#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
....“ ምናገባህ ? ሞዛዛ ?" ስትለው ድምጿ የብሽቀት ቅላጺ ነበረው ።
“እውነት ብርቄ ፥ ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ?” አላት ሳምሶን?
"አራት ዓመት!”
"የአራት ዓመት የሥራ ልምድ ! ከሌሎቹ አንጻር ሲታይ ትንሽ ነው ” እላት ሳምሶን "
“ መላጣ ! ” አለችው ፡ ጭንቅላቱን በዐይኗ ቂጥ እያየችው ።
“ በአራት ዓመት ውስጥ ስምሽን ለመለወጥ አልሞክርሽም ? ”አላት እስክንድር ሲቀልድባት ፡ “ እዲስ የከተማ
ስም እንደ ራሄል ኤደን ማርታ ፡ ዓለም ከተሜ ለመሆን እ ? ”
“ሒድ'ደረቅ ! ”
ሒድ፡ደረቅ !ሒድ፡ደረቅ!ደረቅ ማርታ በቅናት ቅንድቧን እያርገበገበች ከፊቱ ድቅን አለችበት ። በሐሳቡ ቁመናዋን ቃኘ በሞቅታ መንፈስ እንደገና አለማት ፡ ኪሱ ባዶ ማለም ብቻ ! ማነጣጠር ብቻ !
"ሒድ ፡ ደረቅ የሴቶች የጋራ ፈሊጽ ” አለ በልቡ ።
የብርቅነሽ ጥሬነት አስገረመው ፡ ስትጫወት የባላገር ለዛ አላት ። ንቅሳቷ ባላገርነቷን ይመሰክራል የባላገር ስሟን
አልለወጠችም " እምብዛም የከተሜ ጭምብል አላጠለቀችም ግን ከሀገርሽ ለምን ወጣሽ ? ” አላት በድንገት ።
“ ሆሆይ !ጋዜጠኛ ነህ እንዴ ?”
ባልሆን ፥ ይህን ሥራ ምን አስመረጠሽ ፡ ማለቴ ነው ። ””
“ ዋ ! ወድጄን መሰለህ ? ግድ ሆኖብኝ እንጂ ” ከማለቷ ፊቷ የኀዘን ጭጋግ ለበሰ
“ ምነው ?እንዴ? ” አላት እስክንድር ስሜቷን ተከትሎ ስሜቱ እየዳመነ።
“ ባልተቤቴ ነው ለነዚ ያበቃኝ ! በሱ ምክንያት ነው ሀገሬን ለቅቄ የወጣሁት እያለች የታሪኳ ዳር ዳር ጨረፈችው
በፍቅር ለቀረባት ሁሉ ታሪኳን ታወራለች
ልስ ልስ ሆኖ ለቀረባት የአንጀቷን ትዘከዝካለች የተማረ መስሎ ለታያት ችግሯን አፍረጥርጣ ትናገራለች ። መፍትሔ ይገኝልኛል ብላ አይደለም :: የውስጧን ተንፍሳ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን የመንፈስ እረፍት ታገኛለች።
«« እባክሽ አታጓጊን ፣ በደንብ አጫውቺን" አላት እስክንድር ታሪኳን ለመስማት ተጣድፎ።
“ አያችሁ እናንተ ዕድለኞች ናችሁ : ከደኅና ቤተሰብ በመወለዳችሁ ወይም ከተማ በማደጋችሁ ለመማር በቅታችሆል እኔ የቀለም ትምህርት የለኝም ማንበብና መፃፍ እንኳ የቻልኩት አሁን የመሰረተ ትምህርት ዘመቻ ከተጀመረ ወዲህ ነው።
የድሀ ገበሬ ልጅ ነኝ ። ያውም በእንጀራ
እናት ያደግኩ !ህም እቴ! ታድያ በአሥራ አራት ዓመቴ ተዳርኩ ። ባሌ ገበሬ ነበር ። እኔ ሁለተኛ ሚስቱ ነኝ ።የመጀመሪያ ሚስቱ ከተጋቡ መንፈቅ እንኳ ሳይሞላቸው ሞታበት ነበር ። ወላጆቼም ሲድሩኝ ይህን ያቃሉ በእድሜ በሰል ያለ ነው ። ጸባዩም ጥሩ ነው ለትዳሩ ታታሪ ነው ” ተባለና ተሰጠሁ ።
“ ጎጆአችንን እያሞቅን ፡ የባላባቶችን ግልምጫና ዱላ በጋራ እየተቀበልን መኖር ጀመርን ፡ ምን ይሆናል ። እግዜር ለትንኮሉ ማሕፀኔን ድፍን እደረገው። ዓመት ጠበቅን ሁለት ዓመት ጠበቅን ልጅ የለም ። በእኔና በባልተቤቴ መሐል ቅሬታ መጣ ያም ሆኖ አልተቃቃርንም ። ድህነት ያስተሳስረን ነበር ። እሱ ከገበሬዎቹ ጋር ውጭ ደክሞ ውሎ ሲመጣ ከቤት ያለሁ
ረዳቱ እኔው ነበርኩ በባላባት ጅራፍ ጀርባው ቆስሎ ሲመጣ አንጀቴ እየተንሰፈሰፈ የማለቅስላት እኔ ነበርኩ ዋ! እቴ ምን ያደርጋል!
እንዲህ እንዲህ እያልን አምስት ዓመት ያህል እንደኖርን አብዮቱ ፈነዳ ። ለውጥ መጣ ። ደክመን ለባላበት መገበሩ ቀረ። እፎይ አለን ። ቤታችን ሙሉ ሆነ እውነቴን ነው ደህና ነገር መብላት መልበስም ጀመርን ። ምን ይሆናል ። ከድህና
ኑሮ ጋር ተያይዞ ነገር መጣ ባልተቤቴ ሌላ ሴት ጋር በስርቆት መሔድ ጀምሯል የሚል ወሬ ሰማሁ ። ስውል ሳድር እኔም
ነገሩን ደረስኩበት። እንዲያውም አንድ ልጅ እንደ ወለደችለት አረጋገጥኩ ። ቀናሁ ! ቅናት አንገበገበኝ ። በሐሳብ
ተብከነከንኩ። ጨስኩ ።ቤት ውስጥ !
መቀመጥ አቃተኝ ብዙም ሳልቆይ ጓዝ ምንጓዝ ሳልል በርሬ ወጥቼ አዲስ አበባ ገበኋት !
“ እዚህ ስደርስ ደግሞ ያዘጋጀሁት ማረፊያ የለኝ ፥ እንደሁ ሜዳ ቀረሁ ። ትንሽ ቀን ሰንብቼ በደላላ አማካይነት
ግርድና ተቀጠርኩ። ስድስት ወር እንደ ሰራሁ ግርድናን እርም ብዬ ተውኩት። አባስኩ እቴ ! የሰው ቤት ሹሮ ሲያልቅ
እኔ ላይ ማፍጠጥ ። ዕቃ ሲጠፉ እኔን መወንጀል ። ምነው ከዚህ ሁሉ ሥጋዬን ሸጨ ባድር አልኩና ሽርሙጥና ጀመርኩ
እላችኋለሁ ።
ብርቅነሽ ስትናገር ታላቅ ማዕበል ተነሥቶ ባሕር ውስጥ የከታቸውን ያኸል ሥስቱም ጸጥ ብለው ነበር ። አሳዘነቻቸው። ምስኪን ጥሬ ፍጥረት ! በመጠጥ ሞቅታ ኃይል ለሁሉ ነገር ግዴለሽ ሆኖ የቆየው አቤል እንኳ፥ ከብርቅነሽ አፍ የድህነት ድምፅ ሲሰማ ቸል ማለት አልቻለም ። ሕዋሳቱ በኀዘን ስሜት ተወራጩ ::
ግን ዝዎም ብለሽ ከምትኮበልይ ፥ ሰላምን በአካባቢሽ በሚገኘው የሴቶች ወይም የገበሬ ማኅበር አመልክተሽ መፍ
ትሔ ኣትፈልጊም ነበር ? ” እላት እስክንድር ፡ ከማዘኑ የተነሣ የሚናገረው ጠፍቶት ።
ዋ እቴ ! ቤት ከፈረሰ ወዲያ ሁሉስ ምን ሊበጅ ? አየህ ፡ ቅናት ከመጣ ቤት ፈረሰ ማለት ነው። ለሁሉም እኔ ለማንም አላማከርኩ ። የሚያለቅሱ ልጆች የሉኝ ' ነጠላ ሰው ምናለበት አልኩና ብር ብዬ አዲስ አበባ ፣ ”
ታዲያ ባልሽ ሊፈልግሽ አልመጣም ” አላትአቤል በሁኔታዋ ስሜቱ ተነክቶ ።
“ ውእእይ • ሥራ አጥቶ ! እንዲያውም ከዚያ ሀገር ለንፀግድ የሚመላለሱ ሰዎች እዚሁ ቡና ቤት አግኝቼ ሲነግሩኝ' ውሽማውን ጠቅልሎ ይዟል አሉኝ • እዩዬ ! ” ብላ ሳትጨርስ ጥሬ ሰማች «
“ ብርቅነሽ ? ! አንቺን'ኮ ነው ? ” የቡና ቤት ባለቢቷ ድምፅ ነበር
“ እመት ! ወይ ጕዱ ዛሬ ! ” እያለች ብርቅነሽ ከተቀመጠችበት ተነሣች
“ እንድዩ ! ሰው ሲገባ አትታዘዥም እንዴ! ምን ይጎልትሻል ? ”
ብርቅነሽ የውስጧን ተንፍሳ ቃጠሎዎን አብርዳ ተነሣች ፡ እስክንድር ተከዘ ቃጠሉዋ ወደ እሱ ተላለፈበት ኀዘኗ ጠልቆ ወጋው ። ቅናት ተፈጥሮአዊ ነው ሀብታምና ድሀ አይልም ። የወደደ ሁሌ ለወደደው ነገር ይቀናል ። ለቀናበት ነገር ይሠዋል ። ብርቅነሽ የቅናትን እሳት ሸሽታ ኮበለለች ። ከቅናት ሸሽታ ሴትኛ አዳሪ ሆነች "
እስክንድር ሐሳቡ ከግላዊነት ወደነማኅበራዊነት መጠቀ ለእሱ ሲጋራ መግዣ መስጠት ያቃታቸው ደሀ እናቱ ላይ ሆኑ፡ሕዝቧን በሰፊው ማስተማር ' በቂ ኢንዱስትሪ ከፍታ እነብርቅነሽን ማሠማራት ያልቻለች ረሀብን ለማጥፋት
ማይምነትን ለማጥፋት ርካሽ ልምዶችን ለማስወገድ በባህል ለማደግና የቴክኖሎጂ ውጤት ተጠቃሚ ለመሆን የልጆቿን እጅ የምትማጠን እናት ሀገር፡እጆቿን ዘርግታ በሐሳቡ ታየችው
ከሐሳቡ ፋታ አግኝቶ እሱነቱን ወዳለበት ሲመልስ ምሶን ዐይኑን አፍጥጦ ተመለከተ ።አስተያየቱ አላማረውም ። በልቡ ምርምርህን እዚያው ዩኒቨርስቲው ውስጥ አድርገው ፥ ይሄ መጠጥ ቤት ነው የሚለው መሰለው "
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
....“ ምናገባህ ? ሞዛዛ ?" ስትለው ድምጿ የብሽቀት ቅላጺ ነበረው ።
“እውነት ብርቄ ፥ ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ?” አላት ሳምሶን?
