#ልጩህበት !!
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ታድያ ልጩህ እንጂ ሌላ ምን እላለሁ
የገዛ ጩኸቴ ለኔ እየተሰማ
ንዴቴን
ብሶቴን
ናፍቆቴን ባከስመው
እኔ እየጮህኩኝ እኔ እራሴ ልስማው!!
••••አለ። ጨረስክ አልኩት ።አፍጦ እያየኝ•••
"አዎ ግጥሜን ጨርሻለሁ ግን አንተም ዝም ብለህ አትጩህ እሺ •••
እኔ ከባጃጅህ አልወረድኩ አንተ ግን ከገባሁ ጀምሮ ዝም ብለህ ትጮሀለህ ስማኝ የት እና መቼ እንደምትጮህ ካላወክ ዝም ብትል ይሻላል
ያለበለዚያ ሰሚ ሳይኖር ዝም ብለህ ብትጮህ የራስህ ጩኸት እራስህን ያደነቁርህ እንደሆን እንጂ ምንም አታመጣም !"
ብሎኝ ሲያበቃ ደሞ ወድያው ወደሷ ዞረና
"አንድ ግዜ ብቻ ልጩህ በናትሽ ?"
ሲላት ቀርታኝ የነበረችው እንጥፍጣፊ ትግስት ተሟጠጠች •••
አቦ ባባ ክብር ካልወደደልህ እንዴት እንደምትወርድ ላሳይሀ እንግዲህ ብዬ እጄን ለፀብ እያሰናዳሁ ወርጄ ስጠጋው
"ተው ተው ተው ቦክስ አታባክን ወጣቱ መጀመሪያውኑ እንደዚህ ወንድ ብትሆን ኖሮ አንተ ባጃጅ ውስጥ እስካሁን ማን ይቀመጥ ነበር ፈሪ ፈሪ ነገር ነህ !"
እያለ ከባጃጇ ሲወርድ ልጅቷ በሳቅ ፈነደቀች
ግራ ቀኝ እየተወዛወዘ ትንሽ ከባጃጇ ራቅ እንዳለ ዘወር አለና
"ሞት ይርሳኝ ቻው እሺ የኔ ልጅ ልጅ አልኩ እንዴ አንቺን እንኳን አላደርስም !
ቻው እሺ የኔ ልእልት አንቺን የመሰለች ልጅ ከዚህ አስቀያሚ ሹፌር ጋር በማየቴ ደንግጫለሁ !
ፍችው በናትሽ! " እላት።
"እሺ "አለችው በሳቋ መሀል
"ግን መች ትፈችዋለሽ በናትሽ! እ••• እ ••እ ንገሪኛ?" እያለ ሊመለስ ሲል እኔም እየሳኩ ወደሱ ስጠጋ ፊቱን አዙሮ ከቆምንበት በስተቀኝ መንገድ ዳር ወዳለችው የማትዘጋዋ መጠጥ ቤት አመራ።
ባጃጃን አስነስቼ ከዩንቨርስቲው በቅርብ ርቀት
ጨለማ ውስጥ አቆምኳትና ከመሪው ላይ ተነስቼ እሷ አጠገብ ተቀመጥኩ ። ፊቷ ተቀያየረ።
ካቆምንበት እንቀጥላ አልኳትና
ቅድም የፈለከውን አርገኝ ስትይ ምን ለማለት ፈልገሽ ነበር ?
"በቃ ከፈለክ ልትሰድበኝም ከፈልክ ልታወርደኝም ትችላለህ ሌላ ምንድን ነው?" አለችኝ የጭንቀቷን
ወደ ዩንቨርስቲው ዞሬ ተመለከትኩ አጠገባችን ነው ግቢው ከሩቅ ይታያል ሳቄ መጣ አብራኝ ሳቀች።
ሀይ ስትደርሺ ነው እንዴ ልታወርደኝ ትችላለህ እምትይው? ስላት•••
ጭንቅላቷን ወደ ግራ ሰበቀችና በዝምታ እጇን እያፍተለተለች አይን አይኔን ታየኝ ጀመር
የሆነ ስሜት ተሰማኝ
ታውቂያለሽ ሁለት ወንድሞች አሉኝ ግን እህት የለኝም ቢሆንም እናት አለኝ የማይሆን ቢሆንም እናትም ባይኖረኝ እራሱ አንቺ ላይ የሚጨክን አንጀት የለኝም
ምንም አልደርግሽምም አልሰድብሽምም አላወርድሽምም እሺ መጀመሪያውኑ ብር እንደሌለሽ ብትነግሪኝና በነፃ እንዳደርስሽ ብትጠይቂኝ ለስራ ብወጣም ከሰአቱ አንፃር ላውሬ ጥዬሽ አልሄድም ነበር ።
እያሰብኩ የነበረው ምናልባት መጥፎ ባህሪ ያለው የባጃጅ ሹፌር አጋጥሟት ቢሆን ኖሮስ እያልኩ ነው።
ግን ምን አጋጥሞሽ ነው ማለቴ
በዚህ ሰአት ብቻሽን እዛ ጭፈራ ቤት በር ላይ ለምን ቆምሽ ?ስለራስሽም ብትነግሪኝ ደስ ይለኛል
"አጋጣሚው ከብዙ ነገሮች ጋር የተያያዘ ነው ኬቱ ጋር ልጀምርልህ?
