አትሮኖስ
286K subscribers
118 photos
3 videos
41 files
567 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት
;
;
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ


እስክንድር በምልክት አሳየው ። በዚያ ሁሉ ጠጪ መሐል ሁለት እጁን እኪሱ አድርጎ ፡ ሁሉንም በንቀት ዐይን እየተመለከተ ነበር ወደ ሽንት ቤቱ የሔደው ።

“ ቢራዋ ሥራዋን እየሠራች ነው ” አለ እስክንድር የአቤል አረማመድ እያየ ።

“ ግን ምን ይሻለዋል ?” አለ ሳምሶን " በአቤል ሁኔታ በማዘን ' “ አሁን በማዕረግ የሚመረቅ ይመስልሃል ? ” እስክንድር ገርሞት ሣቀ ። የሳምሶን ጥያቄ ግን ከቅን
መንፈስ የመነጨ ነበር ። አቤል የሚወደውም የሚያከብረውም በማዕረግ ተማሪነቱ ነው ። የአቤል የማዕረግ ተማሪነት በዩኒቨርስቲው ውስጥ በብዙ ተማሪዎች ዘንድ ይታወቃል
እንደ እስክንድር ጠጋ ብለው የማያውቁት አሁንም የዓመቱ የፕሬዚዳንት የከፍተኛ የማዕረግ ሽልማት ከአቤል እጅ አይወጣም የሚል ግምት አላቸው ። ሳምሶንም የመኝታ ክፍል ጓደኛው ቢሆንም ቅሉ በትምህርት ያን ያህል መድከሙን አያውቅም ነበር ።

“ እውነቴን ኮ ነው ። ምን ያሥቅሃል ?”

ማዕረጉ ቀርቶ በዚህ ዓመት መመረቁ ራሱ ነው እኔን የሚያጠራጥረኝ” አለው እስክንድር " በኀዘን ስሜት ፊቱ
ተለዋውጦ።

“ ያሳዝናል ! ግን ምን ታረገዋለህ! ” አለና ሳምሶን "ቢራውን ከጠርሙሱ ውስጥ እየጨለጠ ፥ “ በነገራችን ላይ መውደቂያችንን እናዘጋጅ እንጂ ! መቼም ዛሬ ወደ ካምፓስ አንገባም” አለው ።

እስክንድር የሳምሶን ሐሳብ ገባሁ ፤አንድ ሴሚስተር ሙሉ ታፍኖ የቆየ ስሜቴ ተነሣ ነገር ግን ኪሱ አስተ ማማኝ አልነበረም ።

“ እኔጋ በቂ ገንዘብ የለማ ! ” አለው ልመና በተቀላቀለበት ድምፅ ከልብ ተዝናንቶ ።

አቤልም እሺ የሚል አይመስለኝም ። ከአሁን በፊት ውጭ እድሮ አያውቅም ።
“ ምን ትቀልዳለህ ? ጭራሽ ? እምልህ ...”
“ አዎ ፡ ከእኔ ጋር ስንተዋወቅ ይኸው አራት ዓመት አለን አንድ ቀንም ኣድርጎት አያውቅም ።

እንግዲያው ዛሬ ድንግሉን ማስወሰድ አለብን ? ”አለ ሳምሶን ተንኮልም የፍቅር ስሜትም እየተሰማው ።

“ እዩዬ ! ተው እባክህ ! ” አለ እስክንድር ' በተዘበራረቀ ስሜት ።

“ ምናለበት ? አንተ ደሞ ! እንዲያውም ሴት ከቀመሰ የዐይኑ ፍቅር ይለቀው ይሆናል ። ገንዘብ እንደሆን እኔ ይዣለሁ ብዬሃለሁ ።

እስክንድር የሳምሶን ሁኔታ ራሱ እንግዳ ሆነበት ። ሳምሶን አብዛኛውን ጊዜ በኪሱ በርካታ ገንዘብ ይይዛል ። ወላጆቹ ደኅና ገቢ አላቸው ። አባቱ በአንድ ኢንተርናሽናል ድርጅት ውስጥ በጥሩ ደመወዝ ይሠራሉ ። በእናቱ ስም ደግሞ
መስጊድ አካባቢ የሰዓት መሸጫ ሱቅ አላቸው ። ወላጆቹ ለሳምሰን በወር ተቆራጭ ካደረጉለት ሃምሳ ብር ሌላ
ሊጠይቃቸው ብቅ ባለ ቁጥር አንድ ወይም ሁለት ባለ አሥር ኖት ሳያሽጉት አይመለስም ። ታዲያ ሳምሶን ይህን ሁሉ ገንዘብ ሲይዝ " ለመጠጥ ማጥፋት አይወድም። የሱ ገንዘብ የሚያልቀው በምግብ ነው ። መብላት ፡ ስፖርት መሥራት ግንባታ ብቻ ! በዩኒቨርስቲው አቅራቢያ ካሉት ምግብ ቤት ባለቤቶች ውስጥ እሱን የማያዉቅ የለም ። ዛሬ ገንዘቡን ለመጠጥና ለሴት ለማውጣት መዘጋጀቱ ነው እስክንድርን ያስገረመ።

“ እንዴት ነው ? ዛሬ ግንባታው ቀርቶ ለማፍረስ ነው መሰል የታጠቅከው ” አለው እስክንድር እየሣቀ ።

“አንዳንዴ ያስፈልጋል እባክህ ! ”
አሳላፊዋ አራት ጠርሙስ ቢራ ይዛ መጣች አንዱ ለራስዋ መሆኑ ነው ።

ቢራ እዚሁ ጓዳ መጥመቅ ጀመራችሁ እንዴ ? "
አላት እስክንድር ፡ ከታዘዘች መዘግየቷን ለመጠቆም ።

“ ቆየሁ እንዴ?አንድ ሰካራም ይዞ ሲነተርከኝ ነው” አለች ፥ ቢራውን እየከፈተች ።

“ አንቺው መጠጥ አቅርበሽለት አንቺው፡ሰካራም ትይዋለሽ ? በይ ነይ በይ ” አለና ሳምሶን ፡ ዳሌዋ ላይ ቸብ አደረጋት ቸብታው ጠንከር ያለ ስለ ነበር ዳሌዋን ለበለባት።

