#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....መያዣ መጨበጫ በሌለው ቋጥኝ ላይ ተንጠልጥያለሁ፡፡ የሙጥኝ ብዬ የተጣበቅሁት ድንጋይ ቅቤ እንደተቀባ አሎሎ እያሙለጨለጨ ያሰቃየኛል፡፡ ነፍስና ስጋዬ በጭንቀት ተወጥረው
ይሟገታሉ። ቀና ብዬ ተመለከትኩ፡፡ ወደ ተራራው አናት ለመውጣት የማደርገው ጉዞ ሊደረስበት ይቅርና፤ ከቶም የማይታሰብ ሆኖ አገኘሁት..እንደ ብረት ምጣድ ክብ ሆኖ፤ በአናቴ ላይ ሊወድቅ የተዘጋጀ የሚመስል፤ ግዙፍ አለታማ ድንጋይ አየሁ፡፡ የመሹለኪያ አማራጩን
በፍርሃት ተውጬ አማተርኩ፡፡ አሞራ አይደለሁ በክንፌ አልበር ነገር
ሰው መሆኔን የጠላሁት የዚያን ጊዜ ነው፡፡
ከዚህ በላይ ሽቅብ የመውጣቱ ጉዳይ ተስፋ አስቆራጭ ሆነብኝ::በመጣሁበት መንገድ ለመመለስ ፈለግሁ፡፡ ያለኝ የመጨረሻው አማራጭ እሱ ብቻ ነበር፡፡ ምን ያደርጋል? በወጣሁበት መንገድ የመውረድ ምኞቴም እንደ በረዶ በውስጤ የቀዘቀዘው ጎንበስ ብዬ ቁልቁል ስለመከት ነው፡፡ እንዴት አድርጌ፤ እንደምንስ ብርታቱንና ኃይሉን አግኝቼ፤ የዚያን ያህል ሽቅብ ልወጣ እንደቻልኩ ሳስበው፤ ለራሴ ደነቀኝ፡፡
ማርታዬ፤ የኔዋ ውብ ማርታ፤ ዐይኖቿ እንደንጋት ኮከብ የሚያበሩት ማርታ፤ ከበረዶ የሚነፃፀሩ ውብ ነጫጭ ጥርሶቿ ልብን የሚፈለቅቁት የኔዋ ቆንጆ ፤ በእኒያ አለንጋ መሳይ ጣቶቿ ስትደባብሰኝ
ቀለበቷን ለመሆን የሚያስመኘኝ ፍቅርኛዬ ነበረች፤ ኃይሉን በውስጤ የፈጠረችው::
እነዚያ ውብ ከናፍሮቿ የግማሽ ጨረቃን ቅርጽ ይዘው ፈገግ ስትል፤ ልቤ ያለመወርወርያ ገርበብ እንዳለ መዝጊያ፧ ብርግድ የሚልላት ማርታዬ ነበረች ኃይሉንና ብርታቱን ሰጥታ እዚያ ቋጥኝ ላይ በቅዠት ያስወጣችኝ፡፡ የዛሬው አዳሬን አያድርግብኝና፤ ለወትሮው መንፈሴን በሚያስደስት በልዩ ምናባዊ ዓለም ውስጥ የሚያስዋኘኝ ጣፋጭ መዓዛዋ አሁንም ድረስ ያውደኛል፡፡ እያንዳንዳቸው ጥቃቅን ህዋሳቶቼ ከፍቅር
ድርና ማግ እንደተሰሩ ሁሉ፤ መላ አካላዊ ተፈጥሮዬም ወደር የማይገኝለት የማርታዬ የፍቅር ጥልፍና የሽመና ጥበብ ውጤት ሆኖ ይሰማኛል። ጣፋጭ አንደበቷ፣ ዜማዋ፣ ለዛዋ ...ቃናዋ ... ዛሬም ህያው
ነው ለኔ፡፡
ፍቅር የህይወት ቅመም መሆኑን ከማንም ባላነሰ የተረዳሁ ይመስለኛል፡፡ በእነዚያ
ባልታደልኩባቸው ጊዜያቶች ውስጥ
የህይወትን ለዛ ቢስ ጣዕም እስከሚበቃኝ ድረስ አጣጥሜዋለሁ። የህይወቴ ቅመም በድንገት ስትለየኝ ህይወቴ ባዶ ሆነች፡፡ አዎን ጭውው... ያለ መጋዘን በውስጡ ወደል ወደል አይጦች የሚሯሯጡበት
መጋዘን... በኔም ባዶ ህይወት ውስጥ ጭንቀትና ብስጭት እንደልባቸው ይሯሯጡበታል እሷን ባስታወስኩኝ ቁጥር አካሌ እሳት ውስጥ እንደወደቀ ሙዳ ሥጋ ጭብጥ ኩርምት እርር ድብን ይላል፡፡
ፍቅር የራስ መውደድ ነፀብራቅ ነው የሚሉ ካሉ ተሳስተዋል፡፡እኔ እሷን የማያት ከራሴ አስበልጬ ነው። እራሴንም በሷ ውስጥ አልወደድኩም፡፡ እንደዚህ ዓይነቶቹ በፍቅር አበድን! አንቺ ከሌለሽ፤ አንተ ከሌለህ ፤ እየተባባሉ ሲሸነጋገሉ ከቆዩ በኋላ፤ እንደኛው በአጋጣሚ ከተለየ
በማግስቱ ሁሉንም ነገር እንዳልነበረ ረስተውት፤ ከአዲስ ፍቅረኛ ጋር አዲስ ዓለም ለሚቀጩት ወረተኞች ሊሆን ይችላል ፡፡ በገቡት ቃል ኪዳን ፀንተው፤ በመንፈስ አብረው ቆይተው፤ እስከ ወዲያኛው የአካል ግብአተ መሬት ድረስ ፍቅረኞቻቸውን የሚከተሉ መኖራቸውን አልዘነጋውም።
ማርታዬ ለኔ በውስጤ በቅላ፤ አድጋና ጎምርታ ለፍሬ የበቃች የህይወቴ መሠረት ነች:: ፍቅራችን በድቡሽት ላይ የተገነባ ቤት ዓይነት አልነበረም፡፡ ሲቀር የሚቀርም አይደለም፡፡ በልቤ ውስጥ ተተክላ ሥሮቿን ከራስ ጠጉሬ እስከ እግር ጥፍሬ ዘርግታ አድጋና አብባ የምትገኘው
ማርታ ፍቅሬን በቀላሉ ከልቤ ውስጥ ነቅዬ ልጥላት አልቻልኩም።
ከእንግዲህ በኋላ ማርታን ከኔ ልብ ውስጥ ነቅሎ ከማውጣት ይልቅ ነፍሴን ከህያው አካሌ ውስጥ ነቅሎ ማስወጣቱ ይቀላል። ማርታ ከአቅሜ በላይ በቤተሰብ ተፅዕኖ ዐይኖቿ እንደ ጅረት ውሃ ያለማቋረጥ እምባቸውን እየረጩ ብትለየኝም በሷ አልፈረድኩባትም።
እሷ እኮ ለኔ ልዩ ሰው ነበረች፡፡ ልዩ የምትሆንባቸው ብዙ ምክንያቶች አሉኝ፡፡ ከህይወት ታሪኬ አጀማመርና ሂደት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው:: የማርትዬ እንባ አሁን ድረስ ሲፈስ ይታየኛል፡፡ ከዚያም
በኋላ ሰው አትሆንም። በሀዘን የቆሰለው ልቧ በቀላሉ የሚድን አይሆንም፡፡ ህመሟ ጠልቆ ይጠዘጥዘኛል፡፡ እንባዋ እንደ እንፋሎት ያቃጥለኛል፡፡ ለምን ትሉኝ ይሆናል፡፡
“ይዘኸኝ ጥፋ ሲራኬ እንሂድ... እንሽሽ” እያለች ፍርሀቷን ስትገልጽልኝ ችላ እያልኳት፤ እንደፈራችው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተለያይተን
በመቅረታችን ነው፡፡በደለኛነት ማቆሚያ ወደሌለው የአድማስ ጫፍ ያስሮጠኛል።
እንደጉም ወደማይጨበጥ ዓለም ይወሰደኛል። ወደማልደርስበት አዲስ
ዓለም... እሮጣለሁ፡፡ ፀፀት አእምሮዬን ይገዘግዘዋል። ከእንባ ጭጋግ ባሻገር እጆች ይውለበለቡልኛል፡፡ ነጫጭ ጥርሶች እንደተገሸለጠ የመስኖ በቆሎ እሸት ተውበው ልቤን ያማልሉታል። የብር ጉልላት የመሰሉ ዓይኖች እየተንከባለሉ ሆዴን ያባቡታል። ልደርስባቸው እሮጣለሁ::በጣም እሮጣለሁ፡፡ መቆሚያ የሌለው መድረሻ የሌለው ...የማይጨበጥ ከንቱ ሩጫ....
በድን አይደለሁ ትኩስ ደም በውስጤ ይዘዋወራል። ከአጥንትና ከጅማት የተዋቀረው አካሌ ለኔነቴ መገለጫ ብቸኛው ህያው ምስክር ቢሆንም ውስጤ ግን በህልም ዓለም የሚመራ ዓይነት ሆኗል። አስባለሁ፣አሸታለሁ፣ አዳምጣለሁ፣ እቀምሳለሁ፣ በስሜት ህዋሳቶቼ የማሸታት ቆንጂዬዋን ውብ ጠረን ያላት ማርታዬን ነው፡፡ የዚህችን
ማለቂያና ማብቂያ፤ የሌላት ብልጭልጭ ዓለም ቅጭልጭልታና ጩኸት የማዳመጫ ጆሮ የለኝም፡፡ ለጆሮ ሳይሆን ለልብ የሚሰማ ጣፋጭ ድምጽ
በውስጤ ያንሾካሹካል ::
ሰመመን ወስዶ ዳር በሌለው ሰፊና ውብ ዓለም ውስጥ ያዝናናኛል፡፡ ከሳሽና ተከሳሽ በዳይና ተበዳይ፣ አባራሪና ተባራሪ፣ አጥፊና ጠፊ፣ ወደሌለበት ወደ አንድ ልዩ ዓለም... አዳምጣለሁ፡፡ ኮሽታ አይሰማም፡፡ ህይወት ፀጥ እረጭ ብላለች፡፡ ሁሉም በሰላም የራሱን
ህይወት ይመራል፡፡ በአዲሱ ዓለም፡፡ ያለረብሻ፣ ያለስቃይ፣ ያለረሀብ ያለሀዘን፣ ያለከሳሽ ተከሳሽ፣ ያለተቃራኒ በአንድ አቅጣጫ ብቻ ... ነጣቂና ተነጣቂ በሌለበት በአዲሱ ዓለም... ድህነት ሀብታምነት በሌለበት ውብ ዓለም ህይወት ትጓዛለች፡፡
ዐይኖቼ ፈጠዋል ቁምነገሩ ዐይን ከሆነ እኔም ማለፊያ ትላልቅ ዐይኖች ነበሩኝ፡፡ ከሰው ልጅ ውጫዊ ባህሪ በስተጀርባ የአውሬነት ፀባዩን ማየት የማይችሉ ዐይኖች። በጥርጣሬ ያልተሞሉ ፈዛዛ ዐይኖች፡፡ እንደ ነብር ዐይኖች እየተንቀዠቀዡ አካባቢያቸውን በጥርጣሬ የማይቃኙ ዐይኖች፡፡
ሻምበል ብሩክ መጽሐፉን ከደነና አርዕስቱን ተመለከተው፡፡ እንደገና ጀርባውን ገልብጦ የደራሲውን ፎቶግራፍ በጥንቃቄ አየው።እንደገናም የራሱን ህይወት በመጽሀፉ ታሪክ ውስጥ አየው። በዕድሏን በማርታ፤ ውስጥ ሲራክን ደግሞ ዐራሱ ውስጥ፡፡ የራሱ የህይወት ታሪክ ቅንጭብጭብታ በድርሰቱ ውስጥ ተጠቃቅሶ ስላገኘው ያለዕረፍት አንብቦ ለመጨረስ ጉጉት አደረበት። የማርታ መጨረሻዋ ናፈቀው፡፡ የባለታሪኩ የሲራክ የህይወት አቅጣጫ ወዴት እንደሚያመራ ለማወቅ ልቡ ተንጠለጠለች...
ዐይኖቹ እንባ እንደቋጠሩ በዕድሏን አሰባት፡፡ የልጅነት ፍቅራቸው ታወሰው፡፡ የአደፍርስ ምስል ከፊቱ ድቅን አለ። ፍቅሩን የነጠቀው ነጣቂ፡፡በዚህም ምክንያት ለረጅም ጊዜ ስሜቱ ቆስሏል፡፡ ልቡ ደምቷል። ፍቅርን ሸሽቷት ኖሯል፡፡ ፍቅር ግን እሱ ሲሸሻትም እሷ አልሽሸችውም። ይኸውም እንደ አዲስ መንፈሱን የሚንጥ፤ የተቀበረ ስሜቱን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....መያዣ መጨበጫ በሌለው ቋጥኝ ላይ ተንጠልጥያለሁ፡፡ የሙጥኝ ብዬ የተጣበቅሁት ድንጋይ ቅቤ እንደተቀባ አሎሎ እያሙለጨለጨ ያሰቃየኛል፡፡ ነፍስና ስጋዬ በጭንቀት ተወጥረው
ይሟገታሉ። ቀና ብዬ ተመለከትኩ፡፡ ወደ ተራራው አናት ለመውጣት የማደርገው ጉዞ ሊደረስበት ይቅርና፤ ከቶም የማይታሰብ ሆኖ አገኘሁት..እንደ ብረት ምጣድ ክብ ሆኖ፤ በአናቴ ላይ ሊወድቅ የተዘጋጀ የሚመስል፤ ግዙፍ አለታማ ድንጋይ አየሁ፡፡ የመሹለኪያ አማራጩን
በፍርሃት ተውጬ አማተርኩ፡፡ አሞራ አይደለሁ በክንፌ አልበር ነገር
ሰው መሆኔን የጠላሁት የዚያን ጊዜ ነው፡፡
ከዚህ በላይ ሽቅብ የመውጣቱ ጉዳይ ተስፋ አስቆራጭ ሆነብኝ::በመጣሁበት መንገድ ለመመለስ ፈለግሁ፡፡ ያለኝ የመጨረሻው አማራጭ እሱ ብቻ ነበር፡፡ ምን ያደርጋል? በወጣሁበት መንገድ የመውረድ ምኞቴም እንደ በረዶ በውስጤ የቀዘቀዘው ጎንበስ ብዬ ቁልቁል ስለመከት ነው፡፡ እንዴት አድርጌ፤ እንደምንስ ብርታቱንና ኃይሉን አግኝቼ፤ የዚያን ያህል ሽቅብ ልወጣ እንደቻልኩ ሳስበው፤ ለራሴ ደነቀኝ፡፡
ማርታዬ፤ የኔዋ ውብ ማርታ፤ ዐይኖቿ እንደንጋት ኮከብ የሚያበሩት ማርታ፤ ከበረዶ የሚነፃፀሩ ውብ ነጫጭ ጥርሶቿ ልብን የሚፈለቅቁት የኔዋ ቆንጆ ፤ በእኒያ አለንጋ መሳይ ጣቶቿ ስትደባብሰኝ
ቀለበቷን ለመሆን የሚያስመኘኝ ፍቅርኛዬ ነበረች፤ ኃይሉን በውስጤ የፈጠረችው::
እነዚያ ውብ ከናፍሮቿ የግማሽ ጨረቃን ቅርጽ ይዘው ፈገግ ስትል፤ ልቤ ያለመወርወርያ ገርበብ እንዳለ መዝጊያ፧ ብርግድ የሚልላት ማርታዬ ነበረች ኃይሉንና ብርታቱን ሰጥታ እዚያ ቋጥኝ ላይ በቅዠት ያስወጣችኝ፡፡ የዛሬው አዳሬን አያድርግብኝና፤ ለወትሮው መንፈሴን በሚያስደስት በልዩ ምናባዊ ዓለም ውስጥ የሚያስዋኘኝ ጣፋጭ መዓዛዋ አሁንም ድረስ ያውደኛል፡፡ እያንዳንዳቸው ጥቃቅን ህዋሳቶቼ ከፍቅር
ድርና ማግ እንደተሰሩ ሁሉ፤ መላ አካላዊ ተፈጥሮዬም ወደር የማይገኝለት የማርታዬ የፍቅር ጥልፍና የሽመና ጥበብ ውጤት ሆኖ ይሰማኛል። ጣፋጭ አንደበቷ፣ ዜማዋ፣ ለዛዋ ...ቃናዋ ... ዛሬም ህያው
ነው ለኔ፡፡
ፍቅር የህይወት ቅመም መሆኑን ከማንም ባላነሰ የተረዳሁ ይመስለኛል፡፡ በእነዚያ
ባልታደልኩባቸው ጊዜያቶች ውስጥ
የህይወትን ለዛ ቢስ ጣዕም እስከሚበቃኝ ድረስ አጣጥሜዋለሁ። የህይወቴ ቅመም በድንገት ስትለየኝ ህይወቴ ባዶ ሆነች፡፡ አዎን ጭውው... ያለ መጋዘን በውስጡ ወደል ወደል አይጦች የሚሯሯጡበት
መጋዘን... በኔም ባዶ ህይወት ውስጥ ጭንቀትና ብስጭት እንደልባቸው ይሯሯጡበታል እሷን ባስታወስኩኝ ቁጥር አካሌ እሳት ውስጥ እንደወደቀ ሙዳ ሥጋ ጭብጥ ኩርምት እርር ድብን ይላል፡፡
ፍቅር የራስ መውደድ ነፀብራቅ ነው የሚሉ ካሉ ተሳስተዋል፡፡እኔ እሷን የማያት ከራሴ አስበልጬ ነው። እራሴንም በሷ ውስጥ አልወደድኩም፡፡ እንደዚህ ዓይነቶቹ በፍቅር አበድን! አንቺ ከሌለሽ፤ አንተ ከሌለህ ፤ እየተባባሉ ሲሸነጋገሉ ከቆዩ በኋላ፤ እንደኛው በአጋጣሚ ከተለየ
በማግስቱ ሁሉንም ነገር እንዳልነበረ ረስተውት፤ ከአዲስ ፍቅረኛ ጋር አዲስ ዓለም ለሚቀጩት ወረተኞች ሊሆን ይችላል ፡፡ በገቡት ቃል ኪዳን ፀንተው፤ በመንፈስ አብረው ቆይተው፤ እስከ ወዲያኛው የአካል ግብአተ መሬት ድረስ ፍቅረኞቻቸውን የሚከተሉ መኖራቸውን አልዘነጋውም።
ማርታዬ ለኔ በውስጤ በቅላ፤ አድጋና ጎምርታ ለፍሬ የበቃች የህይወቴ መሠረት ነች:: ፍቅራችን በድቡሽት ላይ የተገነባ ቤት ዓይነት አልነበረም፡፡ ሲቀር የሚቀርም አይደለም፡፡ በልቤ ውስጥ ተተክላ ሥሮቿን ከራስ ጠጉሬ እስከ እግር ጥፍሬ ዘርግታ አድጋና አብባ የምትገኘው
ማርታ ፍቅሬን በቀላሉ ከልቤ ውስጥ ነቅዬ ልጥላት አልቻልኩም።
ከእንግዲህ በኋላ ማርታን ከኔ ልብ ውስጥ ነቅሎ ከማውጣት ይልቅ ነፍሴን ከህያው አካሌ ውስጥ ነቅሎ ማስወጣቱ ይቀላል። ማርታ ከአቅሜ በላይ በቤተሰብ ተፅዕኖ ዐይኖቿ እንደ ጅረት ውሃ ያለማቋረጥ እምባቸውን እየረጩ ብትለየኝም በሷ አልፈረድኩባትም።
እሷ እኮ ለኔ ልዩ ሰው ነበረች፡፡ ልዩ የምትሆንባቸው ብዙ ምክንያቶች አሉኝ፡፡ ከህይወት ታሪኬ አጀማመርና ሂደት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው:: የማርትዬ እንባ አሁን ድረስ ሲፈስ ይታየኛል፡፡ ከዚያም
በኋላ ሰው አትሆንም። በሀዘን የቆሰለው ልቧ በቀላሉ የሚድን አይሆንም፡፡ ህመሟ ጠልቆ ይጠዘጥዘኛል፡፡ እንባዋ እንደ እንፋሎት ያቃጥለኛል፡፡ ለምን ትሉኝ ይሆናል፡፡
“ይዘኸኝ ጥፋ ሲራኬ እንሂድ... እንሽሽ” እያለች ፍርሀቷን ስትገልጽልኝ ችላ እያልኳት፤ እንደፈራችው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተለያይተን
በመቅረታችን ነው፡፡በደለኛነት ማቆሚያ ወደሌለው የአድማስ ጫፍ ያስሮጠኛል።
እንደጉም ወደማይጨበጥ ዓለም ይወሰደኛል። ወደማልደርስበት አዲስ
ዓለም... እሮጣለሁ፡፡ ፀፀት አእምሮዬን ይገዘግዘዋል። ከእንባ ጭጋግ ባሻገር እጆች ይውለበለቡልኛል፡፡ ነጫጭ ጥርሶች እንደተገሸለጠ የመስኖ በቆሎ እሸት ተውበው ልቤን ያማልሉታል። የብር ጉልላት የመሰሉ ዓይኖች እየተንከባለሉ ሆዴን ያባቡታል። ልደርስባቸው እሮጣለሁ::በጣም እሮጣለሁ፡፡ መቆሚያ የሌለው መድረሻ የሌለው ...የማይጨበጥ ከንቱ ሩጫ....
በድን አይደለሁ ትኩስ ደም በውስጤ ይዘዋወራል። ከአጥንትና ከጅማት የተዋቀረው አካሌ ለኔነቴ መገለጫ ብቸኛው ህያው ምስክር ቢሆንም ውስጤ ግን በህልም ዓለም የሚመራ ዓይነት ሆኗል። አስባለሁ፣አሸታለሁ፣ አዳምጣለሁ፣ እቀምሳለሁ፣ በስሜት ህዋሳቶቼ የማሸታት ቆንጂዬዋን ውብ ጠረን ያላት ማርታዬን ነው፡፡ የዚህችን
ማለቂያና ማብቂያ፤ የሌላት ብልጭልጭ ዓለም ቅጭልጭልታና ጩኸት የማዳመጫ ጆሮ የለኝም፡፡ ለጆሮ ሳይሆን ለልብ የሚሰማ ጣፋጭ ድምጽ
በውስጤ ያንሾካሹካል ::
ሰመመን ወስዶ ዳር በሌለው ሰፊና ውብ ዓለም ውስጥ ያዝናናኛል፡፡ ከሳሽና ተከሳሽ በዳይና ተበዳይ፣ አባራሪና ተባራሪ፣ አጥፊና ጠፊ፣ ወደሌለበት ወደ አንድ ልዩ ዓለም... አዳምጣለሁ፡፡ ኮሽታ አይሰማም፡፡ ህይወት ፀጥ እረጭ ብላለች፡፡ ሁሉም በሰላም የራሱን
ህይወት ይመራል፡፡ በአዲሱ ዓለም፡፡ ያለረብሻ፣ ያለስቃይ፣ ያለረሀብ ያለሀዘን፣ ያለከሳሽ ተከሳሽ፣ ያለተቃራኒ በአንድ አቅጣጫ ብቻ ... ነጣቂና ተነጣቂ በሌለበት በአዲሱ ዓለም... ድህነት ሀብታምነት በሌለበት ውብ ዓለም ህይወት ትጓዛለች፡፡
ዐይኖቼ ፈጠዋል ቁምነገሩ ዐይን ከሆነ እኔም ማለፊያ ትላልቅ ዐይኖች ነበሩኝ፡፡ ከሰው ልጅ ውጫዊ ባህሪ በስተጀርባ የአውሬነት ፀባዩን ማየት የማይችሉ ዐይኖች። በጥርጣሬ ያልተሞሉ ፈዛዛ ዐይኖች፡፡ እንደ ነብር ዐይኖች እየተንቀዠቀዡ አካባቢያቸውን በጥርጣሬ የማይቃኙ ዐይኖች፡፡
ሻምበል ብሩክ መጽሐፉን ከደነና አርዕስቱን ተመለከተው፡፡ እንደገና ጀርባውን ገልብጦ የደራሲውን ፎቶግራፍ በጥንቃቄ አየው።እንደገናም የራሱን ህይወት በመጽሀፉ ታሪክ ውስጥ አየው። በዕድሏን በማርታ፤ ውስጥ ሲራክን ደግሞ ዐራሱ ውስጥ፡፡ የራሱ የህይወት ታሪክ ቅንጭብጭብታ በድርሰቱ ውስጥ ተጠቃቅሶ ስላገኘው ያለዕረፍት አንብቦ ለመጨረስ ጉጉት አደረበት። የማርታ መጨረሻዋ ናፈቀው፡፡ የባለታሪኩ የሲራክ የህይወት አቅጣጫ ወዴት እንደሚያመራ ለማወቅ ልቡ ተንጠለጠለች...
ዐይኖቹ እንባ እንደቋጠሩ በዕድሏን አሰባት፡፡ የልጅነት ፍቅራቸው ታወሰው፡፡ የአደፍርስ ምስል ከፊቱ ድቅን አለ። ፍቅሩን የነጠቀው ነጣቂ፡፡በዚህም ምክንያት ለረጅም ጊዜ ስሜቱ ቆስሏል፡፡ ልቡ ደምቷል። ፍቅርን ሸሽቷት ኖሯል፡፡ ፍቅር ግን እሱ ሲሸሻትም እሷ አልሽሸችውም። ይኸውም እንደ አዲስ መንፈሱን የሚንጥ፤ የተቀበረ ስሜቱን
👍3
#ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
ጊዜ መደፊት አይገፈትርም።ጊዜ ለሰው ጭንቀትም ሆነ ደስታ ደንታ የለውም።
የራሱን ሥርዓት ጠብቆ የሚጓዘው፤ያለፈ ጊዜ አይመለስም ፤የወደፊቱ ደግሞ እንደ
ፈለግጉት ፈጥኖ አይመጣም። ሰው በጊዜ ቁጥጥር ሥር ነው እንጂ ጊዜ በሰው ቁጥጥር ስር አይደሉም ሰዓት ሰው ሠራሽ ነገር ነው ፤ ሞላውን በማዞር ካለበት ሰዓት ወይም ደቂቃ ማስቀደም ይቻላል ። የቀን መቁጠሪያም ሰው ሠራሽ
ነገር ነው ፤አንዱን ወር አልፎ ሌላውን ወር ማየት ይቻላል ።ቀንን ገፍቶ ማስመሸት፣ ወይም ምሽት ጎፍቶ ማንጋት ግን
የማይቻል ነው ።
አቤል ቢቸግረው እንዲህ አይነት የጊዜ ምርምር ውስጥ ገባ ። ችግሩ ነው ምርምሩን የጋበዘው ቀኑ አልመሽልህ "
ሌሊቱ አልነጋልህ እያለው ተቸገረ ለሌላው ተማሪ የዕረፍት ጊዜ ለእሱ ግን የመጨረሻው ደረጃ የጭንቀት ጊዜ
ሆኖበታል ። ቀንም ይተኛል ፡ ማታም ይታኛል ። ነገር ግን እንቅልፍ አይወስደውም ። እንዲሁ አልጋው ላይ እየተገላበጠ በሐሳብ መብከንከን ሆነ ። ጊዚ ከመቼውም ይልቅ የኋሊት እየተጎተተ የሚያቃስት መስለው ።
ሳምሶን ለዕረፍቱ ወደ ቤቱ ስለ ሔደ መኝታ ክፍላቸው ውስጥ የቀሩት አቤል ፡ እስክንድርና "ድብርት ” ብቻ ነበሩ ። “ ድብርት ” ፈተና ካለቀ በኋላ ያሳየው ለውጥ ቢኖር አልጋ ማንጠፉ ብቻ ነው ። በተረፈ እንደ ጥንቱ “ድብርት ጥናቱም ቢቀር ያው አልጋውን በጋቢ ጋርዶ በራሱ ሕልም ውስጥ መኖሩን አልተወም ። ወደ ውጭ ቢወጣ ብቻውን ነው ።
እስክንድር የዕረፍት ጊዜ ጓደኛው መጽሐፍ ነው ።የአማርኛና የእንግሊዝኛ ልብወለድ መጽሐፎችን እየተዋሰ
ሲያነብ ስለሚውል፥ ቀኑ በፍጥነት ነው የሚገሰግስለት ማንበብ ስልቸት ሲለው፡ወደ መዝናኛው ክበብ እየሔደ ቼዝ
ይጫወታል ። መቼም ከሱ ቦታ ሰው ቢጠፋ ሚስተር ሆርስ አይጠፋም ።
እስክንድር በዚህ ሁኔታ የዕረፍቱን ጊዜ ቢያሳልፍም ከአቤል ጋር አብሮ መጨነቁ አልቀረለትም ። ዐቅሙ በሚፈቅደው መጠን አቤልን ለማዝናናት የማያደርገው ሙከራ የለም ። ከአነበባቸው መጽሐፎች ውስጥ ጥሩ የሚላቸውን መርጦ ይሰጠዋል ። አቤል ግን ነጻ ኣዕምሮ ስለሌለው፥ አንዱንም ከነጣዕሙ አንብቦት አያውቅም ። ጀምሮ ሳይጨርሰው ይቀራል ። ወይም በግል ሐሳቡ ውስጥ እየዋዠቀ ገጹን
በመቁጠር ብቻ ይጨርሰዋል ። እስክንድር ወደ ቼዝ መጫወቻው ቦታ ሲሔድ አቤል አብሮት እንዲሔድ ለማድረግ ቢሞክርም እሺ አላለውም ፡ ከሚስተር ሆርስ ጋር ከተጣላ ወዲህ የመዝናኛ ክበቡን ረግጦት አያውቅም ።
አቤል ወደ ውጭ ብቅ እያለ ከሰዎች ቢቀላቀል ፡ ጊዜውን መዝናኛ ቦታዎች እየሔደ ቢያሳልፍና በአንዳንድ እን
ቅስቃሴዎች ቢሳተፍ፡ ጭንቀቱ እንደሚቀልለት እስክንድር
ቢረዳም ፡ ይህን ለማድረግ ሁኔታዎች አልተመቻቹለትም አብዛኛው መዝናኛ ገንዘብ ይጠይቃል ። ይህን ማሟላት
አይችሉም ። ገንዘብ በማይጠይቅበት መዝናኛ ቦታ ለመዋል ደግሞ የአቤል ሙሉ ፈቃደኝነት አይገኝም ። ሌላ ቀርቶ
ከእስክንድር ጋር ከሚያወራበት ጊዜ ይልቅ፡ ብቻውን ተደብሮ ውስጥ ውስጡን ነገር ሲያብሰለስል የሚውልበት ጊዜ
ይበልጣል ።
ትዕግሥት በተለያየ መልክ በሕልሙ እየመጣች ትታየዋለች ። አንዴ ይጣላሉ ፤አንዴ ጥላው በመሔዷ የተሰማውን ቅሬታ ይገልጽላታል ፤ አንዳንዴ ደግሞ ደብረ ዘይት ድረስ ሔዶ ሲገናኛት ያድራል ቀን ያሰበውን ማታ በሕልሙ ይደግመዋል አንዳንዴ በቅዠት ይወራጫል ።
ከትዕግሥት ናፍቆት ጋር ተደርቦ የወላጆቹ በተለይም የእናቱ ሁኔታ ፊቱ ላይ እየተደቀነበት መጨነቁ አልቀረም ።
ያስብ ያስብና ሁሉም ነገር ፍቺ የሌለው እንቆቅልሽ ይሆንበታል ። ሆኖም እንቆቅልሽ ነው ብሎ አይተወውም ።
ተመልሶ በዚያው ሐሳብ ዙሪያ ይሽከረከራል ፡ በሐሳብ ከመብከንከኑ ጋር የምግብ ፍላጎቱም እየቀነሰ ስለመጣ
በጣም ከስቶ ነበር ። ግን ለዚህ ደንታ አልነበረውም ። አካሉ መንምኖ ነፍሱ ብቻ ከውስጥ ሚን ሚን እስክትል ይጠብቃታል
ብርቅነሽ ትዝ ስትለው የደስታ ብርሃን ትፈነጥቃለች ።ስለ እሷ ማሰብ ደስ ይለዋል። አብሯት ካደረ ጀምሮ የመውደድ ስሜት ተቀርጾበታል ። የፍቅሩን ዐይነት ግን በግል ለይቶ ማወቅ አልቻለም ። ትዕግሥትን ይወዳታል ፡ ብርቅነሽን ይወዳታል ። የመወደዱ ዐይነት ይለያያል ሲያስቡት ደስ የሚልና ሲያስቡት የሚያስቃይ ፍቅር ! ስለ ብርቅነሽ ማሰብ ያስደስተዋል ፤ አያሠቃየውም ፤ ጭንቅላቱን አይበጠብጠውም ። ስለ ትዕግሥት ማሰብ ግን ያሰቃየዋል፥
ይበጠብጠዋል ፤ ያስለቅሰዋል ። እንዲያም ሆኖ ፍቅሩ ለምታሠቃየው ለትዕግሥት ያደላል ። ሙሉ ልቡን ያሳረፈው በትዕግሥት ላይ ነው ። ቀርቦ ምስጢሩን ካካፈላት ፥ ገላዋን ካቀፈውና ትኩሳቷን ሲቀበል ካደራት ሴት ይልቅ ከዐይኑ ላላለፈች ሴት ፍቅሩ ማመዘኑ ለምን እንደያነ ሊገባው አልቻለም ። “ የፍቅር ምስጢሩ ምንድነው ? ሲል አሰበ "
ፍቅር የሚወደው ሥቃይን ይሆን እንዴ ? ?
