#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...የከተማው ዋና ዋና መንገዶች በዩኒቨርስቲው ተማሪዎች መወረር ጀምረዋል ። የአራት ኪሎና እካባቢዋ ቡና
ቤት አሳላፊዎች፥ ለተማሪ ሻይ ቡና በማቅረብ ተዋክበዋል ። የተማሪዉ አንሶላዎች'ልብሶች በየሥርቻው ተወርውረው የከረሙ የእግር ሹራቦች ከውሃ በመታረቅ ላይ ናቸው ሕሜት ፥ ውረፋ ፡ ዘለፋና ቀልድ ጊዚአቸውን
ጠብቀው ተመልሰዋል በሴሚስተሩ ውስጥ በዩኒቨርስቲው የተደረገች አንዳች ነገር ሳትቀር እየተነሳች መብጠልጠያዋ ጊዜ ነው።
ይህ ሁሉ ፈተና ማለቁን የሚያበሥር ነው የፈተና ውጤት ቀርቦ ማዕበሉ ማንን ጠርጎ ማንን እንደ ተወ እስኪታወቅ ድረስ ለሁለት ሳምንቱ የዕረፍት ቀናት አብዛኛው ተማሪ ከዚህ ክልል አይወጣም ።
እቤልና እስክንድርም የመጨረሻውን ፈተና እንደ ተፈተኑ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል ። የተዝረከረኩ ዕቃዎች
ለማስተካከል እንኳ፥ ወደ መኝታ ክፍላቸው አልተመለሱም።ተያይዘው በቀጥታ ወደ እስክንድር እናት ቤት ተክለ ሃይማኖት አካባቢ ሔዱ። አቤል ለአውደ አመትና አልፎ አልፎም ለዕረፍት እነ እስክንድር ቤት መሔድ የጀመረው ገና የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ሳለ ከእስክንድር ጋር እንደተዋወቁ ነው።አንዳንዴ አብረው ይሔዱና የተገኘውን ቀማምሰው ተጫውተው ይመለሳሉ ። ዘንድሮ ግን አቤል ቤታቸው ሳይሔድ ቆይቷል ።
የጠፋው ሰው እንደ ምን አላችሁ ልጆቼ ?
እሁና እናትየዋ ፥ ሁለቱን አቅፈው ሳሙዋቸው ።
“ አቤል ፣ ምነው እንዲህ ጠፋህ ልጄ ?”
ምን እባክዎን ፥ ጥናት በዝቶ ነው
“ ቢሆንስ ታዲያ ፥ አንዳንዴ መቼስ እናት ቤት ብቁ ተብሎ የተገኘውን ቀማምሶ ይኬዳል ። አሀን ፈተና ጨረሳችሁ አይደለም ? ”
“ አዎ መቼስ"
“ እንግዲህ አንድ ፈተና ነዋ የቀራችሁ ? የፊታችን ሰኔ መመረቂያችሁ አይደለም ?
አቤል ዝም አለ ። እስክንድር ስሜቱ ስለ ገባው ቶሎ ብሎ ጣልቃ ገባ ።
“ አዎ ! አይዞሽ ደርሰናል ” አላቸው « እጁ ላይ ሲጋራ መኖሩን ያዩት ይሄኔ ነበር ።
« ይኼንን ሲጋራህን ምናለ ብትተወው እስክንድር ? አቤል ጓደኛህን አትመክረውም ? ! ”
ብዙ ዓመት የተናገሩት ነገር ነው ። ሆኖም ዐይናቸው ባየ ቁጥር ዝም ማለት አይችልም ። አቤል ከመቅለስለስ ልላ
ምንም አልመለሰም።
“አይዞሽ ፡ በቅርቡ አቆማለሁ” አላቸው እስክንድር ራሱ ። እሳቸው ሣቁ ሁሌም
የሚላቸው ነገር ስለሆነ።
ማዘር ሙች አቆማለሁ ። አራት ወር ያህል
ብቻ ታገሽኝ ብቻ አላቸው።
ከልቡ ለማቆም ቆርጦ ነበር እናትየው ግን ጊዜው ደርሶ እስካሳዩ ድረስ ሊያምኑት አይችሉም ።
“ምግብ አቀረቡላቸው ከበላሉ በኋላ ሲጫወቱ ቆይተው ሲመሻሽ እስክንድርና አቤል ሊሔዱ ሲሉ፡-
ዛሬ ለምን ከዚሁ ስትጫወቱ አታድሩም ” እሉ እናትየዋ ።
“ አአይ እንሔዳለን ። እዚያው ካምፓችን ይሻለናል አለ እስክንድር እሳቸው በሚናገሩት አይነት ፣
እስክንድር በዕረፍቱ ሰሞን አቤልን ጥሎ ቤት መክረም አልፈለገም። አብረው እንዳይሆኑ ደግሞ ቤቱ አይበቃም።
ሁለት መኝታ ብቻ ነው ያለው “ አንዱ የናትየዋ ነው " በአንዱ መኝታ ላይ ከታናሽ ወንድሙ ጋር ሦስት ሆነው ተጨናንቀው መክረሙን ኣልፈለገም ። በዚያ ላይ እናትየዋ ለእነሱ የሚያቀርቡትን ምግብ ጣፈጠ አልጣፈጠልኝ ብለው ሲጨነቁ እንዲከርሙ አይፈልግም " ከአሁን በፊትም ቢሆን ትልቁ የክረምት ዕረፍት ላይ ካልሆነ የገናወን ዕረፍት ቤቱ አሳልፎ አያውቅም ። እዚያው ዩኒቨርስቲ
ውስጥ የሚከርመው ። እናትየውም ይህንኑ ስለሚያውቁ ብዙም አላግደረደሩት "
ተሰናብተዋቸው ከውጭው በር እንደ ደረሱ። እናትየው እስክንድርን ወደ ኋላ አስቀሩትና አንድ ነገር እጁ ውስጥ
ሽጉጥ አደረጉለት።
“ ምንድነው እሱ ? ” አላቸው ፡ ምን እንደሆን ልቡ እያወቀ።
“ ያዘው ለዚያ ለምናምንቴ ለሱስህ ይሆንሃል አሉት ። የዐሥር ብር ኖት ነበር ።
እኔ ከሌላ ቦታ አላጣም እባክሽ ። ይሄ ለራስሽ ይሁንሽ ” አላቸው ።ለመግደርደር ያህል ሳይሆን ከልቡ ነበር ።
ምን ጊዜም ከእናቱ ገንዘብ ሲወስድ ልቡ ያዝናል ። እንደ ሲጋራ ሱሰኝነቱ አይቅበዘበዝም ።
ያዘው ግድ የለህም” ። እኔ አለኝ ። አንድ አረርባ ብር የመንደር ዕቁብ ነበረችኝ ፤እሷ ወጥታልኝ ነው ” አሉት ።
አመስግኖ ብሯን ኪሱ ከተተ ወዲያው ማርታ በሀሳቡ መጣችበት ግን በዐሥር ብር ምን ሊኮን ?