“ እንደዬ ! ታዲያ ዱላው ምንድነው ? ” አለች ተቆጥታ ዳሌዋን በእጅዋ እያሻሸች

ዝም በይና ቁጭ በይ ! ከፈለግኩ ጥርስሽን ነው የማረግፈው አላት ሳምሶን እንደ ልማዱ ።

እስክንድር ነገሩ ማየሉን ሲያይ ተደናገጠ

“ ኧረ እባክህ ! የማነህ ሒድና የሚስትህን ጥርስ አውልቅ " የእኔን የብርቅነሽን አይደለም። ስለ ቢራው እንደሆን ኬረዳሽ ! ” ብላው የከፈተችውን ቢራ ጥላ ተነሣች ብርቅነሽ አምርራ ልትሔድ ስትል'እስክንድር እጅዋን
ይዞ አባብሎ አስቀመጣት ።

“ አንቺ ደሞ እረፊ እንግዲህ ። እሱ ለጠዋታ ያህል ነው የነካሽ
እየተመናቀረች ከሳምሶን ርቃ እስክንድር ጎን ተቀምጠች ። ሳምሶንም ጥርሱን እያንቀጫቀጨባት ነበር ። በማይ
ረባ ነገር ተለካክፈው የጎሪጥ መተያየታቸው እስክንድርን
አስገረመው ።

“ ሁለታችሁም ዕረፉ ፡ ይሄ ቡና ቤት ነው በሰላም ጠጥተን መጫወት ነው የምንፈልገው ”አላቸው : ከግንባሩ ኮስተር ብሎ ፥ ግን በሆዱ እየሣቀ ።

የእስክንድር ሐሳብ እነሱጋ ረግቶ አልቆየም ። በድንገት አንድ ሐሳብ አእምሮውን ወጋው ።አቤል ወደ ሽንት
ቤት ከሔደ ቆይቷል ፤ግን አልተመለሰም ። እስክንድር ልቡ መጥፎ ነገር ጠረጠረና ድንገት ከተቀመጠበት ተነሣ ።

ምነው ?” አለው ሳምሶንም ፡ በሁኔታው ተደናግጦ ።

“ ምንም አይደለም ፥ መጣሁ ” ብሎ እስክንድር ወደ ሽንት ቤቱ ሄደ ። አቅለሽልሾት ይሆናል በሚል ግምት ሳምሶን ነገሩን ቸል አለው ።

እስክንድር ከመጸዳጃ ቤቱ አጠገብ ሲደርስ አቤል እጁን በኪሱ እንዳደረገ ግድግዳ ተደግፎ ቆሞ ነፋስ ሲቀበል አገኘው። ዐይኑ በርበሬ መስሏል ።አላፊ አግዳሚውን በንቀት ዐይን ነው የሚመለከተው።

ቴክሱ ምነው ? ”አለው እስክንድር ፥ ደህና መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ"

“ ወረፋ ሆኖብኝ ነው እባክህ ! ”

“ የሽንት ወረፋ ? በል እንግዲህ ጠብቅ ። ምን ታረገዋለህ ? ” ብሎት እስንድርን ወደ መጣበት ተመለሰ ።አቤል አንድ አደጋ ደርሶቀታል የሚል ሥጋት ስለ ነበር፡ በሰላም በማግኘቱ ልቡ ተረጋጋ ። ምንጊዜም አያምነውም አንድ ቀን በራሱ ላይ የሞት ቅጣት ይፈርዳል የሚል ፍራቻ አለው።

ወደ መቀመጫው ሲምለስ ብርቅነሽና ሳምሶን ተስማተው ጎን ለጎን ተቀምጠው ሲያወሩ አገኛቸው ።

ታረቃችሁ እንዴ ? ”

“ ዱሮስ መች ተጣላን ? አንተ ደሞ ” አለችና ብርቅነሽ ጠየቀችው፡ ፡

ቀድሞውንም ጸበኞች የሚገባበዙት መሐላቸው ገላጋይ ሲኖር ነው ። ብቻቸውን ሲሆኑ አንደኛው ዐቅሙን
ዐውቆ ወይም ጥቅሙን ከጉዳቱ አመዛዝኖ ጸባዩን ያሳምራል ? አለ እስክንድር በልቡ ።

“ ያንን ነገር “ኮ ለብርቅነሽ ነገርኳት” አለው ሳምሶን' ዓይኑን እስክንድር ላይ ተክሎ "

የቱን ነግር ? ”

የአቤልን ነዋ ! በቃ እሷ ይዛው ትደር ።

ሳምሶን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መሆናቸውን አጫውቷት ከዚያው ቡና ቤት መኝታ እንድትይዝ ገንዘብም
ሰጥቷታል ።

“ አንተ ዛሬ የልጁን ድንግል ለማስወሰድ ታጥቀህ ተነሥተሃል ማለት ነው? ” አለ እስክንድር ጉጉቱ አስገርሞት እየሣቀ ።

“መሆን አለበት ብዬሃለሁ ። አድቬንቸር ነው
“ አንቺስ ? በነገሩ ተስማማሽ ? ” አላት እስክንድር ፊቱን ወደ ብርቅነሽ መልሶ።

ውይ በደስታ ነዋ ! እንዲያም ድንግል ወንድ ደርሶኝ አያውቅም ። ዕድሌ ሆኖ የተፈተነ ብቻ ነው የሚደርሰኝ።

ስትናገር ሣቅ ሃቅ ስለምትል የቀልዷን ይመስላል እንጂ ብርቅነሽ የምትናገረው የልቧን ነበር ። ወሲብ ጀማሪ ደርሷት
አያውቅም ። የልጅነት ባሏም ቢሆን ሁለተኛ ሚስቱ ነበረች ።ቡና ቤቱ ውስጥ የሥራ ጓደኞቾ፥ “ ዛሬ የአንዱን ጀማሪ ድንግል ወሰድን ” እያሉ ሲያወሩ ትቀናለች በዚህ ወሬ የተካነችው የቡና ቤቱ ባለቤት ነች የጥንት ዝናዋን ስታወራ ይሄ አርዕስት
👍1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና


በድንገት የተከሰተው አደጋ ክፉኛ ስላስደነገጠው ሻምበል ብሩክ ቀን እረፍት፤ ሌት እንቅልፍ፤ የሚባል ነገር አጥቶ እንደዚሁ በከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ ከረመ፡፡ ለዚሁ ጉዳይ ሲልም ከመስሪያ ቤቱ የአስራ አምስት ቀን ፈቃድ ወሰደ፡፡ በዚህ ፈቃድ በወሰደበት ጊዜው
ውስጥ ደግሞ ብዙ መሯሯጥ ይጠበቅበታል፡፡መጀመሪያ ሆስፒታል የተኛች እናቷን ማረጋጋት አለበት :: ከዚያም ለወንድሟ በቂና አሳማኝ ምክንያት መስጠት ይጠበቅበታል ይህንን ሁሉ ሲያደርግ በሀሳብ የምትረዳውና ! አብራው የምትሯሯጠው! አዜብ ብቻ ነች፡፡ አዜብ ስለደረሰው አደጋ የትህትና አክስት እንዲያውቁት ፈልጋ ነበር፡፡

"አይሆንም ትርፉ ማስደንገጥ ብቻ ነው የሚሆነው፡፡ እነሱ ካወቁ ወሬው መዛመቱና፤ እናትዋ ጆሮ መድረሱ የማይቀር ስለሚሆን፤ በሚስጥር ቢያዝ ይሻላል” በማለት የተከራከረው ሻምበል
ነው፡፡ሻምበል ለእናቷ የሚሰጠው ምክንያት አሳማኝ እንዲሆን ሀሳብ
ሲያወጣና፧ ሲያወርድ፤ አዜብም እንደዚሁ ያሳምናታል ብላ ያሰበችውን ምክንያት ስትደረድር፤ ቆዩና ሁለቱም ይሆናል ባሉት ሃሳብ ላይ በጋራ ከተስማሙ በኋላ፤ ይህንኑ ሊያስረዳ ወደ የካቲት አስራ
ሁለት ሆስፒታል አቀና፡፡ ትህትና ከእናትዋ ጋር በአይነ ስጋ ከተገናኙ ሶስት ቀን ሆኗቸዋል፡፡ አንዱአለምም ድምጹ ከጠፋ ሳምንት አልፎታል፡፡በነገሩ እናት ግራ ተጋብታለች፡፡
"ልጆቼን ምን ነካብኝ?" በሚል ጭንቀት ተውጣለች፡፡ትናንትና ሆስፒታል መጥታ ያስተዳደረቻት ሰራተኛዋ ነበረች፡፡ ትህትና ከቤት ያለማደሯን ብቻ ነው የነገረቻት፡፡ በሽታዋን ማዳመጡን ትታ ልጆችዋን
እያብሰለሰለች፤ በሀሳብ እንደተዋጠች ነበር ሻምበል ብሩክ የደረሰው፡፡ብሩክን ስታየው በደስታ ልቧ ቀጥ አለች ::
"ትህትናዬስ ብሩኬ?" ከኪሱ አውጥቶ ይሰጣት ይመስል በጉጉት አይን አይኑን እያየች ጠየቀቸው፡፡ ሻምበል ብሩክ እንደማፈር ብሎ ሳቅ አለና፤ ተቅለሰለሰ፡፡ ለዘዴው...
“ምነው ብሩኬ በደህና ነው?" ከሁኔታው የከፋ ችግር እንደሌለ ተረድታለች፡፡
“ምንም ችግር የለም እማማ፡፡ ምን የኛ የወጣቶች ነገር...
የሚያሰጋ ነገር ያለመኖሩን ከሁኔታው ብትገነዘብም ምክንያቱን ለማወቅ
ቸኮለች፡፡
"ምንድነው እሱ ታዲያ?
ትህትና ምንም እንኳ እጮኛዬ ብትሆንም፤ ከትዳር በፊት እርግዝና ማለት፤ ትንሽ ያልተለመደ ስለሆነ... አንጠልጥሎ ተወው። ነገሩ ገባት
ከዚያ በላይ ልታስጨንቀው አልፈለገችም እሱ ግን ቀጠለ "ከጋብቻ በፊት ልጅ መውለድ የቤተሰብን ክብር መንካት ነው የሚል እምነት አላት፡፡ ተመካከርንና ማህጸኗ እንዲጠረግላት አደረግን፡፡ አሁን
ራስ ደስታ ሆስፒታል ትንሸ እረፍት ትውለድ ስላሉኝ አስተኝቻታለሁ።"አለና አጭር ድራማውን አጠናቀቀ፡፡ እናት የልጇን አቋም በእርግጥ ታውቀዋለች፡፡
አባቷ ያሳደጋትም በዚያ እምነት ጸንታ
እንድትኖር ነውና፤ በወሰደችው እርምጃ የተቃወሞ ድምጽ አላሰማችም፡፡
ነገሩን ውስጥ ውስጡን ስታብላላ ቆየችና......
“ሻምበል አደራህን! ትሁቴ ህጻን ልጅ ናት።እንደታላቅ ወንድም ተንከባከባት፡፡ እሷ ምኑንም የማታውቅ አንድ ፍሬ
ልጅ ናት፡፡ ለመጠንቀቁም ቢሆን አንተ ትሻላለህ፡፡ እሷ ምኑን ታውቀዋለች ብለህ
ነው?" የአሁኑ ስህተት እንዳይደገምና፤ በሌላ ጊዜ ተጨማሪ ጉዳት
እንዳይደርስባት፤ ሻምበል ሃላፊነቱን እንዲወጣ በማሳሰብ፤ አደራዋን
አጠበቀች፡፡ እሱም ትህትና ከሆስፒታል እንደወጣች ይዟት እንደሚመጣ
ቃል ገባላት፡፡ በመጠኑም ቢሆን ልቧ ትንሽ እረፍት አገኘ፡፡
“የአንዱአለሜ ወሬስ ? ምነው ጭልጥ ብሎ ጠፋ?" አከታትላ ጠየቀችው፡፡
“እኔ ራሴ ካገኘሁት ሳምንት ሆኖኛል እማማ፡፡ ለፈተናው ዝግጅት ሸፍቷል፡፡ ዘንድሮ አንደኛ ካልወጣሁ ሰው አይደለሁም ሲል የፎከረውን ለመፈፀም ቆርጦ መነሳቱን ትህትና ነግራኛለች። ምንም አያስቡ፤ ፈተናውን እንደጨረሰ እንዲመጣ እነግረዋለሁ።” ምክንያቱ
