁ…ይሄኔ ይቺንም እንደዛ ብሎት ይሆናል? ዳሩ ምን አገባኝ አርፌ ጣፋጩን ምግብ አልበላም…ምግቡን በልተን ካጋመስን ቡኃላ አንድ አንድ እንቁላል ፊታችን አስቀመጠች…እሱን እየፈረካከስን ስንበላ ለአባቴ ደገመችለት ለእኔም ድጋሜው ይደርሰኛል ብዬ ስቁለጨለጭ ዘለለችኝና በምትኩ ስጋ ያዘለ አጥንት ፊት ለፊታችን ደረደረች፤ እሱን መጋጥ ጀመርኩ ቀጥሎ አባቴ ‹‹በቃኝ…. በቃኝ ››ሲላት
‹‹ቆይ እንጂ መቋደሻውስ ?››አለችና የሆነ ስጋ በማውጣት በእጆ አንጠልጥላ ወደ እሱ ዘረጋችለት እሱም አንደኛውን ጫፍ ያዘ ሁለቱም ወደ ራሳቸው ሳብትና ጠመዘዙት ሁለት ቦታ ተከፈላ እሷ እጅ ላይ የቀረውን ለእሱ ስታጐርሰው የእሱን ደግሞ ለእሷ አጐረሳት…‹‹ ምን ያሽቃብጡብኛል?… የየራሳቸውን ለየራሳቸው አይጐርሱም እንዴ..?››ስል አሰብኩ በልቤ ግን ምን ያሽቃብጡብኛል ማለት ምን ማለት ነው? እኔ እናጃ ብቻ የሆነ ሰው የሆነ ቦታ ይህቺን ቃል ለእንደዚህ አይነት ድርጊት ሲጠቀምባት ሰምቼ ይሆናል..የሆነ ሆኖ ጠገብንና ምግቡ ተነሳ ብና ተፈላ ጠጣን….ኸረ ተሳስቼ ነው እነሱ ናቸው የጠጡት እኔ አልጠጣውም..ዳግሞ አንድ የዘለልኩት ነገር አለ የሆ የፈረንጅ አረቄ ነው ብላ በትንሾ ብርጭቆ ሞልታ ሰጠችው..
‹‹ ጅን ትወዳለህ አይደል?›› እያለች
‹‹አዎ ግን..!››
‹‹ግን ምን ?ባክህ አትፍራው አያሰክርህም… ለዛ ነገርም አሪፍ ነው ሲሉ ሰምቼያለው››አለችው.ለየትኛው ነገር እንደሆነ ግን ለእኔ ሊገባኝ ባይችልም
‹‹አኸ!! ለራስሽ ብለሽ ነዋ ያዘጋጀሽው?››
‹‹አነተ..አረ አበልጆቼ አክፋይ ሲመጡ አምጥተውልኝ ነው…ሆሆሆ..!!!እንዲሁ በባዶውስ መች ቻልኩህ?›››አለችውና ለምን እንደሆነ አላውቅም ደንግጣ ወደእኔ አየች እሱንም ሳየው ምቾት አይነበብበትም
‹‹.ደግሞ መች ቻልኩህ ስትል ምን ለማለት ፈልጋ ነው ?ነው ወይስ ይዋጣልን ተባብለው ይደባደቡ ይሆን?››ብዙ ጊዜ የትልልቅ ሰዎች ወሬ ለምን እንደሚወሳሰብ አይገባኝም….ከምሽቱ አንድ ሰዓት አካባቢ ሲሆን አፍ ለአፍ ገጥመው ትንሽ በመንሾካሾክ ልሰማው ያልቻልኩትን ነገር ከተነጋገሩ በኃላ እኔና አባቴ ተያይዘን ወደ አጐቴ ቤት ተመለስን ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ቡኃላ አባቴ ድንገት ሹልክ ብሎ ጠፋ….ከአጐቴ ልጅ ጋር እየተጫወትኩ እና እየተላፋው ልጠብቀው ብሞክርም የውሀ ሽታ ሆኖ ቀረ… እኔም ድካም አዛለኝና በእንቅልፍ ተሸነፍኩና ተኛው..ጥዋት ስነሳም አልመጣም
ግራ ገባኝ ‹‹ጥሎኝ ወደ ቤት ተመለሰ እንዴ….?››የአጐቴን ሚስት ጠየቅኮት
‹‹አይ አለ እዚሁ ነው አረፋፍዶ ይመጣል››አለቺኝ ቅሬታ በሚነበብበት ፊት…
እኔ ግን ከዚህ በላይ በትዕግስት ልጠብቀው አልፈለግኩም….አረሳሳውና ማንም ሳያየኝ ሹልክ ብዬ ወደ ትናንትናዋ ሴትዩ ቤት አመራው
