አትሮኖስ
286K subscribers
119 photos
3 videos
41 files
573 links
╔╦╦╦═╦╗╔═╦═╦══╦═╗
║║║║╩╣╚╣═╣║║║║║╩╣
╚══╩═╩═╩═╩═╩╩╩
ግጥሞች አዳዲስና ቆየት ያሉ የታዋቂ ደራሲያን መፅሐፍቶችን በ PDF እንዲሁንም
ያልተነበቡ ድርሰቶችን ግጥሞችን ታሪኮችን ያገኙበታል።


Contact. @atronosebot
please dont touch the leave button.😔😳😳
Download Telegram
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሀያ_አንድ


#ድርሰት_በትክክል_ገና


ውድ አንባብያን ከላይ በለቀቅናቸው ሁለት ክፍሎች ላይ ማለትም 39, እና 40 ያልነው በስተት ነው ክፍል19 እና 20 ናቸው ስለተፈጠረው ስተት ይቅርታ እየጠየቅን በቀጣዩ ክፍሎች ላይ እናስተካክላለን..የቁጥር ስተት ብቻ ነው እንጂ የክፍል መቆራረጥ የለውም። መልካም ንባብ።
=========================
....“እኔና አንተ ሌላ ቀጠሮ ይኖረናል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ሰፋ አድርገን
እንወያያለን እሺ?” አለው፡፡ አንዱ አለም በደስታ ተቀበለው። ርዕሱ ተቀየረ፡፡

ምሳው አብቅቶ የሚጠጣ ነገር ሲታዘዝ፤
አንዱአለም ቢራ፤ አዜብና ትህትና ደግሞ ጭማቂ፤ አዘዙ፡፡ በወንድሟና በጓደኛዋ ፊት በመሆኑ እንጂ ከሻምበል ጋር ብቻ ብትሆን ኖሮ በዛሬው የፌሽታ ቀን ቢራ ትጠጣ ነበር፡፡ እድሜ ለዶክተር ባይከዳኝ ቢራ አለማምዷታል፡፡
ሻምበል ብሩክ ለትህትና የሆነ ነገር በጆሮዋ ሹክ አላት::
እንዲያ ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብሎ ፤ በግራ ክንዱ ትከሻዋን እቅፍ አድርጎ፤አዜብ ስትመለከት በድጋሜ ቀናች፡፡ እንደዚህ ያፈቀረችው እና ያፈቀራት ሰው አጋጥሟት አያውቅም፡፡ የሷ ጓደኞች የሳምንት ግፋ ካለ የአንድ ወር ብቻ ናቸው፡፡ ችግሩ ከማን እንደሆነ እራሷን እየጠየቀች እስከዛሬ ድረስ መልስ ያላገኘችለት ጉዳይ ነው፡፡ አብዛኞቹ “አዜቢና አዜቢና” እያሉ
እያቆላመጡ ይጠጓትና፤ ከአንድ ቀን ግብዣ በኋላ በሁለተኛው ቀጠሮ
ላይ ጨርቅ ተጋፍፈው፤ በዚያው እብስ ብለው ይጠፋሉ፡፡ እንደውነቱ ከሆነ እሷም ወረተኛ ነች፡፡ በተለይ መኪና ላለው ወንድ ልቧ ይደነግጣል። ለሚያዝናና፤ ለሚያንሸረሽር፤ ልቧ ክፍት ነው። እግረኛው ብዙም አይስባትም፡፡

“አዜቢና ከቦይ ፍሬንዷ ጋር ለምን አልመጣችም?” በማለት ነበር ሹክ ያላት፡፡ ትህትና ሣቅ አለችና...
“ በሚቀጥለው” አለችው፡፡ የሚያወሩት ስለእሷ እንደሆነ ጠርጥራ አዜብ
ትህትናን ጠቀሰቻት፡፡ እሷም መልሳ ጠቀሳቻት። ተጠቃቀሱ። አዜብ
ስለእሷ የምታውቀውን ያህል እሷም ስለአዜብ ታውቃለች፡፡
የሆቴል ልብስ የለበሱት አስተናጋጆች በጎደለ ለመሙላት ሽር ጉድ ይላሉ፡፡ ሻምበል ብሩክ እናቷን ለመጠየቅ መፈለጉን ገልጾ ያሳወቃት ወደ ማምሻው ላይ ነበር፡፡ ሻምበል ይህንን ያልጠበቀችውን እጅግ አስደሳች
የሆነ ሀሳብ ሲያቀርብላት በደስታ ተውጣ ቀና ብላ አየችው:: ፈገግ አለና
ወደ ጎን ተመለከታት፡፡
“ተያይዘን ወደ ቤት” አላት፡፡ ለዚህ ንግግሩ ካሳ ከንፈሩን መሳም ነበር፡፡ምን ያደርጋል? አይመችም።እያማራት፤ ተወችው::
"አይመሽብሽም አዜቢና" አለቻት ጓደኛዋን፡፡
“አይመሽብኝም" አለች ቶሎ ልትለያቸው ስላልፈለገች። በሻምበል ብሩክ ሀሳብ አዜብና አንዱአለም እጅግ ተደሰቱ፡፡ አንዱ አለም እስር ቤት ገብቶ ያደረ ዕለት ትደነግጣለች ብላ ከደበቀቻት በኋላ ሻምበል ብሩክ የተባለ ሰው ዋስ ሆኖ ያስፈታው መሆኑን ለእናቷ የነገረቻት፤ አንዱ አለም በሽተኛን ለመጠየቅ
ተፈትቶ እቤት ሲገባ ነበር፡፡ ከዚያን ቀን በኋላ ግን ስለ ሻምበል ብሩክ
ያልተወራበት ቀን አለ ለማለት ያስቸግራል።
በሆነው ባልሆነው የሻምበል ብሩክ ሥም እንደ ዳዊት ሲደገም እናቷ ጠርጥራለች፡፡ በዚህ ምክንያት ወ/ሮ አመልማል ሻምበል ብሩክን በመልክ ባይሆንም በዝና አውቃዋለች ማለት ይቻላል።
በሽተኛን ለመጠየቅ
ተፈትቶ እቤት ሲገባ ነበር፡፡ ከዚያን ቀን በኋላ ግን ስለ ሻምበል ብሩክ
ያልተወራበት ቀን አለ ለማለት ያስቸግራል።
በሆነው ባልሆነው የሻምበል ብሩክ ሥም እንደ ዳዊት ሲደገም እናቷ ጠርጥራለች፡፡ በዚህ ምክንያት ወ/ሮ አመልማል ሻምበል ብሩክን በመልክ ባይሆንም በዝና አውቃዋለች ማለት ይቻላል።በሽተኛን ለመጠየቅ በሚል ሰበብ ሻምበል ብሩክ ለእናቷ ያልገዛው ነገር የለም። ሥጋው፣ አትክልቱ፣ ለስላሳው፣ ኬኩ ይህንን ሁሉ ገዝተው ተሸክመው እቤት ሲደርሱ ሠራተኛዋ መጥታ በሩን ከፈተችላቸው፡፡ ልጅቷ በሻምበል ብሩክ ላይ ዐይኖቿ ተተክለው ቀሩ፡፡ግርማ ሞገሱ ያስፈራል። ከዚያም ትህትና ቀደም ብላ ወደቤት ገባችና ቤቱን ትንሽ ለማዘጋጀት ጥረት አደረገች። ጠንቃቃና ጽዳት ጠባቂ
ስለሆነች መዝረክረክ አይታይም ነበርና ብዙም አልተቸገረችም፡፡
እማዬ እንግዳ መጥቷል” ብላ ለእናቷ ሹክ ስትላት ማን መጣ ትሁቴ?” ደንግጣ ከተኛችበት ቀና ለማለት ተንደፋደፈች።
ብርድ ልብሱን እያለባበሰቻት፡፡
ወዲያው ሦስቱም ተከታትለው ገቡና ከእንግዳ ማረፊያው ከሶፋ ወንበሩ ላይ አረፍ አሉ። ቤቱ ንጹህና ቅልል ያለ ነበር፡፡ ሻምበል ዙሪያ ገባውን ተመለከተ፡፡ በትልቅ መስታወት ውስጥ ከነግርማ ሞገሱ የሚያየው ፎቶ የአባቷ እንደሆነ ገመተ፡፡ በቤቱ ንጽህናና አያያዝ ልቡ
ተማርኮ...
“የኔና የትሁት ጎጆም እንደዚችው ...” ሲል አሰበ። ትህትና ከደስታዋ ብዛት የምታደርገውን አታውቅም፡፡ የምትይዝ የምትጨብጠው ጥፍት ብሎባታል፡፡

“ሻምበል ብሩክ ነው አይዞሽ” ::
“ብሩኬ ና ወደዚህ” መጣችና እጁን ሳብ አድርጋ ካስነሳችው በኋላ ወደ እናቷ የምኝታ ክፍል ይዛው ገባች፡፡
ወ/ሮ አመልማል ሻምበል ብሩክን እንዳየችው ወደደችው። በቃ ልቧ ያለማመንታት አማችነቱን ተቀበለው። ልጅዋ ፍርጥ አድርጋ ባትነግራትም፤ እሷም ኮረዳ ሆና ባሳለፈችበት ዘመን ውስጥ የድብቅ ፍቅር ምልክቶች ምን ምን እንደሆኑ ቀምሳዋለችና፤ ልጅዋ በሻምበል ብሩክ መረታቷን በቀላሉ እንዳወቀች፤ ከወደደችው ሰው ጋር በወግ
በማዕረግ በትዳር እንድትኖር ምኞቷ ሆነ፡፡
ከዚህ ሁሉ የበለጠው ደግሞ፤ ይዛ የመጣችው ሰው ልብ የሚያስደነግጥ ለግላጋ ወጣት መሆኑን ስትመለከት፤ በደስታ ፈነጠዘች፡፡

“ጤና ይስጥልኝ እናቴ” ሄዶ ጉንጮቿን በተኛችበት ሳማት፡፡
ወ/ሮ አመልማል በዚያን ሰዓት የተሰማትን ስሜት መግለጽ አስቸጋሪ ነው። የሆነ ስሜት የሆነ የደስታ ሲቃ ተናነቃት፡፡

ለመጀመሪያ ቀን የምታየው ጠንበለል ወጣት፤ እሷን እዚያ ለረጅም ጊዜ ከአልጋ ያልተነሳችውን ገመምተኛ፤ ልክ እንደ እናቱ ሄዶ እቅፍ ድግፍ አድርጎ ሲስማት፤ ከልጆቿ አንዱ እንጂ፤ ፍጹም ባዳ ነው
ብሎ ማመን አቃታት፡፡
ይህ ለሷ ከብዶ ታያት እንጂ ፤ ለሻምበል ብሩክ ተወዳጅነትን ካተረፉለት መልካም ባህሪዎቹ አንዱ ነበር፡፡ ሰውን ትንሽ ትልቅ በማለት የማይንቅ፤ የታሰረ የታመመ መጠየቅ የሚወድ ሰው ነው። እሷም
ጉንጬን ሳመችው። እነሱን ስትመለከት የትህትና ልብ በደስታ ዘለለች::አቤት የተሰማት ደስታ!
“አይ ብሩኬ ምን ዓይነት ወርቅ ሰው ነህ?” ብሩክን በልቧ አደነቀችው::
ሻምበል ብሩክ ከዚህ በፊት የኖረ ዘመድ መስሎ ቁጭ አለ::
የመጣለትን ወንበር ትቶ እዚያ አልጋው ጫፍ ላይ አጠገቧ ቁጭ ብሎ
ራሱን ካስተዋወቀ በኋላ፤ ስለበሽታዋ፤ ስለኑሮዋ ስለወደፊቱም ፤ እያነሳሳ ሲያጨዋውታት፤ ከላይዋ ላይ የተገፈፈላት ያህል ተሰማትና፤ በሻምበል ብሩክ ሁለንተና ተመስጣ ጨዋታ ቀጠለች።

አዜብ ስለመሸባት ተሰናብታቸው ወደ ቤቷ የሄደችው የግዷን ነበር ማለት ይቻላል። የሻምበል ብሩክን ሁኔታ ያየ እንግዳ ነው ብሉ ለመናገር ይቸግራል፡፡ በአንድ ጊዜ ቤተኛ ሆኖ ቁጭ አለ። በዚህ ሁኔታ
ሲጨዋወቱ ካመሹ በኋላ ተሰናብቶ ሲወጣ፤ ከወንድሟ ጋር ሆነው
ሸኙት፡፡ ከዚያች ቀን በኋላ ሻምበል ብሩክ ቤታቸው ቤቱ ሆነ።
ከተቀጠረች ሁለተኛ ሳምንቷን ይዛለች፡፡ በእርግጥም ማለፊያ የገቢ ምንጭነቷና ገዳምነቷ ከወዲሁ እየታየ ነው፡፡ ከወትሮው ለየት ባለ ሁኔታ የደንበኞች ቁጥር እየጨመረ ነው።
እዚያ ለገበያ ገብቶ በመጀመሪያ እሷን እንደ ሽንኩርት በዓይኑ ሳይልጣት ወደ መጣበት ጉዳይ የሚመለስ መቼም ጥቂቱ ነው። የዕድሜ አቻዎቿ ብቻም ሳይሆኑ የአሮጊቱ የሽማግሌው
👍21
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሀያ_ሁለት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

“ጤና ይስጥልኝ ወይዘሪት እንዳሻው በቀለ.... እባላለሁ እራሱን በሚገባ አስተዋወቀ። እሷም ስሟን ሰጠችው። ፈርጣማ ወጠምሻ ነው።

“ምን ያህል ጊዜ ሆነሽ ሥራ ከጀመርሽ?” ድዱን እየገለፈጠ
“እንድ ሳምንት ሆኖኛል” በር በሩን እያየች::
“በስመአብ ይህንን ያክል ቀን ስትቆዪ ያለመምጣቴ ደደብ ያሰኘኛል”
“ለምን? ይኸው አሁን ተዋወቅን አይደል? ምን ልዩነት አለው?”
“ተይ እንጂ! ጊዜ እኮ የውጤት አብራክ ነው” ትንሽ እየተውረገረገ።
“እንዴት ማለት?”
“ከአንድ ውጤት ላይ ለመድረስ ድርጊት የሚወሰነው በጊዜ ውስጥ ነው
ማለቴ ነው” ሊፈላሰፍባት ሞከረ፡፡
“አልገባኝም?”::
እንደሻው በልቡ “ተይ እንጂ ቆንጂት? አንድ ሳምንት እኮ ለጥብስ የምትበቂበት ጊዜ ነበር፡፡ አሁን ግን ገና ጥሬ ነሽ፡፡ አንድ
ተጨማሪ የማብሰያ ሳምንት ሳትወስጅብኝ አትቀሪም” አለ፡፡
“ማለቴ ይሄኔ በደንብ ተዋውቀን፣ ተግባብተን፤ ሞቅ ያልን ጓደኛሞች መሆን የምንችልበት ጊዜ ነበር ማለቴ ነው”
ወደ ወ/ሮ አረጋሽ በቆረጣ ተመለከተ።
ወ/ሮ አረጋሽ በዕድሜ ጠና ያለች በዚህ ሱቅ ውስጥ ለረጅም አመታት ተቀጥራ ያገለገለች ቅጥር ሠራተኛ ናት።
ልክ እሱ እሷን ሲያይ፤ እሷም ቀስ ብላ በቆረጣ አየችውና ጠቀሰቸው፡፡
“በኔ ተማመኝ አሁን ነው የማቀላጥፋት በሚል ስሜት
ከንፈሩን ወደ ጎን አጣሞ የግራ ዐይኑን ጨፈን አደረገው። ተግባቡ።
እንደ እውነቱ ከሆነ እንደሻው እዚህም እዚያም እያለ ከሚልከሰከስ፤ ይህችን የመሰለች ልጅ መቀላጠፍ ብቻ ሳይሆን ቢያገባት የወ/ሮ አረጋሽ ምኞች ነበር፡፡ በዚህ የተጀመረው ትውውቅ ቀጠለ፡፡ አበራ በዚያን ዕለት አልነበረም፡፡ እንደሻው ድሮ ወደዚያ ሱቅ ዝር እንደማይል ሁሉ ትህትናን ካየ በኋላ ያንን የጫማ ሱቅ እንደ ቤተ ክርስቲያን ሳይሳለም ወደራሱ
ሱቅ መሄድ አቆመ፡፡
ምንም እንኳን እግሩ እስከሚቀጥንድረስ ቢመላለስም መጀመሪያ አይቷት እንደገመተው ግን አልሆነችለትም፡፡
“እንደሻው በዚህ በኩል ያለህ ሃሳብ ቢለወጥና ጥሩ ወንድሜ ሆነህ ጓደኝነታችን ቢቀጥል ደስታውን አልችለውም:: ከማንም አንሰህ
ሳይሆን፤ የግሌ በሆነ ምክንያት ብቻ ጥያቄህን ለመቀበል ስለማልችል
እባክህን ይቅርታ አድርግልኝ?” ብላ ለመነችው። -
“ምንድነው የግል ችግርሽ?” ሲል ደጋግሞ ጠየቃት፡፡
“እጮኛ አለኝ” ስትል ቁርጡን ነገረችው፡፡