ብዙ ባይዋጥላትም የሻምበልን የማፅናኛ ቃል ከማዳመጥ በስተቀር አማራጭ አልነበራትም፡፡ዝም አለች፡፡ ከዚያም ሻምበል በግማሽ ልቡ ሆኖ፤ የሆነ ያልሆነውን፤ ሲያወራት ከቆየ በኋላ፤ ተሰናብቷት ወደ ትህትና ሩጫውን ቀጠለ....
ትህትና የቀዶ ህክምና ከተደረገላት በኋላ በአንደኛ ማእረግ እንድትተኛ ያደረገው ሻምበል ብሩክ ነው፡፡ ሻምበል አስፈላጊውን ክፍያ በመፈጸም ንጽህናው በተጠበቀና፤ ተጨማሪ በሽተኛ በሌለበት
አንደኛ ማእረግ ውስጥ እንድትተኛ የፈለገበት ዋናው ምክንያት፤
በሚተኙ በሽተኞች ስቃይ ተጨማሪ የአእምሮ መረበሽ ሊደርስባት ይችላል በሚል ፍራቻ ነው፡፡
ለቀዶ ጥገናው የተወጋችው ማደንዘዣ ስራውን በማጠናቀቁ ለአስቸኳይ ህክምናው በተሰጣት በሀያ አራት ሰአት ውስጥ ከሰመመናዊ እንቅልፉ ነቃችና አይኗን ገለጥ አደረገችው፡፡ ጣሪያውን ተመለከተች፡፡ ዙሪያዋን ቃኘች
የት እንዳለች፤ ምን እንደሆነች፤ በፍጹም
አታውቀውም፡፡ የተወጋችው የእንቅልፍ
መርፌ ፤ በጥይት የቆሰለው ሰውነቷና
እንደ ጉድ የፈሰሰው ደሟ መላ
አካሏን ድቅቅ አድርጐታል፡፡ከግራ ጆሮዋ ጀምሮ ፊቷ በአጠቃላይ በፋሻ ተሸፍኗል፡፡በክንዷ ላይ የተሰካውን ግሉኮስ ተመለከተችው፡፡ ጠብ ጠብ... እያለ
ይወርዳል። እንደገና አይኗን ጨፈነች፡፡ትንሽ ቆየችና መልሳ ገለጠችው::
እንደገና በሀሳብ ባህር ውስጥ ገባች፡፡ ምን ነበር የሆነው ? የት ነው ያለችው? እዚህ ለምን መጣች? እሷ ማን ነች? ቆይ .. ቆ ይ.. ምን ነበር የሆነው ? የሆነ
ነገር ብዥ ፧ ብዥ አለባት እንዴ ?..
መርካቶ ውስጥ እንደሻውን... ከዚያ በኋላ እራሷን... እንዴ?
ምንድነው ነገሩ? እሷ ሞታለች አይደለም እንዴ? በሰማይ ቤት ነው ወይንስ በምድር ላይ ያለችው? በዚያች በተሰናበተቻት ምድር ላይ? በፍጹም ሊሆን አይችልም! እንቆቅልሹም ሊገባት አልቻለም፡፡ ከዚያም ፊት ለፊትዋ የተቀመጡትን ሰዎች ትኩር ብላ ተመለከተቻቸው፡፡
ብዥ ፤ ብ ዥ ፤አሉባት አላወቀቻቸውም :: እነሱ በሀዘን ተውጠው አይን አይኗን ይመለከቷታል፡፡ እንደገና ትኩር ብላ ከመታሸግ በተረፈው በቀኝ አይኗ አየቻቸው፡፡ አሁንም አላወቀቻቸውም፡፡ እንቅስቃሴ የላትም፡፡እዚያ ከፊት ለፊቷ ሆነው በሀዘን ኩርምት ጭብጥ ብለው የተቀመጡትን ሰዎች በድጋሜ በጥንቃቄ ተመለከተቻቸው፡፡ የሆነ ምስል መጣላት፡፡
የምታውቀው ምስል በርቀት የምታውቀው ምስል.. አዎን
ታውቃቸዋለች እንጂ !! እንዴ..? በሚገባ ታውቃቸዋለች :: ቀስ ብላ በለሆሳስ ተጣራች "ብ..ሩ. ኬ..... አ . ዜ. ቢ . ና
እህህህ....." በዚህ ጊዜ አዜብ ቀስ ብላ ተነሳችና ሄዳ አጠገቧ ቆመች፡፡ ብሩክም አዜብን ተከትሎ ወደ አልጋው ተጠጋ፡፡ሻምበል እንደዚያ ሆና ሊያያት አልቻለም :: እንባው አመለጠውና ቀስ ብሎ ጉንጮቹን
እያቋረጠ ፈሰሰ፡፡
“እ ማ ዬ...ደ ህ...ና. ነች? ..አ.ን.ዱ.ዬስ..?"
"ሁለቱም በጣም ደህና ናቸው፡፡ ስለ እነሱ ምንም አታስቢ፡፡ እኛ አለን፡፡ አሁን ዋናው ማሰብ ያለብሽ ስለራስሽ ጤንነት ብቻ ነው እሺ?” አዜብ ነበረች፡፡
“እ..ሺ በደከመ ድምጽ፡፡
“ትሁት አዜብ የምትልሽን ስሚያት፡፡ስለ እማማ ምንም የሚያስጨንቅሽ ነገር የለም፡፡እሳቸው አንቺ ስለጠፋሽባቸው ነው ትንሽ ያሰቡት እንጂ በጣም ደህና ናቸው፡፡ ቶሎ ድነሽ ሄደሽ እንዲያዩሽ
በሃሳብና በጭንቀት ራስሽን መጉዳት የለብሽም፡፡ እሺ? አንዱ አለምም ድኗል ማለት ይቻላል፡፡ሰሞኑን መጥቶ ይጠይቅሻል እሺ?” ጉንጮቿን
እየዳበሰ፡፡
እሺ” አለች በድጋሜ፡፡ በዚያው ድክምክም ባለ ድምጿ። አሉኝ የምትላቸውና የምትተማመንባቸው ሁለቱ ጓደኞቿ፤ ደራሾቿ ፤ በዚህ በክፉ ቀን እንኳ ከጐኗ
👍1
#ቆንጆዎቹ


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ

....በለሃጩ አጨማለቃት፡፡ራቁት ገላውን እራቁት ገላዋ ላይ እንደቁንቡርስ አንደባለለው፤ መላ ፊቷን በሚርገበገብ ከንፈሩና በምላሱ አልኮሰኮሰው፤ እጆቿንና እግሮቿን ከአልጋው ጠርዞች ጋር እንደተጠፈሩ አፍዋ በቡትቶ ታጭቆ እንደተጎስጎስ በተንጋለለችበት ጥያፌዋን፣ ምሬቷን ሰውነቷን እያወራጨች አሳየችው፡፡

ግድ አልነበረውም...

