#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
#ፖሊስ_ጣቢያ
የጣቢያው የምርመራ ሹም ሻምበል ብሩክ በላይ በእለታዊ የስራ ጉዳዩ ላይ ተጠምዶ፤ አንገቱን እንዳቀረቀረ ነበር፡፡ የቢሮው በር በቀስታ ተቆርቁሮ በዝግታ ሲከፈት፤ ልብ አላለም ፡፡እሱ በያዘው
አስደናቂ የወንጀል ሪፖርት ተመስጦ በሃሳብ ጭልጥ ብሎ ሄዶ ነበር፡፡ደመ ነፍሱ፤ በሩን ከፍቶ የገባው ከስራ ባልደረቦቹ አንዱ እንደሆነ ነበር
የነገረው፡፡በሩን ቆርቁሮ የገባው እንግዳ ግን ፤ እንደወትሮው ከስራ ባልደረቦቹ
አንዱ አልነበረም፡፡ ባለጉዳይ ነው፡፡ እሱ እንደዚያ አንገቱን አቀርቅሮ የቀረበለትን ፋይል ሲመረምር፤ ከፊት ለፊቱ እጆቹን አጣምሮ የቆመው እንግዳ ደግሞ፤ በድንጋጤ ተውጦ፤ የሱን ሁኔታ ይመረምር ነበር፡፡ዘንካታ ቁመናው ልቡን እንደመሰጠው ፤ መልኩ የሞዛርት ትዝታን
አመጣበት፡፡በተለይ ተጠቅልሎ ሄዶ ከግንባሩ ላይ ሲደርስ ክንብል ያለው
ዞማ ጸጉሩ ልዩ ውበትን አጎናጽፎት ተመለከተ፡፡ ሻምበል ብሩክ የደንብ
ልብሱ አብሮት እንደተፈጠረ ሁሉ እጅግ የሚያምርበት ግርማ ሞገስ ያለው ወጣት መኮንን ነው፡፡ ያ የገባ እንግዳ እሱ ራሱ በሌላ እንግዳ በሆነ የስሜት ሉጋም ተሸምቅቆ ልቡ በሃይል እየመታ፤ ትንፋሹ ቁርጥ፤ ቁርጥ፤እያለበት “እህህ እህህ ...."በማለት ጉሮሮውን ሳለና ድምጽ
አሰማ :: ሻምበል ብሩክ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀና ያለው በዚያ የእንግዳው ቀስቃሽ ድምጽ ምክንያት ነበር፡፡እንደዋዛ ቀና ያለው አንገቱ ዳግም ላለማጎንበስ ምሎ የተገዘተ ይመስል በዚያው ቀረ፡፡ባየው ነገር ተደናግጦና አይኖቹን ማመን ተስኖት እስከሚያስታውቅበት ድረስ ልቡ ዘለላች፡፡እዚህ ጋ ጎደለሽ የማትባል፤ አምላክ እጁን ታጥቦ የሰራት የምታስብል፧
የውበት እመቤት እጆችዋን ወደ ኋላ አጣምራ አንገትዋን አቀርቅራ ከፊት ለፊቱ ቆማ ተመለከተ፡፡ ሻምበል ብሩክ ልጅቷን አተኩሮ በማየት ፈዝዞና “ምን ልርዳሽ?" ብሎ መጠየቅ ግዴታው መሆኑን ዘንግቶት፤ የመጣችበትን ምክንያት ሳይጠይቅ፤ ለረጅም ደቂቃዎች በመዘግየቱ፤ እፍረት ቢጤ ቢሰማውም፤ እሷም ከዚያ በፊት በማንኛውም ወንድ ላይ ተሰምቷት በማያውቅ እንግዳ ስሜት ተሸብባ መቅረቷን ሲያውቅ ኖሮ፤
የእፍረት ስሜቱ ትንሽ በቀነስለት ነበር፡፡ እሱ ምን እንደዚያ እንዳፈዘዘው
ውስጡን ሲጠይቅ፤ ትህትናም “ለምን ደነገጥኩ ግን? የሚል ጥያቄ ለራሷ አቅርባ ነበር፡፡ልቧ የደነገጠበትን የመኮንኑ ተክለ ቁመናና ውበት ወደዚያ ተወት አድርጋ እራሷን ብትዋሽም ከዚያ የበለጠው ዋነኛ ምክንያቷ ግን፤ እንደዚያ ከነ ማእረግ ልብሱ አምሮና ተውቦ ስታየው፣ልቧ በደስታ የሚሞላበትን፤ እጅግ በጣም የምትወደውን፤ የአባቷን ትክለ ቁመና ስላስታወሳት መሆኑ ሳይታወቃት አልቀረም፡፡በትንሽነቷ ጊዜ አባቷ ያንን የምትወድለትን የማእረግ ልብሱን ለብሶ ስታየው፤ ትንሷ ልቧ