ስደርስ አባቴ እንደ ትናንትናው መቀመጫ ላይ ሳይሆን ሴትዬዋ አልጋ ላይ ጉብ ብሎል..ስሩ ያለው ጠረጰዛ ላይ በጓዱጓዳ ሰሀን ትኩስ እንፋሎቱ ከላዩ ላይ መትነን ያላቆመ ገንፎ ቀርቦለታል..እሷም ከጐኑ ቁጭ ብላ እየተጐራረሱ ሳለ ነበር ድንገት ዘው ያልኩባቸው ሁለቱም ብትን ብለው ነው የደነገጡት
‹‹እንዴ ምን ሆንክ ?››አለኝ
‹‹ጠፋህብኛ››መለስኩለት
‹‹ከልጆቹ ተጣላህ እንዴ?››
‹‹አልተጣላውም ግን ጠፋህብኝ››ደግሜ ያንኑ ዓረፍተ ነገር በመናገር ወቀሳዬን አጠናከርኩ
‹‹ና ግባ ቁጭ በል ከአባትህ ጐን››አለቺኝና ሌላ ማንኪያ አምጥታ አስጨበጠቺኝ በልተን ከጨረስን ቡኃላ እሷንም ሆነ የአጐቴን ቤተሰቦች ተሰናብተኝ የመልስ ጉዞ ወደ ቤት እንደደረስን አባቴ በቁሙ እኔን እቤት አስገባኝና ወጥቶ ወደ ዙረቱ ሄደ እናቴ ልጄ እርቦታል ብላ በቆንጆ ሁኔታ ከሰራቸው ልሙጥ ሽሮ በግማሽ እንጃራ ላይ ፈሰስ አድርጋ
አቀ
#የልጅነት_ዕይታ
ይህ ታሪክ የተከሰተው የሁለተኛ ክፍል ተማሪና የዘጠኝ ዓመት ልጅ እያለው ነው በወቅቱ ዱርዬው አባቴ እና ጭምቶ እናቴ በእኔ ላይ የፈጸሙትን አሻጥር ነው የምተርክላችሁ እለቱ ቅዳሜ 10 ሰዓት አካባቢ ነው አባቴ ና ዘመድ ጠይቀን እንምጣ ብሎኝ እናቴን በማስፈቀድ ይዞኝ ወጣ የምንሄደው ወንድሙ ጋር ነው እኛ ከምንኖርበት በመኪና የአንድ ሰዓት መንገድ ነው ፤ አድረን ነገ በማግስቱ እንድንመጣ ማለት ነው፡፡በጥም ነበር የፈነጠዝኩት አንደኛ ሁሌ ከአበቴ ጋር ሆኜ ወደ ሆነ ቦታ ስጓዝ በራስ መተማመኔ ይጨምራል.ሁለተኛ አጐቴ የእኔ እኩያ የሆነ ልጅ አለው ከእሱ ጋር በመጫወት የማሳልፈው ጊዜ ለእኔ ጣፋጭ ነው፡፡
ሄድን…አጐቴ ቤት ደረስን የአጐቴ ሚስት በጣም በጥሩ መስተንግዶ ነበር የተቀበለችን መክሰስ ቀረበልን.ቡና ተፈላ…12 ሰዓት አካባቢ ሲሆን አባቴ መጣው ተጫወት ብሎኝ ከቤት ሲወጣ እምቢ ብዬ ተከተልኩት.ግንባሩን ቢቆጥርብኝም…ሊያስፈራራኝ ቢሞክርም ምን እንደነካኝ አላውቅም ያለወትሮዬ እምቢኝ አልኩት..እንደ ፍላጐቱም ልታዘዝለት አልቻልኩም..በመጨረሻም ብቻ ሳይመስለው..ሁለተኛ ይዞኝ እንደማይመጣ እየዛተብኝ ይዞኝ ሄደ፡፡‹‹ የት ይዞህ ሄደ አትሉኝ…?››ሆነች ቀይ ወፈር ያለች…አዲስ የሚያምር ቀሚስ የለበሰች ሴትዬ ቤት እሱን ስታየው በደስታ ተፍነከነከች ጉንጭ ለጉንጭ ተሳሳሙና ወደ እኔ ጐንበስ ብላ አገላብጣ ሳመችኝ..ልትስመኝ ጐንበስ ባለችበት ወቅት ከሁለት የተቀሰሩ ቀይ ጡቶቾ ስንጥቅ መሀከል የሚመነጭ የሚመስል ደስ ሚል ሽታ ተበትኖ በአፍና በአፍንጫዬ ተመሰገብኝ…
‹‹የቀረህ መስሎኝ እኮ ተበሳጭቼብህ ነበር››አለችው ‹‹እመጣለው ብዬሽ ጨክኜ እንዴት እቀራለው?››አላት..ወደእኔ ገልመጥ እለ
‹‹ልጅህ ደግሞ አንተን ይመስላል ››አለችው እኔን እኔን እያች
‹‹ታዲያ እኔ ወልጄው ማንን እንዲመስልልሽ ትፈልጊያለሽ?››አላት..
