#ብሂላዊ #ምክሮች
#ሀሜት:- ያለ መሳሪያ ሰዉን መግደል ነዉ
#ማጉረምረም:- ባገኙት በቃኝ ብሎ አለማመስገን ነው።
#ቁጣ:- ከስድብ የሚያደርስ የክፉ አድራጎት መሰረት ነው።
#ብስጭት:- የተበሳጩበትን ነገር ሳይሆን ተመልሶ ራስን የሚጎዳ መርዝ ከክህደት የሚያደርስ የሀጥያት ምንጭ ጭንቀትን የሚያነድ ትንሽ ክብሪት ነዉ።
#መርገም:- አቅም ሲያንስ ወደ ላይ የሚወረወር የደካማ ሰዎች ቀስት ነው።
#መሳደብ:- ህሊናን የሚያቆስል ቁስሉ ቶሎ የማይድን አቅም የሌላቸዉ ሰዎች ዱለ ነው።
#ዋዛ #ፈዛዛ:- በስልት የሚቃኙት የስራ ፈቶች በገና ነው።
#ዘፈን:-😕ለዝሙት የሚያነቃ ልብ የሚወጋ ፍላፃ ነው።
#ድንፋታ:- የጀግኖች ባልትና የሰነፎች ጫጫታ
ነው።
#በክፉ #ማንሾካሾክ:- ቀስ ብለዉ ሰዉን የሚገድልበት የአሳባቂዎች ጩህት ነው።
#ነገር:- ማመላለስ የሚዋደዱትን የሚለያዬበት የዲያቢሎስ የግብር ልጆች መሳርያ ነው።
#የአደራ #ገንዘብ #መብላት:- ሳይጥሩ ሳይግሩ የሰዉ ላብ ሲበሉ የሚኖሩበት የሰነፍ ሰዎች መሳርያቸዉ ነው።
#ሰዉን #ማስነወር:- ሰዉ የወደደዉን የተከበረዉን ስም ለማጥፋት የሚቀቡት የምቀኞች ቀለም ነው።
#መሳለቅ:- የማይታይ የቀናተኞች ጦር ነው።
#ተስፋ:- ከማጣት ወደ ማግኘት ለመሸጋገር የሚያገለግል ድልድይ ነው።
#ጠብ:- እሳትን ለማንደድ የሚጫር የነገረኞች የኪስ ክብሪት ነዉ።
#ችኮላ:- የትእግስት ጠላት የፀፀት አባት ነው ልጁም ወይኔ ይባላል።
#ሙከራ:- የስራ ጥልቀትን መለኪያና መመጠኛ ነው።
#የጥበብ #መጀመርያ #እግዚአብሔርን #መፍራት #ነው።
ከ ያለ ጭንቀት የመኖር ምስጢር መፅሀፍ የተወሰደ በዲ/ን የሺጥላ ሞገስ
#ሀሜት:- ያለ መሳሪያ ሰዉን መግደል ነዉ
#ማጉረምረም:- ባገኙት በቃኝ ብሎ አለማመስገን ነው።
#ቁጣ:- ከስድብ የሚያደርስ የክፉ አድራጎት መሰረት ነው።
#ብስጭት:- የተበሳጩበትን ነገር ሳይሆን ተመልሶ ራስን የሚጎዳ መርዝ ከክህደት የሚያደርስ የሀጥያት ምንጭ ጭንቀትን የሚያነድ ትንሽ ክብሪት ነዉ።
#መርገም:- አቅም ሲያንስ ወደ ላይ የሚወረወር የደካማ ሰዎች ቀስት ነው።
#መሳደብ:- ህሊናን የሚያቆስል ቁስሉ ቶሎ የማይድን አቅም የሌላቸዉ ሰዎች ዱለ ነው።
#ዋዛ #ፈዛዛ:- በስልት የሚቃኙት የስራ ፈቶች በገና ነው።
#ዘፈን:-😕ለዝሙት የሚያነቃ ልብ የሚወጋ ፍላፃ ነው።
#ድንፋታ:- የጀግኖች ባልትና የሰነፎች ጫጫታ
ነው።
#በክፉ #ማንሾካሾክ:- ቀስ ብለዉ ሰዉን የሚገድልበት የአሳባቂዎች ጩህት ነው።
#ነገር:- ማመላለስ የሚዋደዱትን የሚለያዬበት የዲያቢሎስ የግብር ልጆች መሳርያ ነው።
#የአደራ #ገንዘብ #መብላት:- ሳይጥሩ ሳይግሩ የሰዉ ላብ ሲበሉ የሚኖሩበት የሰነፍ ሰዎች መሳርያቸዉ ነው።