“ አቤል ፡ በል እንግዲህ ብቅ እያላችሁ ጠይቁኝ ። አሁን ዕረፍት ናችሁ ” አሉት እናትየዋ « አቤልን ቅር እንዳይለው
ከእናቱ ተለይተው ከሔዱ በኋላ እስክንድር ስለ ድህነትና የእናት አንጀት ተቃራኒ ሁኔታ እያብሰለሰለ ነበር
ድህነት እጅዋን ሊያስራት ይሞክራል ፤ እናት እጅን ለልጅዋ ለመዘርጋት ትፍጨረጨራለች ፡፡ ምኞቷና አድራጎቷ እኩል አይሆንም “ በፍቅር ወደ ልጅዋ ስትንጠራራ
ድህንት ጨምድዶ ይይዛታል ግን ያም ሆኖ እትረታም አትሽንፍም እንደ ምንም ተፍጨርጭራ የልጅዋን እጅ
ትነካለች።
“ አሁን ወዴት ነን ?” አለ አቤል " ትንሽ እንደተጓዙ
“ አንድ ቤት ጎራ ብለን ደርቆ የከረመ ጉሮሮአችንን እናርጥብ እንጂ ! ” አለ እስክንድር ።
አቤል ገንዘብ መቆጠብ የማይችለው የእስክንድር እጅ አስግርምት ሳቀ ። ከእናቱ የተቀበላትን ገንዘብ ለማጥፋት
እንደ ቸኮለ ገባው።
“ ይልቅ ቦታ ምረጥ የት ይሻለናል ? ” አለው እስክንድር
“ ወደ ሠፈራችን አቅራቢያ አይሻልም ? ” አለ አቤል ።መቼም ከዩኒቨርስቲው አካባቢ ርቆ መቆየት አይሆንለትምና።
“ ስድስት ኪሎ ደኅና ቡና ቤት የለማ ! ከጠጣን አይቅር ትንሽ ትርምስ ብጤ ያለበት ይሻለናል ። የጠርሙስ ካካታ ! ”
" አራት ኪሎ እንሒዳ! በዚያው ወደ ካምፓስ ለመግባት ይቀርበናል ”
በዚሁ ተስማምተው ወዶ አራት ኪሎ እመሩ ።
እዚያ ሲደርሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ገደማ ሆኖ ነበር እስክንድር ቻቻታ ያለበትን ቦታ መምረጥ ስለፈለገ ከቡና ቤት ቡና ቤት ሲዘዋወሩ በብዛት የሚያገጥማቸው የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበር ። ተማሪው ታስሮ እንደተፋታ ሆኖአል ንኮኒ ትተደግፎ የሚጠጣው የሴት አሳላፊዎችን ዳሌ የሚዳብሰው በቡድን ተቀምጦ እየጠባ የሚንቻቻው ተሜ ነው። ከወላጅ ከዘመድ የተላከ ከወዲያ ወዲህ ተጠራቅሞ ተቀብሮ የቆየ ገንዘብ መውጫው ዕለት ነዉ። በፈተና ማግሥት ሰክሮ መጥቶ ግቢው ውስጥ መደንፋት ፡ የማይጠጡ ተማሪዎችን መረበሽ ። ወይም ሰክሮ በየበረንዳው አድሮ
ጠዋት “ ጀብድ ” አርጎ ማውራት በዩኒቨርስቲ ውስጥ እየተለመደ የመጣ ይመስላል በተለይ ይህ ሁኔታ አይሎ
የሚታየው ከገጠር በወጡ ተማሪዎች ላይ ነው ። የአዲስ አበባው ተማሪ የቡና ቤቱን ትርምስ ከማዘውተር “ የኖርንበት ነው ” በማለት ዐይነት ቆጠብ ይላል ። ገንዘቡንም ቢሆን ከገጠረ እንደ መጡት አጠራቅሞ ማቆየት አይችልም ። አንዳንዱ እንደ ቱሪስት አስጐብኝ ገጠሬዎቹን ይዞ የከተማውን
ምርጥ ቡና ቤቶች በማስተዋወቅ የጋራ “ ጀብድ ” ይፈጽማል
እስክንድር አንድ ሞቅ ያለ ቡና ቤት አግኝተዉ ገቡ አንድ አንድ ቢራ ይዘው ቁጭ ከማለታቸው ፡ ሳምሶን ጉልቤው ዝንጥ ብሎ መጣ ሁሉም አራት ኪሎ መጠጣት የመረጡት ማታ ወደ መኝታ ቤታቸው ለመግባት እንዲቀርባቸው ይመስላል ።
ሳምሶን እስክንድርና አቤልን ሲያገኛቸው ደስ አለው ።በተለይ አቤልን መጋበዝ፤ ይፈልግ ነበር ።ጠዋት የለበሰውን
ቀያይሮ አፍላ ጉልበቱን ወጣጥሮ በሚያሳይ መሉ ጅንስ ሽክ ብሎአል ።
"ከመቼው ተሠየማችሁ ? አላቸው ፡ አጠግባቸው ለመቀመጥ መንበር እየሳበ
“ አንተም ደህና ጊዜ ደርሰሃል ፤ ቁጭ በል አለው እስክንድር።
ሳምሶንም ቢራ አዝዞ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
...የከተማው ዋና ዋና መንገዶች በዩኒቨርስቲው ተማሪዎች መወረር ጀምረዋል ። የአራት ኪሎና እካባቢዋ ቡና
ቤት አሳላፊዎች፥ ለተማሪ ሻይ ቡና በማቅረብ ተዋክበዋል ። የተማሪዉ አንሶላዎች'ልብሶች በየሥርቻው ተወርውረው የከረሙ የእግር ሹራቦች ከውሃ በመታረቅ ላይ ናቸው ሕሜት ፥ ውረፋ ፡ ዘለፋና ቀልድ ጊዚአቸውን
ጠብቀው ተመልሰዋል በሴሚስተሩ ውስጥ በዩኒቨርስቲው የተደረገች አንዳች ነገር ሳትቀር እየተነሳች መብጠልጠያዋ ጊዜ ነው።
ይህ ሁሉ ፈተና ማለቁን የሚያበሥር ነው የፈተና ውጤት ቀርቦ ማዕበሉ ማንን ጠርጎ ማንን እንደ ተወ እስኪታወቅ ድረስ ለሁለት ሳምንቱ የዕረፍት ቀናት አብዛኛው ተማሪ ከዚህ ክልል አይወጣም ።
እቤልና እስክንድርም የመጨረሻውን ፈተና እንደ ተፈተኑ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል ። የተዝረከረኩ ዕቃዎች
ለማስተካከል እንኳ፥ ወደ መኝታ ክፍላቸው አልተመለሱም።ተያይዘው በቀጥታ ወደ እስክንድር እናት ቤት ተክለ ሃይማኖት አካባቢ ሔዱ። አቤል ለአውደ አመትና አልፎ አልፎም ለዕረፍት እነ እስክንድር ቤት መሔድ የጀመረው ገና የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ሳለ ከእስክንድር ጋር እንደተዋወቁ ነው።አንዳንዴ አብረው ይሔዱና የተገኘውን ቀማምሰው ተጫውተው ይመለሳሉ ። ዘንድሮ ግን አቤል ቤታቸው ሳይሔድ ቆይቷል ።
የጠፋው ሰው እንደ ምን አላችሁ ልጆቼ ?