አንድ ቀን ብርቅነሽን ሲያስታውስ ከውስጡ “ሔደህ እያት ” የሚል አንዳች ግፊት መጣበት። ለእስክንድር ሳያማክረው ተደብቆ ብቻውን ሔደ ። ለምን እንደሚሔድና ቢያገኛት ምን እንደሚላት አላሰበበትም ። ገብቶ ለመጫወትም ቢሆን ፥ የሚጠጣ! ለማዘዝ በኪሱ ገንዘብ የለም ። እናም ቡና ቤቱ አጠገብ ሲደርስ ቀጥ ብሎ ቆመ።
የቡና ቤቱ በር ክፍት ነው ። ነገር ግን ድምፅ አይሰማበትም። እንደዚያ ዕለቱ ምሽት ሙዚቃና የሰው ቻቻታ የለበትም ። ከዝንቦች እምታ በቀር ጸጥ ረጭ ብሏል ።
መግባት አልደፈረም ። እየተንጎራደደ ሰው ብቅ እስኪል ይጠብቅ ጀመር ። ጥቂት እንደ ቆየ ፥ አንዲት ሴት የከሰል
ምድጃ ይዛ ከውስጥ ብቅ አለች ። አለባበሷ ግድ የለሽ ነው ።
ሻሿን የገርዳሳ አስራለች ።
አቤል ሲያያት ክው አለ ። የዋህነቷንና ጥሬነቷን አይታ የቡና ቤቷ ባለቤት ማታ ማታ እንደ አሻሻጭ ቀን ደግሞ እንደ ገረድ ነው የምትጠቀምባት ፡ ከሰሉ እንዲቀጣጠልላት ምድጃውን ወደ ንፋስ አድርጋ ቀና ስትል አየችው ቶሎ አልለየችም። ያው እንደ መንገደኛ ነበር የተመለከተችው ። ስታየው ተደናግጦ ጀርባውን ሰጥቷት ወደ ኋላው ሊመለስ ፈልጎ ነበር ። ግን ዐይኑን ከማሸሹ በፊት የምታውቀው ወንድ መሆኑን ለይታ ጥርሷን ብልጭ አረገችለት እሷን ፍለጋ ያልመጣ ለመምሰል እጁን ኪሱ ከትቶ በግዴለሽ አረማመድ ተጠጋት ስሜቱን ለመሸፈን በከንቱ ደከመ እንጂ በድንጋጤ ፊቱ ቀልቶ ግንባሩን አልቦት ነበር።
ውይ ! አንተ ነህ እንዴ ? በሞትኩት ! ምነው ጠፋህ ? ” አለች ከልብ በሆነ አነጋግር ።
ምንም ሳይመልስላት ስሜቱን በፈግግታ ብልጭታ ለመሸፈን እየሞከረ ጨበጣት
ሙት እውነቴን እኮ ነው ጠፋህ ? ቆይ እስኪ ስንት ቀን ሆነን አዎ ሳምንት አልፎሃል ። እኔ ከዛሬ ነገ ትመጣለህህ እያልኩ በልቤ ሳስብህ ነበር አለችው።
“ እነቷን ይሆን እንዴ ? ” ሲል አሰበ ግን አሁንም ከመቅለስለስና ራሰን ከማከክ ሌላ ምንም አልመለሰም ። ድምጿ የእውነት ቅላጼ ነበረው የተናገረችው የልቧን ነው ፤ ለአቤል አንድ ጥሩ የሆነ ስሜት አድሮበታል ። ሴት ያልለመደ መሆኑና የተማረ መሆኑ ፥ በስሜቷ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጎታል እናም እንዳለችው አብራው ካደረችበት ሌሊት በኋላ ዐልፎ ዐልፎ በልቧ ታስበው ነበር ። የተሰማራችበት ሙያ ሆነና በወሲብ ተገናኙ እንጂ ፥ እሷ ለሱ ያደረባት ስሜት ሐሳቧንና ችግሯን እንደምታዋየው
እሱም በዕውቀቱ እንደሚረዳት የቅርብ ዘመዷ ወይም ታናሽ ወንድሟ ዐይነት ነበር
“ በል እሺ ግባ ! በር ላይ አትቁም አለችው ከእሱ አንዳችም ቃል ባለመስማቷ እያዘነች ።
“አአይ ልሒድ ፤ድንገት ሳልፍ'ኮ ነው
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ
ጊዜ መደፊት አይገፈትርም።ጊዜ ለሰው ጭንቀትም ሆነ ደስታ ደንታ የለውም።
የራሱን ሥርዓት ጠብቆ የሚጓዘው፤ያለፈ ጊዜ አይመለስም ፤የወደፊቱ ደግሞ እንደ
ፈለግጉት ፈጥኖ አይመጣም። ሰው በጊዜ ቁጥጥር ሥር ነው እንጂ ጊዜ በሰው ቁጥጥር ስር አይደሉም ሰዓት ሰው ሠራሽ ነገር ነው ፤ ሞላውን በማዞር ካለበት ሰዓት ወይም ደቂቃ ማስቀደም ይቻላል ። የቀን መቁጠሪያም ሰው ሠራሽ
ነገር ነው ፤አንዱን ወር አልፎ ሌላውን ወር ማየት ይቻላል ።ቀንን ገፍቶ ማስመሸት፣ ወይም ምሽት ጎፍቶ ማንጋት ግን
የማይቻል ነው ።
አቤል ቢቸግረው እንዲህ አይነት የጊዜ ምርምር ውስጥ ገባ ። ችግሩ ነው ምርምሩን የጋበዘው ቀኑ አልመሽልህ "
ሌሊቱ አልነጋልህ እያለው ተቸገረ ለሌላው ተማሪ የዕረፍት ጊዜ ለእሱ ግን የመጨረሻው ደረጃ የጭንቀት ጊዜ
ሆኖበታል ። ቀንም ይተኛል ፡ ማታም ይታኛል ። ነገር ግን እንቅልፍ አይወስደውም ። እንዲሁ አልጋው ላይ እየተገላበጠ በሐሳብ መብከንከን ሆነ ። ጊዚ ከመቼውም ይልቅ የኋሊት እየተጎተተ የሚያቃስት መስለው ።
ሳምሶን ለዕረፍቱ ወደ ቤቱ ስለ ሔደ መኝታ ክፍላቸው ውስጥ የቀሩት አቤል ፡ እስክንድርና "ድብርት ” ብቻ ነበሩ ። “ ድብርት ” ፈተና ካለቀ በኋላ ያሳየው ለውጥ ቢኖር አልጋ ማንጠፉ ብቻ ነው ። በተረፈ እንደ ጥንቱ “ድብርት ጥናቱም ቢቀር ያው አልጋውን በጋቢ ጋርዶ በራሱ ሕልም ውስጥ መኖሩን አልተወም ። ወደ ውጭ ቢወጣ ብቻውን ነው ።
እስክንድር የዕረፍት ጊዜ ጓደኛው መጽሐፍ ነው ።የአማርኛና የእንግሊዝኛ ልብወለድ መጽሐፎችን እየተዋሰ
ሲያነብ ስለሚውል፥ ቀኑ በፍጥነት ነው የሚገሰግስለት ማንበብ ስልቸት ሲለው፡ወደ መዝናኛው ክበብ እየሔደ ቼዝ
ይጫወታል ። መቼም ከሱ ቦታ ሰው ቢጠፋ ሚስተር ሆርስ አይጠፋም ።
እስክንድር በዚህ ሁኔታ የዕረፍቱን ጊዜ ቢያሳልፍም ከአቤል ጋር አብሮ መጨነቁ አልቀረለትም ። ዐቅሙ በሚፈቅደው መጠን አቤልን ለማዝናናት የማያደርገው ሙከራ የለም ። ከአነበባቸው መጽሐፎች ውስጥ ጥሩ የሚላቸውን መርጦ ይሰጠዋል ። አቤል ግን ነጻ ኣዕምሮ ስለሌለው፥ አንዱንም ከነጣዕሙ አንብቦት አያውቅም ። ጀምሮ ሳይጨርሰው ይቀራል ። ወይም በግል ሐሳቡ ውስጥ እየዋዠቀ ገጹን
በመቁጠር ብቻ ይጨርሰዋል ። እስክንድር ወደ ቼዝ መጫወቻው ቦታ ሲሔድ አቤል አብሮት እንዲሔድ ለማድረግ ቢሞክርም እሺ አላለውም ፡ ከሚስተር ሆርስ ጋር ከተጣላ ወዲህ የመዝናኛ ክበቡን ረግጦት አያውቅም ።
አቤል ወደ ውጭ ብቅ እያለ ከሰዎች ቢቀላቀል ፡ ጊዜውን መዝናኛ ቦታዎች እየሔደ ቢያሳልፍና በአንዳንድ እን
ቅስቃሴዎች ቢሳተፍ፡ ጭንቀቱ እንደሚቀልለት እስክንድር
ቢረዳም ፡ ይህን ለማድረግ ሁኔታዎች አልተመቻቹለትም አብዛኛው መዝናኛ ገንዘብ ይጠይቃል ። ይህን ማሟላት
አይችሉም ። ገንዘብ በማይጠይቅበት መዝናኛ ቦታ ለመዋል ደግሞ የአቤል ሙሉ ፈቃደኝነት አይገኝም ። ሌላ ቀርቶ
ከእስክንድር ጋር ከሚያወራበት ጊዜ ይልቅ፡ ብቻውን ተደብሮ ውስጥ ውስጡን ነገር ሲያብሰለስል የሚውልበት ጊዜ
ይበልጣል ።
ትዕግሥት በተለያየ መልክ በሕልሙ እየመጣች ትታየዋለች ። አንዴ ይጣላሉ ፤አንዴ ጥላው በመሔዷ የተሰማውን ቅሬታ ይገልጽላታል ፤ አንዳንዴ ደግሞ ደብረ ዘይት ድረስ ሔዶ ሲገናኛት ያድራል ቀን ያሰበውን ማታ በሕልሙ ይደግመዋል አንዳንዴ በቅዠት ይወራጫል ።
ከትዕግሥት ናፍቆት ጋር ተደርቦ የወላጆቹ በተለይም የእናቱ ሁኔታ ፊቱ ላይ እየተደቀነበት መጨነቁ አልቀረም ።
ያስብ ያስብና ሁሉም ነገር ፍቺ የሌለው እንቆቅልሽ ይሆንበታል ። ሆኖም እንቆቅልሽ ነው ብሎ አይተወውም ።
ተመልሶ በዚያው ሐሳብ ዙሪያ ይሽከረከራል ፡ በሐሳብ ከመብከንከኑ ጋር የምግብ ፍላጎቱም እየቀነሰ ስለመጣ
በጣም ከስቶ ነበር ። ግን ለዚህ ደንታ አልነበረውም ። አካሉ መንምኖ ነፍሱ ብቻ ከውስጥ ሚን ሚን እስክትል ይጠብቃታል
ብርቅነሽ ትዝ ስትለው የደስታ ብርሃን ትፈነጥቃለች ።ስለ እሷ ማሰብ ደስ ይለዋል። አብሯት ካደረ ጀምሮ የመውደድ ስሜት ተቀርጾበታል ። የፍቅሩን ዐይነት ግን በግል ለይቶ ማወቅ አልቻለም ። ትዕግሥትን ይወዳታል ፡ ብርቅነሽን ይወዳታል ። የመወደዱ ዐይነት ይለያያል ሲያስቡት ደስ የሚልና ሲያስቡት የሚያስቃይ ፍቅር ! ስለ ብርቅነሽ ማሰብ ያስደስተዋል ፤ አያሠቃየውም ፤ ጭንቅላቱን አይበጠብጠውም ። ስለ ትዕግሥት ማሰብ ግን ያሰቃየዋል፥
ይበጠብጠዋል ፤ ያስለቅሰዋል ። እንዲያም ሆኖ ፍቅሩ ለምታሠቃየው ለትዕግሥት ያደላል ። ሙሉ ልቡን ያሳረፈው በትዕግሥት ላይ ነው ። ቀርቦ ምስጢሩን ካካፈላት ፥ ገላዋን ካቀፈውና ትኩሳቷን ሲቀበል ካደራት ሴት ይልቅ ከዐይኑ ላላለፈች ሴት ፍቅሩ ማመዘኑ ለምን እንደያነ ሊገባው አልቻለም ። “ የፍቅር ምስጢሩ ምንድነው ? ሲል አሰበ "
ፍቅር የሚወደው ሥቃይን ይሆን እንዴ ? ?
አንድ ቀን ብርቅነሽን ሲያስታውስ ከውስጡ “ሔደህ እያት ” የሚል አንዳች ግፊት መጣበት። ለእስክንድር ሳያማክረው ተደብቆ ብቻውን ሔደ ። ለምን እንደሚሔድና ቢያገኛት ምን እንደሚላት አላሰበበትም ። ገብቶ ለመጫወትም ቢሆን ፥ የሚጠጣ! ለማዘዝ በኪሱ ገንዘብ የለም ። እናም ቡና ቤቱ አጠገብ ሲደርስ ቀጥ ብሎ ቆመ።
የቡና ቤቱ በር ክፍት ነው ። ነገር ግን ድምፅ አይሰማበትም። እንደዚያ ዕለቱ ምሽት ሙዚቃና የሰው ቻቻታ የለበትም ። ከዝንቦች እምታ በቀር ጸጥ ረጭ ብሏል ።
መግባት አልደፈረም ። እየተንጎራደደ ሰው ብቅ እስኪል ይጠብቅ ጀመር ። ጥቂት እንደ ቆየ ፥ አንዲት ሴት የከሰል
ምድጃ ይዛ ከውስጥ ብቅ አለች ። አለባበሷ ግድ የለሽ ነው ።
ሻሿን የገርዳሳ አስራለች ።
አቤል ሲያያት ክው አለ ። የዋህነቷንና ጥሬነቷን አይታ የቡና ቤቷ ባለቤት ማታ ማታ እንደ አሻሻጭ ቀን ደግሞ እንደ ገረድ ነው የምትጠቀምባት ፡ ከሰሉ እንዲቀጣጠልላት ምድጃውን ወደ ንፋስ አድርጋ ቀና ስትል አየችው ቶሎ አልለየችም። ያው እንደ መንገደኛ ነበር የተመለከተችው ። ስታየው ተደናግጦ ጀርባውን ሰጥቷት ወደ ኋላው ሊመለስ ፈልጎ ነበር ። ግን ዐይኑን ከማሸሹ በፊት የምታውቀው ወንድ መሆኑን ለይታ ጥርሷን ብልጭ አረገችለት እሷን ፍለጋ ያልመጣ ለመምሰል እጁን ኪሱ ከትቶ በግዴለሽ አረማመድ ተጠጋት ስሜቱን ለመሸፈን በከንቱ ደከመ እንጂ በድንጋጤ ፊቱ ቀልቶ ግንባሩን አልቦት ነበር።
ውይ ! አንተ ነህ እንዴ ? በሞትኩት ! ምነው ጠፋህ ? ” አለች ከልብ በሆነ አነጋግር ።
ምንም ሳይመልስላት ስሜቱን በፈግግታ ብልጭታ ለመሸፈን እየሞከረ ጨበጣት
ሙት እውነቴን እኮ ነው ጠፋህ ? ቆይ እስኪ ስንት ቀን ሆነን አዎ ሳምንት አልፎሃል ። እኔ ከዛሬ ነገ ትመጣለህህ እያልኩ በልቤ ሳስብህ ነበር አለችው።
“ እነቷን ይሆን እንዴ ? ” ሲል አሰበ ግን አሁንም ከመቅለስለስና ራሰን ከማከክ ሌላ ምንም አልመለሰም ። ድምጿ የእውነት ቅላጼ ነበረው የተናገረችው የልቧን ነው ፤ ለአቤል አንድ ጥሩ የሆነ ስሜት አድሮበታል ። ሴት ያልለመደ መሆኑና የተማረ መሆኑ ፥ በስሜቷ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጎታል እናም እንዳለችው አብራው ካደረችበት ሌሊት በኋላ ዐልፎ ዐልፎ በልቧ ታስበው ነበር ። የተሰማራችበት ሙያ ሆነና በወሲብ ተገናኙ እንጂ ፥ እሷ ለሱ ያደረባት ስሜት ሐሳቧንና ችግሯን እንደምታዋየው
እሱም በዕውቀቱ እንደሚረዳት የቅርብ ዘመዷ ወይም ታናሽ ወንድሟ ዐይነት ነበር
“ በል እሺ ግባ ! በር ላይ አትቁም አለችው ከእሱ አንዳችም ቃል ባለመስማቷ እያዘነች ።
“አአይ ልሒድ ፤ድንገት ሳልፍ'ኮ ነው
👍2
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....ቀጠሮው ደረሰ፡፡ ትህትና ድንበሩ ለተመሠረተባት ክስ መልስ የምትሰጥበት ቀን... ጠበቃዋ አቶ ምንውየለት ተዘራ በመልሱ ላይ ተከሳሽ ሆን ብላ ተሰናድታ ሳይሆንእንደሻው በቀለ በእሷና በወንድሟ
ላይ በፈጸመውና ባስፈጸመው ተደጋጋሚ ወንጀል ምክንያት ህሊናዋ ስለቆሰለ፤ ንብረትነቱ የወላጅ አባቷ የነበረውን ከቤት የተቀመጠ መሣሪያ በድንገት ይዛ በመውጣት፤ በደም ፍላት ተነሳስታ፤ ድርጊቱን መፈጸሟን፣ ወጣት እንደሻው በቀለ በፈጸመባት አስገዳጅ የግብረ ሥጋ
ግንኙነት ምክንያት፤ ክብረ ንጽህናዋ በመደፈሩ፤ ለትዳር ከወጠነችው እጮኛዋ ጋር ከመጣላቷም በላይ፤ ታናሽ ወንድሟ አንዱዓለም ድንበሩ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ምክንያት፤ በእንደሻው በቀለ አማካይነት በገንዘብ በተገዛ ወሮበላ ተደብድቦ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት መሆኑን፤ እነዚህ
ተደራራቢ ጥቃቶች፤ ወንጀሉን እንድትፈጽም ያነሳሷት ድርጊቶች
ከመሆናቸው በተጨማሪ፤ ወጣቷ በዕለቱ ወጣት እንደሻውን ለማጥቃት ብቻ ሳይሆን በራሷ ህይወት ላይ የወሰደችው ቅጽበታዊ ሙከራ ሁሉ፤ የነበረባትን የአእምሮ ጭንቀት ደረጃ በግልጽ የሚያሳይ በመሆኑ፧ ክቡር ፍርድ ቤቱ የዕድሜዋን ሁኔታ፤ የደረሰባትን የሞራል መገደድ፣ የቤተሰብ ኃላፊነት ደረጃዋንና ከዚህ በፊት የነበራትን መልካም ስነ ምግባር፧ ከግምት ውስጥ በማስገባት በነፃ እንዲያሰናብታት ሲል በመጠየቅ መልስ ሰጠ፡፡
ለዚህም መልስ የመልስ መልስ እሰጣለሁ በማለት ዐቃቤ ህጉ ስለጠየቀ፤
የመልስ መልሱን እንዲሰጥ ተደረገ፡፡
ከዚህ በኋላ በፓሊስ የቀረበው የምርመራ መዝገብ፣ የሀኪም ማስረጃና፤ በእግዚቢትነት የተያዘው ኮልት ሽጉጥ ለፍርድ ቤቱ ቀረቡ፡፡ ዐቃቤ ህጉ በሰጠው የመልስ መልስ ላይ ተከሳሽም ሆነች
ወንድሟ ተፈጽሞብናል የሚሉት ወንጀል ቢኖር፤ በወቅቱ ጉዳዩን ለህግ አቅርበው ፍትህን መጠየቅ ሲችሉ፤ ይህንን ሳያደርጉ ቀርተው፤ ተከሳሽ ከተመሰረተባት የክስ ጭብጥ፤ ምክንያትና ውጤት ጋር፤ግንኙነት የሌለውን ሀተታ በመልስ ውስጥ በመዘርዘር፤ በነፃ እንድትለቀቅ የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን፤ ወንጀልን ማካካስ የማይቻል
በመሆኑም በመልሱ ላይ የቀረበው የወንጀል ማካካሻ ጥያቄ ውድቅ
እንዲደረግ ጥያቄ በማቅረብና ፤ ተከሳሽ እራሷን ለማጥፋት ያደረገችው ሙከራም ህጋዊ ድጋፍ የሌለው ህገውጥ ድርጊት ከመሆን አልፎ ከጥፋትዋ ነፃ እንድትወጣ በቂና አሳማኝ ምክንያት ሊሆን የማይችል
ስለሆነ፤ ክቡር ፍርድ ቤቱ በተከሳሽዋ ላይ የጥፋተኛነት ውሳኔ
በዚህም መሰረት
ቃለ መሀላ
እንዲሰጥልኝ በማለት ስለተከራከረ ፤ ለተፈጸመው ወንጀል ያውቁልኛል
የሚላቸውን ምስክሮች እንዲያቀርብ ተደረገ በምስክርነት ያቀረባቸው ሶስት ምስክሮች ፍ/ቤት ቀርበው እንዲፈጽሙ ከተደረገ በኋላ ፤ ወንጀሉ የተፈጸመበትን ቦታ፣ ቀንና ሰዓት ጠቅሰው ተከሳሽ እንደሻው በቀለን በአራት ጥይቶች ደጋግማ ማቁሰሏን በማረጋገጥ፤ ተመሳሳይነት ባለው ቃል መሰከሩ፡፡
የዐቃቤ ህጉ ምስክሮች ተሰምተው እንዳበቁ በተከሳሽ ላይ የቀረቡት ማስረጃዎች ከበድ ያሉ ሆነው በመገኘታቸው፤ ፍ/ቤቱ ተከሳሽን
እንድትከላከል ትዕዛዝ ሰጠ፡፡በዚህ ጊዜ የተከሳሽ የመከላከያ ምስክሮች ሆነው የቀረቡት
1ኛ ወ/ት አዜብ ተሾመ
2ኛ ወ/ት ወርቅ ያንጥፉ አደራ
3ኛ. አቶ አበራ ፈይሳ
አስፈላጊውን ቃለ መሀላ ከፈጸሙ በኋላ፤ ተከሳሽ በአስተዳደግ፤ በተማረችበት ትምህርት ቤት፤ በሥራ ቦታዋ ላይም ሆነ በመኖሪያዋ አካባቢ የነበራትን ሥነ ምግባር፣ ከዚህ በፊት ተከሳ ያልተቀጣች ጨዋ ወጣት መሆኗንና፤ ወጣት እንደሻው በቀለ ድምጽ በሌለው መሣሪያ አስገድዶ ክብረ ንጽህናዋን ለመድፈሩ፤ እያንዳንዳቸው የሚያውቁትንና
ያዩትን ዘርዝረው መሰከሩ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ እራሱ ሻምበል ብሩክ ፍርድ ቤት ቀርቦ ከእጮኛው ከትህትና ድንበሩ ጋር ወጥነውት የነበረው የትዳር ዕቅድ፤
ከተፈጸመባት አስገዳጅ የክብረ ንጽህና መደፈር ጋር ተያይዞ በተፈጠረ
ያለመግባባት ምክንያት መበላሸቱን አስረዳ፡፡
ፍ/ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክርና የቀረቡትን ማስረጃዎች ከመረመረ በኋላ
“ተከሳሽ በማያጠራጥር ሁኔታ ድርጊቱን የፈጸመች ሆና ስለአገኘናት በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ቁጥር 27/524.ለ/ መሠረት ጥፋተኛ ነች ብለናል”
ሲል የጥፋተኛነት ውሣኔውን ሰጠ፡፡
ጥፋተኛነትዋ ተረጋግጦ ውሣኔ ከተሰጠ በኋላ፤ ቀሪው በቅጣት ውሣኔው ላይ የሚካሄድ ክርክር ነው፡፡በዚህ መሠረት ተከሳሽዋ ለፈፀመችው ወንጀል የቅጣት ውሣኔውን ለመስጠት እንዲያስችል ዐቃቤ ህጉ የቅጣት ማቅለያ ወይንም የማክበጃ ሃሣብ ካለው እንዲያቀርብ ፍርድ ቤቱ ስለጠየቀ፤ ተከሳሽ ትህትና ድንበሩ በቀልን በልቧ በማሳደር፤ በቂ ዝግጅት በማድረግና፤ የጦር መሣሪያ በመያዝ፤ ከሥራ ቦታው ድረስ ሄዳ ወጣት እንደሻው በቀለን በአራት ጥይቶች ደጋግማ ህይወቱን ለማጥፋት ሙከራ ማድረጓ በበቂ ማስረጃ የተረጋገጠባት በመሆኑ፡ ለዚህ ለፈጸመችው ወንጀል ተመጣጣኝ ቅጣት እንድታገኝ የወንጀለኛ መቅጫ ህግና አንቀጽ ጠቅሶ ጠየቀ፡፡
የተከሳሽ ጠበቃም እንደዚሁ ስለህጉና፤ ስለጉዳዩ፤ በማብራራት ቅጣቱ እንዲቀልላት አስተያየቱን አቀረበ፡፡
በዚህ የቅጣት ማቅለያ አስተያየት ላይ በወጣት እንደሻው በቀላ ወላጆች ቤት ውስጥ ተቀጥረው የሚያገለግሉት በተለይ የወጣት እንደሻው የሥጋ ዘመድ የሆነው አቶ አበራ ፈይሣ የዝምድና ደረጃው ሳያግደው በሃቅ እንደመሰከረውና፤ በቤት ሠራተኛነት ተቀጥራ የምታገለግለው ወይዘሪት ወርቅ ያንጥፉ አደራ በዐይኗ ባየችው ድርጊት ላይ በሰጠችው የምስክርነት ቃል በተረጋገጠው መሠረት፤ እንደሻው በቀለ ሃይል ተጠቅሞ፤ በተከሳሿ ላይ የሞራል ተቃራኒ የሆነ፤ የወደፊት የትዳር ህይወቷን ያበላሸና፤ ከምትኖርበት ማህበረሰብ ባህልና እምነት አንፃር ዝቅተኛ ግምት የሚያሰጣትን ወንጀል የፈጸመባት በመሆኑ፤ ከዚሁ ወንጀል ጋር በተያያዘም ጋርጠው መራን በገንዘብ በመግዛት በወንድሟ ላይ የድብደባ ወንጀል በማስፈጸም ያደረሰባት ድርብ፤ ድርብርብ ጥቃት ለጋ አእምሮዋን የነካና፤ ለወንጀል ያነሳሳት ድርጊት መሆኑን :: ወጣቷ
በምትኖርበትም ሆነ በተማረችበት ትምህርት ቤት ውስጥ ፍጹም ጨዋና
ዕላማዊ ዜጋ መሆኗ የተመሰከረላት ከመሆኑ በተጨማሪ፧ ወላጅ አባቷ
ለግዳጅ ተጠርቶ በጦር ሜዳ ላይ በመሞቱ ምክንያት፧ በለጋ እድሜዋ
ከራሷ ጭምር ሶስት ቤተሰብ የማስተዳደር ሃላፊነት የተሸከመች ወጣት
በመሆንዋ ክቡር ፍርድ ቤቱ.....