እንደሻው ግን እንኳን እጮኛ ባሏ ቢሆን ደንታ የሌለው አጥር ዘላይ መሆኑን
አላወቀችም ብትለምነው ብትማፀነው
እሷን ካልቀመሰ እንደሚሞት ሁሉ እሺ ካላለችው፤ ከስራ እንድትባረር ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማይል እየገለጸ፤ ያስፈራራት፤ ጀመር፡፡
ይህ ጊዜያዊ ስሜቱ ቀስ በቀስ እንደሚለወጥና፤ ልመናዋን እንደሚቀበላት ተማምና፤በምታገኘው ጊዜ ሁላ በጸባይ ትቀርበው ነበር።

እንደሻው እንዳስበው ሳይሳካለት መቅረቱን ሲያውቅ አማላጅ አድርጐ የላካት ወ/ሮ አረጋሽ ትህትናን ለብቻዋ ጠራቻትና...ትሁት በእጅ የያዙት ወርቅ ከመዳብ ይቆጠራል አይነት ሆንሽብኝ እኮ!
ምንም ትንሽ ልጅ ብትሆኝ አመለካከትሽ ብስል መሆኑን ከተረዳሁት ውዬ አድሬአለሁ። አሁን ግን ሳይሽ ልጅነትሽ የለቀቀሽ አልመስል አለኝ፡፡
ሰማሽ የኔ ልጅ? ዕድል እጅ ላይ የምትወድቀው አንድ ጊዜ ብቻ ነው።
እንደገባችም ካልተጠቀሙባትና አንዴ ካለፈች ደግሞ በፀፀት ትጎዳለች እንጂ
ተመልሳ አትገኝም። በዚህ በቁንጅና ወቅት በዚህ በልጅነት ጊዜ ችላ
የተባለ እድል ደግሞ በእኛ ዕድሜ ላይ ከደረሱ በኋላ ና! ብለው ቢለምኑት፤ ቢጣሩት፤ ተመልሶ አይመጣም፡፡እንደታኘከ የሸንኮራ አገዳ መመጠጥና የትም ተጥሎ መቅረት ነው ትርፉ። ልብሽ ልብ ይበል!፡፡ ዛሬ የደነደነው ልብሽ ነግ ደም እንዳያለቅስ?። እግዚአብሔር ከዚህ የሀብት ባህር ውስጥ አምጥቶ ሲጥልሽ፤ በየወሩ አፍንጫዬ ላይ የሚወረወርልኝ
ሳንቲም ይበልጥብኛል ብለሽ ይህንን ሁሉ ሀብት ንብረት ብትገፊ፧
ዕድልሽ የተገፋ ነው የሚሆነው :: እወቂበት፡፡ የዚህ ቤት የሽማግሌው
አጠቃላይ ንብረት ወራሽ እንደሻው መሆኑን አትዘንጊ!! የጠየቀሽን
አድርገሽ ልጥፍ፤ ጥብቅ፧ ነው ልጄ ዋእ...!”
ያልደሰኮረችላት ዲስኩር አልነበረም፡፡ ትህትና ወይ ንቅንቅ!
“አመሰግናለሁ እትዬ አረጋሽ፡፡ ያለሽ ቀና አመለካከት፣ ምክርሽም ሁሉ ለኔ ጥሩ በመመኘት፣ እኔ ጥሩ ደረጃ ላይ እንድደርስ በማስብ እስከሆነ
ድረስ ከልቤ ነው የማመሰግንሽ :: እንደሻው ቢበዛብኝ እንጂ አንሶኝ
እንዳልሆነ አምናለሁ፡፡ በሁሉም ረገድ ከኔ የበለጠች ማግኘት የሚችል ሲሆን እኔ ግን ለሱ የማልገባ እዚህ ግቢ የማልባል መናጢ ደሀ መሆኔንም አልዘነጋሁትም፡፡ ይህንን ሁሉ ደግሞ ለሱ ነግሬዋለሁ። እትዬ አረጋሽ የማፈቅረው ጓደኛ አለኝ፡፡ በሱ ላይ ደርቤ ማፍቀር አልችልም፡፡
እባክሽን ይቅርታ እንዲያደርግልኝና ሀሳቡን እንዲለውጥ ለምኝልኝ?”
በማለት እግሯ ላይ ወድቃ እያለቀሰች ለመነቻት፡፡
ወ/ሮ አረጋሽ በልጅቷ ንግግር ልቧ ቢነካም፤ ጉልበተኛው እንደሻው ያጋጨኛል ብላ ስለፈራች! የአደራ መልዕክቱን ለእንደሻው ሳታደርስላት ቀረች፡፡

የወይዘሮ አረጋሽ አማላጅነት
በቀጠሮ እየተጓተተ ውጤት የማይታይበት ሆኖ በመገኘቱ እንደሻው ተናደደና አበራን አማከረው::
“ይህቺ ጭንጋፍ አሮጊት ያነጋገረቻት አልመሰለኝም፡፡በንዴት መንጋጭላዋን ከማውለቄ በፊት ምን አለበት ብትገላግለኝ?!” ሲል ለአበራ ጥያቄ አቀረበለት፡፡
“እንዴት ማለት?”
“ትህትናን በጣም አፍቅሬአታለሁ፡፡ በተደጋጋሚ አነጋግሬአታላሁ፡፡ፈቀደኛ አልሆነችም፡፡ እሺ ብትላት ብዬ አበራሽን አማላጅነት ልኬባት ነበር፡፡ ለሷም እሺ ያለቻት አልመሰለኝም፡፡ አንተ አለቃዋ ስለሆንክ ልትፈራህ ትችላለች፡፡ በእውነት ነው የምልህ አበራ የወደድኳት፡፡ በቀላሉ አገኛታለሁ ብዬ ነበር የገመትኩት፡፡ እንደገመትኩት አልሆነም፡፡ ልታግባባልኝ የምትችለው የመጨረሻው ሰው አንተ ብቻ ነህ፡፡” ለመነው፡፡ እንደሻው እንደተስገበገበባት ከሁኔታው ተገነዘበ፡፡
አበራና እንደሻው ፍቅራቸው በከፈቱት ንግድ ምክንያት እየጠበቀ የሄደ
ሽሪኮች ስለሆኑ እምቢ ሊለው አልፈለገም።

“አይዞሽ! እንደሻው ሁሉንም ነገር ለኔ ተይው! እኔ እጨርሰዋለሁ! በኔ ተማመኝ!” ጀርባውን ቸብ፤ ቸብ፤ በማድረግ ተስፋ በተስፋ አደረገው። አበራ ሙሉ በሙሉ ተማምኖ የእሺታ ቃሏን ለመቀበል ብቻ ያነጋገራት
“ልሸኝሽ በማለት በመኪና ውስጥ ካስገባት በኋላ ነበር፡፡

ስሚ ትህትና!” ፊት ለፊት እየተመለከተና መሪውን እያስተካከለ።
“አቤት ጋሽ አበራ” አንድ የሚነግራት ነገር እንዳለ በመጠራጠር ስሜት ወደጐን እያየችው፡፡
“እንደሻው አነጋግሮሽ ነበር መሰለኝ” መሪውን በእጁ እየመታ።
“ስለምኑ?”
“ያው ነዋ!! እንደሚወድሽ” ፍርጥ አደረገው፡፡ ምን ዙሪያ ጥምጥም
መሄድ ያስፈልጋል?።
ትንሽ እንደማፈር አለችና በኃይል መምታት የጀመረው ልቧ ሲረጋጋላት፡-
“አነጋገርኳት አለ እንዴ?” አለችው፡፡
“ከዚያም አልፎ አረጋሽንም እንደላከብሽ ሳይደብቅ አጫውቶኛል” እየሳቀ።

አዎን እንደሱ ነው”ውጭ ውጭውን በመስታወቱ አሻግራ እየተመለከተች፡፡
“ታዲያ ምን መልስ ሰጠሽው?”
“ያው እንደነገረህ ነዋ ጋሽ አበራ?” የሰጠችውን መልስ እያወቀ
እንደሚጠይቃት ገብቷታል።
" መልሱ ያንቺ መሆኑ አጠራጥሮኝ ነው እኮ የምጠይቅሽ?” የአለቅነት ስሜቱ እየታገለው ነበር፡፡በዚህ ላይ ደግሞ ስራውን ምን ያህል እንደምትፈልገውና ችግረኛ መሆኗን በሚገባ ያውቃል፡፡

“ምንም አያጠራጥርም ጋሼ አበራ፡፡ በእርግጥ እንደሻው የሚጠላ ወይንም
ለኔ የሚያንስ ልጅ ሆኖ አይደለም። እንደኔ ያለች ደሃ እሱን
👍1🔥1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሀያ_ሶስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

ሻምበል ብሩክና ትህትና ድንበሩ ከተዋወቁ ዛሬ ልክ አንድ ወራቸው፡፡ የፍቅራቸው ወርሃዊ ልደት ውል የሚበጅበት ቀን በመሣሣም ደረጃ የቆየው ፍቅር ዛሬ ወደ አካላዊ ውህደት ሊሸጋገር እቅድ ተይዞለታል። ሻምበል ብሩክም ሆነ ትህትና የዛሬውን ቀን በልዩ ጉጉት ነው የጠበቁት።

እሁድ ዕለት አሥመራ መንገድ በሚገኘው በሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር የወሰነችበት ቀን ነበር፡፡ ወደ ዶክተር ባይከዳኝ ቀጠሮ ስትሄድ የሚሰማት ስሜት ከቀጠሮው በስተጀርባ ባለው ምክንያት አስገዳጅነት እንጂ በፍቅር አስገዳጅነት አልነበረም፡፡
ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር የምትፈጽማቸው ግንኙነቶች እውነተኛ ስሜቷን የምትገልጽባቸው ሳይሆኑ፤ በተላበሰችው ጭምብል እውነተኛ ማንነቷን ደብቃ፤ በመድረክ ላይ ትያትር የምትሰራ ተዋናይ ሆና ነው የምትውለው፡፡ በሻምበል ብሩክ ፍቅር ግን ሰውነቷ እንደሻማ እየቀለጠ፣
ልቧ በዕልልታ እየጨፈረች፤ ሁለንተናዋን አሳልፋ የምትሰጠው በደስታ ስሜት ሰክራ ነው፡፡ በተለይ የመጀመሪያዋ በሆነው የወንድ ልጅ ፍቅር የተረታችለት ሰው፤ እንደዘመኑ ወጣቶች በአንድ ነገር ላይ ብቻ ትኩረት የሚሰጥ ሳይሆን በሷ ቦታ ሆኖ ሁሉን ነገር የሚያስብላትና፤
የሚያጽናናት፤ ሆኖ በመገኘቱ ፈጣሪዋን ታመሰግናለች፡፡
ብቻ አንዳንድ ጊዜ የሰው ልጅ ሥጋ ለባሽ ፍጡር ነውና፣ ሰው ተላላና ደካማ ፍጡር ነውና፤ ሰው ሰው ነውና፤ ይህ ሁሉ ፍቅር ድንገት ብን ብሎ ጠፍቶ፣ ሻምበል ብሩክም ተለውጦ፣ እንዳይከዳት ልቧ
መጠርጠሩ አልቀረም፡፡
እንደዚያ ታስብና ደግሞ አስተሳሰቧ ትክክል ባለመሆኑ እራሷን ወቅሳ “ብሩኬ አይለወጥም”
በማለት መልሳ መጽናናትን ታሳድራለች፡፡ በዛሬው ዕለት ሻምበል ብሩክ ቤት ለማደር ቀጠሮውን በልቧ የወሰደችው በከፍተኛ ደስታ ነው። ምናልባት የዛሬው አዳር ደግሞ ያንን ተንከባክባ ያቆየችውን የልጃገረድነት ወግ፣ ብር አምባሯን የምትፈተሽበት ወቅት ሊሆን ይችላል፡፡ ከዚያ በኋላ “ዞር በይ” ቢላትስ? ልቧ
በመጠራጠርና፤ ባለመጠራጠር፤ስሜት መሀል ገብቶ ሲዋዥቅ ከዋለ በኋላ
አንድ ነገር አሰበች።

ለሻምበል ብሩክ ልጃገረድ መሆኗን ገልጻለት፤ እንደ ወጉ፤ እንደ ሥርዐቱ፤ በጫጉላ ቤት ብር አምባሯን ልትሰጠው ያላትን ምኞች የሱን ስሜትና ፍላጐት ከተረዳች በኋላ ካሳወቀችውና በአጠቃላይ ስለማንኛውም ነገር አብረው በጋራ መወሰን እንደሚችሉ ገምታ፤ በዚሁ ሃሳብ ፀናች።
“እማይዬ ዛሬ አዜቢና ጋ ነው የማድረው ፓርቲ አዘጋጅታለች' በማለት እናቷን ዋሸቻት።
“ባርቲ ደግሞ ምንድነው ትሁቴ?” እናት በመጠራጠር ስሜት፡፡
“ያው ነዋ! ጓደኞቿ ተሰባስበን ስንጫወት ማደር ማለት ነዋ!” እየሳቀች፡፡
አደራሽን የኔ እራስሽን ጠብቂ!!” እናቷ ዐይን ዐይኖቿን እያየቻት።የውጭ አዳር የተሰማው ገና ዛሬ ነው፡፡
“ምንም ችግር የለም:: ማሚ ሙች!” ጉንጫን ሳመቻት፡፡ እናቷ በልቧ
ዝግጅቷን አሰበችው፡፡ በጠዋት ተነስቶ መተጣጠቡ፣ ቀኑን ሙሉ ሲመረጥ የተዋለው ልብስ፣ ሦስት ጊዜ አውልቃ ቀይራለች። መስተዋቱ ሥራ አልፈታም፡፡ መኳኳሉ ሁሉ ያልተለመደ ነበር።
በልቧ ወደ ሻምበል ብሩክ እንደምትሄድ ብታውቀውም የሰጠቻትን ምክንያት ይሁን ብላ ተቀበለቻት፡፡
ዛሬ ሻምበል ብሩክ ጋ የምታድር መሆኗን ለአንዱአለም ስለነገረችው በጊዜ ወደቤት እንዲገባ ተስማምተዋል። በዚህ ላይ የቤት ሰራተኛዋ እታፈራሁ ታክላበት እናቷን በመንከባከብ በኩል ኃላፊነቱን
ስለሚወስዱ የሚያስጨንቃት ነገር አልነበረም፡፡ ሁሉንም አጥብቃ አደራ
ብላ፤ ከቤት የወጣችው ከቀኑ አሥራ ሁለት ሰዓት ላይ ነበር።
ሻምበል ብሩክ ዛሬ ሽር ጉድ ሲል አርፍዷል። አልጋው ቦታ ሲመረጥለት፤ ሲንከራተት፤ የቤቱ ቁሳቁሶች በሙሉ በአዲስ መልክ አንዴ በጭንቅላታቸው፧ አንዴ በእግራቸው፤ ሲቆሙ፤ ቦታ ሲመረጥላቸው ነው የተዋለው፡፡
በዛሬው የቤት ዝግጅት ላይ ሠራተኛዋ ብቻ ሳትሆን ሁለቱም ታናናሽ ወንድሞቹ አብረውት ቤቱን ሲያተራምሱት ነው የዋሉት፡፡
በመጨረሻ ላይ ግን ከዚያ በፊት ያልታየበት ዓይነት ሥርዓትና መልክ ይዞ ሲያይ ሻምበል ብሩክ ተደነቀ፡፡
በእርግጥም ይህ ሁሉ የሆነው በትህትና ምክንያት መሆኑን ሲያስብ፤ የትዳር ውጥኑ አግባብ መሆኑን አመነ። በዚያ በቤቱ ሥርዓት ተማርኮ ወደሌላ ሃሳብ ውስጥ ገባ፡፡
ባለፋቸው መጥፎ ጊዜያቶች ውስጥ የተጐዳ ልቡ፣ በትህትና የወደፊት የትዳር እመቤቱ አማካይነት ሊታደስና፤ ሲታነጽ፤ ታየው።
እናም የትዳር መዓዛ በርቀት ሸተተው፡፡ ይህ በርቀት የሚሸተው የትዳር መዓዛ ቀርቦ እንዲያውደው ተመኘ፡፡
ትህትና እስከምትመጣለት የቀጠሮው ሰዓት እስከሚደርስ ድረስ ተንቆራጠጠ።
ዛሬ የሚነግራት ትልቅ ጉዳይ አለው። እሷም እንደሱ በጉዳዩ
ላይ ፈቃደኛ ከሆነች ጉዳዩ የምሥራች ይሆናል። እሷን የፈለጋት ጊዜያዊ
ፍቅረኛ እንድትሆነው ሳይሆን፤ ዘላቂ የትዳር ጓደኛው እንድትሆን ነው::
ይህ እሱ የጓጓለትን በፀጋ ከተቀበለችለት ደስታው እጥፍ ድርብ ይሆናል፡፡
“ትሁት.. ትሁት.. ትሁት.. ስሟን ደጋገመው። በልቡ፡፡