በደስታ እየዘለለች ፤እሷም እንደ አባቷ እንዲያምርባት፣ በዚያ በትንሽ ሰውነቷ ላይ ያንን ትልቅ ኮት ትደነቅር ፧ ሱሪው ውስጥ ትገባና እየተጎተተች ስትዘንጥ ፤ አባቷ በሳቅ ሲፈነዳ “አያምርብኝም አባዬ
"ስትለው፡፡
"እንዴታ ትህትናዬ በጣም እንጂ! አንቺም ስታድጊ እንደኔ ወታደር ትሆኝና ፤ ዩኒፎርምሽን ለብሰሽ፤ እንደዚህ ታጥቀሽ ፤ እንዴት እንደሚያምርብሽ ይታየኛል፡፡" ሲላት ቶሎ አድጋ፤ ያንን ዩኒፎርም
ለብሳ የምር የምትዘንጥበትን ጊዜ ስትናፍቅ፤ እያደገች ስትመጣ ደግሞ
ያንን ከጎኑ ሻጥ የሚያደርገውን ሽጉጥ ትቀበለውና፤ እሷም ጎኗ ላይ ሻጥ አድርጋ ስትንጎራደድ፤ ልዩ ደስታን ይሰጣት ነበር፡፡አባቷ ያንን ሽጉጥ ጥይቶቹን ከውስጡ ያወጣና ስለ አተኳኮሱ፧ ስለ አጠቃቀሙ ፤
እያሳያት፤ ባዶውን ሲሰጣት ታነጣጥርበትና ምላጩን ሳብ
ስታደርገው ፤ እሱም የውሸት ወደ ኋላ ሲወድቅላት፤ ከዚያም ትመጣና
ከሞተበት እንዲነሳ ስትኮረኩረው፡፡ከዚያም በሳቅ እየተፍለቀለቀ እቅፍ
አድርጎ ወደ ላይ አንስቶ ሲስማት፤ ይህ ሁሉ የነበረው ሁኔታ ..እሱ ታስቧት
ይሆን? ወይንስ ወንድሟን እንዲፈታላት መልአክ አድርጋ በሀሳቧ የሳለችው ሰው ነው ? እሷም አልገባትም ::
በህይወት እያለ ይሰማት የነበረው ስሜት አፈር ከለበሰ ይሄውና አመታት መቆጠር ጀምረዋል፡፡ አሁን ግን ለመጀመሪያ ጊዜ ያ ስሜት ፊት ለፊቷ በምታየው መኮንን ምክንያት በትዝታነቱ ተቀስቅሶባት
የገባችበትን ምክንያት እስከምትዘነጋው ድረስ አፈዘዛትና ቆማ ቀረች፡፡
ሻምበል ብሩክ የገባበት ሁኔታ ቀስ በቀስ አልፎለት፤ ስሜቱን መግዛት ሲጀምር።
ፊት ለፊቱ የቆመች ልጅ ምን እንደምትፈልግ መጠየቅ እንደሚገባው
ሲታሰበው፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ፊቱን ፈካ፤ ጥርሶቹን ብልጭ አደረጋቸው፡፡ እግዚኦ ! ጥርሶቹ እንዴት ነው የሚያምሩት? ስሜቷ እንደገና ተለዋወጠና ልቧ ትር ትር አለባት
አይኖቿ እንደዚያ ፍጥጥ ብለው ሲመለከቱት ሻምበልም ምን ልታዘዝ የኔ እመቤት?" የሱም ስሜት አብሯት እየተለዋወጠበት፡፡
"ወንድሜ ታስሮብኝ ነው የመጣሁት " ትንፋሽዋ እየተደነቃቀፈ፡፡
“እሺ ወንበሩ ላይ አረፍ በይና ንገሪኝ እስቲ በእጁ ወንበሩን እያመለከታት፡፡
ሻምበል ብሩክ ስሜቱ ለሁለት ተከፍሏል ፡አይኖቹ ከፊት ለፊቱ የሚታየውን ድንቅ ውበት በማድነቅ ስራቸውን ሲሰሩ ፤ ጆሮዎቹ ደግሞ የአቤቱታውን ምክንያት ለማዳመጥ ተከፍተዋል፡፡ ትህትናም አፏ
ስለአጋጠማት ችግር ሲያወራ፤ ልቧ ፊት ለፊቷ በተቀመጠው መኮንን ውብ ትክለ ቁመና ተማርኮ ከውስጥ እየሟሸሸባት ነበር፡፡
የእለት ሁኔታ መዝጋቢው ለእርስዎ እንዳመለክት ነግረውኝ ነው የመጣሁት”
“በምን ጉዳይ ነው የታሰረው? ማነው ስሙ? " አከታትሎ ጠየቃት፡፡
“አንዱአለም ድንበሩ ነው ስሙ"
"በዚያ በዲፕሎማት መኪና ላይ ስርቆሽ ከፈጸሙት ውስጥ ነው?"