ሀ. ተከሳሽ ወንጀሉን ለመፈጸም የተነሳሳችበትን ሁኔታ
ለ. የተከሳሽን የዕድሜ ሁኔታ
ሐ. ተከሳሽ ወንጀሉን ስትፈጽም የነበረችበትን ሁኔታ
መ. የተከሳሽን የቤተሰብ ኃላፊነት ደረጃ
ሠ. ተከሳሽ ከዚህ በፊት በማናቸውም ወንጀል ተከሳ ቅጣት ያልተፈፀመባትና፤ ለወደፊቱ ያላትን የሥነ ምግባር ታራሚነት ከግምት ውስጥ በማስገባት እስከዛሬ ድረስ በማረሚያ ቤት የቆየችበት ጊዜ በቂ
ሆኖ ቅጣቱ እንዲቀልላት በማለት አስተያየቱን ሰጠ፡፡
ከዚህ በኋላ የሚቀረው ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን መርምሮ የቅጣት ውሣኔ የሚሰጥበትን ዕለት በጉጉትና በናፍቆት መጠባበቅ ብቻ ሆነ
አንዱአለም በአሁኑ ሰዓት ምጽዋ በባህር ኃይል ውስጥ በስልጠና ላይ ይገኛል፡፡ ለኪስ የሚሰጠውን አነስተኛ ገንዘብ የሚልከው ለእህቱ ነው፡፡ እህቱ በማንኛውም ረገድ እንድትበረታ፣ መታሰር ማለት በህይወት ውስጥ ከሚገጥሙ የኑሮ ውጣ ውረዶች አንዱ እንጂ ከህብረተሰቡ መገለል ማለት ያለመሆኑን እየገለጸ “አይዞሽ” እያለ በማጽናናትና፤ ስለሱ እንዳታስብ በቀይ ባህር ዳርቻ፣ በመርከብ ላይ፣ ብቻውንና ከጓደኞቹ ጋር
ሆኖ የተነሣቸውን ፎቶ ግራፎች ለሷና
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
....ቀጠሮው ደረሰ፡፡ ትህትና ድንበሩ ለተመሠረተባት ክስ መልስ የምትሰጥበት ቀን... ጠበቃዋ አቶ ምንውየለት ተዘራ በመልሱ ላይ ተከሳሽ ሆን ብላ ተሰናድታ ሳይሆንእንደሻው በቀለ በእሷና በወንድሟ
ላይ በፈጸመውና ባስፈጸመው ተደጋጋሚ ወንጀል ምክንያት ህሊናዋ ስለቆሰለ፤ ንብረትነቱ የወላጅ አባቷ የነበረውን ከቤት የተቀመጠ መሣሪያ በድንገት ይዛ በመውጣት፤ በደም ፍላት ተነሳስታ፤ ድርጊቱን መፈጸሟን፣ ወጣት እንደሻው በቀለ በፈጸመባት አስገዳጅ የግብረ ሥጋ
ግንኙነት ምክንያት፤ ክብረ ንጽህናዋ በመደፈሩ፤ ለትዳር ከወጠነችው እጮኛዋ ጋር ከመጣላቷም በላይ፤ ታናሽ ወንድሟ አንዱዓለም ድንበሩ ከዚሁ ጋር በተያያዘ ምክንያት፤ በእንደሻው በቀለ አማካይነት በገንዘብ በተገዛ ወሮበላ ተደብድቦ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት መሆኑን፤ እነዚህ
ተደራራቢ ጥቃቶች፤ ወንጀሉን እንድትፈጽም ያነሳሷት ድርጊቶች
ከመሆናቸው በተጨማሪ፤ ወጣቷ በዕለቱ ወጣት እንደሻውን ለማጥቃት ብቻ ሳይሆን በራሷ ህይወት ላይ የወሰደችው ቅጽበታዊ ሙከራ ሁሉ፤ የነበረባትን የአእምሮ ጭንቀት ደረጃ በግልጽ የሚያሳይ በመሆኑ፧ ክቡር ፍርድ ቤቱ የዕድሜዋን ሁኔታ፤ የደረሰባትን የሞራል መገደድ፣ የቤተሰብ ኃላፊነት ደረጃዋንና ከዚህ በፊት የነበራትን መልካም ስነ ምግባር፧ ከግምት ውስጥ በማስገባት በነፃ እንዲያሰናብታት ሲል በመጠየቅ መልስ ሰጠ፡፡
ለዚህም መልስ የመልስ መልስ እሰጣለሁ በማለት ዐቃቤ ህጉ ስለጠየቀ፤
የመልስ መልሱን እንዲሰጥ ተደረገ፡፡
ከዚህ በኋላ በፓሊስ የቀረበው የምርመራ መዝገብ፣ የሀኪም ማስረጃና፤ በእግዚቢትነት የተያዘው ኮልት ሽጉጥ ለፍርድ ቤቱ ቀረቡ፡፡ ዐቃቤ ህጉ በሰጠው የመልስ መልስ ላይ ተከሳሽም ሆነች
ወንድሟ ተፈጽሞብናል የሚሉት ወንጀል ቢኖር፤ በወቅቱ ጉዳዩን ለህግ አቅርበው ፍትህን መጠየቅ ሲችሉ፤ ይህንን ሳያደርጉ ቀርተው፤ ተከሳሽ ከተመሰረተባት የክስ ጭብጥ፤ ምክንያትና ውጤት ጋር፤ግንኙነት የሌለውን ሀተታ በመልስ ውስጥ በመዘርዘር፤ በነፃ እንድትለቀቅ የቀረበው ጥያቄ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን፤ ወንጀልን ማካካስ የማይቻል
በመሆኑም በመልሱ ላይ የቀረበው የወንጀል ማካካሻ ጥያቄ ውድቅ
እንዲደረግ ጥያቄ በማቅረብና ፤ ተከሳሽ እራሷን ለማጥፋት ያደረገችው ሙከራም ህጋዊ ድጋፍ የሌለው ህገውጥ ድርጊት ከመሆን አልፎ ከጥፋትዋ ነፃ እንድትወጣ በቂና አሳማኝ ምክንያት ሊሆን የማይችል
ስለሆነ፤ ክቡር ፍርድ ቤቱ በተከሳሽዋ ላይ የጥፋተኛነት ውሳኔ
በዚህም መሰረት
ቃለ መሀላ
እንዲሰጥልኝ በማለት ስለተከራከረ ፤ ለተፈጸመው ወንጀል ያውቁልኛል
የሚላቸውን ምስክሮች እንዲያቀርብ ተደረገ በምስክርነት ያቀረባቸው ሶስት ምስክሮች ፍ/ቤት ቀርበው እንዲፈጽሙ ከተደረገ በኋላ ፤ ወንጀሉ የተፈጸመበትን ቦታ፣ ቀንና ሰዓት ጠቅሰው ተከሳሽ እንደሻው በቀለን በአራት ጥይቶች ደጋግማ ማቁሰሏን በማረጋገጥ፤ ተመሳሳይነት ባለው ቃል መሰከሩ፡፡
የዐቃቤ ህጉ ምስክሮች ተሰምተው እንዳበቁ በተከሳሽ ላይ የቀረቡት ማስረጃዎች ከበድ ያሉ ሆነው በመገኘታቸው፤ ፍ/ቤቱ ተከሳሽን
እንድትከላከል ትዕዛዝ ሰጠ፡፡በዚህ ጊዜ የተከሳሽ የመከላከያ ምስክሮች ሆነው የቀረቡት
1ኛ ወ/ት አዜብ ተሾመ
2ኛ ወ/ት ወርቅ ያንጥፉ አደራ
3ኛ. አቶ አበራ ፈይሳ
አስፈላጊውን ቃለ መሀላ ከፈጸሙ በኋላ፤ ተከሳሽ በአስተዳደግ፤ በተማረችበት ትምህርት ቤት፤ በሥራ ቦታዋ ላይም ሆነ በመኖሪያዋ አካባቢ የነበራትን ሥነ ምግባር፣ ከዚህ በፊት ተከሳ ያልተቀጣች ጨዋ ወጣት መሆኗንና፤ ወጣት እንደሻው በቀለ ድምጽ በሌለው መሣሪያ አስገድዶ ክብረ ንጽህናዋን ለመድፈሩ፤ እያንዳንዳቸው የሚያውቁትንና
ያዩትን ዘርዝረው መሰከሩ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ እራሱ ሻምበል ብሩክ ፍርድ ቤት ቀርቦ ከእጮኛው ከትህትና ድንበሩ ጋር ወጥነውት የነበረው የትዳር ዕቅድ፤
ከተፈጸመባት አስገዳጅ የክብረ ንጽህና መደፈር ጋር ተያይዞ በተፈጠረ
ያለመግባባት ምክንያት መበላሸቱን አስረዳ፡፡
ፍ/ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክርና የቀረቡትን ማስረጃዎች ከመረመረ በኋላ
“ተከሳሽ በማያጠራጥር ሁኔታ ድርጊቱን የፈጸመች ሆና ስለአገኘናት በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ቁጥር 27/524.ለ/ መሠረት ጥፋተኛ ነች ብለናል”
ሲል የጥፋተኛነት ውሣኔውን ሰጠ፡፡
ጥፋተኛነትዋ ተረጋግጦ ውሣኔ ከተሰጠ በኋላ፤ ቀሪው በቅጣት ውሣኔው ላይ የሚካሄድ ክርክር ነው፡፡በዚህ መሠረት ተከሳሽዋ ለፈፀመችው ወንጀል የቅጣት ውሣኔውን ለመስጠት እንዲያስችል ዐቃቤ ህጉ የቅጣት ማቅለያ ወይንም የማክበጃ ሃሣብ ካለው እንዲያቀርብ ፍርድ ቤቱ ስለጠየቀ፤ ተከሳሽ ትህትና ድንበሩ በቀልን በልቧ በማሳደር፤ በቂ ዝግጅት በማድረግና፤ የጦር መሣሪያ በመያዝ፤ ከሥራ ቦታው ድረስ ሄዳ ወጣት እንደሻው በቀለን በአራት ጥይቶች ደጋግማ ህይወቱን ለማጥፋት ሙከራ ማድረጓ በበቂ ማስረጃ የተረጋገጠባት በመሆኑ፡ ለዚህ ለፈጸመችው ወንጀል ተመጣጣኝ ቅጣት እንድታገኝ የወንጀለኛ መቅጫ ህግና አንቀጽ ጠቅሶ ጠየቀ፡፡
የተከሳሽ ጠበቃም እንደዚሁ ስለህጉና፤ ስለጉዳዩ፤ በማብራራት ቅጣቱ እንዲቀልላት አስተያየቱን አቀረበ፡፡
በዚህ የቅጣት ማቅለያ አስተያየት ላይ በወጣት እንደሻው በቀላ ወላጆች ቤት ውስጥ ተቀጥረው የሚያገለግሉት በተለይ የወጣት እንደሻው የሥጋ ዘመድ የሆነው አቶ አበራ ፈይሣ የዝምድና ደረጃው ሳያግደው በሃቅ እንደመሰከረውና፤ በቤት ሠራተኛነት ተቀጥራ የምታገለግለው ወይዘሪት ወርቅ ያንጥፉ አደራ በዐይኗ ባየችው ድርጊት ላይ በሰጠችው የምስክርነት ቃል በተረጋገጠው መሠረት፤ እንደሻው በቀለ ሃይል ተጠቅሞ፤ በተከሳሿ ላይ የሞራል ተቃራኒ የሆነ፤ የወደፊት የትዳር ህይወቷን ያበላሸና፤ ከምትኖርበት ማህበረሰብ ባህልና እምነት አንፃር ዝቅተኛ ግምት የሚያሰጣትን ወንጀል የፈጸመባት በመሆኑ፤ ከዚሁ ወንጀል ጋር በተያያዘም ጋርጠው መራን በገንዘብ በመግዛት በወንድሟ ላይ የድብደባ ወንጀል በማስፈጸም ያደረሰባት ድርብ፤ ድርብርብ ጥቃት ለጋ አእምሮዋን የነካና፤ ለወንጀል ያነሳሳት ድርጊት መሆኑን :: ወጣቷ
በምትኖርበትም ሆነ በተማረችበት ትምህርት ቤት ውስጥ ፍጹም ጨዋና
ዕላማዊ ዜጋ መሆኗ የተመሰከረላት ከመሆኑ በተጨማሪ፧ ወላጅ አባቷ
ለግዳጅ ተጠርቶ በጦር ሜዳ ላይ በመሞቱ ምክንያት፧ በለጋ እድሜዋ
ከራሷ ጭምር ሶስት ቤተሰብ የማስተዳደር ሃላፊነት የተሸከመች ወጣት
በመሆንዋ ክቡር ፍርድ ቤቱ.....
ሀ. ተከሳሽ ወንጀሉን ለመፈጸም የተነሳሳችበትን ሁኔታ
ለ. የተከሳሽን የዕድሜ ሁኔታ
ሐ. ተከሳሽ ወንጀሉን ስትፈጽም የነበረችበትን ሁኔታ
መ. የተከሳሽን የቤተሰብ ኃላፊነት ደረጃ
ሠ. ተከሳሽ ከዚህ በፊት በማናቸውም ወንጀል ተከሳ ቅጣት ያልተፈፀመባትና፤ ለወደፊቱ ያላትን የሥነ ምግባር ታራሚነት ከግምት ውስጥ በማስገባት እስከዛሬ ድረስ በማረሚያ ቤት የቆየችበት ጊዜ በቂ
ሆኖ ቅጣቱ እንዲቀልላት በማለት አስተያየቱን ሰጠ፡፡
ከዚህ በኋላ የሚቀረው ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን መርምሮ የቅጣት ውሣኔ የሚሰጥበትን ዕለት በጉጉትና በናፍቆት መጠባበቅ ብቻ ሆነ
አንዱአለም በአሁኑ ሰዓት ምጽዋ በባህር ኃይል ውስጥ በስልጠና ላይ ይገኛል፡፡ ለኪስ የሚሰጠውን አነስተኛ ገንዘብ የሚልከው ለእህቱ ነው፡፡ እህቱ በማንኛውም ረገድ እንድትበረታ፣ መታሰር ማለት በህይወት ውስጥ ከሚገጥሙ የኑሮ ውጣ ውረዶች አንዱ እንጂ ከህብረተሰቡ መገለል ማለት ያለመሆኑን እየገለጸ “አይዞሽ” እያለ በማጽናናትና፤ ስለሱ እንዳታስብ በቀይ ባህር ዳርቻ፣ በመርከብ ላይ፣ ብቻውንና ከጓደኞቹ ጋር
ሆኖ የተነሣቸውን ፎቶ ግራፎች ለሷና
👍4
#ቆንጆዎቹ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
#ቆንጆዎቹ
“ማርቆስ” አለ ጀኔራሉ ጥፋትህ ፍጹም ከይቅርታ በላይ ነው::"
ማርቆስ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዘመናት ሚያውቀው አስተማሪው አለቃውና ጓደኛው ፊት ላይ ጽያፍ የተሞላ ቅዝቃዜ የተመለከተ መሰለው፡፡
“በአጭሩ የውጭ ጉዳዩ ሰው ከቁጥጥር ውጭ ሆኗል።”አለ ጀኔራሉ በንዴት የቀሉ ዓይኖቹን ከማርቆስ ላይ አንስቶ በስተግራ በተቀመጠው ምክትሉ በሆነው በአንድሬ አማሪ ላይ እየተከለ፡፡
“እኔ መጀመሪያውኑ…” ዣክ ዊልያም ፊቱ ላይ ጎልቶ የሚታየውን ንቀትና ጥላቻ ሳይደብቅ፡፡ ዓይኖቹን በኮሎኔል ማርቆስ ላይ ተክሎ ጀመረ።
በቃ! አለ ጀኔራሉ አቋርጦት “እሁን ባለፈና በሞተ ነገር ላይ ጊዜዬን ማጥፋት
አልፈልግም፡፡ ያለን ጊዜ በደቂቃዎች የሚቆጠር ነው፡፡ ይህ ሰው ወደ ድሬዳዋ የሄደው እንደምፈራው የካልቨርትን መሸሸጊያ አግኝቶ ከሆነና ምስጢሩንም አስገድዶ እጁ ካገባ ምን እንደሚከተል ልትገምቱ ትችላላችሁ፡፡”
ለአንድ አፍታ የፀጥታው ቡድን ሃላፊ ንግግሩን አቁሞ በረጅሙ ተነፈሰ፡፡ በአፍንጫው ላይ ሽፍ ያለው ላብ በክፍሉ ውስጥ ካለው ቀዝቀዝ ካለው አየር ጋር ሲያገናዝቡት ሰውየው በንዳድ የሚሰቃይ ይመስላል፡፡
“ለማንኛውም እናንተን ቢሮዬ ድረስ ከመጥራቴ በፊት ከዚህ ወዲያ ምን ማድረግ እንዳለብን ዝርዝር ዕቅድ አውጥቻለሁ፡፡” አለ ጀኔራሉ ቀጥሎ
“ጉዳዩን ከአሁን በኋላ አንድሬ በቀጥታ እየተከታትልክ በየአንድ አንድ ሰዓቱ
ሪፖርት ታደርግልኛለህ፡፡” አለ ወደምክትሉ ፊቱን መልሶ
የፀጥታው ክፍል ምክትል አዛዥ ጭንቅላቱን በስምምነት ነቀነቀ፡፡
“በቅድሚያ ኣለ ጀኔራሉ ፊቱን የአጥቂ ስለላ ሃላፊ ወደሆነው ወደ ዣክ ዊልያም መልሶ በቅድሚያ ዣክ ድሬዳዋ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች….
በገበያ ቦታዎች…. እ... የውጭ ዜጎች በሚኖሩበት ክልል.… ተከታታይ የፈንጂ
አደጋዎችን ትጥላለህ፡፡ ይህ በሚቀጥለው አንድ ሰዓት ውስጥ እንዲጠናቀቅ እፈልጋለሁ፡፡” አለ ጀኔራሉ በጣቱ ጠረጴዛውን እየተመተመ፡፡ “እንድሪ” ፊቱን ወደ ምክትሉ መለሰ፡፡ “የፈንጂ አደጋዎቹ፡፡ እንደደረሱ ወድያውኑ
ድሬዳዋ ገብተህ እያንዳንዱን በር ትዘጋለሁ፡፡ ለጊዜው በማንኛውም የቴሌኮ
ሙኒኬሽንና የፖስታ አገልግሎቶች ጥብቅ ክትትል አደርጋለሁ፡፡ ከዛም ውጪ አራት የኮማንዶ ሃይል ወደዚያው ልኬልሃለሁ ማንኛውም የመጓጓዣ መስመር ከአንድ ሰዓት በኋላ ይዘጋል፡፡ አንድሬ አሁኑኑ ቀጥታ ወደ ድሬዳዋ በረህ ከተማዋን ትመነጥራለህ፡፡ ቤት ማፍረስ ካለብህ አፍርስ፤ ጉድጓድ መማስ ካለብህ ማስ፤ ያንን ሠይጣን ቀኑ ሳይመሽ በፊት እጅህ ማስገባት አለብህ:: ለምናደርገው ሁሉ ያፈንጂዎቹን “ፍንዳታ የአሸባሪዎች ጥቃት
መሆኑን በማጉላት ዣክ በቂ አሳሳች ፕሮፖጋንዲ እያዘጋጀ ለመገናኛ
ብዙሃን ያቀርባል።” ፊቱን ወደ ዣክ ዊልያም መልሶ ተናገረ፡፡
“እዚህ ላይ ይቅርታ፡፡” አለ ሩዋንዳዊው አንድሬ አማሪ፡፡ “ድሬዳዋ የአሸባሪዎቹ ጥቃት እንደደረሰ እዛ ያሉ የመንግሥት ሃይሎችና ፖሊስም ጣልቃ ሊገቡብን ይችላሉ፡፡”
“ለዚያ አታስብ” አለ ጀኔራሉ እጁን ወደጎን አወናጭፎ “ያ የኔ ስራ ነው፡፡ ማንኛውም የመንግሥት ሃይል ጣልቃ አይገባም፡፡ፈንጂዎቹን የምናፈነዳውና አሳሳች ፕሮፖጋንዳ የምንነዛው የሕዝቡን ስነልቦና ለመጠበቅና የጠላትን ጥርጣሬ ላለማነሳሳትና ሽፋን ለመፍጠር ነው፡፡በመንግሥት በኩል ችግር አይኖርም:: ድሬዳዋ በእጅህ ናት::”
“እዛ ከተላከው ሃይል ጋር እንዴት ነው የምገናኘው?” አለ ኣንድሬ ኦማሪ፡፡
“ወደዛው ትበራለህ። እንዳልኩህ እራት የኮማንዶ ሃይል ከነሙሉ ትጥቁ ወደዛው በሮ ከአውሮፕላኑ ሳይወርድ- በተጠንቀቅ ይጠብቅሃል፡፡በተረፈ ከዚህ ከተላከው ሃይል ጋር የሚኖርህ ግንኙነት ቀጥታ በሃይሉ አዛዥ አማካኝነት ይሆናል፡፡”
ጀኔራሉ ተክታታይ ትዕዛዞችን ሲያስተላልፍ ከቆየ በኋላ ከተቀመጠበት ተነስቶ ሲቆም በክፍሉ ውስጥ ያሉት ሁሉ ተነስተው በተጠንቀቅ ቆሙ::
“አሁን” አለ ጀኔራሉ ሰዓቱን እየተመለከተ፡፡ “ከጠዋቱ አስራ ሁለት ከሩብ ነው፡፡ ዣክ አንድ ሰዓት ተኩል ከመሆኑበፊት ፈንጂዎች እንዲፈነዱ፡፡አንድሬ ከአንድ ሰዓት ተኩል እስከ ሁለት ድሬዳዋ ታርፋለህ፡፡ ከሁለት እስከ ሦስት ባለው ሰዓት ሃይልህን አቀናጅተህ ስራህን ትጀምራህ” ጀኔራሉ በረጅሙ ተነፈሰና ያመነታ መስለ። “ከአሁን ወዲያ ይህን ጉዳይ እዚሁ ልናቆየው አንችልም:: ዝርዝር ሁኔታውን ለበላዮቹ ማስታወቅ ይኖርብኛል፡፡ምን ያህል አደገኛ ሁኔታ ላይ እንዳለን አስተውሉ፡፡ ለምትሰሩት ማንኛውም ስህተት በቀጥታተ ጠያቂ አድርጌ አቀርባችኋለሁ፡፡” አለ ጀኔራሉ የዣክ ዊልያምን ፊት እየሸሸ፡፡ “መሄድ ትችላላችሁ::”
ሁለቱ ባለስልጣናት ከወጡ በኋላ ጀኔራሉ በወንበሩ ላይ ተቀመጠና ፊቱን በተጠንቀቅ በቆመው ኮሎኔል ማርቆስ ላይ መለሰ፡፡
ጋዜጠኛዋጋ ሄደህ ጥበቃውን ተከታተል፡፡” አለው ከፊቱ ዘወር
እንዲልለት በመፈለግ፡፡ ኮሎኔል ማርቆስ በተጠንቀቅ ሠላምታ ሰጥቶ ፊቱን
መልሶ ወደበሩ ሲያመራ “ኮሎኔል” አለ አለቅየው ፊቱ ላይ ንዴት የተቀላቀለበት ጽያፌ እየተነበበ …እሷ ደግሞ እንዳታመልጥህ፡፡”
ኮሎኔል ማርቆስ በድጋሚ ወታደራዊ ሠላምታ ኣቅርቦ በፀጥታ ከክፍሉ ወጣ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በተከታታይ የፈንጂ ድምጾች ድሬዳዋ ስትናወጥ ናትናኤል ከተኛበት ስስ ፍራሽ ላይ በርግጎ ተነሳ፡፡
ተከታትለው ሌሎች ሁላት ፍንዳታዎች ጠባቧን ከተማ ሲንጣት፤ ያለበትን ክፍል በርና መስኮት ሲያርገፈግፉት ናትናኤል ተነስቶ ቆመና ዙሪያውን ቃኘ፡፡ በፍንዳታው ውስጥ አጉረምርሞ ተገላብጦ መልሶ የተኛው ካልቨርት አሁንም ከገባበት የስካር ባህር ብቅ ያለ አይመስልም፡፡
ናትናኤል ካልቨርትን በጭንቀት ተመለክተው፡፡ ከአንድ ቀን በፊት
ሲያገኘው ብስጭት ተስፋ መቁረጥና ስካር የተሻሙት ግማሽ እሬሳ ነበር፡፡
በዛን ሰዓት ናትናኤል ከካልቨርት ጋር ቁጭ ብሎ ለማውራት መሞከር
ፍሬቢስ መሆኑን ለመረዳት አልተቸገረም። ይልቁንም በቅድሚያ የካልቨርትን አመኔታ ሊያገኝበትና ሊያረጋጋውም የሚችልበትን መንገድ መረጠ ከጎኑ ፍራሽ ላይ ቁጭ ብሎ አረቄ ሲጠጣ ቆየ፡፡
አለፍ አለፍ እያለ ግራ የተጋባው ካልቨርት
“ማነህ? ለምን አትገለኝም?… ምንድነው የምትጠብቀው?” እያለ በስካር መንፈስ ሲወተውተውም ናትናኤል መልስ አልሰጠውም።
ከሰዓት በኋላ ናትናኤል ካልቨርት ከተሸሸገበት ጠባብ ክፍል ውጥ
የምሥራችን እናት አነጋገራቸው፡፡
“ድንገት በመምጣቴ ይቅርታ…የላከችኝ የምሥራች ነበረች፡፡ ግን በዚህን ዓይነት ሁኔታ ላያ ይሆናል ብለን አልገመትንም ነበር፡፡" እላቸው የካልቨርት ስካር ያስደነገጠው መስሎ፡፡
“ምን አባቴ ላድርገው? በጠዋት ተነስቶ አረቂ ነው ማታ ተኝቶ አረቂ ነው…ምግብ ሲሉት በሩቁ እጁን ያውለበልባል አረቄ የከለከልኩት ጊዜ ሲያቃስት ማደር ነው..ተው አይሉት ነገር አፉ እንግዳ…እኔ'ኮ ጨነቀኝ፡፡
አንድ ነገር አድርጊ አልላት ነገር ድምጿ ጠፋ፡፡ሰወ አልክባት..ማንም ማወቅ
የለበትም ብላኝ እንዴት አድርጌ ለሰው ልናገር?” ሴትየዋ የተማረሩ መሰሉ፡፡
“ግድ የለም:: ዋናው ነገር በህይወት መቆየቱ፡ ነው:: ብቻ እርሶ ትንሽ ተቸገሩ፡፡ የምሥራችን አይሆንም አታስቸግሪያቸው ብያት ነበር፡፡ እምቢ አለች እንጂ፡፡” በተቻለው የልጃቸው የምሥራች የቅርብ ወዳጅ ለመምሰል ጣረ፡፡
“እኔማ ምን ችግር አለብኝ..ቢበዛ የገዛ ገዝቡን፤ ቢጠጣ የገዛ ብሩን ከኔ ሳንቲም
አላወጣ.…ግን ቢሆንም... ሰው እንዲህ ራሱን በመጠጥ በመርዝ ልበለው እንጂ ሲገድል ሲያዩ ህሊናም አያርፍ፡፡”
“እውነት አለዎት፡፡”
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሰርቅ_ዳ
#ቆንጆዎቹ
“ማርቆስ” አለ ጀኔራሉ ጥፋትህ ፍጹም ከይቅርታ በላይ ነው::"
ማርቆስ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዘመናት ሚያውቀው አስተማሪው አለቃውና ጓደኛው ፊት ላይ ጽያፍ የተሞላ ቅዝቃዜ የተመለከተ መሰለው፡፡
“በአጭሩ የውጭ ጉዳዩ ሰው ከቁጥጥር ውጭ ሆኗል።”አለ ጀኔራሉ በንዴት የቀሉ ዓይኖቹን ከማርቆስ ላይ አንስቶ በስተግራ በተቀመጠው ምክትሉ በሆነው በአንድሬ አማሪ ላይ እየተከለ፡፡
“እኔ መጀመሪያውኑ…” ዣክ ዊልያም ፊቱ ላይ ጎልቶ የሚታየውን ንቀትና ጥላቻ ሳይደብቅ፡፡ ዓይኖቹን በኮሎኔል ማርቆስ ላይ ተክሎ ጀመረ።
በቃ! አለ ጀኔራሉ አቋርጦት “እሁን ባለፈና በሞተ ነገር ላይ ጊዜዬን ማጥፋት
አልፈልግም፡፡ ያለን ጊዜ በደቂቃዎች የሚቆጠር ነው፡፡ ይህ ሰው ወደ ድሬዳዋ የሄደው እንደምፈራው የካልቨርትን መሸሸጊያ አግኝቶ ከሆነና ምስጢሩንም አስገድዶ እጁ ካገባ ምን እንደሚከተል ልትገምቱ ትችላላችሁ፡፡”
ለአንድ አፍታ የፀጥታው ቡድን ሃላፊ ንግግሩን አቁሞ በረጅሙ ተነፈሰ፡፡ በአፍንጫው ላይ ሽፍ ያለው ላብ በክፍሉ ውስጥ ካለው ቀዝቀዝ ካለው አየር ጋር ሲያገናዝቡት ሰውየው በንዳድ የሚሰቃይ ይመስላል፡፡
“ለማንኛውም እናንተን ቢሮዬ ድረስ ከመጥራቴ በፊት ከዚህ ወዲያ ምን ማድረግ እንዳለብን ዝርዝር ዕቅድ አውጥቻለሁ፡፡” አለ ጀኔራሉ ቀጥሎ
“ጉዳዩን ከአሁን በኋላ አንድሬ በቀጥታ እየተከታትልክ በየአንድ አንድ ሰዓቱ
ሪፖርት ታደርግልኛለህ፡፡” አለ ወደምክትሉ ፊቱን መልሶ
የፀጥታው ክፍል ምክትል አዛዥ ጭንቅላቱን በስምምነት ነቀነቀ፡፡
“በቅድሚያ ኣለ ጀኔራሉ ፊቱን የአጥቂ ስለላ ሃላፊ ወደሆነው ወደ ዣክ ዊልያም መልሶ በቅድሚያ ዣክ ድሬዳዋ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች….