ልክ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ታላቋ እንግዳ የዱር ጽጌረዳ መስላ አምራና፤ ደምቃ ከች! አለች፡፡ ቤቱን ከዚህ ቀደም አንድ ሁለት ጊዜ አይታዋለች፡፡ የዛሬውን ልዩ የሚያደርገው ለማደር ወስና የመጣችበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡
ሻምበል ብሩክ ከደጅ ወጥቶ እየተጠባበቃት ነበር። በሁለመናው
አቅፎ ተቀበላት፡፡
ከዚያም አጥሩን ዘልቀው እየተሳሳቁ፣ እጅ ለእኛ ተያይዘው ወደ ቤት ገቡ፡፡
የሻምበል ብሩክ ሁለት ታናናሽ ወንድሞቹ ሰላምታ አቅርበውላት ትንሽ ከተጫወቱ በኋላ የግል ነፃነት ሊሰጧቸው ወጡ።
ዛሬ የሻምበል ብሩክ ቤት ልዩ ሆናለች:: ትህትናም ከዚያ በፊት ያየቸው ቤት መሆኑ እስከሚያጠራጠራት ድረስ የቤት ዕቃዎቹ አቀማመጥ አስደንቋታል፡፡
ሻምበል ብሩክ የትዳር ምኞቱን ሊገልጽላት ሲያሰላስል፤ እሷ ደግሞ ሌላ የምትገልጽለት እጹብ ድንቅ የሆነ የምስራች ነበራት። ሻምበል ብሩክ በፍቅር ቢወድቅላትም፤ ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ ያልገመተውን ገፀ በረከት ልታቀርብለት ማሰቧን ቢያውቅ ኖሮ ምንኛ ደስተኛ ይሆን ነበር?፣
ቀለል ያለ እራት ከበሉ በኋላ ይሄንን የቀዘቀዘ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራቸውን
መኮምኮም ቀጠሉ። ዛሬ ቢራው አልመረራትም። የፍቅር ስኳር
ተጨምሮበት ነው መሰል፤ ከምትወደው ሰው ጋር በፍቅር እየቀለጡ፤ ሲኮመኩሙት ማር ሆነና ቁጭ አለ፡፡ ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ሆና ስትጠጣው የግራዋ ጭማቂ ያህል ነበር የሚመራት። አሁን ግን ጣፈጣት፡፡
አንዱን ቢራ ጨረስችና በህይወቷ ለመጀመሪያ ጊዜ ሁለተኛውን የቢራ ጠርሙስ ጨበጠች፡፡ ሻምበል ብሩክ የወደፊት የትዳር ጓደኛው ከምትሆን ቆንጆ ጋር እያሳለፈ ባለው ጊዜ እጅግ ከመደሰቱም በላይ ከረጅም ዓመታት በፊት እጮኛው ከነበረችው በድሏ ጋር ያሳልፉ የነበረውን ዓይነት ልዩ ስሜት አጫረበትና፤ ጨዋታውን በሰፊው ቀጠለ። እየተቃቀፉ መላላሱ ፤ መሳሳሙ፤ ሁሉ ለጉድ ነበር፡፡
ከምሽቱ ሦስት ሰዓት ሲሆን ወደ መኝታ ክፍላቸው መሄድ ፈለጉ።
የመኝታ ክፍሏ በንጽህና የተጠበቀች ናት። እንደገቡ በነጭ ስስ የመጋረጃ ጨርቅ የተሸፈነውን ባለመስታወት መስኮት ሲገልጡት ፍንትው ብላ ደምቃ የወጣችው ጨረቃ ብርሃኗን ወደመኝታ ክፍላቸው ውስጥ አዘለቀችላቸው...

ያንን የጨረቃ ውበት ሲያስተውሉ፤ መብራቱን አጠፉት በዚያች ክፍል
ውስጥ ጨረቃና ፍቅር ነገሱ ከዚያም ልብሳቸውን እንደለበሱ አልጋቸው ላይ ጋደም ብለው መላፋታቸውን ቀጠሉ....
የትህትና ሁኔታ የተለየ ነበር ከዚያ በፊት ለወንድ ልጅ የነበራት ስሜት ምን እንደ ነበረና አሁን ምን እየሆነች እንዳለች
ስታስበው
👍2🔥21
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሀያ_አራት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

...ከቀኑ አሥር ሰዓት ተኩል ሆኗል፡፡ ዶክተር ባይከዳኝ በዛሬው ዕለት ከመሰል የሥራ ባልደረቦቹ ጋር ከፍተኛ የቀዶ ጥገና ሕክምና አጋጥሞት ነበር የዋለው፡፡ የቀዶ ጥገናው የተደረገላት ሴት በማኅፀን ዕጢ
በሽታ የምትሰቃይ ነበረች፡፡የሆድ ዕቃዋ ተከፍቶ ተከፈፍቶ የተገመተውና፤ በተግባር የታየው የሰማይና ምድር ያህል
ልዩነት ነቀረው።

በማህፀኗ ላይ ለአራት ሰአት የተደረገው የቀዶ ሕክምና ከሁለት ኪሎ ግራም በላይ ዕጢ እንዲወጣላት አስቻለ፡፡ ዶክተር ሰውነቱ በሥራ ደክሞ ስለዛለ በቂ ዕረፍት ለመውሰድ በጊዜ ወደ ቤቱ ገብቶ አልጋው ላይ ጋደም ለማለት ፈልጓል፡፡
ከድካሙ ቀለል እንዲለው ፤ በቀዝቃዛ ውሃ ገላውን ሙልጭ አድርጉ ከታጠበ በኋላ፤ የጥጥ ፒጃማውን እንደለበሰ ነበረ የተኛው፡፡በዚሁ መሀል ትህትና ገርበብ ያለውን የመኝታ ክፍሉን በር ከፍታ ገባች::
በዛሬው ዕለት ያለወትሮዋ የተርከፈከፈችው ሽቶ ቀድሟት ገባና
ክፍሉን በመዓዛው አወደው:: የዱር ጽጌረዳ፣ ጣፋጭ መዓዛ፤ እሷም
የጽጌረዳ አበባ መስላለች። ወትሮ ከሚያውቃት ትህትና በእጥፍ አምራ
ተውባለች፡፡ ኮቴዋን ሳታሰማ ወደሱ ትመጣለች፡፡
ቁልቁል ትመለከተዋለች፡፡ ገርበብ ባሉት ዐይኖቹ ሰረቅ አድርጎ አያት፡፡ በልቡ ውበቷን አደነቀ። ቀጭን ሳቋ ጆሮውን ሰረሰረው፡፡ ዐይኖቹን ገለጥ አድርጉ በሚያየው ነገር ተደንቆ፤ ሽቅብ ተመለከታት፡፡ እሷም በፈገግታ ተሞልታ እየተፍለቀለች ጐንበስ ብላ ጉንጬን ሳመችው፡፡
ከበላዩ ቆሞ፤ ውብ ፈገግታን የሚለግስ፤ በኋላም በአካል የሚዳስስ፤ መልአክ መስላ ታየችው፡፡
የዛሬው አመጣጧ ድንገተኛ ሆኖበታል። የተቀጣጠሩት ለዛሬ አልነበረም፡፡ እንዴት ቀድማ መጣች? ገረመው። ከቀጠሮ በፊት መምጣቷ ምናልባትም በፍቅሩ ወጥመድ እየወደቀችለት ለመሆኗ ፍንጭ ስለሰጠው የደስታ ስሜት የሠራ አካላቱን አዳረሰው፡፡
“የደብረዘይቱ የሽርሽር ውጤት እየታየ ነው” አለ በልቡ፡፡ የሚገርመው ደግሞ አንጀቱን ለመብላት ያላደረገችው ጥረት የለም፡፡ የለበሰችው ስስ ተካፋች ጃኬት እኒያ ገና ከሩቅ ሲያያቸው ውሃ
የሚሆንላቸው! ጡቶቿን፤ አጋልጦ ያሳያል። በዚህ ላይ እኒያን ውብ ባትና ጭኖቿን፣ በግልጽ የሚያሳይ አጭር ቀሚስ ነው የለበሰችው፡፡

“በቃ በፍቅር ወድቃልኛለች ማለት ነው”
በስሜት እንደሰከረ ፍዝዝ ባሉት ዐይኖቹ ይመለከታት ጀመር። ጭውው አለበት፡፡ ሽውው የሚል ነፋስ ሲነፍስ፣ የፍቅር አማልክት በያሬዳዊ የሙዚቃ ቅኝት
ስለፍቅር ሲያዜሙ ፧ ተሰማው፡፡ ድብት የሚያደርግ የድካም ስሜት..ድቅቅ
ያለ ሰውነት በደስታ የሰከረ ቀልብና ልብ፡፡
አሁንም ከት ብላ ሳቀች። አሳሳቋ እንደ ገደል ማሚቶ አስተጋባ፡፡ ሁኔታዋ ሁሉ ግርም ብሉት፤ አፉን ከፍቶ ይመለከታት ጀመር፡፡ ዐይን አፋራ፣ ቅልስልሷ ፤ ትህትና መሆኗን ተጠራጠረ፡፡ ፍቅር ያንን ሁሉ
የእፍረት ማቅ አሽቀንጥራ እንድትጥል አድርጓታል ማለት ነው? ፍቅር እውር ነው ወይስ እውር ያደርጋል? በትክክል እውር እንደሚያደርግ ከሷ እንደዚህ የውቦች ቁንጮ ሆናለት፤ ከቀጠሮአቸው በፊት ሹልክ ብላ ስትመጣለት ምን ይባላል? ማመን አልቻለም፡፡
ዐይኖቹን አሸት አሸት አድርጉ ሁለት እጆቹን ወደላይ ዘረጋና
“ትሁትዬ” አላት በደከመ ድምጽ።
ቀስ በቀስ ያ ሰውነቱ እየጋለ መሄድ ጀምሮ ነበር፡፡ በተለይ የዘረጋላት እጆቹን ወደዚያ ውርውር አድርጋ..
“ከቀጠሮ በፊት ስለመጣሁ መዘነጥህ ነው?” ብላ ከተሰቀለው መስታወት
ውስጥ ፊቷን ለማየት ዘወር ስትል፤ አጭሩ ቀሚስ እላይ ድረስ ዘልቆ እኒያ የሚያማምሩ ጭንና ባቶቿን ወለል አድርጉ ሲያሳየው አልቻለም፡፡ቀስ በቀስ እንደ ካውያ እየጋለ በመሄድ ላይ የነበረው ሰውነቱ የሚያደርገውን ያሳጣው ጀመር፡፡
በተለይ የምትሽኮረመም ሴት ይወዳል። እንዲያ ግፍትር አድርጋው ስትሽኮረመም፧ እልህ ያዘው። በዚህ ላይ ባቶቿ ኑ ብሉኝ! ኑ ብሉኝ! እያሉ ይጋብዛሉ። በዚያ ባዶ ቤት ውስጥ፤ በዚያ ሰፊ የሞዝቦልድ አልጋ ላይ እየተንከባበሉ፤ ያንን ባለፈው ጊዜ ተልፈስፍሶ ያመለጠውን ሲሳይ ዳግም እንዳያመልጠው ሊሞክር ቸኩሎ ተነሳና...
“ከቀጠሮ በፊት መምጣትሽ ምን ያህል ልቤን እንዳስደሰተው ከፍተሽ ባየሽው የኔ ቆንጆ?” በጀርባዋ በኩል ሄዶ፤ በሁለት እጆቹ እቅፍ አድርጓት፤ አንገቱን በአንገቷ ውስጥ ቀበረና! ጡቶቿን ያሻሻቸው
ጀመር..
ቀስ በቀስ እየሞቀች ስትሄድ ግለቷ ተሰማው። ከዚያም አፏ እንደተከፈተ ዘወር ስትልለት፤ በተከፈተው አፉ ቀለባት፡፡ ከዚያም እጆቹ ወገቧ ላይ ሲጠመጠሙ፤ እጆቿ ደግሞ በአንገቱ ዙሪያ እንደ ድር
ተጠንጥነው፤ ሰስሜት ተዋህደው ነጐዱ.....
እኒያ ውብ አይኖቿ ስልምልም ብለው ጠፉ፡፡ ከዚያም ቀስ ብለው እየተደነቃቀፉ፤ እየተደጋገፉ፤ ወደ አልጋው ሄዱና ወደቁ፡፡ ዛሬ ትህትና እንደዚያን ዕለቱ ዐይኖቿ በእንባ አልተሞሉም፡፡ ይልቁንም በደስታ እየተፍለቀለቀች፤ በፍቅር፤ ለፍቅር፤ ስትል ሁለመናዋን በግልጽ እየሰጠችው ነው፡፡
ዶክተር በዛሬው ዕለት ብር አምባር ለመስበር በእርግጠኝነት መንፈስ ተሞልቷል፡፡ በደብረ ዘይቱን የሽርሽር ወቅት በተለይም በሆራ ራስ መኝታ ክፍል ውስጥ ሲልፈሰፈስ ያመለጠው
እንዳያመልጠው በመስጋት፤ ኃይሉን የአንበሳ፤ አድርጎ ትግሉን ቀጠለ፡፡
የታጠቀችው የውስጥ ሱሪ ከዚህ በፊት የሚያውቀው ነጩ ባለወንፊቱ ነበር፡፡ በስሜት ደርተው ሲታገሉ፣ በፍቅር ስሜት ተውጣ የሆነ ነገር እያቃሰተች በጆሮው ሹክ አለችው፡፡ “አስገ...ው...ባ..ው..ው."