“ኸረ እሱ ሌባ አይደለም" ፈርጠም ብላ፡፡
"ቆይኝ አንድ ጊዜ "አለና የቀረበለትን ሪፖርት ለማውጣት የጠረጴዛውን
መሳቢያ ከፈተ፡፡ በዚያ በስርቆት ወንጀል ላይ የተሳተፉት ሶስት ሰዎች ሲሆኑ የአንዱአለም ስም የለበትም፡፡
ልክ ነሽ፡፡ በዋናው ስርቆት ላይ አልነበረም
"ለምን ታሰረ ታዲያ?" በልቧ" ዋና ስርቆትና ሁለተኛ ስርቆት የሚባል
ነገር አለ እንዴ? እያለች ነበር፡፡
“ምን መሰለሽ? በስርቆቱ ላይ ባይኖርበትም ከሌቦቹ ጋራ በአንድ ላይ
ሆነው የተሰረቀውን ገንዘብ ሲያጠፉ ከተገኙ ሰዎች ጋር አብሮ ተገኝቶ ነው የተያዘው" በማለት ስለሁኔታው አስረዳት፡፡
ታዲያ አሁን አይለቀቅም?" በልምምጥ መልክ አይኖቿን በአይኖቹ ላይ
አንከራተተቻቸው፡፡
ያንተ ያለህ !እንዴት ነው አይኖቿ የሚያምሩት? አይኖቿን ለመሸሽ
አይኖቹ ወዲያና ወዲህ ተሯሯጡ :: የሚሄዱበት አጥተው ማምለጥ
ሲሳናቸው ደግሞ ተመልሰው መጡ፡፡ በአይኖቿ ባህር ውስጥ ሰጥመው በተዘረጋላቸው መረብ እንደ አሳ ሊዋጡ.......
“ስምሽ ማነው የኔ እመቤት?" ::
"ትህትና ድንበሩ" እየተቅለሰለሰች፡፡
“አንዱአለም ታላቅሽ ነው ወይስ ታናሽሽ?"
"ታናሼ ነው "
ሻምበል ብሩክ በስርቆቱ ወንጀል ላይ የተሳተፉት ዋነኞቹ ወንጀለኞች በእስር ቤት እንዲቆዩና፤ ሌሎቹ በዋስትና እንዲለቀቁ እሱና ሻለቃ ለሜሳ ቀደም ብለው ተወያይተው መመሪያ የሰጡበት ጉዳይ ነው፡፡የ ፶ አለቃ ውብሸት በመመሪያው መሰረት ሊያስተናግዳት ሲችል ለምን ወደ እሱ እንደላካት? ግራ ቢገባውም ልቡ አንድ ነገር ጠረጠረና በራሱ ግምት ትንሽ ፈገግ አለ፡፡
ይህቺን እንኮይ አንድ በላት ማለቱ ይሆን?"
"አንቺ ዋስ ሆነሽ ልታስፈቺው ነው የመጣሽው?"
“አዎን፡፡ ከፈቀዱልሽ ትችያለሽ ብለውኛል"
"ማነው እንደሱ ያለሽ?"