ከፈለግሽው።
"በናትህ አሁን መሽቷል ሞባይሌን ዶርም ጥዬው ወጥቼ ነው ከፈለክ ስልኬን ያዝና ነገ ወይ በሚመችህ ቀን ደውልልኝ አወራሀለሁ!"
እዚሁ ባጃጅ ውስጥ እናድራታለን እንጂ አልፋታሽም አልኳት ኮስተር ብዬ
" እያስገደድከኝ ነው ማለት ነው አለች እሷም በስሱ ከስተር ብላ
ስትስቅም ስትኮሳተርም የሚያምርባት ሴት እሷን አየሁ።
አሁን ከተለያየን ቡሀላ ልታገኝኝ ፍቃደኛ ሁኚ አትሁኝ እርግጠኛ ስላልሆንኩ አሁኑኑ እንድትነግሪኝ እየለመንኩሽ ነው! ከተጫንኩሽ ይቅር ብትነግሪኝ ግን የመጣሽበትን ሂሳብ እንደከፈልሽ እቆጥረዋለሁ አልኳትና አሁንም እኩል ሳቅን።
"ክትክትክትክት ኧረ ባክህ
እሺ ግን ባጭሩ ነው በደንብ እንድትረዳው ገባ ብዬ ብጀምርልህ ይረዝምብኛል?"
አቦ ንገሪኝኛ አታጓጊኝ!።
" እኔ
እኔ
እኔ ማለት እኔ ደሀ ከሚባል ቤተሰብ ነው የተወለድኩት ።
አባቴ አናፂ ነው እናቴ ደግሞ ሽንኩርት ቲማቲም ምናምን ነው ጉሊት ውስጥ የምትቸረችረው
ሁለቱም ፀሀይ ላይ ውለው ፊታቸው ጠቁሮ ከሚያገኙት ገቢ ውስጥ አብዛኛውን እኔን ከሰፈሬ እና ከትምህርት ቤት ጓደኛቼ እኩል ማድረግ ባይችሉ እንኳን ክፍተቱን በመጠኑ አጥብበው ብዙ ሳይሰማኝ እንዳድግ ለማድረግ አውለውታል።
ሳይለብሱ ያለብሱኛል
ለነሱ ርካሽ የተባለውን ጫማ እየተጫሙ ለኔ ውድና ሁለት ሶስት ቅያሪ ጫማ እንዲኖረኝ ለማድረግ ለነሱ የሚያስፈልጉዋቸውን ሁሉ ወደ ጎን ትተዋል !
ሳይደሰቱ እኔን ለማስደሰት የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል!
ቢኮራረፉ እኔ ፊት ይስቃሉ!
ቢያዝኑ እኔ ፊት ደስተኛ ለመምሰል ይሞክራሉ!
በአጠቃላይ ለራሳቸው ሳይኖሩ ለኔ ደክመው ለኔ ኖረው ያስተማሩኝን ቤተሰቦቼን ለማስደሰት የምችለው በትምህርቴ ስጎብዝ ነውና ምንም ነገር ሳያታልለኝ በርትቼ በመማር ወደ ዩንቨርስቲ መግቢያ የሚሆን ውጤት አምጥቼ ባስደሰትኳቸው ማግስት ነበር አባዬ እኔ ወደዚህ ለመምጣት የሚያስፈልገኝን ነገር ለሟሟላት ከበፊቱ በተለየ ሁኔታ ያገኘውን ስራ በሙሉ እየሰራ ገንዘቡን እኔው ጋር ማጠራቀም የጀመረው •••"
አለችና ዝም አለች።
ምነው ቀጥይ እንጂ ስላት
"ስላባዬ ሳወራ ጨነቀኝ !
ትንሽ ዝምታ ተፈጠረ በመሀላችን።
ሲጨንቀኝ ደሞ ምን ትዝ እንዳለኝ ታውቃለህ?"
ምን ትዝ አለሽ ?
አንዴ ልጩህ እሚለው የቅድሙ ሰካራም ።
አንዴ ልጩህ እንዴ?"
ስትለኝ ሁለታችንም ባንድ ግዜ ከነበርንበት ሙድ ወጥተን ከባጃጇ ጣራ በላይ ሳቅን።
በናትሽ ቀጥይልኝ ? አልኳት ሳቄን ስጨርስ። ካሳቁ መልስ ደሞ ባንዴ ፊቷን ቅጭም አርጋ ቀጠለች•••
አባዬ ድካሙና እንቅልፉ ተደራርቦበት ነበር ።
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ •••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_ሶስት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
ታድያ ልጩህ እንጂ ሌላ ምን እላለሁ
የገዛ ጩኸቴ ለኔ እየተሰማ
ንዴቴን
ብሶቴን
ናፍቆቴን ባከስመው
እኔ እየጮህኩኝ እኔ እራሴ ልስማው!!