በከርዳዳ ጺም የተሸፈነ ፊቱን ከፊቷ ላይ አንስቶ እስረኛው ምርኮኛው በሆነው ከስሩ በተንጋለለላት ገላዋ ላይ አንቀዋለሰው፣ አይን አዋጅ ሆነበት:: ..በደመነፍስ ያዳብሳት ጀመር፡፡ በል..በል የሚለውን ግፊት፤

ሂድ..ሂድ የሚለውን ስካር ሩጥ..ሩጥ የሚለውን እብደት ጥድፊያ አምቆ
መቆየቱ ጣፋጭ የስቃይ ስሜት ፈጠረለት፡፡ ከረሜላውን ከአፉ ከትቶ
ኮረሻሽሞ ጎረዳድሞ ከመዋጡ በፊት፣ የጎረሰውን ከረሜላ እየመላለሰ በመዳፉ
ላያ እየተፋ በስስት በስቃይ ስሜት እያየ ቀስቃዩ በሰቀቀኑ እንደሚደሰት ህፃን
የጓጓለትን የተንቀዋለለለትን ገላዋን ከስሩ አጋድሞ ተሰቃየ ለራቁት ገላዋ
ሳሳለት፡፡

ፂማም ፊቱን ወደ ደረቷ አስጠግቶ በጡቶቿ መሃል ወደቀ፡፡ሳያጎረድማት መጠጣት፤ ሳይኮረሽማት ላሳት፤ መልሶ ከአፉ አውጥቶ ተመለከታት::አውሬ ሆነች፡፡ ጥላቻዋ እየጨመረ. ምሬታ እየኮረረ. እልኋ እየጋመ በመጣ ቁጥር የልቡ ምት እየጨመረና ትንፋሹ እየተፋጀ መጣ ሰውነቱ በላብ አሙለጨለጨ ፊቱን ከጡቶቿ መሃል አውጥቶ ቁልቁል
አዘገመ...

ወገቧን ሰብቃ ሰደበችው ፧ ሽንጧን እያላጋች ረገመችው፧ ጭኖቿን
እያማታች ተፋችው

ደስታው ወሰን አጣ…

ጎንበስ ብሎ የሚወራጭ . አካሏን በለሀጩ በራሱ ከንፈሮቹ ተረከበው:: እንደ እንፋሎት የሚጋረፍ፡ ትንፋሹ ለስላሳ ቆዳዋን ፈጃት ፡ ለበለባት:: ህሊናቸውን መሳት የጀመሩ ደዳራ ጣቶቹ የሴት አካልዋን በጭካኔ አፍረጠረጡት፡፡

በሩ ተበረገደ፡፡

በጉልበቶቿ መሃል እንደተንበረከከ በድንጋጤ ፊቱን ወደጀርባው መነጨቀው የተመለከተውን አልወደደውም፡፡ በር ላይ በድን ይመስል የተገተረው ሰው የሚያየውን ትርዒት ለመረዳት ጊዜ ፈጀበት:: የሚመለከተው እየተገለጸለት ሲሄድ በእልህ ይንቀጠቀጥ ጀመር፡፡

“ጠርጥሬሃለሁ! አንት ውሻ ጠርጥሬሃለሁ!” አለ ማርቆስ በሩን
ለቅቆ ወደ ክፍሉ ከመግባቱ በፊት ከኮቱ ስር ሽጉጡን ላጥ አድርጎ አቀባብሎ
እላይዋ ላይ በተከመረባት ሰው ላይ እየደገነ። “እንዳትነቃነቅ... ከዚያ አልጋ
ላይ ለመውረድ ሞክርና እንደ ውሻ እገድልሃለሁ!” አለ ማርቆስ ሽጉጠን
እንደደገነ ወደ ስልኩ እያመራ፡፡ “ትንሽ ተነቃነቅና ምክንያት ስጠኝ ግንድህን አጋድምሃለሁ!” በቀኝ የያዘውን ሬድዮ ወደ አፉ ኣስጠግቶ ተናገረ።
“ሃሎ… ቆንጆዎቹ ቡድን ለ... አስቸኳይ ነው... ዜሮ አራት” ለጥቂት ደቂቃዎች ዝም አለ፡፡ “ቁጥር አንድ ጋር አገናኝኝ፡፡” የሬዲዮ መገናኛውን በግራው እንደጨበጠ በቀኙ የያዘውን ሽጉጥ እላይዋ ላይ በተከመረው ሰው
ላይ ደግኖ ተጠባበቀ፡፡ “ሃሎ …ዜሮ አራት በፍጥነት እፈልግሃለሁ… እዚሁ
ድረስ… ሌላ ሰው አይደለም አንተ ራስህ ተገኝታህ መመልከት አለብህ።”
አነጋግሮ ሊያበቃ ስልኩን ዘግቶ ሽጉጡን ወደፊት ኣስቀድሞ ወደ አልጋው
ተጠጋ፡፡

“ጉድህን እናየዋለን” አለ ማርቆስ ጺማሙን ሰውዬ በጥላቻ
እየተመለከተ፡፡

“ይቅርታ አድርግልኝ ማርቆስ፡፡ ሌላው ይቅር ልብሴን ልልበስ፡፡” አለ ሰውየው በጭኖቿ መሃል እራቁቱን እንደተንበረከከ በልምምጥ ፊት ማርቆስን እየተመለከተው፡፡

“ከማነው ሃጢያታችንን የምንሸሽገው? ለዓመታት አንዳችን የአንዳችንን ሃጢያት እንዳናይ የገዛ ሃጢያታችን እንዳይታይ ፊታችንን ስንመላለስ ቆይተናል፡፡ ከአሁን ወዲያ ግን ገበናችን መገለጥ አለበት፡፡
ከኃጢያታችን እራቁታችንን መተያየት አለብን። : እውነት ተሽፋፍና ተጀቧቡና አትኖርም፡፡ እራቁቷን ነው የምታምር፡፡” በዕልህ ተንቀጠቀጠ፡፡
“እራቁቷን!”