"አራት ዓመት!”
"የአራት ዓመት የሥራ ልምድ ! ከሌሎቹ አንጻር ሲታይ ትንሽ ነው ” እላት ሳምሶን "
“ መላጣ ! ” አለችው ፡ ጭንቅላቱን በዐይኗ ቂጥ እያየችው ።
“ በአራት ዓመት ውስጥ ስምሽን ለመለወጥ አልሞክርሽም ? ”አላት እስክንድር ሲቀልድባት ፡ “ እዲስ የከተማ
ስም እንደ ራሄል ኤደን ማርታ ፡ ዓለም ከተሜ ለመሆን እ ? ”
“ሒድ'ደረቅ ! ”
ሒድ፡ደረቅ !ሒድ፡ደረቅ!ደረቅ ማርታ በቅናት ቅንድቧን እያርገበገበች ከፊቱ ድቅን አለችበት ። በሐሳቡ ቁመናዋን ቃኘ በሞቅታ መንፈስ እንደገና አለማት ፡ ኪሱ ባዶ ማለም ብቻ ! ማነጣጠር ብቻ !
"ሒድ ፡ ደረቅ የሴቶች የጋራ ፈሊጽ ” አለ በልቡ ።
የብርቅነሽ ጥሬነት አስገረመው ፡ ስትጫወት የባላገር ለዛ አላት ። ንቅሳቷ ባላገርነቷን ይመሰክራል የባላገር ስሟን
አልለወጠችም " እምብዛም የከተሜ ጭምብል አላጠለቀችም ግን ከሀገርሽ ለምን ወጣሽ ? ” አላት በድንገት ።
“ ሆሆይ !ጋዜጠኛ ነህ እንዴ ?”
ባልሆን ፥ ይህን ሥራ ምን አስመረጠሽ ፡ ማለቴ ነው ። ””
“ ዋ ! ወድጄን መሰለህ ? ግድ ሆኖብኝ እንጂ ” ከማለቷ ፊቷ የኀዘን ጭጋግ ለበሰ
“ ምነው ?እንዴ? ” አላት እስክንድር ስሜቷን ተከትሎ ስሜቱ እየዳመነ።
“ ባልተቤቴ ነው ለነዚ ያበቃኝ ! በሱ ምክንያት ነው ሀገሬን ለቅቄ የወጣሁት እያለች የታሪኳ ዳር ዳር ጨረፈችው
በፍቅር ለቀረባት ሁሉ ታሪኳን ታወራለች
ልስ ልስ ሆኖ ለቀረባት የአንጀቷን ትዘከዝካለች የተማረ መስሎ ለታያት ችግሯን አፍረጥርጣ ትናገራለች ። መፍትሔ ይገኝልኛል ብላ አይደለም :: የውስጧን ተንፍሳ ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን የመንፈስ እረፍት ታገኛለች።
«« እባክሽ አታጓጊን ፣ በደንብ አጫውቺን" አላት እስክንድር ታሪኳን ለመስማት ተጣድፎ።
“ አያችሁ እናንተ ዕድለኞች ናችሁ : ከደኅና ቤተሰብ በመወለዳችሁ ወይም ከተማ በማደጋችሁ ለመማር በቅታችሆል እኔ የቀለም ትምህርት የለኝም ማንበብና መፃፍ እንኳ የቻልኩት አሁን የመሰረተ ትምህርት ዘመቻ ከተጀመረ ወዲህ ነው።
የድሀ ገበሬ ልጅ ነኝ ። ያውም በእንጀራ
እናት ያደግኩ !ህም እቴ! ታድያ በአሥራ አራት ዓመቴ ተዳርኩ ። ባሌ ገበሬ ነበር ። እኔ ሁለተኛ ሚስቱ ነኝ ።የመጀመሪያ ሚስቱ ከተጋቡ መንፈቅ እንኳ ሳይሞላቸው ሞታበት ነበር ። ወላጆቼም ሲድሩኝ ይህን ያቃሉ በእድሜ በሰል ያለ ነው ። ጸባዩም ጥሩ ነው ለትዳሩ ታታሪ ነው ” ተባለና ተሰጠሁ ።
“ ጎጆአችንን እያሞቅን ፡ የባላባቶችን ግልምጫና ዱላ በጋራ እየተቀበልን መኖር ጀመርን ፡ ምን ይሆናል ። እግዜር ለትንኮሉ ማሕፀኔን ድፍን እደረገው። ዓመት ጠበቅን ሁለት ዓመት ጠበቅን ልጅ የለም ። በእኔና በባልተቤቴ መሐል ቅሬታ መጣ ያም ሆኖ አልተቃቃርንም ። ድህነት ያስተሳስረን ነበር ። እሱ ከገበሬዎቹ ጋር ውጭ ደክሞ ውሎ ሲመጣ ከቤት ያለሁ
ረዳቱ እኔው ነበርኩ በባላባት ጅራፍ ጀርባው ቆስሎ ሲመጣ አንጀቴ እየተንሰፈሰፈ የማለቅስላት እኔ ነበርኩ ዋ! እቴ ምን ያደርጋል!
እንዲህ እንዲህ እያልን አምስት ዓመት ያህል እንደኖርን አብዮቱ ፈነዳ ። ለውጥ መጣ ። ደክመን ለባላበት መገበሩ ቀረ። እፎይ አለን ። ቤታችን ሙሉ ሆነ እውነቴን ነው ደህና ነገር መብላት መልበስም ጀመርን ። ምን ይሆናል ። ከድህና
ኑሮ ጋር ተያይዞ ነገር መጣ ባልተቤቴ ሌላ ሴት ጋር በስርቆት መሔድ ጀምሯል የሚል ወሬ ሰማሁ ። ስውል ሳድር እኔም
ነገሩን ደረስኩበት። እንዲያውም አንድ ልጅ እንደ ወለደችለት አረጋገጥኩ ። ቀናሁ ! ቅናት አንገበገበኝ ። በሐሳብ
ተብከነከንኩ። ጨስኩ ።ቤት ውስጥ !
መቀመጥ አቃተኝ ብዙም ሳልቆይ ጓዝ ምንጓዝ ሳልል በርሬ ወጥቼ አዲስ አበባ ገበኋት !