እሁና እናትየዋ ፥ ሁለቱን አቅፈው ሳሙዋቸው ።
“ አቤል ፣ ምነው እንዲህ ጠፋህ ልጄ ?”
ምን እባክዎን ፥ ጥናት በዝቶ ነው
“ ቢሆንስ ታዲያ ፥ አንዳንዴ መቼስ እናት ቤት ብቁ ተብሎ የተገኘውን ቀማምሶ ይኬዳል ። አሀን ፈተና ጨረሳችሁ አይደለም ? ”
“ አዎ መቼስ"
“ እንግዲህ አንድ ፈተና ነዋ የቀራችሁ ? የፊታችን ሰኔ መመረቂያችሁ አይደለም ?
አቤል ዝም አለ ። እስክንድር ስሜቱ ስለ ገባው ቶሎ ብሎ ጣልቃ ገባ ።
“ አዎ ! አይዞሽ ደርሰናል ” አላቸው « እጁ ላይ ሲጋራ መኖሩን ያዩት ይሄኔ ነበር ።
« ይኼንን ሲጋራህን ምናለ ብትተወው እስክንድር ? አቤል ጓደኛህን አትመክረውም ? ! ”
ብዙ ዓመት የተናገሩት ነገር ነው ። ሆኖም ዐይናቸው ባየ ቁጥር ዝም ማለት አይችልም ። አቤል ከመቅለስለስ ልላ
ምንም አልመለሰም።
“አይዞሽ ፡ በቅርቡ አቆማለሁ” አላቸው እስክንድር ራሱ ። እሳቸው ሣቁ ሁሌም
የሚላቸው ነገር ስለሆነ።
ማዘር ሙች አቆማለሁ ። አራት ወር ያህል
ብቻ ታገሽኝ ብቻ አላቸው።
ከልቡ ለማቆም ቆርጦ ነበር እናትየው ግን ጊዜው ደርሶ እስካሳዩ ድረስ ሊያምኑት አይችሉም ።
“ምግብ አቀረቡላቸው ከበላሉ በኋላ ሲጫወቱ ቆይተው ሲመሻሽ እስክንድርና አቤል ሊሔዱ ሲሉ፡-
ዛሬ ለምን ከዚሁ ስትጫወቱ አታድሩም ” እሉ እናትየዋ ።
“ አአይ እንሔዳለን ። እዚያው ካምፓችን ይሻለናል አለ እስክንድር እሳቸው በሚናገሩት አይነት ፣
እስክንድር በዕረፍቱ ሰሞን አቤልን ጥሎ ቤት መክረም አልፈለገም። አብረው እንዳይሆኑ ደግሞ ቤቱ አይበቃም።
ሁለት መኝታ ብቻ ነው ያለው “ አንዱ የናትየዋ ነው " በአንዱ መኝታ ላይ ከታናሽ ወንድሙ ጋር ሦስት ሆነው ተጨናንቀው መክረሙን ኣልፈለገም ። በዚያ ላይ እናትየዋ ለእነሱ የሚያቀርቡትን ምግብ ጣፈጠ አልጣፈጠልኝ ብለው ሲጨነቁ እንዲከርሙ አይፈልግም " ከአሁን በፊትም ቢሆን ትልቁ የክረምት ዕረፍት ላይ ካልሆነ የገናወን ዕረፍት ቤቱ አሳልፎ አያውቅም ። እዚያው ዩኒቨርስቲ
ውስጥ የሚከርመው ። እናትየውም ይህንኑ ስለሚያውቁ ብዙም አላግደረደሩት "
ተሰናብተዋቸው ከውጭው በር እንደ ደረሱ። እናትየው እስክንድርን ወደ ኋላ አስቀሩትና አንድ ነገር እጁ ውስጥ
ሽጉጥ አደረጉለት።
“ ምንድነው እሱ ? ” አላቸው ፡ ምን እንደሆን ልቡ እያወቀ።
“ ያዘው ለዚያ ለምናምንቴ ለሱስህ ይሆንሃል አሉት ። የዐሥር ብር ኖት ነበር ።
እኔ ከሌላ ቦታ አላጣም እባክሽ ። ይሄ ለራስሽ ይሁንሽ ” አላቸው ።ለመግደርደር ያህል ሳይሆን ከልቡ ነበር ።
ምን ጊዜም ከእናቱ ገንዘብ ሲወስድ ልቡ ያዝናል ። እንደ ሲጋራ ሱሰኝነቱ አይቅበዘበዝም ።
ያዘው ግድ የለህም” ። እኔ አለኝ ። አንድ አረርባ ብር የመንደር ዕቁብ ነበረችኝ ፤እሷ ወጥታልኝ ነው ” አሉት ።
አመስግኖ ብሯን ኪሱ ከተተ ወዲያው ማርታ በሀሳቡ መጣችበት ግን በዐሥር ብር ምን ሊኮን ?