••••አለ። ጨረስክ አልኩት ።አፍጦ እያየኝ•••
"አዎ ግጥሜን ጨርሻለሁ ግን አንተም ዝም ብለህ አትጩህ እሺ •••
እኔ ከባጃጅህ አልወረድኩ አንተ ግን ከገባሁ ጀምሮ ዝም ብለህ ትጮሀለህ ስማኝ የት እና መቼ እንደምትጮህ ካላወክ ዝም ብትል ይሻላል
ያለበለዚያ ሰሚ ሳይኖር ዝም ብለህ ብትጮህ የራስህ ጩኸት እራስህን ያደነቁርህ እንደሆን እንጂ ምንም አታመጣም !"
ብሎኝ ሲያበቃ ደሞ ወድያው ወደሷ ዞረና
"አንድ ግዜ ብቻ ልጩህ በናትሽ ?"
ሲላት ቀርታኝ የነበረችው እንጥፍጣፊ ትግስት ተሟጠጠች •••
አቦ ባባ ክብር ካልወደደልህ እንዴት እንደምትወርድ ላሳይሀ እንግዲህ ብዬ እጄን ለፀብ እያሰናዳሁ ወርጄ ስጠጋው
"ተው ተው ተው ቦክስ አታባክን ወጣቱ መጀመሪያውኑ እንደዚህ ወንድ ብትሆን ኖሮ አንተ ባጃጅ ውስጥ እስካሁን ማን ይቀመጥ ነበር ፈሪ ፈሪ ነገር ነህ !"
እያለ ከባጃጇ ሲወርድ ልጅቷ በሳቅ ፈነደቀች
ግራ ቀኝ እየተወዛወዘ ትንሽ ከባጃጇ ራቅ እንዳለ ዘወር አለና
"ሞት ይርሳኝ ቻው እሺ የኔ ልጅ ልጅ አልኩ እንዴ አንቺን እንኳን አላደርስም !
ቻው እሺ የኔ ልእልት አንቺን የመሰለች ልጅ ከዚህ አስቀያሚ ሹፌር ጋር በማየቴ ደንግጫለሁ !
ፍችው በናትሽ! " እላት።
"እሺ "አለችው በሳቋ መሀል
"ግን መች ትፈችዋለሽ በናትሽ! እ••• እ ••እ ንገሪኛ?" እያለ ሊመለስ ሲል እኔም እየሳኩ ወደሱ ስጠጋ ፊቱን አዙሮ ከቆምንበት በስተቀኝ መንገድ ዳር ወዳለችው የማትዘጋዋ መጠጥ ቤት አመራ።
ባጃጃን አስነስቼ ከዩንቨርስቲው በቅርብ ርቀት
ጨለማ ውስጥ አቆምኳትና ከመሪው ላይ ተነስቼ እሷ አጠገብ ተቀመጥኩ ። ፊቷ ተቀያየረ።
ካቆምንበት እንቀጥላ አልኳትና
ቅድም የፈለከውን አርገኝ ስትይ ምን ለማለት ፈልገሽ ነበር ?
"በቃ ከፈለክ ልትሰድበኝም ከፈልክ ልታወርደኝም ትችላለህ ሌላ ምንድን ነው?" አለችኝ የጭንቀቷን
ወደ ዩንቨርስቲው ዞሬ ተመለከትኩ አጠገባችን ነው ግቢው ከሩቅ ይታያል ሳቄ መጣ አብራኝ ሳቀች።
ሀይ ስትደርሺ ነው እንዴ ልታወርደኝ ትችላለህ እምትይው? ስላት•••
ጭንቅላቷን ወደ ግራ ሰበቀችና በዝምታ እጇን እያፍተለተለች አይን አይኔን ታየኝ ጀመር
የሆነ ስሜት ተሰማኝ
ታውቂያለሽ ሁለት ወንድሞች አሉኝ ግን እህት የለኝም ቢሆንም እናት አለኝ የማይሆን ቢሆንም እናትም ባይኖረኝ እራሱ አንቺ ላይ የሚጨክን አንጀት የለኝም
ምንም አልደርግሽምም አልሰድብሽምም አላወርድሽምም እሺ መጀመሪያውኑ ብር እንደሌለሽ ብትነግሪኝና በነፃ እንዳደርስሽ ብትጠይቂኝ ለስራ ብወጣም ከሰአቱ አንፃር ላውሬ ጥዬሽ አልሄድም ነበር ።
እያሰብኩ የነበረው ምናልባት መጥፎ ባህሪ ያለው የባጃጅ ሹፌር አጋጥሟት ቢሆን ኖሮስ እያልኩ ነው።
ግን ምን አጋጥሞሽ ነው ማለቴ
በዚህ ሰአት ብቻሽን እዛ ጭፈራ ቤት በር ላይ ለምን ቆምሽ ?ስለራስሽም ብትነግሪኝ ደስ ይለኛል
"አጋጣሚው ከብዙ ነገሮች ጋር የተያያዘ ነው ኬቱ ጋር ልጀምርልህ?
ከፈለግሽው።
"በናትህ አሁን መሽቷል ሞባይሌን ዶርም ጥዬው ወጥቼ ነው ከፈለክ ስልኬን ያዝና ነገ ወይ በሚመችህ ቀን ደውልልኝ አወራሀለሁ!"