“ እዚህ ስደርስ ደግሞ ያዘጋጀሁት ማረፊያ የለኝ ፥ እንደሁ ሜዳ ቀረሁ ። ትንሽ ቀን ሰንብቼ በደላላ አማካይነት
ግርድና ተቀጠርኩ። ስድስት ወር እንደ ሰራሁ ግርድናን እርም ብዬ ተውኩት። አባስኩ እቴ ! የሰው ቤት ሹሮ ሲያልቅ
እኔ ላይ ማፍጠጥ ። ዕቃ ሲጠፉ እኔን መወንጀል ። ምነው ከዚህ ሁሉ ሥጋዬን ሸጨ ባድር አልኩና ሽርሙጥና ጀመርኩ
እላችኋለሁ ።
ብርቅነሽ ስትናገር ታላቅ ማዕበል ተነሥቶ ባሕር ውስጥ የከታቸውን ያኸል ሥስቱም ጸጥ ብለው ነበር ። አሳዘነቻቸው። ምስኪን ጥሬ ፍጥረት ! በመጠጥ ሞቅታ ኃይል ለሁሉ ነገር ግዴለሽ ሆኖ የቆየው አቤል እንኳ፥ ከብርቅነሽ አፍ የድህነት ድምፅ ሲሰማ ቸል ማለት አልቻለም ። ሕዋሳቱ በኀዘን ስሜት ተወራጩ ::
ግን ዝዎም ብለሽ ከምትኮበልይ ፥ ሰላምን በአካባቢሽ በሚገኘው የሴቶች ወይም የገበሬ ማኅበር አመልክተሽ መፍ
ትሔ ኣትፈልጊም ነበር ? ” እላት እስክንድር ፡ ከማዘኑ የተነሣ የሚናገረው ጠፍቶት ።
ዋ እቴ ! ቤት ከፈረሰ ወዲያ ሁሉስ ምን ሊበጅ ? አየህ ፡ ቅናት ከመጣ ቤት ፈረሰ ማለት ነው። ለሁሉም እኔ ለማንም አላማከርኩ ። የሚያለቅሱ ልጆች የሉኝ ' ነጠላ ሰው ምናለበት አልኩና ብር ብዬ አዲስ አበባ ፣ ”
ታዲያ ባልሽ ሊፈልግሽ አልመጣም ” አላትአቤል በሁኔታዋ ስሜቱ ተነክቶ ።
“ ውእእይ • ሥራ አጥቶ ! እንዲያውም ከዚያ ሀገር ለንፀግድ የሚመላለሱ ሰዎች እዚሁ ቡና ቤት አግኝቼ ሲነግሩኝ' ውሽማውን ጠቅልሎ ይዟል አሉኝ • እዩዬ ! ” ብላ ሳትጨርስ ጥሬ ሰማች «
“ ብርቅነሽ ? ! አንቺን'ኮ ነው ? ” የቡና ቤት ባለቢቷ ድምፅ ነበር
“ እመት ! ወይ ጕዱ ዛሬ ! ” እያለች ብርቅነሽ ከተቀመጠችበት ተነሣች
“ እንድዩ ! ሰው ሲገባ አትታዘዥም እንዴ! ምን ይጎልትሻል ? ”
ብርቅነሽ የውስጧን ተንፍሳ ቃጠሎዎን አብርዳ ተነሣች ፡ እስክንድር ተከዘ ቃጠሉዋ ወደ እሱ ተላለፈበት ኀዘኗ ጠልቆ ወጋው ። ቅናት ተፈጥሮአዊ ነው ሀብታምና ድሀ አይልም ። የወደደ ሁሌ ለወደደው ነገር ይቀናል ። ለቀናበት ነገር ይሠዋል ። ብርቅነሽ የቅናትን እሳት ሸሽታ ኮበለለች ። ከቅናት ሸሽታ ሴትኛ አዳሪ ሆነች "
እስክንድር ሐሳቡ ከግላዊነት ወደነማኅበራዊነት መጠቀ ለእሱ ሲጋራ መግዣ መስጠት ያቃታቸው ደሀ እናቱ ላይ ሆኑ፡ሕዝቧን በሰፊው ማስተማር ' በቂ ኢንዱስትሪ ከፍታ እነብርቅነሽን ማሠማራት ያልቻለች ረሀብን ለማጥፋት
ማይምነትን ለማጥፋት ርካሽ ልምዶችን ለማስወገድ በባህል ለማደግና የቴክኖሎጂ ውጤት ተጠቃሚ ለመሆን የልጆቿን እጅ የምትማጠን እናት ሀገር፡እጆቿን ዘርግታ በሐሳቡ ታየችው
ከሐሳቡ ፋታ አግኝቶ እሱነቱን ወዳለበት ሲመልስ ምሶን ዐይኑን አፍጥጦ ተመለከተ ።አስተያየቱ አላማረውም ። በልቡ ምርምርህን እዚያው ዩኒቨርስቲው ውስጥ አድርገው ፥ ይሄ መጠጥ ቤት ነው የሚለው መሰለው "
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
እነሱ ለትህትና ሕይወት እንደዚያ ሲሯሯጡ ደግሞ የእንደሻው ወላጆች ደግሞ የልጃቸውን ህይወት ለማትረፍ ከላይ ከተች እየተሯሯጡም ብቻ ሳይሆን እየተራወጡ ናቸው። የእንደሻው ጉዳት ከባድ ነበር። በተለይ አንዷ ጥይት የራስ ቅሉን በስታው ስላለፈች፤ የአእምሮ ቀውስ
እንዳያስከትልበት፤ ከፍተኛ ስጋት አለ፡፡
በተፈጠረው አደጋ ምክንያት የእንደሻው ወላጆችና የአዜብ ወላጆችም ግንኙነት አቋርጠዋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ...
"ያቺን የተረገመች ልጅ አምጥታ ልጃችንን ልታስገድለው የነበረችው አዜብ ነች በሚል ሲሆን፤ ፀቡን ከአዜብ ጋር ብቻ ሳይሆን ከቤተሰቦቿ ጭምር አድርገውታል :: እነሱ እንደዚያ ብለው ይናገሩ እንጂ ፤ የአዜብ ወላጆች ሁኔታው ሊፈጠር የቻለው አለሌው ልጃቸው
በፈፀመው ተደጋጋሚ አስነዋሪ ድርጊት ሳቢያ መሆኑን ሲያውቁ የክርስትና ልጃችን ነው በሚል ምክንያት ብቻ ፤ በትህትና ላይ ሊፈርዱባት
አልደፈሩም....
"ሁሉንም ስራው ያውጣው በማለት መጨረሻውን ለማየት እየተጠባበቁ ናቸው፡፡ ትህትና ጤናዋ በከፍተኛ ፍጥነት እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም፤ ጐን ለጐን በነፍስ ማጥፋት ሙከራ ወንጀል በአቃቤ ህግ ክስ ተመሰረተባት፡፡ አዜብና ብሩክ ይህንን እንዳወቁ ቀጣዩ ትኩረታቸው
በምን ላይ መሆን እንዳለበት በስፋት ተመካከሩ፡፡ ከዚያም አንዳንድ
በመከላከያነት ይጠቅማሉ ያሏቸውን ማስረጃዎች ለማሰባሰብ ፤ ሁለቱም
በየፊናቸው ሩጫ ጀመሩ፡፡ ለዚህ ጉዳይ አበራ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገመቱ :: ምክንያቱም አበራ በእንደሻው ክህደት የደረሰበትና፤ በትህትና ላይ ስለተፈፀመው ወንጀል በሚገባ የሚያውቅ የአይን ምስክር ስለነበረ ነው፡፡ አበራ በእንደሻው ስለተፈፀመበት ክህደት ለአገሩ ሁሉ ሲያወራ ለአዜብም አጫውቷት ነበር ፡፡
ከዝምድና ይልቅ ገንዘብን አስበልጦ አስር
አመት ሙሉ ያጠራቀምኩትን ገንዘቤን ወስዶ ከከበረበት በኋላ ከዳኝ፡፡ በጋራ
እናድግበታለን ብሎ የገባውን ቃሉን አፍርሶ አባረረኝ " በማለት በምሬት ነበር የገለፀላት፡፡ ታዲያ ያ ሁሉ በደል የተፈፀመበት ሰው ፍርድ ቤት ቀርቦ እውነቱንና የሚያውቀውን ከመናገር ወደኋላ ሊል ይችላል? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ በፍፁም ወደኋላ አይልም ስትል ተማመነች፡፡ምክንያቱም እሱ እንደዚያ በንዴት እየተንቀጠቀጠ
ሲነግራት...
“አይዞህ አበራ ተወው፡፡ አንተ ጤና ሁን እንጂ ፤ገንዘብ አላፊ ጠፊ ነው፡፡ በክህደት የተገኘ ገንዘብ ደግሞ የትም አያደርስም፡፡
ከሰራህ ከካደህ ሰው በላይ መሆን ትችላለህ :: አይዞህ! እግዚአብሄር ላንተ ያለውን ምንግዜም አታጣውም " በማለት ትልቅ የማፅነኛ ቃል ለግሳው ነበር፡፡ ያንን
የሰጠችውን የተስፋ ቃል እንኳ አስታውሶ እሺ ይላት ይሆን? ወይንስ እሱም እንደወላጆቹ ተደርቦ ከእውነት ጀርባ ይቆም ይሆን? ልቧ ተጠራጠረ፡፡ ለማንኛውም አለችና ስልክ ደወለችለት :: ስልኩን አነሳና እሷ መሆንዋን ሲያውቅ የሞቀ ሰላምታ አቀረበላት፡፡ ትንሽ እፎይ አለች በልቧ፡፡ለጉዳይ እንደምትፈልገው
ስትገልፅለት፤ በደስታ ተቀብሎ የሚገናኙበትን ቦታ ተቀጣጥረው
ተሰነባበቱ፡፡ በማግስቱ በቀጠሮው ቦታ ቀድሞ የደረሰው እሱ ነበር።
የተፈለገበትን ጉዳይ ስትነግረው...