በገበያ ቦታዎች…. እ... የውጭ ዜጎች በሚኖሩበት ክልል.… ተከታታይ የፈንጂ
አደጋዎችን ትጥላለህ፡፡ ይህ በሚቀጥለው አንድ ሰዓት ውስጥ እንዲጠናቀቅ እፈልጋለሁ፡፡” አለ ጀኔራሉ በጣቱ ጠረጴዛውን እየተመተመ፡፡ “እንድሪ” ፊቱን ወደ ምክትሉ መለሰ፡፡ “የፈንጂ አደጋዎቹ፡፡ እንደደረሱ ወድያውኑ
ድሬዳዋ ገብተህ እያንዳንዱን በር ትዘጋለሁ፡፡ ለጊዜው በማንኛውም የቴሌኮ
ሙኒኬሽንና የፖስታ አገልግሎቶች ጥብቅ ክትትል አደርጋለሁ፡፡ ከዛም ውጪ አራት የኮማንዶ ሃይል ወደዚያው ልኬልሃለሁ ማንኛውም የመጓጓዣ መስመር ከአንድ ሰዓት በኋላ ይዘጋል፡፡ አንድሬ አሁኑኑ ቀጥታ ወደ ድሬዳዋ በረህ ከተማዋን ትመነጥራለህ፡፡ ቤት ማፍረስ ካለብህ አፍርስ፤ ጉድጓድ መማስ ካለብህ ማስ፤ ያንን ሠይጣን ቀኑ ሳይመሽ በፊት እጅህ ማስገባት አለብህ:: ለምናደርገው ሁሉ ያፈንጂዎቹን “ፍንዳታ የአሸባሪዎች ጥቃት
መሆኑን በማጉላት ዣክ በቂ አሳሳች ፕሮፖጋንዲ እያዘጋጀ ለመገናኛ
ብዙሃን ያቀርባል።” ፊቱን ወደ ዣክ ዊልያም መልሶ ተናገረ፡፡
“እዚህ ላይ ይቅርታ፡፡” አለ ሩዋንዳዊው አንድሬ አማሪ፡፡ “ድሬዳዋ የአሸባሪዎቹ ጥቃት እንደደረሰ እዛ ያሉ የመንግሥት ሃይሎችና ፖሊስም ጣልቃ ሊገቡብን ይችላሉ፡፡”
“ለዚያ አታስብ” አለ ጀኔራሉ እጁን ወደጎን አወናጭፎ “ያ የኔ ስራ ነው፡፡ ማንኛውም የመንግሥት ሃይል ጣልቃ አይገባም፡፡ፈንጂዎቹን የምናፈነዳውና አሳሳች ፕሮፖጋንዳ የምንነዛው የሕዝቡን ስነልቦና ለመጠበቅና የጠላትን ጥርጣሬ ላለማነሳሳትና ሽፋን ለመፍጠር ነው፡፡በመንግሥት በኩል ችግር አይኖርም:: ድሬዳዋ በእጅህ ናት::”
“እዛ ከተላከው ሃይል ጋር እንዴት ነው የምገናኘው?” አለ ኣንድሬ ኦማሪ፡፡
“ወደዛው ትበራለህ። እንዳልኩህ እራት የኮማንዶ ሃይል ከነሙሉ ትጥቁ ወደዛው በሮ ከአውሮፕላኑ ሳይወርድ- በተጠንቀቅ ይጠብቅሃል፡፡በተረፈ ከዚህ ከተላከው ሃይል ጋር የሚኖርህ ግንኙነት ቀጥታ በሃይሉ አዛዥ አማካኝነት ይሆናል፡፡”
ጀኔራሉ ተክታታይ ትዕዛዞችን ሲያስተላልፍ ከቆየ በኋላ ከተቀመጠበት ተነስቶ ሲቆም በክፍሉ ውስጥ ያሉት ሁሉ ተነስተው በተጠንቀቅ ቆሙ::
“አሁን” አለ ጀኔራሉ ሰዓቱን እየተመለከተ፡፡ “ከጠዋቱ አስራ ሁለት ከሩብ ነው፡፡ ዣክ አንድ ሰዓት ተኩል ከመሆኑበፊት ፈንጂዎች እንዲፈነዱ፡፡አንድሬ ከአንድ ሰዓት ተኩል እስከ ሁለት ድሬዳዋ ታርፋለህ፡፡ ከሁለት እስከ ሦስት ባለው ሰዓት ሃይልህን አቀናጅተህ ስራህን ትጀምራህ” ጀኔራሉ በረጅሙ ተነፈሰና ያመነታ መስለ። “ከአሁን ወዲያ ይህን ጉዳይ እዚሁ ልናቆየው አንችልም:: ዝርዝር ሁኔታውን ለበላዮቹ ማስታወቅ ይኖርብኛል፡፡ምን ያህል አደገኛ ሁኔታ ላይ እንዳለን አስተውሉ፡፡ ለምትሰሩት ማንኛውም ስህተት በቀጥታተ ጠያቂ አድርጌ አቀርባችኋለሁ፡፡” አለ ጀኔራሉ የዣክ ዊልያምን ፊት እየሸሸ፡፡ “መሄድ ትችላላችሁ::”
ሁለቱ ባለስልጣናት ከወጡ በኋላ ጀኔራሉ በወንበሩ ላይ ተቀመጠና ፊቱን በተጠንቀቅ በቆመው ኮሎኔል ማርቆስ ላይ መለሰ፡፡
ጋዜጠኛዋጋ ሄደህ ጥበቃውን ተከታተል፡፡” አለው ከፊቱ ዘወር
እንዲልለት በመፈለግ፡፡ ኮሎኔል ማርቆስ በተጠንቀቅ ሠላምታ ሰጥቶ ፊቱን
መልሶ ወደበሩ ሲያመራ “ኮሎኔል” አለ አለቅየው ፊቱ ላይ ንዴት የተቀላቀለበት ጽያፌ እየተነበበ …እሷ ደግሞ እንዳታመልጥህ፡፡”
ኮሎኔል ማርቆስ በድጋሚ ወታደራዊ ሠላምታ ኣቅርቦ በፀጥታ ከክፍሉ ወጣ፡፡
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
በተከታታይ የፈንጂ ድምጾች ድሬዳዋ ስትናወጥ ናትናኤል ከተኛበት ስስ ፍራሽ ላይ በርግጎ ተነሳ፡፡
ተከታትለው ሌሎች ሁላት ፍንዳታዎች ጠባቧን ከተማ ሲንጣት፤ ያለበትን ክፍል በርና መስኮት ሲያርገፈግፉት ናትናኤል ተነስቶ ቆመና ዙሪያውን ቃኘ፡፡ በፍንዳታው ውስጥ አጉረምርሞ ተገላብጦ መልሶ የተኛው ካልቨርት አሁንም ከገባበት የስካር ባህር ብቅ ያለ አይመስልም፡፡
ናትናኤል ካልቨርትን በጭንቀት ተመለክተው፡፡ ከአንድ ቀን በፊት
ሲያገኘው ብስጭት ተስፋ መቁረጥና ስካር የተሻሙት ግማሽ እሬሳ ነበር፡፡
በዛን ሰዓት ናትናኤል ከካልቨርት ጋር ቁጭ ብሎ ለማውራት መሞከር
ፍሬቢስ መሆኑን ለመረዳት አልተቸገረም። ይልቁንም በቅድሚያ የካልቨርትን አመኔታ ሊያገኝበትና ሊያረጋጋውም የሚችልበትን መንገድ መረጠ ከጎኑ ፍራሽ ላይ ቁጭ ብሎ አረቄ ሲጠጣ ቆየ፡፡
አለፍ አለፍ እያለ ግራ የተጋባው ካልቨርት
“ማነህ? ለምን አትገለኝም?… ምንድነው የምትጠብቀው?” እያለ በስካር መንፈስ ሲወተውተውም ናትናኤል መልስ አልሰጠውም።
ከሰዓት በኋላ ናትናኤል ካልቨርት ከተሸሸገበት ጠባብ ክፍል ውጥ
የምሥራችን እናት አነጋገራቸው፡፡
“ድንገት በመምጣቴ ይቅርታ…የላከችኝ የምሥራች ነበረች፡፡ ግን በዚህን ዓይነት ሁኔታ ላያ ይሆናል ብለን አልገመትንም ነበር፡፡" እላቸው የካልቨርት ስካር ያስደነገጠው መስሎ፡፡
“ምን አባቴ ላድርገው? በጠዋት ተነስቶ አረቂ ነው ማታ ተኝቶ አረቂ ነው…ምግብ ሲሉት በሩቁ እጁን ያውለበልባል አረቄ የከለከልኩት ጊዜ ሲያቃስት ማደር ነው..ተው አይሉት ነገር አፉ እንግዳ…እኔ'ኮ ጨነቀኝ፡፡
አንድ ነገር አድርጊ አልላት ነገር ድምጿ ጠፋ፡፡ሰወ አልክባት..ማንም ማወቅ
የለበትም ብላኝ እንዴት አድርጌ ለሰው ልናገር?” ሴትየዋ የተማረሩ መሰሉ፡፡
“ግድ የለም:: ዋናው ነገር በህይወት መቆየቱ፡ ነው:: ብቻ እርሶ ትንሽ ተቸገሩ፡፡ የምሥራችን አይሆንም አታስቸግሪያቸው ብያት ነበር፡፡ እምቢ አለች እንጂ፡፡” በተቻለው የልጃቸው የምሥራች የቅርብ ወዳጅ ለመምሰል ጣረ፡፡
“እኔማ ምን ችግር አለብኝ..ቢበዛ የገዛ ገዝቡን፤ ቢጠጣ የገዛ ብሩን ከኔ ሳንቲም
አላወጣ.…ግን ቢሆንም... ሰው እንዲህ ራሱን በመጠጥ በመርዝ ልበለው እንጂ ሲገድል ሲያዩ ህሊናም አያርፍ፡፡”
“እውነት አለዎት፡፡”
👍4
#የፍቅር_ሰመመን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
.....በመጨረሻም የሚፈልገውን ጥል እንዳሰበው አገኘው፡፡ ኬስሌ ጀምስ፡፡
ይህ ኬስሊ ጀምስ የተባለ ወጣት ዋት መንደር ውስጥ የተወለደ የወረደ
ህይወት ያለው ሴት አቃጣሪና በትርፍ ጊዜውም የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪ
ሲሆን አውቆ የተሳሳተ መረጃ ሰጠውና የመጀመሪያውን ትልቁን የወንጀል
ምርመራ ጉዳዩን አሳጣው፡፡ ከፍርድ ቤት ከወጣ በኋላ ጄሪ በቀጥታ ጄምስን
ፍለጋ ጄምስ ወደሚገኝበት ቤት አመራ፡፡ ጄምስንም መኪናው ውስጥ አገኘው፡፡ ከመኪናው ጎትቶ አውርዶት ሰው ሁሉ እያየው እስኪበቃው ድረስ ቀጠቀጠው፡፡ ልጁ ለሶስት ሳምንት ያህል በፅኑ ህሙማን ክፍል ከቆየ በኋላ እንደምንም ብሎ ህይወቱ ተረፈ::፡ ነገር ግን ዕድሜውን በሙሉ በተሽከርካሪ
ወንበር ላይ እንደሚያሳልፍ እንዲሁም ደግሞ መሰረታዊ የሆኑ የተፈጥሮ
ግዴታዎቹን እንኳን ለመወጣት የግድ አጋዥ የሚያስፈልገው ሰው ሆነ::
ጄሪ በሰው መግደል የሙከራ ወንጀል ተከስሶ ፍርድ ቤት ቀረበ፡፡ ሁሉም
በፍርድ ቤቱ የሚገኙ ወንዶች ጄሪ በስራው ላይ እያለ ጄምስን ሊይዘው ሲል
ስለተቃወመውና እንደዚሁም ደግሞ መሳሪያ ሊመዝበት ስለነበረ ጄሪ ራሱን
ለመከላከል ሲል ያደረገው ነገር ነው ብለው መሰከሩለት፡፡ ነገር ግን የኬስሊ
ጄምስ እናት ፍርድ ቤት ቀርባ እየተንሰቀሰቀች እና እየጮኸች እህቶቹም ያኔ በፖሊስ እስኪሞት ድረስ የተደበደበው የመጨረሻ ዝቃጭ ወንድማቸውን
የወደፊቱን ብሩህ ህይወቱን እንደተነጠቀበት አድርገው አራገቡት፡፡
ሚክ ጆንስን የፍርድ ሂደቱን በየቀኑ ሲከታተል ነበር፡፡ ችሎቱን በማስኬድ ላይ የምትገኘውን ሊብራል (ነፃ አሳቢ፣ ለዘብተኛ) ጨጓራ የምትልጠው ሴት ዳኛ የጄምስ ቤተሰብ የሚናገረውን እያንዳንዱን ቃላት በውስጧ ስትይዝ እየታዘባት ነበር፡፡ በተለይ ደግሞ የጄምስ ቤተሰቦች ስለዚህ የማይረባ ልጃቸው የሌለውን የውሽት ነገሮች እያወሩ የጄሪን ጥሩ ሥም እንዲጨቀይ ስላደረጉ በንዴት ጨጓራው ይላጥ ነበር፡፡ ግን ምንም ማድረግ አይችልምና ዝም አለ፡፡ ጄሪ የግድ የዳኛውን ልብ የሚያሳዝን ታሪክ መፍጠር ያስፈልገዋል፡፡
የመጀመሪያው በሚስቱ ሞት የተነሳ ከፍተኛ ሀዘን ደርሶበት ስለነበር
የአዕምሮ አለመረጋጋት ስለደረሰበት ነው የሚል የመከላከያ ሀሳብን አቅርቦ
ጠበቃው ተከራከረለት፡፡ በመቀጠል ትንሿ ልጁን ጁሊን አቅርቦ ጁሊ እንዴት
አባቷን እንደምትወድ እና እናቷ ከሞተች ጀምሮ ቤተሰቡ በጣም እንደተጎዳ
ጭምር ተናገረች፡፡ የጄሪ የቀድሞ የትቤት እና የእግር ኳስ ክለቡ ጓደኞቹም
ለጄሪ መሰከሩለት፡፡ ምን ይሄ ብቻ የአካባቢው ፖስተርም ፍርድ ቤት ቀርቦ
ስለ ጄሪ መልካም ባህሪ እና ሃይማኖተኝነት ጭምር የምስክርነት ቃሉን
ሰጠ፡፡
ነገር ግን ይህቺ ሸርሙጣ ኒኪ ሮበርትስ የተባለችው ሴት የምስክርነት ሳጥን ውስጥ ገብታ የምስክርነት ቃሏን ስትሰጥ የጄሪ የመከራ ህይወት ተጀመረ፡፡ ዶክተር ሮበርትስ ከፍተኛ ሀዘን በሀዘንተኛው ላይ ስለሚያሳድረው የስነ ልቦና ችግር የባለሙያ ምስክር ሆና ነበር የቀረበችው፡፡ ከፍተኛ የሆነ ሀዘን ላይ ያለ ሰው ጄሪ ያደረገውን ነገር ያደርጋል? ከፍተኛ ሀዘን
ልንቆጣጠረው የማንችለውን የአመፃ ስሜትን በሰዎች ላይ ያሳድራል? ጄሪ
ከቫክ በጣም ከፍተኛ ሀዘን ውጥ ስለነበረ ሀዘኑም አዕምሮውን ኬስሊ ላይ
ጥቃት ሲሰራም በትክክለኛ አዕምሮው አልነበረም? የሚሉ የባለሙያ መልስ
የሚያስፈልጋቸው ጥያቄዎች ለዶክተር ሮበርትስ ቀርቦላት ነበር፡፡ እሷ ግን
መልሶቹን ስትመልስ
“አያደርግም፡፡”
“አያሳድርም፡፡”
“እንደዚህ የሚባል ነገር የለም፡፡”
የሚሉ መልሶችን ሰጠች
ዶክተር ሮበርትስ በሰጠችው ሙያዊ ምስክርነት ውስጥ አንድም የጄሪን
ነገር ያካተተ ሚዛናዊ አስተያየት አላከለችም፡፡ በእሷ ሙያዊ አስተያየት
ደግሞ ጄሪ ምንም አይነት የአዕምሮ ችግር እንደሌለበት አስረዳች፡፡
ጥቃቱንም ሲፈፅም በድንገት ሳይሆን አቅዶበት ነው አለች፡፡ ምናልባትም ጄሪ
ባለው የዘረኝነት እና የራስ ወዳድነት ምክንያት ጥቃቱን ሲፈፅም ከሀዘን
ይልቅ የሀይለኝነት ስሜቱን ለማንፀባረቅ ስላሰበ ነው ብላ ሁሉ ነገሩን በጄሪ
ላይ ደፈደፈችበት፡፡ ሚክ ጆንሰን ይህቺ ቀጭን ዶክተር ተብዬ ባለሙያ ስለ
ጄሪም ሆነ በሥራ ላይ ስላሉ ፖሊሶች ምን ያህል አደጋን ከእንደነዚህ ኬስሊ
ጄምስን ከመሳሰሉ ሰዎች እንደሚቀበሉ አታውቅም እና እርር እያለ የእሷን
ምስክርነት ቁጭ ብሎ ሰማት፡፡
በመጨረሻም ጄሪ ኮቫክ ከፍተኛ ወንጀለኛ ሆኖ ተገኘና ይህቺ ለዘብተኛ
ዳኛ የሃያ አምስት ዓመት የእስር ፍርድን ፈረደችበት፡፡ ለሁለት ጊዜ ያህል
ይግባኝ ቢልም በእነዚህ ሁለቱ የይግባኝ ጊዜዎችም ይህቺ የተረገመች ኒኪ
ሮበርትስ የተባለች ሴት በፍቃደኝነት እየቀረበች ከጄሪ በተቃራኒ ሆና
ምስክርነቷን ሰጠች፡፡ በቃ እንዲሁ እንደቀልድ በኒኪ ሮበርትስ የተነሳ ሚክ
ጆንስን ጓደኛው ጄሪ ኮቫክ ቀሪ ዕድሜውን በእስር ቤት እንዲያሳልፍ
አስፈረደችበት፡፡
ወደ ድሮ ጓደኛው ዞሮ ፈገግ እያለም ለራሱ እንኳ የማይሰማውን በጎነትን ጓደኛው እንዳያጣ አስቦለት ሦስተኛውን ይግባኝ እንዳመለከተለት ነገረው፡፡
“ጥሩ ነገር የምናገኝ ይመስልሃል?” ብሎ ጄሪ ጠየቀው፡፡
“ይመስለኛል” ግን የአሁኑ ይግባኛችን ጊዜ ሊወስድ ይችላል፡፡
ለሚቀጥሉት ስድስት ሳምንታትም ከፍርድ ቤት ምንም አይነት ምላሽ ላናገኝ እንችላለን” አለው ሚክ፡፡
“አታስብ እስር ቤት ውጥ ስትሆን እኮ የሚኖርህ ብቸኛ ነገር ጊዜ ብቻ
ነው። ይልቅ አንተ በመርማሪነት ስለያዝነው ጉዳይ ንገረኝ እስቲ? በጩቤ
ተወግተው ነው ሰዎቹ የተገደሉት ብለኸኝ ነበር አይደል?” ብሎ ጄሪ
ጠየቀው፡፡
“አዎን” ብሎ ጆንሰን ትንሽ ተንተባተበና “በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ይመስለኛል፡፡ ትንሽ መፍጠን ባንችልም ወደ መቋጫው እየቀረብን ሳይሆን አይቀርም”
ዶክተር ኒኪ ሮበርትስ ከዚህ የዞምቢ ግድያ ጋር ስላላት ግንኙነት ላጄሪ
ሊነግረው አልፈለገም ወይም ደግሞ ስለ ዝርዝር ነገሩ ሊያጫውተው ፈቃደኛ
አልሆነም፡፡ ሚክ ጆንሰን ኒኪ በባሏ የመኪና አደጋ ግድያ ላይ እጂ እንዳለበት
ሙሉ በሙሉ ያምናል፡፡ ያህንን ማረጋገጥ ግን ይጠበቅበታል፡፡ ከተሳካለት
በመረጃ አስደግፎ እሷን ፍርድ ቤት ያስቀርብና በጄሪ ላይ የሰጠችው
የምስክርነት ቃል ተቀባይነት እንዳያገኝ በማድረግ ጄሪን ያስለቅቀዋል፡፡
ወይም ደግሞ እሱ ላይ መስክራ ቀሪ ዕድሜውን በእስር ቤት እንዲያሳልፍ
ያስፈረደችበት ሴት፣ ልክ እንደ እሱ እስር ቤት ቀሪ እድሜዋን እንድታሳልፍ
ሲያደርግ ያሳውቀዋል፡፡ አሁን ግን ይህንን ሀሳቡን ላጄሪ ቢነግረው ያልሆነ
ተስፋ ያድርበትና ምናልባት ጉዳዩ እንዳስበው ባይሳካለት ይጎዳል ብሎ
በማስብ ሳይነግረው ቀረ፡፡
በቀረው የጥየቃ ሰዓታቸው ሁለቱ ሰዎች ብዙ ሳያወሩ ቁጭ ብለው ቆዩ፡፡ ሚክ በሚቀጥለው ወር መጥቶ እንደሚጠይቀው እና ጁሊ ልጁንም
አብራው እንድትሄድ እንደሚጠይቃት ቃል ገብቶለት ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ሚክ
ጆንሰን ምንም እንኳን ልጅ ባይኖረውም የጓደኛው ብቸኛ ልጁ ጁሊ ኮቫክ
በአባቷ እንደዚህ መሆን ምንኛ እንደሚጎዳት ይገባዋል፡፡ በእርግጥም በድጋሜ ኒኪ ሮበርትስ ከጄሪ የነጠቀችው ሌላኛው ነገር ደግሞ ሴት ልጁን ነው፡፡።
ጁሊ አባቷ ጄሪ ኮቫክ ላይ የሃያ አምስት ዓመት የእስር ፍርድ ሲፈረድበት የ13 ዓመት ልጅ ነበረች፡፡ በዚህ ምክንያት በመካከላቸው ሊኖር የሚገባው የአባት እና የልጅ ግንኙነት ተበጠሰና ለመራራቅ በቁ፡፡
ያቺ ሸርሙጣ ዶክተር ጄሪ ኮቫክን ሁሉ ነገሩን ነው ያሳጣችው፡፡
ጆንሰን ወደ ሎስአንጀለስ እየተመለሰ እያለ መሀል ላይ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_ሲዲኒ_ሼልደን
፡
፡
#ትርጉም_ብርሃኑ_በላቸው
.....በመጨረሻም የሚፈልገውን ጥል እንዳሰበው አገኘው፡፡ ኬስሌ ጀምስ፡፡
ይህ ኬስሊ ጀምስ የተባለ ወጣት ዋት መንደር ውስጥ የተወለደ የወረደ
ህይወት ያለው ሴት አቃጣሪና በትርፍ ጊዜውም የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪ
ሲሆን አውቆ የተሳሳተ መረጃ ሰጠውና የመጀመሪያውን ትልቁን የወንጀል
ምርመራ ጉዳዩን አሳጣው፡፡ ከፍርድ ቤት ከወጣ በኋላ ጄሪ በቀጥታ ጄምስን
ፍለጋ ጄምስ ወደሚገኝበት ቤት አመራ፡፡ ጄምስንም መኪናው ውስጥ አገኘው፡፡ ከመኪናው ጎትቶ አውርዶት ሰው ሁሉ እያየው እስኪበቃው ድረስ ቀጠቀጠው፡፡ ልጁ ለሶስት ሳምንት ያህል በፅኑ ህሙማን ክፍል ከቆየ በኋላ እንደምንም ብሎ ህይወቱ ተረፈ::፡ ነገር ግን ዕድሜውን በሙሉ በተሽከርካሪ
ወንበር ላይ እንደሚያሳልፍ እንዲሁም ደግሞ መሰረታዊ የሆኑ የተፈጥሮ
ግዴታዎቹን እንኳን ለመወጣት የግድ አጋዥ የሚያስፈልገው ሰው ሆነ::
ጄሪ በሰው መግደል የሙከራ ወንጀል ተከስሶ ፍርድ ቤት ቀረበ፡፡ ሁሉም
በፍርድ ቤቱ የሚገኙ ወንዶች ጄሪ በስራው ላይ እያለ ጄምስን ሊይዘው ሲል
ስለተቃወመውና እንደዚሁም ደግሞ መሳሪያ ሊመዝበት ስለነበረ ጄሪ ራሱን
ለመከላከል ሲል ያደረገው ነገር ነው ብለው መሰከሩለት፡፡ ነገር ግን የኬስሊ
ጄምስ እናት ፍርድ ቤት ቀርባ እየተንሰቀሰቀች እና እየጮኸች እህቶቹም ያኔ በፖሊስ እስኪሞት ድረስ የተደበደበው የመጨረሻ ዝቃጭ ወንድማቸውን
የወደፊቱን ብሩህ ህይወቱን እንደተነጠቀበት አድርገው አራገቡት፡፡
ሚክ ጆንስን የፍርድ ሂደቱን በየቀኑ ሲከታተል ነበር፡፡ ችሎቱን በማስኬድ ላይ የምትገኘውን ሊብራል (ነፃ አሳቢ፣ ለዘብተኛ) ጨጓራ የምትልጠው ሴት ዳኛ የጄምስ ቤተሰብ የሚናገረውን እያንዳንዱን ቃላት በውስጧ ስትይዝ እየታዘባት ነበር፡፡ በተለይ ደግሞ የጄምስ ቤተሰቦች ስለዚህ የማይረባ ልጃቸው የሌለውን የውሽት ነገሮች እያወሩ የጄሪን ጥሩ ሥም እንዲጨቀይ ስላደረጉ በንዴት ጨጓራው ይላጥ ነበር፡፡ ግን ምንም ማድረግ አይችልምና ዝም አለ፡፡ ጄሪ የግድ የዳኛውን ልብ የሚያሳዝን ታሪክ መፍጠር ያስፈልገዋል፡፡
የመጀመሪያው በሚስቱ ሞት የተነሳ ከፍተኛ ሀዘን ደርሶበት ስለነበር
የአዕምሮ አለመረጋጋት ስለደረሰበት ነው የሚል የመከላከያ ሀሳብን አቅርቦ
ጠበቃው ተከራከረለት፡፡ በመቀጠል ትንሿ ልጁን ጁሊን አቅርቦ ጁሊ እንዴት
አባቷን እንደምትወድ እና እናቷ ከሞተች ጀምሮ ቤተሰቡ በጣም እንደተጎዳ
ጭምር ተናገረች፡፡ የጄሪ የቀድሞ የትቤት እና የእግር ኳስ ክለቡ ጓደኞቹም
ለጄሪ መሰከሩለት፡፡ ምን ይሄ ብቻ የአካባቢው ፖስተርም ፍርድ ቤት ቀርቦ
ስለ ጄሪ መልካም ባህሪ እና ሃይማኖተኝነት ጭምር የምስክርነት ቃሉን
ሰጠ፡፡
ነገር ግን ይህቺ ሸርሙጣ ኒኪ ሮበርትስ የተባለችው ሴት የምስክርነት ሳጥን ውስጥ ገብታ የምስክርነት ቃሏን ስትሰጥ የጄሪ የመከራ ህይወት ተጀመረ፡፡ ዶክተር ሮበርትስ ከፍተኛ ሀዘን በሀዘንተኛው ላይ ስለሚያሳድረው የስነ ልቦና ችግር የባለሙያ ምስክር ሆና ነበር የቀረበችው፡፡ ከፍተኛ የሆነ ሀዘን ላይ ያለ ሰው ጄሪ ያደረገውን ነገር ያደርጋል? ከፍተኛ ሀዘን
ልንቆጣጠረው የማንችለውን የአመፃ ስሜትን በሰዎች ላይ ያሳድራል? ጄሪ
ከቫክ በጣም ከፍተኛ ሀዘን ውጥ ስለነበረ ሀዘኑም አዕምሮውን ኬስሊ ላይ
ጥቃት ሲሰራም በትክክለኛ አዕምሮው አልነበረም? የሚሉ የባለሙያ መልስ
የሚያስፈልጋቸው ጥያቄዎች ለዶክተር ሮበርትስ ቀርቦላት ነበር፡፡ እሷ ግን
መልሶቹን ስትመልስ
“አያደርግም፡፡”
“አያሳድርም፡፡”
“እንደዚህ የሚባል ነገር የለም፡፡”
የሚሉ መልሶችን ሰጠች
ዶክተር ሮበርትስ በሰጠችው ሙያዊ ምስክርነት ውስጥ አንድም የጄሪን
ነገር ያካተተ ሚዛናዊ አስተያየት አላከለችም፡፡ በእሷ ሙያዊ አስተያየት
ደግሞ ጄሪ ምንም አይነት የአዕምሮ ችግር እንደሌለበት አስረዳች፡፡
ጥቃቱንም ሲፈፅም በድንገት ሳይሆን አቅዶበት ነው አለች፡፡ ምናልባትም ጄሪ
ባለው የዘረኝነት እና የራስ ወዳድነት ምክንያት ጥቃቱን ሲፈፅም ከሀዘን
ይልቅ የሀይለኝነት ስሜቱን ለማንፀባረቅ ስላሰበ ነው ብላ ሁሉ ነገሩን በጄሪ
ላይ ደፈደፈችበት፡፡ ሚክ ጆንሰን ይህቺ ቀጭን ዶክተር ተብዬ ባለሙያ ስለ
ጄሪም ሆነ በሥራ ላይ ስላሉ ፖሊሶች ምን ያህል አደጋን ከእንደነዚህ ኬስሊ
ጄምስን ከመሳሰሉ ሰዎች እንደሚቀበሉ አታውቅም እና እርር እያለ የእሷን
ምስክርነት ቁጭ ብሎ ሰማት፡፡
በመጨረሻም ጄሪ ኮቫክ ከፍተኛ ወንጀለኛ ሆኖ ተገኘና ይህቺ ለዘብተኛ
ዳኛ የሃያ አምስት ዓመት የእስር ፍርድን ፈረደችበት፡፡ ለሁለት ጊዜ ያህል
ይግባኝ ቢልም በእነዚህ ሁለቱ የይግባኝ ጊዜዎችም ይህቺ የተረገመች ኒኪ
ሮበርትስ የተባለች ሴት በፍቃደኝነት እየቀረበች ከጄሪ በተቃራኒ ሆና
ምስክርነቷን ሰጠች፡፡ በቃ እንዲሁ እንደቀልድ በኒኪ ሮበርትስ የተነሳ ሚክ
ጆንስን ጓደኛው ጄሪ ኮቫክ ቀሪ ዕድሜውን በእስር ቤት እንዲያሳልፍ
አስፈረደችበት፡፡
ወደ ድሮ ጓደኛው ዞሮ ፈገግ እያለም ለራሱ እንኳ የማይሰማውን በጎነትን ጓደኛው እንዳያጣ አስቦለት ሦስተኛውን ይግባኝ እንዳመለከተለት ነገረው፡፡
“ጥሩ ነገር የምናገኝ ይመስልሃል?” ብሎ ጄሪ ጠየቀው፡፡
“ይመስለኛል” ግን የአሁኑ ይግባኛችን ጊዜ ሊወስድ ይችላል፡፡
ለሚቀጥሉት ስድስት ሳምንታትም ከፍርድ ቤት ምንም አይነት ምላሽ ላናገኝ እንችላለን” አለው ሚክ፡፡
“አታስብ እስር ቤት ውጥ ስትሆን እኮ የሚኖርህ ብቸኛ ነገር ጊዜ ብቻ
ነው። ይልቅ አንተ በመርማሪነት ስለያዝነው ጉዳይ ንገረኝ እስቲ? በጩቤ
ተወግተው ነው ሰዎቹ የተገደሉት ብለኸኝ ነበር አይደል?” ብሎ ጄሪ
ጠየቀው፡፡
“አዎን” ብሎ ጆንሰን ትንሽ ተንተባተበና “በጥሩ ሁኔታ እየሄደ ይመስለኛል፡፡ ትንሽ መፍጠን ባንችልም ወደ መቋጫው እየቀረብን ሳይሆን አይቀርም”