ለምን እንደሆነ አላውቅም ሁሌ አባትህን ነው የምትመስለው ሲሉኝ እግዚያብሄርነው ነው ምትመስለው እንዳሉኝ ነገር ትንሾ ልቤ በድስታ ትንፈራፈራለች ሴትዬዋ እኛን አስቀምጣ ወደ ጐዲያ ገባችና ሲኒዋን ይዛ በመምጣት አቀራረበች ….ከሰል አቀጣጠለች..እጃችንን አስታጠበችን ና ሚያስጐመዥ የዶሮ ወጥ አቀረበችልን፡፡
‹‹ብሉ… ብሉ…..››ስትል
‹‹ነይ አንቺም ቁጭ በይ አላት››አባቴ ቀብረር ብሎ
‹‹ቡናውን ብቆላ አይሻልም ብለህ ነው?›› አለችው.. ግን ሁኔታዋን ሲያዬት ከእኛ ጋር ቁጭ ብላ ለመብላት የቋመጠች ትመስላለች
‹‹ተይ ባክሽ ይደርሳል››ሲላት ብዙም ሳታቅማማ ኩርሲዋን ይዛ በመምጣት በእሱ እና በእኔ መሀከል ተሰክታ ቁጭ አለች በፈገግታዋ እና ባቀረበችልን ሚያስጐመዥ ዶሮ ወጥ ያስደሰተችኝ ቢሆንም በመሀከላችን በመሰካቶ ግን ቅር አሰኝታኛለች..እንኳን ሌላ ሴት ይቅርና እናቴ እንኳን ከአባቴ ስታርቀኝ ደስ አይለኝም ነበር..እውነቱን ንገረን ካላችሁኝ ግን ብዙውን ጊዜ ቅር ይለኝ የነበረው በእኔና በእናቴ መሀከል አባቴ ሲሰነቀር ነው .አባቴ ከእናቴ ሲያርቀኝ ያበሽቀኛል…ልክ አሁን ይህቺ ሴትዬ እንዳበሸቀችኝ፡፡
አባቴ ምግቡን ደህና አድርጐ ጠቀለለና ይጐርሳል ብዬ ስጠብቅ ለእሷ አጐረሳት…. እሷም የመጀመሪያውን ጉርሻ አጐረሰችው ፈጥጬ የሁለቱን ጉርሻ ቅብብል በማየት ስቁለጨለጭ ‹‹ብላ እንጂ ምን ያደፈዝሀል?›› በሚል የቁጣ ይሁን የትዕዛዝ ባለየለት ንግግር አስበረገገኝ ታምረኛው አባቴ ፡፡
‹‹ወይ አፈር ስሆን እረሳንህ አይደል›› በብጣቂ እንጀራ ወጥ ነካ ነካ አድርጋ እኔንም አጐረሰችኝ ፡፡የአባቴ ሁኔታ ግን በጣም ገርሞኛል እናቴን ብቻ ይመስለኝ ነበር እንደዛ የሚያጐርሰው..ለካ ሌሎችንም ሴቶች በተመሳሳይ ሁኔታ ያጐርሳል…ድግሞ እኮ ‹‹…እኔ ከአንቺ ውጭ እኮ ማጉረስም መጉረስም አልወድም›› እያለ ለእናቴ ጉራውን ሲነፋ ስንት ቀን ሰምቼዋለው መሰላችሁ…ይሄኔ ይቺንም እንደዛ ብሎት ይሆናል? ዳሩ ምን አገባኝ አርፌ ጣፋጩን ምግብ አልበላም…ምግቡን በልተን ካጋመስን ቡኃላ አንድ አንድ እንቁላል ፊታችን አስቀመጠች…እሱን እየፈረካከስን ስንበላ ለአባቴ ደገመችለት ለእኔም ድጋሜው ይደርሰኛል ብዬ ስቁለጨለጭ ዘለለችኝና በምትኩ ስጋ ያዘለ አጥንት ፊት ለፊታችን ደረደረች፤ እሱን መጋጥ ጀመርኩ ቀጥሎ አባቴ ‹‹በቃኝ…. በቃኝ ››ሲላት
‹‹ቆይ እንጂ መቋደሻውስ ?››አለችና የሆነ ስጋ በማውጣት በእጆ አንጠልጥላ ወደ እሱ ዘረጋችለት እሱም አንደኛውን ጫፍ ያዘ ሁለቱም ወደ ራሳቸው ሳብትና ጠመዘዙት ሁለት ቦታ ተከፈላ እሷ እጅ ላይ የቀረውን ለእሱ ስታጐርሰው የእሱን ደግሞ ለእሷ አጐረሳት…‹‹ ምን ያሽቃብጡብኛል?… የየራሳቸውን ለየራሳቸው አይጐርሱም እንዴ..?››ስል አሰብኩ በልቤ ግን ምን ያሽቃብጡብኛል ማለት ምን ማለት ነው? እኔ እናጃ ብቻ የሆነ ሰው የሆነ ቦታ ይህቺን ቃል ለእንደዚህ አይነት ድርጊት ሲጠቀምባት ሰምቼ ይሆናል..የሆነ ሆኖ ጠገብንና ምግቡ ተነሳ ብና ተፈላ ጠጣን….ኸረ ተሳስቼ ነው እነሱ ናቸው የጠጡት እኔ አልጠጣውም..ዳግሞ አንድ የዘለልኩት ነገር አለ የሆ የፈረንጅ አረቄ ነው ብላ በትንሾ ብርጭቆ ሞልታ ሰጠችው..