“ አቤል ፡ በል እንግዲህ ብቅ እያላችሁ ጠይቁኝ ። አሁን ዕረፍት ናችሁ ” አሉት እናትየዋ « አቤልን ቅር እንዳይለው
ከእናቱ ተለይተው ከሔዱ በኋላ እስክንድር ስለ ድህነትና የእናት አንጀት ተቃራኒ ሁኔታ እያብሰለሰለ ነበር
ድህነት እጅዋን ሊያስራት ይሞክራል ፤ እናት እጅን ለልጅዋ ለመዘርጋት ትፍጨረጨራለች ፡፡ ምኞቷና አድራጎቷ እኩል አይሆንም “ በፍቅር ወደ ልጅዋ ስትንጠራራ
ድህንት ጨምድዶ ይይዛታል ግን ያም ሆኖ እትረታም አትሽንፍም እንደ ምንም ተፍጨርጭራ የልጅዋን እጅ
ትነካለች።
“ አሁን ወዴት ነን ?” አለ አቤል " ትንሽ እንደተጓዙ
“ አንድ ቤት ጎራ ብለን ደርቆ የከረመ ጉሮሮአችንን እናርጥብ እንጂ ! ” አለ እስክንድር ።
አቤል ገንዘብ መቆጠብ የማይችለው የእስክንድር እጅ አስግርምት ሳቀ ። ከእናቱ የተቀበላትን ገንዘብ ለማጥፋት
እንደ ቸኮለ ገባው።
“ ይልቅ ቦታ ምረጥ የት ይሻለናል ? ” አለው እስክንድር
“ ወደ ሠፈራችን አቅራቢያ አይሻልም ? ” አለ አቤል ።መቼም ከዩኒቨርስቲው አካባቢ ርቆ መቆየት አይሆንለትምና።
“ ስድስት ኪሎ ደኅና ቡና ቤት የለማ ! ከጠጣን አይቅር ትንሽ ትርምስ ብጤ ያለበት ይሻለናል ። የጠርሙስ ካካታ ! ”
" አራት ኪሎ እንሒዳ! በዚያው ወደ ካምፓስ ለመግባት ይቀርበናል ”
በዚሁ ተስማምተው ወዶ አራት ኪሎ እመሩ ።
እዚያ ሲደርሱ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል ገደማ ሆኖ ነበር እስክንድር ቻቻታ ያለበትን ቦታ መምረጥ ስለፈለገ ከቡና ቤት ቡና ቤት ሲዘዋወሩ በብዛት የሚያገጥማቸው የዩኒቨርስቲ ተማሪ ነበር ። ተማሪው ታስሮ እንደተፋታ ሆኖአል ንኮኒ ትተደግፎ የሚጠጣው የሴት አሳላፊዎችን ዳሌ የሚዳብሰው በቡድን ተቀምጦ እየጠባ የሚንቻቻው ተሜ ነው። ከወላጅ ከዘመድ የተላከ ከወዲያ ወዲህ ተጠራቅሞ ተቀብሮ የቆየ ገንዘብ መውጫው ዕለት ነዉ። በፈተና ማግሥት ሰክሮ መጥቶ ግቢው ውስጥ መደንፋት ፡ የማይጠጡ ተማሪዎችን መረበሽ ። ወይም ሰክሮ በየበረንዳው አድሮ
ጠዋት “ ጀብድ ” አርጎ ማውራት በዩኒቨርስቲ ውስጥ እየተለመደ የመጣ ይመስላል በተለይ ይህ ሁኔታ አይሎ
የሚታየው ከገጠር በወጡ ተማሪዎች ላይ ነው ። የአዲስ አበባው ተማሪ የቡና ቤቱን ትርምስ ከማዘውተር “ የኖርንበት ነው ” በማለት ዐይነት ቆጠብ ይላል ። ገንዘቡንም ቢሆን ከገጠረ እንደ መጡት አጠራቅሞ ማቆየት አይችልም ። አንዳንዱ እንደ ቱሪስት አስጐብኝ ገጠሬዎቹን ይዞ የከተማውን
ምርጥ ቡና ቤቶች በማስተዋወቅ የጋራ “ ጀብድ ” ይፈጽማል
እስክንድር አንድ ሞቅ ያለ ቡና ቤት አግኝተዉ ገቡ አንድ አንድ ቢራ ይዘው ቁጭ ከማለታቸው ፡ ሳምሶን ጉልቤው ዝንጥ ብሎ መጣ ሁሉም አራት ኪሎ መጠጣት የመረጡት ማታ ወደ መኝታ ቤታቸው ለመግባት እንዲቀርባቸው ይመስላል ።
ሳምሶን እስክንድርና አቤልን ሲያገኛቸው ደስ አለው ።በተለይ አቤልን መጋበዝ፤ ይፈልግ ነበር ።ጠዋት የለበሰውን
ቀያይሮ አፍላ ጉልበቱን ወጣጥሮ በሚያሳይ መሉ ጅንስ ሽክ ብሎአል ።
"ከመቼው ተሠየማችሁ ? አላቸው ፡ አጠግባቸው ለመቀመጥ መንበር እየሳበ
“ አንተም ደህና ጊዜ ደርሰሃል ፤ ቁጭ በል አለው እስክንድር።
ሳምሶንም ቢራ አዝዞ
👍1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
#ፖሊስ_ጣቢያ
የጣቢያው የምርመራ ሹም ሻምበል ብሩክ በላይ በእለታዊ የስራ ጉዳዩ ላይ ተጠምዶ፤ አንገቱን እንዳቀረቀረ ነበር፡፡ የቢሮው በር በቀስታ ተቆርቁሮ በዝግታ ሲከፈት፤ ልብ አላለም ፡፡እሱ በያዘው