እዚሁ ባጃጅ ውስጥ እናድራታለን እንጂ አልፋታሽም አልኳት ኮስተር ብዬ
" እያስገደድከኝ ነው ማለት ነው አለች እሷም በስሱ ከስተር ብላ
ስትስቅም ስትኮሳተርም የሚያምርባት ሴት እሷን አየሁ።
አሁን ከተለያየን ቡሀላ ልታገኝኝ ፍቃደኛ ሁኚ አትሁኝ እርግጠኛ ስላልሆንኩ አሁኑኑ እንድትነግሪኝ እየለመንኩሽ ነው! ከተጫንኩሽ ይቅር ብትነግሪኝ ግን የመጣሽበትን ሂሳብ እንደከፈልሽ እቆጥረዋለሁ አልኳትና አሁንም እኩል ሳቅን።
"ክትክትክትክት ኧረ ባክህ
እሺ ግን ባጭሩ ነው በደንብ እንድትረዳው ገባ ብዬ ብጀምርልህ ይረዝምብኛል?"
አቦ ንገሪኝኛ አታጓጊኝ!።
" እኔ
እኔ
እኔ ማለት እኔ ደሀ ከሚባል ቤተሰብ ነው የተወለድኩት ።
አባቴ አናፂ ነው እናቴ ደግሞ ሽንኩርት ቲማቲም ምናምን ነው ጉሊት ውስጥ የምትቸረችረው
ሁለቱም ፀሀይ ላይ ውለው ፊታቸው ጠቁሮ ከሚያገኙት ገቢ ውስጥ አብዛኛውን እኔን ከሰፈሬ እና ከትምህርት ቤት ጓደኛቼ እኩል ማድረግ ባይችሉ እንኳን ክፍተቱን በመጠኑ አጥብበው ብዙ ሳይሰማኝ እንዳድግ ለማድረግ አውለውታል።
ሳይለብሱ ያለብሱኛል
ለነሱ ርካሽ የተባለውን ጫማ እየተጫሙ ለኔ ውድና ሁለት ሶስት ቅያሪ ጫማ እንዲኖረኝ ለማድረግ ለነሱ የሚያስፈልጉዋቸውን ሁሉ ወደ ጎን ትተዋል !
ሳይደሰቱ እኔን ለማስደሰት የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል!
ቢኮራረፉ እኔ ፊት ይስቃሉ!
ቢያዝኑ እኔ ፊት ደስተኛ ለመምሰል ይሞክራሉ!
በአጠቃላይ ለራሳቸው ሳይኖሩ ለኔ ደክመው ለኔ ኖረው ያስተማሩኝን ቤተሰቦቼን ለማስደሰት የምችለው በትምህርቴ ስጎብዝ ነውና ምንም ነገር ሳያታልለኝ በርትቼ በመማር ወደ ዩንቨርስቲ መግቢያ የሚሆን ውጤት አምጥቼ ባስደሰትኳቸው ማግስት ነበር አባዬ እኔ ወደዚህ ለመምጣት የሚያስፈልገኝን ነገር ለሟሟላት ከበፊቱ በተለየ ሁኔታ ያገኘውን ስራ በሙሉ እየሰራ ገንዘቡን እኔው ጋር ማጠራቀም የጀመረው •••"
አለችና ዝም አለች።
ምነው ቀጥይ እንጂ ስላት
"ስላባዬ ሳወራ ጨነቀኝ !
ትንሽ ዝምታ ተፈጠረ በመሀላችን።
ሲጨንቀኝ ደሞ ምን ትዝ እንዳለኝ ታውቃለህ?"
ምን ትዝ አለሽ ?
አንዴ ልጩህ እሚለው የቅድሙ ሰካራም ።
አንዴ ልጩህ እንዴ?"
ስትለኝ ሁለታችንም ባንድ ግዜ ከነበርንበት ሙድ ወጥተን ከባጃጇ ጣራ በላይ ሳቅን።
በናትሽ ቀጥይልኝ ? አልኳት ሳቄን ስጨርስ። ካሳቁ መልስ ደሞ ባንዴ ፊቷን ቅጭም አርጋ ቀጠለች•••
አባዬ ድካሙና እንቅልፉ ተደራርቦበት ነበር ።
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ •••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2
#ልጩህበት ! !
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
"ስላባዬ ሳወራ ጨነቀኝ !
ትንሽ ዝምታ ተፈጠረ በመሀላችን።
ሲጨንቀኝ ደሞ ምን ትዝ እንዳለኝ ታውቃለህ?"
ምን ትዝ አለሽ ?
አንዴ ልጩህ እሚለው የቅድሙ ሰካራም ።
አንዴ ልጩህ እንዴ?"