“ማርቆስ ልብህ ይራራ… ሁላችን እንሳሳታለን… ማረኝ፡”

"ማነው አውሬ… ለተናካሽ እውሬ የሚራራ? ቀሚሷን ገልበው እርቃኗን አንጋለው ለሚያረክሷት፣ ጭኖቿን በርግደው ሴትነቷን አጋልጠው ለባእድ
ለሚሽጧት አፍሪካ ርህራሄ አይኖራትም፡፡ ምህረት ምንድነው? በየዋህነት ለቸረቸራችሁ፣ በልበ ገርነቷ ለሽረሞጣችሁ፣ በድንግልናዋ ላቃጠራችሁ ምህረት ምንድነው? አፍሪካ መቼ ነው ቀሚሷን ዝቅ የምታደርግ፣ ጭኖቿን የምትሰበስብ፣ እፍረቷን የምትሸፍን? እናንተ ስትጠረጉ ብቻ ነው! ምህረት አያሻም! ራቁታችንን መተያየት አለብን!”

የክፍሉ በር ከጀርባው ሲበረገድ የተንበረከከው ጺማም ሰው ዓይኖቹን ጨፈነ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
የቢሮውን በር በርግዶ ሲገባ ብርጋድየር ጀኔራሉ ከጠረጴዛው ጀርባ እንደተቀመጠ አፍጥጦ ተመለከተው፡፡
“ያዝነው!” አለ ማርቆስ ትንፍስ ትንፍስ እያል፡፡
“ናትናኤልን?” አለ ጀኔራሉ የሰማውን ለማረጋገጥ፡፡
“አዎ፡፡” አለ ማርቆስ ጭንቅላቱን ነቅንቆ ፀጉሩን እየደባበሰ፡፡
“ብታምነኝም ባታምነኝም እራሴን እስከምጠላ ተስፋ ቆርጬ ነበር፡፡”

“እንዴት ያዝስከው? ማለቴ የት?” አለ ጀኔራሉ ማርቆስን ተቀመጥ ሳይለው በቆመበት እንዳፈጠጠበት፡፡

“ባቡር ላይ፡፡” አለ ማርቆስ ወደፊት ተራምዶ ወንበር ላይ እየተቀመጠ፡፡ “ዛሬ ማታ ወደ ድሬዳዋ ለመሄድ ባቡር ላይ ሲሳፈር እዛ የመደብኳቸው ሁለት ሠራተኞቼ አይተውት አብረውት ተሳፍረዋል፡፡”

“ወደ ድሬዳዋ ተሳፍራል ነው የምትለኝ? ያዝኩት ያልከኝ መስሎኝ ነበር'ኮ፡፡” አለ ጀኔሪሉ ፊቱን አኮሳትሮ “መከታተሉ ምንድነው ትርጉሙ ለምን ቀጥታ አላስወገድከውም? "

“አታስብ... ከአዲስ አበባ እስከ ድሬዳዋ ያሉትን ጣቢያዎች በሙሉ በሰዎቻችን ሸኛቸዋለሁ፡፡”

“ባበሩ ሳያነሳ ለምን አልያዝከውም
“ጀኔራል ሰውየው ትኬት ሲቆርጥ ሰዎቻችን አላዩትም፡፡ ምናልባት
በሌላ ሰው እስቆርጦም ሊሆን ይችላል:: ድንገት ባቡር ላይ ሲሳፈር ያዩ ሠራተኞቼ ምርጫ ስላልነበራቸt ስልክ ደውለው ሲያስታወቀኝ ባበር ጣቢያ ውስጥ አስወጋጅ ሃያል ስላልነበረ ተከትለውት እንዲሳፈሩ አዘዝኳቸው።

ታዲያ ምኑን ነው ያዝኩት የምትለኝ?”

“ከዚህ ወድያ ሊያመልጥ አይችልም:: በየትኛውም ጣበያ ቢወርድ
ከማንም ጋር ከመገናኘቱ በፊት እንዲያስወግዱት ትዕዛዝ አስተላልፌአለሁ::”አለ ማርቆስ በፍጹም እርጋታ:: “በየጣብያው የሚጠባበቁት ሰዎች አሉ።

“አንተ ራስህ ለምን ድሬዳዋ በረህ አትጠብቀውም? የምልህ ይህን
ሰው አደገኛ ነው ጀኔራሉ ተረበሸ… “አንተ ራስህ ቀድመህ ብትጠበቀው
እመርጣለሁ:::”
“አንድ ሄሊኮፕተር እዛጋጅቼ እየተጠባበቅሁ ነው… ቀጥታ ወደ
ድሬዳዋ እንዳልበር ምናልባት በመሃል ሊወርድ ስለሚችል ባቡሩ እያንዳንዱን
ጣቢያ ሲያልፍ፡-የጣቢያው ያሉ ሰዎች የሬድዮ መልዕክት እያስተላለፉልኝ
እየጠበቅሁ ነው::”

“የት ነው ያለው ኣሁን?” አላ ጀኔራሉ በጉጉት፡፡
“ባቡሩ ናዝሬትን ማለፉን :: እንዳረጋገጥኩ ነው ወዳንተ የመጣሁት:: አላ ማርቆስ፡፡

ማርቆስ!” አለ ጀኔራሉ ፊቱ በጭንቀት ተወሮ፡፡ “ይህ አካሄድህ አላማረኝም እንበልና ይህ ሰው በሁለት ጣቢያዎች መሃል ከባቡሩ ቢዘል ምን ልታደርግ ነው? ከቦታው ላይ ምን ያህል ዘግይተህ እንደምትደርስ አታውቅም?”