አስደናቂ የወንጀል ሪፖርት ተመስጦ በሃሳብ ጭልጥ ብሎ ሄዶ ነበር፡፡ደመ ነፍሱ፤ በሩን ከፍቶ የገባው ከስራ ባልደረቦቹ አንዱ እንደሆነ ነበር
የነገረው፡፡በሩን ቆርቁሮ የገባው እንግዳ ግን ፤ እንደወትሮው ከስራ ባልደረቦቹ
አንዱ አልነበረም፡፡ ባለጉዳይ ነው፡፡ እሱ እንደዚያ አንገቱን አቀርቅሮ የቀረበለትን ፋይል ሲመረምር፤ ከፊት ለፊቱ እጆቹን አጣምሮ የቆመው እንግዳ ደግሞ፤ በድንጋጤ ተውጦ፤ የሱን ሁኔታ ይመረምር ነበር፡፡ዘንካታ ቁመናው ልቡን እንደመሰጠው ፤ መልኩ የሞዛርት ትዝታን
አመጣበት፡፡በተለይ ተጠቅልሎ ሄዶ ከግንባሩ ላይ ሲደርስ ክንብል ያለው
ዞማ ጸጉሩ ልዩ ውበትን አጎናጽፎት ተመለከተ፡፡ ሻምበል ብሩክ የደንብ
ልብሱ አብሮት እንደተፈጠረ ሁሉ እጅግ የሚያምርበት ግርማ ሞገስ ያለው ወጣት መኮንን ነው፡፡ ያ የገባ እንግዳ እሱ ራሱ በሌላ እንግዳ በሆነ የስሜት ሉጋም ተሸምቅቆ ልቡ በሃይል እየመታ፤ ትንፋሹ ቁርጥ፤ ቁርጥ፤እያለበት “እህህ እህህ ...."በማለት ጉሮሮውን ሳለና ድምጽ
አሰማ :: ሻምበል ብሩክ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀና ያለው በዚያ የእንግዳው ቀስቃሽ ድምጽ ምክንያት ነበር፡፡እንደዋዛ ቀና ያለው አንገቱ ዳግም ላለማጎንበስ ምሎ የተገዘተ ይመስል በዚያው ቀረ፡፡ባየው ነገር ተደናግጦና አይኖቹን ማመን ተስኖት እስከሚያስታውቅበት ድረስ ልቡ ዘለላች፡፡እዚህ ጋ ጎደለሽ የማትባል፤ አምላክ እጁን ታጥቦ የሰራት የምታስብል፧
የውበት እመቤት እጆችዋን ወደ ኋላ አጣምራ አንገትዋን አቀርቅራ ከፊት ለፊቱ ቆማ ተመለከተ፡፡ ሻምበል ብሩክ ልጅቷን አተኩሮ በማየት ፈዝዞና “ምን ልርዳሽ?" ብሎ መጠየቅ ግዴታው መሆኑን ዘንግቶት፤ የመጣችበትን ምክንያት ሳይጠይቅ፤ ለረጅም ደቂቃዎች በመዘግየቱ፤ እፍረት ቢጤ ቢሰማውም፤ እሷም ከዚያ በፊት በማንኛውም ወንድ ላይ ተሰምቷት በማያውቅ እንግዳ ስሜት ተሸብባ መቅረቷን ሲያውቅ ኖሮ፤
የእፍረት ስሜቱ ትንሽ በቀነስለት ነበር፡፡ እሱ ምን እንደዚያ እንዳፈዘዘው
ውስጡን ሲጠይቅ፤ ትህትናም “ለምን ደነገጥኩ ግን? የሚል ጥያቄ ለራሷ አቅርባ ነበር፡፡ልቧ የደነገጠበትን የመኮንኑ ተክለ ቁመናና ውበት ወደዚያ ተወት አድርጋ እራሷን ብትዋሽም ከዚያ የበለጠው ዋነኛ ምክንያቷ ግን፤ እንደዚያ ከነ ማእረግ ልብሱ አምሮና ተውቦ ስታየው፣ልቧ በደስታ የሚሞላበትን፤ እጅግ በጣም የምትወደውን፤ የአባቷን ትክለ ቁመና ስላስታወሳት መሆኑ ሳይታወቃት አልቀረም፡፡በትንሽነቷ ጊዜ አባቷ ያንን የምትወድለትን የማእረግ ልብሱን ለብሶ ስታየው፤ ትንሷ ልቧ
በደስታ እየዘለለች ፤እሷም እንደ አባቷ እንዲያምርባት፣ በዚያ በትንሽ ሰውነቷ ላይ ያንን ትልቅ ኮት ትደነቅር ፧ ሱሪው ውስጥ ትገባና እየተጎተተች ስትዘንጥ ፤ አባቷ በሳቅ ሲፈነዳ “አያምርብኝም አባዬ
"ስትለው፡፡
"እንዴታ ትህትናዬ በጣም እንጂ! አንቺም ስታድጊ እንደኔ ወታደር ትሆኝና ፤ ዩኒፎርምሽን ለብሰሽ፤ እንደዚህ ታጥቀሽ ፤ እንዴት እንደሚያምርብሽ ይታየኛል፡፡" ሲላት ቶሎ አድጋ፤ ያንን ዩኒፎርም
ለብሳ የምር የምትዘንጥበትን ጊዜ ስትናፍቅ፤ እያደገች ስትመጣ ደግሞ
ያንን ከጎኑ ሻጥ የሚያደርገውን ሽጉጥ ትቀበለውና፤ እሷም ጎኗ ላይ ሻጥ አድርጋ ስትንጎራደድ፤ ልዩ ደስታን ይሰጣት ነበር፡፡አባቷ ያንን ሽጉጥ ጥይቶቹን ከውስጡ ያወጣና ስለ አተኳኮሱ፧ ስለ አጠቃቀሙ ፤
እያሳያት፤ ባዶውን ሲሰጣት ታነጣጥርበትና ምላጩን ሳብ
ስታደርገው ፤ እሱም የውሸት ወደ ኋላ ሲወድቅላት፤ ከዚያም ትመጣና
ከሞተበት እንዲነሳ ስትኮረኩረው፡፡ከዚያም በሳቅ እየተፍለቀለቀ እቅፍ
አድርጎ ወደ ላይ አንስቶ ሲስማት፤ ይህ ሁሉ የነበረው ሁኔታ ..እሱ ታስቧት