ዶክተር ኒኪ ሮበርትስ ከዚህ የዞምቢ ግድያ ጋር ስላላት ግንኙነት ላጄሪ
ሊነግረው አልፈለገም ወይም ደግሞ ስለ ዝርዝር ነገሩ ሊያጫውተው ፈቃደኛ
አልሆነም፡፡ ሚክ ጆንሰን ኒኪ በባሏ የመኪና አደጋ ግድያ ላይ እጂ እንዳለበት
ሙሉ በሙሉ ያምናል፡፡ ያህንን ማረጋገጥ ግን ይጠበቅበታል፡፡ ከተሳካለት
በመረጃ አስደግፎ እሷን ፍርድ ቤት ያስቀርብና በጄሪ ላይ የሰጠችው
የምስክርነት ቃል ተቀባይነት እንዳያገኝ በማድረግ ጄሪን ያስለቅቀዋል፡፡
ወይም ደግሞ እሱ ላይ መስክራ ቀሪ ዕድሜውን በእስር ቤት እንዲያሳልፍ
ያስፈረደችበት ሴት፣ ልክ እንደ እሱ እስር ቤት ቀሪ እድሜዋን እንድታሳልፍ
ሲያደርግ ያሳውቀዋል፡፡ አሁን ግን ይህንን ሀሳቡን ላጄሪ ቢነግረው ያልሆነ
ተስፋ ያድርበትና ምናልባት ጉዳዩ እንዳስበው ባይሳካለት ይጎዳል ብሎ
በማስብ ሳይነግረው ቀረ፡፡
በቀረው የጥየቃ ሰዓታቸው ሁለቱ ሰዎች ብዙ ሳያወሩ ቁጭ ብለው ቆዩ፡፡ ሚክ በሚቀጥለው ወር መጥቶ እንደሚጠይቀው እና ጁሊ ልጁንም
አብራው እንድትሄድ እንደሚጠይቃት ቃል ገብቶለት ተሰናብቶት ወጣ፡፡ ሚክ
ጆንሰን ምንም እንኳን ልጅ ባይኖረውም የጓደኛው ብቸኛ ልጁ ጁሊ ኮቫክ
በአባቷ እንደዚህ መሆን ምንኛ እንደሚጎዳት ይገባዋል፡፡ በእርግጥም በድጋሜ ኒኪ ሮበርትስ ከጄሪ የነጠቀችው ሌላኛው ነገር ደግሞ ሴት ልጁን ነው፡፡።
ጁሊ አባቷ ጄሪ ኮቫክ ላይ የሃያ አምስት ዓመት የእስር ፍርድ ሲፈረድበት የ13 ዓመት ልጅ ነበረች፡፡ በዚህ ምክንያት በመካከላቸው ሊኖር የሚገባው የአባት እና የልጅ ግንኙነት ተበጠሰና ለመራራቅ በቁ፡፡
ያቺ ሸርሙጣ ዶክተር ጄሪ ኮቫክን ሁሉ ነገሩን ነው ያሳጣችው፡፡
ጆንሰን ወደ ሎስአንጀለስ እየተመለሰ እያለ መሀል ላይ
#የወዲያነሽ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ሰኞና ማክሰኛ ተከታታዮቹም ቀናት በየተራ አልፈው ቅዳሜ ደረሰ፡፡ሁላችንም በሐሳባችን እንደ ጸናን ሰነበትን
ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ዘጠኝ ተኩል ገደማ ላይ ደርሶ ብርድ ብርድ ስላለኝ ፀሐይ ለመሞቅ ምድረ ግቢው መኻል ተቀመጥኩ በየወዲያነሽ አእምሮ ውስጥ
ያለው ጥያቄ ሳይመለስ በመሰንበቱ ሥጋቷ አልተወገደም፡፡ በአንዲት ትንሽ ነጭ ፎጣ ብርጭቆ እየወለወለች ዝግ ብላ መጣችና “አሁን ነው እንዴ የምንሄደው? እ...!» ብላ ንግግሯን በጥያቄ አንጠለጠለችው::
«አንቺና ጋሻዬነህ የምትሄዱት ሌላ ጊዜ ነው:: ቀኑን እኔና አንቺ
እንወስነዋለን፡፡ ዛሬም ሆነ ነገ የምሄደው እኔ ነኝ። ከነዚያ ከተከለከሉ መጻሕፍት አንብባ የነገረችሽን የእስረኛዋን ጓደኛሽን የምክር ቃላት አትርሺ፡ መብት
የሚገኘው በትግል ነው፡፡ ጨቋኞች በሰላምና በውዴታ መብት እይሰጡም ብላ
ነግራኛለች አላልሽም? እኔና አንቺም» ብዬ ዝም አልኳት። ከጀመርኩት አርእስት ውጪ «አዎ እውነትህን ነው: ከመንገድ ሲገቡ ያላሰቡትን ያልሰሙትን ነገር ተናግሮ ክፉም ደግም መስማትና መናገር ለእርሳቸውም ሆነ
ለእኛ ነገር ማበላሸት ነው» ብላ የብርጭቆይቱን ጥራት ለማረጋገጥ ትክ ብላ ተመለከተቻት ንግግሯን ሰምቼ ዝም ስላልኩ ወደ ቤት ገባች፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ አባቴን እንኳን ደኅና” መጣህ ለማለት ወደ ወላጆቼ ቤት ገሠገሥኩ፡፡
ባለፈው ጊዜ ወላጆቼን ለመጠየቅ ስሔድ ይጨመድደኝ የነበረው
ሥጋትና ፍርሃት እንዲሁም የሕሊና ረብሻ እጅግ በጣም ተቀነሰ። እረጋገጤ ደልዳላ ከመሆኑም በላይ ቀና ብዬ ተራመድኩ፡፡ ዱሮ ደረጃውን የምወጣው አንድ
በአንድ ሲሆን ዛሬ ግን ሁለትና ሦስቱን በአንድ ጊዜ አጠቃለልኩት። ደረጃውን
ጨርሼ ፊቴን ወደ በሩ መለስ ሳደርግ የብዙ ሰዎች ድምፅ ሰማሁ፡፡ ወደ ውስጥ ለመዝለቅ የነበረኝ ድፍረት ከፍ አለ። እቤቱ ውስጥ ለነበሩት ሁሉ ጎንበስ ብዬ
እጅ ነሣሁ፡፡ ከዚያም በቀጥታ ወደ አባቴ ሄድኩና እጅ ነሥቼ ጨበጥኩት።
«እንኳን ደኅና ገባህ! የሄድክበት ሁሉ ቀናህ! » አልኩና አንገቴን በትሕትና ሰበር አድርጌ ከፊቱ ገለል ብዬ ቆምኩ፡፡
እንኳን ደኅና ቆያችሁኝ አዎ ደኅና ደርሼ መጣ። ሁሉም ደህና
ቆየኝ። ክብሩ ይስፋ!ና! እዚች አጠገቤ ና አጠገቡ የነበረውን ወንበር በጣቱ አሳየኝ። እንኳን በደህና ገቡ ለማለት ያመጡትንና ሌሎችንም እንግዶች አንድ
በአንድ አየኋቸው፡፡ በሰዎች ላይ የሚታየው ፈገግታና የአቀማመጣቸው ሁናቴ
የተለያየ በመሆኑ አባቴን በተለያየ የአስተሳሰብ ደረጃ እንደሚመለከቱት ያስታውቃል። አንዳንዱ ውስጣዊ ጭንቀት አስገድዶት በግድ ፈገግ ብሏል።
ለማስደሰትና በግድ ለመደሰት ብሉ በደረቅ ፈገግታ ፊቱን ያጨማደደም አለ።የአንዳንዶቹን ፊት ደግሞ የበታችነት ስሜት ስለተጫነው ፊታቸው ከልቅሶ በኋላ የሚታይ ፊት እንጂ ለደስታ የቀረበ ገጽታ አይመስልም፡፡
ሁለትና ሦስቱን እንደ አባቴ የቅርብ ጓደኞች ስለምመለከታቸው በእነርሱ ላይ የነበረኝን ጥላቻ ለመርሳትም ሆነ ለማሻሻል ያለኝ አቅም በጣም አነስተኛ ነበር። ሕሊናዬ ዘወትር ይበቀላቸዋል፡፡ ወረቀት እያገላበጡ የሚዶልቱት ሁሉ ትውስ ሲለኝ፡ የሰውን ሕልውና አርደውና አወራርደው የሚገድሉ ይመስሉኛል።
ክርክርና ወሬ ሲጀምሩ ማንም በአጠገባቸው እንዲያልፍ ስለማይፈልጉ ዓለምን
የተንኮል ገበያ እንጂ የመልካም ምግባር አደባባይ እንድትሆን የሚያስቡ አይመስሉም፡፡ እናቴ እንኳን ደበቅ እያለች «መጡ ደግሞ እነ ጋጠው ገሽልጠው»
ትላቸው ነበር፡፡
ለእኔም እንደ እንግዶቹ ጠላ ደረሰኝ፡፡ ከዚህም ከዚያም የሚመጣውን ወሬ እየሰማሁ ጠላዬን ሁለት፣ ሦስት ጊዜ አስሞላሁ፡፡ እንግዶቹ አንድና ሁለት እየሆኑ ተራ በተራ እጅ እያነሡ ሄዱ።
እናቴና የውብነሽ ከአሁን አሁን ተናግሮ ጉድ ይፈላ ይሆን በማለት
በአስጨናቂ ሐሳብ እንደሚሠቃዩ ስጋታቸው በየፊታቸው ላይ ይታወቃል፡፡ ከእኔ ጋር ማዶ ለማዶ መፋጠጡን ስለ ጠሉት ሁለቱም ወደ ማድ ቤት ወረዱ፡፡
እኔና አባቴ በጣም በመጠነኛ መግባባት ስለ ጭሰኛ' ስለ ግብር' ስለ ሲሶና እርቦ ስለ ገሚስና ከአሥር አንድ፣ እንዲሁም ስለ ሕግና ስለ እኔ የልጅነት ዓመታት እስከ ምሽቱ ሁለት ሰዓት እንደነገሩ አወራን። ከዚያ በኋላ
ግን፡ እነዚያ ለሁለት ሳምንት የተለዩት የወንጀለኛ መቅጫና የፍትሐ ብሔር ሕግ መጻሕፍት ትዝ ስላሉት «ትንሽ ሥራ አለብኝ፡ ከእናትህና ከአጎትህ ጋር ተጫወት» ብሎኝ ወደ መኝታ ቤት ገባ።
ከአባቴ ጋር ተዝናንቼ ሳወራና ስጫወት በመልሶቼም እየተማመንኩ ስመልስ የመጀመሪያ ጊዜ ነበር፡፡ አባቴ ገባ ከማለቱ እኅቴና እናቴ ተካ አሉ።
የፌሩት ጉዳይ ባለመነገሩ የሁለቱም ፊት ፈገግታ አጋተ። ሩብ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ አባቴ እንደገና ተመልሶ መጣ። ኖር ብለን ተቀበልነው። እምብዛም
ሳይጠጋ ቆም አለና እነዚያን በዕድሜና በክርክር ጽሑፍ ንባብ የተዳከሙ ዐይኖቹን በግራ እጅ ጣቶች እያሻሸ ሳልነግርህ እንዳትሄድ ብዬ ነው የተመለስኩት ዘንድሮስ በጣም ጎብዘሃል አሉ፡፡ መቼ እንደሆነ አላውቅም፡ አንድ ወዳጂ ሰዉ ጋር መንገድ ላይ አየሁት ብሉ ነገረኝ። አዎ ምንም ይሁን ምን እያደር ልብ
ሲገዙ ነው የሚታወቀው» አለና የቤቱን ግድግዳ ባይኑ ዞረው፡፡ የእናቴን የየውብነሽ ልብ በፍርሃት ተበዝብዞ ፊታቸው ድንጋጢ በሚያሯሩጠው ደም ጢም
ኣለ።
ከተቀመጥኩበት ተነሥቼ «ምን ነገሩሁ? ምን አሉህ?» አልኩና የሰማውን ለመስማት ጓጓሁ። «እሱስ ይሁን፡ እንዲያው እስከ ዛሬ ለምን ደብቀሽኝ ብዬ ነው:: ነገ እነግርሃለሁ፡፡ አበጀህ! ጠላትም ወዳጅም ደስ አይበለው ብሎ ለመመለስ ሲጀምር «አሁኑኑ ብትነግረኝስ?» አልኩት፡፡
«ነገም እኮ ሩቅ አይደለም። ነገ ይሻላል» ብሎ ሊገባ ሲል «እኔም ብዙ ነገር እነግርሃለሁ» አልኩና እኔም ነገሩን ችላ አልኩት፡፡ እናቴ በፍርሃትና በጥርጣሬ እየዋለለች «ምን ሰምቶ ይሆን? ምን ነግረውት ይሆን ጌታዬ?» አለች
ከንፈሯ ሥር በሚንደፋደፉ ቃላት።
«ነገ በአንድ ላይ እንሰማዋለን» ብዬ ሊንቀሳቀስ የነበረውን ነገር እንዳጠፋ ልጅ ኮረኮምኩት፡፡ ነገሩ ሁለት ቤት ያለው ሆነና ራቴን በልቼ ወደ ቤቴ ተመለስኩ።
የዕለቱን ወሬ ለመስማት በከፍተኛ ጉጉት የምትጠባበቀዋ የወዲያነሽ፣ ከልጅዋ ጋር ስታወራ ደረስኩ እና ከጎኗ ተቀመጥኩ፡፡ ከእኛ ራቅ ብሎ በብረት
ምድጃ ውስጥ የተንተረከከው የከሰል ፍም የቢቱን አየር አሙቆታል። በወላጆቼ ቤት ስላጋጠመኝ ነገር አንድ በአንድ ጠየቀችኝ፡፡ የየወዲያነሽ ነገር ስለሆነብኝ ደከመኝና ታከተኝ ሳልል መለስኩላት፡፡ «እኛንስ መቼ ነው የምትወስደንና እጅ
ነሥተን፤ ጫማ ስመን፤ የሚሉንን የሚሉን?» አለችና የመንፈስ ጭንቀት ስለ ተሰማት አቀረቀረች። «በክብርና በይፋ ነው ይዤሽ የምቀርበው! ይህቺ የማከብራትና የምወዳት ባለቤቴ ናት ብዬ የምናገረውና የማስረዳው እኔ ነኝ፡፡በመለማመጥና በማጎብደድ ሳይሆን አባቴ በመሆኑና ለወላጅነቱ ክብር ብቻ ብዩ ያውም ክብረ ሕሊናሽን በማይነካ ሁኔታ እጅ ትነሺ ይሆናል» ብዬ አገጫን ይዤ አበረታታኋት።
«አንተ እንዳልከ! እኔ እንዲሁ ነው የምቀባጥረው» ብላ፤ ረጋ ባለ
እረማመድ ወደ ጓዳ ገባች፡፡ በውስጧ ፍርሃት እንደልቡ ይጨፍራል፡፡ከሠራተኛይቱ ጋር ራት አቀረቡ፡፡ መብላቴን ሳልናገር ደስ ይላት ዘንድ ዝግ ብዬ በላሁ። ጋሻዬነህ እንኳ ወግ ደርሶት «በእማምዬ ሞት፡ በእኔ ሞት» እያለ ደጋግሞ አጎረሰኝ፡፡ ዕለታዊ ድርጊት የአካባቢ ቅጂ ነው፡፡
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በኀይለመለኮት_መዋዕል
...ሰኞና ማክሰኛ ተከታታዮቹም ቀናት በየተራ አልፈው ቅዳሜ ደረሰ፡፡ሁላችንም በሐሳባችን እንደ ጸናን ሰነበትን
ቅዳሜ ከሰዓት በኋላ ዘጠኝ ተኩል ገደማ ላይ ደርሶ ብርድ ብርድ ስላለኝ ፀሐይ ለመሞቅ ምድረ ግቢው መኻል ተቀመጥኩ በየወዲያነሽ አእምሮ ውስጥ
ያለው ጥያቄ ሳይመለስ በመሰንበቱ ሥጋቷ አልተወገደም፡፡ በአንዲት ትንሽ ነጭ ፎጣ ብርጭቆ እየወለወለች ዝግ ብላ መጣችና “አሁን ነው እንዴ የምንሄደው? እ...!» ብላ ንግግሯን በጥያቄ አንጠለጠለችው::
«አንቺና ጋሻዬነህ የምትሄዱት ሌላ ጊዜ ነው:: ቀኑን እኔና አንቺ
እንወስነዋለን፡፡ ዛሬም ሆነ ነገ የምሄደው እኔ ነኝ። ከነዚያ ከተከለከሉ መጻሕፍት አንብባ የነገረችሽን የእስረኛዋን ጓደኛሽን የምክር ቃላት አትርሺ፡ መብት
የሚገኘው በትግል ነው፡፡ ጨቋኞች በሰላምና በውዴታ መብት እይሰጡም ብላ
ነግራኛለች አላልሽም? እኔና አንቺም» ብዬ ዝም አልኳት። ከጀመርኩት አርእስት ውጪ «አዎ እውነትህን ነው: ከመንገድ ሲገቡ ያላሰቡትን ያልሰሙትን ነገር ተናግሮ ክፉም ደግም መስማትና መናገር ለእርሳቸውም ሆነ
ለእኛ ነገር ማበላሸት ነው» ብላ የብርጭቆይቱን ጥራት ለማረጋገጥ ትክ ብላ ተመለከተቻት ንግግሯን ሰምቼ ዝም ስላልኩ ወደ ቤት ገባች፡፡
ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ አባቴን እንኳን ደኅና” መጣህ ለማለት ወደ ወላጆቼ ቤት ገሠገሥኩ፡፡
ባለፈው ጊዜ ወላጆቼን ለመጠየቅ ስሔድ ይጨመድደኝ የነበረው
ሥጋትና ፍርሃት እንዲሁም የሕሊና ረብሻ እጅግ በጣም ተቀነሰ። እረጋገጤ ደልዳላ ከመሆኑም በላይ ቀና ብዬ ተራመድኩ፡፡ ዱሮ ደረጃውን የምወጣው አንድ
በአንድ ሲሆን ዛሬ ግን ሁለትና ሦስቱን በአንድ ጊዜ አጠቃለልኩት። ደረጃውን
ጨርሼ ፊቴን ወደ በሩ መለስ ሳደርግ የብዙ ሰዎች ድምፅ ሰማሁ፡፡ ወደ ውስጥ ለመዝለቅ የነበረኝ ድፍረት ከፍ አለ። እቤቱ ውስጥ ለነበሩት ሁሉ ጎንበስ ብዬ
እጅ ነሣሁ፡፡ ከዚያም በቀጥታ ወደ አባቴ ሄድኩና እጅ ነሥቼ ጨበጥኩት።
«እንኳን ደኅና ገባህ! የሄድክበት ሁሉ ቀናህ! » አልኩና አንገቴን በትሕትና ሰበር አድርጌ ከፊቱ ገለል ብዬ ቆምኩ፡፡
እንኳን ደኅና ቆያችሁኝ አዎ ደኅና ደርሼ መጣ። ሁሉም ደህና
ቆየኝ። ክብሩ ይስፋ!ና! እዚች አጠገቤ ና አጠገቡ የነበረውን ወንበር በጣቱ አሳየኝ። እንኳን በደህና ገቡ ለማለት ያመጡትንና ሌሎችንም እንግዶች አንድ
በአንድ አየኋቸው፡፡ በሰዎች ላይ የሚታየው ፈገግታና የአቀማመጣቸው ሁናቴ
የተለያየ በመሆኑ አባቴን በተለያየ የአስተሳሰብ ደረጃ እንደሚመለከቱት ያስታውቃል። አንዳንዱ ውስጣዊ ጭንቀት አስገድዶት በግድ ፈገግ ብሏል።
ለማስደሰትና በግድ ለመደሰት ብሉ በደረቅ ፈገግታ ፊቱን ያጨማደደም አለ።የአንዳንዶቹን ፊት ደግሞ የበታችነት ስሜት ስለተጫነው ፊታቸው ከልቅሶ በኋላ የሚታይ ፊት እንጂ ለደስታ የቀረበ ገጽታ አይመስልም፡፡
ሁለትና ሦስቱን እንደ አባቴ የቅርብ ጓደኞች ስለምመለከታቸው በእነርሱ ላይ የነበረኝን ጥላቻ ለመርሳትም ሆነ ለማሻሻል ያለኝ አቅም በጣም አነስተኛ ነበር። ሕሊናዬ ዘወትር ይበቀላቸዋል፡፡ ወረቀት እያገላበጡ የሚዶልቱት ሁሉ ትውስ ሲለኝ፡ የሰውን ሕልውና አርደውና አወራርደው የሚገድሉ ይመስሉኛል።
ክርክርና ወሬ ሲጀምሩ ማንም በአጠገባቸው እንዲያልፍ ስለማይፈልጉ ዓለምን
የተንኮል ገበያ እንጂ የመልካም ምግባር አደባባይ እንድትሆን የሚያስቡ አይመስሉም፡፡ እናቴ እንኳን ደበቅ እያለች «መጡ ደግሞ እነ ጋጠው ገሽልጠው»
ትላቸው ነበር፡፡
ለእኔም እንደ እንግዶቹ ጠላ ደረሰኝ፡፡ ከዚህም ከዚያም የሚመጣውን ወሬ እየሰማሁ ጠላዬን ሁለት፣ ሦስት ጊዜ አስሞላሁ፡፡ እንግዶቹ አንድና ሁለት እየሆኑ ተራ በተራ እጅ እያነሡ ሄዱ።
እናቴና የውብነሽ ከአሁን አሁን ተናግሮ ጉድ ይፈላ ይሆን በማለት
በአስጨናቂ ሐሳብ እንደሚሠቃዩ ስጋታቸው በየፊታቸው ላይ ይታወቃል፡፡ ከእኔ ጋር ማዶ ለማዶ መፋጠጡን ስለ ጠሉት ሁለቱም ወደ ማድ ቤት ወረዱ፡፡
እኔና አባቴ በጣም በመጠነኛ መግባባት ስለ ጭሰኛ' ስለ ግብር' ስለ ሲሶና እርቦ ስለ ገሚስና ከአሥር አንድ፣ እንዲሁም ስለ ሕግና ስለ እኔ የልጅነት ዓመታት እስከ ምሽቱ ሁለት ሰዓት እንደነገሩ አወራን። ከዚያ በኋላ
ግን፡ እነዚያ ለሁለት ሳምንት የተለዩት የወንጀለኛ መቅጫና የፍትሐ ብሔር ሕግ መጻሕፍት ትዝ ስላሉት «ትንሽ ሥራ አለብኝ፡ ከእናትህና ከአጎትህ ጋር ተጫወት» ብሎኝ ወደ መኝታ ቤት ገባ።
ከአባቴ ጋር ተዝናንቼ ሳወራና ስጫወት በመልሶቼም እየተማመንኩ ስመልስ የመጀመሪያ ጊዜ ነበር፡፡ አባቴ ገባ ከማለቱ እኅቴና እናቴ ተካ አሉ።
የፌሩት ጉዳይ ባለመነገሩ የሁለቱም ፊት ፈገግታ አጋተ። ሩብ ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ አባቴ እንደገና ተመልሶ መጣ። ኖር ብለን ተቀበልነው። እምብዛም
ሳይጠጋ ቆም አለና እነዚያን በዕድሜና በክርክር ጽሑፍ ንባብ የተዳከሙ ዐይኖቹን በግራ እጅ ጣቶች እያሻሸ ሳልነግርህ እንዳትሄድ ብዬ ነው የተመለስኩት ዘንድሮስ በጣም ጎብዘሃል አሉ፡፡ መቼ እንደሆነ አላውቅም፡ አንድ ወዳጂ ሰዉ ጋር መንገድ ላይ አየሁት ብሉ ነገረኝ። አዎ ምንም ይሁን ምን እያደር ልብ
ሲገዙ ነው የሚታወቀው» አለና የቤቱን ግድግዳ ባይኑ ዞረው፡፡ የእናቴን የየውብነሽ ልብ በፍርሃት ተበዝብዞ ፊታቸው ድንጋጢ በሚያሯሩጠው ደም ጢም
ኣለ።
ከተቀመጥኩበት ተነሥቼ «ምን ነገሩሁ? ምን አሉህ?» አልኩና የሰማውን ለመስማት ጓጓሁ። «እሱስ ይሁን፡ እንዲያው እስከ ዛሬ ለምን ደብቀሽኝ ብዬ ነው:: ነገ እነግርሃለሁ፡፡ አበጀህ! ጠላትም ወዳጅም ደስ አይበለው ብሎ ለመመለስ ሲጀምር «አሁኑኑ ብትነግረኝስ?» አልኩት፡፡
«ነገም እኮ ሩቅ አይደለም። ነገ ይሻላል» ብሎ ሊገባ ሲል «እኔም ብዙ ነገር እነግርሃለሁ» አልኩና እኔም ነገሩን ችላ አልኩት፡፡ እናቴ በፍርሃትና በጥርጣሬ እየዋለለች «ምን ሰምቶ ይሆን? ምን ነግረውት ይሆን ጌታዬ?» አለች
ከንፈሯ ሥር በሚንደፋደፉ ቃላት።
«ነገ በአንድ ላይ እንሰማዋለን» ብዬ ሊንቀሳቀስ የነበረውን ነገር እንዳጠፋ ልጅ ኮረኮምኩት፡፡ ነገሩ ሁለት ቤት ያለው ሆነና ራቴን በልቼ ወደ ቤቴ ተመለስኩ።
የዕለቱን ወሬ ለመስማት በከፍተኛ ጉጉት የምትጠባበቀዋ የወዲያነሽ፣ ከልጅዋ ጋር ስታወራ ደረስኩ እና ከጎኗ ተቀመጥኩ፡፡ ከእኛ ራቅ ብሎ በብረት
ምድጃ ውስጥ የተንተረከከው የከሰል ፍም የቢቱን አየር አሙቆታል። በወላጆቼ ቤት ስላጋጠመኝ ነገር አንድ በአንድ ጠየቀችኝ፡፡ የየወዲያነሽ ነገር ስለሆነብኝ ደከመኝና ታከተኝ ሳልል መለስኩላት፡፡ «እኛንስ መቼ ነው የምትወስደንና እጅ
ነሥተን፤ ጫማ ስመን፤ የሚሉንን የሚሉን?» አለችና የመንፈስ ጭንቀት ስለ ተሰማት አቀረቀረች። «በክብርና በይፋ ነው ይዤሽ የምቀርበው! ይህቺ የማከብራትና የምወዳት ባለቤቴ ናት ብዬ የምናገረውና የማስረዳው እኔ ነኝ፡፡በመለማመጥና በማጎብደድ ሳይሆን አባቴ በመሆኑና ለወላጅነቱ ክብር ብቻ ብዩ ያውም ክብረ ሕሊናሽን በማይነካ ሁኔታ እጅ ትነሺ ይሆናል» ብዬ አገጫን ይዤ አበረታታኋት።
«አንተ እንዳልከ! እኔ እንዲሁ ነው የምቀባጥረው» ብላ፤ ረጋ ባለ
እረማመድ ወደ ጓዳ ገባች፡፡ በውስጧ ፍርሃት እንደልቡ ይጨፍራል፡፡ከሠራተኛይቱ ጋር ራት አቀረቡ፡፡ መብላቴን ሳልናገር ደስ ይላት ዘንድ ዝግ ብዬ በላሁ። ጋሻዬነህ እንኳ ወግ ደርሶት «በእማምዬ ሞት፡ በእኔ ሞት» እያለ ደጋግሞ አጎረሰኝ፡፡ ዕለታዊ ድርጊት የአካባቢ ቅጂ ነው፡፡
👍3
#የተወጋ_ልብ
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ፀጉሩን ተላጨና ቁምጣ ሱሪውን አወለቀ! በምትኩ ቀጭን ቦላሌውን ለበሰ፡፡ ከላይ ሸሚዝና ኮቱን ደርቦ ሽክ.. ኳ! ብሎ ሲታይ ያ ጎንቻ! ያ አስፈሪው ጎንቻ! ያ ባለጎፈሬው ሽፍታ! መሆኑን እንኳንስ የማያውቀው የሚ
ያውቀውም ቢሆን ለማመን ይቸገር ነበር፡፡ውስጣዊ እሱነቱ ሳይሆን ውጫዊ ማንነቱ ተቀይሯል። የከተማው ሰው
የሚለብሰውን ልብስ ለብሶ ሰው መሰል አውሬነቱን የሚያሳስት አይነት ሆኗል።
በዚያች ምሽት በጠፍ ጨረቃ ከዓለሚቱ ጋር ተያይዘው ጠፉ... ከኢተያ ከተማ እስከ ዴራ ከተማ በእግራቸው ተጓዙ በሌሊት መኪና ተሳፈሩና ናዝሬት ገቡ፡፡ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ ወደዚያ የከተማ ጫካ፣ ወደዚያ የከተማ ዋሻ ገብተው ሊደባለቁ በአዲስ አበባ መኪና ላይ ተሳፈሩ። ከእንግዲህ በኋላ ጎንቻን ፈልጎ ማግኘት ከእንግዲህ በኋላ ዓላሚቱን ፈልጎ
ማግኘት ቁና አሸዋ ውስጥ የወደቀች ጤፍ ለማግኘት እንደመሞከር ነው፡፡ ከእንግዲህ ወዲያ ዓለሚቱ ባሏን ያስገደለች እየተባለች ከምትጠበስበት የሀሜት ምላስ ልትድን እፎይ ልትል ነው፡፡ እነኝያ የገደ ቢስ
ልጆች ጨርሰው ከዐይኖቿ ሊርቁላትና ሰላማዊ ሰዎች መስለው ከአዲስ አበባ ህዝብ ጋር ሊቀላቀሉ የቀራቸው በሰዓታት የሚቆጠር ጊዜ ብቻ
ነው፡፡
ከእንግዲህ ወዲያ የጎንቻን ፍቅር ሙቀቱ እስከሚያቃጥላት ድረስ እንደ ልቧ ልትሟሟቀው ሁኔታው ተመቻችቶላታል። ከእንግዲህ በኋላ የልታጌጥ፣ እንደፈለገችው ልትዘል፣ ልትቦርቅ ልጓሙ ተፈቶላታል።
ጎንቻም አንጎሉን ሲያዞረው በኖረው በዓለሚቱ ፍቅር ወፈፍ በሚያደርገው በዓለሚቱ ናፍቆት ክፉኛ ተጎድቶ ነበር። አብዛኛውን ጊዜ በጫካ ውስጥ ትዝታዋን ብቻ እያቀፈ በማደር ሲሰቃይ ኖሯልና ናፍቆቷ ነፍሱን መንጥቆ ሳያወጣው በፊት ጥሩ ዘዴ ፈጥራ ይዛው በመኮብለሏ አልተከፋም፡፡ያንን ቢያሽተው ቢምገው የማይጠግበው መዓዛዋን በየቀኑ በየደቂቃው ሊያጣጥመው ነውና ኩብለላው ብዙም አላስጨነቀውም ነበር። የተሳፈሩበት ሎንቺና ወስዶ ለገሃር ጣላቸው፡፡
ጎንቻ ከጫካ ያመለጠ አውሬነቱ የታወቀው ገና ከመኪና ላይ እንደወረደ ነበር፡፡ ተይዛ ያመለጠች ሚዳቋ መሰለ፡፡ ሽው!...ሽው!... ውር!... ውር
በሚሉት መኪኖች መሀል ሲገባ ሮጦ ሊያመልጥ ሞከረ። እንጣጥ!