"መርማሪው"
ትህትና? ደግሞም አንቱ አትበይኝ አንተ እያልሽ አስረጂኝ”
"ስንት አመትሽ ነው
፡
፡
#ክፍል_አስራ_ስድስት
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
#ፖሊስ_ጣቢያ
የጣቢያው የምርመራ ሹም ሻምበል ብሩክ በላይ በእለታዊ የስራ ጉዳዩ ላይ ተጠምዶ፤ አንገቱን እንዳቀረቀረ ነበር፡፡ የቢሮው በር በቀስታ ተቆርቁሮ በዝግታ ሲከፈት፤ ልብ አላለም ፡፡እሱ በያዘው
አስደናቂ የወንጀል ሪፖርት ተመስጦ በሃሳብ ጭልጥ ብሎ ሄዶ ነበር፡፡ደመ ነፍሱ፤ በሩን ከፍቶ የገባው ከስራ ባልደረቦቹ አንዱ እንደሆነ ነበር
የነገረው፡፡በሩን ቆርቁሮ የገባው እንግዳ ግን ፤ እንደወትሮው ከስራ ባልደረቦቹ
አንዱ አልነበረም፡፡ ባለጉዳይ ነው፡፡ እሱ እንደዚያ አንገቱን አቀርቅሮ የቀረበለትን ፋይል ሲመረምር፤ ከፊት ለፊቱ እጆቹን አጣምሮ የቆመው እንግዳ ደግሞ፤ በድንጋጤ ተውጦ፤ የሱን ሁኔታ ይመረምር ነበር፡፡ዘንካታ ቁመናው ልቡን እንደመሰጠው ፤ መልኩ የሞዛርት ትዝታን
አመጣበት፡፡በተለይ ተጠቅልሎ ሄዶ ከግንባሩ ላይ ሲደርስ ክንብል ያለው
ዞማ ጸጉሩ ልዩ ውበትን አጎናጽፎት ተመለከተ፡፡ ሻምበል ብሩክ የደንብ
ልብሱ አብሮት እንደተፈጠረ ሁሉ እጅግ የሚያምርበት ግርማ ሞገስ ያለው ወጣት መኮንን ነው፡፡ ያ የገባ እንግዳ እሱ ራሱ በሌላ እንግዳ በሆነ የስሜት ሉጋም ተሸምቅቆ ልቡ በሃይል እየመታ፤ ትንፋሹ ቁርጥ፤ ቁርጥ፤እያለበት “እህህ እህህ ...."በማለት ጉሮሮውን ሳለና ድምጽ
አሰማ :: ሻምበል ብሩክ ለመጀመሪያ ጊዜ ቀና ያለው በዚያ የእንግዳው ቀስቃሽ ድምጽ ምክንያት ነበር፡፡እንደዋዛ ቀና ያለው አንገቱ ዳግም ላለማጎንበስ ምሎ የተገዘተ ይመስል በዚያው ቀረ፡፡ባየው ነገር ተደናግጦና አይኖቹን ማመን ተስኖት እስከሚያስታውቅበት ድረስ ልቡ ዘለላች፡፡እዚህ ጋ ጎደለሽ የማትባል፤ አምላክ እጁን ታጥቦ የሰራት የምታስብል፧
የውበት እመቤት እጆችዋን ወደ ኋላ አጣምራ አንገትዋን አቀርቅራ ከፊት ለፊቱ ቆማ ተመለከተ፡፡ ሻምበል ብሩክ ልጅቷን አተኩሮ በማየት ፈዝዞና “ምን ልርዳሽ?" ብሎ መጠየቅ ግዴታው መሆኑን ዘንግቶት፤ የመጣችበትን ምክንያት ሳይጠይቅ፤ ለረጅም ደቂቃዎች በመዘግየቱ፤ እፍረት ቢጤ ቢሰማውም፤ እሷም ከዚያ በፊት በማንኛውም ወንድ ላይ ተሰምቷት በማያውቅ እንግዳ ስሜት ተሸብባ መቅረቷን ሲያውቅ ኖሮ፤
የእፍረት ስሜቱ ትንሽ በቀነስለት ነበር፡፡ እሱ ምን እንደዚያ እንዳፈዘዘው
ውስጡን ሲጠይቅ፤ ትህትናም “ለምን ደነገጥኩ ግን? የሚል ጥያቄ ለራሷ አቅርባ ነበር፡፡ልቧ የደነገጠበትን የመኮንኑ ተክለ ቁመናና ውበት ወደዚያ ተወት አድርጋ እራሷን ብትዋሽም ከዚያ የበለጠው ዋነኛ ምክንያቷ ግን፤ እንደዚያ ከነ ማእረግ ልብሱ አምሮና ተውቦ ስታየው፣ልቧ በደስታ የሚሞላበትን፤ እጅግ በጣም የምትወደውን፤ የአባቷን ትክለ ቁመና ስላስታወሳት መሆኑ ሳይታወቃት አልቀረም፡፡በትንሽነቷ ጊዜ አባቷ ያንን የምትወድለትን የማእረግ ልብሱን ለብሶ ስታየው፤ ትንሷ ልቧ