ይሆን? ወይንስ ወንድሟን እንዲፈታላት መልአክ አድርጋ በሀሳቧ የሳለችው ሰው ነው ? እሷም አልገባትም ::
በህይወት እያለ ይሰማት የነበረው ስሜት አፈር ከለበሰ ይሄውና አመታት መቆጠር ጀምረዋል፡፡ አሁን ግን ለመጀመሪያ ጊዜ ያ ስሜት ፊት ለፊቷ በምታየው መኮንን ምክንያት በትዝታነቱ ተቀስቅሶባት
የገባችበትን ምክንያት እስከምትዘነጋው ድረስ አፈዘዛትና ቆማ ቀረች፡፡
ሻምበል ብሩክ የገባበት ሁኔታ ቀስ በቀስ አልፎለት፤ ስሜቱን መግዛት ሲጀምር።
ፊት ለፊቱ የቆመች ልጅ ምን እንደምትፈልግ መጠየቅ እንደሚገባው
ሲታሰበው፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ፊቱን ፈካ፤ ጥርሶቹን ብልጭ አደረጋቸው፡፡ እግዚኦ ! ጥርሶቹ እንዴት ነው የሚያምሩት? ስሜቷ እንደገና ተለዋወጠና ልቧ ትር ትር አለባት
አይኖቿ እንደዚያ ፍጥጥ ብለው ሲመለከቱት ሻምበልም ምን ልታዘዝ የኔ እመቤት?" የሱም ስሜት አብሯት እየተለዋወጠበት፡፡
"ወንድሜ ታስሮብኝ ነው የመጣሁት " ትንፋሽዋ እየተደነቃቀፈ፡፡
“እሺ ወንበሩ ላይ አረፍ በይና ንገሪኝ እስቲ በእጁ ወንበሩን እያመለከታት፡፡
ሻምበል ብሩክ ስሜቱ ለሁለት ተከፍሏል ፡አይኖቹ ከፊት ለፊቱ የሚታየውን ድንቅ ውበት በማድነቅ ስራቸውን ሲሰሩ ፤ ጆሮዎቹ ደግሞ የአቤቱታውን ምክንያት ለማዳመጥ ተከፍተዋል፡፡ ትህትናም አፏ
ስለአጋጠማት ችግር ሲያወራ፤ ልቧ ፊት ለፊቷ በተቀመጠው መኮንን ውብ ትክለ ቁመና ተማርኮ ከውስጥ እየሟሸሸባት ነበር፡፡
የእለት ሁኔታ መዝጋቢው ለእርስዎ እንዳመለክት ነግረውኝ ነው የመጣሁት”
“በምን ጉዳይ ነው የታሰረው? ማነው ስሙ? " አከታትሎ ጠየቃት፡፡
“አንዱአለም ድንበሩ ነው ስሙ"
"በዚያ በዲፕሎማት መኪና ላይ ስርቆሽ ከፈጸሙት ውስጥ ነው?"
“ኸረ እሱ ሌባ አይደለም" ፈርጠም ብላ፡፡
"ቆይኝ አንድ ጊዜ "አለና የቀረበለትን ሪፖርት ለማውጣት የጠረጴዛውን
መሳቢያ ከፈተ፡፡ በዚያ በስርቆት ወንጀል ላይ የተሳተፉት ሶስት ሰዎች ሲሆኑ የአንዱአለም ስም የለበትም፡፡
ልክ ነሽ፡፡ በዋናው ስርቆት ላይ አልነበረም
"ለምን ታሰረ ታዲያ?" በልቧ" ዋና ስርቆትና ሁለተኛ ስርቆት የሚባል
ነገር አለ እንዴ? እያለች ነበር፡፡
“ምን መሰለሽ? በስርቆቱ ላይ ባይኖርበትም ከሌቦቹ ጋራ በአንድ ላይ
ሆነው የተሰረቀውን ገንዘብ ሲያጠፉ ከተገኙ ሰዎች ጋር አብሮ ተገኝቶ ነው የተያዘው" በማለት ስለሁኔታው አስረዳት፡፡
ታዲያ አሁን አይለቀቅም?" በልምምጥ መልክ አይኖቿን በአይኖቹ ላይ
አንከራተተቻቸው፡፡
ያንተ ያለህ !እንዴት ነው አይኖቿ የሚያምሩት? አይኖቿን ለመሸሽ
አይኖቹ ወዲያና ወዲህ ተሯሯጡ :: የሚሄዱበት አጥተው ማምለጥ
ሲሳናቸው ደግሞ ተመልሰው መጡ፡፡ በአይኖቿ ባህር ውስጥ ሰጥመው በተዘረጋላቸው መረብ እንደ አሳ ሊዋጡ.......
“ስምሽ ማነው የኔ እመቤት?" ::
"ትህትና ድንበሩ" እየተቅለሰለሰች፡፡
“አንዱአለም ታላቅሽ ነው ወይስ ታናሽሽ?"
"ታናሼ ነው "
ሻምበል ብሩክ በስርቆቱ ወንጀል ላይ የተሳተፉት ዋነኞቹ ወንጀለኞች በእስር ቤት እንዲቆዩና፤ ሌሎቹ በዋስትና እንዲለቀቁ እሱና ሻለቃ ለሜሳ ቀደም ብለው ተወያይተው መመሪያ የሰጡበት ጉዳይ ነው፡፡የ ፶ አለቃ ውብሸት በመመሪያው መሰረት ሊያስተናግዳት ሲችል ለምን ወደ እሱ እንደላካት? ግራ ቢገባውም ልቡ አንድ ነገር ጠረጠረና በራሱ ግምት ትንሽ ፈገግ አለ፡፡
ይህቺን እንኮይ አንድ በላት ማለቱ ይሆን?"
"አንቺ ዋስ ሆነሽ ልታስፈቺው ነው የመጣሽው?"
“አዎን፡፡ ከፈቀዱልሽ ትችያለሽ ብለውኛል"
"ማነው እንደሱ ያለሽ?"