በዚህ ጊዜ ዶክተር በሲቃ ስሜት ተውጦ ካሰበበት ለመድረስ ጥድፊያውን ቀጠለ፡፡
እሷ ለሚሆነው ነገር ሙሉ ለሙሉ እራሷን ዝግጁ አድርጋ ሲመለከት፤ ደስታው እጥፍ ድርብ ሆነ፡፡ ዶክተር ላብ በላብ ሆኗል።ትህትናም በላብ ተነክራለች። ከረጅም ጊዜ ትግል በኋላ ...
“ዋ!!.......ይ!! !” ብላ ጮኸችና የዶክተር ባይከዳኝን ሰውነት በጥፍሮቿ ግጥም አድርጋ ይዛ አለቀሰች፡፡ ዶክተር ስለተቧጠጠ ገላው ደንታም ሳይሰጠው በድል አድራጊነት እርካታ ተውጦ ግዳዩን ለማየት ተጣደፈ፡፡
በእርግጥም ድል አድርጓል፡፡ በዚያው ስሜቱ እስከሚረካ ድረስ ቆየ። ከዚያም ተዘርራ ተመለከታት፡፡ ይህ ውስጥ ለውስጥ ያደርገው የነበረው ስሜታዊ ትግል፤ ቀስ በቀስ በውስጡ ሲሯሯጥ ከቆየ በኋላ፤ አንድ ደረጃ ላይ ሲደርስ፤ ወደ ገሀዳዊው ዓለም ተለወጠ፡፡
በዚህ ለውጥ ሰዓት ከእግር ጥፍሩ፤ እስከራስ ጠጉሩ ድረስ የነዘረው ንዝረት አባነነውና፤ በላብ እንደተዘፈቀ ከገባበት የቅዠት ዓለም ወጣ! እግዜኦ! ዶክተር በዚያን ሰዓት የተሰማውን የስሜት ስብራት በቃላት ማስቀመጥ ይከብዳል።
ያ ሁሉ ዓለም፣ ያ ሁሉ ደስታ፤ እንዲህ እንደዋዛ እንደጉም በንኖ ጠፋና፤ የሱን ስሜት እንዳይሽር አድርጎ አቁስሎት በፀፀት ጉድቶት አለፈ፡፡ ያ ሁሉ የድል አድራጊነት ስሜት በቅጽበት ቦታውን ለሽንፈት ለቀቀና፤ በዶክተር ባይከዳኝ ልብ ውስጥ ሀዘን ጥቁር ደመናውን አጥልቶበት ሄደ...
“ቡል ሺት! ” አለና ትራሱን በቡጢ ጠልዞ የሆነውን ነገር እንደ አዲስ አስተዋለ፡፡ በቅዝቃዜው ስሜት ተጠራጥሮ ሲዳብስ፤ ፒጃማውን ረጥቦ አገኘው፡፡ ከዚህ በኋላ ሁኔታዎችን ቀስ ብሎ ይመረምር ጀመር።
በቀላሉ የሚልፈሰፈሰው አካሉ አሳድሮበት የነበረው ሥነ ልቡናዊ ተጽዕኖ
ለጥቂት ጊዜ እራሱ በፈጠረው ትንሽ የቅዠት ደሴት ውስጥ ጠፍቶ፤ነበር
ጊዜያዊ የተስፋ ጮራ በልቡ ውስጥ እንደፈነጥቅበት፤ እሱም ጓደኞቹ
ማድረግ የሚችሉትን ሁሉ ለማድረግ እንደሚችል፤ አረጋግጦለት ነበር።.....

ድንግልናን መግሰስ በማይችል አካላዊ ብቃቱ ለዘመናት አዝኖ እንዳልኖረ ሁሉ፤ በዚህች ቅጽበት፤
2👍2🔥1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሀያ_አምስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

ቀናት ገሠገሡ። ሳምንታት አለፉ። አሮጌው ሄደ፡፡ አዲሱ መጣ፡፡ የጊዜ
ዑደት ሕግ ሥርዓቱን ጠብቆ በአንድ አቅጣጫ ወደፊት ያመራል።
ህይወት ግን በዝብርቅርቅና በውጣ ውረድ ቀለበት ውስጥ እየተዟዟረች
ትህትና ድንበሩና ሻምበል ብሩክ በላይ በከንፈር ማህተም ያፀደቁትን ቃል
ኪዳን ጠብቀዋው ስለወደፊቱ የትዳር ህይወታቸው በሰፊው መወያየቱን
ከጊዜ ጋር ትራመዳለች::
ቀጥለዋል።
ሻምበል ብሩክ በቤተሰቡ ልብ ውስጥ ዘልቆ ከገባና ዝምድናውን ካጠናከረ በኋላ ያ ቤት ድሮ የትህትና አባት መቶ አለቃ ድንበሩ እያለ የነበረውን የህይወት ሙቀት ቀስ በቀስ መላበስ ጀምሯል፡፡
ይህ አባት አከል የወደፊት የትዳር ጓደኛዋ፤ ወድቆባት የነበረውን የህይወት ሸክም አቀለለላት፤ “አለሁልሽ” እያላት ነው፡፡ ለእናቷ የተጠየቀውን ገንዘብ ከፍሎ ሆስፒታል ተመልሳ እንድትገባ ያደረገ
ዕለት...
“ ለምን ሌላ ሆስፒታል አናስተኛትም ብሩኬ?” ስትለው፡፡
“የመጀመሪያው ሆስፒታል ምን አለን ትሁት?” አላት፡፡
“እሱማ ምንም አላለን፤ አማራጭ እስካለን ድረስ ለምን ሆስፒታል አንቀይርም ለማለት ፈልጌ ነው እንጂ” አለችው መልሳ።
“እንደኔ፤ እንደኔ፤ መጀመሪያ ሲከታተላቸው የቆየው ዶክተር
ቢያክማቸው ውጤቱ ያማረ ይሆናል ባይ ነኝ፡፡ አዲስ ዶክተር ማለት አዲስ ህክምናን ሀ ብሎ እንደመጀመር ነው የሚሆነው፡፡ ይሁን ካልሽም እሺ” አላት ዐይን ዐይኖቿን በፍቅር እያየ።
ከዶክተር ባይከዳኝ ሙሉ ለሙሉ ለመራቅ እንጂ፤ በህክምናው በኩል ተደናቂ ሀኪም መሆኑን ዘንግታው አልነበረም፡፡ ሻምበል ብሩክም ልክ አዜብ እንዳለቻት ሁሉ ህክምናውን የመጀመሪያው ሀኪም
እንዲቀጥል ሀሳብ ሲያቀርብላት ጥያቄዋን አነሳች፡፡
በዚህ ሰዓት ሆስፒታል በመቀየር ከምታገኘው ጥቅም ይልቅ የእናቷን ጤንነት ከመጀመሪያው ጀምሮ ሲከታተል በቆየው ዶክተር ህክምናውን መቀጠሉ የሚያስገኘው ጥቅም አመዝኖ ታያትና...
“እንግዲያውስ ይሁን” በማለት ተስማማች። ዕድሜ ለሱ። ዛሬ የሰላምና የንፁህ አየር እየተነፈሰች የወደፊት የትዳር ህይወቷን ትልም በመንደፍ ላይ ነች ፤ እናቷ ተገቢውን ህክምና እንድታገኝ የሚቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው። በሻምበል ብሩክ ከፍተኛ ምክርና ጥረት አንዱአለም
ችላ ብሎት የነበረው ትምህርቱን በሚገባ መከታተል ጀምሯል።
ይህ ውጣ ውረድ የበዛበት ህይወቷን ለማስተካከል እንድትችል ማካካሻ ያገኘችበት መልካም እድል
ሊሆንላት፤ የዶክተር ባይከዳኝና
የእንደሻው ጥላ ደግሞ በሄደችበት እየተከተላት፤ ሀሳቧን ጠቅለል አድርጋ
እንዳትተኛ እንቅፋት ከመሆን አልቀረላትም፡፡
ዶክተር ባይከዳኝ በፍቅሯ እንደተቃጠለ ነው። እንዲያውም እስከመጨረሻው የሱ ሆና እድትቀር የነበረው ምኞቱን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማሳካት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል።
ልዩ ልዩ ስጦታዎች ያበረክትላት ጀምሯል። የዶክተር ባይከዳኝ ጥርስ የሌለው አንበሳነት፤ በህይወቷ ላይ ችግር የማያስከትል በመሆኑ እናቷ ሙሉ ለሙሉ ከበሽታዋ ድና እስከምትወጣ የተለመደውን ከልብ ያልመነጨ ፍቅር እያቀመሰችው ለመቆየት ወስናለች።
ይህንን የወሰነችው ደግሞ ብቻዋን አልነበረም፡፡ ከአዜብ ጋር በደንብ አድርገው ከተወያዩበትና ከተማመኑ በኋላ ነው።
“አዜቢና ለምን ቁርጡን አልነግረውም?” በማለት ስሜቷን ለጓደኛዋ ስትገልጽላት።
“ምን ብለሽ ትሁት?” ስትል ጠየቀቻት።
“በቃ እጮኛ እንዳለኝና እንዲተወኝ ብጠይቀውስ?”
“ሞኝ ሆንሽ እንዴ ትሁት? እንደሱ ብለሽ ብትነግሪው የሚያምንሽ ይመስልሻል? ጠልተሽው የደረብሽበት ነው የሚመስለው፡፡
በዚህ ላይ ይሄ ሁሉ የስጦታ ግርግር ፍቅር መሆኑን አትርሺ!!
ምን ቸገረሽ ለትንሽ ጊዜ ብትታገሺ? ፍቅር የያዘው ሰው ፍቅሩን ለሌላ አሳልፎ መስጠት ስለማይፈልግ ሌላ አፈቀርኩ ብለሽ ብትነግሪው ጥሩ አይመጣም፡፡ ያፈቀረ ብዙ ነገር ከማድረግም ወደኋላ አይልም፡፡ አቅሙን እንደሆነ የምታውቂው ነው፡፡ ጉዳት እስካላስከተለብሽ ድረስ ማሚ ድነው እስከሚወጡ እየሸወድሽው ብትቆዪ ምናለበት? በዚህ ላይ ታዋቂ ሀኪም ነው” ስትል አማከረቻት።
እሱን በአሁኑ ሰዓት ማጣት ጉዳት እንጂ ጥቅም ስለሌለው ከሻምበል ብሩክ ጋር ጋብቻቸውን እስከሚፈጽሙ ድረስ ግንኙነታቸው እንደነበረ እንዲቀጥል ተስማሙ።
በተቻላት መጠን ግን ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ያላትን ግንኙነት ለማርገብ ጥረት እንድታደርግ፤ ቀስ በቀስ የግንኙነት ገመዱን ለማላላት እየቀጠሩ መጥፋት፤ ሲገናኙ መለማመጥና ምክንያት እየሰጡ
በአጭር ጊዜ ውስጥ ላለመገናኘት ከፍተኛ ጥረት ማድረግ በዚህ
ውስጥ እንዲጠቃለሉ በስፋት ተማከሩበት። በዚሁ መሠረት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ለረጅም ጊዜ ሳይገናኙ
ቀሩ። ለረጅም ጊዜ ያለመገናኘታቸው ደግሞ እንደግምታቸው ተስፋ የመቁረጥና የመረሳሳትን አዝማሚያ ከማሳየት ይልቅ ' ዶክተር በናፍቆት
ተጠብሶና፤ በፍቅር ተቃጥሎ፤ እንዲጠብቃት አደረገው፡፡ሻምበል ብሩክ አስፈላጊውን ክፍያ ሁሉ ፈጽሞ እናቷን
ሆስፒታል ባስገባችበት ዕለት ተገናኙ። እናቷ በገንዘብ እጥረት ምክንያት
ከሆስፒታል እንድትወጣ ሲደረግ! ስለገንዘብ ከሆነ አለሁልሽ ብሏት
ነበር፡፡ በክፍያ ችግር ምክንያት መሆኑን ልትገልጽለትና በሽንፈት እጇን
ስላልፈለገች... “ለገንዘቡ አይደለም ዶክተር፤ እናቴ ከሆስፒታል ወጥታ በቤት ውስጥ ለመታከም ስለፈለገች ነው
” በማለት ነበር መልስ የሰጠችው::
አሁን እናቷን ሆስፒታል መልሳ ማስተኛቷን ሲያውቅ ቶሎ ቶሎ ለመገናኘት እድል ይፈጥርለታልና በጣም ተደሰተ፡፡ እሷ ግን ይህንን አልወደደችውም።ሻምበል ብሩክ ግንኙነታቸውን እንዳይደርስበት ሰጋች።
ሆኖም እሱን ከማንኛውም ጥርጣሬ ነፃ የምታደርግበት የራሷ ማረጋገጫ
አላትና፧ ተጽናናች። ሁሌም ለእሷ ንፁህ የመሆን ማህተሙ አብሯት እስካለ ድረስ ዶክተር ባይከዳኝ የእናቷ ሀኪም ከመሆኑ ባሻገር ሌላ ጉዳይ ይኖራቸዋል ብሎ እንደማይገምት ተማምና፤ ከዶክተር ጋር ያላትን ቀዝቃዛ ግንኙነት ቀጠለች።
ይህ ሁኔታ በዚሁ ቀጥሎ ሳለ፤ አንድ ቀን ሻምበል ብሩክ በፖሊስ መምሪያ የተካሄደውን ስብሰባ ተካፍሎ፤ ምሳውን ከበላ በኋላ፤ ወደ ቢሮው ለመመለስ የያዛትን የመንግስት መኪና በሚያሽከረክርበት ወቅት አዲስ ነገር ተፈጠረ።
ከቀኑ አሥር ሰዓት ተኩል ሆኗል።
ብሔራዊ ቲያትር አካባቢ ነው። የትራፊክ መብራት ይዞትእንደቆመ፤ በስተቀኝ በኩል ከፊት ለፊቱ ቀደም ብላ የቆመችውን ነጭ
ኦፔል መኪና እንደዋዛ በዐይኖቹ ገረፍ አደረጋት።
በዚያች መኪና ውስጥ እንደዋዛ ያየው ነገር የትኩረት ስሜቱን ሳበውና፤ መኪናውን ቀስ ብሎ ትንሽ ወደፊት በማንቀሳቀስ ተጠጋ፡፡ፍጹም ሊሆን የማይችል ነገር ነው። አእምሮው ሊጠረጥረው የማይችለውን
ነገር በማየቱ፤ አይኖቹን ተጠራጠረ። የሚያየውን እውነታ ህሊናው በቀላሉ ሊቀበልለት ስላልቻለ፤ ቀይ መብራት በርቶ
መኪኖች ሲለቀቀቁ እንኳ አልታወቀውም ነበር። የሚያየው ነገር እውነት መሆኑን፤ አይኖቹ የሚያሳዩት የሌለ ነገር ሳይሆን፤ ያለውን ሀቅ መሆኑን፤ ሲረዳ ግን፤ ጭንቅላቱ በከባድ ነገር እንደተመታ ሁሉ፤ ክው ብሎ ደርቆ ቀረ።
በሚያየው ነገር ምክንያት ሰውነቱን ማተኮስ ስለጀመረው! የመኪናውን የበር መስታወት ወደታች ዝቅ አድርጎ ንፋስ አስገባ፡፡ በዚያች መኪና ውስጥ ያለቸው ትህትና ድንበሩ መሆኗን
ሲያረጋግጥ፤
መኪናውን የሚያሽከረክረውን ሰው ማንነት ለመለየት ፈለገና አተኩሮ
ተመለከተው፡፡ ያውቀዋል። ዶክተር ባይከዳኝ ነው።ጉድ ፈላ! ስራውን ትቶ የዚህን ተአምር ማብቂያ ሊከታተል
ወሰነ። መብራቱ አረንጓዴ በርቶ ሲለቀቁ ነጫን ኦፔል መኪና ተከትሎ ያሽከረክር ጀመር ክትትሉ እንዳይታወቅበት
🔥2👍1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሀያ_ስድስት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