እንጣጥ! እያለ የአንዱ መኪና ራት ሊሆን ትንሽ ቀረው። መንገዱ መሀል ሲደርስ ሰግጠጥ.. ሰግጠጥ እያደረገው አንዴ ወደ ፊት አንዴ ደግሞ ወደ ኋላ ለማምለጥ ዓለሚቱን ክፉኛ ታገላት።እሷም መደናበሯ አልቀረም ቆይ ጎንቻዬ እኔን ተከተለኝ፡፡ ቀስ በል። እኔ ወደምሄድበት ረጋ ብለህ ተራመድ። መኪኖቹን አትመልከት። ያዞርሃል ... ቀስ ...አዎ እንደሱ ጎሽ
..እጆቹን ግጥም አድርጋ ያዘችው እንደምንም ብለው እየተጓተቱ አስፋልቱን ተሻገሩ።
“እሺ ...አዞረኝ እኮ…ቆይ ቁጭ ልበል" አላት፡፡ ደገፈችውና ወደ አንድ ህንፃ አጥር ጥግ ሄዱ፡፡ ተረከዙ ላይ እንደ ዝንጀሮ ቁጢጥ አለ፡፡ ጭውው..አለበት። ጭንቅላቱን በሁለት እጆቹ ያዘው። ዐይኖቹ ጭፍን ክድን ጭፍን
ክድን አሉ፡፡ መኪና ላይ ያልተሰማው የማጥወልወል ስሜት ተሰማው፡፡
"ርቦህ ይሆናል ጌታዬ ርቦህ ነው። ቆይ እዚህ ጋር የማየው ሆቴል ቤት ነው መሰለኝ" ባሻገር ከሚታየው ቤት ላይ ጣቷን ቀስራ አሳየችው።ቆዳቸው የተገፈፈ በጎች ሳይበለቱ ተሰቅለዋል። የሰንጋ ብልቶች በአይነት በአይነታቸው በስርአት ተዘጋጅተው በወረንጦ ላይ ተንጠልጥለዋል፡፡
ልክ ነው ምግብ ቤት ነው" አለችውና ከተቀመጠበት አስነስታው ተያይዘው
ትደጋግፈው ወደ ስጋ ቤቱ አመሩ....
የሚበላ ነገር አለ?" ብላ ጠየቀች፡፡
“አዎን!” አለ ሻጩ፡፡
“ምን አለ?"
“ሁሉም ነገር አለ፡፡ የፈለጋችሁትን..." ወደ ውስጥ እንደመዝለቅ አለችና የሻጩን ዐይን ዐይን በልምምጥ ተመለከተችው።
“በል እስቲ ቀይ ወጥ በእንጀራ..“ፈራ ተባ እያለች ጠየቀቸው። ዓለሚቱ ከልጁ ጋር ስትነጋገር ጎንቻን እንደ ህፃን ልጅ ግራ እጁን ግጥም አድርጋ
ይዛው ነበር፡፡ ጎንቻ...ያ ወንዱ..ጎንቻ... ያ አስፈሪው ጎንቻ አስፈሪነቱ ጀግንነቱ ከሹሩባው ጋር አብሮ እንደተላጨ ሁሉ ወኔው በኛሮ ጫካ ውስጥ ተጥሎ እንደቀረ ሁሉ ዐይኖቹ ፈጠው ርቦት ሲቁለጨለጭ ቀበሮ
የፈሳባት ጦጣ መስሎ ሲታይ እሱነቱን የማይክድ አልነበረም።
“በሉ ጥፉ ከዚህ! ፋራዎች! ገገማዎች! ይሄ የሥጋ መሸጫ ሉካንዳ እንጂ የእንጀራ መሽጫ ጉሊት መስለሽ?! አይተሽ አትጠይቂም?!” ጮኸባት።
ሽምቅቅ አሉ፡፡ አቤት አደነጋገጥ ወጥቶ ፀብ እንዳይፈጥር ጎንቻም በንዴት እልህ ውስጥ እንዳይገባና ገና አንዱንም ሳይይዙት መዘዝ ውስጥ እንዳይገባ ፈራች ፀብ ከተፈጠረ ፖሊስ ይዞ እንዳያንገላታቸው ስጋት አደረባትና
ዐይኖቹ መቅላት ልቡ የንዴት ደም መርጨት ሰውነቱ መቆጣት
የጀመረው ጎንቻን ሙጭጭ አድርጋ ይዛ የስድብ መዓት ከሚያወርድባቸው ጎረምሳ ሽሹ...ጎንቻ አንድ ቂም በልቡ ቋጠረ፡፡ ርቦት ሆዱ የእህል
ያለህ! በሚልበት ሰዓት ወስፋት የሚቆልፍና ወሽመጥ የሚበጥስ የስድብ መርዝ ቀመሰ። እንደምንም ብለው እየተጓተቱ ሄዱና እንጀራ የሚሽጥበት ምግብ ቤት በጠቋሚ አገኙ። በሉ፣ጠጡ፣ ጠገቡ። ጊዜው እየመሸ
ሲመጣ አሁንም በጥቆማ አልቤርጎ ተከራዩ። ምን ችግር አለ? ብር እንደሆነ ዕድሜ ለጎንቻ! በሽበሽ ነው፡፡ ከሰባት ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ይዘዋል። ጎንቻን ትንሽ ያስቸገረው መብራቱ ነበር፡፡ ብርሃን በጣም በዛበት። ዐይኑ በአንድ ጊዜ የአምፖሉን ብርሃን መቋቋም አልቻለም፡፡
ሊተኙ አካባቢ አምፖሉን ቀድሞ ለማጥፋት የሞከረው እሱ ነበር፡፡ “ኡፍ ኡፍፍ. ኡፍፍፍ..!" እንደ ኩራዙ ሞከረ። በኋላ ግን ዓለሚቱ በድርጊቱ እየሳቀች ማጥፊያውን ቀጭ... ቋ! አድርጋ አጠፋችውና በችሎታዋ እየተኩራራችበት ተቃቅፈው ተኙ፡፡
ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት አካባቢ ጎንቻ ሽንቱ ወጠረውና የመኝታ ቤቱን በር ቷ! አድርጎ ከፍቶ ወጣ፡፡ የተከፈተውን ድምፅ የሰማው ሽማግሌ ዘበኛ
“ማነው?” አለ በተጎተተ ድምፅ፡፡
"እኔ ነኝ!" አለ ጎንቻ።
"ወዴት ነው?"
ለውሃ ሽንት!"
“የውሃ ሽንት ተሆነ ቦቦው አለልህ አይደለም?! የት ልትሸና ነው? አሁን የሽንት ቤቱ በር ቁልፍ ነው" አለና ዘበኛው ቁጣ ቀረሽ መልስ ሰጠው፡፡
"የምን ቦቦ ነው የምትለኝ ጃል?! ሽንቴ መጥቷል እኮ ነው የምልህ!... "
በዘበኛው ኃይለ ቃል ልክ መለሰለት።
“ጤናም የለው እንዴ ሰውየው?" ዘበኛው ካፖርቱን እላዩ ላይ ጣል
አድርጎ አጭር ዱላውን ይዞ ወጣ፡፡
ሂድ ግባ! ቦቦው የተዘጋጀው ላንተ እኮ ነው!" አለና ጮኹ፡፡
“የት ነው የምሄድልህ?!"
"አልጋው ስር አለልህ እኮ ነው የምልህ!"
“አልጋ ስር ሽና ነው የምትለኝ?!"
እዚህ ደጅ ግን መሽኛ ቦታ የለም! ያንተ ቢጤ ሰካራሞች ናቸው እዚህ እንኳን አልጋ ስር አልጋህም ላይ ሽናው! እሱ የኔ ችግር አይደለም!
ሽንታቸውን እየሸኑ የጉንፋን መጫወቻ ያደረጉኝ!” በንዴት ጮኸ፡ በዚህ በሁለቱ ጭቅጭቅ መሃል ዓለሚቱ ልቧ በፍርሃት ተውጦ እያዳመጠች ና። የውሽማዋን አመል ስለምታውቅ ሽማግሌውን ሲጥ!
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በትክክል_ገና
...ፀጉሩን ተላጨና ቁምጣ ሱሪውን አወለቀ! በምትኩ ቀጭን ቦላሌውን ለበሰ፡፡ ከላይ ሸሚዝና ኮቱን ደርቦ ሽክ.. ኳ! ብሎ ሲታይ ያ ጎንቻ! ያ አስፈሪው ጎንቻ! ያ ባለጎፈሬው ሽፍታ! መሆኑን እንኳንስ የማያውቀው የሚ
ያውቀውም ቢሆን ለማመን ይቸገር ነበር፡፡ውስጣዊ እሱነቱ ሳይሆን ውጫዊ ማንነቱ ተቀይሯል። የከተማው ሰው
የሚለብሰውን ልብስ ለብሶ ሰው መሰል አውሬነቱን የሚያሳስት አይነት ሆኗል።
በዚያች ምሽት በጠፍ ጨረቃ ከዓለሚቱ ጋር ተያይዘው ጠፉ... ከኢተያ ከተማ እስከ ዴራ ከተማ በእግራቸው ተጓዙ በሌሊት መኪና ተሳፈሩና ናዝሬት ገቡ፡፡ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ ወደዚያ የከተማ ጫካ፣ ወደዚያ የከተማ ዋሻ ገብተው ሊደባለቁ በአዲስ አበባ መኪና ላይ ተሳፈሩ። ከእንግዲህ በኋላ ጎንቻን ፈልጎ ማግኘት ከእንግዲህ በኋላ ዓላሚቱን ፈልጎ
ማግኘት ቁና አሸዋ ውስጥ የወደቀች ጤፍ ለማግኘት እንደመሞከር ነው፡፡ ከእንግዲህ ወዲያ ዓለሚቱ ባሏን ያስገደለች እየተባለች ከምትጠበስበት የሀሜት ምላስ ልትድን እፎይ ልትል ነው፡፡ እነኝያ የገደ ቢስ
ልጆች ጨርሰው ከዐይኖቿ ሊርቁላትና ሰላማዊ ሰዎች መስለው ከአዲስ አበባ ህዝብ ጋር ሊቀላቀሉ የቀራቸው በሰዓታት የሚቆጠር ጊዜ ብቻ
ነው፡፡
ከእንግዲህ ወዲያ የጎንቻን ፍቅር ሙቀቱ እስከሚያቃጥላት ድረስ እንደ ልቧ ልትሟሟቀው ሁኔታው ተመቻችቶላታል። ከእንግዲህ በኋላ የልታጌጥ፣ እንደፈለገችው ልትዘል፣ ልትቦርቅ ልጓሙ ተፈቶላታል።
ጎንቻም አንጎሉን ሲያዞረው በኖረው በዓለሚቱ ፍቅር ወፈፍ በሚያደርገው በዓለሚቱ ናፍቆት ክፉኛ ተጎድቶ ነበር። አብዛኛውን ጊዜ በጫካ ውስጥ ትዝታዋን ብቻ እያቀፈ በማደር ሲሰቃይ ኖሯልና ናፍቆቷ ነፍሱን መንጥቆ ሳያወጣው በፊት ጥሩ ዘዴ ፈጥራ ይዛው በመኮብለሏ አልተከፋም፡፡ያንን ቢያሽተው ቢምገው የማይጠግበው መዓዛዋን በየቀኑ በየደቂቃው ሊያጣጥመው ነውና ኩብለላው ብዙም አላስጨነቀውም ነበር። የተሳፈሩበት ሎንቺና ወስዶ ለገሃር ጣላቸው፡፡
ጎንቻ ከጫካ ያመለጠ አውሬነቱ የታወቀው ገና ከመኪና ላይ እንደወረደ ነበር፡፡ ተይዛ ያመለጠች ሚዳቋ መሰለ፡፡ ሽው!...ሽው!... ውር!... ውር
በሚሉት መኪኖች መሀል ሲገባ ሮጦ ሊያመልጥ ሞከረ። እንጣጥ!
እንጣጥ! እያለ የአንዱ መኪና ራት ሊሆን ትንሽ ቀረው። መንገዱ መሀል ሲደርስ ሰግጠጥ.. ሰግጠጥ እያደረገው አንዴ ወደ ፊት አንዴ ደግሞ ወደ ኋላ ለማምለጥ ዓለሚቱን ክፉኛ ታገላት።እሷም መደናበሯ አልቀረም ቆይ ጎንቻዬ እኔን ተከተለኝ፡፡ ቀስ በል። እኔ ወደምሄድበት ረጋ ብለህ ተራመድ። መኪኖቹን አትመልከት። ያዞርሃል ... ቀስ ...አዎ እንደሱ ጎሽ
..እጆቹን ግጥም አድርጋ ያዘችው እንደምንም ብለው እየተጓተቱ አስፋልቱን ተሻገሩ።
“እሺ ...አዞረኝ እኮ…ቆይ ቁጭ ልበል" አላት፡፡ ደገፈችውና ወደ አንድ ህንፃ አጥር ጥግ ሄዱ፡፡ ተረከዙ ላይ እንደ ዝንጀሮ ቁጢጥ አለ፡፡ ጭውው..አለበት። ጭንቅላቱን በሁለት እጆቹ ያዘው። ዐይኖቹ ጭፍን ክድን ጭፍን
ክድን አሉ፡፡ መኪና ላይ ያልተሰማው የማጥወልወል ስሜት ተሰማው፡፡
"ርቦህ ይሆናል ጌታዬ ርቦህ ነው። ቆይ እዚህ ጋር የማየው ሆቴል ቤት ነው መሰለኝ" ባሻገር ከሚታየው ቤት ላይ ጣቷን ቀስራ አሳየችው።ቆዳቸው የተገፈፈ በጎች ሳይበለቱ ተሰቅለዋል። የሰንጋ ብልቶች በአይነት በአይነታቸው በስርአት ተዘጋጅተው በወረንጦ ላይ ተንጠልጥለዋል፡፡
ልክ ነው ምግብ ቤት ነው" አለችውና ከተቀመጠበት አስነስታው ተያይዘው
ትደጋግፈው ወደ ስጋ ቤቱ አመሩ....
የሚበላ ነገር አለ?" ብላ ጠየቀች፡፡
“አዎን!” አለ ሻጩ፡፡
“ምን አለ?"
“ሁሉም ነገር አለ፡፡ የፈለጋችሁትን..." ወደ ውስጥ እንደመዝለቅ አለችና የሻጩን ዐይን ዐይን በልምምጥ ተመለከተችው።
“በል እስቲ ቀይ ወጥ በእንጀራ..“ፈራ ተባ እያለች ጠየቀቸው። ዓለሚቱ ከልጁ ጋር ስትነጋገር ጎንቻን እንደ ህፃን ልጅ ግራ እጁን ግጥም አድርጋ
ይዛው ነበር፡፡ ጎንቻ...ያ ወንዱ..ጎንቻ... ያ አስፈሪው ጎንቻ አስፈሪነቱ ጀግንነቱ ከሹሩባው ጋር አብሮ እንደተላጨ ሁሉ ወኔው በኛሮ ጫካ ውስጥ ተጥሎ እንደቀረ ሁሉ ዐይኖቹ ፈጠው ርቦት ሲቁለጨለጭ ቀበሮ
የፈሳባት ጦጣ መስሎ ሲታይ እሱነቱን የማይክድ አልነበረም።
“በሉ ጥፉ ከዚህ! ፋራዎች! ገገማዎች! ይሄ የሥጋ መሸጫ ሉካንዳ እንጂ የእንጀራ መሽጫ ጉሊት መስለሽ?! አይተሽ አትጠይቂም?!” ጮኸባት።
ሽምቅቅ አሉ፡፡ አቤት አደነጋገጥ ወጥቶ ፀብ እንዳይፈጥር ጎንቻም በንዴት እልህ ውስጥ እንዳይገባና ገና አንዱንም ሳይይዙት መዘዝ ውስጥ እንዳይገባ ፈራች ፀብ ከተፈጠረ ፖሊስ ይዞ እንዳያንገላታቸው ስጋት አደረባትና
ዐይኖቹ መቅላት ልቡ የንዴት ደም መርጨት ሰውነቱ መቆጣት
የጀመረው ጎንቻን ሙጭጭ አድርጋ ይዛ የስድብ መዓት ከሚያወርድባቸው ጎረምሳ ሽሹ...ጎንቻ አንድ ቂም በልቡ ቋጠረ፡፡ ርቦት ሆዱ የእህል
ያለህ! በሚልበት ሰዓት ወስፋት የሚቆልፍና ወሽመጥ የሚበጥስ የስድብ መርዝ ቀመሰ። እንደምንም ብለው እየተጓተቱ ሄዱና እንጀራ የሚሽጥበት ምግብ ቤት በጠቋሚ አገኙ። በሉ፣ጠጡ፣ ጠገቡ። ጊዜው እየመሸ
ሲመጣ አሁንም በጥቆማ አልቤርጎ ተከራዩ። ምን ችግር አለ? ብር እንደሆነ ዕድሜ ለጎንቻ! በሽበሽ ነው፡፡ ከሰባት ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ይዘዋል። ጎንቻን ትንሽ ያስቸገረው መብራቱ ነበር፡፡ ብርሃን በጣም በዛበት። ዐይኑ በአንድ ጊዜ የአምፖሉን ብርሃን መቋቋም አልቻለም፡፡
ሊተኙ አካባቢ አምፖሉን ቀድሞ ለማጥፋት የሞከረው እሱ ነበር፡፡ “ኡፍ ኡፍፍ. ኡፍፍፍ..!" እንደ ኩራዙ ሞከረ። በኋላ ግን ዓለሚቱ በድርጊቱ እየሳቀች ማጥፊያውን ቀጭ... ቋ! አድርጋ አጠፋችውና በችሎታዋ እየተኩራራችበት ተቃቅፈው ተኙ፡፡
ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት አካባቢ ጎንቻ ሽንቱ ወጠረውና የመኝታ ቤቱን በር ቷ! አድርጎ ከፍቶ ወጣ፡፡ የተከፈተውን ድምፅ የሰማው ሽማግሌ ዘበኛ
“ማነው?” አለ በተጎተተ ድምፅ፡፡
"እኔ ነኝ!" አለ ጎንቻ።
"ወዴት ነው?"
ለውሃ ሽንት!"
“የውሃ ሽንት ተሆነ ቦቦው አለልህ አይደለም?! የት ልትሸና ነው? አሁን የሽንት ቤቱ በር ቁልፍ ነው" አለና ዘበኛው ቁጣ ቀረሽ መልስ ሰጠው፡፡
"የምን ቦቦ ነው የምትለኝ ጃል?! ሽንቴ መጥቷል እኮ ነው የምልህ!... "
በዘበኛው ኃይለ ቃል ልክ መለሰለት።
“ጤናም የለው እንዴ ሰውየው?" ዘበኛው ካፖርቱን እላዩ ላይ ጣል
አድርጎ አጭር ዱላውን ይዞ ወጣ፡፡
ሂድ ግባ! ቦቦው የተዘጋጀው ላንተ እኮ ነው!" አለና ጮኹ፡፡
“የት ነው የምሄድልህ?!"
"አልጋው ስር አለልህ እኮ ነው የምልህ!"
“አልጋ ስር ሽና ነው የምትለኝ?!"
እዚህ ደጅ ግን መሽኛ ቦታ የለም! ያንተ ቢጤ ሰካራሞች ናቸው እዚህ እንኳን አልጋ ስር አልጋህም ላይ ሽናው! እሱ የኔ ችግር አይደለም!
ሽንታቸውን እየሸኑ የጉንፋን መጫወቻ ያደረጉኝ!” በንዴት ጮኸ፡ በዚህ በሁለቱ ጭቅጭቅ መሃል ዓለሚቱ ልቧ በፍርሃት ተውጦ እያዳመጠች ና። የውሽማዋን አመል ስለምታውቅ ሽማግሌውን ሲጥ!
👍4❤2
#ያልታበሱ_እንባዎች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....ጥቂት ቀናት አለፉ። አንድ ቀን ምሽት ላይ በልሁና መርዕድ በምህጻረ ቃል አምሆ ተብሎ በሚጠራው ሆቴል ውስጥ ከውጭ ወደ ቡና ቤቱ ሲገቡ በስተቀኝ በኩል በምትገኝ ብቸኛ ጠረጴዛ ላይ ቁጭ ብለው ከአንዲት የቡና ቤቱ እስተናጋጅ
ጋር እየተቃለዱ ይጠጣሉ። ከጠረጴዛው ፊትለፊት ያለው ባንኮኒና የቡና ማሽን ብቻ
ስለሆነ ቦታው እንደ ልብ ለመጫወት አመቺ ነው። የቀልዳቸውና የጭውውታቸው
ማዕከልም የመርዕድ ዓይን አፋርነት ነው:: አስተናጋጇ ባህሪውን ቀደም ብላ ስለምታውቅ በነገር እየነካካች ታሳፍረው ይዛለች፡፡መቼም የአንተን ድንግል የምወስደው እኔ ነኝ፡፡» ትለዋለች ጉልበቱንና ጭኖቹን እያሻሸች።
«እስቲ እንደ ምንም ብለሽ ገላግይው::» በልሁ እየሳቀ፡፡
«አቦ ተይኝና ሌላ ወሬ አምጪ!» ይላል መርዕድ የአስተናጋጇን እጅ ከላዩ ላይ ለማንሳት እየሞከረ።
አይዞህ! ቦታውን እንደሆነ እኔው ራሴ አሳይሃለሁ፡፡» አስተናጋጇ አሁንም።
«እንዲህ ከመባል ሞት ይሻላል መርዕድ!» እያለ በልሁ ይስቃል::
እንዲህና እንዲያ እያሉ በመጫወት ላይ ሳሉ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል አካባቢ ሁለት ሰዎች ተከታትለው ወደ ቡና ቤቱ ገቡና ግራ ቀኝ ተመለከቱ፡፡ ከበሩ
በስተግራ በኩል ያለው ዋናው ሳሎን በሰው ተሞልቷል። በቀኝ በኩል ያለችው ጠረጴዛ ደግሞ በእነበልሁ ተይዛለች። በቀጥታ ወደ ባንኮኒው በመጠጋት ጀርባቸውን ለእነበልሁ ሰጥተው ቆሙ:: ወዲያው ደግሞ በድሉ አሸናፊ ከውጭ መጥቶ
ተቀላቀላቸው:: እሱ ከመሀል ሌሎቹ ግራና ቀኝ በመሆን ፈንጠር ፈጠር ብለው ተደረደሩና የሚጠጡትን አዘዙ፡፡ ለሁሉም አረቄ ቀረበላቸው ::
በልሁ ግን ቅፍፍ ይለው ጀመር፡፡ እሱና በድሉ ቀድሞም ተዳፍጠው ነበር የኖሩት. ዜሬ ደግሞ ገና ሲገባ ገልመጥ አድርጎት ነበርና
እንዲሁም ከተማ ውስጥ አይቷቸው ከማያውቃቸው ሰዎች ጋር ገጥሟልና ጥርጣሬ ገባው መጠጥ አወሳሰዳቸውም አላምር አለው ግልብጥ ግልብጥ ያደርጉታል። በሹክሹክታም ሲወያዩ ያያቸዋል። ወደ ኋላቸው ዞር እያሉ ሲገላምጡት ያይ ጀመር
መርዕድና አስተናጋጇ የሚያወሩትን ትቶ እነ በድለን መከታተል ቀጠለ፡፡
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ ከምሽቱ ሁለት ሰአት አለፈ። የመደመጥ እድሉን እዚያው የተፈጠረበት አገር ረስቶ የመጣው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በቡና ቤቱ ውስጥ ተከፍቶ ያለ ምንም አድማጭ ለራሱ ይጮሀል። ዜና እወጃውን ጨርሶ የግብርና ፕሮግራም ማስተላለፍ ጀምሯል።የመስኖ ስራ እንቅስቃሴ እያሳየ ገበሬዎች ያገኙትን ጠቀሜታ ይዘረዝራል።
በድለና ጓደኞቹ ከቴሌቪዥኑ ፕሮግራም ጋር የተያያዘ ወሬ ማውራት ጀመሩ። ያም ቢሆን ከበልሁ ጀሮ ደረሰና እሱም በጥንቃቄ ያዳምጥ ጀመር፡፡ከበድሉ በስተቀኝ በኩል ከቡና ማሽኑ አጠገብ ቆሞ የሚጠጣው የበድሎ ጓደኛ "ስሚ አንቺ"
ሲል ጨራት ከባንኮኒ ውስጥ ቆማ የነበረችውን አስተናጋጅ።
«አቤት» አለችው።
የኢትዮጵያ ገበሬዎች ቴሌቪዥን ገዙ ወይስ እኔና አንቺን ገበሬ ለማድረግ ተፈልጎ ነው ይኸ ፕሮግራም የሚተላለፈው ? ሲል ጮክ ባለ ድምፅ ጠየቃት።
«እኔ ምን አወቄ?» አልች አስተናጋጇ።
«የከተማ ገበሬ ሞልቷሌ አትይውም!» አላት ሌላው የበድሉ ጓደኛ ከግራ በኩል ሆኖ ወደ ኋላ
ዞር ብሎ በልሁንም አየት አደረገው፡፡
«ይኽ ከየጓሮው ወፍ ዘራሽ ቡና የሚለቅመው?» ሲል የመጀመሪያው ተናጋሪ ጠየቀ።
«ሞፈርና ቀንበራቸውን ሰቅለው ወደ ከተማ የገቡ ገበሬዎች ስላሉ
ጎምዥተው እንዲመለሱ ይሆናል፡፡ አለና በድሉ ወደ ኋላው ዞር ብሎ በልሁን ገልመጥ ሲያደርገው ዓይን ለዓይን ግጥምጥም አሉ፡፡
«አሃ» አለ በልሁ፡፡ ነገሮች ሁሉ ይበልጥ እየገቡት ሄዱ። ሁኔታው የበለጠ ጆሮውን ጥሎ እንዲያዳምጥ አደረገው።
ከተማ ውስጥ ገብቶ ማውደልደል የጀመለ ገበሬ ምንም ቢሉት ምን
ቢያደርጉት ተመልሶ ገጠር አይገባም፡፡» አለ የመጀመሪያው ተናጋሪ የበድሉ ጓደኛ፡፡
እሱም በልሁን ዞር ብሎ ሲያየው አሁንም ከበልሁ ጋር ተገጣጠሙ::
«ወዶ ነው! ተጎዶ ይመለሳል፡፡» በማለት በድሉ ሲጨምር በልሁ
ሁለመናውን ይነዝረው ጀመር፡፡ በልሁ ጠብ ጠብ ሲሸተው ትንፋሽ ያጥረዋል፡፡እስኪጀምር ድረስ መላ ሰውነቱ ይንዘፈዘፋል። ዓይኑ ይፈጣል፡፡ ያ በሽታው ተነሳበት:: በዚያው ስሜት ውስጥ ሆኖ ምልልሳቸውን ማዳመጡን ቀጠለ፡፡
«ስሚ አንቺ!» ሲል ተጣራ በድሉ አሁንም እስተናጋጇን፡፡
«አቤት»
«ይህን ቴሌቪዥን ዝጊና «ቆይ ብቻ» የሚለውን ካሴት ክፈች፡፡ ይኸ ሴት አውል ሁሉ ልብ ቢገዘ» አለና አሁንም ዞር ብሎ በልሁን ገላመጠው ።
በዚህ ጊዜ በልሁ ለየለት፡፡ ተዘጋጅተው እንደመጡብትም በትክክል ተረዳ፡፡
ወዲያው በግራ ጣቱ ላይ ያጠለቃትን ባለ ፈርጥ ቀለበት ወደ ቀኝ ጣቱ አዛወራት፡፡
ጡንቻውን ማጠባበቅ ጀመረ። አንዲት የትንኮሳ ቃልና ግልምጫ ብቻ ቀረችው። ይጠባበቃትም ጀመር።
በድሉ አሁንም ቀጠለ፡፡ እንኳን የግብርና ወሬ መስማት የግብርና ባለሙያ ነኝ ባይ በከተማው ውስጥ ማየት አስጠልቶናል። አለና ብርጭቆዉን ብድግ አድርጎ
አረቄውን ጨለጠና ከመጠን በላይ ባንኮኒ እያንኳኳ «ቶሎ በይ ነዳጅ ጨምሪ ዛሬ የማነደው አለኝ» አለና አሁንም ወደ በልሁ ዞር አለ።
«ስማ አንተ» አለው በልሁ መርእድን
«ወይ» አለ መርእድ። መሰከረ እየሆነ ያለውን ነገርም ይከታተል ነበርና ደንግጦ መግቢያ ቀዳዳ አቷል
«ከተቀመጥክበት ንቅንቅ እንዳትል እሺ»
«ለምን ወጥተን አንሄድም?» አለ መርዕድ፡፡
«ጉዳዩን እስከምፈፅም" ጠብቀኝ» አለና በልሁ ከወንበሩ ላይ ተነስቶ
በቀጥታ ወደ ባንኒው አመራ፡፡ በበድሉ እና በቀኙ በኩል ባለው ጓድኛው መካከል ባንኮኒ ተደግፎ ቆመና «ጎበዝ» አላቸው ሦስቱንም ተራ በተራ እየተመለከተ፡፡
«የጨዋታችሁ ደስ አለኝና መጣሁ።» እያጋበዛችሁኝ ወይ እየጋበዝኳችሁ እንጫወት
ብዬ ነው::» አላቸው ዓይኑን ፈጠጥ ያለ ቢሆንም ነገር ግን ፈገግ ብሎ
«ታውቀናለህ?» አለው በድሉ በቁመት የሚበልጠውን በልሁን አንጋጦ እየተመለከተ፡፡
«ይመስለኝ ነበር፡፡ አሁን ግን እንደማንተዋወቅ ገባኝ፡፡ ግን ደግሞ ሳንተዋወቅ እንለያይም።» ሲል መለሰለት በልሁ ረጋ ብሎ። «ተገድጄ ወደ አገሬ ልመለስ ነውና የወጪ ልበልህ፤ ጠጣ!» አለው አሁንም እያፌዘ።እስከዚህ ወቅት
ድረስ የበድሉ ጓደኞች ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ አላደረጉም፡፡ ግን በልሁን በግርምት ዓይን ይመለከቱታል።
«ነገር ፈልገሃል እንዴ?» አለ በድሉ አሁንም በልሁን እየተመለከተ::»
«ራሱ ፈልጎኝ ነው የመጣሁት።
አሁን ጠጣ! ካልጠጣህ ግን
እመታሀለሁ፡፡»