ስትለኝ ሁለታችንም ባንድ ግዜ ከነበርንበት ሙድ ወጥተን ከባጃጇ ጣራ በላይ ሳቅን።
በናትሽ ቀጥይልኝ ? አልኳት ሳቄን ስጨርስ። ካሳቁ መልስ ደሞ ባንዴ ፊቷን ቅጭም አርጋ ቀጠለች•••
አባዬ ድካሙና እንቅልፉ ተደራርቦበት ነበር ።
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ •••
••••
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ በሂወቴ እማረሳው መጥፎ አጋጣሚ ተፈጠረ ቀኑ አርብ ነበር አባዬ እንደተለመደው በለሊት ነበር ወደ ስራ የወጣው
ያን ሰሞን የሚሰራበት ቦታ ከኛ ቤት ብዙ ስለማይርቅ እንደነገ ልጀምር ማታ እማዬን በጥዋት እየተነሳሽ ምሳ አትቋጥሪልኝ ቀስ ብለሽ ስሪና አለሜ ታምጣልኝ አላት ስሜ ኤደን ቢሆንም አባ ግን አለሜ የኔአለም እያለ ነው እሚጠራኝ።
ለአራት ቀናት ምሳውን ስራ ቦታ እየወሰድኩለት እስኪበላ እያዋራሁት እምለሳለሁ በአምስተኛው ቀን ጓደኛዬ አርብ እለት ከማዬ ጋር ልብስ ይዥበት የምመጣውን ቦርሳ ለመግዛት አብረን ወጥተን ስለነበር ምሳውን ሳላደርስለት ሰአቱ ሄደብኝ በውስጡ ልጄን ምን አጋጠማት እያለ ሲጨነቅ ነበር ለካ ከቀኑ ሰባት ሰአት ተኩል ላይ ምሳውን ይዤ ከቤት ወጣሁ ከ15 ደቂቃ ቡሀላ ደረስኩ።
ቀና ስል•••
አባዬ በግምት ከመሬት አምስት ሜትር ከፍታ ላይ ተሰቅሎ ስራውን እየሰራ ነው አባ ብዬ ጮክ ብዬ ስጣራ ስቆይበት ጭንቀት ላይ የነበረው አባዬ የኔን የልጁን ድምፅ ድንገት ሲሰማ ደነገጠ መስለኝ ሳይጠነቀቅ እኔን ለማየት የያዘውን ለቆ ዞረ!
ወድያው ከላይ ቁልቁል ሲምዘገዘግ አይኔን ማመን ተሳነኝ በሂወቴ እንደዛን ቀን ደንግጬ አላውቅም ውሃ ሆንኩ ወደ ወደቀው አባቴ መጠጋት ፈርቼ በቆምኩበት ስጮህ ባከባቢው የነበሩ ሰራተኛች ከወደቀበት አንስተው አናቱ ላይ ውሀ ሲያፈሱበት ተመለከትኩ
ተርፏል አባቴ !
ተርፏል አባቴ !
እያልኩ ወደሱ በመሮጥ እያለቀስኩ አንገቱ ላይ ተጠመጠምኩበት።
እግሩና የጎን አጥንቱ ላይ ጉዳት ደረሰበት ያን ቀን አሰሪው ሀኪም ቤት ወስዶ ህክምና ተደረገለት ከዛን ቀን ቡሀላ ግን ዘወር ብሎም አላየውም
ከ አምስት ቀን ቡሀላ እኔ ጋር ያለው ለዩንቨርስቲ ጉዞዬ ብሎ ያጠራቀመው ገንዘብ ለሱ ህክምና እንዳልጠቀምበት ብሎ ሳይሻለው ተሽሎኛል ብሎ ከሀኪም ቤት ወጣና እቤታችን ተኛ
ለሊት ለሊት ሲያቃስት ስለሰማሁት አባ እሺ በለኝ እና በደንብ ታከም እኔ ጋር ባለው ብር ታክመህ ካልዳንክ ወደ ዩንቨርስቲ እንደማልሄድ እወቀው ስለው እሺ አለኝ።
አሳክሜው የተረፈችኝን ይዤ መጣሁ እዚህ ከመጣሁ አራት ወር ሊሞላኝ ነው ግን እስካሁን ስራ አልጀመረም እማዬ በምትሰራው ብቻ ስለሚኖሩ እማን ላለማጨናነቅ ብዬ ምንም ወጪ የለብኝም ብር እንዳትልኪልኝ አልኳት
እዚህ ደግሞ ብዙ ወጭዎች አሉ ኖቶችን(ሀንድ አውቶችን) ኮፒ ከማረግ ጀምሮ ብዙ ነገሮች አሉ በተለይ ሴት ልጅ ከወንድ ልጅ በባሰ ሁኔታ እጇ ላይ ሳንቲም ያስፈልጋታል ሁሉንም ፍላጎቷን ማስቀረት ብትችል የሞድየስን እና የአንዳንድ ነገር ወጪዎቿ ግድ ናቸው።