"ተይ እንጂ አዜብ እቤት ድረስ የወሰድኳት እኮ እኔ ነኝ፡፡በወንጀለኛነት አያስጠይቅህም ነው የምትይኝ?" ሲል በጥርጣሬ ጠየቃት።
"ስለሱ ከሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል፡፡ አንተን በወንጀል
ተባባሪነት እንዳያስጠይቅህ በቂ ምክንያት ማቅረብ ይቻላል፡፡”
"ለምሳሌ ምን?"
"አበራ ሙት ምንም አትፍራ! በዚህ ጉዳይ አንተ በጥፋተኛነት እንድትጠየቅ የሚፈልግ ሰው የለም፡፡ አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር ፧ አንተ ይዘሃት የሄድከው ወደ ቀጣሪዋ ቤት እንጂ፤ ወንጀል
ወደሚፈጸምበት ጫካ ውስጥ አይደለም፡ቀጣሪዋ ቤት አደረስካት ማለት፤ እንደሻው ደብድቦና፤ አስገድዶ፧ ክብረ ንፅህናዋን እንዲደፍራት አደረክ ማለት አይደለም :: የቀጣሪዋን ቤት የወንጀል መፈፀሚያ ዋሻ ያደረገው ወንጀለኛ ብቻ ነው ለዚህ ተጠያቂ የሚሆነው፡፡ አይዞህ ምንም የሚያስፈራ ነገር የለውም፡ አበራን ለማሳመን ብሎ ብሩክ ያስጠናትን ደሰኮረችለት፡፡ አበራ ልቡ ትንሽ ተለሳለሰ፡፡
"በሌላ በኩል ብታየው ደግሞ የቀጣሪዋ ባለቤት ልጅ የቅጥር ውል እንድትፈርም ይዘሃት ና ብሎ አዘዘህ :: አንተም ይህን ነገርካት። እሷም እሺ ብላ ሳታስገድዳት በፈቃደኝነት አብራህ ሄደች። ከዚያም አንተ በሌለህበት እንደሻው ወንጀል ፈፅሞባት ደረስክ፡፡ በቃ፡፡ ይህ አይደለም
ታሪኩ? አንተን የሚያስጠይቅህ ምኑ ነው ታዲያ?" ስትል የማደፋፈሪያ
ሀሳብ አዥጐደጐደችለት፡፡
በልቡ ያሳደረው ጥርጣሬ ሙሉ ለሙሉ ባይጠፋለትም፤ በአዜብ አቀራረብ ተስማማ፡፡ እንዳለችውም እሱን በቀጥታ ተጠያቂ ሊያደርገው የሚችል ጭብጥ እንደሌለ ተሰማው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ
ያቺ ምስኪን እንጀራ ፈላጊ ልጅ ፤ በደም ተጨማልቃ ወድቃ ያያት እለት የተሰማው ስሜት ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡ በተፈፀመባት ወንጀል ከልቡ አዝኖ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ያ ግፈኛ ከሃዲ ከሱቁ ካባረረው በኋላ አሁን አሁን በርካታ ካፒታል በማንቀሳቀስ በቅናት እያቃጠለው
ነው፡፡ በጥይት መቃጠሉን የሰማ እለት " እሰይ የእጁን ነው ያገኘው"ነበር ያለው፡፡ አሁን ደግሞ እሱ ተጠያቂ በማይሆንበት ሁኔታ ለምን ያየውን ከመመስከር ወደ ኋላ ማለት እንደሌለበት ተገነዘበ ፡፡ያየኽውን እውነት መሰከርክ ብሎ የሚፈርድበት ዘመድ እንደማይኖርና፤ ቢኖርም መፅሀፍ ቅዱስ ይዞ በሚፈፅመው መሃላ በውሸት መስክሮ ነፍሱን ማስኮነን እንደሌለበት ተሰማው። እንደሻውን ሊበቀል
የሚችልበትን ይህንን መልካም አጋጣሚ ሊጠቀምበት ወሰነ : እንቢ ቢልስ የት ሊደርስ ? በተለይ አዜብ እየነገረችው
ያለው ፣ ባለስልጣን ፖሊስ ከአዜብ በስተጀርባ መኖሩን ነው፡፡ በተለይ "ሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል"
ስትለው ምን እያለች እንደሆነ
ገብቶታል፡፡አልመሰክርም ቢል በተባባሪ ወንጀለኛነት ተፈርጆ፣ ለፍርድ እንደሚቀርብ እየነገረችው ነው፡፡ ይሄንን ጭምር አስቦ፤ ልቡ ስለፈራ፤ ያየውን ሁሉ በዝርዝር ሊያስረዳና፤ ለትህትና ድንበሩ የመከላከያ ምስክር ሊሆን ቃል ገባላት፡፡ ቃል መግባት ብቻም ሳይሆን ተጨማሪ ማስረጃ ጠቆማት..
"እኔ ብቻ ሳልሆን በዚያን እለት ሁኔታውን የተመለከተችው የቤት ሰራተኛዋ ወርቅ ያንጥፉም ያየችውን ሁሉ እውነቱን ሳትደብቅ እንድትመሰክር እናደርጋለን :: ደግሞም ትመሰክራለች፡፡ አትጠራጠሪ!
በትህትና ሁኔታ በጣም ነው ያዘነችው፡፡እሷም ስመ እግዚአብሄርን ጠርታ
ያየችውን ሁሉ ትመሰክራለች፡፡ አይዞሽ ! " አላት፡፡ አዜብ ከጠበቀችው በላይ ተባባሪ ሆኖ ስለኣገኘችው፤ በደስታ እቅፍ አደረገችው፡፡ በዚሁ መሰረት አበራና ወርቅ ያንጥፉ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው፤ የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ተደረገ፡፡ ቀኑን፡ ሰአቱን፡ የድርጊቱን አፈፃፀም፡ ዝርዝር ሁኔታውን፤ በሙሉ በአንድ አይነትና ፤ ተመሳሳይ በሆነ ቃል
መሰከሩ። ያም ብቻ ሳይሆን አንዱአለምን ጋርጠው በሚል ቅፅል ስሙ በሚታወቀው ወሮበላ እንዳይሞት፤ እንዳይድን፤ አደርጐ ያስደበደበው
መሆኑን፤ ራሱ እንደሻው በኩራት ሲናገር መስማቱን፧ ጭምር ገለፀ፡፡
በእርግጥም እንደሻው ያንን ለአበራ የተናገረው፤ ይሄ ይመጣብኛል ብሎ ሳይሆን፤ አንተም አርፈህ የማትቀመጥና ወሬ አበዛለሁ የምትል ከሆነ፤ አስወቅጥሀለሁ፤ የሚል ማስጠንቀቂያ ለመስጠት ነበር፡፡ ሆኖም በዚህ አጋጣሚ እንደሻውን የደበደበው ጉልበተኛ
ስለታወቀ፤ ወዲያውኑ ታድኖ እንዲያዝ ሲደረግ ፤ አበራ ማንነቱን በማሳየትና የሚገኝበትን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
እነሱ ለትህትና ሕይወት እንደዚያ ሲሯሯጡ ደግሞ የእንደሻው ወላጆች ደግሞ የልጃቸውን ህይወት ለማትረፍ ከላይ ከተች እየተሯሯጡም ብቻ ሳይሆን እየተራወጡ ናቸው። የእንደሻው ጉዳት ከባድ ነበር። በተለይ አንዷ ጥይት የራስ ቅሉን በስታው ስላለፈች፤ የአእምሮ ቀውስ
እንዳያስከትልበት፤ ከፍተኛ ስጋት አለ፡፡
በተፈጠረው አደጋ ምክንያት የእንደሻው ወላጆችና የአዜብ ወላጆችም ግንኙነት አቋርጠዋል፡፡ ምክንያታቸው ደግሞ...
"ያቺን የተረገመች ልጅ አምጥታ ልጃችንን ልታስገድለው የነበረችው አዜብ ነች በሚል ሲሆን፤ ፀቡን ከአዜብ ጋር ብቻ ሳይሆን ከቤተሰቦቿ ጭምር አድርገውታል :: እነሱ እንደዚያ ብለው ይናገሩ እንጂ ፤ የአዜብ ወላጆች ሁኔታው ሊፈጠር የቻለው አለሌው ልጃቸው
በፈፀመው ተደጋጋሚ አስነዋሪ ድርጊት ሳቢያ መሆኑን ሲያውቁ የክርስትና ልጃችን ነው በሚል ምክንያት ብቻ ፤ በትህትና ላይ ሊፈርዱባት
አልደፈሩም....