«ኣ?» ብሎ በድሉ ቀስቀስ ሊል ሲል በልሁ ድንገት አንገቱን አነቀወ። ገበሬ አይደለሁ ፊትህን ላርሰው ነው» አለና በመሀል ፊቱ ላይ ሀይለኛ ቡጢ አሳረፈበት፡፡ በፍጥነት ደገመው ከቀኙ በኩል ያለውን የበድለን ጓደኛ እንቅስቃሴ
ይከታተል ነበርና እውነትም ሲንቀሳቀስ አይቶት ኖሮ በቃሪያ ጥፊ ዓይነት በሀይል ሲሰነዝርበት ጆሮ ግንዱን አገኘው። ሰውየው ባላሰበው ሁኔታና ሀይል ስለተመታ
ከመርዕድ እግር ስር ወድቆ ጥቅልል አለ። መርዕድ በዚያው ጀመረው። በወደቀበት
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ድርሰት_በአሰፋ_በቀለ_ገየሱስ
....ጥቂት ቀናት አለፉ። አንድ ቀን ምሽት ላይ በልሁና መርዕድ በምህጻረ ቃል አምሆ ተብሎ በሚጠራው ሆቴል ውስጥ ከውጭ ወደ ቡና ቤቱ ሲገቡ በስተቀኝ በኩል በምትገኝ ብቸኛ ጠረጴዛ ላይ ቁጭ ብለው ከአንዲት የቡና ቤቱ እስተናጋጅ
ጋር እየተቃለዱ ይጠጣሉ። ከጠረጴዛው ፊትለፊት ያለው ባንኮኒና የቡና ማሽን ብቻ
ስለሆነ ቦታው እንደ ልብ ለመጫወት አመቺ ነው። የቀልዳቸውና የጭውውታቸው
ማዕከልም የመርዕድ ዓይን አፋርነት ነው:: አስተናጋጇ ባህሪውን ቀደም ብላ ስለምታውቅ በነገር እየነካካች ታሳፍረው ይዛለች፡፡መቼም የአንተን ድንግል የምወስደው እኔ ነኝ፡፡» ትለዋለች ጉልበቱንና ጭኖቹን እያሻሸች።
«እስቲ እንደ ምንም ብለሽ ገላግይው::» በልሁ እየሳቀ፡፡
«አቦ ተይኝና ሌላ ወሬ አምጪ!» ይላል መርዕድ የአስተናጋጇን እጅ ከላዩ ላይ ለማንሳት እየሞከረ።
አይዞህ! ቦታውን እንደሆነ እኔው ራሴ አሳይሃለሁ፡፡» አስተናጋጇ አሁንም።
«እንዲህ ከመባል ሞት ይሻላል መርዕድ!» እያለ በልሁ ይስቃል::
እንዲህና እንዲያ እያሉ በመጫወት ላይ ሳሉ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል አካባቢ ሁለት ሰዎች ተከታትለው ወደ ቡና ቤቱ ገቡና ግራ ቀኝ ተመለከቱ፡፡ ከበሩ
በስተግራ በኩል ያለው ዋናው ሳሎን በሰው ተሞልቷል። በቀኝ በኩል ያለችው ጠረጴዛ ደግሞ በእነበልሁ ተይዛለች። በቀጥታ ወደ ባንኮኒው በመጠጋት ጀርባቸውን ለእነበልሁ ሰጥተው ቆሙ:: ወዲያው ደግሞ በድሉ አሸናፊ ከውጭ መጥቶ
ተቀላቀላቸው:: እሱ ከመሀል ሌሎቹ ግራና ቀኝ በመሆን ፈንጠር ፈጠር ብለው ተደረደሩና የሚጠጡትን አዘዙ፡፡ ለሁሉም አረቄ ቀረበላቸው ::
በልሁ ግን ቅፍፍ ይለው ጀመር፡፡ እሱና በድሉ ቀድሞም ተዳፍጠው ነበር የኖሩት. ዜሬ ደግሞ ገና ሲገባ ገልመጥ አድርጎት ነበርና
እንዲሁም ከተማ ውስጥ አይቷቸው ከማያውቃቸው ሰዎች ጋር ገጥሟልና ጥርጣሬ ገባው መጠጥ አወሳሰዳቸውም አላምር አለው ግልብጥ ግልብጥ ያደርጉታል። በሹክሹክታም ሲወያዩ ያያቸዋል። ወደ ኋላቸው ዞር እያሉ ሲገላምጡት ያይ ጀመር
መርዕድና አስተናጋጇ የሚያወሩትን ትቶ እነ በድለን መከታተል ቀጠለ፡፡
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ ከምሽቱ ሁለት ሰአት አለፈ። የመደመጥ እድሉን እዚያው የተፈጠረበት አገር ረስቶ የመጣው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በቡና ቤቱ ውስጥ ተከፍቶ ያለ ምንም አድማጭ ለራሱ ይጮሀል። ዜና እወጃውን ጨርሶ የግብርና ፕሮግራም ማስተላለፍ ጀምሯል።የመስኖ ስራ እንቅስቃሴ እያሳየ ገበሬዎች ያገኙትን ጠቀሜታ ይዘረዝራል።
በድለና ጓደኞቹ ከቴሌቪዥኑ ፕሮግራም ጋር የተያያዘ ወሬ ማውራት ጀመሩ። ያም ቢሆን ከበልሁ ጀሮ ደረሰና እሱም በጥንቃቄ ያዳምጥ ጀመር፡፡ከበድሉ በስተቀኝ በኩል ከቡና ማሽኑ አጠገብ ቆሞ የሚጠጣው የበድሎ ጓደኛ "ስሚ አንቺ"
ሲል ጨራት ከባንኮኒ ውስጥ ቆማ የነበረችውን አስተናጋጅ።
«አቤት» አለችው።
የኢትዮጵያ ገበሬዎች ቴሌቪዥን ገዙ ወይስ እኔና አንቺን ገበሬ ለማድረግ ተፈልጎ ነው ይኸ ፕሮግራም የሚተላለፈው ? ሲል ጮክ ባለ ድምፅ ጠየቃት።
«እኔ ምን አወቄ?» አልች አስተናጋጇ።
«የከተማ ገበሬ ሞልቷሌ አትይውም!» አላት ሌላው የበድሉ ጓደኛ ከግራ በኩል ሆኖ ወደ ኋላ
ዞር ብሎ በልሁንም አየት አደረገው፡፡
«ይኽ ከየጓሮው ወፍ ዘራሽ ቡና የሚለቅመው?» ሲል የመጀመሪያው ተናጋሪ ጠየቀ።
«ሞፈርና ቀንበራቸውን ሰቅለው ወደ ከተማ የገቡ ገበሬዎች ስላሉ
ጎምዥተው እንዲመለሱ ይሆናል፡፡ አለና በድሉ ወደ ኋላው ዞር ብሎ በልሁን ገልመጥ ሲያደርገው ዓይን ለዓይን ግጥምጥም አሉ፡፡
«አሃ» አለ በልሁ፡፡ ነገሮች ሁሉ ይበልጥ እየገቡት ሄዱ። ሁኔታው የበለጠ ጆሮውን ጥሎ እንዲያዳምጥ አደረገው።
ከተማ ውስጥ ገብቶ ማውደልደል የጀመለ ገበሬ ምንም ቢሉት ምን
ቢያደርጉት ተመልሶ ገጠር አይገባም፡፡» አለ የመጀመሪያው ተናጋሪ የበድሉ ጓደኛ፡፡
እሱም በልሁን ዞር ብሎ ሲያየው አሁንም ከበልሁ ጋር ተገጣጠሙ::
«ወዶ ነው! ተጎዶ ይመለሳል፡፡» በማለት በድሉ ሲጨምር በልሁ
ሁለመናውን ይነዝረው ጀመር፡፡ በልሁ ጠብ ጠብ ሲሸተው ትንፋሽ ያጥረዋል፡፡እስኪጀምር ድረስ መላ ሰውነቱ ይንዘፈዘፋል። ዓይኑ ይፈጣል፡፡ ያ በሽታው ተነሳበት:: በዚያው ስሜት ውስጥ ሆኖ ምልልሳቸውን ማዳመጡን ቀጠለ፡፡
«ስሚ አንቺ!» ሲል ተጣራ በድሉ አሁንም እስተናጋጇን፡፡
«አቤት»
«ይህን ቴሌቪዥን ዝጊና «ቆይ ብቻ» የሚለውን ካሴት ክፈች፡፡ ይኸ ሴት አውል ሁሉ ልብ ቢገዘ» አለና አሁንም ዞር ብሎ በልሁን ገላመጠው ።
በዚህ ጊዜ በልሁ ለየለት፡፡ ተዘጋጅተው እንደመጡብትም በትክክል ተረዳ፡፡
ወዲያው በግራ ጣቱ ላይ ያጠለቃትን ባለ ፈርጥ ቀለበት ወደ ቀኝ ጣቱ አዛወራት፡፡
ጡንቻውን ማጠባበቅ ጀመረ። አንዲት የትንኮሳ ቃልና ግልምጫ ብቻ ቀረችው። ይጠባበቃትም ጀመር።
በድሉ አሁንም ቀጠለ፡፡ እንኳን የግብርና ወሬ መስማት የግብርና ባለሙያ ነኝ ባይ በከተማው ውስጥ ማየት አስጠልቶናል። አለና ብርጭቆዉን ብድግ አድርጎ
አረቄውን ጨለጠና ከመጠን በላይ ባንኮኒ እያንኳኳ «ቶሎ በይ ነዳጅ ጨምሪ ዛሬ የማነደው አለኝ» አለና አሁንም ወደ በልሁ ዞር አለ።
«ስማ አንተ» አለው በልሁ መርእድን
«ወይ» አለ መርእድ። መሰከረ እየሆነ ያለውን ነገርም ይከታተል ነበርና ደንግጦ መግቢያ ቀዳዳ አቷል
«ከተቀመጥክበት ንቅንቅ እንዳትል እሺ»
«ለምን ወጥተን አንሄድም?» አለ መርዕድ፡፡
«ጉዳዩን እስከምፈፅም" ጠብቀኝ» አለና በልሁ ከወንበሩ ላይ ተነስቶ
በቀጥታ ወደ ባንኒው አመራ፡፡ በበድሉ እና በቀኙ በኩል ባለው ጓድኛው መካከል ባንኮኒ ተደግፎ ቆመና «ጎበዝ» አላቸው ሦስቱንም ተራ በተራ እየተመለከተ፡፡
«የጨዋታችሁ ደስ አለኝና መጣሁ።» እያጋበዛችሁኝ ወይ እየጋበዝኳችሁ እንጫወት
ብዬ ነው::» አላቸው ዓይኑን ፈጠጥ ያለ ቢሆንም ነገር ግን ፈገግ ብሎ
«ታውቀናለህ?» አለው በድሉ በቁመት የሚበልጠውን በልሁን አንጋጦ እየተመለከተ፡፡
«ይመስለኝ ነበር፡፡ አሁን ግን እንደማንተዋወቅ ገባኝ፡፡ ግን ደግሞ ሳንተዋወቅ እንለያይም።» ሲል መለሰለት በልሁ ረጋ ብሎ። «ተገድጄ ወደ አገሬ ልመለስ ነውና የወጪ ልበልህ፤ ጠጣ!» አለው አሁንም እያፌዘ።እስከዚህ ወቅት
ድረስ የበድሉ ጓደኞች ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ አላደረጉም፡፡ ግን በልሁን በግርምት ዓይን ይመለከቱታል።
«ነገር ፈልገሃል እንዴ?» አለ በድሉ አሁንም በልሁን እየተመለከተ::»
«ራሱ ፈልጎኝ ነው የመጣሁት።
አሁን ጠጣ! ካልጠጣህ ግን
እመታሀለሁ፡፡»
«ኣ?» ብሎ በድሉ ቀስቀስ ሊል ሲል በልሁ ድንገት አንገቱን አነቀወ። ገበሬ አይደለሁ ፊትህን ላርሰው ነው» አለና በመሀል ፊቱ ላይ ሀይለኛ ቡጢ አሳረፈበት፡፡ በፍጥነት ደገመው ከቀኙ በኩል ያለውን የበድለን ጓደኛ እንቅስቃሴ
ይከታተል ነበርና እውነትም ሲንቀሳቀስ አይቶት ኖሮ በቃሪያ ጥፊ ዓይነት በሀይል ሲሰነዝርበት ጆሮ ግንዱን አገኘው። ሰውየው ባላሰበው ሁኔታና ሀይል ስለተመታ
ከመርዕድ እግር ስር ወድቆ ጥቅልል አለ። መርዕድ በዚያው ጀመረው። በወደቀበት
👍12
#ምንዱባን
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ልክ ፍቅረኛዋን የምትደባብስ ይመስል በለስላሳ እጆችዋ ድንጋዩን በማሻሸት አመሰገነችው:: «ምነው ተጫጫነኝ፣ ማን አለ ከአጠገቤ»
እንደሚባለው ሁሉ ምንም እንኳን በዓይንዋ ባታየውም ከአጠገብዋ ሰው እንደቆመ ከበዳት:: ይህ እንዴት ሆነ ቢባል በቃላት ለመግለጽ ያስቸግራል፡፡
ፊትዋን አዙራ ከተመለከተች በኋላ ብድግ አለች:: እሱው ነበር:: ቆብ
ወይም ኮፍያ አላጠለቀም:: ሰውነቱ ገርጥቶአል፡፡ ትንሽ ከሳ ያለ ሰውነት ያለው ሲሆን የለበሰው ልብስ ጠቆር ያለ ነው፡፡ ፊቱ ጎልቶ ይታይ እንጂ አፍንጫው ሰልከክ ያለ ለመሆኑ ይታያል::
ኮዜት ብትደነግጥም የጩኸት ድምፅ ለማሰማት አልደፈረችም::
አንድ ነገር ወደፊት የሳባት ስለመሰላት ወደኋላ ሸሸት አለች:: ልጁ ከነበረበት አልተነቃነቀም:: ዐይኑን ለማየት ባትችልም በሀዘን መሞላቱን ገመተች::
ኮዜት ወደኋላ ስትሸሽ ከግንድ ጋር ስለተላተመች ያንኑ ግንድ ተደግፋ
ቀረች:: ዛፉን ተደግፋ ባትቆም ኖሮ እጅ እግርዋ ስለዛለባት ትወድቅ ነበር፡፡ዛፉን ተደግፋ እንደቆመች ድምፁን ሰማች:: ያን ድምፅ ከዚያ በፊት ሰምታው አታውቅም:: በጣም ዝግ ብሎ ነበር የሚናገረው::
«ይቅርታሽን፣ እዚህ ነው ያለሁት፡፡ ልቤ ሊፈነዳ ነው:: መኖር እየተሳነኝ ነው ከዚህ የመጣሁት፡፡ ከመቀመጫው ላይ የወረወርኩትን ፅሑፍ አንብበሽዋል? ለመሆኑ ማን እንደሆንኩ አውቀሽኛል? አትፍሪኝ::ጊዜው በጣም
ቆይቷል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የተያየንበት ቀን ታስታውሺዋለሽ?
ዘወትር ትሄጅበት የነበረው የሽርሽር ቦታ! በአጠገቤ ያለፍሽበት ቀንስ ቀኖቹ ሰኔ 16 እና ሐምሌ 2 ነበሩ፡፡ አሁንማ ዓመት ሊሞላው ምን ቀረው።
ዓይንሽን እንኳን ሳላይ ብዙ ጊዜ አለፈ፡፡ ማታ ማታ ከዚህ እመጣለሁ አትፍሪ፣ ግድ የለሽም፣ ከዚህ ማንም የለም:: ከዚህ የምመጣው የመኝታ ክፍልሽን መስኮት በሩቁ ለማየት ነው:: ከዚህ አካባቢ በምመጣበት ጊዜ
ደግሞ ድንገት በአካባቢው ካለሽ እንዳትደነግጪ እያልኩ ስራመድ
በዝግታ ነበር፡፡ አንድ ቀን ስትዘምሪ ሰምቼሽ በጣም ደስ አለኝ፡፡ ከክፍልኝ ውስጥ ሆነሽ ስትዘምሪ መስማቴ ያስከፋሻል? ጉዳት ያለው አይመስለኝም። አየሽ፣ አንቺ እኮ ለእኔ መልአኬ ነሽ፡፡ አንዳንድ ጊዜ እስቲ ከዚህ እንድቀመጥ
ፍቀጂልኝ፡፡ በቅርቡ እንደምሞት አውቃለሁ፡፡ ይህን ብታውቂ! እኔ እኮ እንደ አምላክ ነው የማመልክሽ! ይቅርታ አድርጊልኝ፤ ንግግር አላውቅም
ከአንቺ ጋር ማውራቴን ረስቼአለሁ፡፡ ምናልባት ሳላውቀው አናድጄሽ ወይ አበሳጭቼሽ ይሆናል፡፡ አዘንሽብኝ?
«ወይ እማዬ!» አለች፡፡ ልክ እንደሚሞት ሰው ተዝለፈለፈች፡፡
ከነበረበት ወደ እርስዋ ሮጠ፡፡ ከወደቀችበት እቅፍ አድርጎ አነሳት!
ምን እንደሚያደርግ ሳይታወቀው በጣም በመጭመቅ አቀፋት:: እየተንገዳገደ ወደ ላይ ብድግ አደረጋት፡፡ አካሉ በጭስ የተሞላ ይመስል ሰውነቱ ውስሳ
እየተነነ የሚሄድ ነገር እንዳለ ተሰማው:: መንፈሳዊ ተግባርም የሚያከናው መሰለው፡፡ ምንም እንኳን ከልቡ አስጠግቶ ቢያቅፋትም የፍቶተ ስሜት ጨርሶ አልተሰማውም፤ እውነተኛ ፍቅር የፍቶተ ሥጋ መርካት አይደለምና፡ ልጁ ከእውነተኛ ፍቅር ወጥመድ ውስጥ ለመግባቱ ምልክት
ነበር፡፡
እጁን ይዛ ወደ ልብዋ አስጠጋችው:: ወረቀት ከጡቶችዋ መኖሩን ተገነዘበ፡፡ ዝግ ባለ ድምፅ ተናገረ::
«እንግዲያውማ ትወጂኛለሽ ማለት ነዋ!»
ጆሮን በኃይል ካላቀኑ በማይሰማ በጣም ዝቅ ባለ ድምፅ መልስ
ሰጠችው::
«እስቲ ዝም በል፤ እሱንማ የምታውቀው ነው::»
በሀፍረት የቀላው ፊትዋን ላለማሳየት ኩራት በተሰማውና በፍቅር በሰከረው ወጣት ብብት ስር ራስዋን ደበቀች::
ከድንጋዩ መቀመጫ ላይ ቁጭ ሲል እርሱዋም ከአጠገቡ
አለች:: ዝምታ ሰፈነ፡፡ ከዋክብት ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል:: እንዴት ነው ከንፈሮቻቸው የተገናኙት? እንዴት ነው አእዋፍ በዚህ ሰዓት ማዜም
የጀመሩት? እንዴትስ አበቦች ሊፈኩ ቻሉ?
አለቀ! በቃ ! ሥሮቻቸው የተነቀሉ እስኪመስላቸው ተሳሳሙ::
የሁለቱም ሰውነት ነፋስ እንዳወዛወዘው ቅጠል ተንቀጠቀጠ፡፡ በጨለማ
የሁለቱም ዓይኖች ቦግ ስላሉ ተፋጠጡ፡፡ ብርዱ አልተሰማቸውም፤ ድንጋዩ
አልቆረቆራቸውም፤ መሬቱና ሳሩ አልቀዘቀዛቸውም:: አሁንም በመፋጠጥ እየተያዩ ነው፡፡ ልባቸው በአሳብ ተሞልቷል፡፡ ሳይታወቃቸው እጅ ለእጅ
ተጨባብጠዋል፡፡
ለማንኛውም እንዴት አድርጎ ከአጥር ግቢው ውስጥ እንደገባ
አልጠየቀችውም፤ ለመጠየቅም አልፈለገችም፡፡ የእርሱ ከዚያ መገኘት እንግዳ ነገር
አልሆነባትም::
አልፎ አልፎ የማሪየስ ጉልበት የኮዜትን ጉልበት ሲነካ ሁለቱም
በደስታ ይፈካሉ፡፡ ቆይታ ኮዜት አንዳንድ ቃል ትወረውራለች፡፡ ስትናገር ነፍስዋ ከከንፈርዋ ጫፍ ላይ እንደሆነች ከከንፈርዋ ጋር አብሮ ተንቀጠቀጠ ለማለት ይቻላል፡፡
ቀስ በቀስ ዝምታው ተወግዶ ማውራት ጀመሩ፡፡ እንደገና የፍቅር
ስበታቸው ሞልቶ ስለፈሰሰ ዝም ተባባሉ፡፡ ምድርም ዝም አለች፡፡ ነፋስ እንኳን «ዝም በል» ብለው ያዘዙት ይመስል ፀጥ አለ፡፡ እንደገና ጨዋታ ጀመሩት፡፡ እነዚህ ሁለት እንደ ጥቅምት ውሃ የጠሩ ፍጡሮች ስለነበሩ ስላለፈው ምኞታቸው፣ ወፈፍ አድርጎአቸው ስለፈጸሙት ተግባር፣ ስለደስታ
ዘመናቸውን ፣ ስለተከፉበት ጊዜ እንዲሁም አንዱ ሌላውን ምን ያህል ይመኝ እንደነበር አንድም ነገር ሳይደባበቁ ተጫወቱ፡፡ አንዱ ስለሌላው ስለነበረው
ምኞትና አድናቆትም ተነጋገሩ፡: ሳይተያዩ ሲቀሩ ሁለቱም ምን ያህል ተስፋ ቆረጠው እንደነበር ተገላለጹ፡፡ ከሁለቱም ልብ ውስጥ የነበረው ሁሉ እንደ ውሃ ፈሰሰ፣ ተንቆረቆረ:: ስለዚህ ከአንድ ሰዓት በኋላ ወጣቱ የወጣትዋ፣
ወጣትዋ የወጣቱ ሕይወት ማለት እርሱ እርስዋን፣ እርስዋ እርሱን ሆኑ፡፡አንዱ ሌላው ልብ ወስጥ ዘልቆ ገባ፡፡ አንዱ የሌላው ጌታ ሆነ፡፡ አንዱ በሌላው ረካ፤ ፈካ፤ ተደሰተ፡፡
ልባቸው ውስጥ የነበረው ነገር ተሟጥጦ ሲያልቅ ጭንቅላትዋን
ከትከሻው ላይ አሳርፋ ጥያቄ ጠየቀችው::
«ስምህ ማነው?»
«ስሜ ማሪየስ ይባላል» አለ::
«የአንቺስ?»
«ኮዜት እባላለሁ፡፡››
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ማምለጥ
ምንም እንኳን ቴናድዬ የታሠረው ከተለየ ክፍል ውስጥ ቢሆንም
እርሱና ሌሎች ሦስት ሽፍቶች የማምለጥ አድማ ይመታሉ፡፡ ሁለቱ ሽፍቶች ከምድር ቤት ውስጥ ሲሆኑ ቴናድዬ ብቻውን ፎቅ ላይ ነበር፡፡ ከአደሙ
መካከል አንደኛው አደገኛነቱ ታውቆ እንዲሁ ለብቻው ነበር የታስረው::
በምን ተአምር ጠርሙስ ቪኖ እንዴት ሊያስገባ እንደቻለ ባይታወቅም መጠጡ ቴናድዬ ክፍል ውስጥ ተገኝቷል ይህ መጠጥ በውስጡ ሱስ
የሚያሲዝ እንደ ሐሺሽ ያለ ቅመም እንደነበረበት ይነገራል
መቼስ በእያንዳንዱ እስር ቤት ውስጥ እስረኞች እንዲያመልጡ
የሚተባበሩና እምነታቸውንና መሐላቸውን ለገንዘብ የሚሰጡ ጉበኞች ወይም ሌቦች ወይም ቀጣፊዎች አይታጡም: እንደነዚህ ያሉ ሰዎች ከደመወዛቸው
በላይ ገቢ አላቸው::
ሁለቱ ሽፍቶች አንድ ቀን ጠዋት ማምለጣቸውና ከመንገድ
የሚጠብቋቸው ለመሆኑ የሚያወቁ ሌሎች ሁለት ሽፍቶች ከውስጥ ይቀራሉ እነርሱም ለማምለጥ ዘዴ ይፈጥራሉ በአጋጣሚ በእለቱ በረዶ የተቀላቀለበት ከባድ ዝናብ ይጥል ስለነበር በዚህ አጋጣሚ በመጠቀምና ጨለማን ተገን
በማድረግ እነዚያ ሁለት ሽፍቶች በፈጠሩት ዘዴ ተጠቅመው ለማምለጥ ችለዋል::
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ከዬሐንስ_ገፃዲቅ
....ልክ ፍቅረኛዋን የምትደባብስ ይመስል በለስላሳ እጆችዋ ድንጋዩን በማሻሸት አመሰገነችው:: «ምነው ተጫጫነኝ፣ ማን አለ ከአጠገቤ»
እንደሚባለው ሁሉ ምንም እንኳን በዓይንዋ ባታየውም ከአጠገብዋ ሰው እንደቆመ ከበዳት:: ይህ እንዴት ሆነ ቢባል በቃላት ለመግለጽ ያስቸግራል፡፡
ፊትዋን አዙራ ከተመለከተች በኋላ ብድግ አለች:: እሱው ነበር:: ቆብ
ወይም ኮፍያ አላጠለቀም:: ሰውነቱ ገርጥቶአል፡፡ ትንሽ ከሳ ያለ ሰውነት ያለው ሲሆን የለበሰው ልብስ ጠቆር ያለ ነው፡፡ ፊቱ ጎልቶ ይታይ እንጂ አፍንጫው ሰልከክ ያለ ለመሆኑ ይታያል::
ኮዜት ብትደነግጥም የጩኸት ድምፅ ለማሰማት አልደፈረችም::
አንድ ነገር ወደፊት የሳባት ስለመሰላት ወደኋላ ሸሸት አለች:: ልጁ ከነበረበት አልተነቃነቀም:: ዐይኑን ለማየት ባትችልም በሀዘን መሞላቱን ገመተች::
ኮዜት ወደኋላ ስትሸሽ ከግንድ ጋር ስለተላተመች ያንኑ ግንድ ተደግፋ
ቀረች:: ዛፉን ተደግፋ ባትቆም ኖሮ እጅ እግርዋ ስለዛለባት ትወድቅ ነበር፡፡ዛፉን ተደግፋ እንደቆመች ድምፁን ሰማች:: ያን ድምፅ ከዚያ በፊት ሰምታው አታውቅም:: በጣም ዝግ ብሎ ነበር የሚናገረው::
«ይቅርታሽን፣ እዚህ ነው ያለሁት፡፡ ልቤ ሊፈነዳ ነው:: መኖር እየተሳነኝ ነው ከዚህ የመጣሁት፡፡ ከመቀመጫው ላይ የወረወርኩትን ፅሑፍ አንብበሽዋል? ለመሆኑ ማን እንደሆንኩ አውቀሽኛል? አትፍሪኝ::ጊዜው በጣም
ቆይቷል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ የተያየንበት ቀን ታስታውሺዋለሽ?
ዘወትር ትሄጅበት የነበረው የሽርሽር ቦታ! በአጠገቤ ያለፍሽበት ቀንስ ቀኖቹ ሰኔ 16 እና ሐምሌ 2 ነበሩ፡፡ አሁንማ ዓመት ሊሞላው ምን ቀረው።
ዓይንሽን እንኳን ሳላይ ብዙ ጊዜ አለፈ፡፡ ማታ ማታ ከዚህ እመጣለሁ አትፍሪ፣ ግድ የለሽም፣ ከዚህ ማንም የለም:: ከዚህ የምመጣው የመኝታ ክፍልሽን መስኮት በሩቁ ለማየት ነው:: ከዚህ አካባቢ በምመጣበት ጊዜ
ደግሞ ድንገት በአካባቢው ካለሽ እንዳትደነግጪ እያልኩ ስራመድ
በዝግታ ነበር፡፡ አንድ ቀን ስትዘምሪ ሰምቼሽ በጣም ደስ አለኝ፡፡ ከክፍልኝ ውስጥ ሆነሽ ስትዘምሪ መስማቴ ያስከፋሻል? ጉዳት ያለው አይመስለኝም። አየሽ፣ አንቺ እኮ ለእኔ መልአኬ ነሽ፡፡ አንዳንድ ጊዜ እስቲ ከዚህ እንድቀመጥ
ፍቀጂልኝ፡፡ በቅርቡ እንደምሞት አውቃለሁ፡፡ ይህን ብታውቂ! እኔ እኮ እንደ አምላክ ነው የማመልክሽ! ይቅርታ አድርጊልኝ፤ ንግግር አላውቅም
ከአንቺ ጋር ማውራቴን ረስቼአለሁ፡፡ ምናልባት ሳላውቀው አናድጄሽ ወይ አበሳጭቼሽ ይሆናል፡፡ አዘንሽብኝ?
«ወይ እማዬ!» አለች፡፡ ልክ እንደሚሞት ሰው ተዝለፈለፈች፡፡
ከነበረበት ወደ እርስዋ ሮጠ፡፡ ከወደቀችበት እቅፍ አድርጎ አነሳት!
ምን እንደሚያደርግ ሳይታወቀው በጣም በመጭመቅ አቀፋት:: እየተንገዳገደ ወደ ላይ ብድግ አደረጋት፡፡ አካሉ በጭስ የተሞላ ይመስል ሰውነቱ ውስሳ
እየተነነ የሚሄድ ነገር እንዳለ ተሰማው:: መንፈሳዊ ተግባርም የሚያከናው መሰለው፡፡ ምንም እንኳን ከልቡ አስጠግቶ ቢያቅፋትም የፍቶተ ስሜት ጨርሶ አልተሰማውም፤ እውነተኛ ፍቅር የፍቶተ ሥጋ መርካት አይደለምና፡ ልጁ ከእውነተኛ ፍቅር ወጥመድ ውስጥ ለመግባቱ ምልክት
ነበር፡፡
እጁን ይዛ ወደ ልብዋ አስጠጋችው:: ወረቀት ከጡቶችዋ መኖሩን ተገነዘበ፡፡ ዝግ ባለ ድምፅ ተናገረ::
«እንግዲያውማ ትወጂኛለሽ ማለት ነዋ!»