‹‹ ጅን ትወዳለህ አይደል?›› እያለች
‹‹አዎ ግን..!››
‹‹ግን ምን ?ባክህ አትፍራው አያሰክርህም… ለዛ ነገርም አሪፍ ነው ሲሉ ሰምቼያለው››አለችው.ለየትኛው ነገር እንደሆነ ግን ለእኔ ሊገባኝ ባይችልም
‹‹አኸ!! ለራስሽ ብለሽ ነዋ ያዘጋጀሽው?››
‹‹አነተ..አረ አበልጆቼ አክፋይ ሲመጡ አምጥተውልኝ ነው…ሆሆሆ..!!!እንዲሁ በባዶውስ መች ቻልኩህ?›››አለችውና ለምን እንደሆነ አላውቅም ደንግጣ ወደእኔ አየች እሱንም ሳየው ምቾት አይነበብበትም
‹‹.ደግሞ መች ቻልኩህ ስትል ምን ለማለት ፈልጋ ነው ?ነው ወይስ ይዋጣልን ተባብለው ይደባደቡ ይሆን?››ብዙ ጊዜ የትልልቅ ሰዎች ወሬ ለምን እንደሚወሳሰብ አይገባኝም….ከምሽቱ አንድ ሰዓት አካባቢ ሲሆን አፍ ለአፍ ገጥመው ትንሽ በመንሾካሾክ ልሰማው ያልቻልኩትን ነገር ከተነጋገሩ በኃላ እኔና አባቴ ተያይዘን ወደ አጐቴ ቤት ተመለስን ከምሽቱ ሶስት ሰዓት ቡኃላ አባቴ ድንገት ሹልክ ብሎ ጠፋ….ከአጐቴ ልጅ ጋር እየተጫወትኩ እና እየተላፋው ልጠብቀው ብሞክርም የውሀ ሽታ ሆኖ ቀረ… እኔም ድካም አዛለኝና በእንቅልፍ ተሸነፍኩና ተኛው..ጥዋት ስነሳም አልመጣም
ግራ ገባኝ ‹‹ጥሎኝ ወደ ቤት ተመለሰ እንዴ….?››የአጐቴን ሚስት ጠየቅኮት
‹‹አይ አለ እዚሁ ነው አረፋፍዶ ይመጣል››አለቺኝ ቅሬታ በሚነበብበት ፊት…
እኔ ግን ከዚህ በላይ በትዕግስት ልጠብቀው አልፈለግኩም….አረሳሳውና ማንም ሳያየኝ ሹልክ ብዬ ወደ ትናንትናዋ ሴትዩ ቤት አመራው
ስደርስ አባቴ እንደ ትናንትናው መቀመጫ ላይ ሳይሆን ሴትዬዋ አልጋ ላይ ጉብ ብሎል..ስሩ ያለው ጠረጰዛ ላይ በጓዱጓዳ ሰሀን ትኩስ እንፋሎቱ ከላዩ ላይ መትነን ያላቆመ ገንፎ ቀርቦለታል..እሷም ከጐኑ ቁጭ ብላ እየተጐራረሱ ሳለ ነበር ድንገት ዘው ያልኩባቸው ሁለቱም ብትን ብለው ነው የደነገጡት
‹‹እንዴ ምን ሆንክ ?››አለኝ
‹‹ጠፋህብኛ››መለስኩለት
‹‹ከልጆቹ ተጣላህ እንዴ?››
‹‹አልተጣላውም ግን ጠፋህብኝ››ደግሜ ያንኑ ዓረፍተ ነገር በመናገር ወቀሳዬን አጠናከርኩ
‹‹ና ግባ ቁጭ በል ከአባትህ ጐን››አለቺኝና ሌላ ማንኪያ አምጥታ አስጨበጠቺኝ በልተን ከጨረስን ቡኃላ እሷንም ሆነ የአጐቴን ቤተሰቦች ተሰናብተኝ የመልስ ጉዞ ወደ ቤት እንደደረስን አባቴ በቁሙ እኔን እቤት አስገባኝና ወጥቶ ወደ ዙረቱ ሄደ እናቴ ልጄ እርቦታል ብላ በቆንጆ ሁኔታ ከሰራቸው ልሙጥ ሽሮ በግማሽ እንጃራ ላይ ፈሰስ አድርጋ
አቀ
👍8
#ማፍቀር_ወይስ_መለየት ?
:
#አጭር_ልብወለድ
:
ቅዳሜ ከሰአት በኋላ ፣ፀጥ ረጭ ብሏል፣ የቤታችን የግድግዳ ሰአት ብቻ . . .ችው . . . ችው
እያለ በዚህ ፀጥታ ውስጥ ይሰማል። ማንም የለም እኔና እኔ ብቻ። በውስጤ የብቸኝነት ስሜት ተሰማኝ። በዚህ በጠራራ ፀሐይ እቤት ውስጥ ለብቻ መቀመጥ ምን ያህል ይከብዳል እያልኩ ከራሴ ጋር አወራለው።
ዞር ብዬ ክላሲካል ሙዚቃ ሲያሰማ ወደ ነበረው ቴፕ ስመለከት መብራት ሄዶ ዝም እንዳለ ታወቀኝ። ሀሳቤን ሰበሰብኩና በእጄ ወደያዝኩት ልብ ወለድ መፅሀፍ አቀርቅሬ ማንበቤን ቀጠልኩ።
በጥሩ ተመስጦ ውስጥ እንዳለው ድንገት ከአጠገቤ የነበረው ስልክ ጮኸና ቀልቤን ገፈፈው።በጣም ደነገጥኩ። በራሴ መደንገጥ ተገረምኩና እራሴን አረጋግቼ የስልኩን እጀታ በጉጉት አነሳሁት።
<<ሃሎ>> አልኩኝ በትህትና
<<ሄሎ>> አለችኝ አንዲት ልጅ በሚያባባና በሚያምር የድምፅ ቅላፄ።
<<ማንን ፈለጉ ?>>
<<እ. . .ናሆምን ላገኘዉ እችላለሁ ?>>
በዚህን ግዜ የልብ ትርታዬ ፍጥነቱን ጨመረ።
ድምፆም አዲስና የሚማርክ ስለሆነብኝ ማን ልትሆን ትችላለች? በሚል ከራሴ ጋር ትንሽ ተሟገትኩና።
<<ነኝ. . . ማን ልበል?>>
<<. . . ሜሮን እባላለሁ >>
<<ሜሮን?.. .ይቅርታ. . . አላስታወስኩሽም፣ ሜሮን ማን ?>>
<<ሜሮን አለሙ>>