“አብረውት የተሳፈሩት ሰዎች የነፍስ ወከፍ መሳሪያ የታወቁ ናቸው፡፡”

“የነፍስ ወከፍ መሣሪያ ይታጠቁ እንጂ ለዚህ ሥራ የሰለጠነና የተዘጋጁ አይመስሉኝም። ተራ የክትትል አባላት ናቸው… አይደለም?” አለ ጀኔራሉ ጠረጴዛውን ቡጢ ደልቆ፡፡

“እርግጥ የክትትል ሠራተኞች ናቸው ግን”

ማርቆስ! ማርቆስ! ምን እየሰራህ ነው?
👍3
#የፍቅር_ሰመመን


#ክፍል_ሰላሳ_ስድስት


#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን


#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው


“ተቀመጪ እባክሽን” አላት ወፍራሙ የግል መርማሪ ዴሪክ ዊሊያምስ
በአንድ እጁ የእንኳን ደህና መጣሽን አቀባበል፣ በሌላኛውም እጁ ደግሞ
እንድትቀመጥ እየጋበዛት፡፡ ቆዳ ወንበሩ ላይ ያሉትን ወረቀቶችም ጠርጎ አነሳላት።

“የዛሬው ውሎሽ እንዴት ነበር ዶክተር ሮበርትስ?” ብሎ ደስ በሚል ስሜት ጠየቃት። ቅድም በስልክ ካወራት በኋላ ጥሩ ስሜት ውስጥ ነው የሚገኘው።

“በእርግጥ ውሎዬ አድካሚ ነበር” ብላ ኒኪ እውነቱን ነግራው ጣቶቿን ሞዠቀች። “በእውነቱ ሁለቱን ታካሚዎቼን እንደማላድናቸው ዛሬ ላይ ለማወቅ ችያለሁ።” ብላ መለስችለት፡፡ ለምን እንደሆነ ባይገባትም ከዴሪክ ዊሊያምስ የሆነ ነገሩ የደህንነት ስሜት እንዲሰማት ያደርጋታል፡፡ ማለትም ሌሎች እሷን ለማማለል የሚፈልጉ ሰዎች ከሚያደርጉት እንክብካቤ በተለየ መልኩ ቅልል ይላታል፡፡

“ሁለት ብቻ? ዕድለኛ ሰው ነሽ ባክሽ፡፡” ብሎ ወደ ጉዳያቸው ከመግባታቸው በፊት ዴስኩን ነፃ አደረገ፡፡ “ባይገርምሽ ሁሉም ደምበኞቼ ከብዙ ጊዜ አስቀድመው ነው ነገሮች የተዘበራረቀባቸው። አንቺን ሳይጨምር
ማለቴ ነው እንግዲህ።” ብሎ ከቀለደ በኋላ ፈገግ ሲል ኒኪም ፈገግ አለች፡፡

“እሺ ያገኘኸው አዲስ ነገር ምንድነው?” ኒኪ በጉጉት ተሞልታ “ስለ ባሌ ውሽማ ቢሆን ደግሞ ደስ ይለኛል” አለችው።

“ስለ እሷ አይደለም፡፡ ይቅርታ” ብሎ ሲመልስላት በጉጉት ተሞልቶ
የነበረው የኒኪ ፊት ዳመነ፡፡

“አሁን ገና አይደለም እንዴ ምርመራውን የጀመርነው? እመኚኝ የጣውንትሽን ጉዳይ በቅርቡ እንቋጨዋለን። ዛሬ ላንቺ የምነግርሽ ነገር” ብሎ በኩራት ተሞልቶ ከተመለከታት በኋላ “በእውነት እንደ ጅማሬ በጣም ቆንጆ የሆነ ነገር ነው ብዬ አስባለሁ።” አላት፡፡

“እሺ እስቲ አስገርመኝ” አለችው ኒኪ የሚነግራትን ነገር ለማወቅ ጓጉታ፡፡

ዴሪክ ዊሊያምስ ጉሮሮውን አጥርቶ “አንቺ የሰጠሺኝን ነገሮችን በደንብ
አድርጌ ካነበብኩኝ በኋላ ጉዳዩን ከትሬይ ሬይሞንድ ለመጀመር ውሳኔ ላይ
ደረስኩኝ”

በዚሁ መሰረት ወደ ዌስትሞንት ሄዶ ምርመራውን ለመጀመር ሲል መርማሪ ፖሊስ ጆንሰንን እንዳገኘው፣ ጆንስን በዚያ ዘረኛ አመለካከቱን በሚያሳይ ሁኔታ የሬይሞንድን ቤተሰቦችም ሆነ በዙሪያቸው የሚገኙ የአደንዛዥ
ዕፅ አዘዋዋሪዎችን በጣም ተጭኖ
መረጃ እንዲነግሩት የጠየቃቸው መሆኑን እና ይሁን እንጂ ምንም ዓይነት መረጃ ሳያገኝ እንደሄደ፣ ይሄ ደግሞ ለእሱ ጥሩ ዕድልን እንዳመቻቸለት ካስረዳት በኋላ
ሲቪል መስሎ በመቅረብ መረጃዎችን እንዲሰጡት ሲጠይቃቸው ዕፅ
አዘዋዋሪዎቹ ልባቸውን ከፍተው መረጃዎቹን ወደሱ እንዳፈሰሱለት
ተረከላት፡፡ ኒኪ የዊሊያምስን ትረካ በጥሞና እያዳመጠችው ነበር፡፡ ዊሊያምስ ትረካውን አቋረጠና

“ትሬይ አደንዛዥ ዕፅ መጠቀሙን ያቆመው ባለቤትሽን አግኝቶ ከታከመ
በኋላ ነበር። ማለቴ ሁለት ዓመት አልፎታል አይደል?” ሲል ጠየቃት፡፡”

“አዎ ልክ ነህ። በዶውግ እገዛ የተነሳ ነው ዕፁን መጠቀሙን ያቆመው::”
ብላ መለሰችለት፡፡

“ልክ ብለሻል” ብሎ ዊሊያምስ በመቀጠልም “ግን ነገሮች እንደዚህ በቀላሉ የሚተው አይደሉም። መጠቀም ከማቆሙ በፊት ትሬይ በተለይ የ ሄሮይን
አደንዛዥ ዕፅን ያዘዋውር ነበር፡፡ በመጨረሻ ላይ ግን አዲስ የዲስሞርፊን
አይነት አደንዛዥ ዕፅን ማዘዋወር ጀመረ። ዕፁ በተጠቃሚዎቹ ላይ አደገኛ
አካላዊ እና አዕምሮአዊ ችግርን የሚያደርስ ነው። ተጠቃሚዎቹ ክሮክዲልዐብለው ነው የሚጠሩት” አላት፡፡