በደስታ እየዘለለች ፤እሷም እንደ አባቷ እንዲያምርባት፣ በዚያ በትንሽ ሰውነቷ ላይ ያንን ትልቅ ኮት ትደነቅር ፧ ሱሪው ውስጥ ትገባና እየተጎተተች ስትዘንጥ ፤ አባቷ በሳቅ ሲፈነዳ “አያምርብኝም አባዬ
"ስትለው፡፡
"እንዴታ ትህትናዬ በጣም እንጂ! አንቺም ስታድጊ እንደኔ ወታደር ትሆኝና ፤ ዩኒፎርምሽን ለብሰሽ፤ እንደዚህ ታጥቀሽ ፤ እንዴት እንደሚያምርብሽ ይታየኛል፡፡" ሲላት ቶሎ አድጋ፤ ያንን ዩኒፎርም
ለብሳ የምር የምትዘንጥበትን ጊዜ ስትናፍቅ፤ እያደገች ስትመጣ ደግሞ
ያንን ከጎኑ ሻጥ የሚያደርገውን ሽጉጥ ትቀበለውና፤ እሷም ጎኗ ላይ ሻጥ አድርጋ ስትንጎራደድ፤ ልዩ ደስታን ይሰጣት ነበር፡፡አባቷ ያንን ሽጉጥ ጥይቶቹን ከውስጡ ያወጣና ስለ አተኳኮሱ፧ ስለ አጠቃቀሙ ፤
እያሳያት፤ ባዶውን ሲሰጣት ታነጣጥርበትና ምላጩን ሳብ
ስታደርገው ፤ እሱም የውሸት ወደ ኋላ ሲወድቅላት፤ ከዚያም ትመጣና
ከሞተበት እንዲነሳ ስትኮረኩረው፡፡ከዚያም በሳቅ እየተፍለቀለቀ እቅፍ
አድርጎ ወደ ላይ አንስቶ ሲስማት፤ ይህ ሁሉ የነበረው ሁኔታ ..እሱ ታስቧት
ይሆን? ወይንስ ወንድሟን እንዲፈታላት መልአክ አድርጋ በሀሳቧ የሳለችው ሰው ነው ? እሷም አልገባትም ::
በህይወት እያለ ይሰማት የነበረው ስሜት አፈር ከለበሰ ይሄውና አመታት መቆጠር ጀምረዋል፡፡ አሁን ግን ለመጀመሪያ ጊዜ ያ ስሜት ፊት ለፊቷ በምታየው መኮንን ምክንያት በትዝታነቱ ተቀስቅሶባት
የገባችበትን ምክንያት እስከምትዘነጋው ድረስ አፈዘዛትና ቆማ ቀረች፡፡
ሻምበል ብሩክ የገባበት ሁኔታ ቀስ በቀስ አልፎለት፤ ስሜቱን መግዛት ሲጀምር።
ፊት ለፊቱ የቆመች ልጅ ምን እንደምትፈልግ መጠየቅ እንደሚገባው
ሲታሰበው፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ፊቱን ፈካ፤ ጥርሶቹን ብልጭ አደረጋቸው፡፡ እግዚኦ ! ጥርሶቹ እንዴት ነው የሚያምሩት? ስሜቷ እንደገና ተለዋወጠና ልቧ ትር ትር አለባት
አይኖቿ እንደዚያ ፍጥጥ ብለው ሲመለከቱት ሻምበልም ምን ልታዘዝ የኔ እመቤት?" የሱም ስሜት አብሯት እየተለዋወጠበት፡፡
"ወንድሜ ታስሮብኝ ነው የመጣሁት " ትንፋሽዋ እየተደነቃቀፈ፡፡
“እሺ ወንበሩ ላይ አረፍ በይና ንገሪኝ እስቲ በእጁ ወንበሩን እያመለከታት፡፡
ሻምበል ብሩክ ስሜቱ ለሁለት ተከፍሏል ፡አይኖቹ ከፊት ለፊቱ የሚታየውን ድንቅ ውበት በማድነቅ ስራቸውን ሲሰሩ ፤ ጆሮዎቹ ደግሞ የአቤቱታውን ምክንያት ለማዳመጥ ተከፍተዋል፡፡ ትህትናም አፏ
ስለአጋጠማት ችግር ሲያወራ፤ ልቧ ፊት ለፊቷ በተቀመጠው መኮንን ውብ ትክለ ቁመና ተማርኮ ከውስጥ እየሟሸሸባት ነበር፡፡
የእለት ሁኔታ መዝጋቢው ለእርስዎ እንዳመለክት ነግረውኝ ነው የመጣሁት”
“በምን ጉዳይ ነው የታሰረው? ማነው ስሙ? " አከታትሎ ጠየቃት፡፡
“አንዱአለም ድንበሩ ነው ስሙ"
"በዚያ በዲፕሎማት መኪና ላይ ስርቆሽ ከፈጸሙት ውስጥ ነው?"