#ሰዉን #ማስነወር:- ሰዉ የወደደዉን የተከበረዉን ስም ለማጥፋት የሚቀቡት የምቀኞች ቀለም ነው።
#መሳለቅ:- የማይታይ የቀናተኞች ጦር ነው።
#ተስፋ:- ከማጣት ወደ ማግኘት ለመሸጋገር የሚያገለግል ድልድይ ነው።
#ጠብ:- እሳትን ለማንደድ የሚጫር የነገረኞች የኪስ ክብሪት ነዉ።
#ችኮላ:- የትእግስት ጠላት የፀፀት አባት ነው ልጁም ወይኔ ይባላል።
#ሙከራ:- የስራ ጥልቀትን መለኪያና መመጠኛ ነው።
#የጥበብ #መጀመርያ #እግዚአብሔርን #መፍራት #ነው።
ከ ያለ ጭንቀት የመኖር ምስጢር መፅሀፍ የተወሰደ በዲ/ን የሺጥላ ሞገስ
👍2
#የጥበብ_ፈተና
ለአንድ ነብስሽ እንኳ ለራስሽ ሳታቂ ለሌላ እመተርፊ
ሰው ሆነሽ ተፈጥረሽ ከሰው እምትልቂ ከሰው እምትገዝፊ
ሀ) በድምፅ ብትወከይ
ለ) ጆሮ ማያዳምጥሽ እማይለይ ውስጥሽ
ሐ)ቢቀርፁሽ ብትሳይ
መ)ለተመልካች ባዳ
ለእይታ እንግዳ
ሠ)በቃል ብትፃፊ
ረ)ለአንባቢ እማትገቢ።
እምትጋነኚ
እማትታመኚ
ከሰዓሊው እርቀሽ ከመስመር የወጣሽ ማየሸገልፅሽ ቀለም
ነፍስ ሚያለመልም ድምፅ አልባ ሙዚቃ ዜማ እንዳንቺ የለም
በመላው ምድረረ ዓለም።
ከገጣሚው ይልቅ አይረሴ ግጥም መንፈስ የሚያፀና
ከባለቅኔው ይበልጥ ተለይቶ ሚታይ የላቀ ልእልና
ከድርሰት በላይ ነሽ የደራሲ አሳር የጥበብ ፈተና።
አክሱም አይወክልሽ ላሊበላ አይሆንም ዕውነትሽን ማሳያ
ዘመን ተሻጋሪ ሕያው ለዝንታለም የሌለሽ አምሳያ
የሰማይ መቀነት ቀስተ ደመና ነው ሰንደቅሽ መታያ።
ሀገሬ ኢትዮጵያ ሆገሬ ኢትዮጵያ!
ስሜት ቢነ ቃቃ ስሜት ቢነሳሳ ሐሳብ ቢሰበሰብ
በረቀቀ ምናብ በጠሊቅ ልቡና ሺ ጊዜ ቢታሰብ
በቅርፅና ይዘት
መቼም አይፈጠር እንዳንቺ ገፀሀገር እንዳንቺ ገፀ ሰብ፡፡
ለአንድ ነብስሽ እንኳ ለራስሽ ሳታቂ ለሌላ እመተርፊ
ሰው ሆነሽ ተፈጥረሽ ከሰው እምትልቂ ከሰው እምትገዝፊ
ሀ) በድምፅ ብትወከይ
ለ) ጆሮ ማያዳምጥሽ እማይለይ ውስጥሽ
ሐ)ቢቀርፁሽ ብትሳይ
መ)ለተመልካች ባዳ
ለእይታ እንግዳ
ሠ)በቃል ብትፃፊ
ረ)ለአንባቢ እማትገቢ።
እምትጋነኚ
እማትታመኚ
ከሰዓሊው እርቀሽ ከመስመር የወጣሽ ማየሸገልፅሽ ቀለም
ነፍስ ሚያለመልም ድምፅ አልባ ሙዚቃ ዜማ እንዳንቺ የለም
በመላው ምድረረ ዓለም።
ከገጣሚው ይልቅ አይረሴ ግጥም መንፈስ የሚያፀና
ከባለቅኔው ይበልጥ ተለይቶ ሚታይ የላቀ ልእልና
ከድርሰት በላይ ነሽ የደራሲ አሳር የጥበብ ፈተና።
አክሱም አይወክልሽ ላሊበላ አይሆንም ዕውነትሽን ማሳያ
ዘመን ተሻጋሪ ሕያው ለዝንታለም የሌለሽ አምሳያ
የሰማይ መቀነት ቀስተ ደመና ነው ሰንደቅሽ መታያ።
ሀገሬ ኢትዮጵያ ሆገሬ ኢትዮጵያ!
ስሜት ቢነ ቃቃ ስሜት ቢነሳሳ ሐሳብ ቢሰበሰብ
በረቀቀ ምናብ በጠሊቅ ልቡና ሺ ጊዜ ቢታሰብ
በቅርፅና ይዘት
መቼም አይፈጠር እንዳንቺ ገፀሀገር እንዳንቺ ገፀ ሰብ፡፡
👍2