#አውጉስታ

ቅዱስ ገብርኤል የሚከበርበት የዓመቱ በአል ደረሰ፡፡ ይህንን በዓል የእንደሻው ወላጆች የሚያከብሩት ሐረርጌ ቁልቢ ገብርኤል በመሄድ ነው። ለዓመቱ ገብርኤል የተሳሉትን ስለት ይዘው፣ ትንሹ ልጃቸው ሲሳይን አስከትለው፤ ለመሄድ የባቡር ትኬት ቀደም ብሎ ተቆርጧል።
ገብርኤል የሚከበርበት ቀን እንደ ነገ ሆኖ፤ ትህትና ሥራዋን በምታከናውንበት ወቅት ደግሞ አንድ ደስ የሚል ዜና ሰማች፡፡ ትናንትና ሻምበል ብሩክን በስልክ ስታነጋግረው የድሮው ሻምበል ብሩክ ሳይሆን ትንሽ የመቀዝቀዝና፤ የመለወጥ ስሜት ስላየችበት ብስጭትጭት ብላ
ነበር የዋለችው። ይህንን ብስጭቷን ሲያካክስላት ነው መሰል የደስደስ
ያለው ወሬ ከአበራ ሰማች፡፡
የምስራች!” አላት አበራ እየፈነደቀ።
“ምስር ብላ” አለችው የምሥራቹ ናፍቋት፡፡
“ጋሼን ምን እንዳስነካሻቸው አላውቅም፡፡ለማንም ያላደረጉትን ነው ላንቺ እያደረጉ ያሉት፡፡የገቡልሽን ቃላቸውን ጠብቀዋል፡፡ ከነገ ጀምሮ ደመወዝሽ አንድ መቶ ብር ሆኖ በገንዘብ ያዥነት እንድትሰሪ ተወስኗል”
በደስታ ብዛት ሄዳ አበራን እቅፍ አደረገችው። እሱም እቅፍ አደረጋት።

“ዛሬ እቤት ይዘሀት ትምጣና አዲስ ውል ትፈርም ብለውኝ ነበር። ዛሬ ሥራ ስለሚበዛ ለነገ ይሻላል ብያቸዋለሁ” አላት ድምጹን ዝቅ አድርጎ፡፡
ትህትና በእርግጥም በሥራዋ ቀልጣፋና ደከመኝን የማታውቅ ልጅ መሆኗን ማንም ይመሰክርላታል።
“ለማንም እንዳትናገሪ ታዲያ! በተለይ ይህቺ አሮጊት ከሰማች ታብዳለች” :: ይህቺ አሮጊት የሚለው ወ/ሮ አረጋሽን ነው። በእርግጥም ወይዘሮ አረጋሽ በዚህ የጫማ መሸጫ አዳራሽ ውስጥ ዘጠኝ ዓመት ሙሉ ሰርታ ደመወዟ አሁንም ዘጠና ብር ብቻ ነበር፡፡
“ጋሼ አበራ ሙት ለማንም አልናገርም” ቃል ገባችለት፡፡ በዚሁ መሠረት ተደስታ ውላ፤ ተደስታ አደረች፡፡ ትንሽ ቅር ያላት ሻምበል ብሩክ በስልክ ስታነጋግረው ከወትሮው የቀዘቀዘበት ምክንያት ግራ
ስላጋባት ነበር።ምክንያቱን ለማወቅ
ሄዳ እስከምታገኘውና የሳምንቱ
"መጨረሻ እስከሚደርስ ድረስ ከመቸኮሏ በስተቀር ሁሉም ነገር ሰላም ነው፡፡ እናቷ በጥሩ ሁኔታ ላይ ነው ያለችው። አንዱዓለም ጠንካራ ተማሪ ሆኗል። ይኸውና እሷ ደግሞ ዛሬ ዕድገት የማግኘቷን ዜና ሰማች፡፡ ይህንን የዕድገት ውሏን ለመፈረም አቶ በቀለ ከመኖሪያ
ቤታቸው ድረስ እንድትመጣ በሥራ አስኪያጁ በአበራ በኩል የላኩባትን
መልዕክት ተቀብላ ለመሄድ ተዘጋጀች፡፡
በማግሥቱ ሥራ እንደገቡ አበራ ወደ
ወ/ሮ አረጋሽ ጠጋ ብሎ ከትህትና ጋር አንድ ግዜ ወደ ፋብሪካ ደርሰን እንመጣለን” አለና ምክንያቱን አሳውቆ ትህትናን ጠራትና መኪና ውስጥ አስገባት፡፡ ሞቅ ባለ ፍጥነት ከአውጉስታ ፋብሪካ በስተጀርባ ወደሚገኘው ወደ አቶ በቀላ መኖርያ ቤት በረሩ።
ከዚያ ደርሰው የመኪና ጥሩንባ ሲያሰሙ፤ አንዲት ጠቆር ያለች ልጅ እግር የቤት ሠራተኛ የአጥሩን ብረት በር ወለል አድርጋ ከፈተችው፡፡
ቤቱ በዚያ ሰፊ ቦታ ላይ በግርማ ሞገስ ጉብ ብሎ ሲታይ ይማርካል። በልዩ ልዩ አበቦችና ዛፎች አጊጧል። ከትልቁ ቪላ ፊት ለፊት በሰፊው ተንጣሎ የሚታየው የወይን ዛፍ ቀዝቃዛ ጥላን አጐናጽፎት
ምድረ ገነት አስመስሎታል።
በግቢው ውስጥ የማይታይ የአበባ ዓይነት የለም፡፡ ትህትና በአጠቃላይ የቤቱ ውበት ተማርካለች፡፡ ከዚያም ተያይዘው ከመኪናው ወረዱ።
የወጣ ሰው የለም፡፡ አበራ “ቆይ ጠብቂኝ” አለና በጓሮ በኩል ዞረ።እሷ በፊት ለፊቱ በር ቆማ እየጠበቀችው ነበር፡፡
የቤት ሠራተኛዋ አንድ ጊዜ ብቅ ብላ ትህትናን ሰረቅ አድርጋ አየቻትና ተመልሳ ገባች።
“ነይ ትህትና በዚህ በኩል”፡፡ በፊት ለፊቱ ሳይሆን በጓሮው በር አስገባት፡፡
እዚያ ፈቅ ብሎ በተሠራ የውሻ ቤት ውስጥ የታሰረው ትንሽ የፈረንጅ ውሻ ቡፍ ቡፍ አለ። ትህትና ውሻውን ስታየው ግንባሩ ፍጥጥ ብሎ ወደ ውጭ የወጣ ከመሆኑም በላይ ፤ የሆነ የምታውቀው ሰው መልክ አስታወሳትና፤ ትንሽ ሳቅ ብላ አበራን ተከተለችው::

ቁጭ በይ ወንበር ጋበዛት፡፡ ሄዳ ወንበሩ ላይ ተቀመጠች።
“እስከዚያው ምን ይምጣልሽ?” ፊቱ ጥርስ በጥርስ እንደሆነ።
“ጋሽአበራ ምንም አያስፈልግኝም” እሷም በፈገግታ እንደተዋጠች፡፡
ዕድገትን ለመሰለ ፀጋ መጥቶ ባይበላ፤ ባይጠጣስ? ልቧ ያለው በውሉ ሁኔታ ላይ ነበር። በዚህ ላይ የቤቱ ውበት አስደንቋት ዙሪያ ገባውን እየቃኘች ነበር፡፡
“እንደሱ አይባልም፡፡ ምንም ቢሆን እኮ ለቤቱ እንግዳ ነሽ፡፡
እንዳይለምድብሽ፡፡ ለስላሳ ይምጣልሽ?”
“ይሁን እሺ ጋሽ አበራ፡፡”
ትህትና እዛ ክፍል ውስጥ ሆና በዚያች የምታምር ክፍል ውስጥ የተሰቀለውንም፤ የተንጠለጠለውንም፤ በዐይኖቿ እየቃኘች አቶ በቀላ ብቅ ብለው ውሉን እስከሚያስፈርሟት ድረስ በናፍቆት ስትጠባበቅ፤ በግራ በኩል ውስጥ ለውስጥ የተሠራው ባለመስታወት በር ንቅናቄ አሳየ።
እስከዚያን ጊዜ ድረስ አንዳችም ጥርጣሬ ያልተሰማት ልጅ ልቧ እንደመዝለል አለባትና ዐይኖቿ በበሩ ላይ ተተክለው እንደቀሩ፤ ፒጃማ የለበሰ ወጣት ብቅ!!..... አለ፡፡
ያንን ሰው ስትመለከት፤ እጅግ ከመደንገጧ የተነሳ አፏ ተከፍቶ ቀረ። ከዚያም ነፍሷን ስትገዛ “ዋይ!” ብላ እሪታዋን ልታቀልጠው ስትል፡-
“ፀጥ በይ!! ያለበለዚያ!!” አለና ደብቆ የያዘውን እህል ውሃ የማያሰኝ ጩቤ መዘዘው። ዐይኖቿ ተጎልጉለው ወጡ
በድንጋጤ ደምስሮቿ በግንባሯ ላይ ተገታተሩ፡፡ ትንፋሽ ሳታወጣ ፀጥ አለች፡፡
ከዚያም ሁኔታዎች በእንደሻው ፍላጐት መስመር ያለችግር ይቀላጠፉ ጀመር።
ጠጋ አላትና በግራ በኩል በቃሪያ ጥፊ ቢያላጋት ዐይኖቿ በእጥፉ ተጎልጉለው ከመውጣታቸውና ፊቷ ሳምባ ከመምሰሉ በስተቀር ቃል አልተነፈሰችም።የሚያርዳት ነው የመሰላት፡፡
“የምትታዘዥውን የማታደርጊ ከሆነ ይሄ!” አለና በጡቶቿ ሥር ጩቤውን አሳርፎ “ወደ ውስጥ እንዲዘልቅልሽ ይደረጋል!” አላት በጭካኔ ስሜት።
“ተነሽ!!” አለና አንቧረቀባት።
ሹክክ ብላ ተነሳች። ከኋላ በኩል ዞሮ ያንን ዞማ ፀጉሯን ጨመደደና፤ የገባበትን በር በእርግጫ በረገደው፡፡ ከዚያም ወደ ውስጥ ሲገፈትራት፤ ተንገዳግዳ የገባችበት ክፍል ጨለማ ዋጣት...
እዚያ ጨለማ ውስጥ ሆና የገባችበትን ሲኦል ለማየት ዐይኖቿን ስትገልጥ፧ ሄዶ ማብሪያና ማጥፊያውን ቢጫነው፤ እዚያ ክፍል ውስጥ ከዳር እስከዳር የተንጣለለ ሞዝቮልድ አልጋ ተነጥፎ አየች። ይህንን
የምታተኩርበት ስሜትም፤ ጊዜም፤ አልነበራትም፡፡ ማንስ ጊዜ ሰጥቷት?
እንደዚያ ሲለምናት፤ ሲያስለምናት ከርሞ፤ እንቢ ስለአለችው፤ በቀየሰው ዘዴ የገባችለትን ወጣት ሊሰቀላት ቆርጦ ተነስቷል።
“አውልቂ!! አለና ጮኸባት፡፡
ጩቤውን እንደያዘው ነው፡፡ እየተንፈቀፈቀች ዝም ብላ ቆማ
ዐይን ፤ ዐይኑን፤ ታየው ጀመር፡፡ እንባዋን አይቶ የሚያዝንላት መሰላት፡፡
እንባዋ እንደጎርፍ ፈሰሰ፡፡ አቤት በዚያን ሰዓት የተሰማት ስሜት!? ሻምበል ብሩክ መጣባት፡፡
“እውነት ልታደርጊው ትሁትዬ?” የሚላት መሰላት፡፡
“ተይ! ተይ! ትሁት!” በአካል የቀረባት መሰላት። ስቅስቅ ብላ አለቀሰች
“አውልቂ!” አለና እንደገና አንቧረቀባት። በዚህ ጊዜ በእልህና ተውጣ፤ : እንደቆሰለ
አውሬ እየጓጎረች፤ ልታንቀው በሲቃ
ተንደረደረችበት፡፡
እንደሻው አመጣጧን አይቶ ካፈገፈገ በኋላ እዚያ ከመንጋጋዋ በታች የሆነ ደም ስሯ ላይ ክፉኛ ቢመታት፤ ሄዳ በአፍ ጢሟ ተደፋች፡፡
ከዚያም ያንን ሲቋምጥለት የነበረው ገላዋን እርቃኑን ለማየት ተጣድፎ
ልብሶቿን በፍጥነት አወላለቃቸው፡፡ እራሷን ስታ ነበር፡፡ ሙሉ በሙሉ
ልብሷን ካወለቀ በኋላ ወስዶ አልጋው ላይ ዘረራት.... ከዚያም ያንን
👍3
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሀያ_ሰባት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