አሁንም ፈፅሞ ላስታውሳት አልቻልኩም።ሜሮን የምትባል ልጅ ፈፅሞ ማወቄን እርግጠኛ አልነበርኩም።
<<በ. .ጣም.. ይቅርታ የኔ እህት አላወኩሽም።>>
<<ይገርምሀል እኔም አላውቅህም።>>
<<የደወልሽው አንቺ መሰለሽኝ?>>
<<አልተሳሳትክም፤ ማለቴ ስልክህን የአስረኛ ክፍል ማስታወሻ ደብተሬ ላይ ከበስተጀርባው ተፅፎ ነው ያገኘሁት።ሁለት አመት እንዳለፈውና በራሴ እጅ ፅሁፍ ስለመፃፉ እርግጠኛ ነኝ ነገር ግን በምን ቀንና ሁኔታ እንደተፃፈ አላስታውሰውም
<<እና?>>
<<እናማ ብዙጊዜ ሲከነክነኝ የነበረ ስልክ ቁጥር ስለነበር ምን አልባት አንተ ካወከኝ በሚል ነበር የደወልኩት።
መልሶን ማመን አቃተኝ።ለሰኮንዶች ያህል በአይኔ የማውቃቸውን እንስቶች በአይነ ህሊናዬ እየቃኘኋቸው ድምፅን ከምስል ጋር ለማዛመድ ሞከረኩ።ሆኖም በፍፁም ልትመጣልኝ አልቻለችም ።በርግጥ ከሁለት አመት በፊት ስለተከሰተ ነገር ማስታወስ ይከብዳል።
የቀረን ነገር ቢኖር በግምት ልንተዋወቅበት የምንችልበትን ሁኔታ መመርመር ነውና ስለየግል ህይታችን መነጋገር ጀመርን።ስለ ት/ቤትና ስለመኖርያ ስፍራችን፣ ስለቤተሰብ እንዲሁም ስለ ቅርብ ጓደኞቻችን ሳይቀር በግልፅ ተወያየን።በሚገር ሁኔታ ግን አሁንም ከጥርጣሬ ያለፈ እዚህ ቦታ ይሆናል ብለን መወሰን ተቸገርን።
ለቀልድ ነው ብዬ እንኳን እንዳልጠረጥራት የምትሰጠኝ መልሶች ሁሉ ግልፅና ፈጣን ነበሩ።
በተለይ ከንግግሯ በራስ መተማመንና በሳልነቷን ለመገመት ይቻል ነበር።ሁኔታው ቢያስገርመኝም ቀስ በቀስ ምርመራውን ትተን ስለየጎል ህይወታችን ገብተነሰ መጨዋወት ጀመርን።
<<ምን አየሰራሽ ነው አሁን?>>
<<ያው አስረኛ ከጨረስኩ በኋላ የሁለት አመት አካውንቲንግ ፊልድ ተምሬ ነግል ድርጅት ውስጥ በመስራት ላይ ነኝ። አንተስ?>>
<<እኔ እንደምንም የመሰናዶ ትምህርት ተምሬ አ.አ.ዮ የአስተዳደር ትምህርት በመማር ላይ ነኝ>>
<<ኦው ጎበዝ ተማሪ ነሃ . . .!>>
<<ነኝ ብለሽ ነው . . . ለመሆኑ ግን ምን ከይነት ሰው ነሽ ማለቴ መልክሽን?>>
<<...እኔጃ ለመግለፅ ይከብዳል።>> ሳቅ እያለች።
<<ታድያ.... ለምን በአካል አንገናኝም፤ >>ምን አልባት በመልክ ልንተዋወቅ እንችላለን?
ጥያቄውን በድፍረት ነበር ያነሳሁት ፤ሆኖም በፍርሀቴ ልክ መልኳን ለማየት ጉጉቱ ነበረኝ። እርሷም በመግደርደር ይሁን አላውቅም።
<<..መገናኘቱ እንኳን የሚመች አይመስለኝም።>
<<ለምን?>>
<<እኔንጃ?>>
<<ፈራሽ እንዴ?>>
<<አይ መፍራት ሳይሆን ሰሞኑን ክፍት ሰአት ስለሌለኝ ነው።>>
ንግግሯ እንደማቅማማት አይነት ነበር ፤ እርግጠኛ አልነበረችም።
<<እሺ. . . ብዙ አላስጨንቅሽም ባይሆን ስልክሽን ስጭኝና ተደዋውለን ሌላ ግዜ እንገናኛለን።>>
ለተወሰኑ ሰኮንዶች ዝም አለች።የኔንም ግራ መጋባት ጥርጣሬ አጎላችው።
<<ምነው ዝም አልሽ?>>
<<...ስልክም አሁን ልሰጥክ አልችልም።>>
<<እህ..ያሁሉ የግል መረጃሽን በግልፅነት ስትነግሪኝ ቆይተሽ እንዴትስልክ መስጠት ከበደሽ?>>
<<በፍፁም መደበቄ አይደለም።በዚህን ሰአት እኔን የምታገኝበት ስልክ ምን አልባት ለሁለት ቀን ብቻ የሚቆይ ነው ። ሌላ ስልክ በሌላ ግዜ እንጂ አሁን ልሰጥክ አልችልም ወይም አላውቀውም።>>
<<አሀ ገባኝ፣ ቤት ልትቀይሩ ነው አይደል?>>
<<አረ አይደለም >>ሳቅ እያለች ነበር።
<<ምንድን ነው እሱ ግልፅ ሁኚ እንጂ የደበቅሽው ነገር ኦንዳለ ይሰማኛል።>>
<<በቃ ለምን ነገ ወደ ማታ አንገናኝም?>>
የአቋም ለዉጧ አስገርሞኛል፣አስደንግጦኛልም።
አሁን ለመናገር ያልፈለገችው ሚስጥሯም ከልብ አጓጓኝ።
<<ጥሩ የት እንገናኝ?>>
<<ፒያሳ ያለው ቤቲ ካፌ ይመችካል?>>
<<ደስ ይለኛል ስንት ሰአት?>>
<<አስራ ሁለት ሰአት።>>
የሰአት ምርጫዋ ወደ ማታ መሆኑ አይናፋርነቷን ቢያስገምተኝም ለኔም ጥሩ ግዜ ስለነበር ወድያው ምልክቶቻችንን መለዋወጥ ጀመርን ።