"ሁሉንም ስራው ያውጣው በማለት መጨረሻውን ለማየት እየተጠባበቁ ናቸው፡፡ ትህትና ጤናዋ በከፍተኛ ፍጥነት እየተሻሻለ የመጣ ቢሆንም፤ ጐን ለጐን በነፍስ ማጥፋት ሙከራ ወንጀል በአቃቤ ህግ ክስ ተመሰረተባት፡፡ አዜብና ብሩክ ይህንን እንዳወቁ ቀጣዩ ትኩረታቸው
በምን ላይ መሆን እንዳለበት በስፋት ተመካከሩ፡፡ ከዚያም አንዳንድ
በመከላከያነት ይጠቅማሉ ያሏቸውን ማስረጃዎች ለማሰባሰብ ፤ ሁለቱም
በየፊናቸው ሩጫ ጀመሩ፡፡ ለዚህ ጉዳይ አበራ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገመቱ :: ምክንያቱም አበራ በእንደሻው ክህደት የደረሰበትና፤ በትህትና ላይ ስለተፈፀመው ወንጀል በሚገባ የሚያውቅ የአይን ምስክር ስለነበረ ነው፡፡ አበራ በእንደሻው ስለተፈፀመበት ክህደት ለአገሩ ሁሉ ሲያወራ ለአዜብም አጫውቷት ነበር ፡፡
ከዝምድና ይልቅ ገንዘብን አስበልጦ አስር
አመት ሙሉ ያጠራቀምኩትን ገንዘቤን ወስዶ ከከበረበት በኋላ ከዳኝ፡፡ በጋራ
እናድግበታለን ብሎ የገባውን ቃሉን አፍርሶ አባረረኝ " በማለት በምሬት ነበር የገለፀላት፡፡ ታዲያ ያ ሁሉ በደል የተፈፀመበት ሰው ፍርድ ቤት ቀርቦ እውነቱንና የሚያውቀውን ከመናገር ወደኋላ ሊል ይችላል? ስትል ራሷን ጠየቀች፡፡ በፍፁም ወደኋላ አይልም ስትል ተማመነች፡፡ምክንያቱም እሱ እንደዚያ በንዴት እየተንቀጠቀጠ
ሲነግራት...
“አይዞህ አበራ ተወው፡፡ አንተ ጤና ሁን እንጂ ፤ገንዘብ አላፊ ጠፊ ነው፡፡ በክህደት የተገኘ ገንዘብ ደግሞ የትም አያደርስም፡፡
ከሰራህ ከካደህ ሰው በላይ መሆን ትችላለህ :: አይዞህ! እግዚአብሄር ላንተ ያለውን ምንግዜም አታጣውም " በማለት ትልቅ የማፅነኛ ቃል ለግሳው ነበር፡፡ ያንን
የሰጠችውን የተስፋ ቃል እንኳ አስታውሶ እሺ ይላት ይሆን? ወይንስ እሱም እንደወላጆቹ ተደርቦ ከእውነት ጀርባ ይቆም ይሆን? ልቧ ተጠራጠረ፡፡ ለማንኛውም አለችና ስልክ ደወለችለት :: ስልኩን አነሳና እሷ መሆንዋን ሲያውቅ የሞቀ ሰላምታ አቀረበላት፡፡ ትንሽ እፎይ አለች በልቧ፡፡ለጉዳይ እንደምትፈልገው
ስትገልፅለት፤ በደስታ ተቀብሎ የሚገናኙበትን ቦታ ተቀጣጥረው
ተሰነባበቱ፡፡ በማግስቱ በቀጠሮው ቦታ ቀድሞ የደረሰው እሱ ነበር።
የተፈለገበትን ጉዳይ ስትነግረው...
"ተይ እንጂ አዜብ እቤት ድረስ የወሰድኳት እኮ እኔ ነኝ፡፡በወንጀለኛነት አያስጠይቅህም ነው የምትይኝ?" ሲል በጥርጣሬ ጠየቃት።
"ስለሱ ከሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል፡፡ አንተን በወንጀል
ተባባሪነት እንዳያስጠይቅህ በቂ ምክንያት ማቅረብ ይቻላል፡፡”
"ለምሳሌ ምን?"
"አበራ ሙት ምንም አትፍራ! በዚህ ጉዳይ አንተ በጥፋተኛነት እንድትጠየቅ የሚፈልግ ሰው የለም፡፡ አንድ ማወቅ ያለብህ ነገር ፧ አንተ ይዘሃት የሄድከው ወደ ቀጣሪዋ ቤት እንጂ፤ ወንጀል
ወደሚፈጸምበት ጫካ ውስጥ አይደለም፡ቀጣሪዋ ቤት አደረስካት ማለት፤ እንደሻው ደብድቦና፤ አስገድዶ፧ ክብረ ንፅህናዋን እንዲደፍራት አደረክ ማለት አይደለም :: የቀጣሪዋን ቤት የወንጀል መፈፀሚያ ዋሻ ያደረገው ወንጀለኛ ብቻ ነው ለዚህ ተጠያቂ የሚሆነው፡፡ አይዞህ ምንም የሚያስፈራ ነገር የለውም፡ አበራን ለማሳመን ብሎ ብሩክ ያስጠናትን ደሰኮረችለት፡፡ አበራ ልቡ ትንሽ ተለሳለሰ፡፡
"በሌላ በኩል ብታየው ደግሞ የቀጣሪዋ ባለቤት ልጅ የቅጥር ውል እንድትፈርም ይዘሃት ና ብሎ አዘዘህ :: አንተም ይህን ነገርካት። እሷም እሺ ብላ ሳታስገድዳት በፈቃደኝነት አብራህ ሄደች። ከዚያም አንተ በሌለህበት እንደሻው ወንጀል ፈፅሞባት ደረስክ፡፡ በቃ፡፡ ይህ አይደለም
ታሪኩ? አንተን የሚያስጠይቅህ ምኑ ነው ታዲያ?" ስትል የማደፋፈሪያ
ሀሳብ አዥጐደጐደችለት፡፡
በልቡ ያሳደረው ጥርጣሬ ሙሉ ለሙሉ ባይጠፋለትም፤ በአዜብ አቀራረብ ተስማማ፡፡ እንዳለችውም እሱን በቀጥታ ተጠያቂ ሊያደርገው የሚችል ጭብጥ እንደሌለ ተሰማው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ
ያቺ ምስኪን እንጀራ ፈላጊ ልጅ ፤ በደም ተጨማልቃ ወድቃ ያያት እለት የተሰማው ስሜት ፊቱ ላይ ድቅን አለበት፡፡ በተፈፀመባት ወንጀል ከልቡ አዝኖ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ያ ግፈኛ ከሃዲ ከሱቁ ካባረረው በኋላ አሁን አሁን በርካታ ካፒታል በማንቀሳቀስ በቅናት እያቃጠለው
ነው፡፡ በጥይት መቃጠሉን የሰማ እለት " እሰይ የእጁን ነው ያገኘው"ነበር ያለው፡፡ አሁን ደግሞ እሱ ተጠያቂ በማይሆንበት ሁኔታ ለምን ያየውን ከመመስከር ወደ ኋላ ማለት እንደሌለበት ተገነዘበ ፡፡ያየኽውን እውነት መሰከርክ ብሎ የሚፈርድበት ዘመድ እንደማይኖርና፤ ቢኖርም መፅሀፍ ቅዱስ ይዞ በሚፈፅመው መሃላ በውሸት መስክሮ ነፍሱን ማስኮነን እንደሌለበት ተሰማው። እንደሻውን ሊበቀል
የሚችልበትን ይህንን መልካም አጋጣሚ ሊጠቀምበት ወሰነ : እንቢ ቢልስ የት ሊደርስ ? በተለይ አዜብ እየነገረችው
ያለው ፣ ባለስልጣን ፖሊስ ከአዜብ በስተጀርባ መኖሩን ነው፡፡ በተለይ "ሻምበል ጋር በደንብ ተነጋግረንበታል"
ስትለው ምን እያለች እንደሆነ
ገብቶታል፡፡አልመሰክርም ቢል በተባባሪ ወንጀለኛነት ተፈርጆ፣ ለፍርድ እንደሚቀርብ እየነገረችው ነው፡፡ ይሄንን ጭምር አስቦ፤ ልቡ ስለፈራ፤ ያየውን ሁሉ በዝርዝር ሊያስረዳና፤ ለትህትና ድንበሩ የመከላከያ ምስክር ሊሆን ቃል ገባላት፡፡ ቃል መግባት ብቻም ሳይሆን ተጨማሪ ማስረጃ ጠቆማት..
"እኔ ብቻ ሳልሆን በዚያን እለት ሁኔታውን የተመለከተችው የቤት ሰራተኛዋ ወርቅ ያንጥፉም ያየችውን ሁሉ እውነቱን ሳትደብቅ እንድትመሰክር እናደርጋለን :: ደግሞም ትመሰክራለች፡፡ አትጠራጠሪ!