በዚህ ግቢ ማደሪያ ክፍላችን (ዶርም) ውስጥ በጣም የምቀርባቸው ሁለት ጓደኛች አሉኝ የመጣን ሰሞን ስለሂወታችን ስናወራ የሶስታችንም ቤተሰቦቻች በተቀራራቢ የድህነት ህይወት ውስጥ ያሉ እድሚያችን ፣አለባበሳችን፣ ፍላጎታችን ፣ ችግራችን ባጠቃላይ በተመሳሳይ ህይወት ውስጥ ማለፋችን ነው መሰል ቶሎ ለመቀራረብና እንደህታማቾች ለመተሳሰብ እና ለመተዛዘን ግዜ አልፈጀብንም።
እማንለያይ አንዳችን ላንዳችን የምንጨነቅ ሆንን ከቅባት ጀምሮ የሚያስፈልጉንን አዋጥተን እንገዛለን አንዳችን ያንዳችንን ልብስ ለመልበስ ፍቃድ መጠየቅ አያስፈልገንም የነሱን ባላውቅም እኔ ሁለቱንም በጣም ነው እምወዳቸው ።
ትንሽ እንደቆየን በተለይ አንዲት የሶስተኛ አመት ተማሪ ባጋጣሚ ከአንደኛዋ ጋደኛዬ ጋር ተዋውቋ ዶርማችን መጥታ ከተዋወቀችንና በየቀኑ መምጣት ከጀመረች ቡሀላ ነገሮች በፍጥነት መቀያየር ጀመሩ።
እኔ ልጅቷ የምታወራው ነገር ሁሉ ስለማይጥመኝ ብዙም አልቀርባትም ነበር ።
ከሁለቱ ጋር ግን በጣም ተቀራረበች ጭራሽ ከግቢ ውጪ አምሽተው አንዳንዴም አድረው መምጣት ጀመሩ የት ሄዳችሁ ነው? ስላቸው ከሷ ጋር እንደነበሩ ይነግሩኛል የጓደኝነቴን ትምህርታቸው ላይ እንዱያተኩሩና ከሷ ልጅ ጋር መዞሩን እንዲቀንሱ ብነግራቸውም ጭራሽ ባሰባቸው ። እንደውም እኔም አብሬያቸው ዘና እንድል በተለያየ መንገድ ሊያሳምኑኝ ይሞክሩ ጀመር።
በተዋወቋት ባጭር ግዜ ውስጥ እኔ ለፎቶ ኮፒ ተቸግሬ ፍዳዬን ሳይ እነሱ ልብስና ጫማ በየሳምንቱ መቀያየር ጀመሩ ከኔ ጋር ያላቸው ልዩነት እየሰፋ እየሰፋ መጣ የነበሩት ነገሮች በሙሉ ተለዋወጡ እንኳን ከኔ ጋር ቅባት አዋጥተው ሊገዙ እንኳን ከኔ ጋር ልብስ ሊቀያየሩ የበፊቶቹን ልብሶቻቸውን ከፈለኩ መውሰድ እንደምችል ይነግሩኝ ጀመር።
ቅባት ሻንፖ ሎሽን የመሳሰሉትን ነገሮች ገዝተው ሲሰጡኝና እና ለፎቶ ኮፒ የሚሆነኝን ገንዘብ ስፈልግ እንድጠይቃቸው ሲነግሩኝ ከምልህ በላይ ይሰማኝ ጀመር በቃ በፊት ተሰምቶኝ የማያውቅ የበታችነት ስሜት ተረጋግቼ ማጥናት እስክቸገር ድረስ መጥፎ ሁኔታ ውስጥ ከተተኝ።
በዛ ሁኔታ ውስጥ ሆኜ ደግሞ ያቺ ጓደኛቸው እና እነሱ እነሱን እንድመስል አብሬያቸው እንድውል እና እንዳመሽ ባገኙት አጋጣሚ ይወተውኛል ።
በቅርቡ የመጀመሪያው ሴሚስተር ፈተና ነበርና በየትምህርት አይነቱ ያሉትን ኖቶች ኮፒ ለማድረግ በጣም ሳንቲም ያስፈልገኝ ነበር።
ያቺ ጓደኛቸው ያዘነች መስላ ያንን ወጪ በነሱ በኩል
በመሸፈን በውለታ ከያዘችኝ ቡኋላ
ዶርም መጥታ ፈተና ስንጨርስ አብሬያቸው ወጣ ብዬ ለመዝናናት ፍቃደኛ እንድሆንና ቃል እንድገባላት በነሱ ፊት ጠየቀችኝ ለሶስት ሲያዋክቡኝ ግራ ገባኝ !
ደስ ባይለኝም ያቀደችልኝን ቀድሜ መረዳት አልችልም ነበርና ቃል ገባሁ።
ፈተናው ሊያልቅ አንድ ቀን ሲቀረው ጨነቀኝ
ዛሬ ጥዋት ስድስት ሰአት አከባቢ እነሱ ፈተናው በማለቁ ደስ ሲላቸው እኔን ግን ፍርሀት ፍርሀት አለኝ •••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
፡
፡
#ክፍል_አራት
፡
፡
#ድርሰት_በጥላሁን
"ስላባዬ ሳወራ ጨነቀኝ !
ትንሽ ዝምታ ተፈጠረ በመሀላችን።
ሲጨንቀኝ ደሞ ምን ትዝ እንዳለኝ ታውቃለህ?"
ምን ትዝ አለሽ ?
አንዴ ልጩህ እሚለው የቅድሙ ሰካራም ።
አንዴ ልጩህ እንዴ?"