....መንፈሷ ላይድን ቆስሎ፧ ሃሣቧ እዚህም እዚያም እየባከነ፤በተኛችበት ሆና በእንባ እየታጠበች ሁለት ቀን በጓደኛዋ ቤት ካሳለፈች በኋላ፤ ተነሣች፡፡
አካሏ ጠንካራ ቢመስልም፤ መንፈሷ ግን ደካማና የተረበሽ ነበር።በዚህች በሁለት ቀን ውስጥ ከዚህ ዓለም የተገለለች ዓይነት ሰሜት ይስማታል፡፡
የእናቷ፡ የወንድሟና፤ የሻምበል ብሩክ ሁኔታ ከፊቷ ድቅን ይልባታል፡፡
እናቷን ለሁለት ቀን ሳታያት በመቅረቷ ሁለት ዓመት የተለያቻት ያህል በናፍቆት ተቃጥላለች፡፡
“እንዴት ሆና ይሆን?” እያለች ሌሊቱን ስትጨነቅ ነው ያደረችው፡፡እናቷን በህልሟ አይታታለች፡፡ በዚያው ጐን ለጐን የሻምበል ብሩክ ጉዳይ አለ፡፡ ዛሬ እሁድ ስለሆነ ሻምበል ብሩክ እየጠበቃት ነው፡፡ ስለዚህ እሱን ማግኘት አለባት፡፡ ካላየችው ጤነኛ የምትሆን አልመሰላትም፡፡ልቧ ከውስጥ ደም ቢያለቅስም፤ ጥርሶቿ ግን እውነተኛ ስሜቷን በመደበቃቸው፤አዜብ ተጽናናች፡፡
“በቃ እንሂድ”አለቻት ለአዜብ ልብሷን ለባብሳ እንደጨረሰች፡፡
እሺ ትሁት፡፡ መጣሁ ጠብቂኝ” አለችና ሄዳ የታክሲ ገንዘብ ይዛ መጣች፡፡ ከቤት ሲወጡ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ተኩል ሆኖ ነበር፡፡ ዕለቱ እሁድ ነው :: ተያይዘው በታክሲ ወደ የካቲት አስራ ሁለት ሆስፒታል በረሩ...
በዚህ ቀን ሻምበል ብሩክ ከአሁን አሁን ትመጣለች በማለት በጉጉት እየተጠባበቃት ነበር፡፡ ትዕግስት መራራ ነች ፍሬዋ ግን ጣፋጭ ነው የሚለውን ብሂል በሃሣቡ እያውጠነጠነ ፣ትዕግስት አልባ በመሆን ስህተት እንዳይፈጽም ከራሱ ጋር እየተሟገተ ይገኛል፡፡
ከዚህ በፊት ከትዕግስት ውጭ በመሆን ከሱ የማይጠበቅ ድርጊት በመፈጸሙ ተፀፅቶ፤ ለራሱ የገባውን ቃል ዘነጋና፤ ባለፈው ስልክ የደወለችለት ዕለት፤ በድጋሚ ስህተት ፈጸመ፡፡በዚያን ሰዓት ትህትና በሁኔታው ተደናግጣ...
ምን ሆነሃል ብሩኬ?“ ነበር ያለችው፡፡ በአነጋገሩ የድሮው ሻምበል ብሩክ መሆኑ ፍጹም አጠራጥሯት፡፡
ሻምበል ብሩክ እንደበረዶ ቀዝቅዞ ነበር ያነጋገራት :: ይህንን ስህተት መፈጸሙን ያወቀው ግን ስልኩን ከዘጋ በኋላ ነው፡፡
ስልኩን አንስቶ ሲያነጋግራትና፤ሲሰናበታት በነበረው ሁኔታ ተደናግጣ ተደናግጣ “ምን ሆነብኝ?“ በማለት ተጨንቃ፤ ምን እንዳጋጠመው ለማወቅ ፤ እሁድ
አልደርስልሽ አላት፡፡ ሻምበል ብሩክም ስልኩን ከዘጋ በኋላ ምን ያደርግ እንደነበር ሲረዳ ተደናገጠና፤ የሚይዝ የሚጨብጠው ጠፋው፡፡
“ ምን ዐይነት እራሴን መቆጣጠር የማልችል ደደብ ነኝ?” ሲል በራሱ አማረረ
"እሺ አሁን ምን ይሻላል?“ በሚል ጭንቀት ተውጦ ለፈፀመው ስህተት ምክንያት ሲፈልግ አንድ ሃሣብ መጣለት፡፡
ሻምበል ስሜቱ በሁለት ተቃራኒዎች መካከል መዋዠቅ ጀምሯል፡፡ወደር የሌለው ፍቅር በአንድ በኩል፤ የጥላቻ ስሜት በሌላ በኩልእንደከበሮ ወጥረው ይሞግቱታል፡፡
በቃላት ሊገልጸው በማይችለው ሁኔታ ያፈቅራታል፡፡ የዚያን ዕለቱ ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር እጅ ለእጅ ተቆላልፋ ወደ ቤቱ ይዟት ሲገባ የነበረው ሁኔታዋ
ከፊቱ ላይ ድቅን ሲልበት ደግሞ፤ ከአንጀቱ ይጠላታል፡፡
ለማንኛውም ይህ ፍቅሩ ጥላቻውን የሚያጠፋበት፣አሊያም ጥላቻው
ፍቅሩን ከውስጡ ጠራርጉ የሚያስወግድበት፤ እውነተኛው ሰዓት
እስከሚደርስ ድረስ በትዕግስት ለመቆየትና የዚያ የውሽት ልጃገረድነት
ጭምብል ወልቆ እውነተኛው ማንነቷ የሚረጋገጥበትን ጊዜ በጉጉት
መጠባበቁን መረጠ፡፡
በሱ እምነትና ግምት ያ ቀን እሁድ እለት እንዲሆን ወስኗል፡፡ሻምበል እሁድ ዕለት ደርሶለት ይሄ ጥርጣሬና ጥላቻው አንድም የሚወገድበት፤አሊያም ከትህትና ጋር የሚቆራረጥበት ዕለት በመሆኑ የአሁኑ እሁድ ከምንግዜውም የበለጠ ናፈቀው፡፡
ትህትና ደግሞ በበኩሏ ሻምበል ብሩክ እንደዚያ ቅዝቅዝ ብሎና ተለውጦ በስልክ ሲያነጋግራት ተረብሻ፣የመገናኛቸው ዕለት ደርሶላት ሄዳ ምን እንደሆነ እስከምትጠይቀው ድረስ ቸኩላ፤ እሁድን እየተጠባበቀች ነበር፡፡
ሁለት ልቦች በየግል ምክንያቶቻቸውን አምቀው፤ ሰዓቱን በመጠባበቅ ላይ ቢሆኑም፤ ሰዎች በፈለጉት መንገድ ሳይሆን፤ ጊዜ በራሱ ህግና ስርዓት የሚመራ ነውና፤ እሁድ የራሱን አዲስ ክስተት ይዞ ብቅ አለ፡፡
ሰው በጊዜ ቢያቅድም ጊዜ የሰው ተጐታች አይደለምና የታቀደ ሁሉ
አይሳካም :: በተገላቢጦሽ ደግሞ ሰው የጊዜ ተጉታች ነውና፤ አንዳንድ የሰዎች ዕቅድ ጊዜው ካልፈቀደ በዕቅድነቱ ይቀርና ጊዜ የራሱን አዲስ ክስተት ይዞ ይመጣል፡፡
ትህትና ድንበሩ በአበራና በአለሌው እንደሻው አማካይነት በተቀነባበረ ሴራ፤ በአካሏ ላይ ጉዳት ስለደረሰባትና ፤በቀሪ ህይወቷ ላይ ጥቁር ነጥብ የሚጥል ወንጀል ስለተለፈፀመባት፤ በናፍቆት የተጠባበቀችው እሁድ ቢመጣም ያ ቀን ከደረሰባት ዱላና አስገዳጅ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ጉዳት ያገገመችበት ቀን ሆኖ ዋለ፡፡
እንደዚያ የምታፈቅረው ጓደኛዋ ናፍቋት፤ እናቷን ለሁለት ቀናት ያህል ስትለያት የምታደርገው ጠፍቷት፤ በእንባ እየታጠበች በዚያች በሁለት ቀን ውስጥ ወዟ ምጥጥ ብሎ፤ አካሏ ጠውልጉና ውበቷ ተገፍፎ ስትታይ፤ ትህትና ነች ብሎ ለመናገር አስቸጋሪ ነበር፡፡ውበት የስሜት
ነጸብራቅ የመሆኑ እውነታ ከፊቷ ይነበብ ነበር፡፡
ለዚያውም አዜብ ከአጠገቧ ሳትለይ በማንኛውም ረገድ ባታፅናናትና
ባትንከባከባት ኖሮ፤ ጉዳቷ ከዚህም የከፋ ይሆን ነበር፡፡ከዚህ ሁሉ በኋላ በሁለተኛው ቀን ላይ ሰውነቷን ተጣጥባ፤ በቅባት ፊቷን አባብሳ፤ የአዜብን ምርጥ ቀሚስ ለብሳ ፤ ሰው መስላ ተነሣች፡፡
ሞራሏ እንዳይነካና ያለፈውን እንድትረሣ አዜብ ያላደረገችላት ጥረት አልነበረም፡፡ ትህትናም ጓደኛዋን ለማስደሰት ያህል ብቻ ልቧ ከውስጥ ደም እያለቀስ፤ ከላይ ከላይ ፈገግታ እያሳየቻት ተነሳች፡፡
በተለይም በዚያን ዕለት ጨረቃዋ በመኝታ ክፍላቸው ውስጥ ብርሃኗን ስትፈነጥቅ፤ ከሻምበል ብሩክ ጋር ባሳለፈችው አስደሳች ምሽት የተናገረችው ትዝ ይላትና እረፍት ይነሳታል፡፡ ያንን የሚያሰቃይ ስሜቷን ውጣ በፍጹም ጤነኛና ደሰተኛ መስላ ልብሷን ለባብሳ እንደጨረሰች...
"እንሂድ አዜቢና” አለቻት፡፡
እናቷ ይህችን ሁለት ቀን ልጇ ሳትመጣ በመቅረቷ እዚያ ሆስፒታል ውስጥ በእንባ እየታጠበች አንዱአለምን ካልወለድካት እያለች ስታስጨንቀው፤ በሁለተኛው ቀን ላይ የት እንዳለች ቁርጡን ነገራት፡፡
አንዱዓለም እህቱ የት እንዳለች የሰማው ከአዜብ ነው፡፡
• ትሁት ሻምበል ጋ ነች፡፡ ሁለት ቀን እዚያ ስለምትቆይ አንተ ከእናትህ እንዳትለይ አደራህን” ብላ በሚስጥር ስለነገረችው፤ አንዱአለም ዜናውን በደስታ ተቀብሎ ለደቂቃ ከእናቱ እንደማይለይ በገባላት ቃል መሠረት ከዚያ አካባቢ ውልፍት ሳይል ነው የቆየው፡፡
ትህትና በዚህች በሁለት ቀን ውስጥ ሁለት ዓመት እንደተለያቻች ሁሉ ናፍቃት፤ ሆስፒታል ስትደርስ እየሮጠች ሄዳ እናቷ ላይ ድፍት ብላ አለቀሰች፡፡ አዜብ የጓደኛዋን ሁኔታ ስትመለከት አንጀቷ ተላወሰ፡፡አልቻለችም፡፡ አብራት አለቀሰች፡፡
እናቷም ልጇ ላይ ጥምጥም ብላ በስስት እያገላበጠች ሣመቻትና..
በጤናሽ ነው ትሁቴ? አለሽልኝ የኔ እናት? ” ዐይን ዐይኖቿን በጉጉት እያየች፡፡
“ደህና ነኝ እማይዬ አንቺስ እንዴት ነሽ?” እናቷን እያሻሸች በዐይኗ አንዱአለምን ስትፈልግ እሱም የሆነ ነገር ሊነግራት ፈልጐ ምልክት ሲሰጣት አየችና ልትስመው ሄደች.....
“ሻምበል ጋ እንደነበርሽ ነግሬአታለሁ” አላት ድምፁን ዝቅ አድርጉ፡፡
ትንሽ ሣቅ ብላ......
“እሺ" አለችው::
ከዚያም በኋላ ከእናቷ አጠገብ የተኙትን በሽተኛ አዛውንት ጤንነታቸውን ጠይቀው፣ እናቷን ከበው ተቀመጡ፡፡ እናቷ የልጇን
ዐይን፤ዐይን፤በስስት ስትመለከት ሆዷ ቡጭ ቡጭ
👍1
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሀያ_ስምንት


#ድርሰት_በትክክል_ገና

.....ሻምበል ብሩክ ይመስላታል፡፡
የሆነ ደስ የሚል መናፈሻ ውስጥ እጅ ለእጅ ተያይዘው፣ ሲንሸራሸሩ ከቆዩ በኋላ፤ ወደ ኣንድ ጥላው ቀዝቀዝ ያለ፣ ንፁህ አየር ወደሚነፍስበት የወይን ዛፍ ሥር
ይመጡና ከሥሩ ካለው ለምለም ሣር ላይ ጋደም ይላሉ::

በዚህ ጊዜ እሷ እሱን ትራስ አድርጋ፣ ፀጥ ያለውን ኣካባቢ እየቃኙ የተፈጥሮ ውበትን ሲያደንቁ፤ የሁለቱም ዐይኖች ከፊት
ለፊታቸው በሚያዩዋት የጽጌዳ ቅርንጫፍ ላይ ባለችው እንቡጥ ጽጌረዳ አበባ ተማርኮ፤ ጽጌረዳዋን ሲመለከቱ ከቆዩ በኋላ፤ ስለዚያች ጽጌረዳ ለመናገር በአንድ ጊዜ “ እንዴ ” ብለው ይጀምራሉ፡፡

"ምን ልትል ነበር?” ትለዋለች እየሣቀች::
“አንቺስ ምን ልትይ ነበር?” ይላታል እሱም እየሳቀ::

“እንዴት ታምራለች ልል ነበር” ስትለው..
“እኔም እንደሱ ልል ነበር:: ከማማሯም በላይ ደግሞ ልክ የሁለታችንን ፍቅር ትመስላለች ልልሽ ነበር” ይልና ቁልቁል ወርዶ ከንፈሯን ይስማታል፡፡

“ማማሯስ እሺ የሁለታችንን ፍቅር እንዴት ነው የምትመስለው?” ትለዋለች:: ስለፍቅራቸው የበለጠ እንዲያወራላት
ጓጉታ::

“ያልፈነዳ እንቡጥ ጽጌረዳ በአበባነት ደረጃ ላይ ካለው ፍቅራችን ጋር ይመሳሰላል” ይላታል፡፡

“አበባው ፍሬ የሚሆነው መቼ ነው ብሩኬ?” አይን፤ ዐይኑን ሽቅብ እያየች ትጠይቀዋለች::
ወፎች የሚዘምሩ ይመስላታል፡፡ ንፋሱ ሽውው ይላል፡፡ዛፎች ይደንሣሉ፡፡ሰማዩ የጠራ ነው፡፡ሌላ ዓለም፡: ልዩ ዓለም.....
“የሠርጋችን ዕለት በዚያ በጫጉላ ቤት ውስጥ አሀዱ ብለን ትዳርን ስንቀድሰው፡፡ አይመስልሽም ትሁቲና? ቆይ እንዲያውም ይህችን ጽጌረዳ ስለፍቅራችን ገፀበረከት ላቅርብልሽ” ይልና ብድግ ብሎ ያቺን የምታምር እንቡጥ ጽጌረዳ አበባ ቀጥፎ ያመጣና
ይሰጣታል::

“በሠርጋችን ዕለት? .... በጫጉላ ቤት? .... አሀዱ ብለን?... ስንቀድሰው?
ምን ዐይነት ጣጣ ነው? የሆነውን ሁሉ
ብነግረውስ? የጫጉላ ቤቱ ዕቅዳችን መፍረሱን፣ እንደሻው አስገድዶ ክብረ ንፅህናዬን መድፈሩን፤ ብገልጽለትስ?
አያምነኝ ይሆን?
በቃሽኝ አታላይ ነሽ ይለኝ ይሆን? ልንገረው? እያለቀስኩ ልግለጽለት
ወይንስ ልተወው? ወይኔ አምላኬ ምን ጣጣ ውስጥ ከተትከኝ? ወይኔ
ብሩኬ በዚህ ምክንያት እንለያይ ይሆን?...” በስጋት ተዋጠች፡፡
ይህንን ፍርሃቷን በልቧ አምቃ በጭንቀት እንደተዋጠች፤
ሻምበል ብሩክ ቀጥፎ የሰጣትን ጽጌረዳ እንባ በጋረዳቸው ዐይኖቿ ትኩር ብላ መመልከቷን ቀጠለች::
ያቺ የምታምር ጽጌረዳ፣ ያንን የመሰለ ማራኪ ውበት የተላበሰች ለምለም እንቡጥ አባባ፣ ቀስ በቀስ እየጠወለገች፣
እየጠወለገች፣እየደረቀች ሄደችና፣ በእጇ ላይ እንዳለች እርር ብላ ተንኮሻኩሻ ደቀቀች::
በዚህ ጊዜ ትህትና በድንጋጤ ተወራጭታ ከገባችበት አስደንጋጭ የህልም ዓለም ስትወጣ፤ ሰውነቷ ሁሉ በላብ ተዘፍቆ
መንቀጥቀጥ ጀመረች::
ቀስ ብላ ያየችውን ህልም ስትመረምር ፍርሃት ነገሰባትና፤ ሆድ ብሷት “በቃ ልክ ነው:: ህልሜ ትክክል ነው:: ብሩኬን አጣሁት ማለት ነው፡፡ ወይኔ ወይኔ” እያለች ስቅስቅ ብላ ዐይኖቿ
እስከሚያብጡ ድረስ አለቀሰች፡፡
ሻምበል ብሩክ ልጃገረድ ያለመህኗን ሲያውቅ፤ ውሸታም ባለጌ አድርጐ እንደሚገምታት፤ በቃሽኝ እንደሚላት፤ ጠርጥራ ልቧ በሀዘን ተሰበረ::
በዚህ መጥፎ ስሜት ውስጥ ገብታ በሃሣብ ስትዋዥቅ ከቆየች በኋላ፤ ሻምበል ብሩክን የራሷ አድርጋ ለማስቀረት የሚያስችላትን ዘዴ ማውጠንጠን ጀመረች፡፡ በመጨረሻም የሆነ ሃሣብ መጣላት::
“ማን ያውቃል? ዛሬም እንደበፊቱ ሁሉ ልጃገረድ የመሆኔ ምልክቱ ሙሉ ለሙሉ ላይጠፋ ይችላልና የማያስታውቅ ከሆነ ለምን አንድ ሙከራ አላደርግም?” ስትል አሰበች። በመጨረሻም ከሻምበል
ብሩክ ጋር ከመገናኘቷ በፊት ራሷን በዶክተር ልትፈትሽ ወሰነች::
አንዴ ላይታፈስ የፈሰሰ ውሃ፤ በድጋሚ የሚገኝ መስሏት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ቀጠሮ ያዘች::
ከመቸኮሏ የተነሳ አርብ ዕለት ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር በያዘችው ቀጠሮ መሠረት
ወደ ቤት እንደደረሱ ተያይዘው ወደ ቤት እንደደረሱ ሠራተኛዋን አገላብጣ ሣመቻት::
ምነው ፍቅርሽ በዛ?” አለቻት ሠራተኛዋ በልቧ፡፡ ትህትና ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ካሳለፈችው ጊዜ ሁሉ ለየት ያለው የዛሬው ነው:: ለዛሬው ግንኙነታቸው የራሷ ምክንያት ስለአላት፤ የሚሆነውን ቶሎ ለማወቅ፤ ቶሎ ወደ አልጋ ለመሄድ
ቸኮለች፡፡
ቢሆንም ግን ይህንን መቸኮሏን
ዶክተር እንዲያውቅባት አላደረገችም::
እንደተለመደው ሁሉ ዶክተር እራሱን ሊፈትሽ፤ እሷም የልጃገረድነት ሚስጥሯን ልትፈትሽ፤ ተፈላልገውና፤ ተግባብተው፤
ተያይዘው፤ ወደ መኝታ ክፍል ገቡ::
ዶክተር በዚያ ረገድ በራሱ ላይ እምነት እያጣ ስለሄደ በውስጡ የነበረው ጉጉት ቀዝቅዟል፡፡ ሆኖም እንደተለመደው የማይጠገብ ውብ የልጅነት ገላዋ የሚያመነጨውን ሙቀት ለመቋደስ ያህል ብቻ መፍጨርጨሩን ቀጠለ፡፡
......
እሷ ደግሞ በሥጋት እንደተዋጠች ከአሁን አሁን
“ምን ዐይነት ሁኔታ ይፈጠር ይሆን? ልጃገረድ በመሆንና ባለመሆን መካከል ያለው ልዩነት ምን ይመስል ይሆን? በማለት ቁርጧን ለማወቅ ልቧ ትር፤
ትር፤ እያለች የሚያደርገውን
እያንዳንዷን እንቅስቃሴ በንቃት ትከታተላለች፡፡