ጆሮን በኃይል ካላቀኑ በማይሰማ በጣም ዝቅ ባለ ድምፅ መልስ
ሰጠችው::
«እስቲ ዝም በል፤ እሱንማ የምታውቀው ነው::»
በሀፍረት የቀላው ፊትዋን ላለማሳየት ኩራት በተሰማውና በፍቅር በሰከረው ወጣት ብብት ስር ራስዋን ደበቀች::
ከድንጋዩ መቀመጫ ላይ ቁጭ ሲል እርሱዋም ከአጠገቡ
አለች:: ዝምታ ሰፈነ፡፡ ከዋክብት ብቅ ብቅ ማለት ጀምረዋል:: እንዴት ነው ከንፈሮቻቸው የተገናኙት? እንዴት ነው አእዋፍ በዚህ ሰዓት ማዜም
የጀመሩት? እንዴትስ አበቦች ሊፈኩ ቻሉ?
አለቀ! በቃ ! ሥሮቻቸው የተነቀሉ እስኪመስላቸው ተሳሳሙ::
የሁለቱም ሰውነት ነፋስ እንዳወዛወዘው ቅጠል ተንቀጠቀጠ፡፡ በጨለማ
የሁለቱም ዓይኖች ቦግ ስላሉ ተፋጠጡ፡፡ ብርዱ አልተሰማቸውም፤ ድንጋዩ
አልቆረቆራቸውም፤ መሬቱና ሳሩ አልቀዘቀዛቸውም:: አሁንም በመፋጠጥ እየተያዩ ነው፡፡ ልባቸው በአሳብ ተሞልቷል፡፡ ሳይታወቃቸው እጅ ለእጅ
ተጨባብጠዋል፡፡
ለማንኛውም እንዴት አድርጎ ከአጥር ግቢው ውስጥ እንደገባ
አልጠየቀችውም፤ ለመጠየቅም አልፈለገችም፡፡ የእርሱ ከዚያ መገኘት እንግዳ ነገር
አልሆነባትም::
አልፎ አልፎ የማሪየስ ጉልበት የኮዜትን ጉልበት ሲነካ ሁለቱም
በደስታ ይፈካሉ፡፡ ቆይታ ኮዜት አንዳንድ ቃል ትወረውራለች፡፡ ስትናገር ነፍስዋ ከከንፈርዋ ጫፍ ላይ እንደሆነች ከከንፈርዋ ጋር አብሮ ተንቀጠቀጠ ለማለት ይቻላል፡፡
ቀስ በቀስ ዝምታው ተወግዶ ማውራት ጀመሩ፡፡ እንደገና የፍቅር
ስበታቸው ሞልቶ ስለፈሰሰ ዝም ተባባሉ፡፡ ምድርም ዝም አለች፡፡ ነፋስ እንኳን «ዝም በል» ብለው ያዘዙት ይመስል ፀጥ አለ፡፡ እንደገና ጨዋታ ጀመሩት፡፡ እነዚህ ሁለት እንደ ጥቅምት ውሃ የጠሩ ፍጡሮች ስለነበሩ ስላለፈው ምኞታቸው፣ ወፈፍ አድርጎአቸው ስለፈጸሙት ተግባር፣ ስለደስታ
ዘመናቸውን ፣ ስለተከፉበት ጊዜ እንዲሁም አንዱ ሌላውን ምን ያህል ይመኝ እንደነበር አንድም ነገር ሳይደባበቁ ተጫወቱ፡፡ አንዱ ስለሌላው ስለነበረው
ምኞትና አድናቆትም ተነጋገሩ፡: ሳይተያዩ ሲቀሩ ሁለቱም ምን ያህል ተስፋ ቆረጠው እንደነበር ተገላለጹ፡፡ ከሁለቱም ልብ ውስጥ የነበረው ሁሉ እንደ ውሃ ፈሰሰ፣ ተንቆረቆረ:: ስለዚህ ከአንድ ሰዓት በኋላ ወጣቱ የወጣትዋ፣
ወጣትዋ የወጣቱ ሕይወት ማለት እርሱ እርስዋን፣ እርስዋ እርሱን ሆኑ፡፡አንዱ ሌላው ልብ ወስጥ ዘልቆ ገባ፡፡ አንዱ የሌላው ጌታ ሆነ፡፡ አንዱ በሌላው ረካ፤ ፈካ፤ ተደሰተ፡፡
ልባቸው ውስጥ የነበረው ነገር ተሟጥጦ ሲያልቅ ጭንቅላትዋን
ከትከሻው ላይ አሳርፋ ጥያቄ ጠየቀችው::
«ስምህ ማነው?»
«ስሜ ማሪየስ ይባላል» አለ::
«የአንቺስ?»
«ኮዜት እባላለሁ፡፡››
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ማምለጥ
ምንም እንኳን ቴናድዬ የታሠረው ከተለየ ክፍል ውስጥ ቢሆንም
እርሱና ሌሎች ሦስት ሽፍቶች የማምለጥ አድማ ይመታሉ፡፡ ሁለቱ ሽፍቶች ከምድር ቤት ውስጥ ሲሆኑ ቴናድዬ ብቻውን ፎቅ ላይ ነበር፡፡ ከአደሙ
መካከል አንደኛው አደገኛነቱ ታውቆ እንዲሁ ለብቻው ነበር የታስረው::
በምን ተአምር ጠርሙስ ቪኖ እንዴት ሊያስገባ እንደቻለ ባይታወቅም መጠጡ ቴናድዬ ክፍል ውስጥ ተገኝቷል ይህ መጠጥ በውስጡ ሱስ
የሚያሲዝ እንደ ሐሺሽ ያለ ቅመም እንደነበረበት ይነገራል
መቼስ በእያንዳንዱ እስር ቤት ውስጥ እስረኞች እንዲያመልጡ
የሚተባበሩና እምነታቸውንና መሐላቸውን ለገንዘብ የሚሰጡ ጉበኞች ወይም ሌቦች ወይም ቀጣፊዎች አይታጡም: እንደነዚህ ያሉ ሰዎች ከደመወዛቸው
በላይ ገቢ አላቸው::
ሁለቱ ሽፍቶች አንድ ቀን ጠዋት ማምለጣቸውና ከመንገድ
የሚጠብቋቸው ለመሆኑ የሚያወቁ ሌሎች ሁለት ሽፍቶች ከውስጥ ይቀራሉ እነርሱም ለማምለጥ ዘዴ ይፈጥራሉ በአጋጣሚ በእለቱ በረዶ የተቀላቀለበት ከባድ ዝናብ ይጥል ስለነበር በዚህ አጋጣሚ በመጠቀምና ጨለማን ተገን
በማድረግ እነዚያ ሁለት ሽፍቶች በፈጠሩት ዘዴ ተጠቅመው ለማምለጥ ችለዋል::
👍21👏2❤1😁1
#የጣሪያ_ስር_አበቦች
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...የእናታችን ባዶ ፍጥጫ ወደ እሱ ዞረ:: ልክ ምን ማለት እንደፈለገ ለመያዝ የምትታገል ይመስል ነበር፡ የተምታታባት ትመስላለች… አይኖቿ ከኔ ወደ ክሪስ ከዚያ ወደ እናቷ ከዚያ ወደ ኬሪ ዘለሉና ተመልሰው ወደ ኮሪ መጡ።
“እማዬ” አለ ክሪስ ጥንክር አድርጎ፡ ካቲ አብራሽ ትሂድ ለኬሪ እኔ አለሁ
ምናልባት ያስጨነቀሽ ያ ከሆነ።"
እንድሄድ አልፈቀዱልኝም።
እናታችን ኮሪን ይዛ ወደ አዳራሹ ወጡ አያትየው ባገኘሁት ድል የጭካኔ
ፈገግታ ሰጥታኝ በሩን ቆለፈችው ኬሪ ወንድሟን በማጣቷ እየጮኸችና እምባዋ እየወረደ ትተዋት ሄዱ። ትንንሽ ደካማ ቡጢዎቿ ጥፋተኛዋ እኔ የሆንኩ ይመስል እኔ ላይ አረፉ፡ ካቲ እኔም
መሄድ እፈልጋለሁ! እንድሄድ እንዲፈቅዱልኝ አድርጊ! ኮሪ እኔ የማልሄድበት ቦታ መሄድ አይፈልግም... ጊታሩን ደግሞ ረስቶታል” አለች።
ከዚያ ቁጣዋ ሁሉ ሲበርድላት፣ ክንዶቼ ላይ ሆና ተንሰቀሰቀች: “ለምን ካቲ? ለምን?”
“ለምን?”
በህይወታችን ትልቁ ጥያቄ ነው።
በህይወታችን ከነበሩት አስቀያሚውና ረጅሙ ቀን ነበር። ኃጢአት ሰርተናል
እና እግዚአብሔር እንዴት በዚህ ፍጥነት ቅጣት ላከብን? ፈጠነም ዘገየም
አያትየው እንዳወቀችው ሁሉ ራሳችን ዋጋ ቢስ መሆናችንን እንደምናረጋግጥ
ያወቀ ይመስል፣ አይኖቹ እኛ ላይ ነበሩ ማለት ነው።
ቲቪ መጥቶ የቀኖቻችንን የተሻለ ክፍል ከመውሰዱ በፊት እንደነበረው እንደ
መጀመሪያው ቀን ቀኑን ሙሉ ቴሌቪዥን እንኳን ሳንከፍት በፀጥታ ቁጭ
ብለን ኮሪ እንዴት እንደሆነ ለመስማት እየጠበቅን ነው።
ክሪስ በሚወዛወዘው ወንበር ላይ ተቀምጦ እኔና ኬሪ ጭኖቹ ላይ ተቀምጠን
በቀስታ ወደፊት ወደኋላ፣ ወደፊት ወደኋላ እየተወዛወዝን ነው።
ለረጅም ጊዜ ጭኖቹ ላይ ስንቀመጥበት የክሪስ እግሮች ለምን እንደማይደነዝዙ
አላውቅም ምግባችንን ለማሰናዳት ተነሳሁ። ጭራሽ አልነካነውም: የቀኑ
የመጨረሻ ምግብ ሲያበቃና ሳህኖቹ ታጥበው ከተቀመጡ በኋላ እኛም ገላችንን ተጣጥበን ለመተኛት ተዘጋጀን፡ ኮሪ አልጋ አጠገብ በመደዳ ተንበርክከን ፀሎታችንን አቀረብን “እባክህ፣ እባክህ ኮሪ እንዲሻለውና ወደ እኛ እንዲመለስ አድርግ አልን ሌላ ነገር ፀልየንም ከነበረ ምን እንደነበረ አላስታውስም ተኛን ወይም ለመተኛት ሞከርን ኬሪን በእኔና በክሪስ መካከል አድርገን ሶስታችንም አንድ አልጋ ላይ ተኛን በሁለታችን መካከል ድጋሚ ምንም
ነገር አይፈጠርም መቼም... መቼም እንደገና አይፈጠርም እግዚአብሔር
እኔና ክሪስን ለመጉዳት ብለህ ኮሪን አትቅጣው አስቀድመን ተጎድተናል
ልናደርገው ፈልገን አልነበረም ጌታ ሆይ አልነበረም በአጋጣሚ ነው
የሆነው ለዚያውም አንድ ጊዜ ብቻ በዚያ ላይ ምንም ደስታ አልነበረበትም።
እግዚአብሔር ሆይ በእውነት በእውነት ደስታ አልነበረበትም
አዲስ ቀን ነጋ ከመጋረጃዎቹ ጀርባ ውጪ ለሚኖሩት በእኛ ለማይታዩት
ህይወት ተጀመረ። ራሳችንን ዘና ለማድረግ፣ ሰዓታችንን ለመሙላትና ለመብላት ሞከርን ክሪስ እየረዳኝ የፍራሹን ልብስ ቀየርኩ ምክንያቱም በጣም ከባባድ በመሆናቸው ብቻዬን ላገባቸው አልችልም፡ በዚያ ላይ ኮሪ በአብዛኛው ሽንቱን ስለሚሸና በየጊዜው መቀየር ነበረበት፡ ክሪስና እኔ አልጋውን አንጥፈን ክፍሉን አፀዳድተን ጨርሰን ኬሪ የሚወዛወዘው ወንበር
ላይ ብቻዋን ተቀምጣ ባዶ አየር ላይ አፍጥጣለች።
አራት ስዓት ገደማ የምንሰራውን ሁሉ ጨርሰን ወደ አዳራሹ ቀረብ ወደሚለው አልጋ ላይ ተቀምጠን በሩ እጀታ ላይ አይኖቻችንን ተክለን ዜናውን ይዛልን የምትመጣልንን እናታችንን እንዲያስገባ እየጠበቅን ነው።
ጥቂት ቆይቶ እናታችን ከማልቀስ ብዛት አይኖቿ ቀልተው መጣች። ከእሷ
ጋር ባለብረት አይኗ አያታችን ረጅም፣ ድርቅ ያለችና እምባ የሌላት ሆና ተከትላታለች።
እናታችን እግሮቿ መቆም አቅቷቸው ወለሉ ላይ እንዳይጥሏት የፈራች
ይመስል በሩን ተደገፈች እኔና ክሪስ ከተቀመጥንበት ዘለን ተነስተን ቆምን፡
ኬሪ ግን እናታችን ባዶ አይን ላይ እንዳፈጠጠች ነው: “ኮሪን በመኪና ወደ
ሆስፒታል እየወሰድኩት ነበር ቅርብ ወዳለው ሆስፒታል ነበር በእውነት"
አለች እናታችን ውጥረት በተሞላበት ሻካራና አሁንም አሁንም እንቅ እንቅ
በሚል ድምፅ፡ “እና የወንድሜ ልጅ ነው ብዬ በውሸት አስመዘገብኩት"
“ውሸት! እማዬ ሁልጊዜ ውሸት እንዴት ነው?” ትዕግስት ባጣ ሁኔታ ጠየቅኳት። ሰማያዊ አይኖቿ ወደ እኛ ዞሩ፡፡ ባዶ ነገር ላይ ያፈጠጡ፣ የጠፋ፣የሆነ ለዘለአለም የጠፋ ነገር የሚፈልጉ አይኖች ሰብአዊነቷ እየፈለጉ
እንደሆነ ገምቻለሁ። “ኮሪ የያዘው የሳምባ ምች ነበር። ዶክተሮቹ የቻሉትን ሁሉ
አድርገው ነበር . . .ግን በጣም በጣም . . . በጣም ዘግይቶ ነበር”
“የሳምባ ምች ነበር?"
“የሚችሉትን አድርገው ነበር?”
“ዘግይቶ ነበር?”
“ነበር… ነበር!
ኮሪ ሞቷል እንደገና አናየውም!
ዜናው ክሪስን ልክ ወንድነቱ ላይ የተመታ አይነት ስሜት ነበር የፈጠረበት
እንደተረገጠ አይነት፡ ወደ ኋላ ተንጋሎና ፊቱን ለመደበቅ ዞሮ ትከሻዎቹ
እየተርገፈገፉ ሲንሰቀሰቅ አይቼዋለሁ።
በመጀመሪያ አላመንኳትም ነበር። ቆምኩ፣ አፈጠጥኩ፣ ተጠራጠርኩ፣ ፊቷ አሳመነኝ እና ልቤ ውስጥ የሆነ ትልቅና ባዶ ቦታ ሲሰፋ ተሰማኝ። ደንዝዤና
ሽባ ሆኜ አልጋው ላይ ወደቅኩ። ልብሶቼ ረጥበው እስክመለከት ድረስ
እያለቀስኩ እንደነበረ አላወቅኩም ነበር
ቁጭ ብዬ እያለቀስኩ ቢሆንም ኮሪ ከህይወታችን ወጥቶ መሄዱን ማመን
አልፈለግኩም ደግሞ ኬሪ፣ ምስኪን ኬሪ ጭንቅላቷን ቀና አደረገች። ወደ
ኋላ ወረወረችና አፏን ከፍታ እሪ... አለች።
ድምፅዋ ተዘግቶ መጮህ እስከማትችል ድረስ ጮኸች: ኮሪ ጊታሩን
ወደሚያስቀምጥበትና ትንንሽ ያለቁ የቴኒስ ጫማዎቹን ወደደረደረችበት
ጥግ ሄደች። መቀመጥ የፈለገችው እዚያ ከጫማዎቹና ከሙዚቃ መሳሪያው ጋር ነበር እና ከዚያች ቅፅበት ጀምሮ አንዲት ቃል እንኳን ከከንፈሮቿ አልወጣም::
“ወደቀብሩ እንሄዳለን?” ክሪስ ጀርባውን እንዳዞረ ጠየቀ።
“ተቀብሯል” አለች እናታችን፡ “በመቃብሩ ላይ የውሸት ስም አፅፌያለሁ"አለችና ከጥያቄዎቻችንና ከክፍሉ ለማምለጥ በጣም በፍጥነት ወጣች
አያትየውም ተከተለቻት፡
በፈሩት አይኖቻችን ፊት ኬሪ በእያንዳንዱ ቀን የበለጠ እየጠወለገች ነው
እግዚአብሔር ኬሪንም ሊወስዳት እንደሚችል እና ሩቅ ቦታ ባለ የመቃብር
ስፍራ በሀሰት ስም ከኮሪ አጠገብ በቅርብ ርቀት የተቀበረ አባት እንኳን
በሌለበት እንደምትቀበር ተሰማኝ።
ማንኛችንም ብዙ መብላት አልቻልንም:: ፈዛዛና የደከመን ሁልጊዜ የደከመን
ሆነናል፡ ምንም ነገር ፍላጎታችንን አያነሳሳውም: ዕንባ ብቻ። ክሪስና እኔ
ውቅያኖስ የሚሞላ ያህል አለቀስን ወቀሳውን ሁሉ የእኛ አደረግነው: ከብዙ
ጊዜያት በፊት ማምለጥ ይገባን ነበር፡ ያንን የእንጨት ቁልፍ ተጠቅመን
ወጥተን እርዳታ መፈለግ እንችል ነበር። ኮሪ እንዲሞት አድርገናል: የእኛ
ሀላፊነት ነበር! ትንሹ ባለ ብዙ ተሰጥኦውና ፀጥተኛው ውድ ልጃችን እንዲሞት አደረግን አሁን ደግሞ ጥግ ላይ ተኮራምታ የምትቀመጥ በየቀኑ እየደከመች የምትሄድ ታናሽ እህት አለችን፡
ክሪስ ኬሪ እንዳትሰማ
ቀስ ባለ ድምፅ “ማምለጥ አለብን ካቲ! በፍጥነት።
አለዚያ ሁላችንም እንደ ኮሪ እንሞታለን፡ ሁላችንም የሆነ ነገር ሆነናል።ለረጅም ጊዜ ተዘግቶብናል፡ የምንኖረው ትክክለኛ ያልሆነ ህይወት ነው፡ ልክ ጀርሞች በሌሉበት አየር አልባ ቦታ እንደመኖር ነው።
፡
፡
#ክፍል_ሰላሳ_ዘጠኝ
፡
፡
#ትርጉም_ሀኒም_ኤልያስ
...የእናታችን ባዶ ፍጥጫ ወደ እሱ ዞረ:: ልክ ምን ማለት እንደፈለገ ለመያዝ የምትታገል ይመስል ነበር፡ የተምታታባት ትመስላለች… አይኖቿ ከኔ ወደ ክሪስ ከዚያ ወደ እናቷ ከዚያ ወደ ኬሪ ዘለሉና ተመልሰው ወደ ኮሪ መጡ።
“እማዬ” አለ ክሪስ ጥንክር አድርጎ፡ ካቲ አብራሽ ትሂድ ለኬሪ እኔ አለሁ
ምናልባት ያስጨነቀሽ ያ ከሆነ።"
እንድሄድ አልፈቀዱልኝም።
እናታችን ኮሪን ይዛ ወደ አዳራሹ ወጡ አያትየው ባገኘሁት ድል የጭካኔ
ፈገግታ ሰጥታኝ በሩን ቆለፈችው ኬሪ ወንድሟን በማጣቷ እየጮኸችና እምባዋ እየወረደ ትተዋት ሄዱ። ትንንሽ ደካማ ቡጢዎቿ ጥፋተኛዋ እኔ የሆንኩ ይመስል እኔ ላይ አረፉ፡ ካቲ እኔም
መሄድ እፈልጋለሁ! እንድሄድ እንዲፈቅዱልኝ አድርጊ! ኮሪ እኔ የማልሄድበት ቦታ መሄድ አይፈልግም... ጊታሩን ደግሞ ረስቶታል” አለች።
ከዚያ ቁጣዋ ሁሉ ሲበርድላት፣ ክንዶቼ ላይ ሆና ተንሰቀሰቀች: “ለምን ካቲ? ለምን?”
“ለምን?”
በህይወታችን ትልቁ ጥያቄ ነው።
በህይወታችን ከነበሩት አስቀያሚውና ረጅሙ ቀን ነበር። ኃጢአት ሰርተናል
እና እግዚአብሔር እንዴት በዚህ ፍጥነት ቅጣት ላከብን? ፈጠነም ዘገየም
አያትየው እንዳወቀችው ሁሉ ራሳችን ዋጋ ቢስ መሆናችንን እንደምናረጋግጥ
ያወቀ ይመስል፣ አይኖቹ እኛ ላይ ነበሩ ማለት ነው።
ቲቪ መጥቶ የቀኖቻችንን የተሻለ ክፍል ከመውሰዱ በፊት እንደነበረው እንደ
መጀመሪያው ቀን ቀኑን ሙሉ ቴሌቪዥን እንኳን ሳንከፍት በፀጥታ ቁጭ
ብለን ኮሪ እንዴት እንደሆነ ለመስማት እየጠበቅን ነው።
ክሪስ በሚወዛወዘው ወንበር ላይ ተቀምጦ እኔና ኬሪ ጭኖቹ ላይ ተቀምጠን
በቀስታ ወደፊት ወደኋላ፣ ወደፊት ወደኋላ እየተወዛወዝን ነው።
ለረጅም ጊዜ ጭኖቹ ላይ ስንቀመጥበት የክሪስ እግሮች ለምን እንደማይደነዝዙ
አላውቅም ምግባችንን ለማሰናዳት ተነሳሁ። ጭራሽ አልነካነውም: የቀኑ
የመጨረሻ ምግብ ሲያበቃና ሳህኖቹ ታጥበው ከተቀመጡ በኋላ እኛም ገላችንን ተጣጥበን ለመተኛት ተዘጋጀን፡ ኮሪ አልጋ አጠገብ በመደዳ ተንበርክከን ፀሎታችንን አቀረብን “እባክህ፣ እባክህ ኮሪ እንዲሻለውና ወደ እኛ እንዲመለስ አድርግ አልን ሌላ ነገር ፀልየንም ከነበረ ምን እንደነበረ አላስታውስም ተኛን ወይም ለመተኛት ሞከርን ኬሪን በእኔና በክሪስ መካከል አድርገን ሶስታችንም አንድ አልጋ ላይ ተኛን በሁለታችን መካከል ድጋሚ ምንም
ነገር አይፈጠርም መቼም... መቼም እንደገና አይፈጠርም እግዚአብሔር
እኔና ክሪስን ለመጉዳት ብለህ ኮሪን አትቅጣው አስቀድመን ተጎድተናል
ልናደርገው ፈልገን አልነበረም ጌታ ሆይ አልነበረም በአጋጣሚ ነው
የሆነው ለዚያውም አንድ ጊዜ ብቻ በዚያ ላይ ምንም ደስታ አልነበረበትም።
እግዚአብሔር ሆይ በእውነት በእውነት ደስታ አልነበረበትም
አዲስ ቀን ነጋ ከመጋረጃዎቹ ጀርባ ውጪ ለሚኖሩት በእኛ ለማይታዩት
ህይወት ተጀመረ። ራሳችንን ዘና ለማድረግ፣ ሰዓታችንን ለመሙላትና ለመብላት ሞከርን ክሪስ እየረዳኝ የፍራሹን ልብስ ቀየርኩ ምክንያቱም በጣም ከባባድ በመሆናቸው ብቻዬን ላገባቸው አልችልም፡ በዚያ ላይ ኮሪ በአብዛኛው ሽንቱን ስለሚሸና በየጊዜው መቀየር ነበረበት፡ ክሪስና እኔ አልጋውን አንጥፈን ክፍሉን አፀዳድተን ጨርሰን ኬሪ የሚወዛወዘው ወንበር
ላይ ብቻዋን ተቀምጣ ባዶ አየር ላይ አፍጥጣለች።
አራት ስዓት ገደማ የምንሰራውን ሁሉ ጨርሰን ወደ አዳራሹ ቀረብ ወደሚለው አልጋ ላይ ተቀምጠን በሩ እጀታ ላይ አይኖቻችንን ተክለን ዜናውን ይዛልን የምትመጣልንን እናታችንን እንዲያስገባ እየጠበቅን ነው።
ጥቂት ቆይቶ እናታችን ከማልቀስ ብዛት አይኖቿ ቀልተው መጣች። ከእሷ
ጋር ባለብረት አይኗ አያታችን ረጅም፣ ድርቅ ያለችና እምባ የሌላት ሆና ተከትላታለች።
እናታችን እግሮቿ መቆም አቅቷቸው ወለሉ ላይ እንዳይጥሏት የፈራች
ይመስል በሩን ተደገፈች እኔና ክሪስ ከተቀመጥንበት ዘለን ተነስተን ቆምን፡
ኬሪ ግን እናታችን ባዶ አይን ላይ እንዳፈጠጠች ነው: “ኮሪን በመኪና ወደ
ሆስፒታል እየወሰድኩት ነበር ቅርብ ወዳለው ሆስፒታል ነበር በእውነት"
አለች እናታችን ውጥረት በተሞላበት ሻካራና አሁንም አሁንም እንቅ እንቅ
በሚል ድምፅ፡ “እና የወንድሜ ልጅ ነው ብዬ በውሸት አስመዘገብኩት"
“ውሸት! እማዬ ሁልጊዜ ውሸት እንዴት ነው?” ትዕግስት ባጣ ሁኔታ ጠየቅኳት። ሰማያዊ አይኖቿ ወደ እኛ ዞሩ፡፡ ባዶ ነገር ላይ ያፈጠጡ፣ የጠፋ፣የሆነ ለዘለአለም የጠፋ ነገር የሚፈልጉ አይኖች ሰብአዊነቷ እየፈለጉ
እንደሆነ ገምቻለሁ። “ኮሪ የያዘው የሳምባ ምች ነበር። ዶክተሮቹ የቻሉትን ሁሉ
አድርገው ነበር . . .ግን በጣም በጣም . . . በጣም ዘግይቶ ነበር”
“የሳምባ ምች ነበር?"
“የሚችሉትን አድርገው ነበር?”
“ዘግይቶ ነበር?”
“ነበር… ነበር!
ኮሪ ሞቷል እንደገና አናየውም!
ዜናው ክሪስን ልክ ወንድነቱ ላይ የተመታ አይነት ስሜት ነበር የፈጠረበት
እንደተረገጠ አይነት፡ ወደ ኋላ ተንጋሎና ፊቱን ለመደበቅ ዞሮ ትከሻዎቹ
እየተርገፈገፉ ሲንሰቀሰቅ አይቼዋለሁ።
በመጀመሪያ አላመንኳትም ነበር። ቆምኩ፣ አፈጠጥኩ፣ ተጠራጠርኩ፣ ፊቷ አሳመነኝ እና ልቤ ውስጥ የሆነ ትልቅና ባዶ ቦታ ሲሰፋ ተሰማኝ። ደንዝዤና
ሽባ ሆኜ አልጋው ላይ ወደቅኩ። ልብሶቼ ረጥበው እስክመለከት ድረስ
እያለቀስኩ እንደነበረ አላወቅኩም ነበር
ቁጭ ብዬ እያለቀስኩ ቢሆንም ኮሪ ከህይወታችን ወጥቶ መሄዱን ማመን
አልፈለግኩም ደግሞ ኬሪ፣ ምስኪን ኬሪ ጭንቅላቷን ቀና አደረገች። ወደ
ኋላ ወረወረችና አፏን ከፍታ እሪ... አለች።
ድምፅዋ ተዘግቶ መጮህ እስከማትችል ድረስ ጮኸች: ኮሪ ጊታሩን
ወደሚያስቀምጥበትና ትንንሽ ያለቁ የቴኒስ ጫማዎቹን ወደደረደረችበት
ጥግ ሄደች። መቀመጥ የፈለገችው እዚያ ከጫማዎቹና ከሙዚቃ መሳሪያው ጋር ነበር እና ከዚያች ቅፅበት ጀምሮ አንዲት ቃል እንኳን ከከንፈሮቿ አልወጣም::
“ወደቀብሩ እንሄዳለን?” ክሪስ ጀርባውን እንዳዞረ ጠየቀ።
“ተቀብሯል” አለች እናታችን፡ “በመቃብሩ ላይ የውሸት ስም አፅፌያለሁ"አለችና ከጥያቄዎቻችንና ከክፍሉ ለማምለጥ በጣም በፍጥነት ወጣች
አያትየውም ተከተለቻት፡
በፈሩት አይኖቻችን ፊት ኬሪ በእያንዳንዱ ቀን የበለጠ እየጠወለገች ነው
እግዚአብሔር ኬሪንም ሊወስዳት እንደሚችል እና ሩቅ ቦታ ባለ የመቃብር
ስፍራ በሀሰት ስም ከኮሪ አጠገብ በቅርብ ርቀት የተቀበረ አባት እንኳን
በሌለበት እንደምትቀበር ተሰማኝ።
ማንኛችንም ብዙ መብላት አልቻልንም:: ፈዛዛና የደከመን ሁልጊዜ የደከመን
ሆነናል፡ ምንም ነገር ፍላጎታችንን አያነሳሳውም: ዕንባ ብቻ። ክሪስና እኔ
ውቅያኖስ የሚሞላ ያህል አለቀስን ወቀሳውን ሁሉ የእኛ አደረግነው: ከብዙ
ጊዜያት በፊት ማምለጥ ይገባን ነበር፡ ያንን የእንጨት ቁልፍ ተጠቅመን
ወጥተን እርዳታ መፈለግ እንችል ነበር። ኮሪ እንዲሞት አድርገናል: የእኛ
ሀላፊነት ነበር! ትንሹ ባለ ብዙ ተሰጥኦውና ፀጥተኛው ውድ ልጃችን እንዲሞት አደረግን አሁን ደግሞ ጥግ ላይ ተኮራምታ የምትቀመጥ በየቀኑ እየደከመች የምትሄድ ታናሽ እህት አለችን፡
ክሪስ ኬሪ እንዳትሰማ
ቀስ ባለ ድምፅ “ማምለጥ አለብን ካቲ! በፍጥነት።
አለዚያ ሁላችንም እንደ ኮሪ እንሞታለን፡ ሁላችንም የሆነ ነገር ሆነናል።ለረጅም ጊዜ ተዘግቶብናል፡ የምንኖረው ትክክለኛ ያልሆነ ህይወት ነው፡ ልክ ጀርሞች በሌሉበት አየር አልባ ቦታ እንደመኖር ነው።
👍46😢6❤3👎1🥰1