“ኸረ እሱ ሌባ አይደለም" ፈርጠም ብላ፡፡
"ቆይኝ አንድ ጊዜ "አለና የቀረበለትን ሪፖርት ለማውጣት የጠረጴዛውን
መሳቢያ ከፈተ፡፡ በዚያ በስርቆት ወንጀል ላይ የተሳተፉት ሶስት ሰዎች ሲሆኑ የአንዱአለም ስም የለበትም፡፡
ልክ ነሽ፡፡ በዋናው ስርቆት ላይ አልነበረም
"ለምን ታሰረ ታዲያ?" በልቧ" ዋና ስርቆትና ሁለተኛ ስርቆት የሚባል
ነገር አለ እንዴ? እያለች ነበር፡፡
“ምን መሰለሽ? በስርቆቱ ላይ ባይኖርበትም ከሌቦቹ ጋራ በአንድ ላይ
ሆነው የተሰረቀውን ገንዘብ ሲያጠፉ ከተገኙ ሰዎች ጋር አብሮ ተገኝቶ ነው የተያዘው" በማለት ስለሁኔታው አስረዳት፡፡
ታዲያ አሁን አይለቀቅም?" በልምምጥ መልክ አይኖቿን በአይኖቹ ላይ
አንከራተተቻቸው፡፡
ያንተ ያለህ !እንዴት ነው አይኖቿ የሚያምሩት? አይኖቿን ለመሸሽ
አይኖቹ ወዲያና ወዲህ ተሯሯጡ :: የሚሄዱበት አጥተው ማምለጥ
ሲሳናቸው ደግሞ ተመልሰው መጡ፡፡ በአይኖቿ ባህር ውስጥ ሰጥመው በተዘረጋላቸው መረብ እንደ አሳ ሊዋጡ.......
“ስምሽ ማነው የኔ እመቤት?" ::
"ትህትና ድንበሩ" እየተቅለሰለሰች፡፡
“አንዱአለም ታላቅሽ ነው ወይስ ታናሽሽ?"
"ታናሼ ነው "
ሻምበል ብሩክ በስርቆቱ ወንጀል ላይ የተሳተፉት ዋነኞቹ ወንጀለኞች በእስር ቤት እንዲቆዩና፤ ሌሎቹ በዋስትና እንዲለቀቁ እሱና ሻለቃ ለሜሳ ቀደም ብለው ተወያይተው መመሪያ የሰጡበት ጉዳይ ነው፡፡የ ፶ አለቃ ውብሸት በመመሪያው መሰረት ሊያስተናግዳት ሲችል ለምን ወደ እሱ እንደላካት? ግራ ቢገባውም ልቡ አንድ ነገር ጠረጠረና በራሱ ግምት ትንሽ ፈገግ አለ፡፡
ይህቺን እንኮይ አንድ በላት ማለቱ ይሆን?"
"አንቺ ዋስ ሆነሽ ልታስፈቺው ነው የመጣሽው?"
“አዎን፡፡ ከፈቀዱልሽ ትችያለሽ ብለውኛል"
"ማነው እንደሱ ያለሽ?"
"መርማሪው"
ትህትና? ደግሞም አንቱ አትበይኝ አንተ እያልሽ አስረጂኝ”
"ስንት አመትሽ ነው