“ይህንን አደንዛዥ ዕፅ አውቀዋለሁ፡፡ የዶውግ ጓደኛ የሆነው ሀዶን ዶፎ
ወደ እነርሱ ክሊኒክ ለመታከም የሚመጡት ተጠቃሚዎች የሚወስዱት
ይህንን ዕፅ እንደሆነ እና አደንዛዥ ዕፁንም ሩሲያውያን እንደሚያመርቱት
ጭምር አጫውቶኛል።” አለችው ኒኪ፡፡
“ልክ ነሽ” አለና ኒኪ ስለ አደንዛዥ ዕፁ በማወቋ ትንሽ ተገረመ፡፡ “ትሬይ ለአንድ የሜክሲኮ አደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪ ነበር ይሠራ የነበረው። የአደንዛዥ ዕፁንም ገበያ ከሩሲያኖቹ ጋር እየተፎካከረ እንዲቀጥል አድርጎላቸው ነበር።
እነዚህ አብሯቸው ይሰራ የነበሩት ሰዎች አዲስ ህይወት መጀመሪያ ስለሚባል ነገር መስማት አይፈልጉም፡፡ እንዲያውም እሱ ሥራውንዐእንዲያቋርጥ በፍፁም የሚፈልጉ ሰዎች አይደሉም::”ፀ

“ግን እኮ እሱ እነዚህን ነገሮች ትቶ አዲስ ህይወት ጀምሯል እኮ!”ብላ ኒኪ ሙግቷን ቀጠለች እና “ዶውግ ከሱስ እንዲፈወስ ካደረገው በኋላ ትሬይ በሙሉ ተለውጧል። እኔም ቢሮዬ ውስጥ ሥራ ሰጠሁት።ትሬይ በየቀኑ ሰዓቱን አክብሮ በመገኘት ሥራውን በብቃት ሲወጣም ነበር”

“ይህ ቀን ቀን አንቺ ቢሮ ውስጥ ሲሰራ የነበረው ሥራው ነው፡፡” አላት፡፡እና ዊልያምስ በመቀጠልም “ባለቤትሽ የአደንዛዥ ዕፅ ሱሰኛን ከሱሱ በደንብ
አድርጎ እንዲላቀቅ የሚያደርግ ትልቅ ባለሙያ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ ነገር
ግን የናርኮቲክ ቢዝነሱን አስመልክቶ ብዙ የሚያውቅ አይመስለኝም፤ ሌላኛው
ትሬይን ቀጥሮ የሚያሰራው ሜክሲኳዊ የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪ አለቃው
ስም ካርሎስ ዲ ላ ሮዛ ይባላል” አላት እና ኒኪን ቀጥ ብሎ እየተመለከተ

ስሙን ስትሰማ ፊቷ ላይ ለውጥ እንዳመጣ ለማጣራት ቢሞክርም ፊትዋ
ላይ የተለየ ነገር ማንበብ አልቻለም። ምክንያቱም ትሬይ ከጀርባ ሆኖ
አደንዛዥ ዕፅ ያዘዋውር ነበር የሚለው ሃሳብ በጣም አስደንግጧት ነበር፡፡

እና ይሄ ያልከው ሰው ነው ትሬይን የገደለው? ወይም ያስገደለው ብለህ
ታስባለህ?”

“ይህንን እንኳ በእርግጠኝነት ልመልስልሽ ያስቸግረኛል ግን ሊሆን የማይችልበት ምክንያት የለም ብዬ እገምታለሁ፡፡ በተለይ ደግሞ አንቺ እንደነገርሽኝ ከሆነ ትሬይ ይህንን ስራውን ለማቆም ሙከራ ካደረገ ሊያስገድሉት ይችላል እላለሁ፡፡ ዴላ ሮዛ ዌስት ሞንት ውስጥ በጣም ትልቅ አሳ ሊሆን ይችላል” ብሎ ዊልያምስ ገለፃውን በመቀጠልም “ነገር ግን በአለም ዙሪያ ከሚገኙ ታላላቅ አደንዛዥ እጽ አምራቾች እና አዘዋዋሪዎች አንጻር ሲታይ እሱ ትንሽዬ የጥብስ አሳ ነው፡፡”

“የ ዴ ላ ሮዛ አለቃ እጅግ በጣም አደገኛ ሰው ነው፡፡ እዚህ ላይ ነው እንግዲህ ነገሩ ገራሚ ነገር የሚታይበት፡፡” አላት፡፡
“የዚህ እጅግ በጣም አደገኛ አለቃ ስም ማን ይባላል?” ብላ ኒኪ ጠየቀች፡፡

“ዶክተር ሮበርትስ ብታምኚኝም ባታምኚኝም ይህንን ሰው በሆነ መልኩ
የምታውቂው ሰው ነው፡፡ ሉዊስ ዶሚኒኩ ሮድሪጌዝ ይባላል።” ኒኪም ግንባርዋን ቋጥራ ስሙን የት እንደምታውቀው እያሰበች ቆየች።

“አኔ ቤታማን የምትባለው የአንቺ ታካሚ የዚህ ሰው ሚስት ናት” ካላት በኋላ ዊልያሚስ ላፕቶፑን አዙሮ የጎግል ኢሜጅ ላይ ያገኘውን የአንድ መልከ መልካም ዳር ዳሩ ላይ ሽበት ጣል ጣል ያደረገበት ጥቁር ሉጫ ጸጉር እና ጠንቃቃ አይኖች ያሉትን የላቲን ተወላጅ ፎቶ አሳያት፡፡
ኒኪም ግራ እንደተጋባች “ሚስተር ዊልያምስ የተሳሳትክ ይመስለኛል
ወይንም ደግሞ እንድትሳሳት ሆነሃል የአኔ ባለቤት እኮ የሪል እስቴቶችን
ገንብቶ የሚሸጥ የቢዝነስ ሰው ነው፡፡” አለችው፡፡

“ዴሪክ ብለሽ ጥሪኝ እባክሽን” ብሎ አስታወሳት እና በመቀጠልም “ምንም
ነገር አልተሳሳትኩም ሉዊስ ሮድሪጌዝ አኔ ቤታማንን ያገባት የዛሬ ስምንት አመት ኮስታሪካ ውስጥ ቀለል ባለ ሰርግ ነው ካላመንሽኝ የምስክር ወረቀታቸውን ኮፒ ላሳይሽ እችላለሁ እኔ ይህ ጉዳይ የሳበኝ ከዚህ በፊት ከሉዊስ ሮድሪጌዝ ጋር የሚገናኝ ስራ ሰርቼ ስለነበር ነው ጉዳዩም አንዲት ሜክሲኮ ውስጥ የጠፋች ወጣት ሴትን አስመልክቶ ነው፡፡ በይፋ ባይሆንም ሁሉም ሰዎች ወጣቷ ልጅ በሰው እንደተገደለች
👍61