የሷን አንድ በአንድ ከሰማሁ በኋላ ፣ የኔንም እንዲሁ ነገርኳት።እንደምልክት አገላለጿ በጣም ውብ ልጅ እንደምትመስል ገምቻለው ።ነገር ግን ከዚህ በፊት ያየኋት ትሆናለች የሚል ሀሳብ አልነበረኝም።
ይቀጥላል
Like 👍 Like 👍
አስተያየት ካሎ በ @atronosebot አድርሱን
:
#አጭር_ልብወለድ
:
ቅዳሜ ከሰአት በኋላ ፣ፀጥ ረጭ ብሏል፣ የቤታችን የግድግዳ ሰአት ብቻ . . .ችው . . . ችው
እያለ በዚህ ፀጥታ ውስጥ ይሰማል። ማንም የለም እኔና እኔ ብቻ። በውስጤ የብቸኝነት ስሜት ተሰማኝ። በዚህ በጠራራ ፀሐይ እቤት ውስጥ ለብቻ መቀመጥ ምን ያህል ይከብዳል እያልኩ ከራሴ ጋር አወራለው።
ዞር ብዬ ክላሲካል ሙዚቃ ሲያሰማ ወደ ነበረው ቴፕ ስመለከት መብራት ሄዶ ዝም እንዳለ ታወቀኝ። ሀሳቤን ሰበሰብኩና በእጄ ወደያዝኩት ልብ ወለድ መፅሀፍ አቀርቅሬ ማንበቤን ቀጠልኩ።
በጥሩ ተመስጦ ውስጥ እንዳለው ድንገት ከአጠገቤ የነበረው ስልክ ጮኸና ቀልቤን ገፈፈው።በጣም ደነገጥኩ። በራሴ መደንገጥ ተገረምኩና እራሴን አረጋግቼ የስልኩን እጀታ በጉጉት አነሳሁት።
<<ሃሎ>> አልኩኝ በትህትና
<<ሄሎ>> አለችኝ አንዲት ልጅ በሚያባባና በሚያምር የድምፅ ቅላፄ።
<<ማንን ፈለጉ ?>>
<<እ. . .ናሆምን ላገኘዉ እችላለሁ ?>>
በዚህን ግዜ የልብ ትርታዬ ፍጥነቱን ጨመረ።
ድምፆም አዲስና የሚማርክ ስለሆነብኝ ማን ልትሆን ትችላለች? በሚል ከራሴ ጋር ትንሽ ተሟገትኩና።
<<ነኝ. . . ማን ልበል?>>
<<. . . ሜሮን እባላለሁ >>
<<ሜሮን?.. .ይቅርታ. . . አላስታወስኩሽም፣ ሜሮን ማን ?>>
<<ሜሮን አለሙ>>
አሁንም ፈፅሞ ላስታውሳት አልቻልኩም።ሜሮን የምትባል ልጅ ፈፅሞ ማወቄን እርግጠኛ አልነበርኩም።
<<በ. .ጣም.. ይቅርታ የኔ እህት አላወኩሽም።>>
<<ይገርምሀል እኔም አላውቅህም።>>
<<የደወልሽው አንቺ መሰለሽኝ?>>
<<አልተሳሳትክም፤ ማለቴ ስልክህን የአስረኛ ክፍል ማስታወሻ ደብተሬ ላይ ከበስተጀርባው ተፅፎ ነው ያገኘሁት።ሁለት አመት እንዳለፈውና በራሴ እጅ ፅሁፍ ስለመፃፉ እርግጠኛ ነኝ ነገር ግን በምን ቀንና ሁኔታ እንደተፃፈ አላስታውሰውም
<<እና?>>
<<እናማ ብዙጊዜ ሲከነክነኝ የነበረ ስልክ ቁጥር ስለነበር ምን አልባት አንተ ካወከኝ በሚል ነበር የደወልኩት።
መልሶን ማመን አቃተኝ።ለሰኮንዶች ያህል በአይኔ የማውቃቸውን እንስቶች በአይነ ህሊናዬ እየቃኘኋቸው ድምፅን ከምስል ጋር ለማዛመድ ሞከረኩ።ሆኖም በፍፁም ልትመጣልኝ አልቻለችም ።በርግጥ ከሁለት አመት በፊት ስለተከሰተ ነገር ማስታወስ ይከብዳል።
የቀረን ነገር ቢኖር በግምት ልንተዋወቅበት የምንችልበትን ሁኔታ መመርመር ነውና ስለየግል ህይታችን መነጋገር ጀመርን።ስለ ት/ቤትና ስለመኖርያ ስፍራችን፣ ስለቤተሰብ እንዲሁም ስለ ቅርብ ጓደኞቻችን ሳይቀር በግልፅ ተወያየን።በሚገር ሁኔታ ግን አሁንም ከጥርጣሬ ያለፈ እዚህ ቦታ ይሆናል ብለን መወሰን ተቸገርን።
ለቀልድ ነው ብዬ እንኳን እንዳልጠረጥራት የምትሰጠኝ መልሶች ሁሉ ግልፅና ፈጣን ነበሩ።
በተለይ ከንግግሯ በራስ መተማመንና በሳልነቷን ለመገመት ይቻል ነበር።ሁኔታው ቢያስገርመኝም ቀስ በቀስ ምርመራውን ትተን ስለየጎል ህይወታችን ገብተነሰ መጨዋወት ጀመርን።
<<ምን አየሰራሽ ነው አሁን?>>
<<ያው አስረኛ ከጨረስኩ በኋላ የሁለት አመት አካውንቲንግ ፊልድ ተምሬ ነግል ድርጅት ውስጥ በመስራት ላይ ነኝ። አንተስ?>>
<<እኔ እንደምንም የመሰናዶ ትምህርት ተምሬ አ.አ.ዮ የአስተዳደር ትምህርት በመማር ላይ ነኝ>>
<<ኦው ጎበዝ ተማሪ ነሃ . . .!>>
<<ነኝ ብለሽ ነው . . . ለመሆኑ ግን ምን ከይነት ሰው ነሽ ማለቴ መልክሽን?>>
<<...እኔጃ ለመግለፅ ይከብዳል።>> ሳቅ እያለች።
<<ታድያ.... ለምን በአካል አንገናኝም፤ >>ምን አልባት በመልክ ልንተዋወቅ እንችላለን?