ስትለኝ ሁለታችንም ባንድ ግዜ ከነበርንበት ሙድ ወጥተን ከባጃጇ ጣራ በላይ ሳቅን።
በናትሽ ቀጥይልኝ ? አልኳት ሳቄን ስጨርስ። ካሳቁ መልስ ደሞ ባንዴ ፊቷን ቅጭም አርጋ ቀጠለች•••
አባዬ ድካሙና እንቅልፉ ተደራርቦበት ነበር ።
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ •••
••••
ልመጣ ሁለት ሳምንት ሲቀረኝ በሂወቴ እማረሳው መጥፎ አጋጣሚ ተፈጠረ ቀኑ አርብ ነበር አባዬ እንደተለመደው በለሊት ነበር ወደ ስራ የወጣው
ያን ሰሞን የሚሰራበት ቦታ ከኛ ቤት ብዙ ስለማይርቅ እንደነገ ልጀምር ማታ እማዬን በጥዋት እየተነሳሽ ምሳ አትቋጥሪልኝ ቀስ ብለሽ ስሪና አለሜ ታምጣልኝ አላት ስሜ ኤደን ቢሆንም አባ ግን አለሜ የኔአለም እያለ ነው እሚጠራኝ።
ለአራት ቀናት ምሳውን ስራ ቦታ እየወሰድኩለት እስኪበላ እያዋራሁት እምለሳለሁ በአምስተኛው ቀን ጓደኛዬ አርብ እለት ከማዬ ጋር ልብስ ይዥበት የምመጣውን ቦርሳ ለመግዛት አብረን ወጥተን ስለነበር ምሳውን ሳላደርስለት ሰአቱ ሄደብኝ በውስጡ ልጄን ምን አጋጠማት እያለ ሲጨነቅ ነበር ለካ ከቀኑ ሰባት ሰአት ተኩል ላይ ምሳውን ይዤ ከቤት ወጣሁ ከ15 ደቂቃ ቡሀላ ደረስኩ።
ቀና ስል•••
አባዬ በግምት ከመሬት አምስት ሜትር ከፍታ ላይ ተሰቅሎ ስራውን እየሰራ ነው አባ ብዬ ጮክ ብዬ ስጣራ ስቆይበት ጭንቀት ላይ የነበረው አባዬ የኔን የልጁን ድምፅ ድንገት ሲሰማ ደነገጠ መስለኝ ሳይጠነቀቅ እኔን ለማየት የያዘውን ለቆ ዞረ!
ወድያው ከላይ ቁልቁል ሲምዘገዘግ አይኔን ማመን ተሳነኝ በሂወቴ እንደዛን ቀን ደንግጬ አላውቅም ውሃ ሆንኩ ወደ ወደቀው አባቴ መጠጋት ፈርቼ በቆምኩበት ስጮህ ባከባቢው የነበሩ ሰራተኛች ከወደቀበት አንስተው አናቱ ላይ ውሀ ሲያፈሱበት ተመለከትኩ
ተርፏል አባቴ !
ተርፏል አባቴ !
እያልኩ ወደሱ በመሮጥ እያለቀስኩ አንገቱ ላይ ተጠመጠምኩበት።
እግሩና የጎን አጥንቱ ላይ ጉዳት ደረሰበት ያን ቀን አሰሪው ሀኪም ቤት ወስዶ ህክምና ተደረገለት ከዛን ቀን ቡሀላ ግን ዘወር ብሎም አላየውም
ከ አምስት ቀን ቡሀላ እኔ ጋር ያለው ለዩንቨርስቲ ጉዞዬ ብሎ ያጠራቀመው ገንዘብ ለሱ ህክምና እንዳልጠቀምበት ብሎ ሳይሻለው ተሽሎኛል ብሎ ከሀኪም ቤት ወጣና እቤታችን ተኛ
ለሊት ለሊት ሲያቃስት ስለሰማሁት አባ እሺ በለኝ እና በደንብ ታከም እኔ ጋር ባለው ብር ታክመህ ካልዳንክ ወደ ዩንቨርስቲ እንደማልሄድ እወቀው ስለው እሺ አለኝ።
አሳክሜው የተረፈችኝን ይዤ መጣሁ እዚህ ከመጣሁ አራት ወር ሊሞላኝ ነው ግን እስካሁን ስራ አልጀመረም እማዬ በምትሰራው ብቻ ስለሚኖሩ እማን ላለማጨናነቅ ብዬ ምንም ወጪ የለብኝም ብር እንዳትልኪልኝ አልኳት
እዚህ ደግሞ ብዙ ወጭዎች አሉ ኖቶችን(ሀንድ አውቶችን) ኮፒ ከማረግ ጀምሮ ብዙ ነገሮች አሉ በተለይ ሴት ልጅ ከወንድ ልጅ በባሰ ሁኔታ እጇ ላይ ሳንቲም ያስፈልጋታል ሁሉንም ፍላጎቷን ማስቀረት ብትችል የሞድየስን እና የአንዳንድ ነገር ወጪዎቿ ግድ ናቸው።