በትህትና ሁኔታ በጣም ነው ያዘነችው፡፡እሷም ስመ እግዚአብሄርን ጠርታ
ያየችውን ሁሉ ትመሰክራለች፡፡ አይዞሽ ! " አላት፡፡ አዜብ ከጠበቀችው በላይ ተባባሪ ሆኖ ስለኣገኘችው፤ በደስታ እቅፍ አደረገችው፡፡ በዚሁ መሰረት አበራና ወርቅ ያንጥፉ ፖሊስ ጣቢያ ቀርበው፤ የምስክርነት ቃላቸውን እንዲሰጡ ተደረገ፡፡ ቀኑን፡ ሰአቱን፡ የድርጊቱን አፈፃፀም፡ ዝርዝር ሁኔታውን፤ በሙሉ በአንድ አይነትና ፤ ተመሳሳይ በሆነ ቃል
መሰከሩ። ያም ብቻ ሳይሆን አንዱአለምን ጋርጠው በሚል ቅፅል ስሙ በሚታወቀው ወሮበላ እንዳይሞት፤ እንዳይድን፤ አደርጐ ያስደበደበው
መሆኑን፤ ራሱ እንደሻው በኩራት ሲናገር መስማቱን፧ ጭምር ገለፀ፡፡
በእርግጥም እንደሻው ያንን ለአበራ የተናገረው፤ ይሄ ይመጣብኛል ብሎ ሳይሆን፤ አንተም አርፈህ የማትቀመጥና ወሬ አበዛለሁ የምትል ከሆነ፤ አስወቅጥሀለሁ፤ የሚል ማስጠንቀቂያ ለመስጠት ነበር፡፡ ሆኖም በዚህ አጋጣሚ እንደሻውን የደበደበው ጉልበተኛ
ስለታወቀ፤ ወዲያውኑ ታድኖ እንዲያዝ ሲደረግ ፤ አበራ ማንነቱን በማሳየትና የሚገኝበትን
👍2❤1
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
..... የረር ጎታ ሲቃረቡ ነበር ሲቲና ከእንቅልፏ የተነሳችው፡፡
“ለምን አትተኛም ነበር? ቀንኮ ይደክምሃል» አለችው:: እንቅልፍ
ያሳቀጣቸውን ጉንጮቿን እያሻሸች::
“ተመችቶሽ ተኛሽ? ” አላት ፈገግ ብሎ፡፡
“አመሰግናለህ፡፡ የሚመች ትከሻ አላህ፡፡” አለች እየሳቀች፡፡ ጎንበስ ብላ ከሻንጣዋ ውስጥ ሎሚ አወጣችና አንድ ለእሱ አንድ ለራሷ ወሰደች::
“ሎማ ያነቃቃል፤ ታውቃለሁ? " አለች የያዘችውን ሎሚ እየመጠጠች፡፡
ድሬዳዋ ለገሃሬ ደርሰው ከባቡሩ ሲወርዱ ናትናኤል ተደነጋገረው:: የባቡር ጣቢያው በሰው ተጨናንቋል፡፡ አንድ እርምጃ ለመራመድ ሁለት ሦስት ሰዎች መገፍተር አለባቸው:: ሰው የት ወደየት እንደሚሄድ መለየት ያስቸግራል፡፡ ብቻ ባለበት ይተራመሳል፧ ይገፋፋል ፧ ይታሻሽል። ከኋላው ተቀምጣ የነበረችው ሴት አብሯት ከተቀመጠው ተሳፋሪ ጋር እያወራች ስትወርድ ዞሮ ተመሰክታት:: አብሯትት ካለው ሰው ጋር ታውራ እንጂ
አይኖቿ ከእርሱ ጋር ነበሩ፡፡ እርግጠኛ ነው... ከዚህ ቀደም አያቷታል፡፡
“የት ነው የምታርፈው አለችው
ሲቲና ቀደማ ከባበሩ እየወረደች::
“እ… አልወሰንኩም።” አላት ከጀርባው ተቀምጣ የነበረችውን ሴት ማንነት ለማስታወስ እየጣረ:: እርግጠኛ ነው.. መልኳን ያውቀዋል ግን ራቀበት፡፡
“ማለቴ ዘመድ ጋ ነው... ወይስ ሆቴል?” አለችው ሲቲና::ድንገት ብልጭ ሲልለት ድጋሚ ፊቱን ወደ ሴትየዋ አዙሮ ተመለከታት፡፡ የአብርሃም ሠራተኛ! ዞሮ ተመስከታት:: ሳያውቀው ዓይን ለዓይን ተጋጩ፡፡ ቀድማው ፊቷን መለሰች:: ሴትየዋ ቀድሞ ካላያቸው ሁለት ሰዎች ጋር ስታወራ ተመለከተ፡፡
“እ..ምን አልሺኝ? አይ…. ሆቴል ነው የማርፈው ለጊዜው፡፡” አለ ፊቱን ወደ ስቲና መልሶ፡፡
“ከፈለግህ እኔጋ ማረፍ ትችላለህ፡ባዶ ቤት ነው ያለሁት፡፡”
“እ... አለ አሁንም ፊቱን መልሶ የአብርሃምን ሠራተኛ ባየበት አቅጣጫ ተመለከተ፡፡ ዓይኑን የምትሸሽ መሰለው፡፡ አብረዋት የነበሩት ሦስት ሰዎች በአጠገቧ የሉም፡፡ ሴትየዋ ብቻዋን ጥግ ይዛ ቆማለች፡፡
«ማለቴ ለሁለት ለሦስት ቀን ችግር የለም ማለቴ ነው፡» ከጎኑ ከጎኑ እየሄደች አንገቷን አቀርቅራ ተናገረችው ሲቲና፡፡
ከሰው ግፊያ ወጣ ብለው ወደዳር ላይ የያዟቸውን ሻንጣዎች ከመሬት ላይ አሳርፎ ቀና ሲል ባሻገር ተመለከታት፡፡ ሴትየዋ አሁንም ታየዋለች:: ምናልባት የት እንያምታውቀኝ ጠፍቷት ይሆናል።" ብሎ አሰበ፡፡
“አስቸግርሽ እንደሆነ…” አለ ፊቱን ወደ ሲቲና መልሶ፡፡
“በፍጹም፡፡” አለች ፊቷ በሃፍረት እየቀላ፡፡
“እ... ” ናትናኤል አመነታ፡፡ ሆቴል አለመያዙ ከዓይን የሚያድነው ብቻ ሳይሆን ገንዘብም የሚቆጥብለት ነው፡፡ ግን ይቺን ልጅ ተከትሎ ከቤቷ ሄዶ ምን እንደሚከተል ለማወቅ አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ መቼም ምሳና እራት ሊያባላት ወይ ለነፍሷ ብላ እንዳላስጠጋችው ግልጽ ነው፡፡ ግን ቢሆንስ እንዴት ድንገት ልታቀርበው ፈለገች? “ምን መሰለሽ…” አለ ግብዣዋን
እምቢ የሚልበት ዘዴ ጠፍቶት ኣቧራ ያበላሸውን ነጭ ጀለቢያውን
እያራገፈ፡፡
“አስቸግራታለሁ ብለህ አስበህ ከሆነ ምንም ችግር የለም፡፡ ባዶ ቤት ነው ከፍቼ የምገባው:: ወላሂ አልኩህ፡፡”
“እስቲ እየሄድን እናውራ፡፡” አለ ናትናኤል - የሰው ትፍግፍግ ማለትና የአየሩ ሙቀት ትንፋሽ ቢያሳጥረው።
ጎንበስ ብሎ ሻንጣውን ሲያነሳ ከጎኑ ቆማ የነበረችው ሲቲና ገፍትራ ከመሬት ደባለቀችው፡፡ መሬት ላይ ሁለቴ ተንኮበሉ ቀና ሲል ነበር ነገሩ ጭንቅላቱን የመታው ከጀርባወ ቆመው የነበሩ አንድ አዛውንት በደም የተጨማለቀ ሆዳቸውን ይዘው ወደ ሠሬት ሲያዘቅጡ አያኖቹን አፍጥጦ
ተመለከታቸው!” እሪ አለች ከጎናቸው የነበረች ወጣት ሴት፡፡ ከወደቀበት
ለመነሳት ሲጣደፍ ሲቲና ሸብረክ ብላ ከተከናነበችው ድሪያ ስር ሽጉጥ
መዥረጥ ስታደርግ አያት:: ተቀደመች:: የያዘችው ሽጉጥ እጇ ወስጥ ተፈናጥሮ ሲወረወር እሷ ደረቷን አፍና ወደ ኋላዋ ወደቀች.. ዙሪያውን ረብሻ ሆነ... ጩኸት... ሩጫ.. ኡኡታ... ቶክስ እሪታ ዙሪያወን አደባለቀው..ናትናኤል ከአንገቷ ቀና አደረጋት...
«ሩ...ጥ! ተክትለውሃል... ሩጥ!» አለችው በግራ እጇ በደም የተዘፈቀውን ደረቷን አፍና እንደያዘች ሲር ሲር ከሚለው ትንፋሿ እየቆነጠበች ‹‹ ሩጥ!»