ጥያቄውን በድፍረት ነበር ያነሳሁት ፤ሆኖም በፍርሀቴ ልክ መልኳን ለማየት ጉጉቱ ነበረኝ። እርሷም በመግደርደር ይሁን አላውቅም።
<<..መገናኘቱ እንኳን የሚመች አይመስለኝም።>
<<ለምን?>>
<<እኔንጃ?>>
<<ፈራሽ እንዴ?>>
<<አይ መፍራት ሳይሆን ሰሞኑን ክፍት ሰአት ስለሌለኝ ነው።>>
ንግግሯ እንደማቅማማት አይነት ነበር ፤ እርግጠኛ አልነበረችም።
<<እሺ. . . ብዙ አላስጨንቅሽም ባይሆን ስልክሽን ስጭኝና ተደዋውለን ሌላ ግዜ እንገናኛለን።>>
ለተወሰኑ ሰኮንዶች ዝም አለች።የኔንም ግራ መጋባት ጥርጣሬ አጎላችው።
<<ምነው ዝም አልሽ?>>
<<...ስልክም አሁን ልሰጥክ አልችልም።>>
<<እህ..ያሁሉ የግል መረጃሽን በግልፅነት ስትነግሪኝ ቆይተሽ እንዴትስልክ መስጠት ከበደሽ?>>
<<በፍፁም መደበቄ አይደለም።በዚህን ሰአት እኔን የምታገኝበት ስልክ ምን አልባት ለሁለት ቀን ብቻ የሚቆይ ነው ። ሌላ ስልክ በሌላ ግዜ እንጂ አሁን ልሰጥክ አልችልም ወይም አላውቀውም።>>
<<አሀ ገባኝ፣ ቤት ልትቀይሩ ነው አይደል?>>
<<አረ አይደለም >>ሳቅ እያለች ነበር።
<<ምንድን ነው እሱ ግልፅ ሁኚ እንጂ የደበቅሽው ነገር ኦንዳለ ይሰማኛል።>>
<<በቃ ለምን ነገ ወደ ማታ አንገናኝም?>>
የአቋም ለዉጧ አስገርሞኛል፣አስደንግጦኛልም።
አሁን ለመናገር ያልፈለገችው ሚስጥሯም ከልብ አጓጓኝ።
<<ጥሩ የት እንገናኝ?>>
<<ፒያሳ ያለው ቤቲ ካፌ ይመችካል?>>
<<ደስ ይለኛል ስንት ሰአት?>>
<<አስራ ሁለት ሰአት።>>
የሰአት ምርጫዋ ወደ ማታ መሆኑ አይናፋርነቷን ቢያስገምተኝም ለኔም ጥሩ ግዜ ስለነበር ወድያው ምልክቶቻችንን መለዋወጥ ጀመርን ።
የሷን አንድ በአንድ ከሰማሁ በኋላ ፣ የኔንም እንዲሁ ነገርኳት።እንደምልክት አገላለጿ በጣም ውብ ልጅ እንደምትመስል ገምቻለው ።ነገር ግን ከዚህ በፊት ያየኋት ትሆናለች የሚል ሀሳብ አልነበረኝም።
ይቀጥላል
Like 👍 Like 👍
አስተያየት ካሎ በ @atronosebot አድርሱን
👍13
YouTube
አስቂኝ #ግጥም
👍11👏1
#የሚፈልጉትን_አይፈልጉትም
#አጭር_ታሪክ
ግልጽ ሰው እወዳለሁ አለችው
ህይወቱን ግልጽ ነገራት ጠላችው
ቀላል ሰው ደስ ይለኛል አለችው
ቀለል ሲል ረከሰባት ሸሸችው
ኩሩ ሰው ምርጫዬ ነው ስትለው ኮራ አለ
ጠበርክ ብላው ሄደች።
የተረጋጋ ሰው እወዳለሁ አለችው
ሲረጋጋ ተንቀራፈፍቅ ብላው ሄደች
የማይጨቃጨቅ ሰው ነው ምርጫዬ አለች
ስህተቷን ሲያልፋት ባትወደኝ ነው ግድ ያለሰጠህ አለችው
አስሬ መገናኘት መደዋወል ምናምን አልወድም አልችው።
መደወሉን ሲቀንስ ብትፈልገኝ ኖሮ ይሄንንም ብልህ ገፍተህ ትመጣ ትደውል ነበር። በቃኸኝ አለችው።
ምን እንዳጠፋ አሰበ።
እስካሁን አልገባውም።
ለአባቱ ነገረው ሁሉንም። አባቱ መለሰለት።
"ሰው ወዳለሁ ያለው ሁሉ አይኮንለትም።
ያለውን ሁሉ የምደረግለት ለአምላክህ ነው።
ሰው እኮ የፈለገውን ነገር ገና መፈለጉን አርግጠኛ አደለም።
የሚወደውን ነገር ለይቶ ያልጨረሰ ፍጡር ነው።
በተለይ እነሱ ወጣቶቹ የሚፈልጉትን ራሱ በቅጡ አይፈልጉትም"
"ምን ልሁንላት?"