በዚህ ግቢ ማደሪያ ክፍላችን (ዶርም) ውስጥ በጣም የምቀርባቸው ሁለት ጓደኛች አሉኝ የመጣን ሰሞን ስለሂወታችን ስናወራ የሶስታችንም ቤተሰቦቻች በተቀራራቢ የድህነት ህይወት ውስጥ ያሉ እድሚያችን ፣አለባበሳችን፣ ፍላጎታችን ፣ ችግራችን ባጠቃላይ በተመሳሳይ ህይወት ውስጥ ማለፋችን ነው መሰል ቶሎ ለመቀራረብና እንደህታማቾች ለመተሳሰብ እና ለመተዛዘን ግዜ አልፈጀብንም።
እማንለያይ አንዳችን ላንዳችን የምንጨነቅ ሆንን ከቅባት ጀምሮ የሚያስፈልጉንን አዋጥተን እንገዛለን አንዳችን ያንዳችንን ልብስ ለመልበስ ፍቃድ መጠየቅ አያስፈልገንም የነሱን ባላውቅም እኔ ሁለቱንም በጣም ነው እምወዳቸው ።
ትንሽ እንደቆየን በተለይ አንዲት የሶስተኛ አመት ተማሪ ባጋጣሚ ከአንደኛዋ ጋደኛዬ ጋር ተዋውቋ ዶርማችን መጥታ ከተዋወቀችንና በየቀኑ መምጣት ከጀመረች ቡሀላ ነገሮች በፍጥነት መቀያየር ጀመሩ።
እኔ ልጅቷ የምታወራው ነገር ሁሉ ስለማይጥመኝ ብዙም አልቀርባትም ነበር ።
ከሁለቱ ጋር ግን በጣም ተቀራረበች ጭራሽ ከግቢ ውጪ አምሽተው አንዳንዴም አድረው መምጣት ጀመሩ የት ሄዳችሁ ነው? ስላቸው ከሷ ጋር እንደነበሩ ይነግሩኛል የጓደኝነቴን ትምህርታቸው ላይ እንዱያተኩሩና ከሷ ልጅ ጋር መዞሩን እንዲቀንሱ ብነግራቸውም ጭራሽ ባሰባቸው ። እንደውም እኔም አብሬያቸው ዘና እንድል በተለያየ መንገድ ሊያሳምኑኝ ይሞክሩ ጀመር።
በተዋወቋት ባጭር ግዜ ውስጥ እኔ ለፎቶ ኮፒ ተቸግሬ ፍዳዬን ሳይ እነሱ ልብስና ጫማ በየሳምንቱ መቀያየር ጀመሩ ከኔ ጋር ያላቸው ልዩነት እየሰፋ እየሰፋ መጣ የነበሩት ነገሮች በሙሉ ተለዋወጡ እንኳን ከኔ ጋር ቅባት አዋጥተው ሊገዙ እንኳን ከኔ ጋር ልብስ ሊቀያየሩ የበፊቶቹን ልብሶቻቸውን ከፈለኩ መውሰድ እንደምችል ይነግሩኝ ጀመር።
ቅባት ሻንፖ ሎሽን የመሳሰሉትን ነገሮች ገዝተው ሲሰጡኝና እና ለፎቶ ኮፒ የሚሆነኝን ገንዘብ ስፈልግ እንድጠይቃቸው ሲነግሩኝ ከምልህ በላይ ይሰማኝ ጀመር በቃ በፊት ተሰምቶኝ የማያውቅ የበታችነት ስሜት ተረጋግቼ ማጥናት እስክቸገር ድረስ መጥፎ ሁኔታ ውስጥ ከተተኝ።
በዛ ሁኔታ ውስጥ ሆኜ ደግሞ ያቺ ጓደኛቸው እና እነሱ እነሱን እንድመስል አብሬያቸው እንድውል እና እንዳመሽ ባገኙት አጋጣሚ ይወተውኛል ።
በቅርቡ የመጀመሪያው ሴሚስተር ፈተና ነበርና በየትምህርት አይነቱ ያሉትን ኖቶች ኮፒ ለማድረግ በጣም ሳንቲም ያስፈልገኝ ነበር።
ያቺ ጓደኛቸው ያዘነች መስላ ያንን ወጪ በነሱ በኩል
በመሸፈን በውለታ ከያዘችኝ ቡኋላ
ዶርም መጥታ ፈተና ስንጨርስ አብሬያቸው ወጣ ብዬ ለመዝናናት ፍቃደኛ እንድሆንና ቃል እንድገባላት በነሱ ፊት ጠየቀችኝ ለሶስት ሲያዋክቡኝ ግራ ገባኝ !
ደስ ባይለኝም ያቀደችልኝን ቀድሜ መረዳት አልችልም ነበርና ቃል ገባሁ።
ፈተናው ሊያልቅ አንድ ቀን ሲቀረው ጨነቀኝ
ዛሬ ጥዋት ስድስት ሰአት አከባቢ እነሱ ፈተናው በማለቁ ደስ ሲላቸው እኔን ግን ፍርሀት ፍርሀት አለኝ •••
💫ይቀጥላል💫
ለአስተያየቶ @atronosebot ን ይጠቀሙ
ለወዳጆ #Share እያደረጉ
👍2