"መርማሪው"
ትህትና? ደግሞም አንቱ አትበይኝ አንተ እያልሽ አስረጂኝ”
"ስንት አመትሽ ነው
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
#ፖሊስ_ጣቢያ
የጣቢያው የምርመራ ሹም ሻምበል ብሩክ በላይ በእለታዊ የስራ ጉዳዩ ላይ ተጠምዶ፤ አንገቱን እንዳቀረቀረ ነበር፡፡ የቢሮው በር በቀስታ ተቆርቁሮ በዝግታ ሲከፈት፤ ልብ አላለም ፡፡እሱ በያዘው
አስደናቂ የወንጀል ሪፖርት ተመስጦ በሃሳብ ጭልጥ ብሎ ሄዶ ነበር፡፡ደመ ነፍሱ፤ በሩን ከፍቶ የገባው ከስራ ባልደረቦቹ አንዱ እንደሆነ ነበር
የነገረው፡፡በሩን ቆርቁሮ የገባው እንግዳ ግን ፤ እንደወትሮው ከስራ ባልደረቦቹ
አንዱ አልነበረም፡፡ ባለጉዳይ ነው፡፡ እሱ እንደዚያ አንገቱን አቀርቅሮ የቀረበለትን ፋይል ሲመረምር፤ ከፊት ለፊቱ እጆቹን አጣምሮ የቆመው እንግዳ ደግሞ፤ በድንጋጤ ተውጦ፤ የሱን ሁኔታ ይመረምር ነበር፡፡ዘንካታ ቁመናው ልቡን እንደመሰጠው ፤ መልኩ የሞዛርት ትዝታን
አመጣበት፡፡በተለይ ተጠቅልሎ ሄዶ ከግንባሩ ላይ ሲደርስ ክንብል ያለው
ዞማ ጸጉሩ ልዩ ውበትን አጎናጽፎት ተመለከተ፡፡ ሻምበል ብሩክ የደንብ
ልብሱ አብሮት እንደተፈጠረ ሁሉ እጅግ የሚያምርበት ግርማ ሞገስ ያለው ወጣት መኮንን ነው፡፡ ያ የገባ እንግዳ እሱ ራሱ በሌላ እንግዳ በሆነ የስሜት ሉጋም ተሸምቅቆ ልቡ በሃይል እየመታ፤ ትንፋሹ ቁርጥ፤ ቁርጥ፤እያለበት “እህህ እህህ ...."በማለት ጉሮሮውን ሳለና ድምጽ
አሰማ :: ሻምበል ብሩክ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀና ያለው በዚያ የእንግዳው ቀስቃሽ ድምጽ ምክንያት ነበር፡፡እንደዋዛ ቀና ያለው አንገቱ ዳግም ላለማጎንበስ ምሎ የተገዘተ ይመስል በዚያው ቀረ፡፡ባየው ነገር ተደናግጦና አይኖቹን ማመን ተስኖት እስከሚያስታውቅበት ድረስ ልቡ ዘለላች፡፡እዚህ ጋ ጎደለሽ የማትባል፤ አምላክ እጁን ታጥቦ የሰራት የምታስብል፧
የውበት እመቤት እጆችዋን ወደ ኋላ አጣምራ አንገትዋን አቀርቅራ ከፊት ለፊቱ ቆማ ተመለከተ፡፡ ሻምበል ብሩክ ልጅቷን አተኩሮ በማየት ፈዝዞና “ምን ልርዳሽ?" ብሎ መጠየቅ ግዴታው መሆኑን ዘንግቶት፤ የመጣችበትን ምክንያት ሳይጠይቅ፤ ለረጅም ደቂቃዎች በመዘግየቱ፤ እፍረት ቢጤ ቢሰማውም፤ እሷም ከዚያ በፊት በማንኛውም ወንድ ላይ ተሰምቷት በማያውቅ እንግዳ ስሜት ተሸብባ መቅረቷን ሲያውቅ ኖሮ፤
የእፍረት ስሜቱ ትንሽ በቀነስለት ነበር፡፡ እሱ ምን እንደዚያ እንዳፈዘዘው
ውስጡን ሲጠይቅ፤ ትህትናም “ለምን ደነገጥኩ ግን? የሚል ጥያቄ ለራሷ አቅርባ ነበር፡፡ልቧ የደነገጠበትን የመኮንኑ ተክለ ቁመናና ውበት ወደዚያ ተወት አድርጋ እራሷን ብትዋሽም ከዚያ የበለጠው ዋነኛ ምክንያቷ ግን፤ እንደዚያ ከነ ማእረግ ልብሱ አምሮና ተውቦ ስታየው፣ልቧ በደስታ የሚሞላበትን፤ እጅግ በጣም የምትወደውን፤ የአባቷን ትክለ ቁመና ስላስታወሳት መሆኑ ሳይታወቃት አልቀረም፡፡በትንሽነቷ ጊዜ አባቷ ያንን የምትወድለትን የማእረግ ልብሱን ለብሶ ስታየው፤ ትንሷ ልቧ
በደስታ እየዘለለች ፤እሷም እንደ አባቷ እንዲያምርባት፣ በዚያ በትንሽ ሰውነቷ ላይ ያንን ትልቅ ኮት ትደነቅር ፧ ሱሪው ውስጥ ትገባና እየተጎተተች ስትዘንጥ ፤ አባቷ በሳቅ ሲፈነዳ “አያምርብኝም አባዬ
"ስትለው፡፡
"እንዴታ ትህትናዬ በጣም እንጂ! አንቺም ስታድጊ እንደኔ ወታደር ትሆኝና ፤ ዩኒፎርምሽን ለብሰሽ፤ እንደዚህ ታጥቀሽ ፤ እንዴት እንደሚያምርብሽ ይታየኛል፡፡" ሲላት ቶሎ አድጋ፤ ያንን ዩኒፎርም
ለብሳ የምር የምትዘንጥበትን ጊዜ ስትናፍቅ፤ እያደገች ስትመጣ ደግሞ
ያንን ከጎኑ ሻጥ የሚያደርገውን ሽጉጥ ትቀበለውና፤ እሷም ጎኗ ላይ ሻጥ አድርጋ ስትንጎራደድ፤ ልዩ ደስታን ይሰጣት ነበር፡፡አባቷ ያንን ሽጉጥ ጥይቶቹን ከውስጡ ያወጣና ስለ አተኳኮሱ፧ ስለ አጠቃቀሙ ፤
እያሳያት፤ ባዶውን ሲሰጣት ታነጣጥርበትና ምላጩን ሳብ