ቀስ በቀስ አካሉ ከአካሏ ጋር እየተሟሟቀ ፤እየተዋሀደ፣ እየተግባባ፤ መጣና የሷ ገላ እሾህ አመኬላውን አስወግዶ ሊያስተናግደው ዝግጁ መሆኑን ሳያውቅ፣ በሀይል ሲታገላት፤ባልጠበቀው መንገድ ተቀብሎ ያስተናግደው ጀመር፡፡
ትህትና ያንን ሁኔታ ስትመለከት ቅስሟ ስብር ብሎ፤ በሃሣብ ጭልጥ ብላ ሄዳ ሌላ ዓለም ውስጥ ገባች፡፡ ዶክተር ባይከዳኝ ደግሞ በዚያ ባጋጠመው አዲስ ሁኔታ ተደንቆ ጉድ ነው!” አለና ለጊዜው ከገባበት ስሜታዊ ረመጥ ወጥቶ እፎይታ ለማግኘት ያህል ጉልበቱን
እንደድሮው እንደአፍላ የጉርምስና ዘመኑ አድርጐ መጫወቱን ቀጠለ፡፡
በቀላሉ ሊበርድ አልቻለም፡፡ ሰፋ ያለ ጊዜ ወስዶ ተጫወተ፡፡
ይህቺ ሰው ጨው አላት መሰለኝ” እያለ በሚያደርገው ነገር ሁሉ እየተደነቀ ነበር፡፡
ነበር፡፡
እሱ እንደዚያ በደስታ ሲቃ ተውጦ ሲቦርቅ ፣እሷ ግን በድን አካሏን ከሥሩ አጋድማ ዐይኖቿ በከፈቱት ቧንቧዎች እየታጠበች
ዶክተር የልቡ ሲደርስ ቀስ በቀስ ከዚያ ከሚናጥበት የስሜት ማዕበል ወጥቶ የሆነውን ነገር እንደ አዲስ ያስበው ጀመር፡፡
በዚህ ጊዜ የሆነ የቅናት ስሜት ተለኮሰበትና ገላው በንዴት እየተቃጠለ ይጨስ ጀመር፡፡በወሲብ በኩል እርካታን ቢያገኝም፣ ልቡ በዚያው ልክ የምሬት
ደም ሲረጭ ተሰማው::
የልቡ ከደረሰ በኋላ ንጽህናዋን የወሰደው እሱ ባለመሆኑ፤የሆነ የቅናትና የዝቅተኝነት ስሜት አእምሮውን ሰርስሮት ገባ፡፡
መጀመሪያ ካገኛት ቀን ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ያደረገው ድካሙ ሁሉ ከንቱ መቅረቱን ሲያስታውሰው፤ ያንን ውብ ገላዋን ለሌላ ሰው አሳልፋ መስጠቷን ሲያሰላስለው፣ በንዴት እያረረ፣ ጨጓራው ተቀቅሎ እንደገነተረ ሥጋ ሲገነትር ተሰማው:: የተናቀ የተተፋ መሰለው፡፡
የዚያን ጊዜ የልቡን በልቡ አድርጐ.....
“ትህትና እንደዚህ የማደርገው እኮ ስለምጠብቅሽ ነው” ያላት ቀን
“ይገባኛል ዶክተር” ነበር ያለችው:: ግን ዋሸችው:: እሱ ሲጠብቃት እሷ ከዳችው።

እሱ ተንከባክቦ ያቆየውን ውድ ነገር ለሌላ አስረክባቸው መጣች:: ዶክተር ሁሉም ነገር እንደሰንሰለት ተያይዞ በሃሣቡ
መጣበት:: ደካማነቱ የራሱ ሆኖ ሳለ ራሷን አሳልፋ የሰጠችውን ልጅ ሞራሏን
ሊነካው ፈለገ፡፡የሱ ሞራል ተነክቷል፤ ቅስሙ ተሰብሯልና፤ አጥንት በሌለው ምላሱ አጥንት የሚሰብር ንግግር ሊናገራት ፈልጎ ... ጠጋ አላትና
👍2
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሀያ_ዘጠኝ


#ድርሰት_በሲሳይ_ንጉሱ

....የመከራ ቋት መሆኗ እያማረራት መፈጠሯን እስከመጥላትና ሞቷን እስከመመኘት ብትደርስም፤ ምሬቷን በልቧ አምቃ፣ መጨረሻውን እሱ የፈጠራት አምላኳ እንዲያሳምረው መፀለይዋን አላቋረጠችም፡፡
ዶክተር ባይከዳኝ እግዚአብሔር አይደለም፡፡ በፈጠራት ነፍስ ላይ
የሚወስነው አንድ እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ መቼ እንደሚወስዳት የሚያውቀው እሱ ብቻ ስለሆነ ፤ ዶክተር ባይከዳኝ እንደማትድን ገልጾ ተስፋ ቢያስቆረጣትም፤ ማን ያውቃል? ፈጣሪ በተአምር ሕይወቷን አትርፎላት፣ ሊተዛዘቡ ይበቁ ይሆናል፡፡ ይህንን ስታስብ፤ ሞቱ ተብለው ደረት የተመታላቸው፤ አበቃላቸው ተብለው ሳጥን የተዘጋጀላቸው፣
በአምላክ ረቂቅ ሥራ ህይወት ዘርተው፤ ለረጅም ዕድሜ ባለፀጋነት የበቁ እንዳሉ ሲታወሳት፣ እንኳንስ ተስፋ ያላት እናቷን፤ ከፈለገ ሬሣ የሚቀሰቅሰው አምላክ፤ በህይወት ሊያቆይላት እንደሚችል በመተማመን፤ የዶክተርን ድንፋታ እየናቀችው፤ እናቷን አሳክማ ለማዳን ትግሏን በጠንካራ መንፈስ ለመቀጠል ወሰነች፡፡

ከዚህ ከእናቷ ህመም በተጨማሪ ደግሞ በተፈጠረው ችግር ምክንያት የሷና የሻምበል ፍቅር ገና በለጋነቱ እንዳይጨናገፍ ከፍተኛ ስጋት ላይ ጥሏታል፡፡
በተለይ የዚያን ዕለት ያየችው ህልም ፍርሃት፤ ፍርሃት፣እንዲላት ዋነኛ ምክንያት ሆኖባታል፡፡
ነገ እሁድ ነው፡፡ ዕሁድ ዕለት እሷና ሻምበል ብሩክ የሚገናኙበት፣ ፍቅር የሚጨዋወቱበት፣ የወደፊት የትዳር ህይወታቸውን እየቀየሱ የሚወያዩበት፤ በአጠቃላይ ሁለቱም በናፍቆት የሚጠብቁትና በሻምበል ብሩክ ቤት በደስታ ውለው የሚያድሩበት ቀን ነው፡፡
ቅዳሜ በጠዋት ተነስታ፤ ለእናቷ አጥሚት አዘጋጅታ፧ ምሣ በሣህን ይዛ፤ ወደ ሆስፒታል ሄደች፡፡ እስከ ቀኑ ሰባት ሰዓት ድረስ ከቆየች በኋላ አንዱዓለምን እናቱ ዘንድ እንዲቆይ አደረገችና፤ ወደዚያች
ችግሯንም ሆነ ደስታዋን እኩል ወደምትካፈልላት ጓደኛዋ ወደ አዜብ
ሄደች፡፡

ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር ትናንትና መገናኘታቸውን፣ ከዚያም ቤቱ ይዟት መሄዱን፣ ከዚያም ራሷን ለመፈተሽ ያደረገችውን ሙከራ፣ ከዚያም ዶክተር ባይከዳኝ ሙልጭ አድርጐ ስድቦ ያባረራት መሆኑን አወራችላትና፤ በመጨረሻም ላይ ዐይኖቿ በእንባ ተሞልተው እናቷ መጨረሻ ደረጃ ላይ በደረሰ.... የካንሰር በሽታ መታመሟንና፤
እንደማትድን የገለፀላት መሆኑን፤ አስረዳቻት፡፡
አዜብ እቅፍ አድርጋ አጽናናቻት፡፡ አቤት እንደዛ እቅፍ አድርጋ ስታጽናናት የተሰማት ስሜት! መዋለድ ብቻውን ምን ዋጋ አለው?አንዳንዱ ተዋልዶም ተመልሶ እንደጠላት ይፈላለጋል፡፡ እንደዚህ ያለው
ጓደኝነት ግን ከመዋለድም በላይ ዋጋ ያለው ነው፡፡ መዋለድ ሳይሆን መዋደድ ነው ተብሉ የለ ወትሮውኑ? ፡፡

ዶክተር ባይከዳኝ ሀኪም እንጂ እግዚአብሔር አይደለም፡፡ ስለማሚ ህይወት የሚያውቀው አንድ እግዚአብሔር ብቻ ነው፡፡ ደግሞ ታያለሽ፤ በአጭር ጊዜ ውስጥ ድነው ከዚያ ሆስፒታል ባይወጡ አዜብ ምን አለች ትይኛለሽ ?” እሷን ለማጽናናት ስትል .
ከእግዜሩ መልዕክት ደርሶኛል ለማለት ትንሽ ነበር የቀራት። ትህትናም ትህትናም
ያለችው ይሄንኑ ነበር፡፡ ድሮውንም የእናቷን ነገር ለፈጣሪ ነበር የሰጠችው፡፡ ልቧ ተጽናና፡፡ ወደ ሌላው ዋና ርእሰ ጉዳይ ተሸጋገሩ፡፡
“የተፈጠረውን ሁሉ ፍርጥርጥ አድርጐ እውነቱን መናገር ይሻላል ወይስ ሌላ መንገድ አለው?” ስትል አዜብን አማከረቻት፡፡
“እውነቱን መናገር ባልከፋ ነበር፡፡ ምን ያህል አምኖሽ ይቀበለዋል የሚለው ነው ችግሩ። አላየሽም ዶክተር እንኳን የሆነውን? እሱስ ልጃገረድ ነኝ ስትይው ከከረምሽ በኋላ ያለመሆንሽን ሲያውቅ ምን ይሰማዋል?ስትዘል የኖረች አይልሽም?” መልሳ ጠየቀቻት፡፡ ትህትና
የዶክተር ሁኔታ መጣባት፡፡ አውሬ ነበር የሆነው፡፡ የሻምበልም ከዚህ ሊለይ እንደማይችል ገመተችና ፈራች ::
"እሱስ እውነትሽን ነው አዜቢና፤ ታዲያ ምን አባቴ ማድረግ ይሻለኛል? ጨነቀኝኮ! እንደነገርኩሽ ህልሜም ጥሩ አልነበረም፡፡ ወይኔ ብሩኬ.... የልቤን እንዴት አድርጌ ባሳየሁት?” ተከዘች፡፡
አዜብ ጉዳዩን ከብዙ አቅጣጫ ተመለከተችው፤ መረመረችው፡፡የሆነውን ሁሉ መናገር፤ ወይንም ሌላ ዘዴ መፈለግ.... በመጨረሻ ላይ የመጣላትን ዘዴ ልትነግራት ካለች በኋላ በቅድሚያ ልታሳምናት ፈለገች፡፡
“ ትሁት የእድልሽን ሳትሞክሪ ከወዲሁ ቶሎ ብሎ እጅ መስጠቱ የሚያዋጣ አልመሰለኝም፡፡ ቀድመሽ እንደዚህ ሆንኩ ብለሽ ተናግረሽ፤አልፈልግሽም ካለ እንዳይቆጭሽ ፡፡ አሪፍ ከሆንሽ በአንድ ጊዜ ልታሳኪው ትችያለሽ፡፡ ካልተሳካልሽ ደግሞ ሁለተኛውን እድል ትጠቀሚያለሽ፡፡
የተፈጠረውን ሁሉ በዝርዝር ታስረጂዋለሽ እርግጠኛ ስለሚያፈቅርሽ ችግርሽ ይገባዋል :: ስለዚህ በቅድሚያ አማራጩን ብትጠቀሚ” አለቻት፡፡ ትህትና አማራጩን ለመስማት ጓጓች፡፡
“ፔሬድሽ መጥቷል?”
“አልመጣም”
ጥያቄውን ለምን እንዳቀረበችላት ለማወቅ
ቸኩላለች፡፡
“መቼ ነው የሚመጣው?”
"እሮብ ወይም ሀሙስ ብዬ እገምታለሁ”
“በቃ እሁድ ዕለት አትሂጂ፡፡ ለእሮብ ወይም ለሀሙስ ቅጠሪው። የዚያን ዕለት አብረሽው እደሪና፤ እሪ ብለሽ አልቅሽ”
ትህትና በጥፊ እንደተመታ ሰው ክው ብላ ደነገጠች፡፡
“ውይ አዜቢና ይሄስ የማይሆን ነው” ተቃወመች፡፡
“ወደድሽም፤ ጠላሽም፤ ያለው አማራጭ እሱ ብቻ ነው ትሁት”
“እንዴት ሊሆን ይችላል? እንዳታለልኩት ካወቀ ደግሞ የባሰ ነው የሚሆነው” በትካዜ ተውጣ፡፡
“ሊያውቅ አይችልም፡፡ ስንቶቹ ናቸው እንደዚህ የሚሽውዱት ዋናው ያንቺ ቅልጥፍና ነው”
በዚህ ጉዳይ ላይ በሰፊው ከተነጋገሩ በኋላ፤ ያለው አማራጭ ይሄና ይሄ ብቻ መሆኑን አሳመነቻት፡፡
ሳምንቱን ሙሉ ከሻምበል ብሩክ ጋር ስልክ ሲደዋወሉ ነበር ያሳለፉት፡፡ ይሁን እንጂ እሷ በእውነተኛ ፍቅር ...
“ብሩኬ " ስትለው፤ እሱ ደግሞ በአንደበቱ “ሀይ ትሁት”ቢላትም፧ በልቡ “አስመሳይ!” ሲላት ነው የከረመው ::
ይሄንን አስመሳይነቷን፤ ሌብነቷን፤ ደርሶበት ቁርጡን እስከሚያውቀው ድረስ በተቻለው መጠን የድሮውን ሻምበል ብሩክን ለመምሰል ጥረት እያደረገ ነው፡፡ ልቡ ቢሻክርም፤ እንደበቱን ለማለሳለስ
እየታገለ ነው የከረመው ::
ቅዳሜ ዕለት ስልክ ደወለችለትና ከአዜብ ጋር በተመካከሩት መሠረት የእሁድ ፕሮግራማቸውን ወደ እሮብና ወደ ሀሙስ እንዲሸጋገር አሳወቀችው፡፡
“ምነው ምን ተፈጠረ ትሁት?” አላት በመገረም፡፡
“ማዘር ብሶባታል እሁድ እለት ሆስፒታል ነው የማድረው”
“ይሄኔ ከዚያ ጅል ዶክተርሽ ጋር ለማደር ነው” የሚል ስሜት ተሰማውና ቅናት ቅጥል ቢያደርገውም፤ ቻል አድርጐ
“ልምጣ እንዴ?ችግር አለ እንዴ ?” አላት ለማግደርደር ያህል፡፡
“አትድከም ብሩኬ ከቻልክ እሁድ ብቅ በል” አለችው፡፡
ሻምበል ከሶስት ቀናት በፊት ሆስፒታል
ሄዶ ጠይቋታል፡፡ አሁን ብሶባታል ብላ የምትነግረውን ዓይነት አልነበረባትም፡፡ እንዲያውም እየተሳሳቁ፤ እየተጨዋወቱ! ነው የዋሉት፡፡
እሮብ ወይም ሀሙስ ደግሞ ያልተለመደ ቀጠሮ ነው፡፡
“ይሁን እስቲ!” አለና ንዴቱን በልቡ አምቆ፡፡
“ምንም ችግር የለውም ትሁት፡፡ ዋናው የማዘር ጤንነት ነው፡፡ግን እሮብ ወይ ሀሙስ ከምትይኝ ወይ እሮብን፤ ወይ ሀሙስን፤ ለምን አልመረጥሽም? ማለቴ እንድጠብቅሽ?”
“ችግር የለውም ብሩኬ፡፡ ትክክለኛውን ቀን ደውዬ እነግርሃለሁ”
“ይሁን እንዳልሽ” በሃሣቧ የተስማማ በመምሰል አንጀቱ እያረረ እሁድ አልደርስልህ ብሎት በተስፋ ሲጠባበቅ፤ አሁን ደግሞ ይኸውና እሁድ ሲደርስ ተጨማሪ ሶስት ወይም አራት ቀን ጨምራበት ቁጭ አለች፡፡ ይህንን ሁሉ ችሎ፣ እሁድ እለት እዚያው ሆስፒታል ሄዶ፤እናቷን ጠይቆ፤ ልክ
👍2
#በፍቅር_ላይ_ሾተላይ