ቀና ሲል አየው:: የጨበጠውን ሽጉጥ ከትከሻው በላይ ይዞ ከፊቱ የሚጋረጡትን ሰዎች አንዴ ወዲህ አንዴ ወዲያ እየገፋ እየገፈታተረ ወደ እሱ እየቀረበ ሲመጣ በሚተራመሰው ሕዝብ መሃል በሩቁ አየሁ
ከአብርሃም ሠራተኛ ጋር የነበረውን አንድ ሰውዬ! እንደ ጥንቸል ተፈናጥሮ ከሚደነባበረው ከሚራበሸው ሕዝብ መሃል እየተሹለከለከ በትርምሱ ውስጥ
ሰመጠ... የአብርሃም ሠራተኛ! የፈጣሪ ያለህ! የአብርሃም ሠራተኛ! ከራሱ ጋር እያነበነበ ሮጠ፡፡ ከጀርባው የተኩስ እሩምታ አጀበው::
ወዴት እንደሚሮጥ.. የት እንደሚደርስ ግድ አልነበረውም:: ብቻ ሮጠ፡፡ እራቅ እንዳለ በሩቁ እንዳይለዩት ጭንቅላቱ ላይ የጠመጠመውን ሽርጡን አውልቆ በእጁ ያዘው:: ትንሽ ከራቀ በኋላ ደግሞ ወደ ጥግ ዞር አለና ጀለቢያውን አውልቆ ወርውሮ ከወገቡ በታች ሽርጡን አጥልቆ ከላይ ነጭ ሸሚዙን እንዳደረገ ከራሱ ጋር እያጉተመተመ ሮጠ፡፡ የአብርሃም
ሠሪተኛ! እንዴት ሊከተሉት ቻሉ? ወደ ድሬዳዋ መምጣቱንስ እንደት አወቁ? ሲቲና ባትገፈትረው'ኮ ወደፊቱ ሲወድቅ ባይስቱት'ኮ.. ' በደም የተጨማለቀ ሆዳቸውን ይዘው ያዘቀጡት ሽማግሌ ታዩት:: የፈጣሪ ያለህ! ገለውት ነበር'ኮ የአብርሃም ሠራተኛ! ወያኔ አብርሃም! ለካ ሳያውቀው!
ሲቲና ማነች? ሩጥ…ተከትለውሃል ሩጥ የምስራችን የገደለቻት ሴት ምንድን ነበር ያለችው? ሩጥ!' ሲቲና ማነች? የፈጣሪ ያለህ! ሁሉ ነገር ተወሳሰበበት:: ማሰቡን አቁሞ ሩጫውን ቀጠለ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ያለበት ቦታ የት እንደሆነ ለመረዳት አልቻለም፡፡ በስተግራው መደዳ የተሰሩ ቤቶች ማስታወቂያዎቻቸውን በየቢሮዎቻቸው ላይ እንዳንጠለጠሉ ተደርድረዋል:: ፈቶግራፍ ቤት..የልብስ ሰፊ...ስዓት ማደሻ..በስተቀኙ ደግሞ በረንዳው ላይ የሳጠራ ወንበሮች የተደረደሩበት በሐረግ የተሸፈነ በረንዳ ያለው ቤት ይታያል ድሪዳዋ፡፡
ወደ ቡና ቤቱ፡ ተጠጋና አካባቢያን ለማጥናት ሞክረ፡፡ የፊተኛው ክፍል ሰፊ ቢሆንም ጨለምለም ያለ ነው፡፡ ፈጠን አለና ወደ ውስጥ ገባ፡፡በትናንሽ ጠረጴዛዎች ዙሪያ የተኮለኮሉ ትናንሽ የብረት ወንበሮች ፈንጠር ፈንጠር ብለው ክብ ክብ ሰርተዋል፡፡ በጋዝ የተወለወለው የሲሚንቶ ወለል ቢያብለጨልጭም ሽታው ይከብዳል:: ቁርስ የሚያቂርጉ የቡና ቤቱ ደንበኞች በየወንበሮቻቸው ተቀምጠሁ ያዘዙትን ይስተናግዳሉ፡፡
ባዶ ወረጴዛ ፈለገና ወንበር ስቦ ተቀመጠ፡፡
“ምን ልታዘዝም ! በስተቀኝ የተንዘላዘለ ፀጉሯን ጣቷ ላይ እየጠመጠመች እየፈታች ጠየቀችው::
ሻይ አላት ቶሎ ለመገላገል፡፡ ፊቷን መልሳ ሄደች፡፡ ናትናኤል ከራሱ ጋር ምክክር ቀጠለ።
ጊዜ የለውም:: መፍጠን አለበት:: አለበለዚያ ያገኙታል በማያውቀው ከተማ ውስጥ ተደብቆ መቆየት ዘበት ነው ግን እንዴት ተከተሉት? ከርብቃ ቤት አምልጦ ሲሮጥ ተከትለውት ነበር ማለት ነው?
መሆን አለበት፡፡ የአብርሃምስ የቤት ሰራተኛ እዚህ ምን አመጣት? ወይኔ!
አብርሃምን ትከታተለው ነበር ማለት ነው! አሁን ደግሞ
የቡና ቤቱ አስተናጋጅ ያዘዘውን ሻይ አምጥታ ፊቱ አስቀመጠችለት::
እባክሽ የእኔ እመቤት የስልክ ቁጥር ማውጫ ደብተር ይኖራችኋል? “ አላት
“ይቅርታ የለንም ለምን ማዞሪያ አይጠይቁም
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ሰባት
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
..... የረር ጎታ ሲቃረቡ ነበር ሲቲና ከእንቅልፏ የተነሳችው፡፡
“ለምን አትተኛም ነበር? ቀንኮ ይደክምሃል» አለችው:: እንቅልፍ
ያሳቀጣቸውን ጉንጮቿን እያሻሸች::
“ተመችቶሽ ተኛሽ? ” አላት ፈገግ ብሎ፡፡
“አመሰግናለህ፡፡ የሚመች ትከሻ አላህ፡፡” አለች እየሳቀች፡፡ ጎንበስ ብላ ከሻንጣዋ ውስጥ ሎሚ አወጣችና አንድ ለእሱ አንድ ለራሷ ወሰደች::
“ሎማ ያነቃቃል፤ ታውቃለሁ? " አለች የያዘችውን ሎሚ እየመጠጠች፡፡
ድሬዳዋ ለገሃሬ ደርሰው ከባቡሩ ሲወርዱ ናትናኤል ተደነጋገረው:: የባቡር ጣቢያው በሰው ተጨናንቋል፡፡ አንድ እርምጃ ለመራመድ ሁለት ሦስት ሰዎች መገፍተር አለባቸው:: ሰው የት ወደየት እንደሚሄድ መለየት ያስቸግራል፡፡ ብቻ ባለበት ይተራመሳል፧ ይገፋፋል ፧ ይታሻሽል። ከኋላው ተቀምጣ የነበረችው ሴት አብሯት ከተቀመጠው ተሳፋሪ ጋር እያወራች ስትወርድ ዞሮ ተመሰክታት:: አብሯትት ካለው ሰው ጋር ታውራ እንጂ
አይኖቿ ከእርሱ ጋር ነበሩ፡፡ እርግጠኛ ነው... ከዚህ ቀደም አያቷታል፡፡
“የት ነው የምታርፈው አለችው
ሲቲና ቀደማ ከባበሩ እየወረደች::
“እ… አልወሰንኩም።” አላት ከጀርባው ተቀምጣ የነበረችውን ሴት ማንነት ለማስታወስ እየጣረ:: እርግጠኛ ነው.. መልኳን ያውቀዋል ግን ራቀበት፡፡
“ማለቴ ዘመድ ጋ ነው... ወይስ ሆቴል?” አለችው ሲቲና::ድንገት ብልጭ ሲልለት ድጋሚ ፊቱን ወደ ሴትየዋ አዙሮ ተመለከታት፡፡ የአብርሃም ሠራተኛ! ዞሮ ተመስከታት:: ሳያውቀው ዓይን ለዓይን ተጋጩ፡፡ ቀድማው ፊቷን መለሰች:: ሴትየዋ ቀድሞ ካላያቸው ሁለት ሰዎች ጋር ስታወራ ተመለከተ፡፡
“እ..ምን አልሺኝ? አይ…. ሆቴል ነው የማርፈው ለጊዜው፡፡” አለ ፊቱን ወደ ስቲና መልሶ፡፡
“ከፈለግህ እኔጋ ማረፍ ትችላለህ፡ባዶ ቤት ነው ያለሁት፡፡”
“እ... አለ አሁንም ፊቱን መልሶ የአብርሃምን ሠራተኛ ባየበት አቅጣጫ ተመለከተ፡፡ ዓይኑን የምትሸሽ መሰለው፡፡ አብረዋት የነበሩት ሦስት ሰዎች በአጠገቧ የሉም፡፡ ሴትየዋ ብቻዋን ጥግ ይዛ ቆማለች፡፡