ስታደርገው ፤ እሱም የውሸት ወደ ኋላ ሲወድቅላት፤ ከዚያም ትመጣና
ከሞተበት እንዲነሳ ስትኮረኩረው፡፡ከዚያም በሳቅ እየተፍለቀለቀ እቅፍ
አድርጎ ወደ ላይ አንስቶ ሲስማት፤ ይህ ሁሉ የነበረው ሁኔታ ..እሱ ታስቧት
ይሆን? ወይንስ ወንድሟን እንዲፈታላት መልአክ አድርጋ በሀሳቧ የሳለችው ሰው ነው ? እሷም አልገባትም ::
በህይወት እያለ ይሰማት የነበረው ስሜት አፈር ከለበሰ ይሄውና አመታት መቆጠር ጀምረዋል፡፡ አሁን ግን ለመጀመሪያ ጊዜ ያ ስሜት ፊት ለፊቷ በምታየው መኮንን ምክንያት በትዝታነቱ ተቀስቅሶባት
የገባችበትን ምክንያት እስከምትዘነጋው ድረስ አፈዘዛትና ቆማ ቀረች፡፡
ሻምበል ብሩክ የገባበት ሁኔታ ቀስ በቀስ አልፎለት፤ ስሜቱን መግዛት ሲጀምር።
ፊት ለፊቱ የቆመች ልጅ ምን እንደምትፈልግ መጠየቅ እንደሚገባው
ሲታሰበው፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ፊቱን ፈካ፤ ጥርሶቹን ብልጭ አደረጋቸው፡፡ እግዚኦ ! ጥርሶቹ እንዴት ነው የሚያምሩት? ስሜቷ እንደገና ተለዋወጠና ልቧ ትር ትር አለባት
አይኖቿ እንደዚያ ፍጥጥ ብለው ሲመለከቱት ሻምበልም ምን ልታዘዝ የኔ እመቤት?" የሱም ስሜት አብሯት እየተለዋወጠበት፡፡
"ወንድሜ ታስሮብኝ ነው የመጣሁት " ትንፋሽዋ እየተደነቃቀፈ፡፡
“እሺ ወንበሩ ላይ አረፍ በይና ንገሪኝ እስቲ በእጁ ወንበሩን እያመለከታት፡፡
ሻምበል ብሩክ ስሜቱ ለሁለት ተከፍሏል ፡አይኖቹ ከፊት ለፊቱ የሚታየውን ድንቅ ውበት በማድነቅ ስራቸውን ሲሰሩ ፤ ጆሮዎቹ ደግሞ የአቤቱታውን ምክንያት ለማዳመጥ ተከፍተዋል፡፡ ትህትናም አፏ
ስለአጋጠማት ችግር ሲያወራ፤ ልቧ ፊት ለፊቷ በተቀመጠው መኮንን ውብ ትክለ ቁመና ተማርኮ ከውስጥ እየሟሸሸባት ነበር፡፡
የእለት ሁኔታ መዝጋቢው ለእርስዎ እንዳመለክት ነግረውኝ ነው የመጣሁት”
“በምን ጉዳይ ነው የታሰረው? ማነው ስሙ? " አከታትሎ ጠየቃት፡፡
“አንዱአለም ድንበሩ ነው ስሙ"
"በዚያ በዲፕሎማት መኪና ላይ ስርቆሽ ከፈጸሙት ውስጥ ነው?"
“ኸረ እሱ ሌባ አይደለም" ፈርጠም ብላ፡፡
"ቆይኝ አንድ ጊዜ "አለና የቀረበለትን ሪፖርት ለማውጣት የጠረጴዛውን
መሳቢያ ከፈተ፡፡ በዚያ በስርቆት ወንጀል ላይ የተሳተፉት ሶስት ሰዎች ሲሆኑ የአንዱአለም ስም የለበትም፡፡
ልክ ነሽ፡፡ በዋናው ስርቆት ላይ አልነበረም
"ለምን ታሰረ ታዲያ?" በልቧ" ዋና ስርቆትና ሁለተኛ ስርቆት የሚባል
ነገር አለ እንዴ? እያለች ነበር፡፡
“ምን መሰለሽ? በስርቆቱ ላይ ባይኖርበትም ከሌቦቹ ጋራ በአንድ ላይ
ሆነው የተሰረቀውን ገንዘብ ሲያጠፉ ከተገኙ ሰዎች ጋር አብሮ ተገኝቶ ነው የተያዘው" በማለት ስለሁኔታው አስረዳት፡፡
ታዲያ አሁን አይለቀቅም?" በልምምጥ መልክ አይኖቿን በአይኖቹ ላይ
አንከራተተቻቸው፡፡
ያንተ ያለህ !እንዴት ነው አይኖቿ የሚያምሩት? አይኖቿን ለመሸሽ
አይኖቹ ወዲያና ወዲህ ተሯሯጡ :: የሚሄዱበት አጥተው ማምለጥ
ሲሳናቸው ደግሞ ተመልሰው መጡ፡፡ በአይኖቿ ባህር ውስጥ ሰጥመው በተዘረጋላቸው መረብ እንደ አሳ ሊዋጡ.......
“ስምሽ ማነው የኔ እመቤት?" ::
"ትህትና ድንበሩ" እየተቅለሰለሰች፡፡
“አንዱአለም ታላቅሽ ነው ወይስ ታናሽሽ?"
"ታናሼ ነው "
ሻምበል ብሩክ በስርቆቱ ወንጀል ላይ የተሳተፉት ዋነኞቹ ወንጀለኞች በእስር ቤት እንዲቆዩና፤ ሌሎቹ በዋስትና እንዲለቀቁ እሱና ሻለቃ ለሜሳ ቀደም ብለው ተወያይተው መመሪያ የሰጡበት ጉዳይ ነው፡፡የ ፶ አለቃ ውብሸት በመመሪያው መሰረት ሊያስተናግዳት ሲችል ለምን ወደ እሱ እንደላካት? ግራ ቢገባውም ልቡ አንድ ነገር ጠረጠረና በራሱ ግምት ትንሽ ፈገግ አለ፡፡
ይህቺን እንኮይ አንድ በላት ማለቱ ይሆን?"
"አንቺ ዋስ ሆነሽ ልታስፈቺው ነው የመጣሽው?"
“አዎን፡፡ ከፈቀዱልሽ ትችያለሽ ብለውኛል"
"ማነው እንደሱ ያለሽ?"
"መርማሪው"
ትህትና? ደግሞም አንቱ አትበይኝ አንተ እያልሽ አስረጂኝ”
"ስንት አመትሽ ነው