"ራስህን ሁንላት!
የምትልህን ትተህ የማትልህን ሁንላት።
ሴቶች ከንግግራቸው ጋ ሩቅ ናቸው።
ያሉህን ትተህ ያላሉህን ስማቸው"
የልጁ ስልክ ጮኸ። እሷ ናት።
~ ~ ~ ~
💧ኤልያስ ሽታኹን💧
#አጭር_ታሪክ
ግልጽ ሰው እወዳለሁ አለችው
ህይወቱን ግልጽ ነገራት ጠላችው
ቀላል ሰው ደስ ይለኛል አለችው
ቀለል ሲል ረከሰባት ሸሸችው
ኩሩ ሰው ምርጫዬ ነው ስትለው ኮራ አለ
ጠበርክ ብላው ሄደች።
የተረጋጋ ሰው እወዳለሁ አለችው
ሲረጋጋ ተንቀራፈፍቅ ብላው ሄደች
የማይጨቃጨቅ ሰው ነው ምርጫዬ አለች
ስህተቷን ሲያልፋት ባትወደኝ ነው ግድ ያለሰጠህ አለችው
አስሬ መገናኘት መደዋወል ምናምን አልወድም አልችው።
መደወሉን ሲቀንስ ብትፈልገኝ ኖሮ ይሄንንም ብልህ ገፍተህ ትመጣ ትደውል ነበር። በቃኸኝ አለችው።
ምን እንዳጠፋ አሰበ።
እስካሁን አልገባውም።
ለአባቱ ነገረው ሁሉንም። አባቱ መለሰለት።
"ሰው ወዳለሁ ያለው ሁሉ አይኮንለትም።
ያለውን ሁሉ የምደረግለት ለአምላክህ ነው።
ሰው እኮ የፈለገውን ነገር ገና መፈለጉን አርግጠኛ አደለም።
የሚወደውን ነገር ለይቶ ያልጨረሰ ፍጡር ነው።
በተለይ እነሱ ወጣቶቹ የሚፈልጉትን ራሱ በቅጡ አይፈልጉትም"
"ምን ልሁንላት?"
"ራስህን ሁንላት!
የምትልህን ትተህ የማትልህን ሁንላት።
ሴቶች ከንግግራቸው ጋ ሩቅ ናቸው።
ያሉህን ትተህ ያላሉህን ስማቸው"
የልጁ ስልክ ጮኸ። እሷ ናት።
~ ~ ~ ~
💧ኤልያስ ሽታኹን💧
👍57🔥8❤7👏1
#አጭር_ታሪክ
አንድ በእድሜ የገፋ አናፂ ፣ ጡረታ ሊወጣ ሲቃረብ የመጨረሻውን ቤት እንዲሠራ ተጠየቀ።
ደክሞት ስለነበረ ለማረፍ ጓጉቶ ርካሽ ቁሳቁሶችን ተጠቅሞ ስራውን በችኮላ ጨረሰ...
ሲጨርስ አሰሪው
''ይህ ቤትህ ነው ለአመታት ያገለገለልክበት ስጦታ'' ብሎ ቁልፉን ሰጠው። አናፂው ደንግጦ በግዴለሽነቱ ተፀፀተ። የራሱን ቤት የገነባው በደካማ ሁኔታ ነበር።
/////////
ዛሬ የምትሰራው ስራ ነገ የምትኖረውን ህይወት ይቀርፃል። ሁልጊዜ ጥሩውን ነገር ስራ!
አንድ በእድሜ የገፋ አናፂ ፣ ጡረታ ሊወጣ ሲቃረብ የመጨረሻውን ቤት እንዲሠራ ተጠየቀ።
ደክሞት ስለነበረ ለማረፍ ጓጉቶ ርካሽ ቁሳቁሶችን ተጠቅሞ ስራውን በችኮላ ጨረሰ...
ሲጨርስ አሰሪው
''ይህ ቤትህ ነው ለአመታት ያገለገለልክበት ስጦታ'' ብሎ ቁልፉን ሰጠው። አናፂው ደንግጦ በግዴለሽነቱ ተፀፀተ። የራሱን ቤት የገነባው በደካማ ሁኔታ ነበር።
/////////
ዛሬ የምትሰራው ስራ ነገ የምትኖረውን ህይወት ይቀርፃል። ሁልጊዜ ጥሩውን ነገር ስራ!
👍57