«ማለቴ ለሁለት ለሦስት ቀን ችግር የለም ማለቴ ነው፡» ከጎኑ ከጎኑ እየሄደች አንገቷን አቀርቅራ ተናገረችው ሲቲና፡፡
ከሰው ግፊያ ወጣ ብለው ወደዳር ላይ የያዟቸውን ሻንጣዎች ከመሬት ላይ አሳርፎ ቀና ሲል ባሻገር ተመለከታት፡፡ ሴትየዋ አሁንም ታየዋለች:: ምናልባት የት እንያምታውቀኝ ጠፍቷት ይሆናል።" ብሎ አሰበ፡፡
“አስቸግርሽ እንደሆነ…” አለ ፊቱን ወደ ሲቲና መልሶ፡፡
“በፍጹም፡፡” አለች ፊቷ በሃፍረት እየቀላ፡፡
“እ... ” ናትናኤል አመነታ፡፡ ሆቴል አለመያዙ ከዓይን የሚያድነው ብቻ ሳይሆን ገንዘብም የሚቆጥብለት ነው፡፡ ግን ይቺን ልጅ ተከትሎ ከቤቷ ሄዶ ምን እንደሚከተል ለማወቅ አስቸጋሪ ይሆናል፡፡ መቼም ምሳና እራት ሊያባላት ወይ ለነፍሷ ብላ እንዳላስጠጋችው ግልጽ ነው፡፡ ግን ቢሆንስ እንዴት ድንገት ልታቀርበው ፈለገች? “ምን መሰለሽ…” አለ ግብዣዋን
እምቢ የሚልበት ዘዴ ጠፍቶት ኣቧራ ያበላሸውን ነጭ ጀለቢያውን
እያራገፈ፡፡
“አስቸግራታለሁ ብለህ አስበህ ከሆነ ምንም ችግር የለም፡፡ ባዶ ቤት ነው ከፍቼ የምገባው:: ወላሂ አልኩህ፡፡”
“እስቲ እየሄድን እናውራ፡፡” አለ ናትናኤል - የሰው ትፍግፍግ ማለትና የአየሩ ሙቀት ትንፋሽ ቢያሳጥረው።
ጎንበስ ብሎ ሻንጣውን ሲያነሳ ከጎኑ ቆማ የነበረችው ሲቲና ገፍትራ ከመሬት ደባለቀችው፡፡ መሬት ላይ ሁለቴ ተንኮበሉ ቀና ሲል ነበር ነገሩ ጭንቅላቱን የመታው ከጀርባወ ቆመው የነበሩ አንድ አዛውንት በደም የተጨማለቀ ሆዳቸውን ይዘው ወደ ሠሬት ሲያዘቅጡ አያኖቹን አፍጥጦ
ተመለከታቸው!” እሪ አለች ከጎናቸው የነበረች ወጣት ሴት፡፡ ከወደቀበት
ለመነሳት ሲጣደፍ ሲቲና ሸብረክ ብላ ከተከናነበችው ድሪያ ስር ሽጉጥ
መዥረጥ ስታደርግ አያት:: ተቀደመች:: የያዘችው ሽጉጥ እጇ ወስጥ ተፈናጥሮ ሲወረወር እሷ ደረቷን አፍና ወደ ኋላዋ ወደቀች.. ዙሪያውን ረብሻ ሆነ... ጩኸት... ሩጫ.. ኡኡታ... ቶክስ እሪታ ዙሪያወን አደባለቀው..ናትናኤል ከአንገቷ ቀና አደረጋት...
«ሩ...ጥ! ተክትለውሃል... ሩጥ!» አለችው በግራ እጇ በደም የተዘፈቀውን ደረቷን አፍና እንደያዘች ሲር ሲር ከሚለው ትንፋሿ እየቆነጠበች ‹‹ ሩጥ!»
ቀና ሲል አየው:: የጨበጠውን ሽጉጥ ከትከሻው በላይ ይዞ ከፊቱ የሚጋረጡትን ሰዎች አንዴ ወዲህ አንዴ ወዲያ እየገፋ እየገፈታተረ ወደ እሱ እየቀረበ ሲመጣ በሚተራመሰው ሕዝብ መሃል በሩቁ አየሁ
ከአብርሃም ሠራተኛ ጋር የነበረውን አንድ ሰውዬ! እንደ ጥንቸል ተፈናጥሮ ከሚደነባበረው ከሚራበሸው ሕዝብ መሃል እየተሹለከለከ በትርምሱ ውስጥ
ሰመጠ... የአብርሃም ሠራተኛ! የፈጣሪ ያለህ! የአብርሃም ሠራተኛ! ከራሱ ጋር እያነበነበ ሮጠ፡፡ ከጀርባው የተኩስ እሩምታ አጀበው::
ወዴት እንደሚሮጥ.. የት እንደሚደርስ ግድ አልነበረውም:: ብቻ ሮጠ፡፡ እራቅ እንዳለ በሩቁ እንዳይለዩት ጭንቅላቱ ላይ የጠመጠመውን ሽርጡን አውልቆ በእጁ ያዘው:: ትንሽ ከራቀ በኋላ ደግሞ ወደ ጥግ ዞር አለና ጀለቢያውን አውልቆ ወርውሮ ከወገቡ በታች ሽርጡን አጥልቆ ከላይ ነጭ ሸሚዙን እንዳደረገ ከራሱ ጋር እያጉተመተመ ሮጠ፡፡ የአብርሃም
ሠሪተኛ! እንዴት ሊከተሉት ቻሉ? ወደ ድሬዳዋ መምጣቱንስ እንደት አወቁ? ሲቲና ባትገፈትረው'ኮ ወደፊቱ ሲወድቅ ባይስቱት'ኮ.. ' በደም የተጨማለቀ ሆዳቸውን ይዘው ያዘቀጡት ሽማግሌ ታዩት:: የፈጣሪ ያለህ! ገለውት ነበር'ኮ የአብርሃም ሠራተኛ! ወያኔ አብርሃም! ለካ ሳያውቀው!
ሲቲና ማነች? ሩጥ…ተከትለውሃል ሩጥ የምስራችን የገደለቻት ሴት ምንድን ነበር ያለችው? ሩጥ!' ሲቲና ማነች? የፈጣሪ ያለህ! ሁሉ ነገር ተወሳሰበበት:: ማሰቡን አቁሞ ሩጫውን ቀጠለ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ያለበት ቦታ የት እንደሆነ ለመረዳት አልቻለም፡፡ በስተግራው መደዳ የተሰሩ ቤቶች ማስታወቂያዎቻቸውን በየቢሮዎቻቸው ላይ እንዳንጠለጠሉ ተደርድረዋል:: ፈቶግራፍ ቤት..የልብስ ሰፊ...ስዓት ማደሻ..በስተቀኙ ደግሞ በረንዳው ላይ የሳጠራ ወንበሮች የተደረደሩበት በሐረግ የተሸፈነ በረንዳ ያለው ቤት ይታያል ድሪዳዋ፡፡
ወደ ቡና ቤቱ፡ ተጠጋና አካባቢያን ለማጥናት ሞክረ፡፡ የፊተኛው ክፍል ሰፊ ቢሆንም ጨለምለም ያለ ነው፡፡ ፈጠን አለና ወደ ውስጥ ገባ፡፡በትናንሽ ጠረጴዛዎች ዙሪያ የተኮለኮሉ ትናንሽ የብረት ወንበሮች ፈንጠር ፈንጠር ብለው ክብ ክብ ሰርተዋል፡፡ በጋዝ የተወለወለው የሲሚንቶ ወለል ቢያብለጨልጭም ሽታው ይከብዳል:: ቁርስ የሚያቂርጉ የቡና ቤቱ ደንበኞች በየወንበሮቻቸው ተቀምጠሁ ያዘዙትን ይስተናግዳሉ፡፡
ባዶ ወረጴዛ ፈለገና ወንበር ስቦ ተቀመጠ፡፡
“ምን ልታዘዝም ! በስተቀኝ የተንዘላዘለ ፀጉሯን ጣቷ ላይ እየጠመጠመች እየፈታች ጠየቀችው::
ሻይ አላት ቶሎ ለመገላገል፡፡ ፊቷን መልሳ ሄደች፡፡ ናትናኤል ከራሱ ጋር ምክክር ቀጠለ።
ጊዜ የለውም:: መፍጠን አለበት:: አለበለዚያ ያገኙታል በማያውቀው ከተማ ውስጥ ተደብቆ መቆየት ዘበት ነው ግን እንዴት ተከተሉት? ከርብቃ ቤት አምልጦ ሲሮጥ ተከትለውት ነበር ማለት ነው?
መሆን አለበት፡፡ የአብርሃምስ የቤት ሰራተኛ እዚህ ምን አመጣት? ወይኔ!
አብርሃምን ትከታተለው ነበር ማለት ነው! አሁን ደግሞ
የቡና ቤቱ አስተናጋጅ ያዘዘውን ሻይ አምጥታ ፊቱ አስቀመጠችለት::
እባክሽ የእኔ እመቤት የስልክ ቁጥር ማውጫ ደብተር ይኖራችኋል? “ አላት
“ይቅርታ የለንም ለምን ማዞሪያ አይጠይቁም
👍1