#ክፍል_ሰላሳ


#ድርሰት_በትክክል_ገና

....መጨረሻውን ለማየት፤ እንደድሮው በስስት ሳይሆን፤ በውስጡ የነበረውን
ጥርጣሬ ለማስወገድ፤ በተቻኮለ ስሜት ወደ አካሏ በኃይል ዘለቀ.....
በዚያን ጊዜ ከድንጋጤው ብዛት የተነሣ መብረቅ እንደመታውአው ክው ብሎ ቀረ፡፡ ውስጡ የነበረው ጥቃት ደም በስሪንጅ ተመጦ! በምትኩ በረዶ የጨመሩበትን
ያህል ደሙ ቀዝቅዞ፤ ወደ በረዶነት
አብጦ የተነረተው ስሜቱ ሙሽሽ ብሎ ሲወርድ ፤ እሷ ደግሞ እንድ ስህተት መፈጸሟን ተረድታ በነቃችበት ያበቃለት ምዕራፍ ላይ “እሪ!” ብላ ጩኸቷን ስታቀልጠው፤ አንድ ሆነ፡፡ነገሩ ጅብ ከሄደ ውሻ ጮኸ ሆኖ ነበር፡፡ ሻምበል ብሩክ በሃሣብ ጭልጥ ብሎ ከገባበት ሰመመን እሪታዋ አስደነገጠውና...
“ምን ሆነሻል?” በማለት በተሰበረ አንደበቱ ጠየቃት፡፡
“ወይኔ ብሩኬ! ጉድ አደረከኝ አይደል?!” ፍራሹ ላይ በደረቷ ድፍት ብላ አለቀሰች፡፡
ሻምበል ብሩክ እንደዚያ ሆና ሲያያት አቤት የተሰማው ስሜት!
አቤት የተቃጠለው መቃጠል!! በአንድ ጥይት ቢያስቀራት ምንኛ ልቡ በወደደ...?
“ምን አደረኩሽ?” አላት፡፡ አእምሮው ከዘመተበት ሳይመለስ ጣራ፤ ጣራውን፤ በድን ሆኖ እየተመለከተ፡፡
“ደግሞ ምን አደረኩሽ ትላለህ?” እዬዬ ብላ አለቀሰች፡፡ ያንን የአዞ እንባዋን ስታወርደው፤ ተገርሞ ፍዝዝ ብሎ እንደትንግርት ያስተውላት ጀመር.... እንደዚያ የሚወዳትና የሚያፈቅራት ልጅ ገላ አባጨጓሬ መስሎ እስከሚታየው ድረስ ኮሰኮሰችው፡፡በደረቱ የሚሳብ እባብ
ሆና ታየችው፡፡ ጠላት፡፡ ከጥላቻ ሁሉ በላይ የሆነ ጥላቻ በልቡ ነግሶ....
“ምን ነበርኩ ለማለት ነው?” አላት ንቀትና ምሬት በሚንፀባረቅበት አንደበት፡፡
“አታየውም እንዴ ያደረከኝን?” በዚህ ጊዜ ሻምበል ሣቁን መቆጣጠር አልቻልም፡፡ በሳቅ ፈነዳ!!፡፡ እሱ እንደዚያ በሣቅ ሲፈነዳ ደንግጣ፣ ........
“ምን ያስቅሃል?” አለችው፡፡
የሌባ ዐይነ ደረቅ መልሶ ልብ ያደርቅ፤ ሁኔታዋን ሲመለከተው ፤ የእስከዛሬው ፍቅር ሁሉ የውሸት መሆኑን፣ የለየላት አስመሳይ ትያትረኛ መሆኗን፣ የዚያን ዕለት እንደዚያ ከዶክተር ባይከዳኝ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዛ እየቦረቀች የገባችው፣ እኔ እኮ ልጃገረድ ነኝ እያለች ያታለለችው፡፡
ለመጀመሪያ ቀን የተገናኙ ዕለት እዚያ እነሱ መኖሪያ ቤት እጥሩ ጥግ
በአየር ላይ እየተንሳፈፈች እንደጥሩ ተዋናይ ፀጉሯን አየር ላይ እየነሰነሰች ትስመው የነበረው፤ በተለይ ለዚያን እለቱ ብለህ ነው የማርከው አይደል? ብላ ያፌዘችበት፡፡ይሄ ሁሉ ሲታሰበው፤ የማስመሰል ችሎታዋ ከከፍተኛ ልምድ የመነጨ መሆኑን ተገነዘበ ። የመጠጥ
ልምዷም ከዚሁ ጩሉሌነቷ የመነጨ መሆኑን ሲያውቅ፤ የእስከዛሬው
የዋህነቱ፣ በቀላሉ መታለሉ፤ ይሄ ሁሉ ታስቦት ጥላቻው ከልክ አለፈና ቋቅ እስከምትለው ድረስ አስጠላችው፡፡ከዚያም ከአልጋው ላይ ብድግ ብሎ፤ የምሽት ልብሱን ለባብሶ፤ የመኝታ ክፍሉን ከውጭ ቆለፈና፤ ወደ ሳሎን ሄዶ ሶፋው ላይ ጋደም አለ፡፡

ሻምበል ብሩክ እዚያ ሶፋ ላይ ተኝቶ በሃሣብ ወደኋላ ጭልጥ. ብሎ ሄዶ በዕድሏን እያሰባት እንባው ኮለል እያለ በጉንጮቹ ላይ ወረደ::
እግዚአብሔር ለምን እያሳየ እንደሚነሳው ግራ ገብቶት
“መጨረሻዬ ምን ይሆን?” በሚል ጭንቀት ተዋጠ፡፡የሰው ልጅ ውስጣዊ ገመናውና፤ውጫዊ ባህሪው ያለመጣጣሙ ሚስጥር ገረመው፡፡
ትህትና ካያት ዕለት ጀምሮ ከልቡ የወደዳት ልጅ ነበረች፡፡በኋላም ዐይኑ ጉድ እስካየበት ቀን ድረስ ሙሉ እምነት ነበረ የጣለባት፡፡
“አይ ሰው? ሰውን ለማመን እንዴት ይቻላል? እራስንም ማመን አይቻልም፡፡ ቀበሮ ለሰው ሞት አነሰው ነበር ያለችው?" ከዚህ በፊት በአንድ ግድግዳ ላይ ተጽፎ ያነበበውን ጥቅስ አስታወሰ፡፡
“ሰው እኮ......"
ይላል፡፡ የማይሞላ የክፋት ጉድጓድ ነው
ማለቱ ይሆን? ሲል አሰበ፡፡ በዚህ ስሜት ተውጦ እንቅልፍ የሚባል ነገር በዐይኑ አልዞር ብሉት እንዲችው ሲገላበጥ ነጋለት ::
ትህትና ደግሞ እዚያ መኝታ ክፍል ውስጥ ስካሯ ሁሉ ጠፍቶ በእንባ እየተንፈቀፈች የቡኮ እቃ መስላለች፡፡
“ለምን ተፈጠርኩ? ለምን እግዚአብሔር በዚህ ሁሉ ቅጣት ይቀጣኛል? ምን አደረኩት?” እያለች አምርራ እያለቀሰች፤ ስትጨነቅ፤የሆነ ሰይጣናዊ መንፈስ ተጠጋትና በጀሮዋ መጥቶ የሆነ ነገር ሹክ
አላት፡፡
ትህትና... ትህትና.... ምን እያደረግሽ ነው? ምን ትጠብቂያለሽ? ለምን ከዚህ ሁሉ ስቃይ አትገላገይም? የወዲያኛውን
የሰላም ዓለም ለምን ፈራሽው? አባትሽ የሄደበት ዓለም አይደለም እንዴ?
ይህንን የመሰለ አእምሮሽ ሊሸከም የማይችለውን ስቃይ አስወግደሽ፤
ለምን እስከወዲያኛው በእፎይታ አትተኝም? ተስፋሽ ምኑ ላይ ነው?
እናትሽ እንደማትድን ዶክተር ቁርጡን ነግሮሻል እኮ!
ሻምበልንም ይኸውና አጥተሽዋል፡፡ ለምን ወደ አባትሽ ዘንድ አትሄጅም?
ሂጅ ወደሱ...ሂጂ. ሂጂ ሂጂ . ሂጅ” አላት፡፡
ከዚያም በቀጭን ገመድ ላይ በድን አካሏ ተንጠልጥሎ በንፋሱ ሃይል ወዲያና፤ ወዲህ፤ ሲወዛወዝ ታያት ...የዚህችን አለም ጣጣ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተገላግላ እፎይ.... ስትል ታያት፡፡ ከዚያም አላፊ አግዳሚው የተንጠለጠለ በድን አካሏን ከቦ አዬ ጉድ! ሲባባልባት፤ ምነው ገና በልጅነቷ ምን አግጥሟት ይሆን እየተባለ ሲነጋገርባት ታያት፡ የፈለገው ይምጣ !! በመሞቷ ቆረጠች፡፡ ከዚህ በላይ መከራን የምትቋቋምበት አቅም ፈጽሞ የላትም አሁን ለሷ የሚያስፈልጋት
እረፍት ብቻ ነው፡፡ ቆማም ቢሆን ሞታለች፡፡የትኛው አለም ከእንግዲህ
ያጓጓታል? እናትዋ፤ ሻምበል ብሩክ፤ አባትዋ ፤ የሌሉበት ባዶ አለም?
መፍትሄው መገላገል ብቻ ነው! ስትል ደመደመች፡፡ በዚህ ውሳኔዋ መካከል ግን ሌላ ሃሰብ መጥቶ ድንቅር አለባት፡፡ ለምን ትህትና? ለምን? እናትሽ እኮ ተስፋዋ ገና አላበቃም፡፡ ሞትሽን ስትሰማ አንድ ቀን
እንደማታድር አታውቂም? ወንድምሽ አንዱአለም ገና ታዳጊ ልጅ እኮ ነው ። ለምን ለሱሰ አታስቢለትም? ካላንቺ ማን አለው? እየተሰቃየሽም የምትከፍይው የመስዋእትነት ዋጋ ስለሆነ ቻል ብታደርጊውስ ? እያለ ይሟገታት ጀመር፡፡ እናቷና የምታፈቅረው ወንድሟ መጡባት፡፡ይህ ድርጊት ሲፈጸም ምን ሊሆኑ እንደሚችሉ ታሰባት። በሞቷ ልትቀጣቸው ቀፈፋት፡፡ ሰውነቷን ውርር አደረጋት፡፡
ይሄንን ሹክ ያላትን እርኩስ መንፈስ ሸሸችው፡፡ ፈራች፡፡
“ምነው ከአዜብ ጋር እንደዚህ ያለውን ምክር ባልተማከርኩ ኖሮ? ምነው እውነቱን በነገርኩት ኖሮ? ” እያለች ስትፀፀት፤ ስታለቅስ መንጋቱ አይቀርምና ለሁለቱም ያ ሌሊት በስቃይ ነጋላቸው፡፡
ሻምበል በማለዳ ተነሣና ልብሱን ለባብሶ፤ የመኝታ ቤቱን በር ከፍቶ፤ ቀስ ብሎ ገባ፡፡ በእንባ ምክንያት ተበላሽቶ ያደረው ፊቷን
ሲመለከት ከልቡ አዘነላት፡፡ ቀስ ብሉ ሄዶ ኣልጋው ጫፍ ላይ ተቀመጠና...
“ግን ለምን እንደዚህ ትሁት ?” አላት ልቡ አሁንም በሃዘን እንደተነካ፡፡
እንደዚያ ቅስሙ ስብር ብሎ ስትመለከተው አልቻለችም፡፡ እንጀቷ ተላወሰና፧ ሄዳ እላዩ ላይ ተጠምጥማ፤ እንደ አዲስ ጧ! ብላ ትንሰቀሰቅ ጀመር፡፡ ሻምበል በረጅሙ ተንፍሶ፤ አተኩሮ አያት፡፡ አለቃቀሷ በብሶት የታፈነና ሳግ የተቀላቀለበት ነበረ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ሻምበል ብሩክ በሁኔታዋ እጅግ አዝኖላት ነበር፡፡ ከዚያም በኋላ ብድግ አለችና
እያለቀሰች የሆነውን ሁሉ ትነግረው ጀመር፡፡ የምትነግረውን ታሪክ
አዳምጦ ካበቃ በሁዋላ፡፡
“ተይው በቃ ትሁት! ቁርጡን ለማወቅ እንጂ የሆነውን ሁሉ በዐይኔ በብረቱ አይቼዋለሁ፡፡ ተይው አትጨነቂ” አላት፡፡
ምን እንዳየ ገርሟት እስከሚነግራት ድረስ አይን አይኑን እያየች በጉጉት ጠበቀችው፡፡